ኤዞፕ ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት። በምኒልክ አደባባይ ፊት ለፊት ያለው የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን ህንፃ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ ነው !! ስልክ:- 09 11 72 36 56 @Mesay21 @Mesay21
ሐገር የታመመች ሰሞን ፪
(ያዕቆብ ብርሃኑ)
*
ኦስካር ዋይልድ ‹‹እውነቱን ስትነግራቸው አስቃቸው፡፡ ካላሳቅካቸው ይሰቅሉሃል፡፡›› ማለቱን ሰምቻለሁ፡፡ ቧልተኞች ያልተመዘገቡ የኅብረተሰብ የስነልቦና ሀኪሞች መሆናቸውንም አውቃለሁ፡፡ እኔ ግን እላለሁ - ሁሉም ነገር ቧልት ሲሆን ሀገር ሥርዓት ያጣል፡፡ ቧልት እንክብል ነው፡፡ ለዚያውም የማደንዘዣ እንክብል... ውሎ ሲያድር አምጡ ድገሙ የሚያስብል ሱስ የሚሆን ‹ድራግ›... ሕመማችን እያከከ እንድንላመደው፣ እንድንዋሃደው የሚያባብል አደንዛዥ እጽ... እንዲህ ዓይነት ኅብረተሰብ ደግሞ በየትኛውም ነገር ውስጥ አቋራጩን ያስሳል፡፡ ለጨቋኝ አገዛዞች ምቹ ነው፡፡ ግልብ ነው፡፡ ከእውነተኛ ጀግኖች ይልቅ ተዋኒያንና ትወና ይወዳል፡፡
እኛው ነን እኮ...
ከውጤቱ ይልቅ ሂደቱ እንደሚሰራን ከረሳን ቆይተናል፡፡ ከጥንት እስከ ዛሬ ጠዋት በኢትዮጵያችን ምድር የሆነው የሚሆነው ይሄው ነው፡፡ በአያቶች ዘመን በተረታችን አማካኝነት ከመማርና እና መስራት ይልቅ ከደህና መወለድ ካልሆነም ከደህና መጠጋት ብልሃት እንደሆነ ይነገረን ነበር፡፡ (ከደህና ተወለድ ወይ ከደህና ተጠጋ) ትናንት - ለመሾም ለመክበር - ከመማር መስራት ይልቅ መሞዳሞድ ይበጅ ነበር፡፡ ዛሬም ቢሆን አገዛዙን የተጠጋጉ ብቻ ድንገቴ ቱጃር ሆነው ብቅ ብለው ያስገርሙናል፡፡ እንደገና ከአገዛዙ ጋር አብረው መደብዘዛቸው ባይቀርም ቅሉ...
እንዲህ ዓይነት ኅብረተሰብ ግን የአቋራጭ ልክፍተኛ ነው፡፡ አቋራጭ ደግሞ ልህቀትን (merit, excellence) ያደኸያል፡፡ ሁሉም ነገር ለችርቻሮ ቀርቦ በገበያ ዋጋ ስለሚተመን ሰው መሆንን ይበድላል፡፡ የምትመዘነው በመክፈል አቅምህ እንጂ በምታበረክተው ልክ አይደለም፡፡ ቅዱስ እንደሆነ የሚሰበክልን ትዳር እንኳን ለገበያ ቀርቦ በደራ ጨረታ ሲወሰን ይታያል፡፡ እናም ሰው ከስምና ከቁጥር የሚያልፍ አሻራ ያለው ፍጥረት ይሆን ዘንድ ይሄን ዘመን ያልሻረው አደገኛ አዝማሚያ መዋጋት ያስፈልገው ይመስለኛል፡፡
ሀገርን፣ ሕዝብን፣ ዘመንና ግለሰብን በምን ትመዝነዋለህ? ለሚለኝ ‹በጀግኖቹ› ይሆናል መልሴ... በጀግኖቹ እመዝነዋለሁ፡፡ ጀግናህን አሳየኝና ማንነትህን እነግርሃለሁ፡፡ ማንንም በጀግናው፣ አርዓያ በሚያደርገው ነገር በዚያ ማንነቱን፣ ምኞቱን፣ ኪሎውን፣ ትልሙንና ሕልሙን መመዘን ይቻላል፡፡ በእርግጥ ሰው እንደ ጅረት በየደረሰበት እንደ ሁኔታው መልኩን የሚገልጥ ነውና ሁሉም ሰው የሕይወት ዘመን ነጠላ ጀግና ይኖረዋል ማለት ዘበት ነው፡፡
ነገር ግን እላችኋለሁ የትኛውንም ኅብረተሰብ ንቃት ለመመዘን ወንዞቹን አትዩ፡፡ መንገዶች፣ ግድቦች፣ አደባባዮች፣ ድልድዮችም... በችሮታ ሲገነቡ አይተናል፡፡ ይልቁንስ የየትኛውንም ኅብረተሰብ የንቃት ደረጃ የሚበ˚የነው አሰላሳዮቹን (thinkers) የሚይዝበት መንገድ ነው፡፡ ኅብረተሰብ አሰላሳዮቹን በሚይዝበት አኳኋን በዚያ የየንቃት ደረጃው (collective consciousness) ይመዝናል፡፡ ማኅበረሰብ አሰላሳዮቹን በሚይዝበት መንገድ የወደፊት ዕጣው - የባርት ወይስ የአርነት - የሚለውን መገምገም ቀላል ነው፡፡
ዛሬ ዘመናችን ሆኖ ተገልጦ ስናየው - ቢያምርም ቢከረፋም - ያኔ በአብርሆቱ ዘመን የአውሮፓን ሥልጣኔ የቀየሱት ባልተኞች አልነበሩም፡፡ እንዲያውም እነ ማርጋሬት ፖሬት፣ ጆርዳኖ ቡሩኖ፣ ኤድዋርድ ዊትማን ዓይነት እና ሌሎችም... ማኅበረሰብ በሁለንተናዊ ግንዛቤው ጥቂት ፈቀቅ ይል ዘንድ ሲሉ - ለነፍሳቸውም ሀቅ ሲሉ - እንደ ጧፍ የተንቀለቀሉቱ፣ እንደ ችቦ ተንቦግቡገው በነፍሳቸው መራር የሕይወት ዋጋ የከፈሉቱ እንጂ...
