ኤዞፕ ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት። በምኒልክ አደባባይ ፊት ለፊት ያለው የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን ህንፃ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ ነው !! ስልክ:- 09 11 72 36 56 ለማዘዝ @Mesay21 @Mesay21
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ከሚጠኑ ጉዳዮች አንዱ
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሣኤው ነገር ነው። አስቀድሞ ሐዋርያት፤
በኋላም ሊቃውንት በመጽሐፍ የጻፉት በቃል የሰበኩት ትምህርት በመሆኑ ተስፋ ለምናደርገው ለትንሣኤ ዘጉባኤ ምስክር ሆኖልን በአንቀጸ ሃይማኖት ምዕመናን ከሚደርሱበት ቅርብ ስፍራ ላይ ተጽፎ በሁልጊዜ ጸሎታችን ውስጥ “#ወንሴፎ #ትንሣኤ #ሙታን #ወሕይወተ #ዘይመጽእ #ለዓለመ #ዓለም" እያልን በተስፋ ስንጸልየው እንኖራለን። በዘመናት ሁሉ የሚነሡ የቤተ ክርስቲያን መምህራን በቃልም ሆነ በመጽሐፍ በተቻላቸው ነገረ ሃይማኖትን መስክረው ሊያልፉ ይገባልና
መምህር ናትናኤል ከመምህራን የተቀበሉትን እውቀት በዚህ መጽሐፍ በኩል ለቤተ ክርስቲያን ሲያበረክቱ አንብበው የሚጠቀሙ ተስፋ ትንሣኤን በልባቸው ይዘው በሃይማኖት ደስ የሚላቸውን ምዕመናን በማሰብ ልቤ በደስታ ይሞላል። ይህን ትምህርተ ትንሣኤን የሚሰብክ መጽሐፍ አንብባችሁ ትንሣኤ ልቡና ይደረግላችሁ ዘንድ ምኞቴ ነው።
#ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ
የአራቱ ጉባኤያት መምህር እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢ
መድኅነ ዓለም ክርስቶስ ድኅነተ ዓለምን ከፅንሰቱ እስከ ዕርገቱ በሠራችው ሥራዎች ፈጽሟል። በዚህ የአድኅኖተ ዓለም ጉዞው የተከናወኑ የተዋሕዶ፣ የተገናዝቦ፣ የከዊን፣ የተዐቅቦ፣ የግብረ ቤዝዎ እና የግብረ አርአያ ተግባራት በጥንቃቄ የሚታዩ እና የሚተረጎሙ ምሥጢራት አሉባቸው። ቅዱሳን ሊቃውንት አባቶቻችንም እድሜአቸውን ያሳለፉት እነዚህኑ ምሥጢራት በተገቢው መንገድ በማብራራት ነው።
በተለይም ጌታችን ከተነሣ ጀምሮ እስከ ዕርገቱ የተናገራቸው ቃላት እና የሠራቸው ሥራዎች
ለአንዳንድ ተጠራጣሪውች የማሰናከያ ደንጋይ ሁነውባቸው እስከ ዘመናችን ዘልቀዋል።
በመ/ር ናትናኤል ባየ የተዘጋጀችው እና በክርስቶስ ትንሣኤ ዙሪያ ትኩረቷን ያደረገችው
“መጽሐፈ ትንሣኤ ለመናፍቃኑ ተሰናክሎ ማሰናከያ የሆኑ ምሥጢራተ ተዋሕዶን
በማብራራት እና ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ በመስጠት ሁነኛ መፍትሔ ሁና አግኝቻታለሁ:: ኦርቶዶክሳውያንም ከኦርቶዶክስ ውጭ ያሉትም ቢያነቧት ላሉት መጽኛ ለጠፉት መገኛ ትሆናለች እና አንብባችሁ ተጠቀሙ እላለሁ።
መ/ር ኀይለ ማርያም ዘውዱ ዘቦሩ ሜዳ
የታላቁ ባለቅኔ ሎሬት ፀጋየ ገብረ መድህን መጽሐፍቶች
፩ እሳት ወይ አበባ
፪ ምጥቀት በቅኔ አክናፍ
በገበያ ላይ ውለዋል።
አከፋፋይ ኤዞፕ መጻሕፍት !!
ኤዞፕ ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት። በምኒልክ አደባባይ ፊት ለፊት ያለው የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን ህንፃ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ ነው !!
ስልክ:- 09 11 72 36 56
የሱባ ቋንቋ
❖ ሉባ፡- ማለት ሰብዕ/ሰው/ሰብአዊ የአማረ አበባ ማለት፤ ለሁሉም ቋንቋ ነባር አላቸው
❖ ነባር የምንለው የሚጠሩበት ስም የአባቶቻችን የአገርየወንዝ፤ ስም በቋንቋው እንዲሰየምና ስሙ ከቋንቋ በፊት ስለነበረ ነባር ይባላል፡፡
10 አናባቢ አስማተ መለኮት
33 ተናባቢ ፊደሎች ያሉት ድንቅ መጽሐፍ በቅርቡ ገበያውን ይቀላቀለዋል።
በቅርብ ቀን በገበያ ላይ ይውላል
ኤዞፕ ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት። በምኒልክ አደባባይ ፊት ለፊት ያለው የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን ህንፃ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ ነው !!
