azop78 | Unsorted

Telegram-канал azop78 - ኤዞፕ መጽሐፍት

8609

ኤዞፕ ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት። በምኒልክ አደባባይ ፊት ለፊት ያለው የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን ህንፃ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ ነው !! ስልክ:- 09 11 72 36 56 @Mesay21 @Mesay21

Subscribe to a channel

ኤዞፕ መጽሐፍት

አዲስ ነገር ለልጆቻችሁ፣ ለልጆቻችን
💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐

“ሕፃናትን ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተዉአቸው አትከልክሏቸውም፤ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደ እነርሱ ላሉት ናትና አለ፡፡” ሉቃስ 18፥16

የብሉይ ኪዳን ለሕፃናት ተከታይ ክፍል የሆነው
'ሐዲስ ኪዳን ለሕፃናት' ፡ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች

ሁለተኛው ዕትም በሥርጭት ላይ ይገኛል
_

የመጽሐፉ መግቢያ
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
የተወደዳችሁ አንባቢዎች፤ ይህ በእጃችሁ ያለው መጽሐፍ ከልጆቻችሁ ጋር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ታሪኮችን በቀላሉ በየዕለቱ እንድታነቧቸው ሆነው የተዘጋጁት የሁለቱ ተከታታይ መጻሕፍት (ብሉይ እና ሐዲስ ኪዳን) አንዱ ክፍል ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በሁሉም ዕድሜዎች ለሚገኙ ለሁሉም ሰዎች መረዳትን የሚሰጥ መለኮታዊ ጥበብን ያስተላልፋል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስን በእምነት መንፈስ የሚያነበው ሁሉ እግዚአብሔርን ለማወቅ ይጥራል፤ እግዚአብሔር ለሁሉም የሰው ዘር ያለውን የተትረፈረፈ ፍቅርም በሕይወቱ ይለማመዳል፡፡
1. ልጆቻችሁ ጥቅሶቹን እንዲያውቋቸው፣ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉት ብዙዎቹ ጥቅሶች አልተለወጡም፡፡
2. ለልጆቻችሁ፣ ይህን መጽሐፍ ዕለት ተዕለት በምትጠቀሙበት ቋንቋ አንብቡላቸው፤ ልጆቻችሁም በቀላሉ ሊከተሏችሁ ይችላሉ፡፡ ልጆቻችሁ ሲያድጉም ማብራሪያዎች ያሉበትን ይህን መጽሐፍ ራሳቸው እንዲያነቡት ፍቀዱላቸው፤ በዚህም ልጆቻችሁ በሂደት መጽሐፍ ቅዱስን ያለረዳት ማንበብ ይችላሉ፡፡
__

ስለመጽሐፉ
¯¯¯¯¯¯¯¯¯
ከስመ ጥሩ ካህን ቀሲስ ታድሮስ ማላቲ ላቅ ያለ ጠቀሜታ ያላቸው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትረካዎች ባማረ ሁኔታ ተጠናቅረው በዚህ መጽሐፍ ቀርበዋል፡፡
ይህ መጽሐፍ ከሕፃናት ጀምሮ እስከወላጆች እንዲሁም በወጣቶች ሃይማኖታዊ ትምህርት ላይ አደራና ሓላፊነት እስካለበት ማንኛውም ሰው ድረስ ሐዲስ ኪዳንን እና በውስጡ የተካተቱትን እጅግ ወሳኝ ታላላቅ ክስተቶች በአስደናቂ ሁኔታ የያዘ በሁሉም እድሜዎች ለሚገኙ ሁሉ የሚጠቅም ነው፡፡
ይህ የከበረ መጽሐፍ አማርኛው ለሁሉም በሚገባ መልኩ የተዘጋጀና በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ በደስታ እንድንጓዝ የሚጋበዝ ሲሆን ለበርካታ ቀጣይ ትውልዶችም ትልቅ ዋጋ ያለው ሐብት ነው፡፡
_
ቀሲስ ታድሮስ ያዕቆብ ማላቲ የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከከህን ሲሆኑ የመጽሐፍ ቅዱስ አንድምታ (ኮሜንታሪ) መጻሕፍትን በመጻፍ የታወቁ ሊቅ ናቸው።
__
ዘኤልያስ ወልደ ሚካኤል የታላቁ ደብር የደብረ ገነት ቅዱስ ኤልያስ ቤተ ክርስቲያን (ጎጃም፣ ደብረ ኤልያስ) የአቋቋም መምህር የመምህር ወልደ ሚካኤል ልጅ ነው። ከቤተ ክርስቲያኒቱ የአብነት ትምህርቶች በተጨማሪ በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ በሥነ መለኮት (BTh) በማዕረግ ተመርቋል። ከዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ በጋዜጠኝነትና ተግባቦት የመጀመሪያ ዲግሪውን ይዟል።

ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሣዊ በርካታ
መንፈሣዊ መጻሕፍት መካከል ከ12 በላይ የሚሆኑትን በመተርጎም ለአንባቢያን አድርሷል። አብርሃምና ይስሐቅ እና ዮሴፍና ቀሚሱ የተሰኙ የልጆች አኒሜሽን ፊልሞችን ተደራሽ አድርጓል።
ከዚህ በተጨማሪ የዕንቁ መጽሔት ዋና አዘጋጅ፣ እንዲሁም የግዮን መጽሔት ማኔጂንግ ኤዲተር በመሆን ሠርቷል።

በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር እየተዘጋጀ በሚገኘው የአማርኛ ማጥኛ መጽሐፍ ቅዱስ ዝግጅት ፕሮጀክት ውስጥ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን በመወከል በዝግጅት ሥራው ከፍተኛ ተሳትፎ አድርጓል።

በአሁኑ ወቅት የሙሉ ጊዜ የመጽሐፍ የትርጉም እና የአርትዖት ሥራ በመሥራት ላይ ይገኛል።




ኤዞፕ ነባርና ቀደምት መጻሕፍት ጥንታዊ ጥበቦች መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ ጥበብ
አራዳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ጀርባ አቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ፊት ለፊት መገኛችን ነው !!
ስልክ:- 09 11 72 36 56
09 20 74 57 40
@Mesay21

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

በኢትዮጵያ 
     የካህኑ የመልከ ጼዴቅ ልጅ
ኢትኤል የግዕዝ ፊደልና ጽሕፈት በሱ ተጀመረ
  በምድያም ካህን በዮቶር ተሻሻለ

ታላቅ የጥበበ ሀረጋት መጽሐፍ እጃችን ላይ !!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

When love beckons to you follow him,
Though his ways are hard and steep.