በእርግጥ አውሮፓዊው ሥልጣኔው የሰውን ልጅ በነፍስ ያራመደ ወይስ ያደኸየ? የሚለውን ለጊዜው እንተወው፡፡ ዛሬ እግርህን አንፈራጠህ ቆሞህ ‹ሰልፊ› ያምትነሳበትን ሥልጣኔ የፈጠሩት ግን ፌዘኞች አልነበሩም፡፡ እንዲያውም ሰው ከአስተሳሰብ ባርነት እንዲላቀቅ፣ ወንጌልን በወንጀል ከሚግት እስራት እንዲፈታ፣ እንደ ስፒኖዛ ያሉ ፈላስፎች አጥንት ድረስ ዘልቆ የሚሰማ እርግማን ውግዘትና መገለል አስተናግደዋል፡፡ ከስለት ጥቃት ለጥቂት ተርፈዋል፡፡ ምስኪኑ ስፒኖዛ የሀያ ሁለት ዓመት ልጅ እያለ ከምኩራብ ሲወጣ ከተሰነዘረበት የስለት ጥቃት ለጥቂት ተረፈ፡፡ ከስለት ጥቃቱ ያተረፈውን የተዘለጠለ ካባ ዘወትር በየአደባባዩ ለብሶ ይታይ ነበር አሉ፡፡ - ለአመጻ! -
ይህም ሁሉ ሆኖ የአውሮፓ የሕዳሴ ጉዞ ሂደቱን የሚያቀጣጥሉ አሳቢያንን የሚያሰናዝር የሚጠብቅ ሆደ ሰፊነት ነበረው፡፡ ለአብነትም ቮልቴር የመሳሰሉ አዋኪ ጠቢባን እልፍ ጊዜ ቢጋዙም፣ አንዳንዴ በጥንቃቄ ቢጎሻሸሙም ሥራዎቻቸውን ለማሰላሰል ሙሉ ለሙሉ ገደብ አልተጣለባቸውም፡፡
ዣን ዣክ ሩሶ፣ አርስቶትል፣ አንስታይን፣ ካርል ማርክስ፣ ጆን ሎክ፣ ኤሚል ዞላ... በአጠቃላይ ሁሉም አፈንጋጭ ፈላስፎች፣ ደራሲያን ወይ ታስረዋል አሊያም ቢያንስ አንድ ጊዜ ተግዘዋል፡፡ የካርል ማርክስማ መብከንክንማ ይለያል፡፡ ከጀርመን ፈረንሳይ፣ ስዊዝ፣ ቤልጄም እንደገና ጀርመን መልሶ ፈረንሳይ በመጨረሻ ወደ ሎንዶን እንዲችው እንደተንከራተተ ዘመኑን ተወጣት፡፡ በተደጋጋሚ አንዳይጽፍ ጋዜጣ እንዳያዘጋጅ ማዕቀብ ቢጣልብትም አንድ ሦስተኛውን የዓለም ሕዝብ ለአብዮት ከማሰለፍ ግን ማንም አላገደውም፡፡
ቢሆንም ምዕራባዊያኑ እንደ እኛ አፍንጫ በመፎነኑ፣ ምላስ በመስለቡ ሙጭጭ አላሉበትም፡፡ ይሄም መለሳለሳቸው በረከት ሆኖላቸው ዛሬ ዘመናዊውን ሙሉ ዓለም የሚያሾር የትርክት የበላይነት አቀዳጅቷቸዋል፡፡
የእኛ ግን ይለያል፡፡ ‹‹ነገሥታት ሸንጋይ ምላስን ይወድዳሉ›› እንዲል አፍሪካዊው ፈላስፋ ዘርዓያዕቆብ ከነገሥታቱ ዘመን ጀምሮ ከአሰላሳዮቹ ይልቅ ተራቢዎች ለመኳንንት እና ለሕዝብ ቅርብ ነበሩ፡፡ ከአሳቢዎቹ ይልቅ አጫዋቾቹን የሚያጀግን ኅብረተሰብ ደግሞ ከእምቢ አሻፈረኝ፣ ከለውጥ ጋር ኩርፍ እንደሚሆን፣ ወደ ንቅዘት እንደሚያዘግም፣ ቧልት፣ እንቶፈንቶ (nugatory) እንደሚያነፈንፍ ግልጽ ነው፡፡
ቧልቱስ ስንኳ ምግባርና ለዛ የለውም፡፡ ስሪቱ ስድና መደዴ ቅይጥ ነው፡፡ መንጋነት ይጠናወተዋል፡፡ ይበልጥ እንዲገርምህ ‹‹ቧልተኝነትን›› ከ‹ጅነሲቲ› ጋር አመሳክሮ ሲራቀቅ ታገኘዋለህ፡፡ ለዚህስ ይሆን በትርክታችን ውስጥ ከአሰላሳዮች ይልቅ ተረበኞች የመበርከታቸው ምክንያቱ? ለዚህ ማመሳከሪያ መዝገብ ድርሳን ማገላበጥ ለምንህ? የቧልቱ ሰሌዳ ‹ቲክቶክ› ብቅ ያለ ሰሞን ከየትኛውም ዓለም በላይ የተረባረበው የእኛው ሰው መሆኑን ልብ ማለት ብቻ ይበቃህ የለምን? የፌስቡኩስ ቢሆን?
