azop78 | Unsorted

Telegram-канал azop78 - ኤዞፕ መጽሐፍት

8609

ኤዞፕ ነባርና ቀደምት መጻሕፍት መገኛ የከተማችን ፈርጥ ቤተ መጽሐፍት። በምኒልክ አደባባይ ፊት ለፊት ያለው የአራዳ ጊዮርጊስ ቤተ/ን ህንፃ አቢሲኒያ ባንክ ያለበት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ ነው !! ስልክ:- 09 11 72 36 56 @Mesay21 @Mesay21

Subscribe to a channel

ኤዞፕ መጽሐፍት

https://vm.tiktok.com/ZMjuyjgr1/

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ኤሎን ማስክ
ኦሪጅና የፒንጊዊን እትም
መጽሐፍ !!!

እጃችን ላይ

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ካህሊል ስለሜሪና ልጅነቱን ስላደመቀችልት ሀገሩ ሊባኖስ ዘምሮ አይጠግብም፡፡ በስደት በኖረባት አሜሪካ ያፈራውን አብዛኛውን ነገር ለሀገሩ ተናዞላታል፡፡ እንዲህ ይላል፡፡ ‹‹የእኔዋ ሊባኖስ በማለዳ ክንፎቻቸውን የሚያማቱ የእርግብ መንጋዎችን ትመስላለች፡፡››
ለእኔም ሀገሬ ሊባኖስን ትመስለኛለች፡፡ ራቅ ራቅ ብለው በበቀሉ ዋርካና ዝግባዎቿ፣ እንደሊባኖስ መሰሎቻቸው ሁሉ ‹ለሕይወት› ዝግ በሆኑ ሴቶቿ ሀገሬ ሊባኖስን ትመስላለች፡፡ ውድቅት ላይ በሹክሹክታ ብቻ በሚሰማ የምስጋና ዜማ አንቀላፍታ ንጋት በምህላ ድምጾች የምትነቃ… ሀገሬ!
ካህሊል ግን እንደ ገጸባህሪው አልሙስጠፋ ጻድቅ ብቻ አልነበረም፡፡ ግለ ታሪኩን ያጠኑ ሰዎች ግብዝ(Hypocrisy)፣ የለየለት ቀጣፊ፣ እንደነበርም መስክረዋል፡፡ ለሜሪ ሕስከል ደጋግሞ ከኢየሱስ ጋር እንደሚገናኝ፣ ራሱም ኢየሱስ እኔ ኢየሱስ ነኝ ብሏታልይባላል፡፡ ግን ቢያንስ ለዛሬ ይህን ስለመሳሰሉ ነገሮች ባናወራስ?
አንድ ስሙን ለማስታወስ የተቸገርኩት ሰው እንዲህ ብሏል፡፡ ‹‹ውብ ፊቶች የተፈጥሮ ድንገቴ ክስተቶች ሲሆኑ ውብ ነፍስ ግን የሕይወት ዘመን የጥበብ ስራ ነች!›› በዚህ ላይ እውነተኛ ጓደኝነት ሲታከልበትማ አስቡት… ካህሊል አዕላፋት የሚረዳቸው አጥተው ወደ ውስጥ እያነፈረቁ በተሸኙባት ዓለም ሜሪ ሐስከልን በማግኘቱ ለዕድለኝነቱ መግለጫ ቃላት አይገኝለትም።
ግን ግን ስንቶቻችን ነን ውብ ጓደኝነታችንን በምስር የለወጥን?
ታላቅ ሰው የመፍጠር እድላችንን እንደ አንዳች ንቀን መወነጃጀልን የመረጥን?
ምናልባት ሁላችንም!

መልካም ንባብ ይኹንልዎ !!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ነገ የመጽሐፍት ምረቃ ተጋብዛችኋል

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ትንሽ ኮፒዎችን አግኝተናል ረከስ ባለ ዋጋ እየሸጥን እንገኛለን

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ከገበያ ጠፍቶ የነበረው አንድሮሜዳ ቁጥር 1እና 2 በድጋሚ ታትመው ላንባቢያን ቀርበዋል።