And when his wings enfold you yield to him,
Though the sword hidden among his pinions may wound you.

And when he speaks to you believe in him,
Though his voice may shatter your dreams as the north wind lays waste the garden.

For even as love crowns you so shall he crucify you. Even as he is for your growth so is he for your pruning.

Even as he ascends to your height and caresses your tenderest branches that quiver in the sun,

So shall he descend to your roots and shake them in their clinging to the earth.
Like sheaves of corn he gathers you unto himself.

He threshes you to make you naked.
He sifts you to free you from your husks.
He grinds you to whiteness.

He kneads you until you are pliant;
And then he assigns you to his sacred fire, that you may become sacred bread for God's sacred feast.

All these things shall love do unto you that you may know the secrets of your heart, and in that knowledge become a fragment of Life's heart.

But if in your fear you would seek only love's peace and love's pleasure,
Then it is better for you that you cover your nakedness and pass out of love's threshing-floor,

Into the seasonless world where you shall laugh, but not all of your laughter, and weep, but not all of your tears.

Love gives naught but itself and takes naught but from itself.

Love possesses not nor would it be possessed;
For love is sufficient unto love.

When you love you should not say, "God is in my heart," but rather, I am in the heart of God.

And think not you can direct the course of love, if it finds you worthy, directs your course.

Love has no other desire but to fulfil itself.

But if you love and must needs have desires, let these be your desires:

To melt and be like a running brook that sings its melody to the night.

To know the pain of too much tenderness.
To be wounded by your own understanding of love;
And to bleed willingly and joyfully.

To wake at dawn with a winged heart and give thanks for another day of loving;
To rest at the noon hour and meditate love's ecstasy;

To return home at eventide with gratitude;
And then to sleep with a prayer for the beloved in your heart and a song of praise upon your lips.
-----
ጂብራን ግዙፍ ስብዕና ነው። ነገር ግን በጣም ትሁት ሰው ነበር። እኔ በአቅሜ እንዲህ ዘክሬዋለሁ። ወደፊት ደግሞ ከዚህ ይበልጥ ልንዘክረው እንሞክራለን። ኢንሻ አላህ!!
------

ያልተነበበውን የካህሊል አማልክትን አንብቡት !!!!!

-------

አፈንዲ ሙተቂ

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

#መተማመንን_አትስበረው!

መተማመን ልክ እንደ ሸክላ ሳህን ነው፡፡

💔አንድ ጊዜ ከሰበርከው በጣም በጥንቃቄና በከፍተኛ ትኩረት እንደገና አንድ ላይ ልታደርገው ትችል ይሆናል፡፡

💔💔 በድጋሚ ከሰበርከው ግን የበለጠ ወደ ብዙ ስብርባሪዎች ስለሚለወጥ እነዚያን ስብርባሪዎች ለመገጣጠም በጣም ረጅም ጊዜና ጥንቃቄ ይፈልጋል፡፡

💔💔💔 ለበለጠ ጊዜ እየሰበርከው ከመጣህ በመጨረሻ እንደገና ሊጠገን በማይችል አይነት ይደቅቃል፡፡

ከዚያ ብዙ ስብርባሪዎችና ብዙ ብናኝ ብቻ ይቀራል፡፡

ወዳጄ መተማመንን አትስበረው!

#በጥበብ_መኖር መጽሐፍ #5ተኛው ዕትም በገበያ ላይ
#The_#the_subtle_art_of_not_giving_a_

በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛል፡፡

📗📙📕
(በየቀኑ አነቃቂ መልእክቶችን፣ ከምናሳትማቸው መጽሐፍት ፒዲኤፍ፣ የገንዘብና የመጽሐፍት ሽልማቶችን ለማግኘት የፌስቡክና ቴሌግራም ገጾቻችንን ይቀላቀሉ።)

👇
/channel/azop78

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

የተወዳጁ ደራሲና ፈላስፋ እጓለ ገብረ ዩሐንስ የከፍተኛ ትምህርት ዘይቤ መጽሐፍ የድጋሜ ህትመት ትሩፋት ደርሶናልና ይድረሳችኹ !!!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት


ከልጅነቴ ጀምሮ በምሽት ስንሸራሸር በዙሪያዬ የማያቸው ዛፎች ሁኔታ ይገርመኛል፡፡ የሌሉ ያህል ጭምት፣ ትዝታን፣ ቁዛሜን የሚጠሩ ንጹህ ፍጥረታት... በተለምዶ ውኃ ቅዱስ እንላለን አይደል? በቅድስና ዛፎቹን የሚስተካከል ነገር አለ እንዴ? ዛፎች የሚሰጡ፣ የሚያበረክቱ፣ የሚያስጠልሉ እንጂ ከማንም ምንም የማይጠብቁ ጽኑ ፍጥረታት ናቸው፡፡ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድኅን እንዳሉት የሰው ልጅ ከሆነ ያለማወቅ ድንግርግር ወደ ፍዝ ንቃት ሲንደረደር መጀመሪያ የተቀበሉት፣ ያስጠለሉት፣ የመገቡት ዛፎች ነበሩ፡፡ ዛሬም ቢሆን!

ከመጽሐፉ የተወሰደ

ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
🙏🙏🙏

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ቆየት ያለ ትግርኛ መጽሐፍ ቅዱስ እጃችን ላይ ይገኛል።

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ቀደምት ኦሪጅናል ቅጅ የኾኑ መጽሐፍት ያገኛሉ። !!!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

The prophet
የመጀመሪያው ትርጉም ነብዩ በዋቅጅራ ጎባ የተተረጎመ !!!!!

