Subscribe ይደረግ
Amasia_Tube" rel="nofollow">https://www.youtube.com/@Amasia_Tube
መንቃት መረገም ነው
(በእውቀቱ ስዩም)
ሰማሽኝ ወይ እቱ!
ለንጀራው ለርስቱ
ፍጥረት ሲተባበር፥
አፍርሼው ተኛሁኝ ፤የቀን ሌቱን ድንበር
ህልም የሚሸጥ ቢሆን ፥ ከብሬልሽ ነበር::
እንዴት እንደዛልሁኝ ፥
በኑሮ እንደታከትሁ
በቅርበት ያላየች ፥
ጸሀይ ያለ ልምዷ ፥ ለመጥለቅ ዘገየች ፥
ልቤን ለንቅልፍ ሰጠሁ
ዓይኔን ለሰመመን
መንቃት መረገም ነው ፤በዚህ በኛ ዘመን ::
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዩች በሙሉ እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በሰላም አደረሳቹ 🙏
አብሮነት ወደ ፊት🙏
መልካም የገና በአል
አንዳንዴ እኔን የሚቆጨኝ . . . (በድሉ ዋቅጅራ)
አንዳንዴ እጅግ አልፎ አልፎ፣
የብቻ አለሜ ሲከፈት፣
. . . . . . . . የብቻ ሰማይ ሲኖረኝ፤
ከጀማው ዥረት መስፈንጠሪያ፣
መሹለኪያ፣
የማርያም መንገድ ሳገኝ፤
በራሴ ቦይ፣ መፍሰስ ሲያድለኝ፤
ጠልቆ - ሚበረብረኝ፤
አሽቶ - ሚፈረፍረኝ፤
አንዳንዴ እኔን የሚቆጨኝ . . .
ጨረቃ የወጣች እለት፣
እሳት ዳር ደጃፍ ያመሸን እለት፣
ለልጆቼ የነገርኩት ተረት፡፡
የፈረሰ ቤተ መቅደስ፣ ጽላት እንደተሸከመ፤
ላያገኝ እየፈለገ፣ ላይደርስ እያዘገመ፤
እንደሚኖር ባህታዊ፣ አይመነዘር ወረት፣
ታልቦ አይጠጣ ጥገት፣
ያተምኩባቸው ተረት፡፡
በወጡ በገቡ ቁጥር፣ . . .
ሲሰርቅ እንደተያዘ፤
መንፈሴ እየናወዘ፣
ቀልቤ እየቃበዘ፤
ፍርዱ እንዳልያዘለት ጠንቋይ፣ ማስፈራሪያ እየደረደርኩ፤
ባባትነት ክብር ዋሻ፣ ዘወትር እንደተሸሸግኩ፡፡
አለሁ፡፡ . . . እንደቆጨኝ፤
አንዳንዴ ብቻ አልፎ አልፎ፣. . .
ሰው መሆኛ መንገድ ሳገኝ፤
በራሴ ቦይ መፍሰስ ሲያድለኝ፡፡
አንዳንዴ፡፡
---------
(በወሎኛ በደጋጎቹ ሀገር)
አቦል ጀባ
አማን ኢማና ጀባ
የወደደሽ ልብሽ ይግባ
የወለደሽ ጀነት ይግባ
እንግዲህ
እዚያዉ ድረሽ
አትነኪ
አትደኪ
አካሌዋ ማሬዋ
አሚን በይግድ የለም
ካሚንታ የሚቀር የለም
አሚን ነዉ ዋልታዉ
አሚን ነዉ ማገሩ
ለሰማይ ላየሩ
ለህዋ ለምድሩ
አሚን በይ
ለመንጋጋሽ ስጋ
ለጎንሽ ፋሚሊ አልጋ
ወደ ጉያዉ የሚያስጠጋ
የሚያቅፍ እንጂ የማይወጋ
ጠይም ሎጋ
ክረምት እስከበጋ
ሉባዋ
ሸጋ ቁጥቢቱ
ባለ አደስ እንጨቲቱ
አንቺ ሙዳይ እቃ
የመሬት ድቡል ቦቃ
ጦሳ አባ ደገኛዉ
አዝዋ ጌጠኛዉ መጀን
እሜቴ ድንብላል
መርሳ አባ ጌትዬ ደጋጎቹ መጀን
አካሌዋ ማሬዋ
አሚን በይ ግድ የለም
ካሚን የሚቀር የለም
አሚን ነዉ ዋልታዉ
አሚን ነዉ ማገሩ....
