ተአምረ ማርያም ላይ በሰራሁት ላይ አንዳንድ ለማጣመም ለሞከሩ ፕሮቴስታንቶች.. እስቲ ጠረጴዛውን ወደ እነርሱ እናዙረው..
https://vm.tiktok.com/ZM2m3s6jV/
"የተራበ ሆድ ለምግብ እንደሚቸኩል
ክርስቶስ ደግሞ ይቅር ለማለት ይቸኩላል"
አርጋኖን ዘእሁድ 2: 7
አይ መታደላችን.. እንደ ኢየሱስ ያለ ሩኅሩኅ ይቅር ባይ አምላክ ባይኖረን አልቆልን ነበር የምር..
ችግሩ ደግሞ የስግጥናችን ስግጥና ይቅርታ ለመጠየቅ ንስሐ ለመግባት አንነሳሳም ብዙ ጊዜ..
ንስሐ እንዳለ ሆኖ ስትጸልይም : "አባ በድያለሁ ይቅርታ አድርግልኝ.." በለው..
መልካም ቀን😊🤗
ኧ ምርጦች.. ዛሬ ልንጀምር ነው የግእዝ ንባብ ምናምን.. እና በጣም ደስ ብሎኛል እኔ ራሱ በደንብ ትኩረት ሰጥቼ ልማር ነው..
ስለዚህም ዛሬ ማለትም አርብ ከምሽቱ 2:30 መግቢያ ይኖረናል.. ያው ላይቭ ነው
የት..?? እዚው ቻናል ላይ..
@Apostolic_Answers
መንፈሳዊ ነገር ላይ ትንሽ መስራት ስትጀምሩ የሚደብረው ፓርት ምን መሰላችሁ..
ቤት ውስጥ "አባ" ምናምን እያሉ ሙድ ለመያዝ ይሞክራሉ እና እኔ ደግሞ ቤት ውስጥ ስሜ አቢ ነው እና አስቡት "አባ አቢ" ስባል😭😭 አባቢ ሎል
እና ደግሞ ዛሬ በጠዋቱ ከቅዳሴ ተመልሰን ስለ ገነት እና ስለ ሲዖል እያወራን አንዷ ምን ብላ ሙድ ብትይዝብኝ..??
"እኔ እንደሆነ የአቢ ጺም ላይ ተንጠልጥዬም ቢሆን ገነት እገባለሁ"
😭😭 ኡፍፍ
የምር ሙድ አትያዙብን😁😁
https://youtu.be/b8t-2LzU5uE
ዩትዩባችንን እስቲ የተወሰነ መንቀሳቀስ እንዲጀምር እናድርገው እና በሰፊው በአዳዲስ ኮንተንቶች ብቅ እንላለን👍👍
ኧ እናንተ የእግዚአብሔር ምርጦች(ኅሩያነ እግዚአብሔር)..
ግእዝ ቀላቀልኩባችሁ..?? አይዞን እንግዲ ልመዱት🤭🤭
ለማንኛውም መልእክተ ዮሐንስ.. ውዳሴ ማርያም እና መዝሙረ ዳዊት በግእዝ ልንማር ነው እዚው ቴሌግራም ላይ በሳምንት ሦስት ቀን..
መማር የምትፈልጉ የገብረ ሥላሴ መዝሙረ ዳዊት መጽሐፍ በአክሱም ማተሚያ ቤት የታተመው ቢኖራችሁ መልካም ነው..
ቀኑን አሳውቃችሁዋለው.. በዚው ሳምንት እንጀምራለን
ግእዝ መጣንልሽ🥴🥴
@Apostolic_Answers
ዛሬ ከአንድ ጉዋደኛዬ ጋር ነበርኩ እና ሚስቱም(gf) አብራው ነበረች እና ምግብ እየበላን ነበር..
ሙሉ ሰዓቱን እሱ እሷን እያጎረሰ እሷ ደግሞ እሱን እያጎረሰችው ነበር.. አንድም እንኳን ለራሳቸው አልጎረሱም..
