በክርስትና ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ሐዋርያዊ መልሶችን ለማቅረብ የምንሞክርበት ቻናል.. YouTube፡ https://m.youtube.com/@apostolicanswers1
ከትግራይ አካባቢ የሆኑ አንዳንድ ወንድም እህቶች ስለ አሁኑ ችግር🤦♂️🤦♂️
https://vm.tiktok.com/ZMY6SvKrn/
9:00
ተንስኡ ለጸሎት
ይህች ሰዓት ጌታችን ኢየሱስ ቅድስት ነፍሱ ከቅዱስ ሥጋው የተለየችበት ስለዚህም የሞተበት ሰዓት ናት.. ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ጌታን እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
@Apostolic_Answers
"በመንፈሳዊ ሕይወቴ በእጅጉ ደክሚያለሁና መፆሜንም እንጃ" ላለኝ አንድ ወንድሜ.. ምናልባት ለሌሎችም ከጠቀመ በሚለው:
ምናልባት ላታስተውለህ ትችላለህ ግን ወደ መንፈሳዊ ሕይወት ለመመለስ አንድ ጥሩ ስቴፕ ላይ ነህ.. ይህም መድከምህን አምነሃል.. ሰው መድከሙን ካላወቀ ብርታትን አይናፍቅም.. ይህ ብቻ ሳይሆን በደከምክባቸው በእነዚህ ወቅቶች ላይ ራስህን መግዛትና ከኃጢአት መራቅ ሲያቅትህ አስተውለህ ይሆናል.. ይህም ከጌታ ተለይተህ ብቻህን ማሸነፍ እንደማትችል ያስተምርሃል ስለዚህም ደግሞ ወደ መንፈሳዊው ሕይወት ስትመልስና የመንፈስ ፍሬዎች ሊታዩብህ ሲጀምሩ እንዳትኮፈስና ሌሎች ደካሞች ላይም እንዳትፈርድ ያደርግሃል.. ምክንያቱም አንተም ያሸንፈከው ኃይልን በሚሰጥህ በክርስቶስ እንጂ በራስህ እንዳልሆነ ታውቀዋለህና.. ስለዛ ለእነርሱም እንድትጸልይላቸው ያደርግሃል.. ይህንን የምልህ አሁን ያለህበት ሁኔታ ወደ መልካም ጤናማ መንፈሳዊ ሕይወት የምትገባበት መነሻህ ነውና ነው..
ይህ እንዲሆን ግን ወደ ክርስቶስ መስቀል መመልከት ተገቢ ነው.. ጌታ የሞተው ማንም ሰው እንዳይጠፋ ነው.. የጌታችን ደም ከኃጢአት ሁሉ የሚያነፃና የሚያድስ ነው.. ግን ደግሞ አስበው በሆነ ውድቀት ውስጥ ስለሆንክ አይ ይቅርብኝ ወደ አምላኬ አልመለስም ብትል ጌታን ምን ያህል እንደምታሳዝነው.. ኃጢአት ስትሰራ ታሳዝነዋለህ አልመለስም ስትል ግን ሞቱን ከንቱ ታደርገዋለህ..
ወደ መስቀሉ የምንመለስበት ቀኑም ሰአቱም አሁን ነው.. ለእኛ ያለን አምላካችን ብቻ ነውና ወደ እርሱ እንጠጋ በእርሱም እንኑር..
በጌታ ፊት ቁምና ለእኔ ያልከኝን ለእርሱም ንገረው: "ጌታ ሆይ ልቤ ደንድኗል ዘልዛላ ሆኚያለሁ.. ሁሉም ነገር ከብዶኛል" በለው.. አያይዘህም "ጌታ ሆይ መልሰኝ እኔም እመለሳለሁ.. ዘመኔን እንደ ቀድሞ አድስ" በለው.. "ያለ አንተ ምንም ማድረግ አልችልምና ጌታ ሆይ ከአንተ ጋር መኖርን ስጠኝ" በለው..
