ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ። ‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3 https://youtu.be/csxxAMGtC4I ለመቀላቀል http://t.me/ortodoxtewahedo
#በከንቱ_አምተናታል
ዮሴፍ በጽኑ መረበሽ የተያዘበት ወቅት ነበር። የእመቤታችን መፀነስ ከሚያወቀው ተፈጥሯዊ አካሔድ ውጪ ስለሆነበት ልቡ ክፉኛ ተሸብሮ ነበር። በእርግጥ ዮሴፍ በእመቤታችን መፀነስ መደናገጡ ብዙም ላያስደንቅ ይችላል። መካን ሆነው ሳለ በልመናቸው ብርታት የወለዱ አሉ÷ እንደነ ሣራ በስተርጅናቸው የፀነሱም አሉ። የእርሷ ግን የተለየ ነው በድንግልና የወለደ ከእርሷ በፊትም ይሁን ከእርሷም በኋላ አልተገኘም።
መጻሕፍት እንደሚነግሩን ዮሴፍ ግን ከመደነቅ ይልቅ ከንግድ ሲመለስ ያገኘው ፈላስፋው ዮሐንስ "ይህቺ ሴት ካንተ ነው የፀነሰችው" ብሎ የተናገረው ቃል ከድንጋጤ አድርሶታል። በዚህም ምክንያት ነበር "መኑ ቀረጸ አክናፈ ድንግልናኪ" ብሎ የመፀነሷን ነገር የጠየቃት። ንጽሕት የሆነች እርሷ ግን "መልአኩ አክብሮ ከነገረኝ ውጪ ሌላ ምንም የማውቀው የለም አለችው" የእመቤታችን ትሕትና መግለጽ የሚቻለው አንደበት የለም ቃሏና ምላሿ ሁሉ በትሕትና የታሹ ናቸው።
ዮሴፍ አሁንም ቢሆን ከጥርጣሬው መዳን አልቻልም አንድ አንድ ጊዜ ፍርሐት እና የሰዎችን ወቀሳ ማስታወስ ወደ ጥርጣሬ አሮንቃ ውስጥ ይከተናል አረጋዊው ዮሴፍም የሆነው እንዲሁ ነው። ይህንን ጥርጣሬውን ልታስወግድለት የወደደች እመቤታችን ግን አአዕዋፍ እንዲራቡ የሚያደርግ አአዕዋም እንዲያፈሩ የሚያደርግ ማን ምስሎሃል? ብላ ከግሰጸችው በኋላ ከደጃቸው የቆመ ደረቅ ግንድ ነበር እርሱን አለምልማ አሳየችው። መልአኩ ትፀንሺያለሽ ብሎ ባበሠራት ወቅት ይህ እንዴት ይሆንልኛል ብትለው "ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም" ብሎ የመለሰላትና እርሷ በተግባር አሳየችው። በተረቱበት መርታት ልማድ ነው።
እመቤታን ያለውንድ ዘር በድንግልና የመጸነሷ ነገር ምትሐት ሳይሆን የእግዚአብሔር ሥራ መሆኑን ብትገልጥለትም። ለቆጠራ ወቅት ግን ይዟት ይወጣ ዘንድ ፈራ። ከእግዚአብሔር ሥራ ይልቅ ፍርሐታችንን እናምነዋለን በዚህም በተሳሳተ እምነታችን የእግዚአብሔር ዓላማ አደናቃፊዎች ሆነን እንገኛለን። ዮሴፍም ያለ ወንድ ዘር እንድትጸንስ ያደረገውን የእግዚአብሔርን ሐይል ሳያስተውል ይዟት ሲወጣ ግን አይሁዶች ሊፈጥሩት የሚችሉት ትንኮሳ አስፈራው።
ይዟት ቢወጣ ሕጋቸውን ቢያስቀራት ደግሞ ያደረገውን ዓውቆ ጥሏት ወጣ እንዳይሉ ወሪያቸውን ፈርቶ ሳለ መልአኩ ከያዘው ፍርሐት አርቆ ይዟት ይወጣ ዘንድ አዘዘው። ዮሴፍ በመልአኩ ትዕዛዝ ይዟት ቢወጣም የዲያቢሎስ የግብር ልጆች የሚሆኑ በትጠጣው ለሞት የሚያደርሳትን ማየ ዘለፋን ትጠጣልን አሉ። የአምላክ እናት እርሷ ግን ማየ ዘለፋን ከጠጣችው በኋላ እነርሱ እንዳሰቡት ሳይሆን ከወትሮው አበራች ጽድልት ሆና ታየች ከፀሐይ ይልቅ አብርታ ተገኘች በጊዜ የተቀሩት አይሁድም ይህን ቢመለከቱ "ይህችን ብላቴና በከንቱ አምተናታል" አሉ።
የእመቤታችንን ክብር ከመናገር እርቀው በከንቱ የሚያሙ ሰዎች የበቀሉት ገና በማኅጸን ሳለች ነው። መወለዷን የጠሉ ዳግመኛ የመውለዷን ነገር አለወደድዱምና በጊዜው ነውር እንደተገኘባቸው ሴቶች እርሷን በከንቱ አሟት። እውነት ደቆ ሐስት ረቆ ባየለበት በእኛ ዘመንም ዓይነ ልቦናቸው የታወረባቸው በከንቱ ያማሉ። የእግዚአብሔርን ሳይሆን የግብር አባታቸውን የዲያቢሎስን ድምፅ እየሰሙ በቅዱሳኑ ላይ በከንቱ ይናገራሉ። ከሁሉ ልቆ የታየው ግን የአይሁድ ከንቱ የሆነው ሐሜታቸው ሳይሆን ስለ ክፉ ፈንታ ክፉ ያለመለሰች የእመቤታችን ትሕትና ነበር።
ዲ/ን ሞገስ አብርሃም
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
✝የዘመኑ ምንኩስና ሕይወት ከቀደሙት ጋር ሲነጻጸር✝
Size:-76.8MB
Length:-1:22:58
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ዋናው መሠረታዊ እውነት ይህ ነው፡- እውነተኛ ለውጥና ትንሳኤ የሚመጣው ቤተክርስቲያንን በመክስና በግላዊ የክለሳ አካሄድ ሳይሆን፣ በታማኝ አገልግሎትና የጋራ ሸክምን በመሸከም ነው።
፮. ሸክሙን መሸከም ወይስ ጣትን መቀሰር?