እጃችን ላይ

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

በምግባሩ ጸጥታና እርጋታን ገንዘቡ ያደረገ ነው።ስብዕናው የሚነበብ መጽሐፍ ነው፡፡ከአንደበቱ ጠባቂ ያለው አርምሞን ገንዘብ ያደረገ ነው፡፡በከተማ የሚኖር፣ቆብ ያልደፋ፣ቀሚስ ያለበሰ፣አሸንክታብ ለብሶ በአደባባይ የማይወጣ ተሃራሚ ስውር መነኩሴ ነው፡፡መጽሐፍቶቹ እጅግ ጥብቅና እንደ አለት የጠነከሩ መለኮታዊ ቃል የነጠበባቸው ናቸው፡፡እጅግ ሲበዛ ለቤተ ክርስቲያን ቀናተኛ ወታደር ነው፡፡ብዙ አኀው የዘመን መክፈያ፣ዳግማዊ ቄርሎስ ወዘተ ይሉታል፡፡እርሱ ግን ሙገሳ ይቅርና ልከኛ ክብር እንኳን አጥብቆ ይሸሻል፤ይጸየፋልም፡፡ነገረ ሃይማኖትንና የዓለምን ርዕዮት ጠንቅቆ በጥልቀት የተረዳ ባለአእምሮ ነው፡፡በመንፈሳዊ ዕይታ እንደ አባቶቹ ነገሮችን እንደ ንስር የሚመለከት ብርሃን ክርስቶስ የሆነለት ብዕረኛ ነው፡፡ንባብና ጽሞና፤ትሕትና እና ትጋት፣ፍቅርና እውቀት በተአቅቦ የተዋሐዱለት እውነተኛ አገልጋይ ገብር ኄር ነው፡፡

ምንፍቅናን እራቁቱን ያስቀረ፣የተኩላውን ለምድ የገፈፈ፤በአውሮጳ የምንፍቅና እና ኦርቶዶክስ ጠል እርዮት ዓለም እንደ አሽከላ የተተበተበችውን ዓለም በወንጌል ስብከት የበጣጠሰ ቅን አገልጋይ ነው፡፡በዓለማዊ ከንቱ ልፍለፋና፣በእነ ዳሪዊን እንስሳዊ የሽቅድድም ንድፈ ሃሳብ(theory) ግብዝነት ባለው እውቀት የተበተነውን አህዛብ ወደ እራሱ የመለሰ የበጎች እረኛ ክርስቶስ ያሰማራዊ የመከሩ ሰራተኛ ነው፡፡

ስብከቶቹ ደርዝ ያላቸው።ምስጢራቸው የረቀቀ፤አስተውሎት የሚፈልጉ፣ከአሮጊቶች ወግና ከዓለም ልፍለፋና ቧልት የነጹ ናቸው፡፡ተጠየቃዊ ንጽጽራዊ ነገረ መለኮት(Comparative theology) መዓዛ የሚሸቱ ናቸው፡፡ 'ሞልቶልኛል፣ድኛለሁ፣ሁሉ የኔ፤' ወዘተ ከሚል የሰይጣን ትምህርት የተላቀቀ በአንጻሩ እንደ ቅዱስ ዮሐንስ፦" ምሳር በዛፉ ሥር ተቀምጧል..." ብሎ የክርስቶስን ቤዛነት ሳይዘነጋ በዚህ መሠረትነት በምግባር፣በቱርፋት፣በጸጋ ክርስቶስን መምሰል(theosis) የሚያደርስ የወንጌል ቃል የሚመግብ እውነተኛ መንገድ ጠራጊ የዘመኔ ዮሐንስ ነው ዲ/ን ያረጋል አበዝ፡፡

እኔም እላለሁ፦ተወዳጆቼ መጽሐፍቱን አንብባችሁ ነፍሳችሁን በእግዚአብሔር መንፈስ አስጊጧት፤የእንግድነት ዘመናችሁን ዋጁት፤በክርስቶስ ባለው ፍቅር እለምናችሗለሁ መንፈሳዊ እረፍት ታገኛላችሁ፡፡በመጨረሻም ለምስጢራት በቅታችሁ እግዚአብሔርን ወደ መምሰል ታድጉበታላችሁ፡፡ይሄ ደግሞ ወደ ዘላለማዊ ሕይወት መድረሻ የቀናዉ መንገድ ነው፡፡

(ዲ/ን መልካሙ ኃይሉ )

/channel/azop78

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ቶ '' ያልተነገረው ጥንታዊው የአባይ ሸለቆ ህዝቦች ፍልስፍና !!!

ይህንን መጽሐፍ ብዙ አንባቢያን አላወቁትም !!
ይህ ማለት ደግሞ መጽሐፉ በውስን ሰወች እጅ ብቻ እንዲቀር አድርጎታል።

የመጽሐፉ ጠቅላላ ይዘት የጥንቱ የኢትዮጵያ ፍልስፍና መሰረታዊ አስተሳሰብ ላይ የሚያወራ ቢሆንም ግን የንባብ ባህላችን እጅጉን አናሳ መሆኑና የሚነበቡትም መጽሐፍት በቲፎዞ የሚጮህላቸው መጽሐፍት በመሆናቸው ተደብቆ የመቅረት እንዲህ አይነት እጣ ፈንታ ከገጠማቸው መጽሐፍት አንዱ ሆኗል።

ብልህ አንባቢያን እጅ ላይ ግን አልፎ አልፎም ቢሆን መመልከት ችያለሁ።


እነሆ ቢያነቡት የሚያተፉበት መጽሐፍ ነው !!!!!

መልካም በዓል እየተመኘሁ የበዓል ጥቆማ ቢሆን ብየ አጋራዋችሁ።


/channel/azop78

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

የጉራጌ ማህበረሰብ ታሪክ የሚያብራራ!!
ባህል
ቋንቋ
ታሪክና

የሚዳስስ መጽሐፍ

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

የስንብት ቀለማት ሁለቱም በአንድ

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ውድ የኤዞፕ መጽሐፍት መደብር ደምበኛችን እነዚኽን ኹለት መጽሐፍትበመደብራችን ሸምተህ ረስተህ ኼደሓልና በክብር ተቀምጠውልኻልና መጥተህ መውሰድ ትችላለህ !!!!




