ortodoxtewahedo | Unsorted

Telegram-канал ortodoxtewahedo - ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

64069

ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ። ‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3 https://youtu.be/csxxAMGtC4I ለመቀላቀል http://t.me/ortodoxtewahedo

Subscribe to a channel

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

📖ቅጠል ረግፎ ቅጠል እንደሚተካው ሁሉ ሰው ወድቆ ሰውን ያኖራል።

📖እኛም ይሄው ነን ይህ ነው ታሪክና ሂደታችን ኑሮና ይህ ህይወታችንን እየወደቁ ያኖሩን እየሞቱ ያተረፉን ኗሪዎች ነን

📖ያንዳችን ሞት ላንዳችን ህይወት ነው በዚህ መንገድ ነው እየተተካካን የተጓዝነው

📖በዚህ ሂደት ነው ሰው ለመሆን የተንገዳገድነው እየሞቱ ያኖሩን እየወደቁ ያተረፉን የህይወት ቀብድ የተከፈለብን ኗሪዎች ነን

📖ያንዳችን ሞት የሌላችን ህይወት ነውና የተከፈለልንን ዋጋ ላለማባከን

📖 በእምነት በእውነትና በፅናት በመኖር ህሊናችንን እናሳርፈው።

📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

http://t.me/ortodoxtewahedo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰

🕹 #ጊዜ_አጠቃቀም

👍 #የጊዜ_አጠቃቀም_ጥቅሞች

🔸የጊዜ አጠቃቀም ጥቅሞች እንደየሰው ቁጥራቸው ሊጨምርና ሊያንስ ይችላል፡፡ እዚህም ጋር የሚከተሉት ሦስት ዋና ዋና ጥቅሞች ቀርበዋል፡፡

1⃣ በሌሎች ዘንድ የሚኖረን ተቀባይነት ከፍ ይላል


🔹አገልጋዮች ከፍተኛ የሆነ ማኅበራዊ ቁርኝት የሚጠበቅብን በመሆኑ የጊዜ አጠቃቀሙን መጀመርና መልመድ በምናደርገው ግንኙነት የሚጠበቅብንን በጊዜው እንድናከናውን ይረዳናል፡፡

🔸በዚህም በሰዎች ዘንድ የተግባር ሰው፣ ቃል አክባሪ፣ ትጉህ፣ ወዘተ የእኛ መገለጫዎች ይሆናሉ፡፡

🔹እነዚህ እሴቶች ደግሞ በመንፈሳዊውም ሆና ዓለማዊው እንቅስቃሴያችን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጉልናል፡፡

2⃣ የተመጣጠነ ሕይወት እንድንመራ ያስችለናል

🔸የጊዜ አጠቃቀምም በመንፈሳዊ፣ አእምሮአዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ጤናዊ አቋማችን የተመጣጠነ እንዲሆን ይረዳናል፡፡

3⃣ ውጤታማነታችን ያሳድጋል

🔹ውጤታማነት ሲለካ ሥራው መሠራቱ ብቻ ሳይሆን የሚታየው ሥራው የፈጀውም ጊዜ አንዱ መለኪያ በመሆኑ ግንዛቤ ውስጥ ይገባል፡፡

🔸ጊዜያችን በአግባቡ የምንጠቀም ከሆነ በሁሉም ረገድ በትንሽ ጊዜ ብዙ ሥራዎችን በማከናወን ውጤታማ መሆን እንችላለን፡፡

#ማጠቃለያ

❇️ጊዜ ሀብት ነው፤ እንዲሁም ጊዜ ለእያንዳንዳችን እኩል የተሰጠን ሀብት ነው፤ በመሆኑም እያንዳንዳችን አጠቃቀሙን ተረድተን ይህን ሀብታችንን ለውጤታማነት ልናውለው ይገባል፡፡

❇️ምንም እንኳ ጊዜ ሀብት ቢሆንም አጠቃቀሙን ካላወቅንበት፣ ሀብትነቱን ካልተረዳን ምንም ዋጋ አይኖረውም፡፡

👌ይህም ማለት ጊዜ ካወቅንበት እና ከሠራንበት የሚጠቅመን ሲሆን ካላወቅንበት ግን ምንም ጥቅም የለውም፡፡

❇️ጊዜ ለሁላችን እኩል የታደለ ሀብት ቢሆንም ጠቀሜታው ግን ለሁላችን እኩል አይደለም፡፡

👌ምክንያቱም የጊዜን ሀብትነት ተረድተው በአግባቡ የተጠቀሙበት ውጤት ሲያገኙበት ይህንን ያልተረዱ ግን ተጠቃሚ አይሆኑም፡፡

❇️ጊዜ ለእያንዳንዷ እንቅስቃሴአችን አስፈላጊ እና ጠቃሚ ሀብት በመሆኑ ትኩረትን ይሻል፡፡

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን

📌ምንጭ
↪️ @Tewahedo12 Channel

⏰⏰⏰
⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰

🙏 ሼር ማድረግ አይርሱ 🙏

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን

📩Coment- @YeBiruk
- @Samiabush

@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የወርቅ መሠላል✝
  
           
Size:-132.4MB
Length:-2:23:00

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

📓#አንድጥያቄ
✟ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለአብርሃም ድንኳን ለኖህ መርከብ ለያዕቆብ መሰላል ለአዳም ምኑ ናት? ✟

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

"ጾመ ሀዋርያት(የሰኔ ጾም)"

ይህ ፆም ሐዋርያት ለማገልገል ከመሰማራታቸው በፊት አገልግሎታቸው የቀና እንዲሆን ለመንፈስ ቅዱስ ስራ መለየትን እግዚአብሔር እንዲሰጣቸው በመለመን የፆሙት ፆም ነው ::

