ኤዞፕ ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት። በምኒልክ አደባባይ ፊት ለፊት ያለው የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን ህንፃ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ ነው !! ስልክ:- 09 11 72 36 56 @Mesay21 @Mesay21
ኦሪጅናል ቨርዥን
1962 ዓ ም የታተመ።
በደጅ አዝማች ከበደ ተሰማ
የታሪክ ማስታወሻ !!!
አንድ ኮፒ ብቻ አለን
ታህሳስ 9 ቀን 1921 ዓ.ም. ሐረር፣ መቂ ጋሪ ሙለታ ባዕት የተወለደው ህጻን አድጎ ጎልምሶ
ኢትዮጵያን እንደሚያስጠራ የአፍሪቃዊነት አተያይና የአንድነት ሀሳብን ከግብር እንዲውል
የሚያደረግ ታላቅ ዲፕሎማት ይወጣዋል ብሎ የጠረጠረ አልነበረም፡፡ ይሁንና አቶ ከተማ ይፍሩ ግን ውጣ ውረዱን አልፎ፣ ስቃይና መከራውን ተቋቁሞ የሀገር መጠሪያ ሆነ ይህ የአቶ ከተማ ታሪክ የትላንቱን የአባቶቻችንና የእናቶቻችንን ልፋትና ግረት አመልካች ተምሳሌ ነው፡ ከህይወቱ ጉዞ የተቀነጨበ አንዱን ሰበዝ - እንጎ ታሪኩ ብቻ ነው የቀረበው
የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ሲመሰረት የነበረው ውዝግብና ገመድ ጉተታ፤ ጽ/ቤቱ አዲስ አበባ
ለማድረግ የተጓበት ርቀት፣ በሀገር ውስጥ በግሉ የደረሰበት ጉንተላና ግፊያ፣ የውጭ ባዕዳን የሚያጠምዱትን ወጥመድና እንቅፋት የማለፍ ጥበቡን ታዩበታላችሁ፡ ሌሎችን ታሪካዊ ኹነቶች በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ኃላፊነት ላይ እንዳለ፣ በንግሰ ነገስቱ ጸሀፊነቱ ወቅትም የነበረውን ፈተና በአቶ ከተማ ታሪክ አቋራጭነት ታጤኑበታላችሁ፡
እና ያ ከጋራሙለታ የወጣው ኢትዮጵያዊ ራሱን መስዋዕት በማድረግ ባገለገላት ሀገር በግፍ
ዘብጥያ በተወረወረበት ክፉ ጊዜ በማስታወሻው ላይ (ጥር 1968 ላይ ) እንዲህ ብሎ ነበር“እውነት ትመነምናለች እንጂ አትሞትም እንደሚባለው በአለኝ አቅም ጊዜው ሁኔታውና አቅሙ በሚፈቅደው ለአገሬ ያደረጉትንና ለማድረግም የሞከርኩትን ጊዜ ወደፊት እንደሚገልጠው ስለማምን
እጽናናለሁ: በተለይ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር በነበርኩ ጊዜ የኢትዮጵያን የውጭ ፖለቲካ ከምን አንስቼ ምን ደረጃ ላይ እንዳደረስኩት ስራውና የኢትዮጵያ ህዝብ በሙሉ ምስክሬ ነው'' እውንም የአቶ ከተማን ስራ ጊዜ ይገልጠዋል፡ ይህ መጽሐፍም የመጀመሪያ ነው፡፡
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
🙏🙏🙏
መጽሐፈ ድጓ
ቅዱስ ያሬድ እንደደረሰው
በሦስት ረድፍ የታተመ
በቀዳማዊ ኋይለስላሴ ዘመን የታተመ!!!
#ጠመንጃና _ሙዚቃን_ተጋበዙልኝ!
ከአገሬው የኪን ፍልስፍና ተነስቶ፥ በ40ዎቹ አርመናውያን አመጣጥ ጎዳና ተምሞ፥ ማርሽ ኢትዮጵያ እና ማርሽ ተፈሪን ተዝቶ፥ የኬቦርክ ናልባንዲያን እና የየኔታ ዮፍታሄ ንጉሴን ፍጥጫ አውስቶ፥ በፋቼታ ኔራ ኩርባ ታጥፎ፥ መሰንቆ እንደ ጦር መሣሪያ የተቆጠረበትን አውድ አውግቶን ይነጉዳል። የሀገር ፍቅር ማኅበርን ከአመሠራረቱ ጀምሮ የነበረውን ታሪክ ለመሰነድ የሄደበት ርቀት እሚደንቅ ነው። የቀብር ቀኑን በገዛ ሙዚቃው ከታጀበለት አሰፋ አባተ፥ እስከ ሙዚቃ የዋጠው ፖለቲካ (አሊ ቢራ)፥ ከሜሪ አርምዴ ታሪክ የአበበ ፍቅር እስካናወዛት አስናቀች ወርቁ ድረስ ያሉ የሕይወት ታሪክ መድብል ብዙ የተለፋበት ሥራ መሆኑን ያሳብቃል። የተለያዩ የሙዚቃ ባንድ ታሪኮችን ማካተቱ ሲገርመን፥ ዓይነስውራን ሙዚቀኞችን ማውሳቱ ደግሞ እጅግ አስደንቆኛል። የ700 ሙዚቃዎች "ካታሎግ" ደግሞ ሌላ ታሪክ ነው።
ደራሲውን እጅ ነስተናል! በንባብ ይለቅ ብለናል! በኢትዮጵያ ሙዚቀኞች ማኅበር፥ በሀገር ፍቅር ማኅበር፥ የሙዚቃ ባንዶች ማኅበር ... ተጋግዘው መሥራት የነበረባቸውን የቤት ሥራ በአንድ ሰው ትከሻ ብቻ መሞከሩ አጃኢብ እንድንል አሰኝቶናል።
📖#ጠመንጃና_ሙዚቃ
✍#ይነገር_ጌታቸው
#ሐምሌ 8፣ 1914
#ኒው ዮርክ
ውድ ሜሪ አንቺ እጅግ የበዛ ሰዎችን የመረዳት መክሊት የተሰጠሽ ሰው ነሽ። ሕይወትን አዳይ ነሽ ። አንቺ ለመጋራት ሳይሆን ሕይወቱን ለማበልጸግ የሆነን ሰው እንደሚወዳጅ ታላቅ መልዓክ ነሽ። በኑረት ዘመኔ ከአንቺ ጋር መተዋወቄ ከምልዓተ ዓለሙ ተፈጥሯዊ ስልተ ምትና ስልተ ስሪት ውጪ የሆነ አስደናቂ ተዓምር ነው።
"ዘማድማን" በተሰኘ መጽሐፌ እንደገለጽኩት የሚረዱን ሰዎች ከሕይወታችን ውስጥ የሆነውን ነገር ይቆጣጠሩብናል። አንቺ ጋ ይሄ የለም። የአንቺ እኔን መረዳት ከማውቃቸው ሁሉ በተለየ ነጻነትን የሚያጎናጽፍ ሰላማዊ ነው። ባለፈው የመጨረሻ ጉብኝትሽ ልቤን በመዳፍሽ ይዘሽ ከላዩዋ ላይ ነቁጥ የምታክል ጥቁር ነገር አገኘሽ።
በዚያችው ቅጽበት ጥቁሯ ነጥብ ለዘለዓለም ከልቤ ላይ ተፋቀች እኔም ሙሉ ለሙሉ ከእሥራቴ ነጻ ወጣሁ።
ይሄው አሁን ደግሞ የተራራ ላይ ብህትውና ላይ ነሽ። በበኩሌ በረቂቅ፣ ስውር፣ ውብ መሬቶች ላይ አርምሞን ከመለማመድ በላይ የሚያስደስት ምንም ነገር እንደሌለ አምናለሁ። ሆኖም ተወዳጄ ሆይ ምልዓቱን Uሰሳን የተራበች ነፍስሽ በአንድ ሰሞን ጀብድ ብቻ እንደማትረካ ኣውቃለሁና አጉል መዳፈርን ተጠንቀቁ። ምክንያቱም ለዳግም የUሰሳ ጉዞ ወደ ተራራ መውጣት ትችይ ዘንድ ደኅንነትሽ መረጋገጥ አለበት። ቤቴ በላክሻቸው ‹አሪቲና ጠጅሳር መልካም መዓዛ ታውዶልሻል። ስለላክሽልኝ እግዚአብሔር ይባርክሽ።
የቴሌግራም ቻናላችን👉👉👉 @azop78
የቴሌግራም ጉሩፓችን👉👉👉 @azopbook
#ማንኛውንም መፅሐፍ ለማዘዝ @Mesay21
የቻናላችን ቤተሰብ ስለሆኑ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነውና ለወዳጅ ዘመደዎት ሊንካችንን ያጋሩት።
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏
1. አገር ማለት
አለቃ ተሰማ ሀብተሚካኤል ግፅው የአገርን ትርጉም እንደሚከተለው ይገልጹለታል፤ ‹‹አገር ልብስ ነው፤›› ብለው ሲያብራሩ «ሰው ኹሉ በልብሱ እርቃነ አካሉን እንደሚሰውር፣ አገርም ልብስ፣ ከለላ፣ መጋረጃ ነው፡፡›› ይላሉ፡፡