በዚህ እምነት ውስጥ ሆነህ አጫጭር ጸሎቶችን ጸልይ.. ለምሳሌ አባታችን ሆይን እና ደግሞ በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ሆነህ ዎክ እያደረክም ሊሆን ይችላል ይህችን አጭር ጸሎት እየደጋገምክ ጸልይ: "ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ"
"ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ"
ድንግልንም ንገራት: "በልጅሽ በኢየሱስ መንገድ እንድሄድ እርጂኝ" በላት ትረዳሃለችም
@Apostolic_Answers
ግጭቱ ያለው በምእመናኑ መካከል ሳይሆን በምእመናኑ እና "ሕግ አስከባሪ" ተብለው በተቀመጡት መካከል እንደሆነ ነው እያየን ያለነው..
በኦሮሚያ ክልል ያለው ምእመኑ ግን እንዴት ደስ እንዳለኝ የምር.. እነ ይቴ ጭሷን(አሁን ጰጵሳለች አሉ😁😁 አንተ እዚ ፍዘዝ ይቴ ጰጵሳለች) ሕዝቡ አንቀበልም ብለው እየሞቱ ነው..
ስለዚህም ሕዝብ ከሕዝብ ጋር አይደለም ግጭቱ
@Apostolic_Answers
ንስሐ መግባት እንዲሁ "ኃጢአት ሰርቻለሁ" ብቻ ማለት ሳይሆን እያንዳንዱን ኃጢአታችንን መዘርዘርም ይጠይቃል..
ሰው ታምሞ ወደ ህክምና ሲሄድ እውነተኛ ፈውስን ማግኘትን ከፈለገ "ታምሚያለሁ" ብቻ ሳይሆን የሚለው እያንዳንዱን የህመሙን ምልክቶች ይዘረዝራል..
እንዲሁ ደግሞ በመንፈሳዊ ህመም ውስጥ ሆነን ከኃጢአት በሽታ መፈወስን የምንፈልግ እኛ እያንዳንዱን ኃጢአታችንን በመዘርዘር ከሁሉም ልንፈወስ ይገባል..
እና ደግሞ ንስሐ መግባት አያስፈራም.. እግዚአብሔር ያውቀዋል ከእኛ የሚፈልገው ኃጢአት ማድረጋችንን አምነን እንድንናዘዝና ይቅርታ እንድንጠይቀው ነው..
የንስሐ አባቶቻችን ሰዎች ናቸው እነሱም ራሳቸው ፈተናን ያውቁታል ይወድቃሉ ይነሳሉ ስለዛ ምንም ልንፈራ አይገባም
ባይሆን ንስሐ የምንገባው ጌታን ስለምንወደው ከእርሱ ጋር አብረን እንድንኖር ስለዚህም ከቅዱስ ምስጢርም እንድንካፈል ነውና ከንስሐ በሁዋላ ወደ ቅዱስ ቁርባን run🏃🏃♀️
@Apostolic_Answers
የጠቅላይ ሚኒስቴሩን ንግግር አሁን አይደል እንዴ የምሰማው..
መጀመሪያ ነገሩ አናደደኝና ትንሽ ቆይቶ ግን አሳቀኝ.. ምንም ideaው በሌላቸው ነገር ላይ ነው እንዴ የሚናገሩት.. ሕግ ማስከበሩ ላይ ብቻ ይበርታ መንግስት እንጂ የራሷን ጉዳይማ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ይተውላት..
ምን ጉድ ነው ጋይስ.. ማለቴ መግለጫው😁😁
@Apostolic_Answers
ተወዳጆች እንግዲህ እስቲ ደግሞ ልናስቸግራችሁ ነው..
1. ከEnglish ወደ አማርኛ አጠር አጠር ያሉ ጽሑፎችን በመተርጎም ልታግዙን የምትችሉ ልጆች ካላችሁ ብታሳውቁኝ እንደው ደስተኛ ነኝ.. ያው ጽሑፎቹን እኛው ነን የምንሰጣችሁ..
2. እንዲሁም ደግሞ ከአማርኛ ወደ ኦሮሚፋም መተርጎም የምትችሉ ልጆች..