ነገርግን አሰላሳዮች ኅብረተሰብን፣ በዘመኑ ቋንቋ ‹አክቲቪስቶች› ደግሞ መንግስትን ይተገትጋሉ፡፡ አሰላሳዮች ስለለምን ኅብረተሰብን ከተባለ ኅብረተሰብን መለወጥ መንግስትን የመለወጥ ዋነኛ መንገድ ስለሆነ... ማንኛውም ኅብረተሰብ የሚመስለውን መንግስት ይሰራል፡፡ ኅብረተሰብ በችሮታ የሚያገኘው አንዳችም ዓይነት መብት አይኖረውም፡፡
በአጭር የተቀጩት የ20ኛው ክፍለዘመን ኢትዮጵያዊ ምሁር ገብረሕይወት ባይከዳኝ ‹አጤ ምኒሊክ እና ኢትዮጵያ› በተሰኘ መጽሐፋቸው ይሄን ሃሳብ ሲያብራሩት...
…………………
ድ…ን…ገ…ት ባነኑ!!!!
“እ -ሃ- ሃ——!ይሄ ነገርማ አንዳች ሚልኪ ቢኖረው ነው እንጂ እንዴት ሆኖ ነው እንዲህ ያለ የግራ ግጥምጥሞሽ ዝም ብሎ የሚገጣጠመው?” ብለው አሰቡ።
ለግራ ዘመም ድርጅታቸው፤ ግራ ከተጋቡ ጓዶቻቸው ጋር፤ ግራ ክንዳቸውን ተመትተው ከዋናው የእስር ቤት በር በስተግራ ካለ ቤት፤ ከባልንጀራቸው ከግራኝ ጎን፤ ለ…ዛውም ከጓደኛቸው ከግራኝ በስተግራ ተኝተው፤ ግራ ተጋብተው አራሳቸውን አገኙት።
ይሄ የግራ ግጥምጥሞሽ ለጥቂት ቀናት ግራ እያጋባቸው ቆየ። በዛ ላይ የግራ ክንዳቸው ቁስል ይጠዘጥዛቸዋል፤ ዝምምምም ብለው ከቆዘሙበት የሃሳብ ባህር ድንገት ወዳጃቸው ግራኝ በስተግራ ጆሯቸው በኩል ተጠግቶ ይነዘንዛቸዋል ግራ ያጋባቸዋል፤ ግራ ገባቸው።
አንድ ሌሊት የአብዮት ጠባቂዎች የእስር ቤቱን በር እንደልማዳቸው ድንገት በይል በርግደው ገቡ። የቆሰለውን የግራ ክንዳቸውን በከስክሳቸው እየረገጡ ያስጮኋቸው ጀመር። “አንተን ብሎ ግራ ዘመም ግራ የገባህ አናርኪስት!!! እውነተኛ ግራ ዘመም እኛ ነን!! ደግሞ
ላንተ ግራ የሰጠህ ማን ነው !" እያሉ እያዳፉ እና እየቀጠቀጡ ከነበሩበት ቤት በስተግራ ካለ
ሌላ ጨለማ ቤት ወሰዷቸው። ያኔ ይበልጥ ግራ ገባቸው።
"ካልጠፋ አቅጣጫ ሰው እንዴት ግራን ይመርጣል? እንዴት በግራ ይጣላል? ግራ እንዴት ከግራ ይለያል? እያሉ በሃሳብ ተዋጡ። "ግራ ዘመም ነኝ" ብለው ህይወታቸውን የሰጡትን ግራ “ግራ አይደለም! ግራ እናሳይሃለን" እያሉ በሚደነፉ ግራ ዘመም ወታደሮች ንግግር ይበልጥ ግራ ገባቸው።
ያን እለት አካላቸው በግርፋት ተተልትሎ እራሳቸውን ስተው አደሩ።
ሲነቁ በግርፋት የቆሰለው የገላቸው ጥዝጣዜ አላስቆም አላስቀምጥ አላቸው፤ አለቀሱ፤ ጮሁ!!!! ሊነጋጋ አካባቢ የጀርባቸውን ቁስል በእራፊ ጨርቅ እየጠረገ በልቅሶ የሚነፈርቅ አንድ ወጣት፤ ወዳጃቸው ግራኝ ሌሊት ማረፉን ሳግ እየተናነቀው አረዳቸው።
ደነገጡ!!! ለግዜው የቁስላቸውን ጥዝጣዜ እረሱት። እንደ ትልቅ ጉርሻ ጉሮሯቸውን አንቆ የያዛቸውን ሳግ እና እንባ ድንገት ዘረገፉት፡
ትኩስ እንባ የቀኝ ጉንጫቸውን እያቋረጠ ሲንዠቀዠቅ ይሰማቸዋል። የቀኝ ጉንጫቸውን ብቻ!። ግራ ጉንጫቸውን ዳበሱ፤ እንባ የለውም፤ ግራ ጉንጫቸውን የሚዳስሱበት እጆቻቸው በቀኝ አይናቸው ብቻ ይታዩዋቸዋል።................
