በክርስትና ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ሐዋርያዊ መልሶችን ለማቅረብ የምንሞክርበት ቻናል.. YouTube፡ https://m.youtube.com/@apostolicanswers1
ሮሜ 8 34 በሌሎች ቋንቋዎች..??😬😬
https://vm.tiktok.com/ZMYbjnydK/
“አብ የበላይ አስተዳዳሪ”
አ.መ.ት
https://vm.tiktok.com/ZMY4r6QUn/
አብ አምላክ
ወልድ አምላክ
መንፈስ ቅዱስ አምላክ
ከሆነ.. እንዴት ታድያ 3 አምላክ አያስብልም..?? ለሚለው
https://vm.tiktok.com/ZMYXMM1jL/
ሰፈር ሰንበት ት/ቤት ውስጥ ትንሽ ነገር አስተምርልን ብለውኝ እያስተማርኳቸው ነበር.. እና በጣም ጸዴ ነበር እኮ
ግን
መሃል ላይ "ጋይስ" አልኳቸው😭😭
ላይቭ ነን
https://www.youtube.com/live/Wa_fz1rQpm0?feature=share
ቅድስት ሥላሴ በፕሮቴስታንቱ🤦♂️🤦♂️
https://vm.tiktok.com/ZMYx7E6pB/
ላይቭ ነን.. ዕብራውያን 8
https://www.youtube.com/live/FG39RGNJQdA?feature=share
ላይቭ ነን
https://www.youtube.com/live/ryxJGgygW7c?feature=share
schedule ነው ደግሞ ለማታ 3፡00
https://www.youtube.com/live/ryxJGgygW7c?feature=share
ከክርስቶስ ጋር በተያያዘ የተነሱ ጥያቄዎችና አጫጭር መልሶች
https://vm.tiktok.com/ZMYmtkdq1/
Maximilian Kolbe የተባለ ካቶሊክ ካህን "ማርያምን እጅጉን ወደድኩ ብለህ አትስጋ ልጇ ኢየሱስ ከወደዳት በላይ ልትወዳት አትችልምና" ይላል..
በጣም ደስ የሚል አባባል.. ግን ደግሞ ይህ ለሁላችን የሚሆንም ነው.. ማንም ሰው ቢሆን ምንም ያህል ቢወደን ክርስቶስ የወደደንን ያህል ግን ሊወደን የሚችል የለም..
ሰው አድርጎ ፈጥሮናል.. በወደቅን ጊዜ ደግሞ አምላክ ሲሆን የባርያን መልክ ይዞልናል.. የባርያን መልክ ይዞ ደግሞ የአይሁድን ምራቅ ተቀብሏል.. በጥፊ ተመቶልናል.. ለመስቀል ሞት እንኳን የተዘዘ ሆኗል.. ይህ ሁሉ ስለ ማን ነው..??
በሃይማኖተ አበው የእለ እስክንድሮስ ክፍል ላይ እንዲህ ይላል:
"እግዚአብሔር ቃል ወደዚህ አለም ይመጣ ዘንድ ከንጽህት ድንግል ማርያም ሥጋን ይዋሃድ ዘንድ ምን አተጋው..??
በጨርቅ ይጠቀለል ዘንድ፣ በበረት ይጣል ዘንድ፣ ከድንግል ጡት ወተትን ይጠባ ዘንድ፣ በዮርዳንኖስ ይጠመቅ ዘንድ ምን አተጋው..??
ሕግ አፍራሽ ጲላጦስ ይዘብትበት ዘንድ በመስቀል ይሰቀል ዘንድ በመቃብር ይቀበር ዘንድ በሦሥተኛውም ቀን ይነሳ ዘንድ ምን አተጋው..??
በፍዳ ተይዘን የነበርን እኛን ያድነን ዘንድ 👉ለእኛ ብሎ አይደለምን..??"
✝️እና ምን..??