ስልክ:- 09 11 72 36 56
ለማዘዝ
@Mesay21
@Mesay21
አዲስ መጽሐፍ ወደ ገበያው ተቀላቅሏል።
ሻሞ
ብሩክ በቀለ
ለውጥ ግዙፉ ቅስመ አፈጣጠር _ ነው። _ ሁሉ ይለዋወጣል። አዘገመም ፈጠነም። በአንድዬ ፈጣሪም ሆነ በሥነ ሳይንስ ቢዘወር_ _ሁሉ ከለውጥ አያመልጥም፡፡ እዚህም "ሻሞ" ብለን ዓለም ብንፈጥርበጊዜና በሁኔታ ተለውጦ እኛ ጋር በደረሰን እውቀትና መረዳት ነው። ከአንደበታዊ ተረት ነጋሪነት_ _ወድጽሕፈታዊ ተረት ነጋሪነት ተሸጋግረን ነው። የአንደበቱ ባይቀርልንም(ተፈጥሮ ነውና) በስልጣኔም _ እገዛ ደግፈን ልናኖረው_ _ጽሕፈትን ፈጥረን ጽሑፋዊ ትረካንና ተራኪን አስገኘን።
የ"ሻሞ"ን ልቦለዳዊ ዓለም ገንቢና ጊዜን ፈጣሪ _ _ ጓድ ብሩክ በቀለ ንጉሴም_ _ባልሟሟ አንደበታቸው ሲተርኩ የኖሩ ቢሆንም ነገረ ልቦለዳዊነትንም ይዘው _ጽሕፈታዊ ተራኪ ሆነው አስራ ስድት አጫጭር ልቦለዶችን ይዘውልን ተከስተዋል።
ዮሐንስ ሀብተማሪያም
• እንዲሁም ባለ ግለ ታሪኩ በነበረው ግላዊ ትጋትና ብርታት፣ ከግለሰቦችም ባገኘው ድጋፍ የሥዕል ኤግዚቢሽን ለማሳየትና በታላላቅ የመንግሥት ባለሥልጣናት ጭምር ለማስጎብኘት ችሏል፡፡ ከዚያም ተነስቶም የወደፊት ሕይወቱን መቀየስ እንደቻለ አመላክቶአል፡፡ በመሆኑም አንባቢ፣ በተለይም ወጣቶች ብዙ ምሳሌነት ያለው ቁም ነገር ሊቀስሙበት ይችላሉ፡፡ በኃላፊነት ላይ የምንገኝ ወገኖችም ወጣቶቻችንን መምከርና ማበረታታት የሚያስገኘውን ታላቅ ጠቀሜታ እንቀስምበታለን ብዬ አምናለሁ፡፡
• በወጣትነት ዘመኑ በተሳተፈበት የጋዜጠኝነት ሙያም በኩል ያጋጠሙትን ልዩ ልዩ ውጣ ውረዶች ሲገልጽ እግረ መንገዱን የዘመኑን ሀሳብን የመግለጽ እውነታ ከነተግዳሮቱ ያሳዬናል።
• የሙያ ወይም የነፍስ ጥሪ አድርጎ በመረጠውና በሥነ ጥበብ ምርምር ላይ ከፍተኛ ሥልጠና ለማግኘት በነበረው ፍላጎትና ትጋት ወደ ሶቪየት ኅብረት ሄዶ ትምህርቱን መከታተሉን የመጽሐፉ ሢሶ ያህሉ ገጾች ያስረዱናል፡፡ በዚያ የትምህርት ዘመንም ያሳለፈውን ሕይወት በሚገልጽባቸው ገጾች ሁሉ የሚያቀርባቸው ልምዶች፣ ምንም እንኳን የግለሰብ መስለው ቢታዩም፣ በዘመኑ የውጪ አገር ትምህርት አያያዝ ላይ ጥቂት ብርሃን መፈንጠቃቸው አይቀርም፡፡ የ‹‹መንገዳማውን ረፋድ›› ረጅም ምዕራፍ በጥሞና ማንበብ ያስፈልጋል፡፡ ስዩም ወደሶቪየት ኅብረት ሄዶ እስከተመለሰበት እለት ድረስ ያለውን ውጣውረድ ፍንትው አድርጎ ያሳየበት ምንባብ እንደሆነ ታዩታላችሁ፡፡ በተለይ አገራችን በለውጥ ማእበል ከመናጧ አስቀድሞ ወደ ሩሲያ ሄደው የመማር እድል ከገጠማቸው ውስጥ የፊታውራሪ ተክለሐዋሪያትን ‹‹የሕይወቴ ታሪክ›› ያነበበም ሆነ ይህንን የስዩምን ‹‹ኩርፊያ የሸፈነው ፈገግታ›› የሚያነብ ወገን በተለምዶ ከአብዮት በፊት በምንለው ዘመን ሩሲያውያን ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን የነበራቸውን የላቀ ግምት ሲረዳ እጅግ አድርጎ መደነቁ አይቀርም፡፡ ስዩም ከገጽ 172- 174 ባሉት ትረካዎቹ በሁለቱ አገሮች መካከል ያለውን የቤት እንሰሳትን በተለይም የውሻን አያያዝ ተገን አድርጎ የሚተርክልን ገጠመኝ እንዲሁ ፈገግም ተከዝም የሚያስደርግ ይዘት አለው፡፡ በድምሩ ስዩምን ያጋጠሙት አብዛኞቹ ሩሲያውያን በእምነታቸው እናንተ ኢትዮጵያውያን ‹‹ልዑላን ናችሁ›› እስከማለት የሚደርስ ሰብአዊ ሚዛን እንደነበራቸው እናነባለን፡፡በጠቅላላው ስለአፍሪካውያንም ሆነ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ዓይነትና ስብጥር በወጉ ተርኮልናል ማለት ይቻላል- በ‹‹እነሆኝ›› ላይ በጠቆመን መሠረት ስንመለከተው፡፡
• በጥቅሉም ሲታሰብ፣ ውጪ አገር ሄደው የሚማሩ ተማሪዎች የሚያጋጥሙዋቸውን የአካባቢና የባህል ግጭት ሁሉ በምሳሌ እያጣቀሱ ስለሚያሳዩን አንዳች የመደነቅና የመገረም ስሜት ያድርብናል፤ እርካታም አናጣበትም፡፡ ቡልጋሪያ ሄዶ በአንድ ሆቴል ውስጥ ምግብ ለማዘዝ ያየውን ፍዳና ያጋጠመውን ከበግ ጭንቅላት ጋር ያደረገውን ፍጥጫ ስናነብ ተራኪነቱንም ሰዓሊነቱንም አጣምሮ የያዘ ባለሙያ እንደነበረ ለመመስከር እንገደዳለን፡፡
• በተጨማሪም በልዩ ልዩ የአገር ውስጥና የዓለም አቀፍ ጥበባዊ ጉባኤዎች ላይ በአዘጋጅነት፣ በተባባሪነት፣ በጥናት አቅራቢነት የተሳተፈ በመሆኑ በነዚያ መድረኮች ሁሉ ያገራችንን ኪነ ጥበብ በማስተዋወቅ ረገድ ያደረገውን ጥረት፣ በወቅቱ ስለነበረው ዓለማቀፋዊ የአስተሳሰብና የትኩረት ምርጫ ሁሉ በግልጽ ያቀርብልናል፡፡ በዚያም ሰበብ ታሪካዊ ዋጋ ያላቸውን መረጃዎች እንቃርማለን፡፡ ሌሎችንም በርካታ የይዘት ነጥቦችን ማንሳት ይቻላል፡፡ የራሱን አገር የኪነጥበብ እድገትና ደረጃ በመመዘን ጎደሎው ጎናችን እጅጉን አመዝኖ ያየውና ሲብከነከን እናስተውላለን፡፡ እንዲሁም ወደ ብቃት የማሳደግ ልፋት ተገቢነት ፍንትው ብሎ ይታየውና ወደፊት ለማስኬድ ሲጣጣር ከሚገጥሙት ፈተናዎችና ጣጣዎች ጋር አዋህዶ ያቀርብልናል፡፡