📖📖 ጠያይም_መላእክት
የኮምዩኒ ዝም ርኩስ መንፈስ
✍✍ቤተማሪያም ተሾመ
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
🙏🙏🙏🙏
ለካ ሁለት ቃላት የሠውንልጅ ህይወት የመከራ ቋት ውስጥ መክተት ይችላሉና።ለካ ሁለት ቃላት ብቻ ማንነትን እልም ያለ ውልአልባ ቀውስውስጥ ለመጨመር ብቃቱ አላቸውና።
ሠማይናምድሩ ዞረብኝ ያለችኝን ሁለት ቃላት ደግሜ ሣስታውሳቸው ውስጤ መቃጠል ይጀምራል።እና በምድር ላይ እንደ ሣር የበቀልኩ ብቸኛ የሠውፍጡር የሆንኩ ያህል ይሠማኛል። " እናትሽ አይደለሁም " ነበር ያለችኝ።
"የጭን ቁስል"
የፍልስፍና ጽንሰ ሐሳብ
አንድ የሩቅ ምስራቅ ፈላስፋ ወደ ንጉሡ ችሎት ተጠርቶ ቀረበ፡፡ ፈላስፋው በሕገቡ ዘንድ በምድር ላይ ታይቶ እንደማይታወቅ ታላቅ ሎጂሽያን ተገምቶ ነበር፡፡ ፈላስፋው ማንኛውም ነገር ተጨባጭ እንዳልሆነ ያስተጋባ ነበር፡ ሁሉም ነገር የተመሠረተው ከሕልም ጋር ልዩነት በሌለው አኳኋን መሆኑን በማስረዳት አበክሮ ይሟገት ነበር፡፡ ንጉሡ የተግባር ሰው (ፕራግማቲክ) ነበር። ሕገ በሙሉ ወደ ቤቱ እንዲከት ትእዛዙን አስተላፈና አንድ ዕብድ ዝኆን በአውራ ጎዳና ላይ እንዲለቀቅ አደረገ፡፡ ፈላስፋው መንገዱ ላይ የፊጢኝ ታስሮ ቆሟል። ፈላስፋው የሚከንፈውን ዝኆን ከርቀት እንደተመለከተ አድነኝ ዝኆኑ ተጨባጭ ነው!›› በማለት ወተወተ፡፡
የሁኔታውን አደገኝነት በመመልከት በዕብደት የሚከንፈው ዝኆን ከጉዞው እንዲገታ ተደረገ፡፡ ፈላስፋውም ዳግም ወደ ንጉሡ ችሎት ቀረበና፤ «አሁንስ ስለፍልስፍናህ ምን ትላለህ?›› ተብሎ ተጠየቀ።
«ሁሉም ነገር ተጨባጭ አይደለም›› አለ፡፡
‹‹ዝኆኑስ?›› ንጉሡ ጥያቄውን ሰነዘረ፡፡
የሚጮኸው ፈላስፋ ተጨባጭ አይደለም:: ፈላስፋውን ከሞት ያዳነውም ንጉሥ ተጨባጭ አይደለም፡፡ ሁሉም ነገር ተጨባጭ አይደለም፡፡ ሆኖም እዚያ አውራ ጎዳና ላይ ደግማችሁ አትሰሩኝ፡፡ ምክንያቱም እኔ ፈላስፋ ነኝ፡ ዝግጁ የሆንኩት ለመስሪ ከር ብቻ ነው፡፡ ከዝኆን ጋር መከራከር ደግሞ አይቻልም፡ በንጉሡ ግዛት ፈላስፎች ካሉ፤ አቅርቧቸውና በመከራከር ለማሳመን ዝግጁ ነኝ›› አለ ይባላል።
የምብግዜም ተመራጭ ቤተ መጽሐፍት ቤታችኹ ኤዞፕ
በሽያጭ ላይ ነን
አዲስ መፅሐፍ
#እሰሩኝ!
"እሰሩኝ" የሚለው ጥቂት ቢሆንም "ፍቱኝ" ስላለ ሚፈታ ግን ማንም የለም።
#ዛሬ_የት_እንዳላችሁ_አትጨነቁ!