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

የናምሩድ ዘርዐ ያዕቆብ ጥናታዊ መጽሐፍ

(ሒሳዊ ንባብ)
**********

ደራሲ፦ ናምሩድ ዘርዐ ያዕቆብ

የመጽሐፉ አርእስት፦ አፈወርቅ ገብረ ኢየሱስ ሕይወቱ፥ ቀደምት ሥራዎቹና በሥራዎቹ ላይ ያተኮረሩ ጥናታዊ ጽሑፎች

የመጽሐፉ ይዘት፦ ግለ ታሪክ፥ ታሪክ፥ ረጅም ልቦለድ እና አጭር ልቦለድ፥ የሥነ ጽሑፍ ጥናት

ዘመን፦2013 ዓ.ም

አሳታሚ፦ ወገግታ አሳታሚ እና ኤዞፕ መጽሐፍ መደብር

ዐማርኛ መነገር የጀመረው ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ7ኛውና በ9ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መካከል ሲሆን፣ ቋንቋው በጽሑፍ የሠፈረው ደግሞ በ14ኛው ክፍለ ዘመን በአፄ ዐምደ ጽዮን መሆኑ በእርግጠኝነት ይነገራል፡፡ ዐማርኛ የአፄ ልሳን በመሆን ማገልገል የጀመረው በ13ኛው ክፍለ ዘመን የአገው ሥርወ መንግሥት በአፄ ይኩኖ አምላክ ተነጥቆ የሰለሞን ሥርወ መንግሥት“በዳግማዊነት” ሲቋቋም እንደነበር ያስረዳሉ።

የአፈወርቅ ገብረ ኢየሱስ በኢትዮጵያ የአማርኛ እድገትና ሥነ ጽሑፍ ከፍተኛ አሰተዋጽኦ አድርጓል። በዚህ መጽሐፉ ውስጥ በውበታቸው ወይም በአጻጻፍ ሥልታቸው ወይም በያዟቸው ሐሳቦች (ቁም ነገሮች) ሳቢያ ህልው ሆነው የሚቆዩ የ1901 ዓ.ም ዘመን እንመለከትባቸዋለን።


እዚህ ላይ ልብ ልንል የሚገባን፣ የአፈወርቅ በመጽሐፍ ውስጥ የምናገኘው የቋንቋቸው ውብና በአጻጻፍ ሥልታቸው አንባቢዎችን ማራኪ ወይም ያቀፏቸው ቁም ነገሮች ወይም ሐሳቦች ሁለንተናዊና መሠረታዊ መሆናቸውን ለማሳየት በአማርኛ ቋንቋ ታሪካችንና ሥነ ጽሑፎቻችን ብሎም የመንግሥት የሥራ ቋንቋ አማርኛ መሆን እንዳለበት በማራኪ ትረካዎች አፈወርቅ ገብረ ኢየሱስ "ዳግማዊ አጤ ምኒልክ" በሚል ርዕስ በ1901 ዓ.ም ከታተመው መጽሐፍ ለማሳያነት የሚከተሉትን አንቀጾች እንጠቅሳለን።

«ዳሩ ግን ማን ነው በመልካም አማርኛ አጣፍጦ አሳምሮ ላንባቢው እንዲቀና፥ ለሰሚው እንዲገባ፥ ትንሽ ትልቁ፥ እሴት ወንዱ እንዲያነበው፤ እንዲያደንቀው፤ እንዲቀና አድርጐ የሚጥፈው ?

የተማሩት ሊቃውንቱም ቅዳሴ፣ ምስጢረ ሥላሴ፣ ድጓ፥ቅኔ፥ መዋሲት፥ ዝማሬ ይመስል በጥንት ባሮጌው ቋንቋ በግዕዝ ብቻ ነው መጣፍ የሚወዱ። ይሄን አሮጌ ቋንቋ ለቤተ ክርስቲያን ትተው የቀረውን የዓለሙን ነገር የዓለሙን ሥራ ግን ሁሉ በሚአውቀው ሁሉ በሚናገረ ቋንቋ በአማርኛ ቢፅፍ ደግ ነበረ።

ደግሞም ለንግድ፣ ለጥበብ ለመንግሥት የሚጠቅመውን አማርኛውን ማረም፥ ማሳመር፥ ማስተማር፥ ማልማት ይሻላል፤ ይገባልም። ዛሬ አለቃ ታየ የሚሉት ደቀመዝሙር ያጤ ምኒልክን ታሪከ ነገሥት ሊጥፋ ታዝዟል ይባላል። እስቲ ተሆነ እናያለን፡፡ አግዚአብሔር ይገዘው፡፡ ነገር ግን ሁሉ እንዲያነበውና እንዲገባው በግዕዝ ትቶ ባማርኛ ባደረገው ደግ ነበረ።