አገር ማለት ሕዝብና መሬት በአንድ ላይ ሆነው በድርጅት ወይም መንግሥት ሲያያዙ ነው፡፡ አገር ያለመሬት አይኖርም፤ አገር ያለሕዝብ አይኖርም፤ አገር ያለድርጅት (ማለት ሲሆን መንግሥት፣ አለዚያ አገዛዝ አይኖርም፡፡ መሬትና ሕዝብም ያለድርጅት አገር አይሆንም፤ ሕዝብና ድርጅትም ያለመሬት አገር አይሆንም፤ መሬትና ድርጅትም ያለሕዝብ ትርጉም የላቸውም፡፡
አለቃ : ደስታ : በእንግሊዝኛ ስቴት steat የሚባለው ቃል ያዘለውን ትርጉም በአማርኛ መንግሥት ለሚለው ቃል ይሰጡታል፤ እንዲህ ይላሉ፤ ያንድ ንጉሥ ግዛት፣ አገሩም፣ ሕዝቡም ባንድነት መንግሥት ይባላል፡፡› አለቃ ደስታ ሕዝብ ሲሉ ሕዝብ የሰፈረበትን መሬት ጭምር ነው።
ሕዝብ የምንለው በዚያ በደም የተገነባ ድንበር ውስጥ በአንድ ዓይነት መብትና ግዴታ ተጠምደው የአገሩ ባለቤት ሆነው የሚኖሩትን ሰዎች በሙሉ _ ነው፡፡ ባለቤትነትንና ባለሥልጣንነትን የሚያመለክተው ሉዓላዊነት የሕዝብ ነው፡፡ በአንድ ሕዝብ ውስጥ ብዙ ዓይነት ልዩነቶች ሊኖሩ ይችላሉ፤ እነዚህ ልዩነቶችን የሚያስተሳስራቸውና ከመከፋፈል ይልቅ ወደኀብረት፣ ከመናናቅ ወደመከባበር፤ ከመጠላላት ወደፍቅር፣ ከመበላለጥ ወደእኩልነት የሚመሩበት ሕግና ሥርዓት ልዩነቶችን ተቀብሎ የዜግነት አንድነትን በማረጋገጥ ሁኔታም በአንድ ላይ የአገሩ ባለቤት ያደርጋቸዋል፡፡
የአንድ አገር ሕዝብ ስንል በአንድ በተወሰነ ጊዜ በዚያ አገር ውስጥ ያሉትን ሰዎች ድምር ብቻ አይደለም፡፡ ለምሳሌ ኢትዮጵያ የምትባል አገር ከተቆረቆረች ጀምሮ ለዚች አገር ክብርና ነፃነት የሞቱትን ሁሉ ይጨምራል፤ ወደፊትም የሚወስዱትንና የእነሱንም ልጆች ያካትታል፡፡ ከኋላ የነበረውንና አሁን የሌለውን ወደፊትም የሚወለደውንና አሁን የሌለውን አብረንና አያይዘን ካላየነው የታሪክ አካሄድንና ሕዝቡ የተሳሰረበትን ሰንሰለት ውሉን እንስታዋለን፡፡ እየሳትነውም ይመስለኛል።
"አገሮች ሁሉ መሬታቸው በተቻለ መጠን በትክክል በድንበር የተከለለ ነው: የትም ቢሆን የእያንዳንዱ አገር የድንበር ታሪክ በጦርነትና በደም የተጻፉ ነው፡፡ 3 ቁጥር ስፍር የሌላቸው ዜጎች ሕይወታቸውን መስዋዕት እያደረጉ የጠበቁት መሬት ነው፡፡ የሰው ልጅ ከግለኛና ስጋት ከተሞላበት ኑሮ ወጥቶ ይነስም ይብዛ በተደራጀ ኅብረት መኖር ከጀመረ አንሥቶ የገዛ መሬቱን ከጠላትና ከወራሪዎች ለመጠበቅ ብዙ የሕይወት መስዋዕት ተከፍሎአል። የአገርን መሬት አስከብሮ የመኖሩ ታሪክ የአንድ ትውልድ ግዴታ ሳይሆን ተከታታይ ትውልዶች በየጊዜያቸው የሚወጡት ግዴታቸው ነው፡፡
2. የአገር ፍቅር
የአንድ አገር መሬት በደንብና በሕግ የተከለለ ነው፤ ድንበር አለው፡ ለጥቂት አገሮች በዚህ ድንበር የተከለለው መሬት ሺህ ዓመታት ወደኋላ ተሂዶ ተሂዶ የማይደረስበት በጣም ረጅም ታሪክ አለው፤ ለምሳሌ ግብፅ፣ ፋርስ፣ የዛሬው ኢራቅና ቻይና ኢትዮጵያም የእንደዚህ ያለ ታሪክ ባለቤቶች ናቸው። በነዚህ አገሮች ውስጥ ሁሉ ተከታታይ ትውልዶች ያደረጉትን ተጋድሎና የከፈሉትን መስዋዕትነት ለመገመት አስቸጋሪ አይደለም፡፡ እነዚህ ተከታታይ ትውልዶች በሀሳብ፣ በሥራና በእምነት ያስተላለፉት የተከማቸ ታሪክ ለአገሮቹ የህልውናቸውና የክብራቸው መሠረት ነው፡፡ የአገር ፍቅር የሚባለው የሚመነጨውም ከዚህ ይመስለኛል፡፡
የአገር ፍቅር የሚባለው : ስሜት : ከየአገሩ ታሪክ ዕድሜ ጋር የሚጠነክርና የሚላላ ይመስላል፡፡ በተለይም የተጻፈ ከሆነ የታሪክ ሽክም በከበደና በተከበረ መጠን የአገር ፍቅር ስሜት የጠነክራል የሚል አስተሳሰብ አለኝ። በአሁኑ ጊዜ ይህ ገለጻ መሠረታዊ ችግር አለበት፡፡ በዘመናችን የመመላለሻ አገልግሎቶች በየዓይነቱ ሰዎችን ከአንዱ አገር ወደሌላ አገር በተለያየ ምክንያት የሚያጓጉዙ በመሆናቸውና ሰዎችም በጥገኝነትም ሆነ ዜግነትን በመለወጥ በሌሎች አገሮች መኖር እየተለመደ በመምጣቱ የአገር ፍቅር የሚባለውን ስሜት የሚበርዙት ሌሎች ተወዳዳሪ ስሜቶች እየተፈጠሩ ነው፡፡ ስለዚህም አንዳንዴ ኃያላን አገሮች አዳዲስ አገሮችእንዲፈጠሩ ተጽእኖ እንደሚያደርጉ በቅርቡ በአውሮፓም ሆነ በአፍሪካ አይተናል፣ የኤርትራ ጉዳይ አንድ ምሳሌ ነው፡፡ ከዚያም በላይ ስለ አፍሪካ - ያልተሳካላቸው አገሮች በእንግሊዝኛ ፌይልድ ስቴትስ በሚል ርዕስ ከአሜሪካ አንድ : ሰነድ ወጥቶ ነበር፣ ዓላማው እነዚህን ያልተሳካላቸው የአፍሪካ አገሮችን በጎሣ ለመሸንሸንና ትንንሽ አገሮችን ለመፍጠር ነበር፣ በዓላማው ከአፍሪካ መሪዎች አንዱ ተስማምተዋል ተብለው የተጠቀሱት የኛው አቶ መለስ ናቸው፡፡ አፄ ገላውዴዎስ ያለውን ቢገነዘበለት አነሰ አይፈቅድ እርኢ ሙስናሁ ለሀገር አምጣነ ሀሎኩ በዛቲ ሕይወት ምድራዊት፤ ትርጉሙ በሕይወት እስካለሁ ድረስ አገር ሲጠፋ ማየትን አልፈልግም፡፡
ብዙ የአውሮፓና የሰሜንና የደቡብ : አሜሪካ አገሮች ትናንት የተፈጠሩ ናቸው ለማለት ይቻላል፤ የእነዚህ አገሮች ታሪክ በጥቂት ምዕተ ዓመታት የሚቆጠር ነው፡፡ የአገር ፍቅር ስሜታቸውም በዚያው መጠን ነው፡፡ ጭቆናና ግፍም የአገር ፍቅር ስሜትን በመቀነስ ትልቅ አስተዋፅኦ አሳቸው። በአሁኑ ጊዜ ብዙ ሰዎች የአገራቸውን ሕይወት ከነሱ ኑሮ ጋር አቆራኝተው ይመለከቱታል። እነሱ ከደላቸውና ከተመቻቸው አገራቸውን ይወድዳሉ፤ ካልተመቻቸውና ካልደላቸው አገር የሚባል ነገር ጉዳያቸው አይደለም።
ሌሎች ደግሞ ሌላ ሚዛን ይዘው ‹አብዮታዊት እናት አገር ይላሉ፤ እናት አብዮታዊት ካልሆነች እናትነትዋን ሊክዱ የዳዳቸው ናቸው፤ ይህ ከማርክስ ፍልስፍና ጋር የሚጋጭ ነው፤ ምክንያቱም በማርከስ ፍልስፍና ህልውና ከንቃተ ኅሊና ይቀድማል፡፡ በእንደዚህ ዓነቶቹ ሰዎች አመለካከት የአገር ሕይወት በዚያ አገር ውስጥ የሚኖሩ የደላቸው ወይም አብዮተኞች የተባሉት ሰዎች ድምር ነው፤ ሌላው የእነሱ መሣሪያ ነው፤ ለእኔ ይህ አመለካከት የተዛባ ነው፤ አብዛኛውን ጊዜ ለአገሩ የሚሞተው ሀብታሙና የደላው አይደለም፤ ትላልቅ ሹሞችም ቢሆኑ ሳይደላቸው ለአገር የሚሞቱ አሉ፤ አንድ ምሳሌ ብቻ ለመጥቀስ ደጃዝማች ባልቻ ደልቶአቸው አይደለም በኢጣልያ ላይ ተነስተው የሞቱት፡፡
የእያንዳንዱ ሰው ኑሮ ለአንድ ለዚያ ለሰውም ሆነ ለአገሩ ዋጋ የለውም :: ማለቱ : አይደለም፡፡ ዋጋ አለው፡፡ የእያንዳንዳችንን የግል የየቤታችንን ችግር ክበንና አጉልተን የአገር ችግር እናድርገው ለማለት ነው፤ የአገር ችግር የሁላችንም፤ የሕዝቡ በሙሉ ችግር ነው፡፡ አለዚያምየመንደሩን ችግርና የአገርን ችግር መለየት ያቅተናል፣ ይህ ስላቃተን ነው አሁን ያለንበት ማጥ ውስጥ የገባነው፡፡
