ጾመ ነብያት በያዝነውሳምንት ይገባል ጾሙን በኦርቶዶክሳዊ የጾም ስርዓት ማሳለፍ ይኖርብናል ማለትም በጸሎት በንስሀ በንባብ ማሳለፍ ይጠበቅብናል።
ለዚህ ጾም ብናነባቸው ብዬ የምጋብዘው መጽሐፍት
ስለ ጌታችን ቅድስት ልደቱ እና ስለ ነገረ-ክርስቶስ የሚናገሩ የአበው መጽሐፍትን
፩ የቅዱስ አትናቴዎስን On the incarnation of the word
፪ የቅዱስ ኤፍሬምን On our lord
፫ የቅዱስ ኤፍሬምን Hymn on the nativity
፬ የቅዱስ አምብሮስን The sacrament of the incarnation of our lord
፭ የቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያን Scholia on incarnation of the only begotten
፮ የቀሲስ ታድሮስን Joyful songs of the glorious nativity let Us praise with the angels by st. jacob of serugh
ሌሎች የአበው ሥራዎች
፯ የቅዱስ ሄሬኔዎስን On the apostolic preaching
፰የቅዱስ ቆጵርያኖስን On the unity of the church (treatise1)
፱ የቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያን On the holyspirit
፲ የቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙን On God and christ the five theological orations
፲፩ የቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስን Catechetical discourse
፲፪ የቅዱስ ኤፍሬምን Hymns on the unleavened bread
አምላከ አበው አንብበን ለመጠቀም ያብቃን!
በቃ ከከቲክቶክ መሰናበቴ ነው☹️☹️😁😁
"አንተን ከዚህ ቲክቶክ ውስጥ እልም አድርጌ ካላጠፋውህ እኔ አይደለሁም"
👉ፈሪ ጌታ ጽጌ ሥጦታው
@Apostolic_Answers
ሴቶችና "የንስሐ አባት"
እሺ ባለፈው ያቋረጥኩትን ዛሬ ላውራችሁ.. እንደምታውቁት አንዳንድ "ካህናት" በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆነው የፕሮቴስታንቶችን አጀንዳ የሚያስፈፅሙ አሉ.. ምናልባት ይህንን የሚያደርጉት ኃይማኖትን በማጣመም ሊሆን ይችላል..
አሁን ግን ክርስቲያኖችን ከቤተ ክርስቲያን የማባረሪያ አዲስ ስልት የሚመስል ነገር እያስተዋልን ነው.. ይህንን በጥናት ደረጃ ለጊዜው 100% እርግጠኛ ባልሆንም ድርጊቱ ግን ስላለ ጥቂት ነገሮችን ልበላችሁ..
አዲስ አበባን ጨምሮ ተለቅ ተለቅ ባሉ እንደ ሐዋሳ ባሉ ከተሞች ላይ እጅግ ተመሳሳይ ነገር እየተፈጠረ ነው.. "ምንድን ነው እሱ..??" አትሉኝም.. እሺ ልዝለቅ ወደ ዋናው ጉዳይ:
ጥቂት የሚባሉ "ካህናት"(አንዳንዶቹ ላይሆኑም ይችላሉ) እጅጉን የምንወዳቸውን የንስሐ አባቶቻችንንም እንዳናምንና ብሎም ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን ጥለን እንድንጠፋ በየከተማው ትልቅ የሆነ ግፍን ይሰራሉ..
ይህ ሥራቸው በየቦታው በጣም ተመሳሳይ ከመሆኑ አንፃር የሆነ ኮርስ የወሰዱ ነው የሚምስሉት
ሥራቸው:- ሴት ክርስቲያኖችን የንስሐ ልጅ አድርገው ይወስዱና ከዚያም እጅጉን አስነዋሪ በሆነ መልኩ መካሪ መስለው sexual የሆኑ ነገሮችን ደጋግመው ያወሯቸዋል.. ስለ ፆታዊ ግንኙነት መምከሩ ሳይሆን ችግሩ ይልቁንም ሁሌም ከዚህ ጋር በተያያዘ ረጅም ወሬ ማውራቱ ነው.. በዚህም አይበቃም ይልቁንም ከእሕቶች ጋር ፆታዊ ነገር ወደ መፈፀም ያመራሉ.. ይህንን ሲያደርጉ ደግሞ አንዳንዴ በድፍረት የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት እንደሆነ ይናገራሉ.. ሌላው ደግሞ ይህንን ሲያደርጉ ነውራቸው እንዳይታወቅ "ለማንም ሰው አትናገሩ" ይላሉ.. ይህ ሴራቸው ሲጋለጥ ደግሞ ሰዎች አዝነው እንዲተዉአቸው የሚያደርጉ ትወናዎችን ያሳያሉ..
በዚህ ውስጥ እነዚህ እሕቶች እምነታቸውን እንዲጠሉና ከቅዱስ ምስጢር(ሥጋ ወደሙ) እንዲርቁ ይሆናሉ.. ከዚያም ሙሉ በሙሉ የጌታን እምነት ይተዋሉ..
እሕቶች እንዲህ ያለ ሰው ድንገት ካጋጠማችሁ በግልፅ ለሰንበት ትምህርት ቤት የበላይ አካላት እና የዛ ሰው ልጆች ከሆኑ ሌሎች እህቶች ጋር በመነጋገር የሆነ ነገር ላይ ድረሱ.. ለህግ መስጠት ካለባችሁም አሳልፋችሁ ስጡ..
እንደውም ሰሞኑን እንዲህ ያለ ነገርን ለማድረግ ሲሞክር የተገኘን አንድ ሰው የዛው ደብር ሰንበት ተማሪዎች ናቸው መሰለኝ ክፉኛ መቱት አሉ😁😁🙊🙊 መቀጥቀጥ ጥሩ ነው አይደለም የሚለውን ብዙም አላውቅም እኔ😉😁 ያው ግን ቀጥታ ለሕግ አሳልፎ መስጠት መልካም ነው..
@Apostolic_Answers