ቤተ ክርስቲያን ዛሬ የምትፈልገው ተጨማሪ ከሳሾችንና በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚተቹትን አይደለም፤ የምትፈልገው የሃቢብ ጊዮርጊስን ዓይነት መንፈስ የተላበሱ ልጆችን ነው። ችግሩን ከማራገብ ይልቅ የመፍትሔው አካል የሚሆኑትን፤ የቤተ ክርስቲያንን ሸክም በትከሻቸው ተሸክመው የክርስቶስን ሕግ የሚፈጽሙትን።
ስለዚህ፣ እያንዳንዱ የበሰለ ኦርቶዶክሳዊ አማኝ ራሱን ሊጠይቅ ይገባል፡- እኔ የቤተ ክርስቲያንን ሸክም አግዤ እየተሸከምኩ ነው? ወይስ በቁስሏ ላይ ጣቴን እየቀሰርኩ፣ የውግዘት ድንጋይ እየወረወርኩ ነው?
የዛሬው ጥሪ፣ ልክ እንደ ሃቢብ ጊዮርጊስ፣ ኃላፊነትን መውሰድ ነው። ይህ ደግሞ በፍቅር፣ በዲሲፕሊን፣ በትሕትናና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስና እርሱ አካሉ በሆነችው ቤተ ክርስቲያኑ ላይ ባለ ጽኑ እምነት የሚከናወን የተቀደሰ ተግባር ነው።
©አቦርሃም ሲሳይ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#ሰኔ_21_እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ለሕንጸተ ቤተ ክርስቲያን ዘእግዝእትነ ማርያም እና ሰኔ ጐልጐታ እንኳን አደረሰን! የእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነቷ ረድኤቷ በረከቷ ጥበቃዋ አይለየን እመ ብዙኃን የብዙኃን እናት ድንግል ማርያም ሆይ ሳይነግሩሽ የሰውን ችግር ጭንቀት የምታውቂ እሩህሩህ እናት ነሽና የጎደለንን ሙይልን በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት ያለው አማላጅነትሽ ፍፁም ረድኤትሽ አይለየን፤ የቃል ኪዳን ሀገርሽን ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያን በምልጃሽ አስቢያት! አሜን፡፡
''በዕንቊ ሰንፔር ትትሐነጽ ወበመረግድ
ሃሌ ሉያ ለአብ ሐጹር የዓውዳ ትበርህ እምከዋክብት
ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ
ጽዮን ቅድስት ቤተ ክርስትያን ደብተራ ፍጽምት''
ዚቅ ዘቅዱስ ያሬድ
እንኳን ለእናታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
✝እግዚአብሔር በሚያደርገው በጎ ነገር ሚካኤል ይታዘዛል✝
Size 51.2MB
Length 55:18
በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
"ቅዱስ ሚካኤል ኾይ"
እንደ ፀሐይ ሥነ ጸዳል የሚያንጸባርቁ በሰማይ ላይ ለሚንበለበሉ አክናፎችኽ ሰላም እላለኹ
የእግዚአብሔር ልዩ መልእክተኛ ሚካኤል ኾይ ከላይ ከሰማይ ተመልክተኽ በምትመጣበት ጊዜ ኹሉ በሲዖል የሚኖሩ ግዞተኞች ሚካኤል ኾይ መጣኽልን ደረስክልን እያሉ ደስታቸውን ይገልጻሉ።"
#መልክአ ቅዱስ ሚካኤል
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
"ቅዱስ ሚካኤል ኾይ"
እንደ ፀሐይ ሥነ ጸዳል የሚያንጸባርቁ በሰማይ ላይ ለሚንበለበሉ አክናፎችኽ ሰላም እላለኹ
የእግዚአብሔር ልዩ መልእክተኛ ሚካኤል ኾይ ከላይ ከሰማይ ተመልክተኽ በምትመጣበት ጊዜ ኹሉ በሲዖል የሚኖሩ ግዞተኞች ሚካኤል ኾይ መጣኽልን ደረስክልን እያሉ ደስታቸውን ይገልጻሉ።"
#መልክአ ቅዱስ ሚካኤል
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
✝እግዚአብሔር በሚያደርገው በጎ ነገር ሚካኤል ይታዘዛል✝
Size 51.2MB
Length 55:18
በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
♦አቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ ተመሰረተ !