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ላይ የደረሰው ምናልባትም በሌላ አገር ታይቶ የማይታወቅ አዲስ ነገር ነው። አንደኛ፣ ኢትዮጵያውያን አይደለንም ብለው ተዋግተው ኤርትራን ያስገነጠሉት ሰዎች ኤርትራን ከቅኝ አገዛዝ አላቅቀው ወደ እናት አገርዋ ወደኢትዮጵያ ለመመለስ የታገሉ፣ የሞቱና የቆሰሉ : ኢትዮጵያውያን ልጆች ናቸው። ሁለተኛ፣ ኢትዮጵያውያን አይደለንም ያሉትንና የአባቶቻቸውን የኢትዮጵያዊነት መስዋዕትነት የካዱት፣ የረዱትና መለየቱን ያቃለሉላቸው የትግራይ ተወላጆች ኢትዮጵያውያን : ናቸው፡፡ ሁለቱም : ለልጆቻቸውና :: ለልጅ ልጆቻቸው የሚያወርሱትን የታሪክ ሐፍረት ለመገመት የሚያዳግት አይደለም። የዚህ የታሪክ ሐፍረት ተሸካሚ ማን ነው ትግርኛ ተናጋሪዎች በአጠቃላይ፣ ወይም
ርቱዓነ ሃይማኖት አበዉ ሊቃውንተ ቤተከርስቲያን የሚያምኑትን ያውቁታል የሚያውቁትን ይኖሩታል የኖሩትን ጽፈው ደጉሰው በትውፊት ለትውልድ ያስላልፉታል
በዚህ ረገድ ተጠቃሽ ከምናደርጋቸው መጻሕፍት መካከል ደግሞ አንዱ መድበላተ አሚን ወምግባር ተሰባስበው የተካተቱበት የአበው ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ጽንዐ ሃይማኖት የተንጸበረቀበት መጽሐፈ ሐዊ ነ ው ::
ሥለዚህ በእንዲህ አይነት ትውፊት አበው በደም ጸንተው በቀለም በርትተው ባቆዩልን ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለን ውሉደ ጥምቀት ደቂቀ ሊቃውንት ክርስቲያኖች ደግሞ በዚህ መንገድ ተተርንሞ የቀረበው መጽሐፍ ተደራሽ መሆናችን በአምላክ ቸርነት በአባቶቻችን ትጋት በቆየችው ሃይማኖት ለመጽናት አይነተኛ መሳሪያ ነው፡፡
ይህን ቆየት ያለ መጽሐፍ እጅግ በብዙ ድካም ተርጉመው የአቀረቡልን የአቋቋም እንዲሁም የቅኔ መምህር ብሎም የነገረ መለኮት ምሩቅ ሊቀ ጠበብት መሠረት ምሕረቱም ኩላዊት ኦርቶዶካሳዊት ቤተከርስቲያን በትውፊት እና በሊቃውንት ትግሐ ሃይማኖት የመጽናቷ አንዱ ማሳያ ናቸው:: ከቡር መምህራችን አምላከ አበው ሊቃውንት በጽንአ አበው ያቆይልን !!!
መጋቤ ሐዲስ ያዕቆብ አስፋው ለመጽሐፈ ሀዊ የሰጡት አስተያየት ነው። መጽሐፉ ገበያ ላይ የጠፋ ቢኾንም ትንሽ ኮፒወች እጃችን ላይ ይገኛል።
ኤዞፕ መጽሐፍት !!!
አዳዲስና ጥንታዊ መጽሐፍትን ለማግኘት
ቴሌግራማችን ጆይን አድርጉ
/channel/azop78
ምሳሌ፡- ‹‹እንዲያውም ጎበዝና ሰነፍ ተማሪዎችን የሚያመሳስለን አንድ ነገር ሁለታችንም ትምህርት አለመውደዳችን እንደሆነ ደርሼበታለሁ›› (ገጽ 1)፤ ‹‹እሱ ሙስሊም አይደለም። ግን የነቢዩ ሞሐመድ ልደት ከከድር ይልቅ ያሳስበዋል›› (ገጽ 2)፤ ‹‹ኮሶ በመድኀኒት ይሽራል። አውግቸው ግን ማርከሻ የለውም›› (ገጽ 12)፤ ‹‹የመምህር አውግቸውን ፊት ከማይ የሚመጣው እንቁጣጣሽ ልብስ ሳይገዛልኝ ቢቀር ይሻለኛል›› (ገጽ 12)፤ ‹‹ራሱ ክላሽ ታጥቆ ሲያበቃ ግን እናባዬን ሊቀማ መሞከሩ ጅል መሰለኝ›› (ገጽ 37)፣ ‹‹ጎሊያድን ያለወንጭፍ የምገጥምበት ሰዓት አሁን መጣ›› (ገጽ 70)፣ ‹‹አምስተኛ ክፍል ት/ቶቹ በዙ። እኔም አበሳዬ በዛ›› (ገጽ 161)፣ ‹‹አባዬ ሲያወራ ያዲሳባው ቤተመንግስት ሦስት አጥር ነው ያለው ይላል። የእኔ ሦስት አጥር እህቴ ናት›› (ገጽ 169) እና ሌሎችም።
#ኑረታዊነት/Existentialism - ይኼ ነጥብ በትረካ ውስጥ ቦግ-ሕልም የሚል አንድ ቴክኒክ ነው፤ ኤግዚስቴንዣሊስም የኑረታዊነት ወ የፍጥሐዊነት መብሰክስክ ነው፤ Existentialists explore questions related to the meaning, purpose, and value of human existence. Common concepts in existentialist thought include existential crisis, dread, and anxiety in the face of an absurd world, as well as authenticity, courage, and virtue…እንዲል ደራሲው በትረካ ዐውድ እና በገጸ-ባሕርይ ሥሜት እየተመራ የተለያዩ ኑረታዊ፣ ፍትሐዊ፣ ፍልስፍናዊ ጥያቄዎችን ያነሳል። ለምሳሌ ገጽ 73፣ 81፣ 138፣ 140፣ 142፣ 144፣ 145፣ 201፣ 250-251 የተነሱ ሐሳቦችን መመልከት እንችላለን።
#ምልክት/Symbolism - ምልክት የድርሰት ማኅበረሰብን ባሕል፣ ሃይማኖት፣ ቋንቋ፣ ወግ ይወክላል። እውነት የሚመነጨው ከምልክትና ከማኅበረሰብ ፎክሎር እንደሆነ ይታመናል። አብነት እንጥቀስ፡- የዛፍና የደብር፣ የእረኛና የሥም ቁርኝት፤ የገጠሩን ውበት፣ እንዲሁም የተፈጥሮአዊ ውበትና የጥበብን ተጋምዶ፣ ንባብና ማኅበረሰብ (አንባቢ ራሱን የሳተ ተደርጎ እንደሚታይ)፣ ዛፍ መትከል?... ወዘተ. እንደምልክትነት ተካትተዋል።
#ከራስ ጋር ንግግር/Interior Monologue - ዋናው ገጸ-ባሕሪይ በተለያዩ ስሜቶች መካከል በመቸንከር ጊዜውን/ሁኔታውን የሚመጥኑ ጥያቄዎችን ለእራሱ ያቀርባል፤ ምላሹንም ራሱ ይሰጣል። ከራስ ጋር ንግግር።
‹‹ፋሲካ ግን መቼ ነው? ሩቅ ነው መሰል›› (ገጽ 165)፣ ‹‹ከክፍሉ ተማሪ እኔ ብቻ ሁለት ጊዜ ተገረፍኩ። ምን ስላደረግሁ? ስለመለስኩ›› (ገጽ 189) እና የመሳሰሉትን።
#ሴራ - (ሀ)፣ የድርሰቱ ዋና ገጸ-ባሕርይ ያለመክሊቱ የሚከታተለው ትምህርት የእግር እሳት ይሆንበታል። (ለ)፣ በቤትም በት/ቤትም ስንፍናውን እየተናገሩ የባሰ እንዲያንገሸግሸው ያደርጉታል። (ሐ)፣ የሥነ-ልቡናዋ መምህርት በት/ቤት ተገኝታ ስለመክሊትና ፍላጎት ብሎም እንዴት ስኬታማ መሆን እንደሚቻል ታወያያቸዋለች። ይኼኔ ‹‹ራስ›› በጣም ይንገሸገሻል፤ ጥልቅ ሕልምም ያልማል። (መ)፣ ሰበብ ፈልጎ ትምህርቱን ጥሎ አያቶቹ ዘንድ ይኮበልላል። (ሠ)፣ ሌጣ መሬት ላይ ዛፍ ተክሎ መንደሩንና አገሩን ይታደጋል። (ረ)፣ የከንቲባው ገዳይ በቁጥጥር ሥር ይውላል። ከሞላ ጎደል ሴራው የምስራቻዊ ድምዳሜ (surprise ending) ዓይነት መልክ አለው።
#‹‹ራስ››ና ስንፍና ሽሽት/A travelling character - ‹‹ራስ›› ከጅምሩ ተንገሽጋሽ ማቲ ነው። አለፍላጎቱ ተማሪ ቤት ተዱሎ ፍዳውን የሚበላ ዓይነት፤ በጉያው ያሉ ግለሰቦች በነገር እየጎነታተሉ፣ ስንፍናውን ብቻ እየደረቱ ያስመርሩት ጀመር። ቢጥር፣ ቢግር ስኬት ጀርባዋን ሰጠቺው። ቢያስር፣ ቢሠራ የትምህርት ፍላጎቱ ነጠፈ። በቤትም በት/ቤትም ተነቀፈ። ስኬትን፣ ራስን ፍለጋ አያቶቹ ጋር ሄደ፤ ተጓዘ። ከአጀብ ተነጥሎ የሚመጥነውን ዓለም ኖረ። ራስን ፍለጋ!