ሐዋ 13:1-3

መሰረታችን ሐዋርያት ናቸውና የዋኖቻችንን ሥራ እኛም መፈጸም ስላለብን እንጾመዋለን፡፡
ሐዋርያትን እንዳፀናቸው በአገልግሎቱም እንዳበረታቸውና እንደለያቸው ሁሉ እኛም እንዲያፀናን እንዲያበረታን በመማፀን ለመልካሙ ሥራ እንተጋ ዘንድ በመለመን እፆመዋለን ከጵራቅሊጦስ ማግስት ጀምሮ ሐምሌ 5 በመፆም ይፈጸማል።

እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን የበረከት ጾም ይሁንልን

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

መ/ር ልደተቃል

ብርቱ አርቶዶክሳዊ ወጣት ቤተ ክርስትያን ብዙ ልደተዎች ያስፈልጓታል በርታልን ወንድማችን ።

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

🔴 መድኃኔአለም 🔴
✍️✍️✍️
መድኃኔአለም ማለት አለምን ያዳነ የአለም መድኃኒት ማለት ነው። ሰው በመበደሉ ምክንያት ከክብር ተዋርዶ ይኖር ነበር።ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የተዋረደውን ሰው እርሱ በመስቀል ተሰቅሎ ወደ ቀድሞ ክብሩ መለሰው። ምን አይነት ፍቅርነው?????
ወንድሜ /እህቴ አስባችሁታል ግን እኛን ለማዳን ብሎእኮ ነው

የተሰቀለው፡ራቁቱን በመስቀል ምን ያህል
አሳፋሪ እንደሆነ እናውቀዋለን
ጌታ ግን እኛን ለማዳን ብሎ መስቀሉን ናቀው።
በፈጠራቸው ፍጥረት ተተፋበት።
እኛን ትእግስት ሊያስተምረን እነርሱን ማጥፋት
እየቻለ እርሱ ግን

💖በፍቅር እያዩ የማያውቁትን አያውቁምና
አባት ሆይ ይቅር በላቸው ይል ነበር።
ክርስቶስ እኛን ለማዳን ሲሰድበት
አልተሳደበም ሲንቁት አልናቃቸውም
ሲታበዩበት ሁሉ እርስ ግን በትህትና ያያቸው ነበር።

💖ታዲያ እኛ ደግሞ እራሳችንን ለማዳን ሰዎች ሲንቁን ሲሰድቡን ሲታበዩን በፍቅር በዝምታ ማለፍ ይጠበቅብናል።
ይህን ካደረግን የክርስቶስ ደቀ መዝሙር እንባላለን።
በ 5 ችንካር ነበር የቸነከሩት።

በመስቀል የተገኙ ድንግል ማርያም ሐዋርያው ዮሐንስ ነበሩ። አንተም በመስቀሉ ስር
ለመገኘት ከፈለግህ ትእግስትን ፍቅርን ትሕትናን ገንዘብ አድርግ።

መድኃኔአለም በቸርነቱ ይቅር ይበለን።

#27 ❤️

"ወዳጄ ሆይ ሮማውያን ወታደሮች ጎንጉነው በጌታችን እራስ ላይ እሾህ እዳቀዳጁት ባሰብህ ጊዜ እጅግ ማዘንህ አይቀርም ። ሆኖም አንተም እሾህ የተባለውን አንድ ኃጢአት በሰራህ ቁጥር በጌታችን ላይ የተደፉትን እሾኾች ቁጥር እንደጨመርህ አስብ ።በፈጣሪ የማያምኑት ሮማውያን ወታደሮች ከጎነጎኑት እሾኽ በላይ የጌታችንን እራስ የበለጠ ዘልቆ የሚወጋው ደሙን አፍስሶ ያዳነን እኛ ክርስቲያኖች በኃጢአታችን የምንጎነጉነው የእሾኽ አክሊል ነው ።{ስለመተላለፋችን የቆሰለው አምላክ በመተላለፋችንም ይቆስላል ።!}

{በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን ከሚለው ርዕስ የተወሰደ )

[ ሕማማት]
{በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ}

መድኃኔዓለም ሆይ አባት ሆይ ይቅር በላቸው በማለት በታላቅ ቃል በመስቀል ላይ ፥ ለተናገረ ቃልህ ሰላም እላለሁ በመስቀል ላይም በሰቀሉህ ጊዜና ጎንህን በጦር በወጉ ጊዜ አንዳችም የተቃውሞ ትንፋሽ ላልተነፈሰ እስትንፋስህም ሰላም እላለሁ ።
መድኃኔዓለም ሆይ ጻድቃንን ያይደለ ኃጥአንን ለማዳን በራሱ ደም ራሱ ለተጥለቀለቀ ስነ መልክህ ሰላም እላለሁ !

