በክርስትና ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ሐዋርያዊ መልሶችን ለማቅረብ የምንሞክርበት ቻናል.. YouTube፡ https://m.youtube.com/@apostolicanswers1
ዌል ትንሽ ማብራሪያ ዋቄፈታ ላይ..
ቅዱስ ጳውሎስ የአቴና ሰዎችን እንዲህ አላቸው:
“..የአቴና ሰዎች ሆይ፥ እናንተ በሁሉ ነገር #አማልክትን እጅግ እንደምትፈሩ እመለከታለሁ። የምታመልኩትን እየተመለከትሁ ሳልፍ፦ #ለማይታወቅ_አምላክ፡ የሚል ጽሕፈት ያለበትን መሠዊያ ደግሞ አግኝቼአለሁና። እንግዲህ ይህን ሳታውቁ የምታመልኩትን እኔ እነግራችኋለሁ።”
[ሐዋ 17: 22]
እነርሱ የማይታወቅ አምላክ ብለው የሚያመልኩት ጣኦትን ሊሆን ይችላል ግን እውነተኛው እርሱ ሳይሆን ይሄ ነው ብሎ ያሳያቸዋል ማለት ነው..
የዋቄፈታ ሰዎችም ደግሞ አይተውትም ሆኖ ድምጹን ሰምተውት የማያውቁት አምላክ አላቸው.. የሁሉ ፈጣሪ እንደሆነም ያስባሉ.. እንግዲያውስ ይህ ዓይነት ክብር የሚገባው ለእውነተኛው አምላክ የኢየሱስ አባት ነው.. ልጁ ኢየሱስም ከአባቱ እንደመገኘቱ ከእርሱ ጋር አንድ የሆነ ጌታ ነው..
እና በዚህ አምነው አምልኮዋቸውን እንዲያስተካክሉ እና ከፈጣሪያቸው ጋር እንዲገናኙ ጥሪ ማቅረብ ማለት ነው.. ያው በፍቅር እና በትህትና..
@Apostolic_Answers
ዌል እንግዲህ thank you for the 300k እና ዛሬ ማታ መጽሐፈ ሩትን እንማራለን ጌታ ከፈቀደ
https://vm.tiktok.com/ZMhhPykSF/
ያለ ቤተ ክርስቲያን የመጽሐፍ ቅዱስን የእግዚአብሔር ቃልነት ማስረዳት አይቻልም..
Textual criticism የሚሰራው እደክታባት እስከተገኙበት ጊዜ ድረስ ብቻ ነው ከዛ በፊት ስላለው ጽሑፍ እርግጠኛ የሆንነው በመንፈሱ እና በሙሽራይቱ ነው..
ከጌታ የተቀበልነው ሃይማኖትም ሆነ ቃለ እግዚአብሔር ተጠብቀው የሚኖሩት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በመንፈስ ቅዱስ ነው..
የራሳቸውን ሰው ሰራሽ “ቤተ ክርስቲያናት” ለማቋቋም ሲሉ የጌታ ቤተ ክርስቲያን ጠላት ሆነው የተነሱ እነርሱ የጌታ መንግስት ጠላት ናቸው.. ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን የጌታ መንግስት ናት..
@Apostolic_Answers
የመጨረሻ እና መዝጊያ ቪዲዮዬ ለፕሮቴስታንቶች..
እና
ለሙስሊሞች ጥሪ.. እነሱን ደግሞ እስቲ እንይ😁😁
https://vm.tiktok.com/ZMhrr7L4b/
ፕሮቴስታንቶች 66 ቀርቶ ከዛ ውስጥ 1 እንኳን የማይሳሳት ብለው የሚያሳዩን መጽሐፍ አይኖርም በነሱ አካሄድ.. ካለ በሉ አሳዩን😊😊
እንዴት እንደሆነ ተመልከቱ ቪዲዮውን
https://vm.tiktok.com/ZMhMVFstw/
“አንተ ሽማግሌ” ምትሉኝ ሰዎች የኤድናሞል ዘመን ልጅ እንደሆንኩ እዩልኝ.. 2002 ላይ መሰለኝ ይሄ😁😁 በተለይ ጸጉሬ😭😭
Читать полностью…እኔ አልቻልኩም ከነዚ ወንድሞች ጋር🤣🤣
“ሳንታ ስለቱ ፤ ጠቅ ነው ውበቱ”😂😂
https://vm.tiktok.com/ZMhjsjCrt/
ቀለል ያለ ዲቤት አድርጋችሁም እንዲህ ስታለቅሱ ምትከርሙ ከሆነ ወይ ማትተዉት ዲቤቱን.. ሰለቸን እኮ ሎል
ተመልከቱ የፋላሲ መአት እና የኛም መልሶቻችን😁😁
https://vm.tiktok.com/ZMhjjGR8b/
አንድ የፕሮቴስታንት “ነቢይ” ጀለስ ነገር አለኝ እና ይመቸው “ገራሚ ሚስት እንደምታገባ ታይቶኛል” አለኝ😁😁 አልቻልኩም በቃ አንተ የምርም ነቢይ ነህ አልኩት ሎል..