#በአጠቃላይ ‹‹ራስ›› እንደ ጣኦስ መልከ ብዙ ቴክኒኮችን ያጨቀ ድርሰት ነው። ከላይ የተገለጹት እና ሌሎች ብዙ ‹ቦግ› ብለው ወዲያው ‹እልም› ያሉ የትረካ ቴክኒኮችን አጭቃለች፤ ደራሲው በቀጣይ ቁስ አካላዊ መሣሪያዎችን፣ እንግዳ ክስተትን፣ ከራስ ጋር ንግግርን፣ የምልክት ፈጠራን እና ሌሎች ቴክኒኮችን በይበልጥ ያዳብራቸዋል ብዬ አምናለሁ።
#አገር ማለት
‹‹አገር ልብስ ነው፤›› «ሰው ኹሉ በልብሱ እርቃነ አካሉን እንደሚሰውር ኹሉ አገርም ለሰው ልጅ ልብስ፣ ከለላ፣ መጋረጃ ነው፡፡››
አገር ማለት ሕዝብና መሬት በአንድ ላይ ሆነው በመንግሥት ሲያያዙ ነው፡፡ አገር ያለመሬት አይኖርም፤ አገር ያለሕዝብ አይኖርም፤ አገር ያለድርጅት ያለ መንግሥት፣ ያለ አገዛዝ አይኖርም፡፡ መሬትና ሕዝብም ያለድርጅት አገር አይሆንም፤ ሕዝብና ድርጅትም ያለመሬት አገር አይሆንም። መሬትና ድርጅትም ያለሕዝብ ትርጉም የላቸውም፡፡ ያንድ ንጉሥ ግዛት፣ አገሩም፣ ሕዝቡም ባንድነት መንግሥት ይባላል፡፡› ሕዝብ የሰፈረበትና በድርጅቱ ውስጥ ያለ መሬት አገር ይባላል።
አገሩንም ለመገንባት ሕዝብ ድንበር አቋርጦ የሚመጣን ወራሪ መክቶ ሰላምና ደህንነት ጠብቆ ሀይማኖቱን አስጠብቆ በሚከፈሉት መሥዋዕትነት ኹሉ አጥንትና ደሙን ገብሮ የሚገነባው ድንበር ላይ በአንድ ዓይነት መብትና ግዴታ የሚኖሩ ሰዎች በሙሉ የአገሩ ባለቤቶች ይባላሉ።
ባለቤትነትንና ባለሥልጣንነትን የሚያመለክተው ሉዓላዊነት ሕዝብ ነው፡፡ በአንድ ሕዝብ ውስጥ ብዙ ዓይነት ልዩነቶች ሊኖሩ ይችላሉ፤ እነዚህ ልዩነቶችን የሚያስተሳስራቸውና ከመከፋፈል ይልቅ ወደኀብረት፣ ከመናናቅ ወደመከባበር፤ ከመጠላላት ወደፍቅር፣ ከመበላለጥ ወደ እኩልነት የሚመሩበት ሕግና ሥርዓት ልዩነቶችን ተቀብሎ የዜግነት አንድነትን በማረጋገጥ ሁኔታም በአንድ ላይ የአገሩ ባለቤት ያደርጋቸዋል፡፡
የአንድ አገር ሕዝብ ስንል በአንድ በተወሰነ ጊዜ በዚያ አገር ውስጥ ያሉትን ሰዎች ድምር ብቻ አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ የምትባል አገር ከተቆረቆረች ጀምሮ ለዚች አገር ክብርና ነፃነት የሞቱትን ሁሉ ይጨምራል፤ ወደፊትም የሚነሱትንና የእነሱንም ልጆች ያካትታል፡፡ ከኋላ የነበረውንና አሁን የሌለውን ወደፊትም የሚወለደውንና አሁን የሌለውን አብረንና አያይዘን ካላየነው የታሪክ አካሄድንና ሕዝቡ የተሳሰረበትን ሰንሰለት ውሉን እንስታዋለን፡፡ ኢትዮጵያ አኹን የገጠማት ይኽ ነው። ውሉን ስተነዋል። መሳታችን ዋጋ እያስከፈለን መጥቷል።
"አገሮች ሁሉ መሬታቸው በተቻለ መጠን በትክክል በድንበር የተከለለ ነው: የትም ቢሆን የእያንዳንዱ አገር የድንበር ታሪክ በጦርነትና በደም የተጻፉ ታሪኮች አሉት፡፡ አገር ህዝቦቿ ሕይወታቸውን መስዋዕት እያደረጉ የጠበቁት መሬት ነው፡፡
የሰው ልጅ ከግለኛነት አስተሳሰብ ወጥቶ የአገርን መሬት ዳር ድንበር አስከብሮ መኖር የአንድ ትውልድ ግዴታ ሳይሆን የተከታታይ ትውልዶች ግዴታ ነው፡፡ አያትህ ለአባትኽ ያወረሰውን አገር አባትህ ለአንተ ካወረሰኽ አንተ ለልጅህ ዳር ድንበሯን ጠብቀህ በውስጧ የሚቀመጡ ቅርሶችን ሰርተኽ የማውረስ ግዴታ አለብኽ።
መነሻ ሀሳቡ ካነበብኩት የፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም መጽሐፍ የተወሰደ ሲኾን !!
ለውሏችኹ ይኹናችኹ ፣
በቸር ዋሉ
በቀጣይ ያገር ፍቅር ማለት
ምን እንደኾን እንከትባለን
Well written in a beautiful early Victorian style, it follows the amazing saga of the adventures Of an appealing, well educated young Englishman in the previously unvisited by any European Wilds of upland modern-day Ethiopia, bringing vividly to light the customs and beliefs of that Exotic land at that time. This work is a factual narrative by Maj. William Cornwallis Harris, who was sent by Queen Victoria to head a mission as the first ambassador from the UK to the KingDom of Goa in the heart of modern Ethiopia. The kings of Goa became the Emperors of Ethiopia in later years. its worth the effort for the insight into local culture of the time and its resemblance in many ways to that of the present. His style is very "Victorian," with elaborately descriptive prose. "Florid" would be a good word to describe it. After a while, however, the reader falls into the rhythm of the prose and the reading becomes easier. The writing style places the reader with in the Victorian milieu.lt is written to provide a narrative of the mission, and a somewhat analyticcal record of observation of terrain, peoples, cultures and customs encountered. He faithfully describes the mission day by day as it moves through punishing terrain, tribal battles, and variOus dangers finally to reach the highlands. He faithfully describes the peoples along the way; their appearance, their customs, their culture culminating in an in-depth look at the culture of Goa; its monarchy, its court, its towns and townspeople, its Coptic Church, and modes of dress, in sufficient detail that the reader feels he has been there in that day and age. Any student of history as well as anyone interested in African history will find this book fascinating.