ምንድን ነው እንዲ መጃጃል..?? ኧረ ወዲያ
.
.
.
.
.
እኔን ግን መሃል ቤት አስቡኝ😭😭 ፑር አክሊል
በኢየሱስ ምልጃ(ጸሎት) እና በቅዱሳን ምልጃ መካከል ያለው መሠረታዊ ልዩነት
ቅዱሳን በቃ እንደኛው መጸለይ ብቻ ነው.. ጸልየው እግዚአብሔር ፈቃዱ ከሆነ ልመናቸው ተቀባይነት ይኖረዋል.. የእርሱ ወዳጆች ናቸውና
የጌታ ጸሎት(ምልጃ) ግን ከደም ጋር የሆነ ነው.. ስለዚህም ዋጋውን እኔ ከፍያለሁ የሚል ሥልጣናዊ ንግግር እንጂ እንደ እኛ ምላሽን የሚጠብቅ አይደለም..
ሌላው ሁለተኛው ትልቁ ልዩነት.. የቅዱሳን ምልጃ ሰው ብቻ እንደ መሆናቸው የሚያቀርቡት ልመና ሲሆን..
ጌታ ኢየሱስ ግን ሲጸልይ ሰው ብቻ አይደለም ይልቁንም አምላክም ነውና ጸሎት ተቀባይም ስለሆነ ሥልጣናዊ ነው.. ስለዚህም እርሱን ሦስተኛ ወገን አማላጅ አያስብለውም..
@Apostolic_Answers
ንስጥሮስ ወይስ ንስጥሮሳዊ ሊቀጳጳስ..??
ተአምረ ማርያም[48] ላይ የሰራሁትን ቪዲዮ ተከትሎ አንድ ወንድሜ ያ የተአምር ክፍል የታሪክ ተፋልሶ እንደሌለበት አድርጎ ፌስቡኩ ላይ የጻፈውን በግሩፓችን ላይ አስቀምጠውት አየሁ..
ያው ወዳጄ ቀጥታ ፌስቡኩ ላይ ስለሆነ የፖሰተው እኔም እዚው ላይ ትንሽ ነገር ልበልበት እሱ ከሰጠው አሳብ ጋር በተያያዘ፡
የወንድሜ አሳብ በአጭሩ እንዲህ የሚል ነው፡ —ክፍሉ ላይ "ንስጥሮስ" የተባለው ራሱ ንስጥሮስ ሳይሆን ይልቁንም ቀደም ሲል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ዘመን የነበረ ሌላ ንስጥሮሳዊ አሳብ ያለው ሌላ የቁስጥንጥንያ ሊቀጳጳስ ነው.. ንስጥሮስ መባሉም ከምንፍቅናው መመሳሰል ነው—
መልካም 3 ነጥቦችን ላስቀምጥ፡
1. ይህ አሳብ ምንም ዓይነት ማስረጃ የሌለው የራሱ የወንድሜ ግምታዊ አሳብ ብቻ ነው
2. ይህ የተአምር ክፍል ከአባ ጊዮርጊስ መጽሐፈ ምስጢር ጽሑፍ ላይ የተካተተ እንደሆነ ጽሑፉ ያመላክታል.. እናም ይኸው ታሪክ በመጽሐፈ ምስጢር የጌና ንባብ(ምዕራፍ 4) ላይ የተቀመጠ ሲሆን "ንስጥሮስ" ተብሎ የተጠራው ግለሰብ ራሱ ንስጥሮስ እንደሆነ ያስቀምጣል፡
ማስረጃ..??