ምንጊዜም ለንባብ ባህል መጎልበት እንተጋለን !!!!!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ምድረበዳ ሌሊት
(በእውቀቱ ስዩም)

ስንት ዘመን ሆነ?
ጥላሁን ገሰሰ
“በምሽት ጨረቃ” ብሎ ከዘፈነ?

አንዳንዴ ሳስበው፥  በጥላሁን ዘመን፥
ልክ እንደ አባት  እቅፍ፥ ሌሊቱ ሲታመን
ባውሬ በቀማኛ
በሮንድ ፥በዘበኛ
ላፍታ ሳይሸበር
ፍቅር በፈቃዱ፥ ውጭ አዳሪ ነበር::

ዘመን ተቀይሮ ፥ 
እንኳን በሌት፥  በቀን ፍርሀት ሲሰፈን
ማነው ዛሬ ደፍሮ
“ በምሽት ጨረቃ?” ብሎ የሚዘፍን?

ያስፈራል መንገዱ
ያስፈራል፥ አጸዱ
ያስፈራል አልፎሂያጅ
ያስፈራል ጎረቤት
የሁሉም ሰው መርህ-በጊዜ ወደ ቤት!

ወትሮ እያባረረው፥
እየገፈተረው
ሀቁና ፈጠራው፥ ባንድ ላይ አድሞ
ወደ ቤቱ ገባ፥ ሰው ከጀንበር ቀድሞ
ደጁ ተቆለፈ
በሰአት እላፊ የታጠረ ትውልድ
የሌሊቱን ውበት፤ ሳይቀምሰው አለፈ::

በሰዎች ልብ ውስጥ፤ ዜማ መቀስቀሷ
ባፍለኞች ልብ ውስጥ፥ ፍቅር መጸነሷ
እያፍለቀለቃት
እስክታስለቅቃት
ከቦታዋ ደርሳ፥ የማለዳ ጀንበር
ጨረቃ  ሰማይ ላይ ትንሰራፋ ነበር::

ዛሬ ሰው ቸግሯት
ብቸኝነት ገርፏት
መሪር እያነባች
ዘግይታ፥ ብቅ ብላ፥  ያለጊዜ ገባች::

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ከሞት ባሻገር !


ዲያቆን ኄኖክ ኃይሌ

አዲስ መጽሐፍ !!
በገበያ ላይ ውሏል።

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

የባህላዊና የውጭ አገር ምግቦች አዘገጃጀት

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ኸሊል ጂብራንን በጨረፍታ
------
አፈንዲ ሙተቂ
------
ሳታስቡት የሚያወዛግባችሁ ሰው ገጥሞአችኋል? አዎን! ይህ ሰው ሳታስቡት ያወዛግባችኋል። ነገር ግን የሚጽፈው ነገር ልብና አዕምሮን የሚያረካ በመሆኑ እርሱን ስታነቡት ውዝግቡን ትረሱትና የእርሱን መዝሙር ትዘምራላችሁ።

በዛሬዋ ምሽት ስለዚህ ድንቅ ሰው ጥቂት ነገሮችን እንጽፍ ዘንድ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል (እናንተም በጥቂቱ ብቻ ብታነቡት ይሻላችኋል። ወደ እርሱ ባሕር ከገባን መውጣቱ ይከብደናልና)።
-------
ይህ ሰው ኸሊል ጂብራን ነው። ጂብራን ማን ነው? በሰፊው የሚያስጽፍ ርእስ ነው። በአጭሩ ግን እንዲህ እንግለጸው።

=> መካከለኛው ምሥራቅ ከጥንቶቹ አል-ገዛሊ፣ አል-ራዚ እና ባያዚድ በስጠሚ ወዲህ ያፈራው ታላቁ የምሳጤ አባት ነው።

=> መካከለኛው ምስራቅ ከታላላቆቹና ከጥንቶቹ አል-ኪንዲ፣ አል-ፈረቢ እና ኢብን ሩሽድ (Averroes) በኋላ ለዓለም ያበረከተው ታላቁ ፈላስፋ ነው።

=> መካከለኛው ምሥራቅ ከጥንቶቹ ሩሚ፣ ሰነዒ፣ ፊርደውሲ፣ ጃሚ እና አጣር ወዲህ ያስገኘው የልብ ምት ገጣሚ (mystic poet) ነው።

=> መካከለኛው ምሥራቅ ከአል-መተነቢህ እና ኢብን ሀውቃል ወዲህ ያፈራው ታላቁ የስነ-ጽሑፍ ንጉሥና ገጣሚ ነው።
------
"ኸሊል ጂብራን ሳታስቡት ያወዛግባችኋል" ብያለሁ። ለዚህም ቀዳሚ ምሳሌ ሆኖ የሚጠቀሰው ስሙ ራሱ ነው። ስሙን በዐረብኛ ሲጽፍ "ጁብራን ኸሊል ጁብራን" ነው የሚለው። ትክክለኛ ስሙም እንደዚያ ነው። ከሀገሩ ወጥቶ የአሜሪካ ነዋሪ ከሆነ በኋላ ግን አሜሪካዊያን በስሙ ተወዛገቡ። እርሱም ይህንን ተገንዝቦ ኖሮ የመጀመሪያውን "ጁብራን" ከስሙ ውስጥ አወጣው። አሜሪካዊያን ሊያነቡት የሚቸገሩትን የ"ኸ" ድምጽ "Kah" በማለት ጻፈው። ከዚያም የአባቱንና የአያቱን ስም አከታትሎ በመጻፍ Kahlil Gibran በሚል ስም ራሱን አስተዋወቀ (የአያቱን ስም ሲጽፍ "ጁ"ን ወደ "ጂ" ቀይሮታል)።

እንግዲህ የሀገራችን ሰዎች ስራዎቹን የሚያውቁት በአብዛኛው በእንግሊዝኛ ስለሆነ ነው የእንግሊዝኛውን ዓለም ተከትለው "ካህሊል ጂብራን" የሚሉት። የዐረብኛ መጽሐፎቹ ግን እስከ መጨረሻው ድረስ "ጁብራን ኸሊል ጁብራን" በሚለው ስም ነበር የሚወጡት። ይህንን ያየ ሰው በእንግሊዝኛ መጻሕፍቱ ላይ ከሚጻፈው ስሙ ጋር አለመመሳሉ ገርሞት ሊወዛገብ ይችላል።
-----
ኸሊል ጂብራን በሌሎች ብዙ ነገሮችም ያወዛግባል። ለምሳሌ ያህል ሁለቱን ብቻ እንጠቅሳለን።