Читать полностью…ዎልትዝ ዛሬ ጧት በማይታወቅ ምክንያት ቀደም ብሎ ተስቷል። ከአልጋው ግርጌ የታየውን የተለመደ የፈረስ ራስ ቅርጽ ምንነት ለማጣራት በክርኑ ዳኸና የራስጌ መብራቱን አበራ። ድንጋጤው በመላ ሰውነቱ ህመም አሰራጨበት፡ በትልቅ መዶሻ ደረቱን የተመታ ይመስል የልብ ትርታው እንጣጥ እንጣጥ እያላ አቅለሸለሸው፡፡
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
🙏🙏🙏🙏
“እዚህ ነው ምወርደው አቁም አቁም - ኦ! ኦ! አቁም
አልኩህ… እዚህ አውርደኝ "
ይኸኔ አዲሱ አርቲስቲክ ፎቅ ደርሰናል ሴትዮዋ ልትወርድ
ስትል
አምስት ስድስት ሰባት
“በል ስሙኒህን እሳቸው ይከፍሌሀል” አለችው''
“ሌላውስ ስሙኒ?”
“የምን ሌላ 'ባክህ?
“እንዲያውም ሰባ አምስት ነበረ”
“እሱን ተወው!”
“አሁን ጭቅጭቁ ይቅርና ሀምሳ ሳንቲም እፈልጋለሁ”
“ስንት ነው ያለባቸው?” አልኩት:
“ሀምሳ ሳንቲም”
ከፈልኩላት የራሴንም ከፈልኩ እና ከመኪናው ወጣሁ::
ፂሜን ለመላጨት ወደ ፀጉር አስተካካይ ቤት አመራሁ::
… ከሰአት በኋላውን ከስህነ ጋር ነበር ያሳለፍኩት፡፡
“ሰሞኑን ብዙ ሳጠና ነበር፡፡ ዛሬ ማታ አባባ የፈቀዱልኝ
እንደሆነ ሲኒማ ትወስደኛለህ?” ብላኝ ነበር::
“በደስታ”
“የት ነው 'ምንገባው?”
የትም ጥሩ ፊልም የለም' ዝምብለን ብሄራዊ ቲያትር እንግባ"
ከሁሉም እሱ ይሻላል?"
“አይ! መሻሉንስ ኢትዮጵያ ይሻላል"
“ታዲያ ለምን ኢትዮጵያ አትወስደኝም?
ወምበሩ ይቆረቁረኛል 'ባክሽን' ብሄራዊ ግን ሶፋው…
“ቀበጥ ነህ”
“ውሸቴን ነው፡፡ ለሶፋው አይደለም"
“ታዲያ ለምንድነው?”
“ሚስጥር ነው፡፡ ለልጆች አይነገርም”
“ንገረኝ”
“እእ!” - ራሴን እያነቃነቅኩ
“እባክህን” - በፈገግታ
“እእ!”
“ተወዋ! _ ይቅር፡፡ እኔ ደሞ ካልነገርከኝ አብሬህ ሲኒማ
አልገባም”
“እሺ-ሺ! እነግርሻለሁ"
“ንገረኛ”
“ብሄራዊ የገባን እንደሆነ፣ ፎቅ ወጥተን ወደ ኋላ መጨረሻ
ተርታ ያለው ወምበር ጋ እንቀመጥና አንቺ ፊልሙን ታያለሽ”
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
🙏🙏🙏
የቼክ ሪፐብሊኩ ተወላጅ የዚህ ተወላጅ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ አዶልፍ ፓርለሳክ ቀደም ሲል ኢትዮጵያን ጨምሮ ብዙ አገሮችን የጎበኙ ሲሆን እ.ኤ.አ በ1935 ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በመምጣት ከንጉሠ ነገሥቱ ፊት ቀርበው የኢትዮጵያን መኰንንነት ማዕረግ ከተሾሙ በኋላ የሰሜኑ ጦር ጠቅላይ አዛዥ ለነበሩት ራስ ካሣ ኃይሉ የጦር አማካሪ በመሆን አገልግለዋል፡ በዚሁ ወቅት በመቶ ሺዎች ከሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ጎን ሆነው ታግለዋል፡ መጽሐፉ ሃበሽስካ ኦዴሳ (Habešská Odyssea) የሃበሻ ጀብዱ የዚያን የገበሬጦር ጀግንነት ለመዘከር የጻፉት ነው፡፡
Читать полностью…ጠመንጃና ሙዚቃን ተጋበዙልኝ! ... ከአገሬው የኪን ፍልስፍና ተነስቶ፥ በ40ዎቹ አርመናውያን አመጣጥ ጎዳና ተምሞ፥ ማርሽ ኢትዮጵያ እና ማርሽ ተፈሪን ተዝቶ፥ የኬቦርክ ናልባንዲያን እና የየኔታ ዮፍታሄ ንጉሴን ፍጥጫ አውስቶ፥ በፋቼታ ኔራ ኩርባ ታጥፎ፥ መሰንቆ እንደ ጦር መሣሪያ የተቆጠረበትን አውድ አውግቶን ይነጉዳል። የሀገር ፍቅር ማኅበርን ከአመሠራረቱ ጀምሮ የነበረውን ታሪክ ለመሰነድ የሄደበት ርቀት እሚደንቅ ነው። የቀብር ቀኑን በገዛ ሙዚቃው ከታጀበለት አሰፋ አባተ፥ እስከ ሙዚቃ የዋጠው ፖለቲካ (አሊ ቢራ)፥ ከሜሪ አርምዴ ታሪክ የአበበ ፍቅር እስካናወዛት አስናቀች ወርቁ ድረስ ያሉ የሕይወት ታሪክ መድብል ብዙ የተለፋበት ሥራ መሆኑን ያሳብቃል። የተለያዩ የሙዚቃ ባንድ ታሪኮችን ማካተቱ ሲገርመን፥ ዓይነስውራን ሙዚቀኞችን ማውሳቱ ደግሞ እጅግ አስደንቆኛል። የ700 ሙዚቃዎች "ካታሎግ" ደግሞ ሌላ ታሪክ ነው።
ደራሲውን እጅ ነስተናል! በንባብ ይለቅ ብለናል! በኢትዮጵያ ሙዚቀኞች ማኅበር፥ በሀገር ፍቅር ማኅበር፥ የሙዚቃ ባንዶች ማኅበር ... ተጋግዘው መሥራት የነበረባቸውን የቤት ሥራ በአንድ ሰው ትከሻ ብቻ መሞከሩ አጃኢብ እንድንል አሰኝቶናል።
#ጠመንጃና_ሙዚቃ
#ይነገር_ጌታቸው
በመደብራችን ያገኙተል👍👍
የቴሌግራም ቻናላችን 👉👉👉 @azop78
የሚፈልጉትን መፅሀፍ ለማዘዝ @Mesay21
የቻናላችን ተከታይ ስለሆኑ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው ።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
📚📚📚📚📖📖
(ሕይወት)
ሕይወት ጭለማ ነው የምንጓዝበት
የደስታችን መብራት፤
መንገድ አሳይቶን ወዲያው የሚጠፉ
የመከራ ዝናም ችግሩ ሲያካፉ
/ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ፤ ለልጃቸው ለፈቃደ ሥላሴ የፃፉት ምክር፤/
ልጄ ሆይ፤ አንተ አስቀድመህ በሰው ላይ አትነሣ፤ ሰው በአንተ ላይ ቢነሣብህ ግን እንዳትሸነፍ ጠንክረህ መክት፡፡ እምነትህንም በእግዚአብሔር ላይ አድርግ፡፡
ልጄ ሆይ፤ ሰው ሳይኖር ብቻህን ከሴት ጋር አትነጋገር፡፡ ባሏ አለመኖሩን በደጅ ጠይቀህ ከደጅ ተመለስ እንጂ ወደ ቤት አትግባ፡፡ ሰው ሳይኖር ብቻህን ከሴት ጋር የተነጋገርህ እንደ ሆነ ግን፤ ምንም ሌላ ምስጢር ባይኖራችሁ በመነጋገራችሁ ብቻ መጠርጠር አይቀርም፡
ልጄ ሆይ፤ እስቲ ያለፉትን ሰዎች ሁሉ አስባቸው፡፡ እነዚያ ሁሉ ጀግኖች ሁሉም መሬት ሆነዋል፡፡ እነዚያ ሁሉ ዓለመኞች፤ እነዚያ ሁሉ ቀልደኞችና ፌዘኞች፤ እነዚያ ሁሉ ግፈኞች፤ እነዚያ ሁሉ በድኃ ላይ የሚስቁና የሚሳለቁ ሁሉም መሬት ሆነዋል፡፡ እነዚያ ሁሉ ድሆች ሲበደሉ፣ ሲያዝኑ፣ ሲያለቅሱ ካንዱ ሀገር ወደ ሌላው ሀገር ሲሰደዱ፣ ሲራቡ፣ ሲጠሙ፣ ሲታረዙ የነበሩ መሬት ሆነዋል፡፡
ስንት ሰዎች የነበሩ ይመስልሃል?