• በሌላም አቅጣጫ፣ በወቅቱ ከየትኛውም አገር ትምህርታቸውን ጨርሰው ወደ አገራቸው ይመለሱ የነበሩ ተማሪዎች ወገናቸውን ለማገልገል የነበራቸውን የመንፈስ ዝግጅት ከአቶ ስዩም ወልዴ ግለ ታሪክ ፍንጭ እናገኛለን፡፡ አቶ ስዩም በፊት ወደ ውጪ ሀገር ለትምህርት የሚሄዱ ወገኖች ፍላጎትና ስሜት ምን እንደነበረ ከአንዳንድ ግለሰቦች ታሪክ ስንሰማው የኖርነው ነው፡፡ ከላይ እንደጠቆምኩት፣ ባለ ታሪኩ ትምህርቱን ጨርሶ ወደ አገሩ የተመለሰበት ወቅት በአገራችን ሥር ነቀል የሆነ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ለውጥ የተደረገበት ነበር፤ ያንን ለውጥ በቀጥታ ተሳታፊ በመሆን ከነውጣ ውረዱ፣ ከነዝባዝንኬው፣ ከነትርምሱ፣ ከነምስቅልቅሉ አቅርቦልናል፡፡ በዘመነ አብዮት መጀመሪያ አካባቢ አገሪቱን አናውጧት ስለነበረው ቀይና ነጭ ሽብር እንዲሁ የሰማውንም ሆነ ያየውን ስቃይና ሰቆቃ ስእላዊ በሆነ መንገድ ፍንትው አድርጎ ያሳዬናል፡፡ ይህንኑም ገለጻውን ‹‹ያልጠረረ ቀትር›› በሚለው ሦስተኛው ምዕራፍ ላይ በሚገባ ገልጾታል፡፡ ስለዚያ አሰቃቂ ዘመን የወ/ሮ ቆንጂትን ምርኮኛ የተሰኘ ልቦለድ ማንበብም የስዩምን ትዝብትና ልምድ ይበልጥ ለመረዳት ያስችላል፡፡
• አንድ ሰው በተሰለፈበት ሙያም ሆነ በሚመደብበት ኃላፊነት ይበልጥም ደግሞ በኮሚቴ ሥራ ውስጥ ተግቶ የሚንቀሳቀስ ከሆነ ለሚመጡ የኮሚቴ ሥራዎች ሁሉ እየታጨና እየታዘዘ መካራ ስቃዩን ያይ እንደነበረ ይህ ግለ ታሪክ ዓይነተኛ ምስክር ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተገናኘ በየሺጥላ ኮከብ የተደረሰው ‹‹ዶሰኛው›› የተሰኘ መጽሐፍ በልቦለድ መልክ ያቀረበውን አንድ ሰው በ13 ኮሚቴ ውስጥ እንዲሳተፍ የተደረገበትን ትረካ እና በግለሰቦች ላይ ይፈጥር የነበረውን የኅሊና ትርምስ እንዲታወስ ያደርጋል፡፡
የአጻጻፍ ገጽታ
ከላይ እጅግ በጣብ ቁጥብ በሆኑ ነጥቦች በስዩም ግለ ታሪክ ውስጥ ከተገነዘብኳቸው ውስጥ ጥቂቶቹን ለመግለጽ ሞክሬያለሁ፡፡ አሁን ደግሞ ስለአገላለጽ ኃይሉ ጥቂት ነጥቦች ላንሳ፡፡ እርግጥ ስዩም ከሕይወት ታሪኩና ከሌሎቹ ሥራዎቹ አኩዋያ ሲታይ የሥነ ጥበብ ታሪክ ተመራማሪና ሃያሲ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ይሁንና ይበልጥ የሚታወቀው ግን በሰዓሊነቱና በስዕል ጥበብ መምህርነቱ እንደሆነም አውቃለሁ፡፡ ይሁንና በሥዕል ረገድ ያለው ተሰጥኦ ምን ያህል እንደሆነ በእኔ ሊመዘን ቀርቶ ሊታሰብ አይችልም፡፡ ቀረበም ራቀ የጥበብ ዋነኛ ገጽታና ጠቀሜታ አሰቃቂ ዘመን የወ/ሮ ቆንጂትን ምርኮኛ የተሰኘ ልቦለድ ማንበብም የስዩምን ትዝብትና ልምድ ይበልጥ ለመረዳት ያስችላል፡፡
• አንድ ሰው በተሰለፈበት ሙያም ሆነ በሚመደብበት ኃላፊነት ይበልጥም ደግሞ በኮሚቴ ሥራ ውስጥ ተግቶ የሚንቀሳቀስ ከሆነ ለሚመጡ የኮሚቴ ሥራዎች ሁሉ እየታጨና እየታዘዘ መካራ ስቃዩን ያይ እንደነበረ ይህ ግለ ታሪክ ዓይነተኛ ምስክር ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተገናኘ በየሺጥላ ኮከብ የተደረሰው ‹‹ዶሰኛው›› የተሰኘ መጽሐፍ በልቦለድ መልክ ያቀረበውን አንድ ሰው በ13 ኮሚቴ ውስጥ እንዲሳተፍ የተደረገበትን ትረካ እና በግለሰቦች ላይ ይፈጥር የነበረውን የኅሊና ትርምስ እንዲታወስ ያደርጋል፡፡
የአጻጻፍ ገጽታ
ከላይ እጅግ በጣብ ቁጥብ በሆኑ ነጥቦች በስዩም ግለ ታሪክ ውስጥ ከተገነዘብኳቸው ውስጥ ጥቂቶቹን ለመግለጽ ሞክሬያለሁ፡፡ አሁን ደግሞ ስለአገላለጽ ኃይሉ ጥቂት ነጥቦች ላንሳ፡፡ እርግጥ ስዩም ከሕይወት ታሪኩና ከሌሎቹ ሥራዎቹ አኩዋያ ሲታይ የሥነ ጥበብ ታሪክ ተመራማሪና ሃያሲ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ይሁንና ይበልጥ የሚታወቀው ግን በሰዓሊነቱና በስዕል ጥበብ መምህርነቱ እንደሆነም አውቃለሁ፡፡ ይሁንና በሥዕል ረገድ ያለው ተሰጥኦ ምን ያህል እንደሆነ በእኔ ሊመዘን ቀርቶ ሊታሰብ አይችልም፡፡
ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን የበርካታ ተወዳጅ ሥነ-ግጥሞች ደራሲ ሆኖ ሳለ፣ “እሳት ወይ አበባ” ብሎ ከሰየመው ከዚህ መድብል ውስጥ ከሚገኙት በቀር ሌሎች ግጥሞቹ በመፅሐፍ መልክ ለህትመት አልበቁም። “እሳት ወይ አበባ” ለመጨረሻ ጊዜ በ1966 ታትሞ ከወጣ በኋላ ባለፉት ዓመታት ጭራሹን ከገበያ ላይ በመጥፋቱ የጸጋዬን ሥራዎች ህያውነት የሚመኙ አድናቂዎች ቅሬታቸውን ገልጠዋል።
ጸጋዬ ገብረ መድኅን ባለፈባቸው የህይወት ውጣውረድ ከአዕምሮውና ከኅሊናው ሰርፀው፣ በርቱዕ ብፅሩ ነጥረውና ተውበው የተወለዱ በርካታ የአማርኛና የእንግሊዝኛ ግጥሞችና ትያትሮች አሉ። በህይወት ሳለ የጠነሰስነውን፡ እነኚህን ሥራዎቹን አሰባስቦ የማሳተሙን ተግባር፡ ለ“እሳት ወይ አበባ” ቅድሚያ በመስጠት ጀምረናል።
ትንሽ ኮፒወች እጃችን ላይ !!!