አማርኛው ግን ገጥ ያለ፣ ቅልጥፍ ያለ ላንደበት የተስማማ፣ ለጆሮ ያልገማ ላንባቢው የሚመች፣ ለሰሚው ማይሰለች እንዲሆን አድርጎ መጣፍ ነው።

ግዕዝ ብቻ ማሳመር አባቱን ንቆ ግዕዝ ብቻ ማክበር፣ አባቱን ገሎ ላማቹ ይነጭ፣ አማቱን ጋርዶ እናቱን ያስፈጭ የሚሉት ነገር ነው። አማርኛ ማልከስከስ አሮጌ ቋንቋ ማደስ የተገባም አይደል፡፡ አማረኛን ማረም፣ ማሳመር ማስተማር ነው፡፡ አማርኛን የሚአሳምር ጠፋ እንጂ ለመዶግዶግማ ፊደል ሳይቆጥር በመጋፊያ እየጣፈ፣ በገል3 እየጫረ ጽሕፈት የተማረ ሁሉስ ይዶገዱግ የለምን?

ያም ሆነ ያም አለቃ ታየን የመሰለ ብልህ የተማረ ሰው አማረኛውን አስተውሎ ይጥፍ ዘንድ ተስፋ አለን። ያጤ ምንልክን ታሪክ በግዕዝ የጣፈ እንደሆነ ግን ታልተፃፈ ቁጥር ነው። ሮማይስጡን ለቤተ ክርስቲያናቸውና በፈረንጅ አገርም የጥንቱን ቋንቋ ለሌላ ነገር ትተው ሁሉም አዲስ ቋንቋቸውን እያረሙ፣ ለልጆቻቸውም ያስተምራሉ። ኢትዮጵያ እንዲሁ ማድረግ ይገባታል (ከገጽ 83 - 84)።

* * * * *

«ኮንት አንቶኔሊ አንሥቶ ውጫሌ የተዋዋልንበት ወረቀት በፈረንሳዊ ቋንቋ የተጻፈው ይታይ አለ። እቴጌ ጣይቱ ግን እኛ የምናውቀው ባማረኛ የተጻፈውን ነው እንጂ የፈረንጅ ቋንቋ አናውቅም:: አንተ ግን የኛን ቋንቋ ታውቃለህና ባማረኛ የተጻፈውን እየው አሉት።

ከዚህ ወዲያ ኮንት አንቶኔሊ ነገሩ ሁሉ እንዳልሆነለት አይቶ በንዴት ያን የታተመውን ደብዳቤ ብጭቅጭቅ አድርጐ ቀዳዶ ጣለና እንግዴህ ፍቅራችን ፈረሰ ብሎ የጦርነቱን ነገር ገልጦ ተናግሮ ወጣ።

እቴጌ ጣይቱ ከት ከት ብለው ስቀው የዛሬ ሳምንትም አድርገው። በዚህ የሚደነግጥልህ የለም። ሂድ የፈከርህበትን አድርግ። እኛም የመጣውን እናነሣዋለን፡፡ እግሩን ለጠጠር ሰጥቶ አገሩን የማያድን ሰው ከዚህ ያለ አይምሰል። የገዛ ደሙን ገብሮ ለገዛ አገሩ መሞት ጌጥ ነው እንጂ ሞት አይባልም። አሁንም ሂድ አይምሽብህ፤ የፈከርህበትን በፈቀደህ ጊዜ አድርገው። እኛም ከዚህኸው እንቆይሃለን አሉት።

ያው ፈረንጅ በንዴት እጅና እግሩ እየተንቀጠቀጠ ፊት እንዲያውም እንዲአ ነበረና ጭው ብሎ ላዳን እንዶድ የጨረሱበት ሸማ መስሎ እጅ ሳይነሣ ተወርውሮ ወጣ (ገጽ 127)።