የድኃ እንባ ሲፈስ የወንዝ ውኃ የሚፈስ የሚመስላቸው ስንት ሰዎች ነበሩ፡፡ ድኃ ሲጮህ ውሻ የሚመስላቸው ስንት ሰዎች ነበሩ፡፡ ድኃ ታስሮ ወይም በሌላ ጭንቅ ነገር ተይዞ ሲሞት የወፍ ግልገል የሚሞት የሚመስላቸው ስንት ሰዎች ነበሩ፡፡ ጉልበት ካለን ብለው በደካሞች ላይ ያሰቡትን ሁሉ የሚሠሩ ስንት ሰዎች ነበሩ፡፡ ሰውን ለማጥፋት እጅግ የሚጥሩ ሰውን ካላጠፉ እንቅልፍ የማይወስዳቸው ስንት ሰዎች ነበሩ፡፡ ነገር ግን ከዚህ ቀድሞ የነበሩት ሁሉም መሬት ሆነዋል፡፡ ከመሬት የተገኘ ሁሉ መሬት ስለ ሆነ ወደ መሬትም የማይመለስ ስለሌለ እኛም ነገ እንደዚያው እንሆናለን፡፡
ስለዚህ በማናቸውም ምክንያት ቢሆን፤ የሰው ደስታውና አዘኑ እጅግ አጭር መሆኑን በጣም እወቅው፡፡
ልጄ ሆይ፤ ሰው ምንም ብልህና አዋቂ ቢሆን በራሱ ሥራ ብቻ ራሱን ችሎ እንደማይኖር ዕወቅ:: ነገር ግን ሁሉም በየሥራው ጸንቶ እርስ በርሱ በሥራ ይፈላለጋል:: ስለዚህ ሰውን ሁሉ አክብረህ ኑር እንጂ ሰውን አትናቅ ሥራውንም አትንቀፍ::
ልጄ ሆይ: አካልህና ልብስህ ዘወትር ንጹህ ይሁን:: እጅህን ለሥራ: ዓይንህን ለማየት: ጆሮህን ለመስማት ፈጣኖች አድርግ:: አፍህን ግን በጠንካራ ልጓም ለጉመህ ያዝ:: አረጋገጥህ በዝግታ አነጋገርህ በለዘብታ ይሁን:: ያልነገሩህን አትስማ: ያልስጡህን አትቀበል: ያልጠየቁህን አትመልስ:: ሽቅርቅር አትሁን: ንብረትህ ተጠቅላላ ይሁን: ምግብና መጠጥህ በልክ ሆኖ ያው የጠዳና የጣፈጠ ይሁን::
ልጄ ሆይ ፈቃደ ሥላሴ፤ አሳብ አታብዛ፤ ወደ ፊትም ምን ነገር ይመጣ ይሆን ብለህ አትጨነቅ፤ ምንም አሳብና ጭንቀት ብታበዛ የሚሆን ነገር ሳይሆን አይቀርም፡፡ ወደ ፊትም እሾማለሁ፤ እሸለማለሁ፤ ብለህ በአሳብህ ደስ አይበልህ፡፡ ለሰውም አትናገር፤ ምናልባት ከተናገርህ በኋላ ሳታገኘው የቀረህ እንደ ሆነ ታላቅ ኀፍረት ይሆንብሃልና፡፡ ወደ ፊት የሚያናድድ ሥራ አትሥራ፡፡ በገዛ እጅህ በሠራኸውና ባለፈው ሥራ አትናደድ፡፡ ልጄ ሆይ፤ ጌታ ለመሆን ትፈልግ እንደ ሆነ ጌትነት ማለት ያለ አሳብና ያለ ጭንቀት መኖር ነው፡፡ አሳብህም ሁሉ ከሞትህ በኋላ ወዲያኛው ዓለም ስለሚሆነው ስለ ነፍስህ ነገር ይሁን እንጂ በዚህ ዓለም በሥጋህ ስለሚሆነው ነገር እጅግ አትጨነቅ፡፡
የቴሌግራም ቻናላችን👉👉👉 @azop78
የቴሌግራም ጉሩፓችን👉👉👉 @azopbook
#ማንኛውንም መፅሐፍ ለማዘዝ @Mesay21
የቻናላችን ቤተሰብ ስለሆኑ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነውና ለወዳጅ ዘመደዎት ሊንካችንን ያጋሩት።
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
🙏🙏🙏🙏
ሕፃኑ የሆነ ድምፅ አወጣ። ዮሲ ውሻዋን ትቶ በሩን ዘግቶ ወደ ልጁ ሄደ ። ሙዳዩን አንስቶ መኝታ ቤት ይዞት ገባ ። ዐልጋ ላይ አብራው እዚህ ቤት የገባቸው ምትክ የተባለችው ልጅ ጋቢ ደርባ ተኝታለች ።
-- አመጣሁት አለ
-- ለምን?
-- እንጃ ፈራሁ.....
ምትክ የለበሰችውን ጋቢ ገለጠችና ቁጭ አለች ፡፡ እጅዋን ወደ ዮሴፍ ዘረጋች ።
-- ዮሴፍዬ ልጄን ልየው በማርያም አለች
-- ለመሆኑ የልጁን ስም ማን ትይዋለሽ ምትክ?
--እ ስሙን? እ? 'ማኩታ' ። አንድ የእኔ ቢጤ አሮጊት ማኩታ ሁኚ ይሉኝ ነበር ። ትርጉሙን አላውቅም ዮሲዬ ። ምንም እንጃ ።
-- ማኩታ እንዴት ስም ሊሆን ይችላል? ትርጉሙን ካላወቅሽ?
-- እንጃ
-- ግን ሲመርቁኝ ነው እንደዛ የሚሉት....ስለዚህ በቃ ስም ይሆነዋል
ዮሴፍ ፈገግ እያለ ሄዶ ልጅዋን ከነሙዳዩ ሰጣትና ዐልጋ ዳር ተቀመጠ ። ምትክ ተቀብላ ፍጡሩን አየችና በአመልካች ጣትዋ በቀስታ ፊቱን ነካካችው ። ሳቅ ተሰማ
-- ይስቃል! አለች..... አይኖቿ በመገረም ተከፈቱ
ዮሴፍ መዳይ ያልያዘ እጅዋን አነሳና ሳመው ።
-- መስኮቱን ልክፈት? አለ
-- እሺ ክፈተው አለች ዓይኖቿን ከልጁ ሳታነሳ
ዮሴፍ ከተቀመጠበት ተነስቶ ሄደና ግራና ቀኝ አንድ ሰፊ መስኮት ከፈተ ። ቢጫ ብርሃን ተገድቦ እንደነበረ ውሃ ጎርፎ ገባ ። ደነገጠ ።
-- እዪ ምትክ የዚህ ዐይነት ብርሃን አይተሽ ታውቂያለሽ?
ምትክ ወደቆመበት ዞር ብላ በድንጋጤ ፡
-እንዴ- ? ዮሲ! አለች ።
መኝታ ቤቱ ወለል ላይ ሰፊ አራት ማዕዘን የፀሐይ ርግብግብታ አርፏል ። የተቃቃ ወፍራም ቢጫ ኩታ ይመስላል ። ዮሲ ጐንበስ ብሎ እጁን እዚህ ሥነ-ጸዳል ውስጥ አስገባ ፡፡ አጁ በቢጫ እሳት የተያያዘ ጥጥ መሰለ ፡፡ እጁን ወደ ጥላው መለሰው ፡፡ እንደገና መልሶ ብርሃን ውስጥ ከተተው ። ምትክ በጋቢ ተጠቅልላ ከዐልጋዋ ተነሳችና ሙዳዩን ፀሐዩ ብርሃን መሃል አመቻችታ አስቀመጠችው ። ሞሳው መሳቅ ጀመረ ። የልጁ ሙዳይ ብቻ ሳትሆን መኝታ ክፍሉ በውህዋሄ ተሞላ ። እውጭ ባለው እርጥበት የተነካ ያልመሰለ ሙቀት ክፍሉ ውስጥ ተረጋግቶ ተቀመጠ ። ከወዲያ ከውጭ መኪናዋ ከቆመችበት ጀምሮ እስከ ቤቱ ግድግዳ ጥግ ያለው የሲሚንቶና የአፈር መሬት በነፀረፃይ በማለለ አደይና ጨሌ
ተሸፈነ ።
ቀድሞ ያልነበሩ በጎችና ላሞች ከየት እንደመጡ ሳይታወቅ እዛ ላይ ፈሰሱ ። አንድ ሁለቱ ወደተከፈተው መስኮት ተጠግተው ፊታቸውን ልጁ ወዳለበት አዙረው የጋጡትን ሳር ማመንዠካቸውን ቀጠሉ ። ዮሴፍና ምትክ ተቃቅፈው ወደ ዐልጋው ሄዱና ጎን ለጎን ተቀመጡ ። በመለዋወጥ ላይ ያለውን ግቢ አፋቸውን ከፍተው ያያሉ ። ዮሴፍ የምትክን ጉንጭ በእጁ ዳበሳት ። እንዳፈረች ሁሉ ኣይኖቿን ጨፍና ኩታ ፊቷ ላይ ደረበች ። በቀስታ ገፈፋትና አተኩሮ አያት ፡፡
-- ምነው ? አለችው
ወደ ደረቱ አጥብቆ ሳባትና አናቷ መሃል ሳማት ። በመከሰት ላይ ያለውን ተአምር ማየታቸውን ቀጠሉ ።..