Ibe Moral of the Story offers a remarkably effective approach that helps students
understand and evaluate moral issues. Through storytelling and story analysis,
using examples from fiction and film, Rosenstand brings classical moral theories to
life and shows students how these theories are applied to the world around them.
This sixth edlition has been thoroughly updated to reflect recent research, events,
and films. It also expands the applied ethics chapter to include the topics of media
bias, abortion, euthanasia, business ethics, and environmental ethics with emphasis
on the isue of global warming.
"ባለፉት ሁለት ሺህ ዘመናት ነገሥታቱንና ጳጳሳቱን "ተሳስታችኋል” ብሎ መጻፍና መናገር ማለት ሰማይን ቀና ብሎ በርግጫ የመምታት ያህል የሚቆጠር ነበር፡፡ ጥሩ መሪዎችን ማከበራችን ጥሩ ባህላችንና ይበል የሚያሰኝ ሲሆን ማጎብደዳችን ግን መጥፎ ውርሳችን ነው
ከመጽሐፉ የተወሰደ፡፡
....እስከ መቼ ይሆን መሪዎቻችን በሥልጣን ላይ ሊሆኑ ባፍ ጢማችን እየተደፋን ስናጎበድድ ኖረን ሲሻሩና ሲሞቱ ብቻ ኃጢአታቸውን የምናበዛው? ለምን ይሆን በሥልጣን ዘመናቸው እንደነ ተቀቀለ ፓስታ የምንጥመለመለውና ድከመታቸውን የማንነግራቸው? እስከ መቼ ይሆን የሙት ወቃሽ ሆነን የምንኖረው??..."
ከመጽሐፉ የተወሰደ፡፡
ከአሁን በኋላ "ተከድኖ ይብሰል!” በሚል አጉል ፈሊጥ ተተብትበን የተከደነው ሳይማሰል ቀርቶ አሮ ሲሸት እያየን አፍንጫችንን መያዝ አንፈልግም! ከአሁን በኋላ የነበረውና ያለው ስሕተት በማጎብደድ መንፈስ ተውጠን ባለመቃወም የታሪክ ተወቃሾች መሆንን አንሻም!፡፡ የአባቶቻችንን ዕዳ ለማቃለል እንሞክራለን እንጂ በዕዳ ላይ ዕዳ ጨምረን በልጆቻችን ጫንቃ ላይ አንጭንም..*
ከመጽሐፉ የተወሰደ፡፡
ስለ አዘጋጁ በጥቂቱ፡- መምህር ቡሩክ ገብረ ሊባኖስ ተስፋዬ ከሕፃንነቱ ጀምሮ ዕድገቱ በቆሎ /አብነት/ ትምህርት ቤት ነው፡፡ የቅዱስ ያሬድን ጸዋትወ ዜማዎች፣ አቋቋምና ቅኔ አጠናቋል፡፡ በመጨረሻም በቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሚሰጠውን የትርጓሜ መጻሕፍትና ባሕረ-ሐሳብ በ1991 ዓ.ም አጠናቆ ተመርቋል፡፡ ከዚያም አዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ አድባራትና ገዳማት የስብከተ ወንጌል ኃላፊ ሆኖ ለዘጠኝ ዓመታት ያህል አገልግሏል፡፡ አሁንም በአውስትራሊያ ቤተ-ከርስቲያን በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡
የሰሎሞን መዝሙር ከመዝሙሮቹ ሁሉ የተለየ መዝሙር ነው፡፡ ውጫዊ ንባቡን ሲመለከቱት ዓለማዊ መጽሐፍ /ልብ ወለድ/ የሚመስል ሲሆን ውስጣዊ ምሥጢሩ ግን ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መልእክት ያለው ነው፡፡
አንዳንድ ሰዎች ሰሎሞን መዝሙሩን በዚህ ዓለም ለምትኖረው ወዳጁ የጻፈው ደብዳቤ እየመሰላቸው እንደ መንፈሳዊ መጽሐፍ አያዩትም፡፡
ቅዱስ ያሬድ መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን /የሰሎሞን መዝሙር/ ስለ ቤተክርስቲያን /ስለ ምእመናን/ እና ስለ ድንግል ማርያም እንዲሁም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተነገረ ተረድቶ ኢየሱስ ክርስቶስንና ድንግል ማርያምን እያመሰገነ ዘምሮታል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ዜማ የደረሰለት የሰሎሞን መዝሙር በቤተክርስቲያናችን በዘመነ ጽጌ ቅዳሜ ቀን ይዘመራል፡፡ ዘመነ ጽጌ /የአበባው ዘመን/ እመቤታችን በአበባ ጌታችን በፍሬ እየተመሰሉ
የሚዘመርበት ወቅት ነው፡፡ መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን /የሰሎሞን መዝሙር/ የሚዘመርበት ጊዜ ዘመነ ጽጌ /የአበባው ዘመን/ አንዲሆን የተመረጠው ሰሎሞን ቤተ ክርስቲያንን፣ ጌታችንንና እመቤታችንን
ድንግል ማርያምን/ በአበባና በፍሬ እየመሰለ ስለተናገረ ነው፡፡
ስለሆነም ይህንን መጽሐፍ የሚያነብ ሰው የተሳሳተ ግንዛቤ እንደ ቆሸሸ ልብስ አውልቆ ጥሎ ሕይወት አድሶ የሰሎሞንን መዝሙር ሊጸልየው የሚጠብቅ በረከተ ትርጓሜ እነሆ፡፡
ከውስጥ ገጽ የተወሰደ
In September 2004 acquired SiX diaries written by Richard George Tyndall
Bright, British army officer. They cover his participation in African
exploration expeditions from June 1897 to September 1908. This archive had
belonged to Humphrey Winterton, a British collector whose African reference
library was well known
In acquiring these diaries it was my intention to make one or more of them
available to a wider audience in a published format. Bright was a candid
observer of places which were at the time largely unknown. He was a
meticulous record-keeper, with a keen eye for details. His diaries thus offer an
unusual insider's look at the evolution of British colonial policy, as well as
providing a factual account of daily life on these expeditions.