3. ወደ ትግረኛም ልትተረጉሙ የምትችሉ
ተዘጋጁ እስቲ በቅርቡ በውስጥ እንድታወሩኝ አደርጋለሁ
ያው ክርስቲያን ወንድም እህቶች ብቻ
@Apostolic_Answers
ቤተ ክርስቲያን ምን ትላለች ነው ቁም ነገሩ
https://vm.tiktok.com/ZMY8ub8WM/
ሦስቱ የኃጢአት ደረጃዎች
መዝ 1: 1
https://vm.tiktok.com/ZMYjMDLJc/
ኧኸ ኧኸ.. ይኸው እኛ ደብር አሁን ምሽት ላይ ብዙ ሰው መጥቶ ጸለይን አሁን ደግሞ ጧፋችንን ለኩሰን ልንዘምር ነው.. በመከራ ውስጥ ሆነን እንዘምራለን..
ደግሞኮ ስንጸልይ ስለራሳችን ብቻ አይደለም.. ስለ ሚያሳድዱንም ጭምር እንጂ.. ምክንያቱም ባለማወቅ(ክርስቶስን) ይህንን ያደርጋሉና..
@Apostolic_Answers
6:00
ተንስኡ ለጸሎት
ይህች ሰዓት ጌታችን ኢየሱስ የተሰቀለበት ሰዓት ናት.. አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር ይሰቀል ዘንድ እርሱ ስለሁላችን ተሰቀለ..
ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ጌታን እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
የምንችል ደግሞ ወደ ቅዳሴ እንሂድ
በመንግስት ሥራ ውስጥ ላሉ ክርስቲያን ወንድም እህቶች
https://vm.tiktok.com/ZMYYpRcDT/
የእመቤታችን ንጽሕናና ቅድስና ሔዋን ከመወደቋ በፊት ያላትን ንጽሕና የሚያሳይ ነው.. ምንም አይነት እንከን የማይገኝበትም እንደሆነች አምናለሁ.. ምንም እንኳን አንዳንድ ታላላቅ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይህንን በማይደግፍ መልኩ የጻፉ ቢኖሩም(እሱን ወደ ፊት ሰፋ ያለ ነገር አዘጋጅቼ አሳያችሁዋለው) በጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ያለው እምነት ግን እመቤታችን ከፍጥረታት ተወዳዳሪ ሊገኝላት የማትችል ናት..
ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩግ ከእመቤታችን ንጽሕና ጋር በተያያዘ እንዲህ ይላል፡
"በትሕትናዋ፣ በንጽሕናዋ፣ በቅድስናዋ እና መልካም በሆነው ፈቃድዋ በእርሱ ተመረጠች.. ከእርሷ የተሻለ ቢኖር ያንን ደግሞ በመረጠ ነበር.."
(homilies concerning the blessed Mary: homily 1: sec 6 on the annunciation)
ታድያ ግን ያዕቆብ ዘስሩግ ይህንን ሲናገር ከሌሎችም ጋር በማነጻጸር እሷ የተሻለች የሆነችው ለእግዚአብሔር ባላት መታመን እንደሆነ ያሳያል እንጂ ገና ከጅምሩም ለእርሷ ከሌሎቹ የተለየ ሥጋ አስቀድሞ ስለተዘጋጀላት ወይም ደግሞ ከአዳም ዘር ተለይቶ አስቀድሞ ለብቻዋ የቀረ ሥጋ ሆኖ እንዳልሆነ ግልጽ ያደርገዋል.. እንዲያማ ቢሆን ንጽጽሩንስ ምን አመጣው ገና ከጅምሩ የተለያየ ሥጋ ተሰጥቷቸው ያስብላል..
ለማንኛውም እመቤታችን አሁን ለእኛም ምሳሌ የምትሆነን ከእኛው ጋር ተመሳሳይ በመሆኗ ነው.. ካልሆነ ግን እንደኛው ያለ ሥጋን ካልያዘች በመንፈሳዊ ሕይወታችን ውስጥ እንደ ምሳሌም ልንይዛት አንችልም..
@Apostolic_Answers
ልክ እንደ ቤተ መንግስት ከአማራም ከኦሮሚያም ከትግራይም ከሌሎችም ተብሎ እየተቆጠረ ጳጳሳ ይኮናል እንዴ..?? ሰማያዊቷን ቤተ ክርስቲያን የምታገለግለው ሰማያዊ ሆነህ ብቻ እንጂ ኦሮሞ ወይም አማራ ስላልክ አይደለም.. ኧረ እንደው ሼም ነው እንዲህ ባልን ቁጥር የመንግስት አካላት እንጂ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች እንዳልሆንን ያስሳብቅብናል.. ጳጳስትን እኮ የሚሾመው መንፈስ ቅዱስ ነው አንተ ማን ነው በሥጋ ዘር መዳቢ አድርጎ የወከለህ..??