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት
የሕግ አገልግሎት መምሪያው ከሕግ ባለሙያዎች ዐቢይ
ኮሚቴ ጋር በመሆን አቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ መሰረተ።
የቤተክርስቲያናችን ሕግ አገልግሎት መምሪያ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ባቀረበው ክስ የወንጀል ምርመራ ተደርጎ የምርመራ መዝገቡ መብቱ ለሚፈቅድለት የዐ/ሕግ ዘርፍ እንዲተላለፍለፍ ጠይቋል።
በወንጀል ተጠርጣሪ /ተከሳሽ - አቶ ትዝታው ሳሙኤል
ተጠርጣሪ /ተከሳሹ ነዋሪነቱን በውጪ ሃገር በማድረግ የቤተክርስቲያኒቱ የበላይ ውሳኔ ሰጪ አካልን ለማዋረድ፣
ለመስደብ እና የምዕመኑን ስሜት ለመንካት ብሎም በሀገሪቱ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እንዲነሳ በማሰብ በተለያዩ የመረጃ ማሰራጫ መንገዶች እና ከ5000 በላይ ተከታዮች ባሉት የራሱ የዪቲዩብ ቻናል በመጠቀም ከፍተኛ ቅስቀሳ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።
በማያያዝም ግለሰቡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዓን አባቶችን፣ በየገዳማቱ ውስጥ የሚገኙ ገዳማውያን መነኮሳትና አገልጋዮችን <<ግብረ ሰዶማውያን ናቸው>> በማለት፣እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን <<የመተት እና ጠንቋይ ቤት ናት >>በማለት፣ሲቀሰቅስ የቆየ መሆኑን የገለጸው መምሪያው ግለሰቡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የምትገለገልባቸውን ሃይማኖታዊ የፀሎት፣የታሪክ ፣የገድላትና ድርሳናት መጻሕፍትን <<ድውያን መጽሐፍት ናቸው መጥፋት አለባቸው>>ማለቱን ገልጿል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቅድስናየምታ
ከብራቸውንና የምትዘክራቸውን ቅዱሳን አባቶች እና እናቶችን << ጣኦታትና ጣኦት አምላኪ>> ናቸው በማለት ግለሰቡ የፈጸመውን የወንጀል አድራጎት በመጥቀስም ክስ መስርቶበታል።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!
እንኳን ለቅድስት ሥላሴ በዓል እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን።
የአብርሐምን ቤት የባረኩ ሥላሴ እኛንም በህይወታችን በኑሮዋጭን በአገልግሎታችን በትዳርአችን በትምርታችን በሥራችን ይባርኩን ።
ሥሉስ ቅዱስ ለሚታምን ሁሉ እምነትን በረከትን ሀገራችን ኢትዮጽያን ሰላም ያድርጉልን አሜን ::
#መልካም እለተ ይሁንልን
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈
ለመቀላቀል ➟ @weludebirhane
ለአስተያየት ➟ @weludebirhane_bot
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼.
ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ በቤተ ክርስቲያን ደን ልማት ላደረጉት አስተዋጽኦ ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሽልማት ተበረከተላቸው።
Mk tv ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም
ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ የአመልድ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር በደን ልማት ላደረጉት አስተዋጽኦ ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሽልማት ተበረከተላቸው።
ሰኔ 4/2017 ዓ/ም በድርጅቱ ዋና መሥሪያ ቤት በተከናወነው የዕውቅናው መርሐ ግብር ላይ የምስጋና ወረቀትም ዶክተሩ የሚመሩት አመልድ ኢትዮጵያ ለአበረከተው አስተጽኦ ከቤተ-ክርስቲያን ደን ፕሮጀክት ተጠቃሚዎች ተበርክቶለታል።
ሽልማቱ የሰጡት በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በደራ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኙ የስድስት አብያተ ክርስቲያናት እና የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ተወካዮች ናቸው።
የአብያተ ክርስቲያናቱ ተወካዮች እንደገለጹት በዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ የሚመራው አመልድ ኢትዮጵያ በአካባቢያችን ለሚገኙ ጥንታዊ ገዳማት እና አድባራት ተፈጥሮአዊ ደኖቻቸው እና ይዞታቸወ እንዲጠበቅ፣ ኅብረተሰቡን በማስተባበር አጥራቸው እንዲታጠር እና በአካባቢው ለሚገኙ ድሃ ማኅበረሰቦች የኑሮ ማሻሻያ ድጎማ በማድረግ ያደረገውን ተግባራት አውስተው ተወካዮቹ ምሥጋና አቀርበዋል፡፡