In presenting one section of the first diary, it is my hope that an obscure but
important aspect of the history of East Africa in the late 19th century will be
illuminated. The introductory material is designed to make its significance
more apparent to those who are not familiar with the times and places
involved.
As in the past, I am indebted to Richard Pankhurst, Professor at the Institute of
Ethiopian Studies in Addis Ababa, for his insights and suggestions; to Glenn
Mitchell of Maggs in London for his assistance with research; and to Nancy
TenBroeck for transcription and editing for publication.
Frederic A. Sharf
November, 2005
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ ውሏል።
እነሆ መጽሐፍት ቤታችን ቀደምትና አዳዲስ መጽሐፍትን ሰድሮ ለእናንተው ምቹ አድርጎ ይጠብቃችዃል።
ትንሽ ስለ መጽሐፉ
……እይታችሁ ስለምን ፊትና ኋላ ሆነ? የቆማችሁበትን ማን ይይላችሁ? ተፈጥሮላይ መጀመሪያውንም መጨረሻውንም አናውቀውም።የምናውቀውን መካከሉን ብቻ እንኑር።መጀመሪያውን ለማየት ወደኋላ አትጎተቱ።መጨረሻውንም ለማወቅ ወደፊት አትጋልቡ።በዛሬላይ አምላክ ሁናችሁ ኑሩ እንጅ።ወደኋላ ካያችሁ ደካሞች ትሆናላችሁ፤ወደፊት ካያችሁ ደግሞ በአምሮት ትቃጠላላችሁ።
የተስተካከለ እይታ ይኖራችሁ ዘንድ ሁለት ዓይኖቻችሁን በውረንጦ አወጣላችኋለሁ።ሌላም ንፁህ የልብ ዓይናችሁን አበራላችኋለሁ።ከዚያም ከብሄርተኞች ጋር ብሄርተኛ፤ከሀይማኖተኞች ጋር ሀይማኖተኛ፤ ከዘረኞች ጋር ዘረኛ አትሆኑም። ከዜጎችም ጋር ዜግነት አይኖራችሁም።ከማህበረሰብ ባርነት ተላቃችሁ የጠራችሁ ግለሰብ ትሆናላችሁ። እናንተ ራሳችሁ እንደሰው ያለም ዜጋ፤እንደተፈጥሮ የዩንቨርስ አባል እንደሆናችሁ ራሳችሁን ታያላችሁ፣ታስባላችሁ።
የምታዩትን ሳይሆን የሚታየውን ታያላችሁ። (ገጽ:216)
ከዓይናውጣ መጽሐፍ የተወሰደ።
David Harvey has written a profound, and profoundly disturbing,
book For thirty years his writings have taken aim at the complacent
conviction that what exists works. Harvey is a scholarly radical; his
writing is free of journalistic clichés, full of facts and carefully thought-
through ideas. This book is beautifully crafted, its prose accessible, its
narrative one of mounting intensity and urgency. The New lmperialism
mounts a stunning indictment of our present institutions of power,
while offering hopeful insights about how these institutions could
be changed.
RICHARD SENNETT
Professor of Sociology,
'Navigating effortlessly between history, economics, geography and
politics, with persuasive argument and lucid prose, David Harvey
places today's headlines in context and makes sense of the early
twenty-first century maelstrom we're all caught up in. His concept
of accumulation by dispossession willgo far. The New Imperialism
is a truly useful book:'
SUSAN GEORGE,
Associate Director,
Amsterdam
«… ያ ሰሜን ኢትዮጵያ፤ የጥንታዊ ስልጣኔ መነሻ፣ የውጭ ወራሪዎች በየዘመናቱ አንገታቸውን ብቅ እያረጉ ሲሰልሉት፣ እየወደሙም ቢሆን ሲወድሙበት የኖረ የዘመናት የጦር አውድማ! ያ ሰሜን ኢትዮጵያ፤ የውጭ ወራሪዎች በፈጠሩት መዘዝ ወንድም ከወንድሙ እየተጋጨ ሲተራረድ፤ አንተም ተው አንተም ተው የሚል ጠፍቶ የእርስ በእርስ መጨራረሻ የሆነ የደም መሬት! ያ ሰሜን ኢትዮጵያ፣ ወንድ ልጇን ያላስገበራት ኢትዮጵያዊት እናት የለችምና የወላድ እርግማን የደረሰበት ይመስል ቦምብና መትረየስ እየለበለበው የደጋ በረሀ ሊሆን የተቃረበ ምድር! ያ ሰሜን ኢትዮጵያ፤ ደም እንደ ውሃ
እየወረደበት፣ አጥንት እየተከሰከሰበት፣ የሰው ልጅ አስከሬን በአውሬ እየተጎተተበት፣ የዋይታ እና ኡኡታ ጩኸት እያደነቆረው ራሱም ሲያለቅስ የሚኖር ያልታደለ ቦታ! ያ ሰሜን ኢትዮጵያ፣ የወደፊት ዕጣ ፋንታው እንኳ ገና በውል ያልታወቀ የሀገር ክፋይ! ታዲያ ... እንዴትሆኖ. . .»
«. .. ማስተዋል የጎደላቸው እብሪተኞች ስልጣን በያዙበት ጊዜና ቦታ ሁሉ አውቆ መገኘትን ያህል የማይድን በሽታ የለም። መሰሪ አካሄዳቸው በገባህ ቁጥር ልብህ ይደማል። ሊዋሹና ሲቀጥፉ በሰማህ ቁጥር አንጀትህ ይቆስላል። የጭካኔ ተግባራቸውን በምታይበት
ጊዜ ውስጥህን ይኮሰኩሰዋል። ያኔ መንፈስህ ይረበሽና አካላዊ ጤናም ታጣለህ፡ ያልታደለች ሀገር ዜጋ ከመሆን የሚመነጭ አለመታደል! ስለዚህ. . .»
እኔ አልኮነንም ሀሰት ተናግሬ፤
እኔ አልታመም ውሸት ተናግሬ፤
ድሃ አልኖረብሽም ድሃዋ ሀገሬ።
ሰዎች ኡኡ በሉ ምነው ዝም አላችሁ፤
ወገኖቼ ጨኹ ምነው ፀጥ አላችሁ፤
ግፍ ራስ አዙሮ ሲጥል እያያችሁ።
እኛ በከንቱ ሞተናል፣
“እናንተ ግን አደራ ራራራራራ.......