እኛም ደግሞ አምላካችንን እንውደደው.. እርሱ አስቀድሞ ወድዶናልና
1ኛ ዮሐንስ 4
19፤ እርሱ አስቀድሞ ወዶናልና እኛ እንወደዋለን።
መልካም ሰንበት እናንተ የክርስቶስ ምርጦች እና ውዶች😊🤗
@Apostolic_Answers
+ሰውን መውደድና እግዚአብሔርን መፍራት +
ሰውን መውደድም ይህ ነው፡ በለመኑን ጊዜ ቸል ሳንል ካለን የተቻለንን ሁሉ እናደርግላቸው ዘንድ ነው፣ ሲቸገሩም ከእነርሱ ጋር እንቸገር ዘንድ ነው፣ ሲያዝኑም ከእነርሱ ጋር እንድናዝን ፣ እኛን ሲበድሉም ቂም እንዳንይዝባቸው ነው ። ፍጹም ሰውን መውደድም በእውነቱ ይህ ነው፤ ጌታችን “ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትሹትን እናንተም እንዲሁ አድርጉላቸው እናንተ የምትጠሉትን ለጓደኛችሁ አታድርጉ ” እንዳለ ማቴ 7፡12
።
እግዚአብሔርን መፍራትም ይህ ነው ፡ ሰይጣን ከኃጢአት ተግባራት ባሳሰበን ጊዜ እነሆ እግዚአብሔር ይመለከተናል ካልን ነው ይህን ብለንም ማድረግ እየቻልን ከተውነው በእኛ ላይ ያለ እርሱን መፍራት ይህ ነው ። ዝሙት እንደማዕበል በእኛ ላይ ቢነሣ፣ ቁጣ በአንደበታችን እንደእሳት ቢንቦገቦግ በልባችን እንደመርዝ ቢሆን በጠላቶቻችን ላይም ማድረግ እየቻልን ከተውናቸው ስለ እግዚአብሔር ብለንም መልካምን ካደረግንላቸው በእውነትም እርሱን መፍራት በእኛ ላይ አለ። የዚህን ዓለም ደስታ ባገኘን ጊዜ እንዳያሰጥመን ከሸሸን፣ የሚጣፍጥ መጠጥ ባገኘን ጊዜም እንዳያሰክረን ከተውነው፣ ኃጢአትን ሲሠሩ በተመለከትናቸው ጊዜ ከዘመዶቻችን ከወዳጆቻችን ከተለየን እርሱን መፍራት ይህ ነው።
...ሃይማኖት፣ ፍቅር ፍርሃት ያለው ሰው በፈሳሽ ውኃ ዳር እንደተተከለች፣ ፍሬዋንም በየጊዜው እንደምትሰጥ ፣ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል መዝ 1፡3
።
በፈሳሽ ውኃ ዳር የበቀለች የተባለችው ሃይማኖተኛ ሰው ነው ይህን ዛፍ የሚያጠጣ ውኃም ሃይማኖት ነው። የዛፉን ሁለንተና የሚጋርደው የማይረግፈው ቅጠልም ለሚለብሱት ከእርቃናቸው የሚሰውራቸው እግዚአብሔርን መፍራት ነው ከዚህ ዛፍ የሚገኘው ፍሬም እግዚአብሔርንና ሰውን መውደድ ነው። የዚህን ዛፍ ፍሬ እግዚአብሔር ከበረድ ከወፍ ይጠብቅ ፣ ቅጠሉንም ከውርጭ ከሙቀት ይጠብቅ ፣ ዛፉንም ከሚቆርጥ ከእሳት የጠብቅ ።
ከሆዱ የሕይወት ውኃ ምንጭ የሚፈልቅበትም ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በውስጡ የበቀለው ዛፍም አዳም ነው፣ የለመለመው ቅጠሉም ኦሪታውያን ናቸው፣ ያማረ ፍሬውም ወንጌላውያኑ ናቸው። ከአብ ዘንድ ለተገኘ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ለመነጨ ለዚህ ውኃ ለክርስቶስ ምስጋና ይገባል ። ዓለምን ሁሉ ለፈጠረ ለእርሱም ከአባቱ፣ ከመንፈስ ቅዱስም ጋር ምስጋና ይግባው። አሜን
ርቱዐ ሃይማኖት ንባብ ዘኒቆዲሞስ ላይ የተወሰደ
ኢየሱስ ምንም ተአምር ማድረግ አልቻለም..??
ማርቆስ 6:5
https://vm.tiktok.com/ZMYV6hQxM/
እመቤታችን የአምላክ እናት.. እንዴት..??
https://vm.tiktok.com/ZMYXGnnfP/
መውደድም ሐዋርያው “እግዚአብሔርን እወድደዋለሁ የሚል፤ ትዕዛዙንም የማይጠብቅ ሐሰተኛ ነው” [1ዮሐ4፡20] እንዳለው ትእዛዙን መፈጸም ነው ትእዛዙን የማይፈጽም በእውነትም ሐሰተኛ ነው ...