( መልክአ - መድኃኔአለም )27❤

@ortodoxtewahedo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

☞ግንቦት 26 እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የልደት በዓላቸው
በሰላም አደረሳችሁ፡፡
☞አባታቸው ፍሬ ቡሩክ እናታቸው ዮስቴና የሚባሉ በሕገ እግዚአብሔር፡
በሃይማኖት በምግባር ጸንተው የሚኖሩ ደጋግ ክርስቲያኖች የገኙ አባት ናቸው፡፡
☞አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ፅንሰታቸው ነሐሴ 26፤ ውልደታቸው ግንቦት
26፤ ዕረፍታቸው ኅዳር 26 ነው፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖት አቡነ ሀብተማርያምን አምስት መቅሰፍታት እንዲጠፋ
በደጄ በደብረ ሊባኖስ ተቀበርልኝ ብለው የለመኗቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ይህ
እንዴት ነው ቢሉ
☞አቡነ ተክለሃይማኖት እኔ ከተቀበርኩበት ቦታ እድትቀበር ቃልኪዳን ግባልኝ
ብለው ጠየቋቸው፡፡
☞አቡነ ሀብተማርያምም አባቴ ሆይ ይህንን አደርግ ዘንድ ሰለምን ትወዳለህ?
አላቸወ፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖትም በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስት መቅስፍቶች አሉና
ሰለዚህ ነው እነዚህም አንዱ መብረቅ ሁለተኛው ቸነፈር ነው ሦስተኛው ረሀብ
ነው፤ አራተኛው ወረርሽኝ ነው አምስተኛው የእሳት ቃጠሎ ነው፡፡ የአንተ አጽም
በውስጡ የተቀበረ እንደሆነ ከነዚህ መቅስፍታት ትድናለች አሏቸው፡፡
☞አቡነ ሀብተ ማርያም ንዑድ ክቡድ የምትሆን አባቴ ሆይ ልዩ ክብር በሚሆን
በአንተ አጽም መቀበር ያልዳነች በእኔ አጽም መቀበር ድኅነትን ታገኛለችን?
ብለው ተከራከሩ በዚህም ጊዜ አቡነ ተክለሃይማኖት መልሰው
☞አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሔር የተሰጠህ እኔ የማውቀው
ክብር አለህና ሰለዚህ ነው፡፡ ይልቅስ እንዳልኩህ በተቀበርኩበት ቦታ እንድቀበር
ቃልኪን ግባልኝ ብለው ማለዷቸው፡፡
☞ይህንንም ሲባባሉ እንዲህ የሚል ቃል መጣላቸው ከወዳጄ ከሀብተ ማርያም
እንደበት ይህ ቃል አይወጣም፤ ዳግመኛም ወዳጄ ተክለሃይማኖት ሆይ እርሱ
በወደደው የሚቀበር አይደለምንና እኔ ከተቀበሩኩበት እንድትቀበር ብለህ
የምታስገድደው ለምንድ ነው?
☞እኔ በወደድሁት ቦታ ይቀበራል እንጂ የሚል ቃል ተነገረ፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖትንም እየለመኑና እየሰገዱከሥላሴ ዙፋን ተንበረከኩ፡፡
☞በሦስተኛውም ይሁን እንዳልከው ይቀበርልህ የሚል ቃል ተሰማ፡፡
☞ዳግመኛ በአንተም አጽም በሀብተ ማርያምም አጽም ቦታህ ከመቅሰፍት
ትድናለህ ልጆችህ ግን በቸነፈር ደዌ ቢሞቱ ከሰማዕትነት ተቆጥሮላቸው ወደ
መንግሥት ሰማያት እንዲገቡ በራሴ ምዬ ቃልኪን ገብቼለሃለሁ አላቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አቡነ ተክለሃይማኖት እጅግ ደስ ተሰኙ፡፡

(ገድለ አቡነ ሀብተማርያም)

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

" የአባቶቻችን ትምህርት እናስተምራለን ፤ ተስፋቸውንም ተስፋ እናደርጋለን ፤ የተማርናት ፤ ተስፋ የምናደርጋት ሃይማኖት ይህች ናት:: እንኖርባታለን ፤ እንሞትባታለን ፤ በእግዚአብሔር ፍቃድ እንነሣባታለን "

ሃይማኖተ አበው
እንቁ መምህራችን የሆኑት እዮብ ይመኑ ትምህርቶች ለማግኘት ከታች ናለድ ሊንክ ይግቡ❤️


የይቱብ ቻናላችን ሰብስክራይብ ያድርጉ
      👇👇👇
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

💍ከጋብቻ በፊት ሩካቤ (sex) መፈጸም ምን ችግር አለው⁉️

💁‍♂ከትዳር በፊት መሳም (ከንፈር ወዳጅ /kiss) ይቻላልን⁉️

👨‍🦱🧑‍🦳ፍቅረኛሞቹ እጅግ በጣም ስለሚውዋደዱ (ሩካቤ/sex) ቢፈጽሙ ምን ችግር አለው⁉️

⛪️በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ከተዋደዱ በኋላ ስሜታቸው ይገደባል⁉️

🤵‍♂የስሜት መግለጫዎች መፈጸም ይቻላል⁉️

በነዚህ ትምህርቶች ዙሪያ እየተማርን እንገኛለን
እርሶም እውቀቱ እዲኖርዎ ከፈለጉ ይህን ማስፈንጠሪያ Link ጠቅ ያድርጉት
                👇👇👇
     @EOTC_-OPEN_channel
     @EOTC_-OPEN_channel
     @EOTC_-OPEN_channel
     @EOTC_-OPEN_channel



        
                     🔔
          🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺‌‌
          ♦️በይቱብ♦️
                    👇🏽👇🏽
🧏መናፍቃን ከሚያነሷቸው ጥያቄዎች⁉️
የጌታችን እናት የአዳም የውርስ ኃጢአት/ጥንተ አብሶ/አለባት⁉️
የጌታችን እናት አልተነሳችም⁉️
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=K22Xvwmx3Xo89L8k
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=K22Xvwmx3Xo89L8k
         👆👆👆
👉ለነዚህ ጥያቄዎች እና ለመሳሰሉት በቂምልሽ ተሰቶበታ ይቱብላይ ታገኙታላቹ።

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

❖ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የዕርገት በዓል በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ።

#ዕርገት

ቤተክርስትያናችን ከምታከብራቸው በዓላት ውስጥ አንዱ የጌታችን የመድኃኒታችን የእየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ነው።ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ በ፵ኛው ቀን ማረጉን በማሰብ ቤተክርስትያናችን ዕርገትን ትንሳኤን በተከበረ በ፵ኛው ቀን ዕርገትን ታከብራለች።በዚህ ዓመትም ቤተክርስትያነችን ዕርገትን ግንቦት21 ታከብረዋለች።
ዕርገት ልክ እንደ ትንሳኤ ሁሉ ቀኑ ይለዋወጣል። ነገር ግን ምንጊዜም ዕርገት ሐሙስን አይለቅም።ልክ ትንሳኤ እሁድን ስቅለት አርብን እደማይለቅ ሁሉ እርገትም ሐሙስን አይለቅም።