"... እያንዳንዱ ሳይንቲስት የሆነ ቀን ላይ የሚያለቅስ ህጻን ልጅ ነበር፤ እያንዳንዱ ታላቅ ኪነ ሕንፃም የሆነ ቀን ላይ ባዶ ካርታ ብቻ ነበር።
ዛሬ የት እንዳላችሁ መጨነቁ አስፈላጊ አይደለም ነገር ግን ነገ የት እንደምትደርሱ ማለምና ማስኬድ ላይ ነው ትልቁ ቁም ነገር ያለው።
ልብ በሉ አልበርት አንስታይን ሲወለድ ከንፅፅር ፅንሰ ሀሳብ ጋር አልተወለደም፤ አይዛክ ኒውተንም የእንቅስቃሴ ህጎቹን በእናቱ ማህፀን ውስጥ ቀምሮ አልወጣም፤
ዱባይ ውስጥ የሚገኘው ስምንት መቶ ሠላሳ ሜትር ገደማ የሚረዝመው “ቡርጅ ካሊፋ” የተሰኘው የዓለማችን ረዥሙ ኪነ ህንፃም ከሆነ ጊዜ በፊት ሕንፃ ሳይሆን ባዶ ካርታ ብቻ ነበር።
ሁሉም ነገር ከባዶ ነው የሚጀምረው።
ስለዚህ እናንተም በሙሉ ተስፋ ከጣራችሁ እና ዓላማችሁን ለማሳካት ቁርጠኛ ከሆናችሁ ከምንም እና ከየትም ተነስታችሁ የስኬትን ጫፍ መቆናጠጥ ትችላላችሁ” በማለት ሰሎሞን ተሰናብቷቸው ከክፍሉ ራመድ ራመድ ብሎ ወጣ።
#ከስሙር_መጽሐፍ_የተቀነጨበ
ከአንድ አብራክ የወጡ በደራሲ #በረደድ ገዳሙ የተጻፉ ሶስት ምርጥ መጽሐፍት
#ሉባር
#ሰርዲዮን እንዲሁም አዲሱ መጽሐፉ
#ስሙር
በኔ ግምት ለታሪክ ለባህልና ለቋንቋ ትኩረት የሚሰጥ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ሊያነበው የሚገባ
Читать полностью…ፊየዶር ሚካሂሎቪች ዶስቶቭስኪ (1821 — 1881 ) ታላቅ ሩሲያዊ ደራሲ፣ ሃያሲ ፣ አጭር ልብ ወለድ ፀሐፊ ' ጋዜጠኛ እና ፈላስፋ ነው፡፡ ለስራዎቹ የሰው ልጅ ስኑልቦና በፖለቲካዊ ፣ ማህበራዊ እና መንፈሳዊ ቀውሶች ውስጥ -
ብተለይም በ19ኛው ክ/ዘመን ሩስያ - ምን ይዘት እንደነበራት ያሳያል፡፡
ከ1846 — 1880 ባሉት አመታት ለአንባቢያን ያበረከተው ስራዎች - The Brother Karamazov (1879) Damons (1871) ፤ The Idiot (1868) Notes from The Underground (1864) እንዲሁም “ወንጀልና ፍርድ "በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ የተመለሰው ይህ መፅሐፍ Crime and Punishement (1866) ተጠቃሾች ናቸው
ዶስቶቭስኪ በፅሑፎቹ በጥልቀት ከሚዳስሳቸው ርዕሳን መካከል ኃይማኖት
ስነ - ልቦና እንደሁም ፍልስፍና ይገኙበታል የእርሱ ስራዎች ድህነትን፣ ራሰማጥፋትን፣ ማታለልን እንደሁም የስነ - ምግባር ፈተናን ይዳስሳል። Crime and Punishment ከ170 በሚበልጡ ቋንቋዎች ተተርጉሞ በመላው አለም የተነበበ ስራው ነው በበርካታ አገራት የቲያትር መድረክን የተቆጣጠረወ
ይህ ድርሰቱ በ1935 ደግሞ ወደ ፊልም ተቀይሮለታል።
በስድስት ክፍሎች የሚተርከው የመጽሐፉ እውነታ አንባቢን እየሞገተ በምናብ እያከራከረ ከፍፃሜ ይደርሳል፡
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
🙏🙏🙏
በነገራችን ላይ የአሊ በርኬ የህያወት ታሪክ በመጸሐፍ ከተዘጋጀ ከሁለት ዓመት በላይ ሆኖታል፡፡መጽሐፉን በኦሮምኛ ያሰናዳው ጋዜጠኛና ደራሲ ኢሳያስ ሆርዶፋ ሲሆን እህቱ ደግሞ ወደ አማርኛ መልሳዋለች፡፡ ኢሳያስ ሆርዶፋ በርካታ መጸሕፍትን በአፋን ኦሮሞ ያሰናዱ ሲሆን በኦሮምኛ በሚጽፉት የሬድዮ ድራማዎችም ይታወቃሉ፡፡የሚገርመው ደራሲ ኢሳያስ አሊን ከደርግ ዘመን ጀምሮ ኢንተርቪው ሰርቼዋለሁ ይላል ይሁን እንጂ ለመጽሐፉ ሽፋን የተጠቀመው ግን የሻምበል ባሻ መኮንን ከበደን ምስል ነው፡፡ሻምበል ባሻ መኮንን ከበደ አሁንም በሕይወት አሉ፡፡እኔ ከወራት በፊት የአሊ በርኬን የህይወት ታሪክ መጽሐፍ እያነበቡ ተገናኝተን አውግተናል፡፡ አስፈላጊ ከሆን ለጥቂት ሰዎች ስልካቸውን እልካለሁ፡፡ከስር የምትመለከቱት ምስል የደራሲው ነው፡፡
ከእንዳለ ጌንቦ የፌስቡክ ገፅ የተወሰደ