እስቲ ዛሬ ማታ በጸሎታችሁ አስቡት የጌታ ጸሎትን እንዲጸልይ ነግሬዋለሁ.. “ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ” የሚለውን..
@Apostolic_Answers
ፕሮቴስታንቶቹ ከትንሽ እስከ ትልቁ በዲቤቱ በጣም እያለቀሱ ስለሆነ የተለቀቀ😁😁
https://vm.tiktok.com/ZMhFnAP3u/
የዛሬው ውይይት.. የምትችሉ ሰዎች የዛሬው ውይይት አያምልጣችሁ
https://vm.tiktok.com/ZMhNDuuqr/
አመሰግናለሁ ግን አይገባም ነበር በእውነቱ ከሆነ..
በጣም በተቻለኝ አቅም charitable ሆኜ ጌታ ኢየሱስ ብቻ ልብ ላይ እንደሚሰራ በማሰብ ተወያይቻለሁ..
ምናልባት ለጥያቄና መልስ ለመመለስ ፈቃደኛ አለመሆንንና ሰዓት መግደልን እዛ አስተውያለሁ እሱን አስተካክለን ሃሙስ ደግሞ እንገናኝ
ዛሬ ቅዳሴ ላይ ከተነበበው የወንጌል ክፍል
“እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም፤ በመንግሥተ ሰማያት ግን ከሁሉ የሚያንሰው ይበልጠዋል።”
[ማቴዎስ 11: 11]
1. ከሴቶች ከተወለዱ መካከል ከዮሐንስ የሚበልጥ የለም ተባለ.. ይህም ነቢይ እንደመሆኑ ነው.. ጌታችን ከየትኞቹም ነቢያት እንደማያንስ መሰከረለት ማንም የሚበልጠው የለም በማለት.. አንድም የዮሐንስን ለየት የሚያደርገው ነቢይነት እንደ ሌሎቹ ስለ ጌታ የተናገረ ብቻ ሳይሆን አይቶታልም.. ጭራሽ አጠመቀው..
2. “በመንግሥተ ሰማያት ግን ከሁሉ የሚያንሰው ይበልጠዋል” ተባለ ይህም እንዲህ ያለ ክብር ያለው ዮሐንስ ገና ወደ ሐዲስ ኪዳን ስላልተሸጋገረ በሐዲስ ከሁሉ የሚያንሰው ዮሐንስን ይበልጣል ተባለ.. ይህ በክርስቶስ የሆነውን ሐዲስ ኪዳን ክብር ያሳያል.. የክርስቶስ መሆን በራሱ በብሉይ ኪዳን ካለው ትልቅ ነገር ያስበልጣልና ነው..
ስለዛ ይህንን ክብር አስጠብቆ መኖር አስፈላጊ ነው.. በሕይወታችን ሁሉ የክርስቶስ እንደመሆናችን መኖር..
@Apostolic_Answers
አንድ ወዳጄ አሁን እንዲህ አለኝ:
ኢሬቻ የዋቄፈታ “ሃይማኖት” ሥርዓተ አምልኮ ነው ይባላል ያው የተለያዩ ባህላዊ ነገሮችንም ቢይዝም ማለት ነው..
እንዲያ ከሆነ እዚህ ቦታ ላይ ክርስቲያን ምናልባት ከተገኘ ሊገኝ የሚገባው:
“ይህ እናንተ ዓለምን የፈጠረ ‘ዋቃ’ የምትሉት የማታውቁት አምላክ የጌታችን ኢየሱስ አባት ነው.. ሁላችንን ከሞት ያድነን ዘንድ ልጁን ላከው.. እርሱም ስለሁላችን ሞቶ ተነሣ.. ስለዚህ እኛም ሞተን እንደማንቀር እርግጥ የሆነ ተስፋን ሰጠን.. ከሞት ታመልጡ ዘንድ በልጁ በኢየሱስ እመኑ..”
ብሎ ለመናገር መሆን አለበት አለኝ.. እንዴት ነው ያስማማል..??
@Apostolic_Answers
አሁን ወደተለመደው ትምህርታችን መመለስ እንችላለን ማለት ነው አይደል😁😁
https://vm.tiktok.com/ZMhrXY6T7/
መቃብር ቦታ አስተዋዋቂ ሆነ ደግሞ ይሄ ጀለስ😆😆 ግን መጨረሻዋን እዩአት ጥሩ መልእክትም አላት..
ፎሎው ምናምን አድርጉት እስቲ ጥሩ ያስተምራል.. ስለ መቃብር የሚያወራው አልፎ አልፎ ብቻ ነው ሎል..
https://vm.tiktok.com/ZMhreWW9J/
ዛሬ ቅዳሴ ላይ ከተነበበው የቅዱስ ወንጌል ክፍል
“በዚህም በዘማዊና በኃጢአተኛ ትውልድ መካከል በእኔና በቃሌ የሚያፍር ሁሉ፥ የሰው ልጅ ደግሞ በአባቱ ክብር ከቅዱሳን መላእክት ጋር በመጣ ጊዜ በእርሱ ያፍርበታል።”
[ማርቆስ 8: 38]
ከላይ ከፍ ብሎ እንደተቀመጠው ጌታችን አስቀድሞ “በኋላዬ ሊከተለኝ የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ” ብሎ ነበር.. እናም ዝቅ ብሎ “በእኔና በቃሌ የሚያፍር..” አለ..