እርሱን መውደድስ ይህ ነው፡ ስለስሙ ሰውነታችንን አሳልፈን ከሰጠን ነው፤ እርሱን መውደድስ ፡ ዓለምንና በውስጡ ያለውን ከናቅን ነው ። እርሱን መውደድስ ከትእዛዛቱ እንዳንሰናከል ነው ። እርሱን መውደድስ መጾም፣ መጸለይ ፣ መትጋት ማገልገል፣ መታቀብ ፣ ዝምታን ገንዘብ ማድረግ ናቸው ። እርሱን መውደድስ በዓላቶቹን ሰንበታቱን ማክበር ፣ እርሱን ብቻ ማምለክ፣ ትእዛዝቱንም መጠበቅ ነው ፤ ከዚህ ሌላ ግን የለም። ትእዛዙን ካልጠበቅህ እግዚአብሔርን በምን ትወድደዋለህ ? ተራቁቶ ታለብሰዋለህን? ተርቦስ ታበላዋለህን? ተጠምቶስ ታረካዋለህን ? እርሱ “የላምን ስጋ አልበላም ፤ የፍየልን ደምም አልጠጣም ዓለም በመላው የእኔ ነው፤ ለእግዚአብሔር የምስጋናን መሥዋዕት ሠዋ፤ ጸሎትህንም ለልዑል እግዚአብሔር አቅርብ” [መዝ 49፡13] ብሏልና... በሌላ ቦታም “እስራኤል ሆይ ታመልከው፣ ታፈቅረው፣ ትፈራው ዘንድ ነው እንጂ ከዚያ በቀር እግዚአብሔር ከአንተ ምን ይሻል? ”[መዝ 49፡23] አለ ።
ርቱዐ ሃይማኖት ንባብ ዘገብርኄር ላይ የተወሰደ
https://www.youtube.com/live/ryxJGgygW7c?feature=share
Читать полностью…ዘፈን ኃጢአት ከሆነ ኳስ ማየትስ..??😀😀
https://vm.tiktok.com/ZMYHhEfdo/
ዘፈን ኃጢአት ነው..??
ገላትያ ላይ የተጠቀሰውስ "ዘፋኝነት" የምር ሰዎች የሚሰምትን ዘፈን ሁሉ የሚመለከት ነው..??
https://vm.tiktok.com/ZMYuG21Gv/
የጌታን መምጣት የምንጠብቀው በጭንቀት ወይስ በጉጉት..??
https://vm.tiktok.com/ZMYmknaqt/
ሙስሊሞች የክርስትናን ትምህርት ለመተቸት ሲሞክሩ መመልከት አዲስ ነገር አይደለም.. የሚያሳዝነው ደግሞ በኢትዮጵያ ባለችው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እስልምና ላይ ብዙም እንዳልተሰራ ግልጽ ነው.. ስለዚህም ለጊዜው አንዲት ነገር አስቢያለው..
እስልምና ላይ መስራት የምትፈልጉ ወይም የጀመራችሁ ወንድሞች ወይም እህቶች ሰብሰብ እንበልና አንዳንድ ሥራዎችን ለመስራት ብንሞክር ብናጠና ምናምን..
ብታሟሉ መልካም ነው ብዬ የማስባቸው
1. የምርም እስልምና ላይ የመስራት ፍላጎቱ ያለው
2. የክርስትና ትምህርት ላይ መሠረታዊ እውቀት ያለው
3. ሙስሊም ወንድም እህቶቹን በመሳደብ ወይም በማንቋሸሽ ሳይሆን በእግዚአብሔር እንደተወደዱ ወንድም እህቶቹ እያየ በፍቅር በመስራት የሚያምን
4. በክርስትና ሕይወቱ ውስጥ የሚጸልይ የሚያስቀድስ(በጣም አስፈላጊ)
5. ኢንግሊዘኛ ቋንቋን አንብቦ በደንብ መረዳት የሚችል(ያው fluent መሆን አይጠበቅባችሁም)
@aklil1 ላይ "እኔ አለሁ" ብቻ ብላችሁ ጻፉልኝ አወራችሁዋለው😉😉