ቀረበም ራቀ የጥበብ ዋነኛ ገጽታና ጠቀሜታ የዘረዘረና በፓፒተስ ሲጃራ የበለዘ፣ ድምጻቸው የሻከረና በግፊት የሚወጣ ሰብአዊነት ያጣ ይመስላል፡፡ (ገጽ 183) ደስታ ታደሰ በጣም ከወደድኳቸውና ካከበርኳቸው በሕይወቴ ካጋጠሙኝ ኢትዮጵያውያን አንዱ ነበር፡፡ ... ሁሉን ሰው በእኩል የማየት፣ የማክበርና የመንከባከብ ባህርይ ያሳያል፡፡ ... ጸጉሩ በተፈጥሮው ቶሎ የሚያድግ ይሆንም በልማድ በአጭር የሚስተካከለው፣ ዐይኖቹ ፈጠጥ ፈጠጥ ያሉ አነስ ብላ በምትታይ ጭንቅላቱ ላይ ሰልካካነቱ የጎላ አፍንጫ ነበረው፡፡ ... (ገጽ 232)
እነዚህንና እነዚህን የመሳሰሉ በርካታ ገለጻዎችን ታገኛላችሁ፡፡ ስዩም ሲገልጽም ሆነ ሲተርክ ወይም ሲያስረዳ አለበለዚያም ተፎካካሪ ሀሳቦችን በክርክራዊ መንገድ ሲያቀርብ ቋንቋም ሆነ ያቀራረብ መንገድ ወይም ስልት የማይቸግረው ነበረ ማለት ይቻላል፡፡
ማጠቃለያ አስተያየት
ከላይ የግለ ታሪኩን አጠቃላይ ትኩረት ጠቁሜያለሁ፡፡ ስለአገላለጽ ብቃቱም በተለይ መጠነኛ ምሳሌዎችን በማቅረብ ለማሳየት ጥሬያለሁ፡፡ ከነዚህ ላይ በመነሳት፣ ጽሑፉ በመታተሙ በአገራችን ዘመናዊ ሥነ ጥበብ ላይ ምርምር ለሚያካሂዱ መምህራንና ተመራማሪዎች፣ የታሪክ ተማሪዎች፣ ጽሑፉ ባተኮረባቸው ዘመናት ውስጥ የነበረውን ያገራችንን ማኅበረ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ለሚያጠኑ የሥነ ማኅበረሰብ ተመራማሪዎች ሁሉ እንደ አንድ የመረጃ ምንጭ ሆኖ ያገለግላል የሚል እምነት አለኝ፡፡ እንዲሁም በኪነ ጥበብ ሙያ ውስጥ የየበኩላቸውን ድርሻ ለተወጡ ወገኖች ተገቢውን አክብሮት ከመስጠትና የታሪክ መታሰቢያዎችን ከማቆም አንጻር የማይናቅ አስተዋጽዖ ይኖረዋል፡፡ እንዲሁም በአተራረክ ቅንብሩ፣ በቋንቋው ግልጽነት፣ ሥእላዊነትና ተስፋ ፈንጣቂነት ሰበብ ሕይወት ምንም ያህል ተግዳሮት ቢበዛባት በቆራጥነት ለሚጋፈጡዋት ወገኖች የራሱዋ ጣእም እንዳላት እንገነዘብበታለን፡፡ ራስን ለችግር ከማስገዛት ይልቅ ችግርን ለመግዛት መጣር ምንኛ አርኪ መሆኑን እናጣጥምበታለን ብዬ በግሌ አምናለሁ፡፡
በመሆኑም፣ ጠቅላላ አንባቢዎችም ከዚህ መጽሐፍ ብዙ ቁም ነገርም ሆነ የመንፈስ እርካታ ያገኙበታል ብዬ አምናለሁ፡፡ በተለይ ደግሞ በአንዳንድ አጋጣሚዎች ከአለቆቻቸውና ከሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር የሚያደርጉዋቸው ክርክሮችና ግፍጫዎች ‹‹እኔ›› እያሉ መተረክ የሚፈጥረው ውስጣዊ ለራስ የማድላት ስጋት ‹‹እውነት ይሆኑ ይሆን;›› የሚያሰኙ ትረካዎች ቢመስሉም ኃላፊነትን ተቀብሎ መኖር እንዴት ዓይነት የአካልና የኅሊና ፈተና እንዳለበት የሚያስገነዝቡ በመሆናቸው ለወቅቱ አንባቢ የሥነ ልቦና ስንቅ ይሆናሉ ብዬም እገምታለሁ፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ አንባቢዎች የስዩምን ግለ ታሪክ አንብበው ሲጨርሱ ምናልባት በኅሊናቸው ውስጥ የሚብሰለሰሉ አንዳንድ ሰብአዊ ጥያቄዎች ማሰላሰላቸው አይቀርም፤ ከነሱ ውስጥ አንዱ ነጥብ ስዩም ወጣትነቱን እንዳለ በትምህርት፣ በሥራና በጉብኝት ክንዋኔዎች የማሳለፉን ያህል ለምን የወጣትነትን አንድ ገጽታ ማሳያ የሆነውን የማፍቀርና የመፈቀርን ጭብጥ ዘለለው የሚያሰኘው ነው፡፡ በአገር ውስጥ በትምህርት ቤት፣ በሥራም ዓለም በጋዜጠኝነት ከወዲያ ወዲህ ሲዘዋወርና ብዙ አድናቂዎች ሲያተርፍና በብዙዎች ዓይን መግባቱን የመግለጹን ያህል በኮረዶች ዘንድ ምንም ዓይነት የመፈለግ አዝማሚያ አላጋጠመውም? የእሱንም ዓይን የሳበች ወጣት አልነበረችም? እንዲሁም ውጪ አገር ሲማር እንዲህ ካለው ሰብአዊ ግንኙነት ሙሉ በሙሉ ታቅቦና የባህታዊ ኑሮ ነው ገፍቶ የመጣው? ያም ሆነ ይህ ‹‹ኩርፊያ የሸፈነው ፈገግታ›› ተነባቢና ጠቃሚም፣ ጠቋሚም መጽሐፍ ነው ብዬ እመሰክራለሁ፡፡
ደረጀ ገብሬ በEthiopian Journal of Languages and Literature Vol. XII No. I January 2012 የታተመ ጽሑፉ።
ኤዞፕ መጻሕፍት:
በትግስት ይነበብ !!