---------------------------------------

እስከዛሬ በእኔ ትሑት አስተያየት ታሪክና ሥነ ጽሑፍን በአንድ ላይ አዋሕዶ በጥናትና በምርምር የተዘጋጀ መጽሐፍ በናምሩድ ዘርዐ ያዕቆብ የተዘጋጀው "የአፈወርቅ ገብረ ኢየሱስ" ሥራ ይመስለኛል። መጽሐፉ ሁለቴ የታተመ ሲሆን፣ ወደፊት ሦስተኛው እትም የሚታተም ከሆነ መጥቍም ቢኖረው መልካም ነው። ምክንያቱም ይህ መጽሐፍ ጥናታዊ በመሆኑ ተመራማሪዎች፥ የሥነ ጽሑፍ ባለሙያዎች፣ጋዜጠኞች የሚፈልጉት ጥናት ለማግኘት በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። እርግጥ የመጽሐፉ ማውጫ ላይ በየክፍሉ የተዋቀረው ምዕራፍ እያንዳንዱ ዓብይ ጉዳይ የሚገልጽ ቢሆንም የቦታ ስምች፣ የሰው ስም፣ በፊደል ቅደም ተከተል በቀላሉ ለማግኘት ያስችላል። በተረፈ ናምሩድ ዘርዐ ያዕቆብ በለመደው እጅ ሌላ ጥናታዊ መጽሐፍ እንደምታበረክት ተስፋ አለ።

በመጨረሻም መጽሐፍ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ልቦለድ (1900 ዓ.ም) እንጎቻ ወግ (አጭር ልቦለድ) ከ1900 ዓ.ም ጀምሮ የታተመው የፈጠራ ሥራዎች፣ የኢትዮጵያ ታሪክን በተለይ የዐፄ ምኒልክ ከልጅነት አስከ ንጉሠ ነገሥትነት ዘመነ መንግሥት ደረስ ያለውን ታሪክ ሸጋ በሆነ አማርኛ ያስቃኛል።

አንባቢያን ሆይ መጽሐፉን አንብቡት ። ታዲያ መጣፉኑ በምታነቡበት ወቅት የእርጋታ ጊዜ፥ የመንፈስ ጸጥታን፥ በአመዛዛኝ ኅሊና፥ በአስተዋይ ልቦና ይሁን። መልካም ንባብ !


ፀጋየ ገብረመድን ሮበሌ እንደፃፈው

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

" THE POWER OF NOW" እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1997 በኤክሃርት ቶሌ ድንቅ
መጽሐፍ ነው።

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ዛሬ በጉዞየ ካጋጠመኝ የነጋድራስ ገብረ ህይዎት ባይከዳኝ መንግስትና የህዝብ አስተዳደር መጽሐፍ በእንግሊዝኛ ትርጉም !!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

የዘፈን ግጥም ደራሲና ጋዜጠኛ ፤ የሴቶች መብት ተከራካሪ የሸዋሉል መንግስቱ በሃረር በአፋን ኦሮሞ የሬድዩ ስርጭት ፕሮግራም ከእውቁ ጋዜጠኛ የሙዚቃ ግጥም ፀሃፊና ደራሲ የአፍራን ቀሎ ባንድ መስራችና ዋና አሰልጣኝ አቡበከር ሙሳ ጋር በመሆን በርካታ የሬዲዩ ፕሮግራሞች በጋራ ይሰሩ ነበር ፣ ከሰሯቸው የሬዲዩ ፕሮግራም መካከል ቅናተኛዋ ሚስት "Jaarti hinaaftu" በሚል የሰሩት የሬድዬ ድራማ በወቅቱ ተወዳጅ ነበር ።

ደራሲና ጋዜጠኛ የሸዋሉል መንግስቱ ከዚህ ቀደም ብሎ በሃረር ከተማ 1962 ዓ/ም ጽፋው በ1968 ዓ/ም በፊንፊኔ የታተመው "እስከ መቼ ወንደላጤ " የሚለው ተወዳጅ ድርሰቷ ይህ ነበር :

በነገራችን ላይ የሸዋሉል መንግስቱ ሀረርጌ ካበቀላቸው የዘፈን ግጥም ደራሲያን ውስጥ እንቁ የጥበብ ባለሙያ ነበረች። የዘፈን ግጥሞቿን ለተለያዩ ድምፃውያን ያበረከተች ሲሆን ከነዚህ ውስጥም ለድምፃዊ ሙሉቀን መለሰ፣ ለድምፃዊ መሀሙድ አህመድ፣ ለክቡር ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ፣ ለክቡር ዶ/ር አሊ ቢራ እና ድምፃዊ አስናቀች ወርቁ በዋናነት ይገኙበታል። ለምሳሌ :-
☞ለድምፃዊ ጥላሁን ገሠሠ
♪ አካም ነጉማ