=> ጂብራን ሲጽፍ ከዐረቡ ዓለም የተገኙ በርካታ ዓሊሞችና ፈቂሆችን ይጠቅሳል። በተለይም ኢማም አል-ገዛሊን በጣም ይወደዋል። ጂብራን ቅዱስ ቁርኣንን እና ሐዲስን በደንብ ያውቃል። በዚህም የተነሳ ብዙ ሰዎች በእምነቱ ላይ ይወዛገባሉ። ቢሆንም ጂብራን ሙስሊም ሳይሆን በሊባኖስ እና በሶሪያ ከሚኖሩት ማሮናይት የካቶሊክ ክርስቲያኖች ነው የተወለደው።

=> ጂብራን የተወለደበት መንደር በአሁኗ ሊባኖስ ውስጥ ነው የሚገኘው። ሆኖም አንዳንዶች ሶሪያዊ ይሉታል። ታዲያ እርሱም ተቃውሞአቸው አያውቅም። ሊባኖስ ለብዙ ክፍለ ዘመናት የሶሪያ አካል ነበረችና።
-----
ውዝግቦቹን ስታልፏቸው ጂብራንን የልብ አድርስ ሆኖ ነው የምታገኙት። ግጥሞቹም ሆኑ በስድ ንባብ የጻፋቸው መጽሐፎቹ ልብን ከማረስረስ አልፈው እውነትን የመናገር ሃይላቸው ከፍተኛ ነው። ለዚህም ነው ላለፉት መቶ ሃያ ዓመታት በፍቅር እየተነበበ ያለው።

ጂብራን ሶስት ዓይነት አጻጻፍ የሚከተል የልብ-ምት (mystic) ገጣሚ እና ጸሐፊ ነው። ሲፈልግ መጽሐፎቹን በግጥም ይጀምርና በግጥም ይጨርሳል። ሲያሻው ግጥምን እንደ አዝማች እያቀነቀነ በየጣልቃው በጣም የሚነሸጡ እና ቀልብን የሚነኩ ታሪኮችን እንደማብራሪያ ያመጣቸዋል። ሲፈልግ ደግሞ በስድ-ንባብ ይጀምርና በስድ ንባብ ይጨርሳል።
------
ኸሊል ጂብራን በኔ ብዕር ሊገለጽ የሚከብድ ግዙፍ ስም፣ ግዙፍ ገጣሚ እና ግዙፍ ጸሐፊ ነው። እኔም ስለእርሱ የሚሰማኝን ከመጫር በቀር ጂብራንን በተሟላ ሁኔታ እገልጸዋለሁ የሚል እሳቤ የለኝም። ምክንያቱም ጂብራን ማለት በመቶ ዓመት አንድ ጊዜ ውልብ ብለው ከሚጠፉት አብሪ ከዋክብት መካከል አንዱ ነው።

በጂብራን ድርሰቶች ውስጥ ገንነው የሚታዩት አራት ህልዮቶች ናቸው። እነርሱም ፍቅር፣ ትህትና፣ ይቅርታ እና ቅንነት ናቸው። የእርሱ ርእዮት በአንድ ላይ ተጠቃልሎ እና ተከሽኖ ሲቀርብ "የሰው ልጆች ሁሉ ቅን ሊሆኑ እና ፍቅርን ሊሰብኩ ነው የተፈጠሩት። እንደዚያ መሆንም ይችላሉ" የሚል ይሆናል። ለዚህም ነበር በፍቅር ሰባኪነቱ የሚታወቀው ነቢዩላህ ዒሳ (ኢየሱስ ክርስቶስ) በጂብራን መጻሕፍት ውስጥ በጣም ገንኖ የሚታየው።
---------
ኸሊል ጂብራን ከጻፋቸው መጻሕፍት መካከል እጅግ ምርጥ የተባሉት ሁለት ናቸው። አንደኛው በዐረብኛ የተጻፈ ሲሆን ሌላኛው በእንግሊዝኛ የተደረሰ ነው። በዐረብኛ ከተጻፉት መጽሐፎቹ መካከል በጣም ተወዳጅና ድንቅ ተብሎ የተጨበጨበለት "አል-አጅኒሃ ሙክተሲራ" ይባላል። ወደ አማርኛ ሲተረጎም "የተሰበሩ ክንፎች" እንደማለት ነው። ይህ መጽሐፍ በ20 ቋንቋዎች ተተርጉሞአል። በየጊዜው Bestseller እየሆነ በኒውዮርክ ታይምስ እና በሌሎች የአሜሪካ ጋዜጦች ይጠቀሳል። ኢርቱዕ አምላክ የተባሉ ሰው በ2001 ወደ አማርኛ ተርጉመውት እንደነበረ አስታውሳለሁ።
----
ጂብራን በእንግሊዝኛ ከጻፋቸው መጻሕፍት መካከል ደግሞ ምርጥ የተባለው "The Prophet" ይሰኛል። ከጅብራን ስራዎች መካከል ደጋግሜ ያነበብኩት እርሱን ነው። በዓለም ዙሪያ በጣም የሚታወቀው የጂብራን ስራም ይህ "The Prophet" ነው። መጽሐፉ ከ100 በሚበልጡ ቋንቋዎች የተተረጎመ ሲሆን ብዙ ከተሸጡት (Bestsellers) መካከልም ነው። እስቲ በጥቂቱ እንተዋወቀው።

"The Prophet" የተጻፈው በአብዛኛው በግጥም ነው። የመጽሐፉ መግቢያ እና መውጫ ግን በስድ-ንባብ ነው የተጻፈው። ይህ መጽሐፍ የአንድን ልብ-ወለዳዊ ነቢይ ትምህርታዊ ተልዕኮ ነው የሚተርከው።

ነቢዩ "አል-ሙስጠፋ" ይባላል። "አል-ሙስጠፋ" ኦርፋሌስ በምትባል አንዲት የወደብ ከተማ ለ12 ዓመት ይኖራል። ከዚያም ወደ ትውልድ መንደሩ ለመመለስ ፈልጎ መርከብ ይጠብቃል። መርከቧን በመጠበቅ ላይ ሳለ የከተማዋ ሰዎች አጠገቡ መጥተው ስለተለያዩ ነገሮች ይጠይቁታል። እርሱም ጥያቄዎቻቸውን መመለስ ይጀምራል። እነርሱም የሚሰጣቸውን መልስ በአንክሮ እና በገረሜታ ይሰሙ ጀመር።

ሰዎቹ ስለፍቅር፣ ስለጋብቻ፣ ስለንግድ፣ ስለእርሻ፣ ስለህግ፣ ስለጉዞ፣ ስለመጽሐፍ....ወዘተ ተራ በተራ ይጠይቁታል። አል-ሙስጠፋም እጅግ በተዋበ እንግሊዝኛ እና ልዩ ጥበባዊ ልቅና በሚታይበት ትህትና የተጠየቀውን ሁሉ እየመለሰ ያስተምራቸዋል። አል-ሙስጠፋ እንዲያ ሲያደርግ የአድማጮቹ ልቦና እና አዕምሮ ቀስ በቀስ እየተቀየረ ይሄዳል። በኋላም ሁላቸውም የትህትና እና የፍቅር ተገዥዎች ይሆናሉ።
-----
በወደቡ ወደ አል-ሙስጠፋ መጥተው ጥያቄ ከጠየቁት መካከል አንዷ አል-ሚጥራ ትባላለች። አል-ሚጥራ ነቢዩ ስለፍቅር እንዲነግራት ነበር የጠየችው። ጂብራን የአል-ሚጥራን ጥያቄ እና የአል-ሙስጠፋን መልስ እንዲህ ነበር የጻፈው።

Then said Almitra, "Speak to us of Love."

And he raised his head and looked upon the people, and there fell a stillness upon them.

And with a great voice he said:

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

አንድ ኮፒ ብቻ እጃችን ላይ አለ !!!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

በጣም ቀደምት የመጀመሪያው በኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግስት የታተመው ቅዱስ ቁርዓን እጃችን ላይ አለን !!!!!!


ምንጊዜም ለንባብ ባህል መጎልበት እንተጋለን !!!!!!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

የዘመናዊት ኢትዮጵያ ነገስታት ታሪክ !!!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

አንድ ኮፒ ብቻ አግኝተናል !!!

አንደምንጊዜውም ቅድሚያ ለመጣ ደምበኛችን እነኾ እንላለን !!!!!!


ኤዞፕ መጽሐፍት
ቀደምት መጽሐፍትን ምንጊዜም ከየያሉበት አሰባስበን ለደምበኞቻችን እናቀርባለን !!!!!!!!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ቆየት ያሉ የፀሎት መጽሐፍትንንና ድርሳናትን አዘጋጅተናል።

ምንጊዜም ለንባብ ባህል መጎልበት እንተጋለን !!!!!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

#ጠመንጃና_ሙዚቃ
የፋሺስት ኃይሎች ለወታደሮቻቸው ከኢትዮጵያዊያን ጋር መገናኘት “መርከስ“ እንደሆነ ቢለፍፉም ሮም ግን ተወዳጅ በነበረው “ፋቼታ ኔራ” ሙዚቃ ከመደነስ አልቦዘነችም:: “ፋቼታ ኔራ” በጦርነቱ ወቅት የወጣ የፍቅር ዜማ ነው፡፡ ትርጉሙም አንድ የጣሊያን ወታደር በአካል የማያውቃትን ውብ የሐበሻ ሴት መናፈቁን ይገልፃል፡፡ “ስጦታ ይዤ መጣሁልሽ" ይላታል፡፡....ይህ ዜማ ወታደሩ በሰሜንና በምሥራቅ ወደ አዲስ አበባ ሲገፋ በሠራዊቱ ውስጥ የተለመደ የድል ዜማ ቢሆንም ፋሺስት የአገሪቱን መዲና በተቆጣጠረ በአሥራ አምስት ቀናት ወስጥ ግን በአዋጅ ታገደ፥፡ “ፋቼታ ኔራን" ብቻ ሳይሆን በሮም ሱቆች ውስጥ የተሰቁሉ ወጣቱን ያነሳሳሉ የተባሉ የሐበሻ ሴቶች ውብ ምስሎች እንዲወርዱ ተደረገ።

በራስ እምሩ ቤት የተመሰረተውን ቡድን በመከታተልና በማክሰም በኩል የሀገር ፍቅር ማኅበሩን መስራች መኮንን ኃብተወልድ ያህል የጣረ ግለሰብ አልነበረም።መኮንን በሳምንቱ መጨረሻ እየተገናኙ የሚመክሩትን ወጣቶች ከመሰለል አንስቶ ቡድኑ እንዲበተን የሚቻላቸውን አድርገዋል፡፡ ተመሳሳይ የውይይት ክበብን በመመስረትም አምዴ ወንድአፍራሽና ማሞ ታደሰን ወደ ሀገር ፍቅር ቡድን ለማዛወር ችለዋል፡፡ በዚህ ወቅት
ሥር ነቀል ለውጥን የሚሻው ግርማሜ ንዋይም አርፎ የሚቀመጥ አልሆነም።

እንዳይላሉ በአምሥቱ ዓመት የወረራው ዘመን ለአርበኞች መሣሪያ ያመላልስ የነበረ ዓይነ ሥውር ነው፡፡ ይህ ሰው አስቀድሞ ጥይት ለአርበኞች ለማድረስ በአኮፋዳው ይዞ ሲንቀሳቀስ ተያዘ፡፡ ይሁንና “ዓይነ ሥውር የእኔ
ቢጤ በመሆኔ ያዘኑልኝ የጣሊያን ወታደሮች እጃቸው ላይ ገንዘብ ቢያጡ የሰጡኝ ነው” ብሎ ነፃ ወጣ፡፡ነገር ግን ከወራት በኋላም የእጅ ቦምቦችን ባቄላ አልብሶ ለአርበኞች ሊያሻግር ሲሞክር በድጋሚ በቁጥጥር
ሥር ዋለ፡፡…

ኢትዮጵያን በጠቅላይ ሚኒስትርነት የመሩት መኮንን እንዳልካቸው በንጉሠ ነገሥቱ የሥልጣን ጠቅላይነት አባዜ በፖለቲካ ሰማያችን ላይ ጎልተው አልመታየታቸው እውነት ቢሆንም ከሤራው ይልቅ ለኪነ-ጥበብ
ማድላታቸው ግን የራሱ ሚና እንደነበረው አያጠያይቅም፡፡ ለዚህ ደግሞ በሚኒስትርነት ቦታቸው ላይ ሆነው በርካታ መጻሕፍትን ለንባብ ማብቃታቸውና በአገሪቱ አዲስ የሆነውን የሲምፎኒ ኦርኬስትራን
መመስረታቸው አብነት ይሆናል፡፡ መኮንን በፕሬዘዳንትነት የመሩት ቀዳሚው የሲምፎን ኦርኬስትራ “The society of friends of music” የሚል መጠሪያ ነበረው::

ሜሪ አርምዴ አገር ምድሩ ሁሉ“ኧረ ጥራኝ ጫካው" እያለ በሚያንጎራጉርበትወቅት ዝመታን አልመረጠችም፡፡ይልቁንስ በአፍላ ዕድሜዋ ብላታ ኅሩይ ከተባሉ የጦር አበጋዝ ጋር ወደ አምባላጌ ዘመተች፡፡ በእዚያም
ከሠራዊቱ ጎን ተሰልፋ ስትፋለም እግሯን በጥይት ተመታች፡፡ አጋጣሚው ያሳዘናቸው አርበኞች ወደ ቤቷ እንድትመለስ ጠይቀዋት ነበር፡፡ ነገር ግን በጄ አላለቻቸውም፡፡ እንዲያውም ከአርበኞች እኩል ጋራ
ሸንተረሩን እያቆራረጠች ወደ ሽሬ ተጓዘች፡፡

   ✍ ይነገር ጌታቸው(ማዕርግ)
   📖መጽሐፉ የተወሰደ

ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
         🙏🙏🙏

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

የመላከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ የቅኔ መጽሐፍት ውስጥ ቁጥርሽረንድ የኾነውና ከገበያ የጠፋው ታላቅ መጽሐፍ እጃችን ላይ !!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

#አንጥረኝነት
#ብረት ስራ
#ወርቅ ስራ
እደጥበብን የሚዳስስ ታሪካዊ ልቦለድ መጽሐፍ !!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

አጫጭር ታሪኮች ስብስብ መጽሐፍት !!!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ለሕማማት ጊዜ የሚኾኑ የፀሎት መጽሐፍትን አዘጋጅተናል !!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ሥርዓት_ዘሰሙነ_ሕማማት ( ከሰኞ እስከ ዓርብ )

#Ethiopia | ሰሙነ ህማማት ማለት :- ሰመነ - ማለት ሳምንት አደረገ ማለት ነው ፡፡ ይሔውም ከእለተ ሆሳዕና ሰርክ እስከ ትንሳኤ ሌሊት ያለውን ጊዜ እና ቀናት የሚያመለክት ነው ፡፡

ሀመ - ማለት ታመመ ማለት ሲሆን ይህም የሰውን ዘር ሁሉ ከዳቢሎስ ባርነት ነፃ ለማውጣት ጌታችን አምላካችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈቃዱ የተቀበላቸውን ፅዋተ መከራዎች የሚያሳስብ ነው ፡፡

የሰሙነ ህማማት እለታት የአመተ ኩነኔ ወይም የአመተ ፍዳ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ክርስቲያኖች የክርስቶስን ውለታ እያሰቡ እጅግ የሚያዝኑበት የሚያለቅሱበት የሚሰግዱበት ቤት ንብረታቸውን ትተው ከሌላው ቀናትና ጊዜያት በተለየ መልኩ አምላካቸውን የሚማፀኑበት ጥዋት ማታ አምላካቸውን ደጅ የሚጠኑበት ፥ ሀጢያታቸውን በቤተክርስቲያን አደባባይ ለካህኑ የሚናዘዙበት ፥ በአመት አንድ ጊዜ ብቻ የሚገኝ ሳምንት ነው ፡፡

መስቀል እንደማይሳለሙት ሁሉ መጨባበጥ ፣ መሳሳምና የትከሻ ሰላምታ መለዋወጠን አይፈጽሙም፡፡ ሰላምታ የማንለዋወጥበት ምክንያት፣ አይሁድ ጌታን ለመስቀል ሰኞ እና ማክሰኞ መከሩ አልሠመረላቸውም፡፡ ምክራቸው የተፈጸመው ረቡዕ ነው፡፡ ስለዚህ አይሁድ እያንሾካሾኩ “እንስቀለው… እንግደለው” ብለው ይማከሩ ነበር፡፡ ይህንን ለማስታወስ ሰላምታ አንለዋወጥም፡፡ መስቀልም አንሳለምም፡፡ ሳምንቱ የክፋት ምክር የተመከረበት እንጂ የፍቅርና የደስታ ሰላምታ የታየበት ባለመሆኑ ይህንን በማሰብ ሰላምታ አንለዋወጥም፡፡

ይሁዳ ጌታን በጠላቶቹ ለማስያዝ “እኔ የምስመው እርሱ ነው፤ ያዙት” ብሎ በሰላምታው ምልክት ሰጣቸው ፥ ይህ ሰላምታ አምሐ ቅድሳት አይደለም፤ ተንኮል የተሞላበት እንጂ፡፡ የዲያቢሎስም ሰላምታ ተመሳሳይ ነው፡፡ ሔዋንን “ሰላም ለኪ” ብሎ ነው ያታለላት፣ የዲያቢሎስ እና የይሁዳ ሰላምታ ሰይጣናዊ ነው፡፡ ስለዚህ ይህንን ወቅትና ሁኔታ ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ሰላምታ ልውውጥ የለም፡፡