የአመልድ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ዓለማየሁ ዋሴ (ፒ.ኤች.ዲ) እንደተናገሩት ለመጀመሪያ ጊዜ ከፕሮጀክት ተጠቃሚዎች መካከል ምስጋና ያቀረቡ መሆናቸውን አውስተው፣ በቀጣይ የቤተ-ክርስቲያን ደንን መሠረት ያደረገ የመልክዐ- ምድር መልሶ ማልማት ፕሮጀክት ሥራ በሌሎች ቦታዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እና በአካባቢው የተሠራው ሥራ ዉጤታማ መሆኑን አድንቀዋል፡፡
ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ በቤተክርስቲያን የደንና ብዝኃ ሕይወት ዙሪያ የተለያዩ ጥናቶችን ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በማካሄድ ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ግንዛቤ መፍጠር የቻሉ ሲሆን እመጓ፣ መርበብት እና ዝጎራ በተባሉት መጽሐፎቻቸውም አንቱታን ያተረፉ መሆናቸው ይነገርላቸዋል።
©የዘገባው ምንጭ አመልድ ኢትዮጵያ ነው።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
🙋♂አንድጥያቄ
✞በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው ሰውን መግደል የጀመረው በማን ነበር ⁉️✟
#ወንድማችንን ፍቱት
ሊቀ ትጉኅን ደረጀ ነጋሽ (ዘወይንዬ) ዛሬ ከግል ቢሮአቸዉ ወጥተዉ ወደ ተሽከርካሪያቸዉ ሲያመሩ ለጥያቄ እንፈልግዎታለን ተብለዉ ደህንነት ነን ባሉ አካላት መወሰዳቸዉን ከቤተሰቦቻቸዉና ከሥራ ባልደረቦቻቸው ከሰማን ቀናት አለፊ ።
ይሁን እንጂ መምህር ደረጀ ነጋሽ እስከ አሁን ያሉበትን ፖሊስ ጣቢያ ለማወቅ አልታቻለም።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ሃቢብ ጊዮርጊስ ግን ቤተ ክርስቲያንን አልከሰሰም፤ ሸክሟን ተሸከመ እንጂ።
፩. የዘመኑ ታሪካዊ ቀውስና የቤተ ክርስቲያን ፈተና
በዐሥራ ዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃና በሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን መባቻ ላይ፣ የግብጽ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ እጅግ ውስብስብ ከሆኑት ፈተናዎች እያስተናገደች ነበር። ቀውሱ የውጭ ጫና ብቻ ሳይሆን፣ ከውስጥ የመነጨና የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕልውና የሚፈታተን ነበር። ይህ ድክመት በአስተዳደር መላሸቅ፣ በመልካም አስተዳደር እጦት፣ በሙስናና በአንዳንድ አገልጋዮች የሥነ ምግባር ውድቀት ተገልጧል። ከዚህም በላይ፣ የትምህርተ ሃይማኖት ዕውቀት በእጅጉ ተዳክሞ፣ የመንፈሳዊ አገልግሎት ጥራትና ስፋት በእጅጉ ቀንሶ ነበር።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ፣ የዚያን ዘመን አሳሳቢ ገጽታ ሲመሰክሩ እንዲህ በማለት ሁኔታውን ያጠቃልሉታል፡-
“በሃያኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ፣ ስብከቶች ደረቅና ሕይወት አልባ ነበሩ፤ መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች ከሞላ ጎደል አልነበሩም፤ ድንቁርና በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ፣ እንዲያውም በቀሳውስቱ መካከል እንኳ ሰፍኖ ነበር።”
ይህ ምስክርነት እንደሚያሳየው፣ ችግሩ የገጸ-ድካም ጉዳይ አልነበረም። ይልቁንም፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሐዋርያዊ ተልዕኮና የአደረጃጀት መሠረት ያናጋ፣ ብዙዎችን ተስፋ ሊያስቆርጥና ለዓመፅ ወይም ለመለያየት ሊዳርግ የሚችል ጥልቅ መንፈሳዊና መዋቅራዊ ቀውስ ነበር። እንዲህ ባለ ከባድ ወቅት፣ የአንድ አማኝ ቤተ ክርስቲያናዊ ንቃተ ህሊና (ecclesiological consciousness) እና ታማኝነት በእጅጉ ይፈተናል።
፪. የዲያቆን ሃቢብ ጊዮርጊስ መነሣትና የመስዋዕትነት መንገድ
በዚህ መንፈሳዊ ጨለማ ውስጥ ነበር ሃቢብ ጊዮርጊስ የተባለው የብርሃን ሰው የተነሳው። እርሱ በቤተ ክርስቲያን ያደገና ዲያቆን እንደመሆኑ፣ የችግሮቹን ስፋትና ጥልቀት ከውስጥ ሆኖ ተመልክቷል። የቤተ ክርስቲያኒቱን የአስተዳደር ድክመት፣ የአገልጋዮቿን የዕውቀት ማነስና የሕዝቡን መንፈሳዊ ጥማት ተገንዝቧል። ነገር ግን፣ እንደ ብዙዎቹ፣ ጣቱን ለመቀሰር፣ ለማሳጣትና ለማጣጣል፣ የውግዘት ድምፅን ለማሰማት ወይንም በራሱ አካሄድ የቤተክርስቲያኒቷን አካሄድ ልከልስ ማለትን አልመረጠም። ይልቁንም፣ በታማኝ አገልግሎትና ሸክምን በመሸከም ለችግሩ ተግባራዊ ምላሽ ሰጠ። መንገዱ የክስ ሳይሆን የመስዋዕትነት ነበር፤ ይህም በገላትያ 6፡2 ላይ ያለውን “የአንዱን ሸክም አንዱ ይሸከም፣ እንዲሁም የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ” የሚለውን ሐዋርያዊ ትዕዛዝ ሕያው ምስክርነት ነው።