እዛው መጽሐፈ ምስጢር ክፍል ቁጥር 10 ላይ እንዲህ ይላል፡
"ከዚህ በኋላ ሁለት መቶ ኤጲስቆጶሳት ስለ እርሱ #በኤፌሶን ተሰበሰቡ ወደ ጉባኤያቸውም ጠርተው ስለ ስህተቱ ገሠጹት....... እርሱ ግን እምቢኝ አላቸው በመንፈስ ቅዱስ አፍ አንድ ሆነው #አውግዘው ከቤተ ክርስቲያን ለዩት..... በመንበረ ጵጵስናውም ስለ ሃይማኖት ቀናተኛ የሆነ የቤተ ክርስቲያንም ዓምድ የሆነ #መክስምያኖስን አስቀመጡት"
ከዚህ የምንወስደው ሁለት ነገር
ሀ. በኤፌሶን ጉባኤ የተወገዘው ራሱ ንስጥሮስ እንጂ ሌላ እንዳልሆነ እናውቃለን
ለ. በመንበረ ጵጵስናውም መክስምያኖስን አስቀመጡት ብሎናል.. መክስምያኖስ(St Maximianus) ደግሞ በቁስጥንጥንያ ራሱን ንስጥሮስን ተክቶ ሊቀጳጳስ የሆነ ሰው ነው [Fr shenouda ishak: christology and council of chalcedon, pg 55]
3. ሦስተኛውና የመጨረሻው ነጥቤ ግን ወንድሜ ያነሳው አሳብ "ተአምር ውስጥ ስህተት ልጊኝ አይችልም" ከሚል ቅድመ እሳቤ በመነሳት ይመስላል ምክንያቱም ትክክለኝነቱን ለማረጋገጥ ከመሞከር ይልቅ እንደው በቃ ልክ ነው ብቻ ብሎ ለሱ ደግሞ ግምታዊ አሳቦችን መስጠት ነው..
ደግሜ የምለው እንደዚህ ያሉ ነገሮች ክርስቲያኖችን ሊያስጨንቁ አይገባም.. የትኛውም የገድላት ሆነ የተአምራት መጽሐፍት የእምነታችን መሠረቶች አይደሉም.. ለኅይወታችን የሚጠቅሙ እንጂ.. ስለዛ ለኅይወት በሚጠቅሙን መንገድ እንጠቀማቸው እንጂ እንደው እዛ ላይ ባለ ጽሑፍ ሁሉ ብዙ አንጨናነቅ..
@Apostolic_Answers
"የሴትን ኃፍረት የሳመ አፈወርቅ ተባለ" የሚለው 👉የተአምረ ማርያም ክፍል ላይ 2 ሃሳቦች አሉኝ
https://youtu.be/dHQn1v9DgNs
"ለሰዎች ምንም የምትሰጠው ከሌለህ፣ ሞቅ ያለ ፈገግታ እና ደግ ቃል ስጣቸው.. ፍቅርን ስጣቸው ፣ ርህራሄን ስጣቸው፣ የማበረታቻ ቃል ስጣቸው፣ ልብህን ስጣቸው።"
አቡነ ሽኖዳ 3ተኛ
@TnshuaBetechrstian
👆👆👆👆
እናንተ ተወዳጆች እስቲ ተቀላቀሏቸው
የክርስትናን ትምህርት ለማስተማር የሚሞክር ሰው እነዚህ ላይ ቢያተኩር እላለሁ:
1. ቅዳሴ አለመቅረት እና የጸሎት ሰው
2. አንባቢ አንባቢ አንባቢ
3. ትምህርትን የሆነ ሰው ስለተናገረው ብቻ ማስተጋባት ሳይሆን ሐዋርያዊ ትውፊትን መከተል.. ይህም ከሐዋርያት ጀምሮ በቅብብሎሽ ውስጥ የሚታይ ትምህርት
4. ሁሌም ራስን ከፍ አድርጎ ለማሳየት ሳይሆን ክርስቶስን ከፍ ለማድረግና አካሉን ለማነጽ መስራት.. ስለዚህም ክርስቲያን ወንድም እህቶችን በማገዝ መንፈስ መንቀሳቀስ
5. ሌላ የሚያስተምሩ ክርስቲያን ወንድሞች ውስጣችንን የሚረብሹት ከሆነና በእነሱም ላይ ክፋትን(ምናልባትም envy) ካሰብን ጊዜ ሳናጠፋ ለዛ ሰው መጸለይ መጀመር.. ለዛ ሰው ስንጸለይ የቀደመው ስሜታችን ተለውጦ እንደውም መውደድ ማፍቀር እንጀምራለን
6. ስለ መምህራን ሁሉ መጸለይ..