ውድ ወዳጆቼ ሰሞኑን ስለስዮም ወልዴ ራምሴ መጽሐፍ በሶሻል ሚዲያ ተደጋጋሚ ያጋራወችኹን ፎቶዎች ተከትሎ ስዩም ወልዴ ማን ነው ? ላላችኹኝ ወዳጆቼ እነኾ ለንባብ ቃርሚያየ ላይ ያገኘውትን የማከብራቸው ደራሲና የስነጽሑፍ መምህር ደረጀ ገብሬ በሆነ ዘመን ያስቀመጡትን ዳሰሳ ነው።
ጽሑፋን ያገኘውት Ethiopian Journal of Languages and Literature Vol. XII No. I January 2012 ከተሰኘ ጆርናል ላይ ሲኾን በደረጀ ገብሬ የተዘጋጀ የመጽሐፍ ዳሰሳ ነው።
ርእስ፡- ኩርፊያ የሸፈነው ፈገግታ
የጽሑፍ ዓይነት ፡- ግለ ታሪክ
ጸሐፊው (ደራሲው)፡- ስዩም ወልዴ ራምሴ
የኅትመት ዘመን ፡- 2002
የገጽ ብዛት፡- 360
ዋጋ፡- በድርቅ ህትመት ብር 50.00
የታተመበት ቦታ፡- አዲስ አበባ
አሳታሚ፡- የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበርና አርቲስቲክ ማተሚያ ድርጅት ተዟዟሪ ሂሳብ አስተዳደር የታተመ
የግለ ታሪኩ ይዘት
‹‹ኩርፊያ የሸፈነው ፈገግታ›› የአንድን ታዋቂ የሥነ ጥበብ ሰው ከልደት እስከ ሀምሳ ዓመት ድረስ ያለውን ውጣ ውረድ የሚተርክ፣ ግለ ታሪክ ነው፡፡ ጸሐፊው ‹‹እነሆኝ›› ብሎ በሰየመው የማስተዋወቂያ ቀዳሚ ክፍል፣በጽሑፌ ውስጥ ያተኮርኩት እኔ ሌሎችን እንደማያቸውና እንደማውቃቸው እንጂ እንደሚያዩኝና እንደሚያውቁኝ አይደለም፡፡ አንባቢዬ እዚህ ህሊና ክርክር ውስጥ አይግባ- የምነግረው እውነቴን እንጂ ሀቄን አይደለም፤ ስለዚህ ነው እንዳየሁት ብዬ የምናገረው፡፡ ... ሰዎች የተናገሩኝን እንጂ ያሰቡኝን ማወቅ አልችልም፤ ያደረጉትን እንጂ ሊያደርጉ የፈለጉትን ማለት አልችልም፡፡ (ገጽ 10)
ሲል እንደጠቆመው በግል ልምዱና አመለካከቱ ላይ ተመርኩዞ ያጋጠመውንና የኖረውን፣ ልዩ ልዩ የሕጻንነት፣ የልጅነት፣ የትምህርትና የሥልጠና እንዲሁም የሥራ ኃላፊነት ያስከተሉበትን ትሩፋትና ፍዳ ከግል አቋሙ አንፃር ቁልጭ አድርጎ በማያሻማ ቋንቋ አቅርቦልናል፡፡ የግለ ታሪኩን መሠረታዊ ማጠንጠኛና ጠቀሜታ ከሚከተሉት ነጥቦች ማስተዋል ይቻላል፡፡
• ‹‹ኩርፊያ የሸፈነው ፈገግታ›› ግለታሪክ በ360 ገጾች ውስጥ የተካተተ ትረካና 23 ያህል ፎቶዎችና ሥእሎች የሚገኙበት ድጉስ ነው፡፡ የሽፋን ፎቶው የባለታሪኩን እውናዊ ገጽታ የሚያሳይ ከመጽሐፉም አጠቃላይ ይዞታ ጋር ተዛማጅነትና ሕያውነት ያለው ሆኖ ይታያል፡፡
• በግለ ታሪኩ አማካይነት በዘመኑ ስለነበረው የአዲስ አበባ የልጆች አስተዳደግ፣ በተለይም በተርታው ቤተሰብ ውስጥ ያለው የልጆች አያያዝ እምብዛም ከገጠሩ ያልተለየ መሆኑን ያሳየናል፡፡ ትምህርትን ከቄስ ትምህርት ቤት መጀመር፣ የየኔታን እግር መሳም፣ ኩርኩም፣ ቁንጥጫ፣ በባዶ እግር መሄድና በምስማር መወጋት፣ ወፎችን በድንጋይ መምታት፣ ዛፍ ላይ መውጣት፣ በአካባቢ የሚገኝ ሙክት ላይ መቀመጥና ጥርስን መሰበር፣ አህያም ሆነ ፈረስ ካጋጠመ ተቀምጦ ለመጋለብ መጣጣር፣ በተገኘው ነገር ሁሉ መሳተፍና የሚያጋጥመውን በጥሞና መቀበል ሁሉ በልጅነት የሚያጋጥሙ ተደጋጋሚ ድርጊቶች ናቸው፤ የከተሜው ስዩምም የልጅነት ሕይወት ይኸው ነው፡፡ ከእናት ቁንጥጫና ግርፊያ፣ ከበርበሬና ከኮሶ መታጠን ጋር የተያያዘ ቅጣት ልማዳዊ ከልጅ ገርቶ ማሳደጊያ ብልሃቶች አንዱ እንደነበር የሚመሰክር ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ያልኩትን ይበልጥ ለመረዳት ግን፣ ‹‹ደማቁ ጠዋት›› የሚለውን የመጀመሪያውን ምእራፍ ስታነብቡ አሁን ከተቀስኩላችሁ ይበልጥ አስቂኝ፣ አስገራሚና አሳሳቢ አንዳንድ ጊዜም አሳዛኝ ትረካዎች ታገኛላችሁ፡፡
• የከተማው አስተዳደርና እያንዳንዱ የከተማ ነዋሪ በምን ዓይነት አቅድ (ፕላን) በተሠሩ ቤቶች ውስጥ ይኖሩ እንደነበር፣ ዛሬ የምናያቸውና በልዩ ልዩ ሰበብ እየፈረሱ የምናስተውላቸው የከተማዋ ቤቶች አጀማመራቸውና አመሠራረታቸው እንዴት እንደነበረ፣ የመንገዶችና ጎዳናዎች አሠራርና አካሄድ፣ የራዲዮ መርሀ ግብር ስርጭት፣ በተለይም የዘፈን መርሀ ግብር ሲኖር ዘፋኞች ከነሙሉ መሳሪያቸውና አጀባቸው ራዲዮ ጣቢያው ድረስ እየሄዱ ያቀርቡ እንደነበር (ዛሬ ሕያው የምለው ዓይነት አቀራረብ) የልጅነት ገጠመኙን አንተርሶ ይተርክልናል፤ በዚያም የተነሳ የአዲስ አበባ የሕይወት ምህዋር እንዴት እንደሚሽከረከር በማሳየት ረገድ ይህ ግለ ታሪክ የበኩሉን ጭላንጭል ያሳያል፡፡ በዚህም ምክንያት ግለሰቡ በኖረበት ዘመን ላይ በአዲስ አበባ አስተዳደርና በነዋሪዎቹ ማኅበረ ባህላዊ ግንኙነትና ሕይወት ላይ ጥናት ለሚያካሂድ ተመራማሪ የጊዜውን ወረራ (መልክ) ለመመልከት ያስችለዋል፡፡
• በዚህ ግለ ታሪክ ውስጥ በቀጥታ ከማይነገሩ ነገር ግን እንደገጠመኝ ከሚፈነጠቁ ቁም ነገሮች ውስጥ በነስዩም መኖሪያ ሰፈር በነበረው የሳት አደጋ ግቢ ውስጥ ተጥሎ የተገኘው የብረት ሐውልት ጉዳይ ነው፡፡ ስዩም ያንን ሀውልት በድንጋይ ሲቀጠቅጠው በሚሰጠው ድምጽ ይደሰታል፡፡ በዚህ ብቻ ግን አያበቃም፡፡ ገጽ 25 ላይ ማንበብ ያቻላል፡፡
• በአዲስ አበባ ከተማ ስለነበረው የትምህርት አሰጣጥና የመምህራን ድርሻ፣ ከዜግነት ስብጥርና ከሥልጠና ብቃትና እምነት ጋር ለመተዋወቅ የሚበጁ ጥቆማዎች ያቀርባል፡፡ ስለመምህራኑ ትጋት፣ ስለትምህርት ቤቶች ስርጭት፣ ንጉሠ ነገሥቱ በትምህርት ቤቶች፣ በመምህራን፣ በተማሪዎችና በወላጆች ላይ ስለነበራቸው ተጽእኖ (ምንም እንኩዋን በተለያዩ የታሪክ ጸሐፊዎች በልዩ ልዩ ሁኔታና ቦታ በተደጋጋሚ የተገለጸ ቢሆንም) የዓይን ምሥክር ሆኖ የሚቀርብ ነው፡፡ ለምሳሌ ከክፍል አንደኛ ለሚወጣ ተማሪ፣ ወይም ከሚማራቸው ትምህርቶች ውስጥ ብልጫ ሲያመጣ የዚያ ትምህርት መምህር በግሉ ስለሚሰጠው ማበረታቻና ሽልማት ሁሉ ስናነብ በአሁኑ ጊዜ በሥራው ላይ የምንገኝ መምህራን ወደ ውስጣችን እንድንመለከት አንዳች የመንፈስ ግዴታ ሽው እንዲልብን የሚያደርግ ይመስለኛል፡፡
• በዘመኑ ስለነበረው የሥራ አቅርቦትና የወጣቶች ተጠቃሚነት አንዳች መረጃ ለሚሻ የበኩሉን ድርሻ ይፈነጥቃል፡፡ በገጠርም ይሁን በከተማ ተወልደው የሚያድጉ ሕፃናት እድሜያቸው በደረሰበት ደረጃ ቤተሰቦቻቸውን በሥራ ያግዛሉ፤ በልዩ ልዩ ገቢ ማስገኛ እንቅስቃሴዎች በመሳተፍ ለግል መጠቀሚያ የሚሆናቸውን ገንዘብ ለማግኘት ይተጋሉ፤ ወጣቱ ስዩም ወልዴም በዚህ ዓይነት ተግባር ይሳተፍ እንደነበረ፣ ከትምህርት ቤት ውጪ ባሉ ትርፍ ጊዜዎቹ ከጓደኞቹ ጋር ከመጫወት አልፎ በንግድ፣ በእጅ ሥራ ሽያጭ፣ በሥእል ሥራና በልብስ ስፌት ጭምር ራሱን ጠምዶ ለትምህርት ቤት የሚሆኑትን ቁሳቁሶች ለማሙዋላት ጥረት ያደርግ ነበር፤ አልፎ ተርፎም ለእናቱ የዘመን መለወጫ በግ ሳይቀር ለመግዛትና ለማሳረድ መቻሉን በደስታ እንደሚያስታውሰው እናነባለን፡፡ ቀላልና አብዛኛው የዚያ ዘመን ወጣቶች ይፈጽሙት የነበረ ተግባር ሊሆን ወይም ሊመስል ይችላል፡፡ ጉዳዩ እሱ አይመስለኝም፡፡ አሁን ላለንበት ኅብረተሰብ በተለይም ለወጣቱ ክፍል የሚኖረው ምሳሌነት ነው፡፡ እርግጥ አሁንም የሥራ ስምሪቱና ዓይነቱ ይለያይ ይሆናል እንጂ በየአካባቢያችን በናሙናነት የምናነሳቸው ሊስትሮዎች፣ ቆሎ ሻጮች፣ ሳምቡሳና ብስኩት አዙዋሪዎች፣ እንዲሁም የቅርብ ክስተት ይሁን እንጂ የመጻሕፍት ሱቅ በደረቴዎች፣ ሎተሪ ሻጮች፣ ተሸካሚዎች ልጆች አናጣ ይሆናል፡፡ የስዩም ትረካ ግን ተግባሩ ከግማሽ ምእተ ዓመትም በፊት የነበረና የብዙ ወጣቶችና ቤተሰቦች ተፈታታኝ እውነታ እንደነበረ ያሳየናልና እንማርበታለን፡፡ የወደፊቱም አንባቢ ይበልጥ ይገለገልበታል ብዬ እገምታለሁ።
ሁሉን ነገር በሥጋ ዓይን እያየ ማስተዋል ለተቀማው ለእኛ ዘመን ትውልድ መጽሐፈ ቀሌምንጦስን ማንበብ አንዱ መፍትሔ ነው።
Читать полностью…Ibe Moral of the Story offers a remarkably effective approach that helps students
understand and evaluate moral issues. Through storytelling and story analysis,
using examples from fiction and film, Rosenstand brings classical moral theories to
life and shows students how these theories are applied to the world around them.
This sixth edlition has been thoroughly updated to reflect recent research, events,
and films. It also expands the applied ethics chapter to include the topics of media
bias, abortion, euthanasia, business ethics, and environmental ethics with emphasis
on the isue of global warming.
።በድጋሜ አንድ ኮፒ የተገኘች
እምየ አፍሪካ !!
ታሪክሽን ያላጠና
ያልፈተሸስ ማን አለ ?
እነዚህን ታላላቅ አፍሪካዊ ዶክመንቶች እነሆ !!