☞ለድምፃዊ ሙሉቀን መለሰ
♪ጀመረኝ
♪ትዝታ
♪ህልም ሆነሽ ቅሪ
♪ጉብል ቀዘባ
♪የምንጃር ሸጋ
♪በእኔ ሞት
♪ውብ አበባ
♪መውደድሽን ብታውቂው
♪ባይሽ ደስ ይለኛል
♪ከሴት እሷ ብቻ

☞ለድምፃዊ መሀሙድ አህመድ
♪አሸወይና
♪ትዝታ
♪ኦሆሆ ገዳማ
♪ስደተኛ ነኝ
♪እንዴት ነሽ ገዳዎ
♪መላ መላ
♪አታውሩልኝ ሌላ
♪መቼ ነው
♪ሳምራዬ

☞ለድምፃዊ አሊ ቢራ
♪ አዋሽ
♪ወይ ሆቢ ሆቢ

☞ለድምፃዊት አስናቀች ወርቁ
♪ እህ ልበል
♪ሰላ በልልኝ

☞ለድምፃዊ አያሌው መስፍን
♪ ሄደች ጋራ ዞራ
ክብር ለሚገባው ክብር እንስጥ
Negash Qemant


አንድ ኮፒ መጽሐፏ እጃችን ላይ አለን

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

አለመኖርን ተመኝቶ ፣
አለመኖርን ፈልጎ ያውቃል፡፡

“አለመኖር ምንድነው?” ተብሎ ቢጠየቅ ግን መልስ የለውም፡፡

“መኖር ራሱ ምንድነው? ለምንድነው የምኖረው?” ጥያቄዎቹ ናቸው፡፡

“ሰው ካለአንዳች ዓላማ ወደ ምድር አልመጣም! ወደ ምድር አይመጣም!” ሲባል ሰምቷል፡፡

ባይረዳውም፡፡

“ሰው ካለአንዳች ዓላማ ወደ ምድር አልመጣም!” ማለት ምን ማለት ይሆን?

ዓላማ ራሱ ምንድነው?

የማንን ዓላማ ነው የሚያስፈጽመው?

“ዓላማህን አስሰህ አሳካው!” ብሎ የላከውስ ማነው?

ሰው በምድር ሲኖር የግድ ዓላማ መሰነቅ ይጠበቅበታል?

ምናልባት የአንድ ሰው ዓላማ ያለ ዓላማ ኖሮ ማለፍ ሊሆን አይችልም?...

"ዛሬ ቅዳሜ አይደለም"

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

የኰለኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ገጽታ

****

ርዕሰ ፦ ኩርፊያ የሸፈነው ፈገግታ
ደራሲ ፦ ሥዩም ወልዴ
የመጽሐፉ ይዘት፦ ግለ ታሪክ
ዘመን ፦ 2002 ዓ.ም
( ሒሳዊ ንባብ)

በቸኛው የሥነ ጥበብ ኀያሲ ሥዩም ወልዴ፤ «ኩርፊያ የሸፈነው ፈገግታ»የተባለው መጽሐፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕትመት የበቃው በ2002 ዓ.ም ሲሆን፣ እሱም ከፍተኛ ግምትና አድናቆት አትርፏል። ይህ መጽሐፍም በ2007 ዓ. ም ለሁለተኛ ጊዜ ታትሟል ። ሆኖም ግን ደራሲው የመጽሐፉን የሕተመት ብርሃን ሳያይ ሞት ቀደመው።

ይህ መጽሐፍ የሥዩም ወልዴ የአምሳ ዓመታት ጉዞው የገጠመውና ያየውን ለዛ ባለው የትረካ ስልት ተከትሎ የዕድሜ ዘመኑን ትውስታ የመዘገበበት ነው።

«ኩርፊያ የሸፈነው ፈገግታ» በሦስት መዕራፎች የተከፈለ ነው። አሥራ አምስት ፎቶዎች እና የደራሲው የሥዕል የፈጠራ ወጤቶች የተካተቱበት ሲሆን፣ በ345 ገጾች የቀረበ ነው።