📖 #የስንብት_ቀለማት
✍ #አዳም_ረታ
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋልን።
🙏🙏🙏
የትግራይና የኤርትራ ተወላጆች በአጠቃላይ ሊሆኑ አይችሉም፡፡
በሺህ ዓመታት በሚቆጠር ታሪካችን ውስጥ ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ ለማድረግ በየጊዜው በሕይወታቸው መስዋዕትነት ከከፈሉት ውስጥ የኤርትራና የትግራይ ተወላጆች ከማንም ያላነሰ ክብር ተጎናጽፈው ይገኛሉ፡፡ በአጠቃላይ ስንናገር ጉልሁ እውነት ይህ ነው። የኤርትራም ሆኑ የትግራይ ተወላጆች በአጠቃላይ አሁን በኢትዮጵያ ላይ በደረሰው አዲስ ነገር የታሪክ ሐፍረት ተሸካሚዎች አይሆኑም ያንን ለሻቢያና ለወያኔ ብቻ እንተውላቸው፡፡ ክብርም ከሆነ ይከበሩበት፤ ሐፍረትም ከሆነ ይፈሩበት።
በኢትዮጵያ ላይ የደረሰው ከኢጣልያ ወረራ ጋር የተያያዘ ነው። የምድረ ባሕርን ወይም የመረብ ምላሽን ስም ኤርትራ ብላ የለወጠች ኢጣልያ ነች፤ የመሬቱን ክልል በውል ያሰወሰነች : ኢጣልያ ነች፡፡ ይህ የሃምሳና የስድሳ ዓመት ታሪክ በሺህ ዓመታት የሚቆጠረውን የኢትዮጵያ ታሪክ በክህደት ለውጦ፣ ኤርትራ በኃይል _ ከኢትዮጵያ አንድትለይ አድርጎአል፡
ችግሩን በትክክል ለይተው ካላወቁት መፍትሔ የተባለው ሌላ ችግር ሆኖ እናገኘዋለን፡፡የኢትዮጵያ ሕዝብ ችግር የሥልጣን ባለቤትነቱን የነጠቀው የአገዛዝ ሥርዓት ሆኖ ሳለ ችግሩ አማራ ነው ተብሎ በጦርነት ኤርትራ ተገነጠለች፣ በዚህም ምክንያት አንድ የአገዛዝ ሥርዓት በነበረበት አገር ሁለት የአገዛዝ ሥርዓቶች በቀሉበት፡፡ አሁን ደግሞ ችግሩ ትግርኛ ተናጋሪ ነው ይባላል፣ ሌላ ስሕተት፣ የሚሠራውም ወደሌላ የስሕተት ውጤትና አገርን ወደማፍረስ ነው፡፡ ተገድደን የገባንበትን ቁልቁለት ሳንጨርሰው መንቃትና አቅጣጫችንን ለመለወጥ ቆርጠን መነሣት አለብን፡፡ እስቲ ከየት ተነስተን የት እንደደረስን እንመርምረው፡፡
የክህደት ቁልቁለት መጽሐፋቸው ገጽ 17 የተወሰደ !!!
ጽንዐ ተዋሕዶ የተሰኘው ይህ የበአማን ነጸረ መጽሐፍ ከካቶሊክ፣ ከቅብዓት፣ ከጸጋና ከተዋሕዶ ጋር በተያያዘ የሚነሡ ብዙ ታሪካዊ ነገሮችን ያጠራል። ከአስተምህሮ አንጻር የሚነሡ ነገሮችንም ተላውያነ ሐዋርያት (Apostolic Fathers) ከሚባሉት የሁለተኛው ክፍለ ዘመን ሊቃውንት አንሥቶ በዘመናችን እስካሉት ሊቃውንት ድረስ ሥራዎቻቸውን በማቅረብ ይመረምራል። በቅርቡ በታተሙ መጻሕፍት ውስጥ ያሉ የተቀብዐ ተኮር ጥቅሶች ትርጓሜ ላይ ያስተዋላቸውን ዋና ዋና ስሕተቶችም ነቅሶ በማውጣት ከጥንት አባቶች ጀምሮ በመጣው ኦርቶዶክሳዊ ትርጓሜ ያበጥራቸዋል። ሌሎች ጉዳዮችንም በጥንቃቄ ይመረምራል። እስካሁን በተጻፉ መጻሕፍት ላይ የያዝናቸውንም ትውፊታዊ ታሪካዊ መቼቶችን ቀዳማይ ምንጮችን በማሳየት በተገቢው መንገድ ይሞግታል። በዚህም ምክንያት ነገረ ተቀብዐን ከነታሪካዊ ዐውዱ በአግባቡ እንድንረዳው ለማገዝ ይህን የበአማን ነጸረን ጽንዐ ተዋሕዶን የሚመስል ሌላ መጽሐፍ እስካሁን አላገኘሁም።
በሥነ ጽሑፋዊ አቀራረቡም በእጂጉ አስተማሪ ነው። ታሪካዊ ጉዳዮችን የሁለቱንም ወገን ቀዳማይ ምንጮች በማቅረብ እያከራከረ፣ እየመረመረ በዲስኩር ትንተና (Discourse Analysis) በማቅረብ _ ለአንባቢ ፍሬ ነገሮችን ያስጨብጣል። የተቀብዐን ጉዳይ ሲያቀርብም ከጥንቶቹ ሊቃውንት በማሳየት ጀምሮ በቅርብ ጊዜ የወጡ መጻሕፍት ላይ ያሉ ጉዳዮችን ስሕተታቸውን በአጉሊ መነጽር በማቅረብ ለእኛ ዘመን ግልብ አንባቢ ለማሳየት የሔደበት ርቅት አስደንቆኛል። ስለዚህም አቀራረቡ ራሱ በቅንነት መማር ለሚሹ ሁሉ መማሪያ እንደሚሆን እምነቴ ነው።
ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ (በሥነ ድርሳን ሁለተኛ ዲግሪ)
ኤዞፕ መፃሕፍት !!!
ወደ መክሊት ሽሽት፤ ‹‹ራስ››
(ዮናስ ታምሩ ገብሬ - አዲስ አድማስ፣ 19፣09፣15)
#መነሻ - ‹‹ራስ›› የደራሲ ፍሬ ዘር ሥራ ነው፤ በ275 ገጽ ዕድሜው በነጠላ ውጤት የተቋጨ ልብ-ወለድ ሲሆን፣ በዋና ገጸ-ባሕርይው (በራስ) ተራዳኢነት እየታገዘ ጭብጡን ተርኳል። ‹‹ራስ›› ለምርጫችንና ለመክሊታችን ቁብ የማይሰጠውን የትምህርት ሥርዐት በወጉ የሚያስቃኝ ድርሰት ነው ብዬ አምናለሁ። በድርሰቱ ውስጥ ‹‹ራስ›› የተባለ ብላቴና በአንገሽጋሹ የትምህርት ሥርዐት ምክንያት አልጋው ቀጋ ይሆንበታል፤ እክፍል ተገኝቶ ትምህርት ከሚከታተል በደዌ ተሰቅዞ የአልጋ ቁራኛ ቢሆን ይመርጣል። ታዲያ ይኼ ብላቴና ያልተጠራበት ድግስ እንደሚቀላውጥ ሰው ውርክብ ውስጥ ይዘፈቃል። ቆሞ መሄድ ሳይችል ብዙ ቁምነገር ይጠበቅበታል፤ ውጤታማ ሊሆን ባለመቻሉ ወደ አያቶቹ ቀዬ ይከተታል - ወደ ገጠር። እዚያ ዛፍ ተካይ ሆነ፤ በትምህርቱ ቢወቀስም መንደሩንና ሀገሩን ታደጋቸው። ‹‹ራስ›› ከተነባቢነት በተረፈ በርከት ያሉ ረድኤቶችን ጀባ የሚለን ድርሰት ነው የሚል እምነት አለኝ። እንሆኝ…
#ሽፋን እና ርእስ - የመጻሕፍ ሽፋኑ ሙሉ በሙሉ ዋናውን ገጸ-ባሕርይ ‹‹ራስ››ን የመግለጽ ሙከራ ነው። ሽፋኑ እንደምንመለከተው የገጸ-ባሕርይውን ሥራ/ተግባር በከፊል ይወክላል ብዬ አምናለሁ። ብሎም ስዕሉ ከድርሰት ሐሳቡ ጋር የማይቃረንና ግልጽ የሆነ መሆኑ ዕሙን ነው። በግሌ እንደ አለመስማማት የማነሳው ሐሳብ ቢኖር፣ የመጻሕፉን ርእስ የሚወክል ስዕል ተስሎ ሳለ ሥሙ አብስትራክት መሆን መቃጣቱን ነው፤ ለዚህም ‹ራ›ን መመልከት ይቻላል፤ የሰው ፊት የመሰለ ድብቅ ስሜት በርእሱ የመጀመሪያ ፊደል ላይ መካተቱ ድረታ ይመስለኛል።