ለሠማይ ላየሩ...
ለህዋ ለምድሩ...
አዋ እናቴዋ...
እርቅ ይሁን...
አትጪ....
አትታጪ....
አግኝ ....
ተገናኝ አትገኚ
እንግዲህ...
አዋ እናቴዋ እንግዲህ...
የቤት ቪላ
ከሎተሪም ቶምቦላ
የሠማይ ሩቢላ
የስንዴ ዛላ
ጧት ማታ የሚበላ
ያልጋ ወጌሻ
ድካም ማስረሻ
ደግሞ መካሻ
አዎ እናቴዋ
አሚን በይ...
የልብ ብራና
የወንድ ጀግና
የስንዴ ዛላ
የልጅ ሳዱላ
የጤፍ አማላ
የወተት ማላ
በቤትሽ ይሙላ
አሚን በይ አካሌዋ
መቼ ይሁን
አሁን!
የእመቤቴ እለት
ማደጌን አውቄ፣
ሔዋኔን ፍለጋ ልቤ እግር አብቅሎ፣
በእመቤቴ ቀን፣
እቅዱን ለማግኘት ማመንታቱን ጥሎ።
መንገድ ጀመረ እና፣
ብዙ በመፈለግ በማጣራት ማስኖ፣
በእመቤቴ እለት፣
ድካሙ አበበ መሰልቸቱ በኖ።
የመቤቴን እለት፣
ደጋግሞ ኖረ እና ወደድኩህ ካለችው፣
አንዱን ሰሞን ጠፍታ፣
ሳታገኘው ስትቆይ መስሎት የጠላችው።
ያገኘውን ማጣት፣
ከብዶ ታየው እና ደጇ ስለት ገብቶ፣
አምኗት ተረጋጋ፣
ጭንቀቱን አጋርቷት መጨነቁን ትቶ።
ብዙ ቆየች እና፣
ሳትደውል ሳያያት በአንዱ የማርያም ቀን፣
ናፈከኝ አለችው፣
በሚጣፍጥ ቃና በለሆሳስ ዘፈን።
ደሥታውን አምቆ፣
ስለቱን ሊያስገባ ሊሰናበታት ሲል፣
ዛሬን አብሯት ውሎ፣
እንዲያድር አዘዘችው በመፈቀሯ ኃይል።
አይሆንም አለና፣
ክልከላዋን ጥሶ መጓዙን ሲጀምር፣
ድጋሜ እንዳይመጣ፣
አበክራ ነግራው ዘጋች የልቧን በር።
አማኝ ምስኪን ልቤ፣
የእመቤቴ ቀን በእናቴ እለት፣
ያገኛትን ወዳጅ፣
በእመቤቴ ቀን ለእምነቱ ሊያጣት፤
ስለቱን ሸምቶ፣
ለሰማችው እናት ወስዶ እያስረከበ፣
አትምጣ ካለችው፣
እሷን አስበልጦ ከመሄድ ታቀበ።
✍️ እያደር ሞገሥ (የሞገሤ ልጅ)
👇👇👇/channel/eyadermoges1 /channel/eyadermoges1 /channel/eyadermoges1
እንሆ በጨዋ ደምብ አዲስ ነገር ይዛ መምጣቷን ቀጥላለች። ዛሬም በየመሃሉ እንደሚያደርገው የ ሞገሤ ልጅ #ትዝታውን ለቤተሠቦቹ ያጋራል። አሁኑኑ ይቀላቀሉን /channel/eyadermoges1
Читать полностью…ነገረ ቅዳሜ
(የሞገሤ ልጅ)
አሁንም ቀጥለናል!