ገና ከወጣትነቱ ጀምሮ ለትምህርት በነበረው ጥልቅ ፍቅር፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀጣይ ትውልድ የማነጽ ኃላፊነት በራሱ ላይ ጫነ። የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ንቅናቄ በመላ ሀገሪቱ በማደራጀት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕፃናትና ወጣቶች የኦርቶዶክሳዊት እምነታቸውን እንዲያውቁና እንዲኖሩባት መሠረት ጣለ። በካይሮ ሥነ-መለኮታዊ ኮሌጅ ውስጥ በአካዳሚክ ዲንነትና በመምህርነት ሲያገለግል፣ ዕውቀትና መንፈሳዊነት የተዋሐደላቸውን አገልጋዮች አፈራ። ድርጊቱ ሁሉ ይመነጭ የነበረው፣ ቤተ ክርስቲያንን በአስተዳደራዊ ድክመቶቿ ውስጥ እያየ እንኳ፣ የማይነቀንቅ የክርስቶስ አካልና የድኅነት ታቦት መሆኗን ካመነበት ጥልቅ ሥነ-መለኮታዊ እምነት ነበር።
ለዚህም ነው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ፣ የአንድን ሰው ታማኝ አገልግሎት ፍሬያማነት ሲመሰክሩ፣ እንዲህ ያሉት፡-
“የሰንበት ትምህርት ቤት ንቅናቄ ከሃቢብ ጊዮርጊስ በቀር ሌላ ፍሬ ባያፈራ ኖሮ እንኳ፣ እርሱ ብቻ በቂ ነበር።”
፫. የመዋቅር ድክመትን ከሃይማኖት ስህተት መለየት
የሃቢብ ጊዮርጊስ ጥበብና ሥነ-መለኮታዊ ልሕቀት ከሁሉ በላይ የሚገለጠው፣ በዘመኑ የነበረውን የመዋቅር ድክመት ከቤተ ክርስቲያን ንጽሕተ ሃይማኖት ጋር ባለማደባለቁ ነው። ቤተ ክርስቲያን በትምህርተ መለኮቷ ኑፋቄን ታስተምራለች ብሎ አንድም ቀን አልከሰሰም። ሥርዓቷን አላጣጣለም፤ ቀኖናዎቿንና ይትባሕሎቿን "ካልከለስኩ" አላለም። ችግሩ ያለው በሐዋርያት በኩል በተሰጠችው የቀናች እምነት ላይ ሳይሆን፣ ያችን እምነት በሚያገለግሉና በሚያስተዳድሩ ሰዎች ላይ በሚታየው ድካም እንደሆነ በሚገባ ተረድቶ ነበር።
ይህ መረዳት፣ ቤተ ክርስቲያን መለኮታዊ-ሰብዓዊ (Theanthropic) ተቋም መሆኗን ከመቀበል ይመነጫል።
እርሷ፣ እንደ ክርስቶስ አካል፣ በመለኮታዊ ተፈጥሮዋ ቅድስት፣ ፍጽምትና ከስህተት የጸዳች ናት፤ ነገር ግን በውስጧ የሚያገለግሉት ሰዎች የሰብዓዊ ድካም ተገዢዎች ናቸው። ቅዱሳን አባቶች ይህንን ልዩነት በሚገባ አስተምረዋል። ለምሳሌ፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የክህነትን ቅድስናና የአገልጋዩን ግላዊ ድካም ሲለይ፣ የክህነቱ ኃይል የሚመነጨው ከሰውየው ማንነት ሳይሆን ከክርስቶስ ሹመት መሆኑን ያስረዳል። ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያም ንስጥሮስን የታገለው፣ የአንጾኪያን ቤተ ክርስቲያን መዋቅር ለመናድ ሳይሆን የተሳሳተውን የሃይማኖት ትምህርት ለማረም ነበር።
ስለሆነም፣ የሃቢብ ጊዮርጊስ መፍትሔ ከቤተ ክርስቲያን ውጭ አዲስ ሥርዓት መመሥረት ሳይሆን፣ በውስጧ በመሆን፣ በትሕትናና በመታዘዝ፣ ያንን ሰብዓዊ ድካም መፈወስና ማነጽ ነበር። ሥራው ሁሉ የሚያሳየው ይህንን ነው፡- በገዛ አረዳዱ "የተበላሸውን" ብሎ የገመተውን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ለማረም አልሞከረም፤ ይልቁንም ያንን ያልተበረዘ ትምህርት ለተራበው ሕዝብ ለማድረስ ራሱን አሳልፎ ሰጠ።
፬. ትምህርቱ ለዛሬው ትውልድ፡- የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ተዛምዶ
ይህ የታሪክ ትምህርት በዘመናችን ላለችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥልቅና አስቸኳይ መልእክት አለው። ዛሬ በርካታ ምእመናን በአስተዳደራዊ ብልሽቶች፣ በመንፈሳዊ አመራር ድክመትና በአንዳንድ አገልጋዮች ሥነ ምግባር ጉድለት የተነሣ በብስጭትና በቅሬታ ተሞልተዋል። ይህ ስሜት መነሻው ቅን ሊሆን ይችላል።
ችግሩ ያለው ለዚህ ስሜት በሚሰጠው ምላሽ ላይ ነው። ብዙዎች፣ ልክ በሃቢብ ጊዮርጊስ ዘመን እንደነበሩት ተቺዎች፣ መላዋን ቤተ ክርስቲያንን ይወቅሳሉ፤ ሐዋርያዊ ትውፊቷን ይጠራጠራሉ፤ አልፎ ተርፎም በግል አስተያየታቸውና ፍልስፍናቸው ያንን ትውፊት ለመተካት ይዳዳሉ። ከዚህም የከፋው፣ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ትይዩ መዋቅሮችንና ርዕዮተ ዓለሞችን ለመገንባት መሞከር ነው፤ ይህም አንድነቷንና ሐዋርያዊ ሥርዓቷን በእጅጉ ይጎዳል። ይህ አካሄድ፣ የቅዱስ ኢግናጥዮስ ዘአንጾኪያ "ከኤጲስ ቆጶሱ ውጭ ምንም ነገር አታድርጉ" የሚለውን ሐዋርያዊ መመሪያ የሚጻረር ነው።