ማኅቶተ ምግባር ወሃይማኖት፣ መጋቤ ምሥጢር ወጥበብ፣ መፍቀሬ ትሕትና ወፍቅር፣የተባለው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በዘመኑ እውነተኛውን ሕይወት የኖረ ነው፡፡ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደ ፀሐይ አብርተው፤ እንደጨረቃ ደምቀው፤ እንደ ከዋክብት አሸብርቀው፤ ወንጌልን በቃላቸው፣ በመጻሕፍቶቻቸው፣ በምግባራቸው ሰብከው ካለፉ ቅዱሳን ሊቃውንት አባቶች መካከል አንዱ ነው፡፡
ተወልዶ ካደገበት ሀገር ተነሥቶ ወንጌልን ዞሮ ባስተማረበት ሁሉ ምስክሮቹ የሚሆኑ የወንጌል አበርክቶዎቹ አሉ፡፡ እርሱ ያልተረጎመው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል፣ ያዳሰሰው ነገረ ሃይማኖት፣ ነገረ ቅዱሳን፣ ነገረ ማርያም፣ ነገረ ቤተ ክርስቲያን የለም ብለን ብንጠቅስም ካገኘናቸው መካከል ከብዙ በጥቂቱ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ
ከመጡት መጻሕፍት መካከል የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል የተረጎመበት ድርሳኑ አንዱ
ነው፡፡
በብዙ ረቂቅና ምጡቅ ሰፊና ጥልቅ በሆኑ መጻሕፍቶቹ የምናውቀውን ቅዱስ ዮሐንስ
አፈወርቅ የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል እንዴት አድርጎ ተርጉሞት ይሆን የሚለውን
እንድናነብ ዕድሉን የሰጠን ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም ባስነበበን እነኋት
ክርስትና፣ ስምንተኛው ቀን፣ የነፍስ ወግ፣ የትኅርምት ሕይወት፣ ኅብረ ወንጌል፣ ድንቅ
እውነትና በሌሎችም መጻሕፍቶቹ ስለምናውቀው “የዮሐንስ ወንጌል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ” የሚለውን በሚገባ ተርጉሞ አቅርቦልናል።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዮሐንስን ወንጌል የተረጎመበትን መንገድ፣ ያመሳጠረበትን
የስብከት ዘዴ ከመጽሐፉ ተረድተናል፡፡ ለምሳሌ “ቀዳሚሁ ቃል፤ መጀመሪያ ቃል ነበረ”
የሚለውን የተረጎመበትን መንገድ እያደነቅን ሳንጨርስ፣ በምዕራፍ ሁለት ስለ ቃና
ዘገሊላው ተአምር፣ ስለቅዱሳን ሐዋርያት፣ ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
ያብራራል፡፡ ቀድሞም ስለእመቤታችን ጽፎ የማይጠግበው፣ ሰብኮ የማጨርሰውን ሊቁ፤
እዚህ ላይ አገኛትና እንዴ አድርጎ እንደተረጎመው ስናነብ ዛሬም አፈወርቅ እንድንል አድጎናል፡፡
ቀጣዮቹንም ምዕራፎች የተረጎመበትን መንገድ እየገለጽን ስለማንዘልቀው ለቅዱሱ የገለጠውን ምሥጢር ለእኛም እንዲገልጥልን ጸሎቱ ትርዳን፡፡
ከመጻሕፍት ዝግጅትና አርትዖት ክፍል
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
🙏🙏🙏
ይህ መጽሐፍ የብር መዶሻ፣ የወርቅ ሚስማር፣ የዳይንድ ብሎኬት እያቀበለ
ሀብት እንድንገነባ የሚረዳ ጽሐፍ ነው!!!
ሀብትህን ማስፋፋት እና ማሳደግ ትፈልጋለህ? ይህን መጽሐፍ ማንበብ አለብህ
ትምህርት ላይ ጎበዝ አይደለህም?... በትምህርት ወድቅሃል? በፍጹም እንዳታዝን!
በዚህ መጽሐፍ ምክንያት ሕይወትህን መቀየር ትችላለህ!
ወላጅ ነህ? ልጆችህ ከስር ጀምሮ ሀብት የሚገነቡበትን ጥበብ ለማስተር ይህ መጽሐፍ ይረዳሀል።
ተቀጣሪ ሰራተኛ ነህ? ተማሪ ነህ? ነጋዴ ነህ?... ይህ መጽሐፍ ያስፈልግሃል።
ከዘመናት ፀሎት ሱባኤ በኋላ የሰው ጠረን ናፍቆኝ ከተማ ወጥቼ
ከአሕዛብ ሸንጎ ከዋናው ምስያጥ የሰው ሳቅ ሞርሙርኝ እዚያ ተገኝቼ
(ናፍቆትም አይወጣ የሰው ትንፋሽ ሙቀት ፈፅሞ አይሠለችም።)
ግና ምን ያደርጋል አሰኘኝ ምናኔ ሰው ሰውን ሲበላ ባይኔ ተመልክቼ
ምስጥ-ገበያ
« ጦርነት ሲጀምር ፖለቲከኞች ጥይት ያቀብላሉ፡፡ባለፀጎች ምግብ ያቀርባሉ፡፡ድሆች ልጆቻቸውን ይለግሳሉ፡፡ጦርነቱ ሲያበቃ ፖለቲከኞች ቀሪ ጥይቱን ይሰበስባሉ፡፡ባለፀጎች ከጦርነቱ በተረፈው ሐብታቸው ማደግ ይጀምራሉ፡፡ድሆች ግን ልጆቻቸውን በመቃብር ስፍራ ይፈልጋሉ »
Читать полностью…አመሰግናለኹ !!!!
የጎንደር ታሪክን መጽሐፍ አስፈልጎኝ በፖሰትኩ ጊዜ የተባበራችኹኝ ወዳጆች እጅግ አመሰግናለኹ።
ከአንድም ኹለት አግኝቻለኹና ምስጋናየ ላቅ ያለ ነው።
እንባ ተናነቀኝ።ዝቅ ብዬ ድንጋይ ፈላለግኩ፤ አገኘሁና አነሳሁ።ልወረውርበት አስብኩ። ምን ያህል እንደሚጎዳው ግን አላውቅም።
ብስተውስ? በህይወቴ የሚገጥመኝን ነገር አሰብኩት በማድረግ እና ባለማድረግ ውስጥ ሆኜ ታገለኝ# ማድረግ የሌለብኝን ነገር እየሞከርኩ እንደሆነ ገባኝ። የሆነ ነገር ባደርግ ስለማልገድለው የምጎዳው እኔ እንጅ እሱ አይደለም። መታገስ ነበረብኝ፣ የሰው ልጅ የሚታገሰው የውስጡን ብሶት እና ስሜቱን አፍኖ የሚይዘው፣ ስለፈለገ ብቻ ሳይሆን በግድ ጭምር እንደሆነተረዳሁ።የውስጤን ንዴት በትዕግስት አፍኜ በእጄ ልወረውረው ያነሳሁትን ድንጋይ ቀስ ብዬ መሬት ላይ ጣልኩት።
#ከኔጌር
ከመጽሐፉ የውስጥ ገጽ የተወሰደ
#ወንጌል_ቅዱስ
ዘእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ
ኢየሱስ ክርስቶስ
ግብረ ሐዋሪያት
ወመልእክተ ሐዋርያት
በልሳነ ግእዝ ወአማርኛ
የአስመረ እትም
#ማሰብ_ዋጋ_ይኖረው_ይሆን?
የአንድ መጽሐፍ ዋጋ የወረቀቱ፣ የቀለሙና የማሳተሚያው ዋጋ እንጂ የሐሳቦች ዋጋ አይደለም። ለሐሳቦች ዋጋ ቢሰጣቸው ዋጋቸው እጅግ በጣም ውድ ስለሚሆን ሊገዙም ሆነ ወይም ሊሸጡ አይችሉም፤ ሊሰጡ ብቻ እንጂ።
ሓሳቦች ከአንዱ ሰው አእምሮ ወደ ሌላው ሰው አእምሮ እና ከአንዱ ሰው ልብ ወደ ሌላ ሰው ልብ ብርሃን የሚያበሩ ሻማዎች ናቸው። ይህን የብርሃን ጮራቸውን በሚወዷቸው እና ሂስ በሚሰጧቸው ሰዎች ላይ ይፈነጥቃሉ።
ስለሆነም የአንድን መጽሐፍ ዋጋ ስትመለከቱ ይህ ዋጋ የሐሳቦችን ዋጋ የሚጨምር አድርጋችሁ አታስቡ፤ መጽሐፉ የተፈለገውን ያህል ዋጋ ቢወጣ ሊገዛው የማይችለው አንድ አሳብ በውስጡ አቅፏልና።
ከዋጋው አንጻር አትራፊ ዋጋ ያለው ወደሚመስለው መጽሐፍ ስንመጣም ደራሲው ወይም ሌሎች ሰዎች ስለፍላጎታቸው ከሚያወጡት ወጭ በስተቀር ትርፉ ምንድን ነው? ይህ የሐሳቦች ዋጋ አይደለም።
የጥሩ መጽሐፍ ጥቅም የሚወሰነው በውስጡ በሚገኙት ሐሳቦች ብቻ አይደለም። በአንባቢው አእምሮና ልብ ውስጥ የሚያመነጫቸው ሌሎች ሐሳቦች ጭምር እንጂ። ታዲያ ለነዚህ የሚመነጩ ሐሳቦችና ስሜቶች ሊተመንላቸው የሚችል ዋጋ ይኖራል ብላችሁ ታስባላችሁ? እነርሱ ከዋጋ በላይ ናቸው!!!
የሕይወት ልምድ
#አዘጋጅ አቡነ ሽኖዳ ሣልሳዊ
#ትርጉም አያሌው ዘ
"አውቀሃል አይደል?"
"ምኑን?"
"የማታውን ተኩስ ነዋ!....እናቴ የጠጅ በርሜል ውስጥ ልትከተኝ ምንም አልቀራት።"
ሲደኒ ሼልደን እያንዳንዱ ሰው በሕይወት ጉዞ ውስጥ ሊገጥመው የሚችለውን ውጣ ውረድ እንዴት ማለፍና ከፍተኛ ስኬት ላይ ለመድረስ እንደሚቻል ያስተማረበት የበሰለ መጽሐፍ።
Читать полностью…ኣንዳንድ ጸሓፊዎች የኣሁኗን ኢትዮጵያን በፊውዳል ዘመን ክነበረችው ኣውሮፓ ጋር
በማወዳደር የዚህችን ኣገር ሥርዓተ ማኅበር hፊውዳል ሥርዓተ ማኅበር ጋር ተመሳሳይ
እንደሆነ ይጽፋሉù ግን ይህ ኣባባል ትክል ነው ወይ? የፊውዳል ሕብረተሰብ የመጀመሪያው ምልክት የመደብ ክፍፍል መኖር መሬትን መደባዊ ጥቅሞች በውርስ የሚተላለፉ መሆናቸው ነው ግን እነዚ ነገሮች በሓበሻ ውስጥ ኣይታዩም፡ በዚህች ኣገር ሹመት ስላላቸው ብቻ ማለትም በኣሁኑ ጊዜ ሥልጣን ላይ ስለሆኑ ብቻ እንደ መኳንንት የሚቆጠሩ ሰዎች ነጋዴዎች፣ ካህናት፣ መነኩሴዎች ወታደሮችና ገበሬዎች ይገኛሉ ግን እነኝ ሰዎች በሹመታቸውና በሚያከናውኑት ሥራ ይለያያሉ እንጂ ራላቸውን የቻሉና እርስ በእርስ የማይገናኙ መደቦች ኣይደሉም፡
ምርኮኞች በገፍ የሚያዙባቸው ጦርነቶች ያለማቋረጥ የሚካሄድና የገዢው መደብ ኣባላት የኣኗኗር ዘይቤ ብዙ ሠራተኞችን የሚፈልግ መሆኑ ባርነት በኣገሪቱ ውስጥ
እንዲኖር ኣድርጓል፡፡ ነገር ግን ይህ ባርነት እኛ ባርነት ብለን ከምንጠራው ነገር ጋር
የሚመሳሰለው በስም ብቻ ነው በኣሁኑ ጊዜ ባርነት በተቋም ደረጃ የለም ኣጤ ምኒልክ
በኣዋጅ ባርነትን ያጠፉ ሲሆን ባሪያ መሸጥና መግዛትም ስለተከለከለ ሲሽጡ የተገኙ
ሰዎች እጃቸው ይቆረጣል
ሓበሻን ከሌሎች ሕዝቦች ጋር በመጠኑ ለማወዳደር ብንፈልግ ይህ ሕዝብ
የሚገለጾው በሚከተለው መሠረት ነው፡፡ እሱም እንደ ፈረንሳይ ልዩ ስጦታ ያለውና
ኣስተዋይ፣ እንደ እንግሊዝ እርምጃ የመውሰድ በሥሩ የሚገኙ, ሕዝቦችን የማስተዳደርና የመሪነት ችሎታ ያለው፣ እንደ ስፔይናዊ ኩሩ፣ እንደ ሩስያዊ ሃይማኖቱን የሚወድ ጠባየ ለስላሳና ታጋሽ፣ እንደ ይሁዳዊ የመነገድ ችሎታ ያለውና በጣም ደፋር ብልጥና ተጠራጣሪ ነው።
ከመጽሐፉ የውስጥ ገፅ የተወሰዱ
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
🙏🙏🙏
አስተሳሰብህ ላይ ስር ነቀል ለውጥ የሚያመጣ፣ ባነቡበከው ቅጽበት ሕይወትህን
በደስታ የሚቀይር፡፡
ኦፕራ ዊንፍ
የአሁን ጊዜ ትሩፋትን (The Power of Now) ለመቋደስና በሁለመናችን ሽቅብ
ለመመንደግ በሚደረገው ጉዞ፣ በሀሳብ የሚባዝነውን አዕምሯችንና ይኸው
እዕምሯችን የፈጠረውን የውሸት ማንነት ከበስተኋላችን አራግፈን እልፍ ማ
ግድ ይለናል።
ይህንን ተአምረኛ መጽሐፍ ገና የመጀመሪያውን ገጽ ማንበብ በጀመርን ቅፅበት የእፎይታ አየር ወደ ምንተነፍስበትና በሁለመናችን ወደ ምንመነደግበት ወደ ላዋው ከፍታ ሽቅብ ይዞን ይጓዛል፡፡ ምንም እንኳ በሁለመናችን ለመመንግ ሽቅብ የምናደርገው ጉዞ ፈታኝ ቢሆንም፣ ጉዟችንን ቀሊል ያደርግልን ዘንድ፣
ኤhሀርት ቶል ንጥር ያለ ቋንቋና፣ አንባቢ ጠያቂ ጸሐፊው ደሞ መላሽ አካሔድን ተጠቅሟል፤ ብሥራት እውነቱም አሰምሮ ተርጉሞታል፡
መጀመሪያ ከታተመባት ጊዜ ጀምሮ ድፍን ዓለምን ያነጋገረ፣ በዘመናት ከተፃ ከስንት አንድ ከሆኑት ምርጥ መጽሐፍት የአሁን ሃያልነት (The power now) አንዱ ድንቅና ሁነኛ መጽሐፍ ሲሆን፣ አንባቢዎች ላይ ሁነኛ ለውጥ
መፍጠር የሚችል ብርቱ አቅም ያለው ተአምረኛ መጽሐፍ፡፡ የአንባቢዎችን ህይወት እስከ ወዲያኛው በበጎው መቀየር የሚችል ጥንቅቅ ያለ መጽሐፍ፡፡
ኤዞፕ ነባርና ቀደምት መጻሕፍት ጥንታዊ ጥበቦች መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ ጥበብ
አራዳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ጀርባ አቡነ ጴጥሮስ ሀውልት ፊት ለፊት መገኛችን ነው !!
ስልክ:- 09 11 72 36 56
09 20 74 57 40
@Mesay21
ጊዮርጊስ ጀባና ወደ አትክልት ተራ መድረክ ዋናው መንገድ ላይ !!!
ከዙላ እሰከ መቅደላ ከእንግሊዝ ጦር ጋር የተጓዘ አሜሪካዊ ጋዜጠኛ የዘገበው ታሪክ፡፡
በአፄ ቴዎድሮስ የመጨረሻዋ ሰ\ት በቦታው የነበረ የአይን ምስክር፡፡
አንድ ጊዜ ተወዳጅ ሀይለኛና ገናና የነበሩትን ንጉሥ የመጨረሻ ምዕራፍ ግልፅና ጥልቅ
በሆነ ሁኔታ ያቀርባል፡፡
ከመቅደላ በፊት የነበሩ ሁኔታዎችን ያስገነዝባል፡፡
መቅደላ እንደዚህ በዝርዝር ቀርቦ ያውቅም፡፡
ስለ እፄ ቴዎድሮስ መነበብ የሚገባው ፅሁፍ፡፡
ከመፅሐፉ የተወሰደ
ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን ።
🙏🙏🙏