ዐረገ በስብሐት

ዐረገ በስብሐት ዐረገ በእልልታ
በስብሐት በእልልታ ዐረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
ሞትን ደል አድርጎ የሰራዊት ጌታ
አረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
እየዘመሩለት መልአክት በደስታ
አረገ በስብሐት በእልልታ

❖ መልካም በዓል #ምሽት/ቀን ይሁንልን።


#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

እመቤታችን በደብረ ምጥማቅ በምትባል ቦታ ወርቅ ወንበር ላይ ተቀምጣ ለአምስት ቀን የታየችበት ነው።

ይህም በዓል ከ33ቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ሲሆን በዚህ ቀን ግብጽ ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቦታ በተሰራች ቤተክርስቲያን እመቤታችን ጻድቃንን መልአክትን አስከትላ ትገለጽላቸው ነበር።

እስላምም ክርስቲያንም በግልጽ ይመለከቷት ነበር። ከየአገሩ ያሉ ሰዎች ይሰበሰባሉ ድንኳን ተክለው ሰቀላ ሰርተው አጎበር ጥለው ይከትማሉ ፤ድንግልም ከግንቦት 21 ቀን ጀምሮ ለአምስት ተ...ከታታይ ቀናት ሳታቋርጥ ትገለጽላቸው ነበር።

ህዝቡ የተለያየ ጥያቄ ይጠይቃታል አዳም አባታችንን አሳይን ይሏታል ግማሹ ነብዩ ዳዊትን ግማሹ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሳይን ይሏታል አንዳንዱም ከዚህ ቀደም የሞተ ዘመዱን እንድታሳየው ይጠይቃታል፤እርሷም ለሁሉም ፍቃዳቸውን ትፈጽምላቸው ነበር።

አዳምን ስትጠራው ከሔዋን ጋር ዳዊትን ስትጠራው ከበገናው ጋር ቅዱስ ጊዮርጊስን ስትጠራው ከጸአዳ ፈረሱ ጋር ነው።የእመቤታችን ረድአት እና በርከቱ በሁላችን ላይ ይድርብን አሜን 🙏

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

👉 ትዝታው ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ እና ከቤተክርስቲያን ጋር ባለው ግንኙነት ዙሪያ የተነሱት ስጋቶች፣ በተለይም የሕግ ክፍል ሚና ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ነው።

የቤተክርስቲያን የሕግ ክፍል ሚና እና ተጠያቂነት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሕግ ክፍል፣ ልክ እንደማንኛውም ተቋም የሕግ ክፍል፣ የቤተክርስቲያኗን ሕጋዊ መብቶችና ጥቅሞች የማስጠበቅ ኃላፊነት አለበት። ይህ የሚያጠቃልለው፡-
የቤተክርስቲያኗን ስም መጠበቅ: ማንኛውም የቤተክርስቲያኗን መልካም ስም የሚጎዳ፣ የሚያጠለሽ ወይም ውሸት የሚያሰራጭ አካል ላይ ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ።
ንብረት ጥበቃ: የቤተክርስቲያኗን ንብረቶች (ሕንፃዎች፣ መሬቶች፣ ቅርሶች፣ ገንዘብ ወዘተ) ከሕገ-ወጥ ወረራ፣ ብዝበዛ ወይም ጉዳት መጠበቅ።
የአስተምህሮ ጥበቃ: የቤተክርስቲያኗን አስተምህሮ የሚጻረሩ ወይም ምእመናንን የሚያደናግሩ ድርጊቶችን ሕጋዊ በሆነ መንገድ መከላከል (ይህ ግን የሃይማኖት ነጻነትን የማያደናቅፍ መሆን አለበት)።
ውሎች እና ስምምነቶች: ቤተክርስቲያን የምትገባባቸውን ማንኛውንም ውሎች እና ስምምነቶች ሕጋዊ ገጽታ ማረጋገጥ።
የውስጥ ክርክሮች: በቤተክርስቲያኗ አባላት ወይም አካላት መካከል የሚፈጠሩ የሕግ ጉዳዮችን መፍታት።
"ቤተክህነቱ የሕግ ክፍል ነፍስ አለው?" የሚለው ጥያቄ
ይህ ጥያቄ ቤተክርስቲያን እንደ ተቋም ለሚያጋጥሟት ችግሮች ምላሽ የመስጠት ፍጥነት እና ብቃት ላይ ያነጣጠረ ነው። "ነፍስ አለው?" ሲባል፣ የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍል ንቁ፣ ብቁ እና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅም አለው ወይ? የሚል ጥያቄን ይዞ ይመጣል።
ተቋማዊ ሕይወት: ማንኛውም ተቋም (እንደ ቤተክርስቲያን) የራሱ ሕግና ሥርዓት ያለው አካል ሲሆን፣ የሕግ ክፍሉም ይህንን ሥርዓት በሕይወት ለማቆየትና ለማንቀሳቀስ ቁልፍ ሚና አለው። ስለዚህ በንድፈ ሀሳብ ደረጃ "ነፍስ" ወይም "ሕይወት" አለው ሊባል ይችላል።
ተግባራዊ ችግሮች: ሆኖም በተግባር ግን እንደ ማንኛውም ትልቅ ድርጅት፣ የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍልም ቢሮክራሲ፣ የሀብት እጥረት፣ የሰው ኃይል ውስንነት ወይም የውሳኔ አሰጣጥ መዘግየቶች ሊያጋጥሙት ይችላሉ። እነዚህ ችግሮች "ነፍስ የለሽ ሬሳ" አስመስለው ሊያቀርቡት ይችላሉ።
ትዝታው እና የቤተክርስቲያን መልካም ስም ጉዳይ
ትዝታው በኢትዮጵያ ውስጥ በቤተክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ሲያቀርባቸው የነበሩ አስተያየቶች በብዙዎች ዘንድ አነጋጋሪ እንደሆኑ ይታወቃል። የቤተክርስቲያኗን መልካም ስም አጠፋተዋል የሚል ቅሬታ ካለ፣ የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍል ይህንን ቅሬታ መርምሮ በሕግ አግባብ ክስ መመስረት የሚችልበትን ሁኔታ ማየት አለበት።
ማስረጃ ማሰባሰብ: "ብዙ ማስረጃ አለ" ተብሎ እንደተጠቀሰው፣ የሕግ ክፍሉ መጀመሪያ እነዚህን ማስረጃዎች በጥንቃቄ ማሰባሰብ፣ ማደራጀት እና ሕጋዊ ክብደት እንዳላቸው ማረጋገጥ አለበት።
የክሱ ዓይነት: ክሱ የስም ማጥፋት (defamation)፣ የሐሰት ወሬ ማሰራጨት ወይም ቤተክርስቲያኗን የሚያጎድፍ ሌላ ሕገ-ወጥ ድርጊት ሊሆን ይችላል።
የፍጻሜ አደራረስ: "ሬሳ የሕግ ክፍል ክስ ቢከስም ለፍጻሜ አያደርስም!" የሚለው አስተያየት የሕግ ክፍሉን አቅም መፈተሽ ነው። ክሱ ለፍጻሜ ለመድረስ ጠንካራ የሕግ መሠረት፣ በቂ ማስረጃ፣ ብቁ የሕግ ባለሙያዎች እና የቤተክርስቲያኗ ከፍተኛ አመራሮች የፖለቲካ ፍቃደኝነትና ድጋፍ ያስፈልገዋል። ያለዚህ ድጋፍ፣ ሕጋዊ ሂደቶች ቀርፋፋ ሊሆኑ ወይም ሙሉ በሙሉ ሊዳክሙ ይችላሉ።

የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍል በሕግ ፊት ስልጣን ያለው አካል ሲሆን፣ የቤተክርስቲያኗን መብቶች ማስጠበቅ የሕግ ግዴታው ነው። ትዝታው በቤተክርስቲያኗ ላይ ጉዳት አድርሷል ተብሎ ከታመነ፣ የሕግ ክፍሉ ያሉትን ማስረጃዎች ተመልክቶ ሕጋዊ እርምጃ የመውሰድ ሥልጣን አለው። ሆኖም የሕግ ሂደቶች ውስብስብ እና ጊዜ የሚጠይቁ በመሆናቸው፣ ውጤታማ ለመሆን ጠንካራ የሕግ አቅም እና ተቋማዊ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ቤተክርስቲያኗ ምን አይነት እርምጃ ትወስዳለች ብለው ያስባሉ?
  
           
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

#ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማታረጅ #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትታደስ #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትጠፋ
#ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትለወጥ
#ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትሻሻል


📖በክርስቶስ ደም የተመሰረተች እውነተኛ ዘላለማዊ ሕይወት ናት ከድንግል ማርያም ፍቅር ከተዋህዶ ማዕድ አይለየን

📖አሜን ተዋህዶ ለዘላለም ትኑር
በዚህ ወቡ በሆነች ሐይማኖት እስከዘላለም ያፅናን።

#አሜን
#አሜን
#አሜን

#share #share #share

📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ያሉበትን ቤት ሁሉ ሞላው
         በዓለ መንፈስ ቅዱስ
Size:-28MB
Length:-1:20:27

በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
  
           
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

“ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።”

  — 1ኛ ቆሮንቶስ 10፥13


#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

🤔 ስለ ምን ማወቅ ይፈልጋሉ ❓

👳‍♂ሰለ ንስሐ
ንስሐ እንዴት እንግባ ⁉️፡
ንስሐ በጾም መግባት ይቻላል⁉️
ሁለት የንስሐ አባት መያዝ የቻላል⁉️
ስለ ስርአተ ቤተክርስቲያን:ስለ ምስጢረ ቁርባን፡ መንፈሰዊ ምክር፡ታሪክ የየእለቱ ስንክሳር ፡
❤️🧡💛💚💙💙💜💚💜💙💚💛ቆየት ያሉ ዝማሬዎች፡አዳዲስ ዝማሬዎች የመዝሙር ግጥሞች
መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች  የበገና ፡የክራር ፡የመሰንቆ  ትምህርት የሚሰጥበት ተከታታይ የሐዲስ ኪዳን ትምህርት የፈለጉት መጽሐፍ የሚያገኙበት የግዕዝ ትምህርት የሚሰጥበት የፈለጉት የሚጠይቁበትና ምላሽ  የሚያገኙበት ቻናል ነው። ለመቀላቀል ከስር Join የሚለውን ንኩት።
                 👇👇👇
         ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
         █   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲      █          
         ◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢




🖥ትምህርቱን በይቱብ መከታተል ለምትፈልጉ⁉️
𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 በማድረግ ይከታተሉ።
         👇🏽👇🏽

https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=pMjUosQePGmp8VuO
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=pMjUosQePGmp8VuO

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ብዙ ስለበደልኩ በእግዚአብሔር ፊት መቅረብ የሚቻለኝ አይደለሁም አትበል፡፡ ተስፋ አትቁረጥ፡፡ ተስፋ በመቁረጥ ምክንያት ኃጢአትህን አትጨምር፡፡

መሓሪ በሆነው _ አምላክ ርዳታ ወደ ቀደመ ማንነትህ መመለስ ይቻልሃል፡፡ እርሱ እንዲህ ብሏልና፡- ወደእኔ የመጣውን ወደውጪ _ አላወጣውም፡፡/ዮሐ 6፡37/

እርሱ ንጽሐ ባሕርይ ስለሆነ ወደ እርሱ የሚቀርቡ ወገኖችን እንደሚያነጻቸው እንደሚቀድሳቸውም እውነተኛ የሆነ ንስሐን እመን፡፡

እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ፡-

« ከክፋት ተመልሰህ መልካም ነገርን አድርግ፡፡/1ኛ ጴጥ 3፡11/

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#በዓለ ጰራቅሊጦስ

የቤ/ክ የልደት ቀን

‹‹ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም›› /ዮሐ. 14፥18/

ጰራቅሊጦስ፡- ቃሉ ግሪክ ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት መጽንኢ በእምነት የሚያጸና፣ መንጽሒ ከኃጢአት የሚያነጻ፣ ናዛዚ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፣ መስተፍስሒ፣ የተጨነቁትን የሚያስደስት፣ ከሣቲ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው፡፡

ጰራቅሊጦስ፡- መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የጰራቅሊጦስ በዓል ታሪክ እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡

ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም የሚሠራውን ሥራ ከጨረሰ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያትን ወደ አባቴ እሄዳለሁ (አርጋለሁ) ሲላቸው ደነገጡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም መደንገጣቸውን አይቶ ‹‹ኢይደንግድክሙ ልብክሙ እመኑ በእግዚአብሔር ወእመኑ ብየ እስመ ውስተ ቤተ አቡየ ብዙኅ ማኅደር ወምዕራፍ ቦቱ›› (ልባችሁ አይደንግጥባችሁ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም እመኑ በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ ማለት ባባቴ ቤት በመንግሥተ ሰማያት ብዙ ማዕርገ ሀብታት አለ) /ዮሐ. 14፥1)

እንዲሁም /በዚሁ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 14፥18/ ላይ እንደተጻፈው ‹‹ኢየጎድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ›› (ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም) ሲል መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን አጽናንቷቸዋል፡፡

/በሉቃስ ወንጌል 24 ቁጥር 49/ ላይ እንደተጻፈው የሰላም አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊያርግ ሲል ቅዱሳን ሐዋርያትን ‹‹አንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ኃይለ እምአርያም›› (እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ) አላቸውና ዐረገ፡፡ እነርሱም ይህን አምላካዊ ቃል መሠረት በማድረግ በኢየሩሳሌም በጽርሐ ጽዮን በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው ተሰብስበው ሳሉ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአረገ በአሥረኛው ቀን በተነሣ በሃምሳኛው ቀን የጰራቅሊጦስ እለት ጧት በሦስት ሰዓት ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወረደላቸው ከዚህ በኋላ ፍርሃት ከውስጣቸው ወጣ መንፈሳዊ ድፍረት አገኙ፡፡

አንድ የዕብራይስጥ ቋንቋ ብቻ ነበር የሚያውቁት ሰባ አንድ ዓይነት ቋንቋ (የአገሩ ሁሉ ቋንቋ) ተገለጸላቸው፡፡ ከእነርሱ ጋር በሰባ ሁለት ዓይነት ቋንቋ ተናገሩ፡፡ የአገሩ ሁሉ ቋንቋ የተገለጸላቸውም ሁሉንም በአገሩ ቋንቋ እንዲያስተምሩ ነው፡፡ ከተለያየ ክፍለ ዓለም የመጡ ነበሩ፡፡ እነዚህ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን? እንዴት የእኛን አገር ቋንቋ ሊናገሩ ቻሉ? በማለት ተገረሙና አመንትተው እርስ በርሳቸው እንጃ ይህ ምን ይሆን? አሉ፡፡ ሌሎች ግን ጉሽ የወይን ጠጅ ጠጥተው ሰክረው ነው አሉ ነገር ግን ቅዱስ ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፡- የይሁዳ ሰዎች በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፡- ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን ቃሎቼንም አድምጡ፡፡ ለእናንተ እንደመሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም ከቀኑ ገና ሦስተኛ ሰዓት ነውና ነገር ግን ይህ በነቢዩ ኢዩኤል የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ነው፡- ይህም ‹‹እግዚአብሔር ይላል በኋለኛይቱ ቀን እንዲህ ይሆናል ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች አገልጋዮች ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ፡፡ ድንቆችንም በላይ በሰማይ ምልክቶችንም በታች በምድር ደምም፣ እሳትም የጢስ ጭጋግም ይሆናል የታወቀችዋም ታላቅዋ የእግዚአብሔር ቀን ሳትመጣ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣል የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል›› /ኢዩ. 2፥28-32/ ይህን መሠረት በማድረግ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ልብን የሚነካ ትምህርት ሰጠ፡፡

ሕዝቡም ቅዱስ ጴጥሮስ በሰጠው ትምህርት ልባቸው ተነካ ቅዱስ ጴጥሮስንና ሌሎቹንም ሐዋርያት ወንድሞች ሆይ ምን እናድርግ? አሉአቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ንስሐ ግቡ ኃጢአታችሁም ይሠረይ ዘንድ ተጠመቁ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ፡፡ የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ አምላካችንም ወደ እርሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉ ሁሉ ነው
ስለዚህ ራሳችሁን ከዚህ ክፉ ዓለም አድኑ ብሎ መከራቸው፡፡ በዚህ ቀን ሦስት ሺህ ሰዎች አምነው ተጠመቁ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው የሞቱና የትንሣኤው ምስክሮች ሆኑ፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በነሱ ላይ ሲያድር ለቤተክርስቲያን ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ፡፡

ይህ የጰራቅሊጦስ በዓል በግሪኮች ቋንቋ ጰንጠቆስጤ ይባላል፡፡ ጰንጠቆስጤ ማለት ሃምሳኛ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ከተነሣ በኋላ ሃምሳኛው ቀን ነው፡፡ ይህም ዕለት በዓለ ሃምሳ፣ በዓለ ጰራቅሊጦስ ነው፡፡

እንዲሁም ታላቁ ሊቅ ቅ/ዮሐንስ አፈወርቅ ይህን በዓል በሚገባ አነጋገር ‹‹የቤተክርስቲያን የልደት ቀን›› ብሎታል፡፡ ይህ በዓል በብሉይ ኪዳን የእሸት በዓል (በዓለ ሰዊት) ይባላል፡፡ እስራኤል የነጻነት በዓላቸውን ከሚያከብሩበት ከበዓለ ፋሲካ ጀምረው ሃምሳውን ቀን በዓል አድርገው ይሰነብታሉ፡፡ በሃምሳኛው ቀን በዓለ ሰዊትን (የእሸት በዓላቸውን) ያከብራሉ፡፡ በሀገራቸው ከመጋቢት እስከ ግንቦት ያለው ወቅት በሀገራችን ከመስከረም እስከ ኅዳር እንዳለው የእሸት ወራት (የጸደይ ወራት) ነውና የእሸት በዓላቸውን የሚያከብሩት በኦሪት ዘሌዋውያን /ምዕራፍ 23፥10-17/ በታዘዘው መሠረት ማንኛውም እሥራኤላዊ ገበሬ ከዘራው ሁሉ በያይነቱ እሸቱን ቆርጦ ተሸክሞ ወደ ምኩራቡ ይመጣል፡፡ በቤተ መቅደስ የሚያገለግለው ካህን ተቀብሎ ባርኮ ጸልዮ የሚጠበሰው እየተጠበሰ የሚታሸው እየታሸ በማኅበር አንድነት ይበላል፡፡ ይህም ‹‹ቀዳምያት›› ይባላል፡፡ የመጀመሪያው ማለት ነው፡፡ ከማንኛውም በረከት የመጀመሪያው እግዚአብሔር ፊት መቅረብ፣ ለእግዚአብሔር መሰጠት እንዳለበት ታዟልና፡፡

በዚህ መሠረት ከበዓለ ጰራቅሊጦስ የምንማረው፡-ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን ‹‹እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ›› ባላቸው መሠረት በኢየሩሳሌም ተቀምጠው ተስፋውን ሲጠባበቁ መንፈስ ቅዱስ ወርዶላቸዋል፡፡ ዛሬ መንፈስ ቅዱስ የሚወርድባት ኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ናት ‹‹ ሚ መጠን ግርምት ዛቲ ዕለት ወዕፅብት ዛቲ ሰዓት እንተ ባቲ ይወርድ መንፈስ ቅዱስ እመልዕልተ ሰማያት›› (ይህች ቀን ምን ያህል የምታስፈራ ናት? ይህች ሰዓት ምን ያህል የምታስጨንቅ ናት? መንፈስ ቅዱስ ከሰማየ ሰማያት የሚወርድባት) /ሥርዓተ ቅዳሴ/ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ እንደ ወረደላቸው ለእኛም እንዲወርድልን ሁልጊዜ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ይገባል፡፡ ከቤተክርስቲያን ተለይቶ ጽድቅ የለም።

ቤተ ክርስቲያን፡- የመንግሥተ ሰማያት በር ናት ‹‹ዛቲ ይእቲ ኆኅታ ለሰማይ›› (ይህች የሰማይ ደጅ ናት) /ዘፍ 28፥17/
በዚህ መሠረት ለእኛም በ40 ቀንና በሰማንያ ቀን የተሰጠን ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እንዳይለየን ሕጉን ትእዛዙን መጠበቅና ጧት ማታ ወደ ቤተ ክርስቲያን መገስገስ ይገባል፡፡
ለዚህም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንዲሁም ቅዱሳን በአማላጅነታቸው ይርዱን፡፡ አሜን

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡
***

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

🛑እነሆ አዲስ ቻናል ይዘንሎት መጣን🛑
በማርያም ይህን ቻናል ሳይቀላቀሉ እንዳያልፉ ይደሰቱበታል መርጠን ለናንተ አቀረብንሎ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

         ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
         █   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲      █          
         ◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ሰንበተ ክርስትያን

እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች።

ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት
(ራዕይ 1፥10)

ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት።

መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን

#መልካም ቀን

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

❤️“ ንዑ ንትመሀር ልሳነ ግእዝ ”
🔅ኑ የግእዝ ቋንቋ እንማር🔅

📜 የሀገራችን የኢትዮጵያ ቀዳማዊና ጥንታዊ ስለሆነው የግእዝ ቋንቋ መሠረታዊ ትምህርት እንሰጣለን። እርስዎም አባቶቻችን ያቆዩልንን ቋንቋ በመማርና ለትውልድ በማስተላለፍ ኃላፊነትዎን ይወጡ!
📜

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ስርዓተ ኦሪት ስርዓተ ሀዲስ ከተፈጸሙባቸው 5 መቅደሶች መሐከል እንዷ የሆነችው የደቡቧ ኮከብ ብርብር ማርያም ነገ የእናታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ መገለጧን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች።
~~~~~~~

የደቡብ ክልል የክርስትና መነሻ እና የጥንታዊ ህገ እግዚአብሔር አምልኮ ማዕከል የሆነችው በጋሞ ጎፋ ሀገረስብከት የምትገኘው ብርብር ማርያም ነገ የእናታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ መገለጧን በደምቀት ታከብራለች።

በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መሰዋተ ኦሪት ከተፈጸመባቸው 5ቱ መቅደሶች መሀከል አንዷ የሆነችው ብርብር ማርያም ገዳም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓላትን እንደ ብሔራዊ በዓላት ልክ የአከባቢው ምዕመናንን እንደሚያከብሩ ይታወቃል።

የቴሌግራም ቻናላችን ከታች ያለውን ሊንክን በመስፈንጠር ቤተሰብ ይሁኑን፤

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

† እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የመገለጥ በዓል (ደብረ ምጥማቅ) በሰላም አደረሳችሁ †

†ደብረ ምጥማቅ †

=>የአርያም ንግሥት: የሰማይና የምድር እመቤት: የሰውነታችንም መመኪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በዚሕች ዕለት በምድረ ግብፅ ለተከታታይ ቀናት ተገልጻለች::

+ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:

+ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድረ ግብፅና ኢትዮዽያ በተሰደደ ጊዜ ከድንግል እናቱ: ከዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ዛሬ ደብረ ምጥማቅ በሚባለው ቦታ ላይ አርፎ ነበር:: ቦታውን ባርኮ ለዘለዓለም ያንቺ መገለጫ ይሁን ብሎም ቃል ኪዳን ገብቶላት ነበር::

+ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት ቤት ሆነ:: እመቤታችንም በልጇ ፈቃድ ግንቦት 21 ቀን አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላት መጣች::

+በዚያ ሕዝበ ክርስቲያንም: አሕዛብም ተሰብስበው ለ5 ቀናት ከእመ ብርሃን ጋር ይሰነብታሉ:: እንግዲህ ልብ በሉት:-
እንኩዋን የአርያም ንግስት: የአምላክ እናቱ እመቤታችንን ይቅርና በዚሕ ዓለም ሰይጣን ቤቱ ያደረጋቸውን: የመዝናኛው ኢንዳስትሪ ዝነኛ ሰዎችን ለማየት የዘመናችን ሰው እንዴት እንደሚቸኩል::

+እመቤታችንን በአካል መመልከት አይደለም ስሟን መጥራት ነፍስን ከሥጋ መለየት የሚችል ጣዕምና ደስታ አለው:: ባይሆን ይሔ ለሚገባውና ላደለው ብቻ ነው::

+የደብረ ምጥማቅና የአካባቢዋ ሰዎች ከእመቤታችን ጋር የሚቆዩባቸው ቀናት የዘለዓለም የሕይወት ስንቅ የሚይዙባቸው ናቸው:: ፈልገው የሚያጡት: ጠይቀው የማይፈጸምላቸው ምንም ነገር አልነበረም:: ነቢያት: ሐዋርያት: ጻድቃን: ሰማዕታት: ደናግል: መነኮሳት: መላዕክትና ሊቃነ መላእክት ለድንግል ማርያም ሲሰግዱ ይታዩ ነበርና:: እመ ብርሃንም እየመላለሰች ትባርካቸው ነበር::

+እነዚያ እርሷን ያዩ ዐይኖች: በፊቷ የቆሙ እግሮች ክብር ይገባቸዋል:: 5ቱ ዕለታት ሲፈጸሙ ሕዝቡ እመቤታችንን በዕንባ ይሰናበቷታል:: እመ ብርሃንም በብርሃን መስቀል ባርካቸው ከቅዱሳኑ ጋር ታርጋለች::

እናቶቻችን የተገለጠች እመቤታችን ለእኛም በረድኤት ትገለጽልን:: ጣዕመ ስሟ በአንደበታችን: ጣዕመ ፍቅሯ በልባችን ይደርብን:: †††

"+ የምድር ባለጠጐች አሕዛብ በፊትሽ ይማለላሉ::
ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ሁሉ ክብሯ ነው::
ልብሷ የወርቅ መጐናጸፊያ ነው::
በሁዋላዋ ደናግሉን ለንጉሥ ይወስዳሉ . . .
በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ::
በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ::
ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ::

+"+ (መዝ. 44:12-17)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር >

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

+ ደብረ ምጥማቅ +

ከሠላሳ ሶስት የእመቤታችን በዓላት አንዱ ነው ግንቦት_21 ቀን የሚከበረው ይህ የእመቤታችን በዓል ደብረ ምጥማቅ በምትባል ቦታ የወርቅ ወንበር ላይ ተቀምጣ ለአምስት ቀን የታየችበት ሲሆን በዚህ ቀን በግብጽ ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቦታ በተሰራች ቤተክርስቲያን እመቤታችን ጻድቃንን መልአክትን አስከትላ ተገለጽላቸው ነበር ።

እመቤታችን በስደት ሳለች ጌታ በዚህ ቦታ በስምሽ ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል ስሙንም ደብረ ምጥማቅ ይሉታል ብሎ ነግሯት ነበር ይኸውም አልቀረም በዚሁ ቦታ በእመቤታችን ስም ቤተ ክርስቲያን ታንጾ ስሙ ደብረ ምጥማቅ ተብሏል ።

በዚህ ዕለት እመቤታችን ከፀሐይ ሰባት እጅ አብርታ ከጉልላቱ ላይ በመንበር ብርሃን ተቀምጣ መላእክት ሊቃነ መላእክት ከበው ሲያመሰግኗት ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃን ሰማዕታት እጅ ሲነሣት ታይታለች

እስከ አምስት ቀንም ምእመናኑን አረማውያኑን አንድ ወገን አድርጋ ስትባርክ ሰንብታለች ከዚህም በኋላ ምእመናንም አረማውያንም በየዓመቱ እነዚህን ከግንቦት 21 እስከ ግንቦት 25 ለአምስት ዕለታት በደብረ ምጥማቅ ተሰብስበው የሚያከብሩ ሆነዋል ።

እኛም ለልጆቿ በሕይወታችን እየተገለጠች በረድኤት በበረከት ትባርከን !!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…
Subscribe to a channel