፭. ኦርቶዶክሳዊው የማነጽ መንገድ፡-
ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ቤተ ክርስቲያንን የምትረዳበትና የማነጽ አካሄዷ ግልጽ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌሶን 4፡11–13 ላይ፣ ክርስቶስ ራሱ ለቤተ ክርስቲያኑ "ሐዋርያትንና ነቢያትን፣ ወንጌላውያንንም፣ እረኞችንና አስተማሪዎችንም" የሰጠው፣ "ቅዱሳን … ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ፣ ለክርስቶስም አካል ሕንጻ" እንደሆነ ያስረዳል። መዋቅርና ሥርዓት የተሰጠው ለማነጽ እንጂ ለመበታተን አይደለም።
የማረምና የማነጽ ሥራ እንዴት መከናወን እንዳለበትም መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስቀምጣል። በይሁዳ መልእክት 1፡22 ላይ "አንዳንዶችንም በምትለዩበት ጊዜ፣ ምሕረት አድርጉላቸው፤ ሌሎችን ግን ከእሳት እየነጠቃችሁ በፍርሃት አድኗቸው" ይላል። ይህ ቃል፣ ችግሮችን የምንቀርብበት መንገድ በጥበብና በልዩነት መሆን እንዳለበት ያስተምራል እንጂ ሁሉን በአንድ ላይ የመውቀስ አካሄድን አይደግፍም።
++ሐራሩኤል ጭርዋቅ++
ጥበብን የለበሳት ጠቢብ ሰሎሞን ለራሱ ሐራሩኤል ጭርዋቅ የሚል ስመ አምላክ የሰፈረበት ቀለበት ነበረው። ትእምርተ መንግሥቱ ግርማ ሞገሱ እሱ ነው ከሴት ሲደርስ አንበሳ መደብ ሲወጣ ቀለበቱን አውልቆ ከዙፋኑ ላይ ያኖረው ነበር። በአንድ ወቅት አንበሳ መደብ ደርሱ ሲመጣ ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ቀለበቱን ከዙፋኑ ማንሳት ባይቻለው ከነዙፋኑ ጠቅሎ ባሕር ላይ ጣለው ሰሎሞን ሲመለስ ዙፋን ቤቱ ከለከለው የንግሥናውን ምልክት ግርማ ሞገሱን አጥቷልና ጎስቋላ ሆነ። ከዚህ በኋላ በገዛ ከተማው ሁለት ሳምንት ለምኗል ሰይጣን የሰው ልቡና አጽንቶበት የሚሰጠው አጥቶ ከመሠግራነ ዓሳ ሄዶ ስመ እግዚአብሔር ጠራባቸው ከመሀከላቸው አንዱም ይህ ዘብዛባ ብሎ የሞተ አሳ ጣለለት ሆድ እቃውን አውጥቶ ለመመገብ ቢቀደው ቀለበቱን አገኘ ቀለበቱን እንዳገኘ ግርማ ሞገሱ ከነክብሩ ተመለሰለት። በሰይጣን የተነጠቀው መንግሥቱ ተመለሰ ብዙዎቹም ሰሎሞን መሆነን ሲያውቁ ንጉሥን ከዚህ ምን አመጣው ብለው ከበቡት ቡሀላም መርበበተ ሰሎሞን የሚባል ስመ አምላክ አትሞ ቀብሮታል።ሰሎሞንን እዚህ ያደረሰው ምንድነው ቢሉ ከዕለታት በአንዳቸው የተራበ ሰው ስመ እግዚአብሔር እየጠራ ሲለምነው ይህ ሰው ምን ሆኗል አለ ተርቦ ነው ቢሉት ረኀብ ምንድነው ብሎ ነበርና የረኀብን ጽናት ሊያሳየው ይህ ተፈጸመበት።>>{ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ}
👇👇👇👇👇
የሰሎሞን መንግሥት እና ንግሥና በቀለበት ምክንያት እንደተመለስ በአዳም የሄድ አንድም ያጣነው ልጅነት እንደ ቃልህ ይደረግልኝ በሚለው የእምነት ቃሏ በእርሷ ተመልሱልናልና መርበብት ሰሎሞን ተብሎ የታተመበት ሐሩራኤል ጭርዋቅ የሚል ስመ አምላክ የተጻፈባት የሰሎሞን ቀለበት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት እንላለን።
የሰው ልጅ በጥንት መርገም ተይዞ በነበረበት ዘመን በንጽህናና በቅድስና አጊጣ በምክረ ከይሲ በአዳም ስህተት ያጣነውን ልጅነት ያገኘንባት ለእርሷ ለሰው እንዲረዳ መሰልንላት አንጂ ከሰሎሞን ቀለበት በብዙ ትልቃለች።
በረከቷ ምልጃዋና ጸሎቷ አይለየን
ዲ/ን ሞገስ አብረሃም
ሰኔ 23 የንጉሥ ዳዊት ልጅ ጠቢቡ ሰለሞን ያረፈበት ቀን ነው ::
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
✝ደስታ ምንድንው?✝
Size:-66.5MB
Length:-1:11:51
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
"ኦ ሚካኤል ኦ መተንብል፣ ካህነ አርያም ትሰመይ ቢጸ ሱራፌል፣ ዘእምርዑሳን ርዑስ ወዘእምልዑላን ልዑል፣ ጊዜ ጸዋዕኩከ ቅረበኒ በምሕረት ወሣህል፡፡"
"አማላጃችን ሚካኤል ሆይ ፈጥኖ ደራሻችን ሚካኤል ሆይ የጌታን ዙፋን ከሚያጥኑ ሱራፌል ካህናት አንዱ ሰማያዊ ካህን አንተ ነህ እኮን። የሰማያውያን ሊቃነ መላእክት ሁሉ አንተ አለቃቸው ነህ እኮን። ይልቁንም የልዑላንም ልዑል አንተ ነህና በጠራሁህ ጊዜ ሁሉ በይቅርታና በቸርነት ድረስልኝ አትራቀኝ።"
(መልክአ ሚካኤል)
በዓለ ቅዱስ ሚካኤል
እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል በዓል አደረሳችሁ!