#የገጸ-ባሕርይ አሳሳል - የሀገሬ ሰው ‹‹ሥምን መልአክ ያወጣል›› የሚላት ብሒል አለችው። በድኅረ-ዘመናዊ ሥነ-ጽሑፍ ሥም ግለሰብን፣ ቦታን፣ ድርጊትን… ወዘተ. ይወክላል። የድርሰት ጭብጥና የገጸ-ባሕርይ አሳሳል የጠለቀ ቁርኝት አላቸው። በድርሰት ለተቀረጸ ገጸ-ባሕርይ ሥራውንና ሥሙን የሚሸት የሥራ ድርሻ መስጠት የተለመደ ነው። የሥራ ድርሻን መሠረት አድርገን የምንሰይመው ሥም ተውላጠ-ሥም በመባል ይጠራል። ድርሰቱ ከቀጥተኛ ሥም ይልቅ ተውላጠ-ሥምን መሠረት በማድረግ ገጸ-ባሕርያትን ሠይሟል፤ ገጸ-ባሕሪያቱም በልካቸው የተሰፋላቸውን ሥራ ሲከውኑ እናስተውላለን። ለአብነት ‹‹ራስ›› የተባለ ማቲ በንጡልነት የራሱን የስኬት ዓለም ሲኖር አስተውለናል።
#ሥነ-ውበት/Aesthetic - በድርሰቱ የተካተቱ ውበታም ቃለት፣ ሐረጋትና ገለጻዎችን እንጥቀስ፡- ‹‹ያስኳላ ጠንቋይ›› (ገጽ 9)፣ ‹‹የንብ እናት ሆንኩ›› (ገጽ 29)፤ ‹‹ላስራ አምስት ደቂቃ እረፍት ሁለት ሰዓት ሙሉ መጓጓት የየለት ተግባሬ ነው›› (ገጽ 1)፣ ‹‹ዓይኑ ተሸነቆረ›› ገጽ 32)፤ ‹‹የቤት ሥራ ሲል ላዬ ላይ ቤት የተሰራብኝ ያህል ትንፋሽ ያጥረኛል›› (ገጽ 2)፣ ‹‹በውርርድ ተሸንፌ ያበሳጨሁት እኔ ሌላው ብስጭቱ ነኝ›› (ገጽ 40) እና ሌሎች በውበታቸው ልብን የሚያሞቁ ትረካዎችን መጥቀስ ይቻላል። በተጠቀሱ መዘርዝሮች አጽንኦት መስጠት ያሻው ጉዳይ እንዳለ መመልከት እንችላለን። የዓረፍተ-ነገር አጀማመር የሥነ-ውበት አንድ አካል ነው፤ የመጀመሪያ ዓረፍተ-ነገር ሰዓቢ፣ ግልጽ፣ እንዲሁም የተነባቢነትንና የአንባቢን ትኩረት የሚስብ መሆን እንዳለበት ይታመናል። ገጽ 1፡- ‹‹ትምህርት አልወድም።›› ብሎ ይጀምራል። ይኼ የሚያሳየው ደራሲው የመጻሕፉን ጽንሰ-ሐሳብ በመጀመሪያዋ ዓረፍተ-ነገር ለመወከል ሲል በተደጋጋሚ እንደከለሰ/እንደሠረዘ ነው።
#ቁስ አካላዊ መሣሪያዎች/Mechanical Devices - ቁስ አካላዊ መሣሪያዎች በኢታሊክስ የተጻፉ ዓረፍተ-ነገሮች፣ የተሠመረባቸው ሐረጋት፣ በቃለ-አጋኖ የሚያልቁ ገለጻዎችንና ሌላንም ያካትታል። የዚህ ቴክኒክ ጠቀሜታ በትረካ ወቅት የሚስተዋሉ የአቅጣጫ፣ የሂደትና የጊዜ መለዋወጦች እና የገጸ-ባሕርይውን ትኩረትና አጽንኦት መጠቆም ነው፤ በታሪኩ ውስጥ ምን እየሆነ እንደሆነ አመላካች ናቸው። ለማሳያ፡- ‹‹ኧረ በታባ!››፤ ‹‹እንደ ፈራሁት!›› (ገጽ 85)፤ ‹‹ዝም!›› (ገጽ 85)፤ ‹‹በታባ!›› (ገጽ 191)፣ ‹‹በሞትኩት!›› (ገጽ 177)፣ ‹‹በታባ ሞት!››፣ ኧረ ምንድነው በታባ!›› ገጽ 265) እና በርካታ በኢታሊክስ የሰፈሩ ዓረፍተ-ነገሮችን መጥቀስ ይቻላል።
#የቃላት መረጣ እና ምጣኔ - በድኅረ-ዘመናዊ ሥነ-ጽሑፍ ደራሲ መረን ነክቶ የሥነ-ጽሑፍ ሐሳቡን ማካለብ የለበትም፤ በቋንቋ አጠቃቀም ረገድ የድርሰቱ ዋና ገጸ-ባሕርይ ልጅ ስለሆነ ቀላል አማርኛን በመጠቀም በእያንዳንዱ ክስተት መሀል ብቅ እያለ ግብረ-መልስን ሰጥቷል የሚል እምነት አለኝ። ብሎም፣ ደራሲው ለዋናው ገጸ-ባሕርይ ግዝፈትን ለመስጠት በማለም ከአድራጊ ወደ ተደራጊ (active voice) የመተረክ ቴክኒክን ተጠቅሟል።
ደራሲ በቋንቋ አጠቃቀሙ እና በብዕር አጣጣሉ ቁጥብ መሆን እንዳለበት ይነገራል። በንባብ ወቅት የሚከተል መታከትን፣ የሐሳብ መሸራረፍን፣ የፍሰት መወለካከፍን ለመቅረፍ ሲባል የድርሰት ሐሳብ በተንዠረገገ ቋንቋ ባይገለጽ መልካም እንደሆነ ስምምነት አለ። ‹‹ራስ›› በተመጠኑ ቃላቶች፣ በውስን ሐረጋት እና በአጫጭር ዓረፍተ-ነገሮች የመተረክ አባዜ ይታይበታል። ምሳሌ እንጥቀስ፡- ‹‹በገላጣ ስፍራ እየተራመድኩ እግሬ ይማታብኛል፣ ንፋስ ያደናቅፈኛል፣ የማውቀው መልሱ ይጠፋኛል፣ ስሜ ራሱ ይዘነጋኛል›› (ገጽ 11)፣ ‹‹ሰርቶ ማሳየት አይቸግረው፣ ለማስረዳት ቃል አያጥረው›› (ገጽ 139)፣ ‹‹በምንም አትደሰትም፣ ማንንም አትቀየምም፣ በምንም አትናደድም›› (ገጽ 158)፣ ‹‹ከውስጥ ስጠብቃት ከውጭ ተከሰተች። አብርታለች! ደሞ ደብተር ይዛለች›› (ገጽ 219)። ከላይ በምሳሌ የጠቀስኳቸውና ሌሎች ቃላት፣ ሐረጋትና ዓረፍተ-ነገሮች ቁልቁል ቢደረደሩ ግጥማዊ ለዛ እንደሚኖራቸው አልጠራጠርም።
#የአፈ-ታሪክ እና የምሳሌያዊ አነጋገር ፈጠራ - ደራሲ በትረካ ዐውድ ውስጥ፣ ወይም በሚቀርጸው ገጸ-ባሕርይ አስገዳጅነት ያልነበሩና አዳዲስ ተረቶችን፣ ምሳሌዎችን፣ አፈ-ታሪክን የመፍጠር ዕድሉ ሰፊ ነው። ‹‹ራስ›› በርካታ አፈ-ታሪኮች፣ ተረትና ምሳሌዎች፣ ሥነ-ቃል እና ምሳሌያዊ አነጋገሮች የተፈጠሩበት ልብ-ወለድ ነው። ነባሩን በአዲስ በመተካት (deconstruction) ደራሲ ፍሬ ዘር በትረካ ዐውዶቹ እንዲሁም በገጸ-ባሕርይው ጠባይ ምክንያት የተለያዩ ሥነ-ቃሎችን፣ ተረቶችንና አፈ-ታሪክን ፈጥሯል፤ ማሳያ እንጥቀስ፡-
‹‹ባንድ ድንጋይ ሁለት ጊዜ ተፈነከትኩ›› (ገጽ 4)፣ ‹‹ከተማ - ከሌሎች ተፋፍጎ ማደር›› (204)፣ ‹‹ወማ - ወንድማለም›› (ገጽ 34)፤ እንዲሁም በገጽ 21፣ 35፣ 39፣ 43፣ 53፣ 127፣ 252 (ሥነ-ቃል)… ወዘተ. የተካተቱ ሐሳቦችን መጥቀስ ይቻላል። ከላይ የጠቀስኳቸው ማሳያዎች የዋናውን ገጸ-ባሕርይ መገለጫዎች የሚወክሉ ናቸው የሚል እምነት አለኝ።
#ዘይቤአዊነት - ፍሬ ዘር ድንቅ የሆነ ተምሳሌት ይቀምማል። በSimulation/ፍጹም ተቃራኒ የሆኑ ሁለት ሐሳቦችን በማገናኘት ጉዳዩ ትኩረት እንዲስብ ያደርጋል። ዘይቤዎቹ በአብዛኛው አነጻጻሪ ሲሆኑ ዋናው ገጸ-ባሕርይ ቋንቋን በመጠቀም ፍትሐዊነትን፣ እውነታን፣ የሐቅ መዛባትን፣ የነገሮች አለመገጣጠምን፣ ግነትን… ይመረምራል። ደግሞ ዘይቤዎቹ ሙድ ዓይነት ትረካ መምሰላቸው ነው።