7. 1, 2, 3 ይሰመርባቸው
"መጠን.."
ነገረ ማርያም ላይ ትልቁ ትምህርት ወላዲተ አምላክ የሚለው ነው..
ከዚህ ውጪ immaculate conception ምናምን የሚል ትምህርት ዘመን አፈራሽ በግለሰቦች የተጀመረ ነው..
አንዳንዴ ፕሮቴስታንቶችን ብቻ ሳይሆን አንዳንድ ክርስቲያኖችንም ስለ ቅዱስ ትውፊት ምንነት በሚገባ ማስተማር ያለብን ይመስለኛል
የሆነ ሰው ሁለት ማስተርሱን በአንዴ ሰራ ይልሃል.. ደስ ይላል በጣም
እና his last word:
“አሁንም ዓለም ከሚደርስበት አድርሽኝ: ሁዋላ ደግሞ በልጅሽ በወዳጅሽ በስተቀኝ እንድቆም አድርጊኝ" [አርጋኖን ዘረቡዕ 2:7]
አሜን በነገር ሁሉ የእመቤታችን አጋዥነት አይለህ.. እንኳን ደስ አለህ😊😊
ከዝሙት ለመራቅ አእምሮ ላይ መስራት የመጀመሪያው መንገድ ነው..
ለምሳሌ ከአንዲት ሕፃን ልጅ ጋር ብትተኛ ምንም ነገር ሊፈጠር አይችልም.. የማይፈጠርበት ምክንያት ደግሞ ገና ከጅምሩም አሳቡ አእምሮህ ውስጥም በጭራሽ ሊመጣ ስለማይችል ነው..
ሕጻናትን እንደፈለግህ ብታጫውታቸው ብታቅፋቸው ብትስማቸው ምናምን ከእነርሱ ጋር ሲሆን አንተም ውስጥህ እንደ እነርሱ ንጹህ ነው.. ስለዛ ምንም ነገር አታስብም..
ይሄንን ነገር ግን ካደገች ሴት ጋር ለማድረግ ብትሞክር መጨረሻህን አስበኸዋል..??😭😭
ተወው አታስበው አታስበው
ይህ የሚሆንበት ምክንያት ግልፅ ነው አእምሮህ እንደነዚህ አይነት ነገሮችን ማሰብ ስለሚጀምር ነው(ታሳፍራለህ ማን lol) ያው በዛ ደረጃ ሲጀመርም መጃጃል ባያስፈልግም በተለያዩ አጋጣሚዎች በሚኖሩን ግንኙነቶችም ግን እንዳንፈተን አእምሮዋችን እንደዚ አይነት ነገር ቀድሞ እንዳያስብ መከላከል.. ድንገት ቢያስብ ራሱ ወዲያውኑ ኢየሱስን መስቀል ላይ ሆኖ ማሰብ..
አንዳንዴ እንደዚ አይነት ነገር እንዳይፈጠር ከመፍራት የተነሳም ማሰብ ሊጀመር ይችላል.. እንዳልኳችሁ ኢየሱስን መስቀል ላይ ሆኖ አስቡት..
በጣም ከባድ ፈተና የዝሙት ፈተና ነው.. ጌታ ኢየሱስ ለሁላችንም ኃይልና ማስተዋልን ያድለን
@Apostolic_Answers
ቪዲዮ መስራት አዝግ ነገር ነው በጣም.. ጭራሽ ከፊታቹ ሰው ቆሞ ደግሞ በቃ ዝገት ነው..
እና የምለው ሲጠፋኝ😭😭
ከ 9 ወር አካባቢ በፊት ነበር😁😁