ዛሬ እየተስተዋለ ያለው ይኸው ሰላምታ ያለመለዋወጥ ሁኔታ ሥርወ መሠረቱ ይህ ነው፡፡ ከጥንት ጀምሮ እዚህ ትውልድ ላይ ደርሷል።

በሳምንቱ ስርአተ ፍትሀት አይደረግም ፡፡ ይኸውም ይህ ሳምንት ከሞት ወደ ህይወት የተሸጋገርንበት ከጨለማ ወደ ብርሀን የተጓዝንበት የመሸጋገሪያ ወራት ምሳሌ በመሆኑ ነው ፡፡

በእለተ ምፅአት መላእክት የመለከትን ድምፅ እንደሚያሰሙ የዳግም ምፅአትን እለት በማሰብ ምዕመናን ጥሪውን ሰምተው ከዚያም አስቀድመው የበአሉ ታዳሚዋች መሆናቸውን ለማጠየቅ በዚህ ሳምንት ዲያቆኑ ቃጭሉን እያቃጨለ ምዕመናኑን ያሳስባል ፡፡

በዚህ የህማማት ሳምንት የስግደት የፀሎትና የፆም ስርዐታችን እንደሚከተለው ነው።

† #ሰግደት
በሰሙነ ሕማማት 41 ጊዜ ኪርያላይሶን ፣ 12 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት እየተዜመ እጅግ አብዝቶ ይሰገዳል። ይህም ክርስቶስ ስለኛ በደልና ኃጢት በሰው እጅ ተይዞ የቀበለውን መከራና ስቃይ ለማሰብ ነው። ክርስቶስ ለኛ ፍቅሩን አንዴ ሞቶ ገልፆልናል። እኛ ግን ስለበደላችን ፣ በፍርድ ሰዓት በግራ እንዳንቆም አብዝተን ንስሐ በመግባት ስጋችንን እናደክማለን።

† #ጸሎት
በስሙነ ሕማማት ከ24 ሰዓት ውሰጥ 10 የጸሎትና የንባብ ሰዓታት ይገኛሉ። እኒህም ከጠዋቱ 1 ሰዓት ፣ 3 ሰዓት ፣ 6 ሰዓት ፣ 9 ሰዓት ፣ 11 ሰዓት እንዲሁም ከምሽቱ 1 ሰዓት ፣ ፣ 3 ሰዓት ፣ 6 ሰዓት ፣ 9 ሰዓት ፣ 11 ሰዓት ናቸው ።
በእነዚህም ሰዓታት የጌታን ስቃይ ለማዘከር መዝሙረ ዳዊትና ግብረ ሕማማት ድርሳነ ማኀያዊ አብዝተው ይጸለያሉ። ይህ በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ የሚደረግ የፀሎት ስርዓት ሲሆን ምዕመናን ተገኝተው ፀሎቱን ተካፋይ ይሆናሉየግል ፀሎታቸውም ከመዝሙረ ዳዊት ፣ ከውዳሴ ማርያምና ከውዳሴ አምላክ ፣ ከሰይፈ ስላሴና ሰይፈ መለኮት ሲሆን መልክዓ መልክዕና ድርሳናት እንዲሁም ተዓምራት በህማማት ሳምንት ባሉ ቀናት ውስጥ አይፀለዩም።

ይልቁንም ከቅዱሳን መፃህፍት የጌታን ያምላካችንን መከራውንና ድካሙን የሚያስታውሱ ከትንቢተ ኢሳያስ ፣ ከትንቢተ ኤርሚያስ ፣ ከመዝሙረ ዳዊት ፣ ግብረ ህማማት በየሰአቱ ይነበባል፡፡

† #ጾም
በሰሙነ ሕማማት ብዙ አዝማደ መባልዕት አዘውትረን የምንመገባቸው ምግቦች አይበሉም ። ይልቁንስ በመራብ በመጠማት በመስገድ በመፀለይ በመፆም በየሰአቱ የጌታችን የአምላካችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራውን ህማሙን ግርፋቱን ድካሙን በማሰብ ይዋላል እንጂ፡፡ በዚህም ሳምንት እስከ ምሽቱ #አንድ_ሰዓት እንድንጾም ይኸውም ቆሎ ዳቦ ወኃና ጨው ብቻ እንደታዘዙ በግብረ ሕማማት ላይ ተጽፎ ይገኛል።


***
+ በሰሞነ ህማማት የሚጸለዮና የማይጸለዮ የጸሎት መጽሐፍት አሉ

=> የማይጸለዮ በሰሞነ ሕማማት የማይደገሙ የጸሎት መጽሐፍት :-

1.ድርሳናት
2.ገድላት
3.መልካ መልክ (መልኮች)

=> የሚጸለዮት ደግሞ:-

1. ውዳሴ ማርያም
2.መዝሙረ ዳዊት በብዛት ከወትሮ በተሐየ ቢያንስ የየዕለቱን ሙሉዉን
3. ሰይፈ መለኮት፣ ሰይፈ ሥላሴ፣ ውዳሴ አምላክ
4. ድርሳነ ማኀየዊ የጌታችን ሕማማትና እንግልቱ ያደረጋቸው ተዓምራትና ዐርኬ መልከአ ማኀየዊ አንድ ላይ የየዕለቱ አለው
5.ላሓ ማርያም የእመቤታችን ለቅሶ ሐዘን

+ የጸሎት መጽሐፍቶቹ ያለን በርትተን እንጸልይባቸው ያልገዛን በዚሁ አጋጣሚ በተለይ ድርሳነ ማኀየዊና ላሓ ማርያምን ገዝተን የጌታችንንም የእመቤታችንን ስቃይ እንግልት ሀዘን እንካፈል በረከት እናግኝ ለሀገራችንና ለዓለም ሰላም ለቤተክርስቲያናችን ፍቅር አንድነት ተግተን እንጸልይ አንዘንጋ

" መልካም ሰሞነ ሕማማት "

ከጌጡ ተመስገን የፌስቡክ ፔጅ የተወሰደ

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

""ጥበብ ይናፍቀኛል፣ ተቻችሎ የሚኖር ሕዝብ ያስቀናኛል፣ ድንቁርና ያስፈራኛል፣ ጦርነት ያስጠላኛል"" ጋሽ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን

Читать полностью…
Subscribe to a channel