በዚህ በዘማዊና በኃጢአተኛ ትውልድ መካከል በጌታ አለማፈር ማለት ጌታ ጌታ ማለት ሳይሆን መስቀሉን ተሸክሞ እርሱን ደግሞ መከተል ነው.. ይህም በሕይወት ነው.. ዝሙትን እና ሌሎችንም ክደን ፈተናውንም ተቋቁመን ዓለምን እምቢ ብለን ጌታን ስንከተል በእርሱ አላፈርንም ማለት ነው.. ዓለም ይሸለኛል የሥጋን ፈቃድ መፈጸምን መርጬ የኢየሱስ ቃል ግን ምንም ነው ብንል ግን ያኔ በጌታ አፍረናልና የሰው ልጅ(ኢየሱስ) በአባቱ ክብር ከቅዱሳን መላእክት ጋር በመጣ ጊዜ በእኛ ያፍርብናል..
ስለዚህም በጌታችንና በቃሉ የምናፍር አንሁን.. ለመመስከርም ለመኖርም..
መልካም የጌታ ቀን
@Apostolic_Answers
እንኳን ደስ አላችሁ..
ኦርቶዶክስ አቃብያነ እምነት እና ፕሮቴስታንት አቃብያነ እምነት እግር ኳስ ግጥሚያ ይኖረናል በቅርቡ..
ሎል😁😁
ጴንጤው ወዳጄ ስለ እኔ የጻፈው😭😭
https://vm.tiktok.com/ZMh2GMvqJ/
ዛሬ ቅዳሴ ላይ ከተባለው ምስባክ
“ምድርኒ ወሀበት ፍሬሃ፤
ወይባርከነ እግዚአብሔር አምላክነ።
ወይባርከነ እግዚአብሔር፤
ወይፍርህዎ ኵሎሙ አጽናፈ ምድር።”
[መዝሙር ዳዊት 67: 6-7]
በግእዝ አጨናነኳችሁ አ..?? አይዞን እኔም ምስባክ ላይ በአማርኛ ሲሉት ስሰማ ጥቅሱን ይዤው ነው😁😁
“ምድር ፍሬዋን ሰጠች፤
እግዚአብሔር አምላካችንም ይባርከናል።
እግዚአብሔር ይባርከናል፥
የምድርም ዳርቻ ሁሉ ይፈሩታል።”
ከዝናብ በኋላ ምድር ፍሬዋን ትሰጣለች.. እንዲሁ ከእግዚአብሔር በረከት ወይም ጸጋ በኋላ ከምድር የተዘጋጀን እኛ ደግሞ ፍሬን እንሰጣለን.. ሰው ጌታችን ኢየሱስ ከሚሰጠው ከሕይወት ውኃ ሳይጠጣ ፍሬን ማፍራት አይችልም.. እኛ ደግሞ ከዚህ ውኃ ጠጥተናልና እንደ ምድረ በዳ እሾህና አመኬላን እንደሚያበቅል ምድር አንሁን.. ከኃጢአት ሁሉ እየራቅን ከጸጋው የተነሳ ፍሬን እናፍራ..
“እግዚአብሔር አምላካችን ይባርከናል”
መልካም የጌታ ቀን
@Apostolic_Answers
ዮሐዴ😁😁
እየገባችሁ ላይክ ሼር ምናምን እያደረጋችሁ አበረታቱት
https://vm.tiktok.com/ZMhLSkWbR/
ዛሬ ማታ ዲቤት..?? ዌል ዛሬ አዎን አለን እንዳትቀሩ😁😁
https://vm.tiktok.com/ZMh85DbbT/
አንዲት እህት እያለቀሰች አሁን በስልክ አወራችኝ..
የቤቱ ታላቅ ወንድም ፕሮቴስታንት ሆነባቸው እና ቤት ውስጥ የነሱን መዝሙር ምናምን እየከፈተ እናትየዋን በጣም ያስቸግራቸው ነበር እና ያለቅሱ ምናምን ነበር.. እና እቺ እህትየዋ ለካ የኛን ቪዲዮዎች እየላከችለት ላይቭንም እንዲሁ ምናምን ነገር.. ከዛ የሆነ ቀን ላይቫችንን እያየ ከዛ ለእህቱ ደወለላት እና እንደተሰማው ምናምን አወራት አሁን በንስሐ ተመለሰ.. ይኸው አሁን የመጨረሻ ደስ ብሏት በቃ እያለቀሰች ነው ራሱ ያወራችኝ.. ጌታ ይመስገን.. የእናት ጸሎት ልጅንም ይረዳል..
@Apostolic_Answers