ሚካኤል ማለት ‹‹መኑ ከመ አምላክ (እግዚአብሔር)፤ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው›› ማለት ነው፡፡ ይህም የእግዚአብሔርን ገናንነትና እርሱን የሚመስል አምላክ እንደሌለ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ፣ ርኀሩኅ፣ ኃያልና ረቂቅ ማንም እንደሌለ የሚያመለክት ነው፡፡
ቅዱስ ሚካኤል ሌሎች መጠሪያዎች አሉት፤ እነዚህም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠውን የባለሟልነት ክብር የሚገልጹ ናቸው፡፡ እነርሱም ‹‹መልአከ ኃይል፣ መጋቤ ብሉይ፣ መልአከ ምክሩ፣…›› ናቸው፡፡ መልአከ ኃይል የተባለው እግዚአብሔር በእርሱ አማካይነት ታላላቅ ሥራዎችን በመሥራት ኃይሉን ስለገለጸና ዲያብሎስን ከነሠራዊቱ ስላሸነፈ ነው፡፡
መጋቤ ብሉይ የተባለበት ምክንያት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእግዚአብሔር እየተላከ ብዙ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራ በመሆኑ ነው፡፡ መልአከ ምክር ወይም የእግዚአብሔር የምክሩ አበጋዝ የተባለበት ምክንያት እግዚአብሔርን በምክሩ ይረዳዋል ለማለት ሳይሆን እግዚአብሔር የሚሠራውን ሥራ ለወዳጁ ለቅዱስ ሚካኤል ይገልጽለታልና በእርሱ አማካኝነት ይሠራል ለማለት ነው፡፡
ቅዱስ ሚካኤል በዚህ ሁሉ ልዕልና ላይ ትሕትናን ደርቦ የያዘ፣ በጸሎቱ ተማጽኖና በተራዳኢነት አምኖ ለሚለምነው ሁሉ ፈጥኖ በመድረስ ከሠራዊተ አጋንንት ተንኰል የሚያድን መልአክ እንደሆነ በቅዱስ መጽሐፍ ተጠቅሶ እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ ሙሴንና እስራኤልን በሲና በረሃ (ዘፀ.፳፫÷፳-፳፪)፤ (ዘፀ.፲፬÷፲፭-፳) ኢያሱን በኢያሪኮ (ኢያ.፭÷፲፫-፲፭)፤ ከአሞራውያንም እጅ ሕዝቅያስን እንደረዳቸው ተጽፏል፡፡ (ኢሳ.፴፯÷፴፮) በትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ ፲ ቁጥር ፲፫ ላይ ‹‹የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሃያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ እነሆም ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ›› በማለት የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት ተገልጿል፡፡ በዚሁ የመጽሐፍ ክፍል ምዕራፍ ፲፪ ቁጥር ፩ ላይ ‹‹በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል›› በማለት ታላቅነቱን፣ ለሰው ልጆች ሁሉ በአማላጅነቱና በተራዳኢነት የሚቆም እንደሆነ በማያሻማ ቃል ተገልጿል፡፡
በአጠቃላይ በኦሪት የእግዚአብሔር መልአክ እየተባለ የሚጠራው አብዛኛውን ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያስተምራሉ፤ በድርሳነ ሚካኤልም ተጽፎ ይገኛል፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ያልረዳው ቅዱስ የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ በዘመነ ሰመዕታትም ሰማዕታትን በተጋድሎ ያጸናቸው ይህ ሩኅሩኅ መላክ እንደሆነ በእነ ቅዱስ ፋሲለደስ እንዲሁም በእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገድላት ላይ በሰፊው ተገልጿል፡፡
የቤተ ክርስቲያን አባቶች በየወሩ በ፲፪ ቀን መታሰቢያውን እንድናደርግ አዘውናል፡፡ ይህንንም ያልቻለ በዓመት አራት ዓበይት በዓላትን ከቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ጀምሮ እንደተቻለ ማዝከር ይገባል፡፡ እነዚህም ኅዳር ፲፪ ቀን ቀጥሎ ሰኔ ፲፪ ቀን ከዚያም ነሐሴ ፲፪ ቀንና ታኅሣሥ ፲፪ ቀን ናቸው፡፡
ሰኔ ፲፪፡- በቅዳሴያችን ‹‹ተውህቦ ምሕረት ለሚካኤል፤ ለሚካኤል ምሕረት (ይቅርታ ርኀራኄ) ተሰጠው እንላለን፤ ነቢዩ ሄኖክም ምሕረት ለሚካኤል መሰጠቱን ገልጿል፤ ትሕትናውን ታዛዥነቱን አስረድቷል፡፡ (ሄኖ.፮÷፭፣፲÷፲፪)
የሰማያውያን ሠራዊት አለቃ፣ ለሰው ሁሉ የሚራራና ስለ ሰው ልጆች ሳያቋርጥ ወደ ፈጣሪው የሚለምን፣ ርኀሩኀና ትሑት የሆነው ኃያሉ ቅዱስ ሚካኤል ባሕራንን ከሞት ያዳነበት፣ የሞቱን ደብዳቤ ወደ ሕይወት የቀየረበት የመታሰቢያው ዕለት ነው፡፡
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
❖ ሰኔ ፲፪ ❖
✞ ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት [በነገዱ ውስጥ፥ በመላእክት ሁሉ ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት..፣ በእስክንድርያ ከተማ ቅዳሴ ቤቱ የከበረበት..፣ የሞት መልእክት የተጻፈባትን የቅዱስ ባሕራንን ደብዳቤ የለወጠበት..፣ ቅድስት አፎምያን ያዳነበት..፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ምሕረትን የሚለምንበት..በእለኚህ ምክንያት ነው በዓሉን የምናከብረው] ✞
"ሰላም ለሚካኤል መሐሪ ውእቱ፤ ወተአዛዚ ለሰብእ በዲበ ሠናይቱ፤ ለቀርነ ዝንቱ መልአክ በድምፀ ንፍሐቱ፤ በከመ ኮነ ቀዳሚ ውስተ ሰማያት ዕርገቱ፤ ለእግዚአብሔር ይከውን ዳግመ ምጽአቱ።"
@ortodoxtewahedo
#ደጉ እና ሩሩህ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል አመታዊ በዓል እንኳን አደረሳቹ።
"ቅዱስ ሚካኤል ኾይ"
እንደ ፀሐይ ሥነ ጸዳል የሚያንጸባርቁ በሰማይ ላይ ለሚንበለበሉ አክናፎችኽ ሰላም እላለኹ
፣
የእግዚአብሔር ልዩ መልእክተኛ ሚካኤል ኾይ ከላይ ከሰማይ ተመልክተኽ በምትመጣበት ጊዜ ኹሉ በሲዖል የሚኖሩ ግዞተኞች ሚካኤል ኾይ መጣኽልን ደረስክልን እያሉ ደስታቸውን ይገልጻሉ።"
#መልክአ ቅዱስ ሚካኤል
" የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።"
#መዝሙረ ዳዊት 34:7፤)
"በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤ ሕዝብም ከሆነ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል፤ በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል። "
#ትንቢተ ዳንኤል 12:1
" የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሀያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤ እኔም ከፋርስ ነገሥታት ጋር በዚያ ተውሁት። "
#ትንቢተ ዳንኤል 10:13
" ነገር ግን በእውነት ጽሑፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም።
"
#ትንቢተ ዳንኤል 10:21፤)ዐ
"የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር። ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም።"
#የይሁዳ መልእክት 1:9፤
"ቅዱስ ሚካኤል ኾይ
እንደ ፀሐይ ሥነ ጸዳል የሚያንጸባርቁ በሰማይ ላይ ለሚንበለበሉ አክናፎችኽ ሰላም እላለኹ
የእግዚአብሔር ልዩ መልእክተኛ ሚካኤል ኾይ ከላይ ከሰማይ ተመልክተኽ በምትመጣበት ጊዜ ኹሉ በሲዖል የሚኖሩ ግዞተኞች ሚካኤል ኾይ መጣኽልን ደረስክልን እያሉ ደስታቸውን ይገልጻሉ።"
#መልክአ ቅዱስ ሚካኤል.
✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
✝ያሉበትን ቤት ሁሉ ሞላው✝
በዓለ መንፈስ ቅዱስ
Size:-28MB
Length:-1:20:27
በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#ሰንበተ ክርስትያን
እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች።
ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት
(ራዕይ 1፥10)
ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት።
መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት መታሸጉን ተከትሎ አባላቱ ቅሬታቸውን ገለጹ !
ሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም [ተሚማ/ አዲስ አበባ]
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአርሲ ሀገረ ስብከት ካሉት ቀደምት እና አንጋፋ ሰንበት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነው የአሰላ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት በደብሩ ሰበካ ጉባኤ አማካይነት መታሸጉን የሚዲያችን የመረጃ ምንጮች ለሚዲያ ክፍላችን መረጃውን አድርሰውናል። ይህንንም ተከትሎ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላት ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
በሚያዝያ 08/2017 ዓ.ም በሰበካ ጉባኤ በቁጥር አካ/ደመ/መዓ/ቤክ/ሰጉ/0320/17 በተጻፈ ደብዳቤ የሰ/ት/ቤቱን ሊቀመንበርና የሕጻናት ክፍል መምህር ዲ/ን አበበ ይልማን ከሥራና ከሰ/ት/ቤቱ ሰብሳቢነት ማገዳቸውን በመግለጹ ሰንበት ት/ቤቱ በቀን ምልዓተ ጉባኤ አድርጎ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሊቀ መንበር የታገደበትን ውሳኔ ጠቅሶ ለሰበካ ጉባኤው በደብዳቤ ለወረዳው ቤተክህነት እና ለወረዳው ሰ/ት/ቤት አንድነት አስገብቶ አፋጣኝ ምላሽ ባለማግኘቱ በድጋሚ ለወረዳ ቤተ ክህነቱ በቀን 16/08/2017 ዓ.ም የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቶ ፤ የወረዳው ቤተክህነት ጉዳዩን ተመልክቶ ሊቀ መንበሩ አለአግባብ መታገዱንና የሰ/ት/ቤቱን መብት የነካ ተግባር መሆኑን ጠቅሶ ለሰበካ ጉባኤው በቁጥር 97/2017 በቀን 17/08/2017 ዓ.ም እገዳው እንዲነሳ ደብዳቤ መጻፉን ለሚዲያችን አስረድተዋል።
ሆኖም ግን ሰበካ ጉባኤው ተፈጻሚ የወረዳ ቤተ ክህነቱን ትዕዛዝ ባለመቀበሉ በ25/09/2017 ለብፁዕ አቡነ ያሬድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ኃላፊና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባል ጠቅሰው ያስገቡት ደብዳቤ ምላሽ ሳይሰጣቸው ሰንበት ትምህርት ቤቱ በግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ታሽጎ አገልግሎት መስጠት ማቆሙን ሚዲያችን ለማወቅ የቻለ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከሀገረ ስብከቱ የተላኩ ልዑካን በተገኙበት የታሸገው የሰንበት ት/ቤት ሂሳብ ነክ እና አባላት ቁጥርን ከያዘው ሳጥን ባሻገር ሌላው የታሸጉት ተከፍተው ሰ/ት/ቤቱ ወደ አገልግሎት እንዲመለስ የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ደብዳቤ ጽፎ ቢልክም ሰበካ ጉባኤው የታሸገውን ለመክፈት ፈቃደኛ ሳይሆን መቅረቱን ለመረዳት ችለናል
ይህንን አስመልክቶ የሚዲያ ተቋማችን የካቴድራሉን አስተዳዳሪ አባ ፍቅረ ሥላሴን በተደጋጋሚ ደውሎ ለማነጋገር ቢሞክርም ሐሳባቸውን በስልክ ለማጋራት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሐሳባቸውን ማካተት ያልቻልን ሲሆን ፤ በተጨማሪም የወረዳው ሊቀ ካህናት እና የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ታምራት ወልዴን ለማግኘት ያደግረነው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
መ/ር አክሊል
ብርቱ አርቶዶክሳዊ ወጣት ቤተ ክርስትያን ብዙ አክሊልዎች ያስፈልጓታል በርታልን ወንድማችን ።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo