 
       
                   
               8749
              8749
          
          ኤዞፕ ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት። በምኒልክ አደባባይ ጣይቱ የባህል ማዕከል ፊት ለፊት የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን፣ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ !! ስልክ:- 09 11 72 36 56 ለማዘዝ @Mesay21 @Mesay21
 
                    ከገበያ ጠፍቶ የነበረው #ገድለ_ቅዱስ_አሮን_መንክራዊ
የተወሰኑ ኮፒዎች ስላገኘን  ያልገዛችሁ ሳያልቅባቹህ .....
 
                    እጅግ ድንቅ ታሪክ ታትሟልና ያንብቡት
ትንሽ ኮፒዎች ብቻ ስለታተሙ ፈጥነው ይሸምቱ
 
                    ፖፕ ሹኑዳ ሣልሳይ
(1971-2012)
ፖፕ ሹኑዳ ሣልሳይ ከ1971- 2012 117ኛው የእስክንድርያ ፖፕና የመንበረ ማርቆስ ፓትረያርክ በመሆን የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን ለ40 ዓመታት መርተዋል፡፡ ዘመነ ፕትርክናቸው 40 ዓመታት ከ4 ወራት ከ4 ቀናት እንደሆነ በዜና መዋዕላቸው ተገልጹዋል፡፡ በዘመነ ፕትርክናቸው በአውሮፓ፣ በአውስትራልያና በሰሜን አሜሪካ ጳጳሳትን በመሾም የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዕድገት እንድታሳይ አድርገዋል፡፡
ፖፕ ሹኑዳ ሣልሳይ ለሰላምና ለአብያተ ክርስቲያናት ግኑኝነት በብዙ ሠርተዋል፡፡ በዕረፍታቸው ቀን እንደተነበበው "የጥንታዊቱ የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ፓትረያርክ፣ በጣም የታወቁ የቤተ ክርስቲያን አባትና መምህር፣ እንዲሁም ዋና የእምነት ጠበቃ፣ የሃያኛውና የሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን የግብፅ መሪና የትውልድ መምሀር" ተብለው ተወድሰዋል፡፡
ፖፑ ከዚህም በተጨማሪ በርካታ የነገረ መለኮት ሥነ ጽሑፍ ሥራዎችን ለአገራቸው ለግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንና ለመላው ዓለም ክርስቲያኖች አበርክተዋል፡፡ ከእነዚህ የነገረ መለኮት ሥራዎቻቸው ውስጥ "The Nature of Christ" የተባለው ይህ ሥራቸው ይገኝበታል፡፡ የመጽሐፉ ይዘትም በሀገራችን “ነገረ ተዋሕዶ" የተባለውን ምሥጢር አጠርና ምጥን አድርጎ በጥልቀትና በስፋት የሚያሳይ ነው።
ተርጓሚው ይህንን "The Nature of Christ" የተባለውን የፖፕ ሹኑዳ ሣልሳይ ሥራ “የክርስቶስ ባሕርይ” በሚል ርእስ ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ ተርጉሞ ሲያቀርብ ኢትዮጵያውያን ካህናትና ምዕመናን እንዲሁም ተመራማሪዎች ብዙ እንደሚያተርፉበት በመተማመን ነው።
ሥርገው ገላው ዶ/ር
 
                    ያልተነበበው መጽሐፍ !!!
ዝርዝር ጽሑፉን ከታች ይመልከቱ
በእውነቱ አፈወርቅ ገብረ ኢየሱስ ማን ናቸው።
 
                    ንጉሡና ሊቁ ክፍለ ዮሐንስ "የእንሰሳት ነፍስ ወደ ሰማይ ነው የሚሄደው ወይስ ሲሞቱ አብሯቸው ነው የሚቀበረው" በሚል ርዕስ ከፍተው ይከራከራሉ። ንጉሡ "ወደ ላይ ነው የሚሄደው" ሲሉ ፤ሊቁ ክፍለ ዮሐንስ ደግሞ" ወደ መሬት ይወርዳል" የሚለውን ሀሳብ አንስተው ክርክር ገጥመዋል።
Читать полностью… 
                    #የዐዲሱ_ዓለም_ክርስትና_እና_የስሕበት_ሕግ
 ከዐዲሱ ዘመን እንቅስቃሴ እና እሳቤ ጋር
✍መምህር ዘበነ ለማ
 
                    በጥሩ ይዞታ ላይ ያለ 
እጅግ ንፁህ
የግራኝ አህመድ ወረራ
ተክለ ፃድቅ መኩሪያ !!!!
 
                    "ክቡራ ምድራችን የተሞላችው በ Matter ነው፡፡ እኛ የምንፈልገው ደግሞ Antimatter ነው፡፡ 1 ግራም አንቲማተር ለማግኘት 1 ቢሊዮን ዓመታት ይወስዳል! እኛ ግን በ 50 ዓመታት 0.25 ግራም ሩብ ግራም ማግኘት ችለናል! በአንጻሩ የበላይ አካሉ ምድር ላይ የሚገኙትን ማተሮች ለመፍጠር ብቻ, 5,972,200,000,000,000,000,000,000 kg 5.972 septillion kilogram. አንቲማተር ተጠቅሟል፡ምድራችን ላይ ማተርን አስቀርቶ አንቲማተርን ሰውሯል"
"መረጃውን ለሚመለከታቸው ቅዱሳን አባቶች ለማድረስ ወደ ዔድን ገዳም የሄደው መልዕክተኛ እየሆነ ያለውን ነገር፥ እየሆነ ነው ብሎ ለማመን ተቸገረ፡ በአንዱ ክስተት ተገርሞ ሳያበቃ፣ ሌሎች ለማመን የሚቸግሩ የተዓምራት አይነቶች በላይ በላይ እየተደረቡበት የማሰቢያ ጊዜና ፋታ እያጣ፣ መረጋጋትም እየተሳነው፣ሲብተከተክ እንዴት አባ? እንዴት.? እያለ መልከ-መልካሙን መነኩሴ ሲጠይቅ ነው የስነበተው።
"እኛ ዓላማችንም፣ መነሻና መድረሻችንም፤ ግልጽ ነው! የምንመራበት የፖለቲካና የኢኮኖሚ ርዕዮትም ይህ ነው! ካፒታሊዝም + ሊበራሊዝም + ኒዮ-ሊበራሊዝም + ዲጂታሊዝም + ግሎባሊዝም = ሳታኒዝም!!! ሳታኒዝምን ለማዋለድ ጠንክረን እየሰራን ነው እየተሳካልንም ነው!"
*እኔ ያጠፋሁት ጥፋት የለም! "መዳንም በሌላ በማንም የለም እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና፡፡ (ስራ 4፡12) ብዬ
መማሪያ መጽሐፉንም፤ መጽሐፍ ቅዱሱንም ጠቅሽ አስተማርኩ፡፡ ክፍል ውስጥ ከነበሩት ከ ሃያ አራት ተማሪዎች ውስጥ ሃያዎቹ ክፍሉን ለቅቀው እየገላመጡኝ ወጡ! ወንጌል ከማስተማር ውጪ ሌላ የሰራሁት ስህተት የለም! ወንጌል ማስተማርና ወንጌል መስበክ ስህተት ከሆነ ደግሞ በዕድሜ ዘመኔ ሁሉ ልክመሆን አልፈልግም
ከመጽሐፉ የተወሰደ
 
                    ሠላም ውድ የኤዞፕ መጽሐፍት ደንበኞች  አልቋል ብለናቹህ የነበረው   
 #የጣና  #መዝሙረ_ዳዊት 
   #ድርሳን አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ ዘውእቱ ዜና ሥለሴ  እና 
#ድርሳነ_ጽዮን   እንደገና ያስገባን በመሆኑ የጠየቃቹህን ደንበኞቻችን  መምጣት ለማትችሉ ባላችሁበት መላክ እንችላለን።
 
                    Berhanou Dinke was born in August 1917 in Entoto, north of Addis Ababa, Ethiopia. He held various important positions in Emperor Haile Selassie's Government and served his country as an honest and dedicated civil servant and gained a reputation as a courageous fighter against corruption. From 1961 to 1965, in his last position in the Emperor's government, he served as Ambassador to the United States and effectively promoted the national interest of his country. In 1965, he submitted his resignation in
protest against the autocratic rule of the Emperor. He spent 27 years (1965-1992) in exile in the United States, far away from the country and the family that he loved, including his daughters Yemisrach, Tsedale and Mulushewa. While in exile, he continued to write his criticisms of the Emperor and the military regime
that replaced the Emperor's government. He led a very simple life and passed away on June 18, 1992 at the age of 74 in Jefferson City, Missouri and was buried in the city's Longview Cemetery.
"From what I know of the situation in Ethiopia, I am quite Prepared to believe that, in his book I Stand Alone, Mr. Dinke has made an acute analysis of affairs in his country. I am also quite prepared to believe that his predictions for his country's future make a great deal of sense. (January 28, 1970)" United States Senator James William Fulbright Chairman, Senate Committee on Foreign Relations
"J Am Not Alone contains a gripping message as it comes from the pen of a man who had suffered for his principles. I recommend it wholeheartedly for any reader." United States Senator Harold E.Hughes
 
                    እንደ መቅድም (ከመጽሐፉ) 
“ዘመናዊ” እየተባለ በሚጠራው የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ታሪክ ውስጥ በ1900 ዓ.ም በሮማ ከተማ ረዥም ልብ ወለድ በማሳተም ብቅ ያለው፤ ኋላም በ1901 ዓ.ም የታሪክ መጽሐፍ ያዘጋጀው አፈወርቅ ገ/ኢየሱስ በውል ለታወቀው ለአማርኛ ቋንቋ የሥነ ጽሑፍ ሥራ ፈር ቀዳጅ መሆኑ የዘርፉን ባለሙያዎች ያስማማል፡፡
አፈወርቅ በዘመናዊውም ሆነ በሀገር በቀል እውቀቶች በሁለት በኩሉ እንደተሳላ ሰይፍ የተሞረደ፤ ባለ ድርብርብ ካባ፤ ባለ ብዙ ማዕረግና ባለ ብዙ ሽልማት፤ “የትልቅ ሰው ልጅ ትልቅ” የተሰኘ የዘመኑ ፈርጥ ነበር፡፡
አፈወርቅ የአማርኛ ቋንቋ ወደ ቋሚ የሥነ-ጽሑፍ ቋንቋነት እንዲሸጋገር ከመሟገትና ምሳሌ ከመሆኑ ባሻገር፣ በተግባር መጻሕፍቱን በዚያው ዘመን አሳትሞ አቅርቧል፡፡ 
በተጨማሪም “ዳግማዊ አጤ ምኒልክ” በተሰኘ መጽሐፉ ውስጥ ጉዳዩን እንዲህ በቀጥታ አንስተው ሞግተዋል፦ “…ዳሩ ግን ማነው በመልካም አማርኛ አጣፍጦ፣ አሳምሮ፣ ላንባቢው እንዲቀና፣ ለሰሚው እንዲገባ፣ ትንሽ ትልቁ ሴት ወንዱ እንዲያነበው፣ እንዲያደንቀው አድርጎ የሚጥፈው? የተማሩት ሊቃውንቱም… በጥንት ባሮጌው ቋንቋ በግዕዝ ብቻ ነው መጣፍ እሚወዱ፡፡
ይሄን አሮጌ ቋንቋ ለቤተክርስቲያን ትተው የቀረውን የዓለሙን ነገር የዓለሙን ሥራ ግን፣ ሁሉ በሚያቀው ሁሉ በሚናገረው ቋንቋ በአማርኛ ቢጽፉ ደግ ነበር፡፡ 
ደግሞም ለንግድ፣ ለጥበብ፣ ለመንግሥት የሚጠቅመውን አማርኛውን ማረም፣ ማሳመር፣ ማልማትና ማስተማር ይሻላል ይገባልም፡፡ 
ዛሬ አለቃ ታየ የሚሉት ደቀ መዝሙር ያጤ ምኒልክን ታሪክ ፍትሐ ነገሥት ሊጥፉ ታዝዟል ይባላል፡፡ እስቲ ተሆነ እናያለን፡፡ እግዚአብሔር ይገዘው፤ ነገር ግን ሁሉ እንዲገባውና እንዲገባው በግዕዝ ትቶ ባማርኛ ባደረገው ደግ ነበር፡፡
አማርኛው ግን ገጥ ያለ፣ ቅልጥፍ ላደገበት የተስማማ፣ ለጆሮ ያልገለማ፣ ላንባቢው የሚመችና ለሰሚው የማይሰለች እንዲሆን አድርጎ መጣፍ ነው፡፡
ግዕዝ ብቻ ማሳመር፣ አማርኛን ንቆ ግዕዝ ብቻ ማክበር፣ “አባቱን ገሎ ላማቹ ይነጭ፣ አማቱን ጋርዶ እናቱን ያስፈጭ” የሚሉት ነገር ነው፡፡ አማርኛ ማልከስከስ አሮጌ ቋንቋ ማደስ የተገባም አይደል፡፡
… አማርኛን የሚያሳምር ጠፋ እንጂ፣ ለመደግደግ ፊደል ሳይቆጥር በመጋፊያ እየጣፈ፣ በገል እየጫረ ጽሕፈት የተማረ ሁሉስ ይደገዱግ የለምን?”1 አፈወርቅ እንዲህ እንዲህ እያለ በኃልዮ በነቢበና በገቢር የፈጸመው አማርኛን “በዘመናዊ” ሥነ ጽሑፍ ታሪክ ውስጥ ወደ መድረክ የማምጣትና የመሪነት ድርሻ እንዲገባው የማድረግ ጉዳይ በአብዛኛው ተሳክቶለታል ማለት ይቻላል፡፡ 
ያም ስለሆነ ይመስላል፤ የአፈወርቅ ሥራዎቹ በዘመነኛና በቀደምት ሃያሲያን ዘንድ እስከ ዛሬ ለመቶ ዓመት ያህል ትኩረት መሳብ የቻሉት፡፡
ይህ ሥራውንና የሕይወት ታሪኩን የያዘው መጽሐፍም በተቻለ መጠን ሂሶችን በማጠቃለልና ሕይወታውን በመዳሰስ ጦቢያን እና ዳግማዊ አጤ ምኒልክ አካቶ እንዲሁም አፈወርቅ በአፈ ቄሣር፣ በሮማ ብርሃንና በአዕምሮ ጋዜጦች ላይ በዚያን ዘመን የጻፋቸውን ተረቶች አንድ ላይ በማሰባሰብ “እንጎቻ ወግ” በሚል ርዕስ ሥር ለማጠናቀር ተሞቅሮበታል፡፡
ሌላው ተጠቃሽ ጉዳይ ከአፈወርቅ ሥራዎች መካከል “ጦቢያ” የተሰኘውና በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ዘመናዊ ልብ ወለድ እንደሆነ የሚጠቀሰው መጽሐፋቸው “ከውጭ ሀገር ድርሰት የተቀዳ ነው፡፡” የሚል ዘመናት የተሻገረዉ ክርክርና የሃያሲያን እይታ ነው፡፡
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሃያሲ የሚባሉት ፕሮፌሰር ታምራት አማኑኤል ስለ ኢትዮጵያ ደራሲያን በሚል ርዕስ (1936 ዓ.ም) ጦቢያን አስመልክተው የሰጡትን የመጽሐፍ ምዘና ጨምሮ አንጋፋው ሃያሲ አስፋው ዳምጤና የሌሎች ታላላቅ የዘርፉ ባለቤቶችን አተያይ በማሰባበብ በመጸሐፍ ውስጥ ለማካተት ተሞክሯል፡፡ 
–በ”ዳግማዊ አጤ ምኒልክ” የታሪክ መጽሐፋቸው ምክንያት በአድርባይነት ፈርጀው የሚተቿቸው አያሌ የዘመናችን ምሁራንና ተደራሲዎችም አሉ፡፡ 
ከነዚህም ውስጥ ይህንን መጽሐፍ አስመልክቶ ነጋድራስ ገ/ሕይወት ባይከዳኝ “አጤ ምኒልክ እና ኢትዮጵያ” በተሰኘ ሥራው (1915 ዓ.ም) አፈወርቅን በሂሳዊ ቅኝት ይሞግታል “ባሕሩ ደምሴ” የተባሉ ባለሙያ ደግሞ “አፈወርቅ ገ/ኢየሱስ ከፋሽስት ኢጣሊያን ጋር መሥራቱ ብቻ መታየት የለበትም፡፡
ከዚህ የሚበልጥ ለሀገራችን ዘመናዊነት ለማምጣት ከታገሉት የለውጥ አርበኛ አንዱ ናቸው” ይላል፡፡ 
በተጨማሪም አንጋፋው ደራሲና ተርጓሚ ሣህለ ሥላሴ ብርሃነ ማርያምና ኦሌንሩኦ የተባለ የታሪክ ተመራማሪ፣ “አፈወርቅ” በሚል ርዕስ በፈረንሳይኛ የታተመውን መጽሐፍ አስመልክቶ ሂሳዊ ንባብ ካደረጉት ዘንድ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ 
የቋንቋና የሥነ ጽሑፍ ተመራማሪ የሆነው ዘመነኛው ባለሙያ ቴዎድሮስ አጥላው “ጦቢያ” የሥነ ጽሑፍ ተመራማሪዎች የሙግት መድረክ፡፡” በተሰኘ ርዕስ እስከ ዛሬ ድረስ በጦቢያ ላይ በሥነ ጽሑፍ ተመራማሪዎች የተሰሩትን ምርምሮች በመፈተሽ የራሱን ቅኝት አድርጓል፡፡
እንደ “ዮናስ አድማሱ፣ ዘሪሁን አስፋውና ታየ አሰፋ” ያሉ የሥነ ጽሑፍ መምህራንና እና ተመራማሪዎች ጦቢያን አስመልክቶ የተለያየ ሐሳባቸውን አንጸባርቀዋል፡፡ 
የዚህ ሥራ አሰናኝ በተቻለ መጠን የተገኙ ሰነዶችን በሙሉ ለማካተት ጥረት አድርጓል፡፡ በአጠቃላይ ከላይ ለመመልት እደሞከርነው በአማረኛ ስነጽሁፍ ጥናት እና ምርምሮች ውስጥ ጦቢያ አብይ ትኩረት ከሳቡ ድርሰቶች ውስጥ ዋንኛዋ ናት፡፡
ከድርሰቷ ፈር ቀዳጅነት ባሻገር በርካታ ጉዳዮች በትኩረት ሳቢነቷ እንደምክንያት ልናነሳ እንችላለን፡፡
አጥኚዎቿን ተንተርሰን የጋራ ስምምነታቸውን እና አሟጋች ሀሳባቸውን መመልከት ተገቢነት ይኖረዋል፡፡ በዚህም መንገድ ነው የድርሰቷን ደረጃ እና ገጽታ መረዳት የሚቻለው፡፡ 
ሁሉም አጥኚዎች በሚባል ደረጃ ጦቢያ የመጀመሪያዋ የአማርኛ ልብ ወለድ እንደሆነች ይስማማሉ፡፡ 
ይሄም የውጪዎቹ ዜጎች ምሪት ውጤት ጥናት ተከትሎ ሲሆን፣ ቶማስ ኬን 1975፣ ና ሞልቬር 1980 ይገኙበታል፡፡ 
እንደ ቶማስ ኪን፤ ሞለቬር፤ ዮናስ አድማሱና ቴዎደሮስ አጥላው ያሉ አጥኚዎች ዘንድ ጦቢያ ክርስቲያናዊ መልክ ያላት የፈጠራ ድርሰት መሆኗን ይገልጻሉ፡፡
የተወሰኑትም አጥኚዎች ከክብረ ነገስት መንፈስና ስጋ ጋር ተመሳስሎ ያላት የአዲሱ ዘመን ሚት ድርሰት ናት ብለው ትንታኔያቸውን አቅርበዋል፡፡ 
እንደ ይታገሱ ጌትነት ጥናት ደግሞ ለዚህ የአተያይ ማዕቀፍ አነሳሹ ዮናስ አድማሱ መሆኑን በማሰቀመጥ፣ በዚህ ጎራ የተሰለፉት አጥኚዎች ድርሰቷን ከውስጥ አሊያም ከውጭ የክብረነገስት መልክ እና መንፈሷን ሲያስሱ በሌላ አቅጣጫ ደግሞ በጦቢያ ጥናት ላይ ከሚነሱ ጉዳዮች ውስጥ አሊጎሪያዊነት ‹‹ምሰላዋ›› ነው፡፡ 
ከዚህ አንጻር በድርሰቱ ውስጥ ጦቢያ የተባለችው ገጸባኅርይ አምሳለ ኢትዮጵያ ናት በማለት ሞልቬርንና ታዬ አሰፋን ጠቅሶ ያብራራል፡፡ 
በሌላ በኩል ከድርሰቷ ቅርጻዊ መልኳ በመነሳት ተረታዊነት የሚጎላባት ይሏታል ሞልቬርና ፍቅሬ ቶሎሳ፡፡ ጦቢያ የሚስማሙባት ብቻ ሳትሆን ልዩነት ያላቸው ሙግቶችን ያስተናገደች ድርሰት ናት፡፡
የሙግቶቹ መንስኤ በአብዛኛው ክትንታኔው አቅጣጫ መነሻት የሚመነጭ ነው፡፡
👉አድራሻ 
አራዳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ጀርባ አቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ፊት ለፊት መገኛችን ነው !!
ስልክ 0920745740
         09 11 72 36 56
👉 የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ
  @azop78
 
                    ኤዞፕ  ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት።  በምኒልክ አደባባይ ጣይቱ የባህል ማዕከል ፊት ለፊት የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን፣ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ !!
ስልክ:-  09 11 72 36 56
       
ለማዘዝ    
@Mesay21
@Mesay21
/channel/azop78
/channel/azop78
 
                    ድንቅ የታሪክ መጽሐፍ !!!
ኤዞፕ  ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት።  በምኒልክ አደባባይ ጣይቱ የባህል ማዕከል ፊት ለፊት የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን፣ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ !!
ስልክ:-  09 11 72 36 56
       
ለማዘዝ    
@Mesay21
@Mesay21
 
                    የአጋታ ክርስቲያን ድርሰቶች !!!!
FIVE LITTLE PIGS
MURDER ON THE LINKS
DEATH IN THE CLOUDS
THIRD GIRL
EVIL UNDER THE SUN
A MURDER IS ANNOUNCED
TOWARDS ZERO
PARTNERS IN CRIME
THE THIRTEEN PROBLEMS
POIROT  SI ANNOIA
CAT AMONG THE PIGEONS
 SLEEPING MURDER
THE SECRET OF CHIMNEYS
THREE-ACT TRaGDE
ELEPHANTS CON REMEMBER
 
                    #የዐፄ_ዘርአ_ያዕቆብ_ዜና_መዋዕል
(1426-1460ዓ.ም)
ትርጉምና ሐተታ (ግእዝ-አማረኛ)
 
                    #ሕይወተ_ማርያም_ድንግል
       ✍ሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ መልአክ
ሕይወተ ማርያም ድንግል በሚል ርዕስ የተጠቀሰው መጽሐፍ እመቤታችን ከፅንሰቷ ወራት ጀምሮ እስከ ዕለተ እረፍቷ የተጓዘችበትን የሕይወት መስመር በምሥጢራዊ አገሳስጥ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መጽሔተ ብርሃን ሆኖ አግኝቼዋስሁ፤ አቀራረቡም ትምህርተ አበውን የተከተለ፣ በትርጓሜ የበሰለ ትውፊተ አበውን አጉልቶ የሚያሳይ ቅዱስ መጽሐፍን መሠረት ያደረገ በመሆኑ እውነተኛ የቤተ ክርስቲያኒቱን ልጆች ያስተምራል ብየ አምናለሁ፤ በጸሐፊውም መንፈሳዊ ኵራት ይሰማኛል፣
ብዙዎች ስለ እመቤታችን መስበክና መጻፍ እንደ ነውር ተቆጥሮባቸው በተፈተኑበት ዘመናችን በቋንቋ አጠቃቀሙ በአቀራረቡ የተዋሕዶ ልጆችን የሚያበረታታ ጽሑፍ በመጻፋቸው አደንቃቸዋስሁ፤ ለወደፊቱም ብዙ እጠብቃስሁ፤ አነሣስቶ ላስጀመራቸው፣ አስጀምሮም ሳስፈጸማቸው ስስዑስ እግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁን፡፡
አባ አብርሃም
የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
 
                    #ምዕላደ_ጥበብ  ቅጽ 1እና 2
ስነ እንስሳትን እንደማጥናት የከበረ ሳይንሳዊም ሆነ ሃይማኖታዊ ሥራ የለም፡፡ በተለይ ደግሞ ሳይንሳዊውን
ዕይታ በቤተ ክርስቲያን ዐውድ መቃኘት ወይም በሃይማኖታዊ ሚዛን አስቀምጦ መግለጥ ከባድነቱን የበለጠ ያከብደዋል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህንን ሥራ በመጠኑም ቢሆን ቀድማ ድልው ያደረገች ቢሆንም
ሌሎች ሳይንሳዊ ዕይታወችን ጨምሮ ክመጻሕፍት ጋር በጋጨ ሞግቶ ዳኝቶ እና አስማምቶ ከአንባቢ ምቹ
አድርጎ ማቅረብ ደግሞ ልሕቀት አዕምሮ የሚጠይቅ ነው፡፡ የእንስሳትን ተፈጥሮና ባሕሪያቸውን ባወቅን
መጠን የእግዚአብሔርን ርቀትና አምላካዊ አሠራር እብልጠን እንድናዘክር ያደርገናል፡፡
በመሆኑም እንደ ባሕሪያቸው በየወገን በየወገናቸው አስቀምጦ አንዱ ሌላውን ሳያጠፋው በተሠራላቸው
ሥርዐት መሠረት ሰዎች እንዲማሩባቸውና እንዲጠቀሙባቸው ያደረገ እግዚአብሔር ምንኛ ድንቅ ነው? በዚህ መጽሐፍ ሳይንስ ያልደረሰባቸው እንስሳት የእግዚአብሔር ፍጥረታት እንደመሆናቸው መጠን
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስነ ባሕርያቸውን አስተጋብታ ለአንባቢ እንደሚመች ሆኖ እንዲቀርብ
ይህንን ጊዜ ስትጠብቅ የኖረች መሆኗን አይቼበታለሁ፡፡ የቃላት አጠቃቀሙ የሃሳብ ፍሰቱ የአቀማመጥ ባሕርያዊ ቅደም ተከተሉ የመጽሐፉን ስነ ጽሑፋዊ ውበትና የጸሐፊውን እምቅ አቅም አጉልቶ የሚያሳይ በመሆኑ ይህንን መጽሐፍ ያዘጋጁ በመንፈስ የምወልዳቸው ልጄን እንዳመሰግናቸውና እንደበረታታቸው ያስገድደኛል፡፡
በመሆኑም በቀጣይ ጊዜያት ጸሐፊው መ/ር በጽሐ ዓለሙ ሊያወጧቸው የሚችሉ የቀሪ እንስሳት ባሕርያትና
ተፈጥሯዊ መስተጋብራቸውን ለማየት በልዩ ጉጉት እየጠበቅኩ በሃይማኖታዊም ሆነ በሳይንሳዊው ዓለም
በእንስሳት ላይ ጥናት ማጥናት የሚፈልግ ቢኖር ሌሎች መጻሕፍትን በመፈለግ ጊዜ ማጥፋት አይኖርበትም።
ምዕላደ ጥበብ በጥበበ ቤተ ክርስትያን በንጹሕ የኢኮሎጂ መነጽር በእርጋታ መመልከት ብቻ በቂ ነው።
አባ ሚካኤል ሊቀ ጳጳስ ዘደ/ጎንደር
 ✍ በመምህር በጽሐ ዓለሙ
 
                    #ቻይና
  #በጋዜጠኛው 
  #ዓይን
በአማረኛና በኦሮመኛ ቋንቋ  የተዘጋጀ አዲስ መጽሐፍ ✍አፈወርቅ እያዩ
 
                    ቀደምት ኦሪጅናል መጻሕፍት በኤዞፕ !!
ኤዞፕ  ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት።  በምኒልክ አደባባይ ጣይቱ የባህል ማዕከል ፊት ለፊት የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን፣ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ !!
ስልክ:-  09 11 72 36 56
       
ለማዘዝ    
@Mesay21
@Mesay21
 
                    የታሪክ መጻሕፍት !!!
ኤዞፕ  ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት።  በምኒልክ አደባባይ ጣይቱ የባህል ማዕከል ፊት ለፊት የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን፣ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ !!
ስልክ:-  09 11 72 36 56
       
ለማዘዝ    
@Mesay21
@Mesay21
 
                    "ክቡራ ምድራችን የተሞላችው በ Matter ነው፡፡ እኛ የምንፈልገው ደግሞ Antimatter ነው፡፡ 1 ግራም አንቲማተር ለማግኘት 1 ቢሊዮን ዓመታት ይወስዳል! እኛ ግን በ 50 ዓመታት 0.25 ግራም ሩብ ግራም ማግኘት ችለናል! በአንጻሩ የበላይ አካሉ ምድር ላይ የሚገኙትን ማተሮች ለመፍጠር ብቻ, 5,972,200,000,000,000,000,000,000 kg 5.972 septillion kilogram. አንቲማተር ተጠቅሟል፡ምድራችን ላይ ማተርን አስቀርቶ አንቲማተርን ሰውሯል"
"መረጃውን ለሚመለከታቸው ቅዱሳን አባቶች ለማድረስ ወደ ዔድን ገዳም የሄደው መልዕክተኛ እየሆነ ያለውን ነገር፥ እየሆነ ነው ብሎ ለማመን ተቸገረ፡ በአንዱ ክስተት ተገርሞ ሳያበቃ፣ ሌሎች ለማመን የሚቸግሩ የተዓምራት አይነቶች በላይ በላይ እየተደረቡበት የማሰቢያ ጊዜና ፋታ እያጣ፣ መረጋጋትም እየተሳነው፣ሲብተከተክ እንዴት አባ? እንዴት.? እያለ መልከ-መልካሙን መነኩሴ ሲጠይቅ ነው የስነበተው።
"እኛ ዓላማችንም፣ መነሻና መድረሻችንም፤ ግልጽ ነው! የምንመራበት የፖለቲካና የኢኮኖሚ ርዕዮትም ይህ ነው! ካፒታሊዝም + ሊበራሊዝም + ኒዮ-ሊበራሊዝም + ዲጂታሊዝም + ግሎባሊዝም = ሳታኒዝም!!! ሳታኒዝምን ለማዋለድ ጠንክረን እየሰራን ነው እየተሳካልንም ነው!"
*እኔ ያጠፋሁት ጥፋት የለም! "መዳንም በሌላ በማንም የለም እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና፡፡ (ስራ 4፡12) ብዬ
መማሪያ መጽሐፉንም፤ መጽሐፍ ቅዱሱንም ጠቅሽ አስተማርኩ፡፡ ክፍል ውስጥ ከነበሩት ከ ሃያ አራት ተማሪዎች ውስጥ ሃያዎቹ ክፍሉን ለቅቀው እየገላመጡኝ ወጡ! ወንጌል ከማስተማር ውጪ ሌላ የሰራሁት ስህተት የለም! ወንጌል ማስተማርና ወንጌል መስበክ ስህተት ከሆነ ደግሞ በዕድሜ ዘመኔ ሁሉ ልክመሆን አልፈልግም
ከመጽሐፉ የተወሰደ