በኦሮሚፋ አልተሰበከም ያለ በቃ መስበክ መስራት እኮ ነው.. እንዲሁ ሽፋን የሚመስል ነገር ብቻ ማንሳት ምንድን ነው..?? መቼስ አትስበክ የሚል የለም..
ሁሉም ነገር ፖሊቲካ ይመስላል.. በፖለቲከኞች መንፈስ ውስጥ ተሆኖ ቤተ ክርስትያንን መምራት አይቻልም..
ቤተ ክርስትያንን የሚመራው እኮ የሆነ ክልል መንግስት ሳይሆን መንፈስ ቅዱስ ነው.. በዚህ ጊዜ የትም አካባቢ ያለ ክርስትያን በጸሎትም በሃሳብም አንድ ሊሆን ይገባዋል..
እንዲያ ከሆነ ደግሞ እኔ ያን ያህል ትልቅ ችግር እንደሚፈጠር አይሰማኝም.. መንጋውን የሚያውከው ይለይና ልባም የኦሮሚፋ ተናጋሪ ወንድሞቻችንና አባቶቻችን በቋንቋውም የበለጠ ወደ መስራት ይገባሉ..
ጌታ ሕዝቡን ይጠብቅ
@Apostolic_Answers
#ኢየሱስ የሚለውን ስም ስንጠራ እንዲሁ በአንደበታችን የማለት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በልባችን ይዘነው በማስተዋል ውስጥ ሆነን ከእኛ ጋር እንዳለ እያሰብን በእምነት እንጥራው..
@Apostolic_Answers
ጌታ ራሱን ያቀረበው የት ነው..??
https://vm.tiktok.com/ZMYRCYoyF/
🚩 በቤተክርስቲያን መጻሕፍት ውስጥ የቤተክርስቲያን አባቶች ከክርስቶስ፥ ከቅድስት ድንግል ማርያም እና ከቅዱሳን ጋር ተያይዞ ትክክለኛ እምነት በሌለው ሰው ላይ ያስተላለፉት እርግማን ይገኛል።
ተሃድሶዎችና ሌሎች የቤተክርስቲያን ተቺዎች ግን እነዚህን ቃላት በመጥቀስ "..የኦርቶዶክስ መጻሕፍት ተራጋሚ ናቸው፥ ለድንግል ማርያም ስዕል ያልሰገደ ይጥፋ በማለት ይራገማሉ፥ በእርግማን የተሞሉ መጻሕፍት ናቸው፥ ተራጋሚ መጻሕፍት እንዴት እውነት ሊሆኑ ይችላሉ...ወዘተ" ሲሉ ይሰማሉ። ይህንንም ሀሳብ እንደ ትችት ያቀርቡታል
የእግዚአብሔር ቃል ግን እንዲህ ይላል 👇
"ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን #የማይወድ ቢኖር #የተረገመ ይሁን። ጌታችን ሆይ፥ ና።"
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 16:22)
"ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል #የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ #የተረገመ ይሁን።"
(ወደ ገላትያ ሰዎች 1:8)
ታዲያ....መጽሐፍ ቅዱስንም በእርግማን የተሞላ ተራጋሚ መጽሐፍ ነው ሊሉት ነው??? 🤔🤔
ከጌታ በራቅን ቁጥር.. ከዚህ ቀደም አልፈን የመጣናቸው አለማዊነት ሁሉ ይናፍቁንና ይማርኩን ይጀምራሉ..
እንደ ምህረቱ እንጂ እንደ እኛ ስንፍና አይሁንብን..
ከጌታ ሊያርቁን የሚችሉትን ነገሮች ሁሉ ከእኛ እንለይ..
መልካም ሰንበት(የጌታ ቀን)
@Apostolic_Answers
እንኳን አደረሳችሁ በድጋሜ ተወዳጆች..
ያው ልብሴን እንድታዩት አይደለም🤭🤭
ቆይ ግን ፎቶ ላይም ላስረዳ ነው እንዴ ምንድነው እጄ😁😁