***
ለብዙ ሠው አንድን ቀን አድሮ ማየት እንደመታደል እንደሚሆን ቢያንስ፣ "በእድሜ ላይ እድሜ ጨምሮ ለዚህ እለት ያበቃን ይመስገን"
የሚለውን የቤ/ክርስቲያን ምስጋና በማድመጡ አብዛኛው ሠው ይሰርጽበታል ብዬ ለማመን አንድን ነገር በትኩረት እንዲታይ ከማድረጊያ መንገዶች አንዱ መደጋገም፣ አንድኛው፣ በትኩረት ሳቢ ቀለም መጻፍ፣ አንዱ ደግሞ የሚንቀሳቀስ ማድረግ እና ሌሎች አንድ አንድ መንገዶች እንዳሉ ያሳወቀኝ መማሬ ነው። አመሰግነዋለሁ።
***
አማርሬ ለማልለውጣቸው ነገሮች ማመንዠክ እየቀናኝ ወደራሴ ነገሮችን ማባባሴ እራሴን እንድነቅፈው ቢያደርገኝም፣ የኔ ማማረር ማቆም የማይሆን ነው እና ለማይቀየር ነገር እራሴን ነቅፌ ችግሩን ከማባባስ ብዬ ትቼዋለሁ። እንደልብ በማማረር ላይ ነኝ! ዛሬ ግን ቴሌግራም ደግ ነው አንድ አንድ ቦታዎች ዘወር ዘወር ስል ቀድሜ ከልቤ የጫርኳቸው ግጥሞች ሜንሽን መደረጋቸውን እና ሪአክት መደረጋቸውን ባመላከተኝ ፕላትፎርሙ አካሄድ ወደኋላ መለስ ብዬ ጎበኘኋቸው። እስኪ ደግሞ እነዛ ጽሁፎቼ ያሉኝን በጥቂት ልበላችሁ!
***
ነቢል መኮንን {ደራሲውን} የማውቀው አንድ ቦታ ነበር። እድሜ ለመአዛ እና ሸገር ካፌ ላይ። የግጥም ፍቅር ባለኝ ልክ ግጥም አላነብም፣ ሲገጥመኝ ከማረከኝ ግን አላልፍም። ታድያ ያ ትልቅ ሠው በጨዋታዎቹ መስማትን እንዳልተው ሰቅዞ ይዞኝ፣ ካልተሳሳትኩ ሙሉ ዝግቱን ተከታትዬ ነበር። የእረፍቱን ዜና የሰማሁ እለት ግን "መቃዠትህ ነው"
የሚለኝ ፍለጋ በልቦናዬ እየማሰንኩ፣ ይህችን ግጥም ጫርኳት።
***
ሄደ ሲሉኝ መጣሁ፣
ልሸኘው ከሄደ፣
ድሮም የኔ ነገር መች ነገር ወደደ።
ቆሞ ሲሄድ ትቼው፣
ሲራመድ ረስቼው፣
መኖሩ ሲተረክ በድኑን ሰስቼው፤
መቃብር ሲገባ ያንን ጥበብ ይዞ፣
በገዛ ድርሰቱ ታጥቦ ተገንዞ፤
አፈሩን ልጋራ ሸክሙ ቢቀለው፣
ድንጋዩ እንዲጫነን አብሬ እምተኛው፤
"ሠውን ማመን ቀብሮ" አባባሉ ገዝቶኝ፣
አምኜው አንድ ቀን ሳምነው እንዳይከዳኝ፣
ለዚህ ነበር ለካ ከህመሙ በላይ መሞቱ ያመመኝ።
መታሰቢያነቱ ለ ታላቁ የጥበብ ሠው፣ ነቢይ መኮንን።
✍️ እያደር ሞገሥ (የሞገሤ ልጅ)
***
እንዳሰቡት ከማይሳካው ነገር ይልቅ እንደተመኙት የማይሆን ነገር መብዛቱ የሚያከራክር አይመስለኝም። ለምን ይዋሻል? ተመኝቻት ነበር! ማንም በመመኘቴ ጫፌን እንዲነካ አልፈቅድም! ምኞት ግን ሃጥያትን ትወልድ ይሆን እንዴ? ይቅር ይበለኝ ከሆነ! ዳሩ ግን አልተሳካም! እኔም ከመጥራት ያለፈ አልጎተትኳትም፣ እሷም ጥሪዬን ከመስማት ያለፈ አንድ እርምጃ አልቀረበችኝም። መብቷ ነው! ያው ታድያ ተለዋጭ መርህ በሷ ጉዳይ ነደፍኩ። ለምን ተለዋጭ እንደሆነ ግን ይገርመኛል! አይ ምኞት! አሁንም ለካ አልተፋታኝም! ብቻ መርሄ ተከታዩ ነበር!
***
መሃል መንገድ ላይ መቆም፣ መንታ መንገድ ላይ ግራ መጋባት፣
የማይገኝን መናፈቅ የማያደምጥን መጣራት፤
ጉዳቱ እጥፍ ነው እና፣
አውቀው እያዩ ማጥፋት፣
ግራ አልጋባ እና በቃ ጨክኜ ልርሳት!
የሞገሤ ልጅ።
ደግ ቀዳሚት ሠንበት!
/channel/eyadermoges1 /channel/eyadermoges1
🔥🔥 አዲሥ ነገር እያመጣን ነው!
በጨዋ ደምብ የተሻለ መነቃቃትን ለመውለድ ለቤተሠቦቿ በቅርቡ በለስ ቀናህ ተብሎ ባይወራላትም ሰበር ነገር ልታስመለክት ነው።
በአዲስ አዲሱ እንመጣለን! አሁኑኑ አይቀላቀሉም ታድያ! እድሉ ከማትረፍ በፊት መትረፍ ለሚሹ ጨዋዎች እንሆ ተከፍቷል! አዲሥ ነገር ይገባችኋል! አሁኑኑ በዚህ ሊንክ: /channel/eyadermoges1 joyn ይበሉ!
#በጨዋ_ደምብ #የሞገሤ_ልጅ #አዲስ_ነገር
ሓገሬ አመማት፣
ጣር እያለፋት ነው ድሕነቷ ገፍቶት፣
ወገኛ ልጆቿ፣
እንዳዩት ለመምሰል ተመላልጠውባት።
እኔ ላክማት ስል፣
በሷ በመውጣቴ እራሷን መስያት፣
እሷን በመሆኔ፣
ላነሳት ስትከብደኝ ተኝቼ አታኛኋት።
#share! /channel/+44E_a1KyVd8yNmI8
የጠጅ ቤት ግጥሞች
#በጨዋ_ደምብ
ጸጉሬን መለጥኩት፣
ጨጓራዬ አለቀ፣
አይምሮዬ ነፍዞ በሚያስለቅስ ሳቀ፤
አጥንቴ እንዳይከሳ፣
ስጋዬን አፍርሼ፣
በኮሪደር ሰበብ በለማሁ ፈርሼ።
ጋጣው በግ ገባበት፣
ከጉሮኖው ፈረስ፣
ከበረት ተነካሽ ከበሩ ፊት ነካሽ፤
ስድስት ቁጥሬን ዘጠኝ፣
አድርገሽ አይተሽው፣
ምነው መሠንበቴን ለአይንሽ ጠላሽው?
በሳማ ገረፉኝ፣
ልብለባው ወረፈኝ፣
አንቺን አንቺን ማለት ለመቁሰል ዳረገኝ፤
እሱን እሱን አትበይ፣
ከእኔ ተማሪ፣
ጠጅ ጠጪ ሆኖ ይቀራል አፍቃሪ።
እንጀራ አይወድም፣
ባዶ ነው መሶቡ፣
ባዋጣ ባዋጣ፣
አይወጣም እቁቡ፤
ወር ጠቋሚው እጣ፣
አንደኛ ነህ ያለው፣
ከጄ ሳያስገባሽ የት ገብተሽበት ነው?
@eyadermoges1 @eyadermoges1 @eyadermoges1
እያጋራን 😁! @afengusbot ማጋራት የምትፈልጉትን ስራ፣ ያላችሁን ጥቆማ፣ ሃሳብ እና የግል ምልከታ ሊቀበላችሁ ዝግጁ ነው። እኛ ወደስራ እንገባበታለን ያጋሩን!
<ይውልህ ምን መሰለህ
መለገስ ጥሩ ነው በረከትን ያመጣል ። ጤና እና ሰላም ካንተ ጋ እንዲሆን ያደርግልሃል ምድራዊም ሰማያዊም ህይወት መንገድ ያቀናል ።
ምን አልባት እምልክ አሁን አይገባህም !!
መለገስን የመሰለ ። ሰው መሆን ። ለሳቅ ምክንያት መሆን የመሰለ ደስታ የለም
እ ....እየገባህ ነው ኣ ??>>
ብዙ መከርኩት ብዙ ። በዝምታ ቃል ሳያወጣ ። እየመከርኩት ሳለ
Uniform የለበሰች ፀጉሯን ቁጥርጥር የተሰራች ትንሽ ልጅ ፈገግ ብላ እኛ ወዳለንበት በኩል ተሻገረች
ይልማ.. ይልማ ..ይልማ ..... አንተ ጋ እየመጣው ነበር ... እማዬ አንዳለችህ አባዬ ደና ሆኗል ፍርድቤቱም ለኛ ወስኖልናል ። በድብቅ ያደረክልንን፤ ሸክማችን እንዳገዝከን አምላክ የጎደለህን ይሙላልህ።በበረከት ያትረፍርፍህ ብላሃለች "አለችው ።
እሺ ..እሺ ብቻ ብሎ ተሰናበታት ። አሁን እኔ ምንም ሳላወራ እንዴት እንደምሰናበተው እያወጠነጠንኩ ነው ...
ያንዳንዱ መልካምነት ምላሱ ላይ ያንዳንዱ ሰው መልካምነት ልቡ ላይ ነው ያለው!!!
© Adhanom Mitiku
🙏 ......🙏
ለአመታት አፅናንቶ
ለተስካር ይረሳል!
ወትሮም በልብ ያለ
በአፍ ይዘነጋል!
ለመርሳት ቢሰክሩ
ማስታወስ ይወለዳል!
የዛን ጊዜ "ግጥም"
በደም ይፈረማል
"አመሰግናለው"
ርዕስ ይሆናል !!
ኤርም 'ከ'
#ትዝታ
በሠንበት ወግ
(የ ሞገሤ ልጅ)
እንደኃገራችን በእድሜ ወደፊት በኑሮ ወደኋላ መጓዝ እኔ እና መሰሎቼ እጣችን እንደሆነ ማሰብ ለመጀመር የተገደድኩት እኔን ጨምሮ አንድ አንድ የማውቃቸው፣
“ድሮ እኮ ጥሩ ነበር”
ማለት እንደምናበዛ በማወቄ ነው።
ምክንያቱም ጥሩ የነበረው ድሮ በእኔ አልተሰራም። በእኔ የተሰራው ዛሬ ግን ጥሩ አይደለም ማለት ነው። ስለዚህ ጥሩ የሰራውን ግለሠብም ሆነ ኅብረተሠብ መሻማት የምንኖርበት ዛሬ ትዝብት ለመሆን ተገዷል።
*ማኅበረሠብ ወታደራዊ እና ዘመናዊ ተብሎ መከፈል ይችላል።
በወታደራዊው የማኅበረሠብ አይነት ውስጥ በእራስህ መንገድ መኖር የማይታሰብ ነው። የሠራሐው ነገር ተቀባይነት የማያገኘው ልክ ስላልሆነ ሳይሆን ባህል ስላልሆነ ሊሆን ይችላል።
በአንጻሩ ግን ዘመናዊ የማኅበረሠብ ክፍል ውስጥ ምርጫህን ከመረጠህ ጋር ወይም ብቻህን ትኖራለህ።
እንደልብ እራስን ማጨማለቅም ማርቀቅም የተፈቀደ ነው።
እራሱን መምራት ላልቻለ ታዲያ ዘመናዊነቱን አልደግፍለትም።
“ሠው ማኅበራዊ እንስሳ ነው” የሚለውን ሳይንሳዊ ትንተና ተቀብሎ ሳያላምጥ በመዋጥ አንተ በምታልፍበት ጎዳና ሲወስብ ታገኘዋለህ። በፈሪሃአምላክ አትንኩ የተባለን ሳይነካ ኗሪ፣
“አምላክ መኖሩን ማስረጃ” ብሎ ይጠይቀው እና ማስረጃዎቹን ከአፈር ከቀላቀለ ብኋላ፣
“አምላክ ሊኖር እንደሚችል ማስረጃው አምላክ እንደሌለ ማረጋገጥ አለመቻሉነው” ይልህ እና አምላክ ሊኖርም ላይኖርም ይችላል ወደብሎ ማመን ያሸጋግርሃል። ከዛ ብስልም ጥሬም ባለመሆን በአምላክህ ትተፋለህ።
እኔ ታዲያ ዘመናዊዉን የማኅበረሠብ አኗኗር በጥቅሉ አልደግፍም፣ የወታደራዊው አይነት ግን በከፊል ውስጤ ነው። እንግዲህ ወደራሴ ትዝታ ግን በሌሎች ወደተሰራ ትላንት መመለሴ ነው።
• ሠፊ በሚባል ቤተሠብ ውስጥ መኖሬ መቻቻልን፣ አንድነትን፣ መተሳሰብን፣ መተባበርን እና መከባበርን እንድረዳ እንዳገዘኝ አምናለሁ። ብዙ ያልቆየ መቀራረብ፣ ረጅም ዘመን ያልተቆጠረበት ኅብረት፣ ያልተጠገበ አብሮ መኖር፣ የተገደበ መቻቻል፣ የሰፋ መነፋፈቅ፣ የተራራቀ መገናኘት፣ የተለካ አብሮ መሆን፣ የተወሰነ መጨዋወት የሰፈነበት ትልቅ ቤተሠብ።
• * 12 ሆነን በምንኖርበት የአባታችን እና እናታችን ቤት ውስጥ ብዙ ጸባያት ነበሩ። ብስጭት፣ የዋህነት፣ ሞኚነት፣ ብልጥነት፣ ሞልቃቅነት፣ ዝምተኝነት፣ እና ሌሎች በውል ምድባቸው ያልተገለጹልኝ በሃሪያት።
• ***
• ወንድማችን ነው። ከሚያጠልቀው ቦት ጫማ በቁመት ኮርቶ ሳይበልጥ እራሱን ማስተዳደር የወሰነ ጀግና። ከላይ ሲረዳን እንደየዋህ የሚያደርገው ደፋር።
እህል የተወቃበትን አውድማ ለሊት ጠርጎ በቁጥር በጣም ትንሽ በኃይል ጠንካራ በሆነች ሳንቲም ዶሮ ገዝቶ ማርባት ጀምሮ እንቁላል ማምረት ይዞ ነበር። ታድያ እኛ ለመንካት አይፈቀድልንም።
የተባበሩት ወንድሞች ዘዴ ታድያ በግዜው ከማስተዋሉ የበለጠ ሆነ እና በጭራሽ ለመንካት የማይፈቀድልን እንቁላል ወደያልተገደበ የምግብ ዝርዝር ተሸጋግሯል። ሃሳቡን ከመናገሬ በፊት ግን ያ በጥብቅ የሚጠበቀው እንቁላል እኔን በደረሠብኝ ግዜአዊ ህመም ጥቅም ላይ በቸርነት ውሏል። ታድያ የዛሬው ትረካዬ ካልሆነችው ተወዳጅ እህቴ ያልታወሰኝ የኃብት ምንጭም ተጨማሪ እንቁላል ታክሎበት ነበር። አሁን ወደታሪኩ ልመለስ።
• የተከማቸው እንቁላል የሚያጓጓን ልጆች መብዛታችን እና በአይምሮ የተሻለ የበሰሉ ጓጊዎች መኖራቸው የዛን ንብረት ክልከላ እንዳይመለስ አድርጎ ማጥፋቱ እሙን ነው። ወደ ማሳመኛው ሃሳብ ቶሎ ወስጄ ላሳያችሁ። የወንድሜን ስም ግን ባምላክ ብዬ ለዚህ ጽሁፍ እጠራዋለሑ። ስለዚህም በታሪኩ ባምላክ እየተባለ የሚገለጸው ወንድሜ ንብረቱን ያስረከበ፣ ወንድሞቼ እያልኩ የምገልጻቸው ወንድሞቼ ደግሞ የሃሳቡ አመንጪ እና የንብረቱ ተጋሪ መሆናቸው ልብ ይባልልኝ።
• *ወንድሞቼ፣
• “ባምላክዬ እንቁላል እንብላ ዛሬ?”
• *ባምላክ፣
• “ማርያምን አንድ ሠው ይነካ እና!”
“ወንድሞቼ፣
“ለምን እንዴ!”
ባምላክ፣
“ዶሮዎቹ የራሴ ናቸዋ አያገባችሁም።”
ወንድሞቼ፣
“እኮ ዶሮዎቹ ናቸዋ ያንተ!”
ባምላክ፣
“እና?”
ወንድሞቼ፣
“እንቁላሉ ደግሞ የኛ ነው!”
ባምላክ፣
“ኧረ እ!”
ወንድሞቼ፣
“እውነት! ስለዚህ ዶሮዎችህን አንነካም፣ እንቁላል ግን እንበላለን።”
*አሁን ላይ በታሪኩ ሁላችንም እንስቃለን። እውቀት ሲደረስበት ይናቃል እንጂ በግዜው የቤቱ ድንቅ ተንኮል ነበር ሃሳቡ። በልጅ አእምሮ የታሰበ ድንቅ ማታለያ።
ሕይወት ጥሩ ሆና ልትዘልቅ ትችል ይሆናል፣ መጨረሻዋ የሚበሠረው በሞት ስለሆነ ግን ደሥ አይልም። በጥሩ ቤታችን እንደነበረ እንዳይቀጥል መጠነኛ እርማት ያደረገ ችግር ግን ነበር፣ እንመጣበታለን። እስከዛው ለሌሎች እያዳረስን! አበቃሁ።
/channel/eyadermoges1 /channel/eyadermoges1 /channel/eyadermoges1
የቻናሉን link ማጋራት እና ድጋፍዎን ማጠናከር አይዘንጉ! ሃሳብ ካለዎት ወይም በቻናላችን እንዲጋራ የሚፈልጉት ስራ ካለዎት @afengusbot ላይ ይላኩልን! አዲስ ነገር ይገባችኋል።
ካደፈጠው እዳ ሁሉ፥ በየበስ፥ ባየር ላይ
ከአውሎ ነፋስም በላይ
ከመሬት መራድም ይልቅ ....
ሰው ነው ሰውን ሚያሳቅቅ
ሰው ነው የሰው አደጋ
ደግሞ በሌላ ገጹ፥ ሰው ነው ለሰው ልጅ ጸጋ
ከስጦታው አካፍለኝ ፥ ካደጋው አስመልጠኝ
አልሳሳት አልልህም፥ የሚታረም ስህተት ስጠኝ !
ደርሷል ደርሷል ደርሷል!
የሞገሤ ልጅ አዲስ ግጥሙን ከደቂቃዎች ብኋላ ለቤተሠቦቹ ያስመለክታል!
አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡ /channel/eyadermoges1 /channel/eyadermoges1
አሁን የተለቀቀ አዲስ እና ማንም ያላየው ግጥም ቻናላችን ላይ አለ! አሁኑኑ ገብተው ይመልከቱ 🏃🏃🏃! 👇👇👇
/channel/eyadermoges24/24416 /channel/eyadermoges24/24416
ቀለድሁና ሳቅ ብትል
ደማም አፏ፥
እንደበቃ ባህታዊ፥
(የረቀቀውን አጉልቶልኝ
የጠበበውን አስፍቶልኝ)
ጠሐይቱ ከዓይኖቿ ማይ፥
ተነካክራ ተለቃልቃ ፥ ስትመለስ ወደሰማይ፥
ዐየሁና... ዐየሁና...
በልጅነት በውብ ዘመን ፥ ድሮ እንደሰሙት ሙዚቃ፥
ሆድ ውስጥ ያለ ባር ባር የሚል ፥ ከሰመመን የሚያነቃ፥
የሚመስል፥
በአሳሳቋ ንፅህና፥
የረሳሁትን መኖር ፥ ደሞ ደሞ አስብና፥
እናፍቅና... እናፍቅና...
አሳሳቋ፥
ከዐይኖቿ ጋር ቅንብሩን፥
የተሳካ ስብጥሩን፥
ፊት ገጿ ላይ የሚራቀቅ ፥ የተፈጥሮን ፍልስፍና፥
አጠናና... አጠናና...
"ትንኝ ልሁን?
ተወርውሬ ፥ ከብሌኗ ስር ልወተፍ?
የዓይኖቿን በር ደጅ ልጥና?
ይለይለት ሞት ይውሰደኝ ፥ ጨው እንባዋን ልጠጣና?"
እል እልና...
አሳሳቋ እንደባህር ዛፍ ፥ ሌላ ቁንጅና ሲገድል፥
ጎኗ ያለውን ውበት ሁሉ ፥ የሌላ ማማር ሲያጎድል፥
የብቻዋን ልዕልና
እታዘብ... እታዘብና...
ከሳቋ ፊት ተቀምጬ
አያታለሁ... አያታለሁ
"ምንሆንክ?"ስትል
"ቀልድ በሆንሁ" እላታለሁ
ቀልድ ልሁንልሽ?
ገጣሚ ሚኪ ምናሴ
"ሚዛን እና መዛኝ!!!"
በኛ ጊዜ ቅኝት፣
ከሰውነት ደጃፍ፣
ከልባችን አካል፣
ከህይወት ግንድ ላይ፣
ክብር እንደ ቅጠል፣
ተቀንጥሶ ሲጣል፣
በየመንገዱ ጥግ፣
ህሊና እንደ ዱቄት፣
ተሰፍሮ ይሸጣል፣
ታዲያ በዚህ መሀል፣
ላካባቢ ውበት፣
ለከተማ ጥራት፣
በፍቅር ተሳስረው፣
ከኖሩበት ሰፈር፣
ለስንት ዘመናት፣
መሬቱ እንዲፀዳ፣
ደሀ እንደ ቆሻሻ፣
ጠርገው እያሶጡ፣
ድንጋይ አሰልፈው፣
በገነቡት ህንፃ፣
ገብተው ተቀመጡ፣
ህይወት ይቀጥላል፣
ከቆመ ህንፃ ስር፣
ሰው ወድቆ ይገኛል!!!
ይገርማል፣
ለካስ የኛን ሰፈር፣
ከሰውነት ይልቅ፣
ድንጋይ ያሱበዋል፣
ለካስ ከተማውን፣
ከሰው ፍቅር ይልቅ፣
ህንፃ ይሻለዋል፣
ለካስ ይሄን ትውልድ፣
ከህሊና በላይ፣
ህግ ያሸንፈዋል፣
ለካስ ሰውነትን፣
በተፈጥሮ ዋጋ፣
ድንጋይ ይበልጠዋል!!!
ታዲያ ከዚህ አንቀፅ፣
ባየነው እርቀት፣
በሚገባን መጠን፣
ጠሪ እና መጠሪያ፣
ሚዛን እና መዛኝ፣
የሚል ሀሳብ ይዘን፣
ቅረቡ እንማማል፣
አንድ በሚያደርገን፣
በምንጠጣው ውሀ፣
እስኪ እንጠያየቅ፣
ሰውነት መጠሪያው፣
ህሊና ነው ደሀ???
ብለህ አትጠይቅ፣
ሌላው በዘመቻ፣
መልስ ይዞ ሲደብቅ፣
አንተ ጊዜ ሆነህ፣
በጥርስህ እየሳክ፣
በልብህ ቀን ጠብቅ፣
ምሬትህን ቀንስ፣
ሰማንያህን ቅደድ፣
ሀዘንህን ፍታት፣
ትንቢት ሰማይ ሆኖ፣
ተስፋ ፀሀይ ይዞ፣
ከንጋት ተቃጥሮ፣
ዶሮ እስኪጮህባት፣
ልመናህን ቆጥብ፣
ይቺን ከንቱ ዓለም፣
አትለማመጣት፣
ለምን?
የተስፋህን መሬት፣
ተኳሹ ነው እንጂ፣
ጥይት መች ገደላት!!!
#መርዕድ ተስፋዬ