መዕራፍ አንድ«ደማቁ ጠዋት»የሚል ሥያሜ ይዟል። ይህ ክፍል የልጅነት ጊዜያቱን፣ ከቄስ ትምህርት ጀምሮ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም የጋዜጠኝነት ሕይወቱ ላይ ያተኩራል።

ሁለተኛው ምዕራፍ፣«መንገዳማው ረፋድ» የሚል የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፣ በሞስኮ ስቴት ዩኒቨርስቲ የነፃ ትምህርት ዕድል አግኝቶ በመጓዝ በትምህርቱ ቆይታው ያጋጠመውንና የታዘበውን ሁኔታ ሲሆን፣ በሥነ ጥበብ ታሪክ የጥበብ ንድፈ ሐሳብና የኀያሲነት ትምህርቶች ወስዶ የኤም, ኤ, ዲግሪ ተመርቆ ወደ አገሩ ሲመለስ የሚተረክበት ምዕራፍ ነው።

ሦስተኛው መዕራፍ፣ «ያልጠረረ ቀትር» የተሰኘ ነው፤ ይህ ክፍል ደግሞ በሕይወቱ የገጠመውን ግላዊና አገራዊ ድርጊቶች የሚያስነብብበት ነው።

የመጽሐፉ ተራኪ በመግቢያው እንዲህ ይላል፦«ይህ ነበር ጉዞዬ ብዬ በዚህች ጽሑፍ ውስጥ ያቀረብኩት ሁሉንም አይደለም፤በጣም ጥቂቱ ነው፤ ያስታወስኩትን ያህል፤ አንባቢዬን እየፈራሁና እየተባው ነው የፃፍኩት፤ ምክንያቱም በአገሬ «እኔ» ብሎ መፃፍ ባለ መለመዱና የግል ሕይወት ገጠመኝ ታሪክ አጻጻፍ ሊዳብር ባለመቻሉ እንግዳነት እየተሰማኝ ነው፤ ትውስቴን ያሰፈርኩት፤ስለዚህም አንባቢዬን ከዚህ ይልቅ የሌላ ነገር ብጽፈለት የበለጠ ይረካ ነበር እያልኩ የፈራሁት» (ገፅ 7 ላይ)።

የደራሲው ሥጋት እውነትነት ያለሁ ነው፤ ምክንያቱም በአንደኛ መደብ (እኔ) ትረካ የተአማኒነት ጥያቄ የሚያጭሩ ጉዳዮች መኖራቸው ሐቅ ነው። በዚህ መጽሐፍ ውስጥም ለመቀበል የሚከብዱ ታሪኮች ያጋጥማሉ፤ ከነዚህም መካከል የፊደል ካስትሮ ወደ ኢትዮጵያ የክብር እንግዳ ሆኖ ምጣታቸውን ተከትሎ በአደባባይ ላይ የጓድ መንግሥቱና የኩባው መሪ የነበሩት የፊደል ካስትሮ ፎቷቸው በሥነ ጥበብ ባለ ሙያ የተሠረው ምስል መሠራት ተከትሎ የሚፈጠረውን የወዝግብ ሁኔታ ተራኪው ስዩም ያቀረበውን ቀጥለን እንመልከት።

«ከተሰጡኝ ተግባሮች አንዱና አጣዳፊው በዘጠኝ ቀን ተሠርተው እንዲያልቁ የታዘዙት የክብር እንግዳ የኩባው ፊደል ካስትሮ እና የደርጉ ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃ/ማርያም ሰምንት የአደባባይ ትላልቅ ምስሎች ሥራ ነው። አንድ ነባር ሠዓሊና አንድ በዚያው ዓመት የተመረቀ ወጣት ሠዓሊ ምስሎቹን እንዲሠሩ ተደረገ፤ ነባሩ የሊቀመንበሩን፤ ወጣቱ የእንግዳውን ከሠሩ በኋላ ጳግሜ 5 ቀን በየተወሰነላቸው ሥፍራዎች ተሰቀሉ።

መስከረም 1 ቀን 1971 ዓ, ም, ከፍተኛ ግርግር ተፈጠረ፤ «ሠዓሊዎቹ እንግዳውን አሳምረው (ካስትሮን) አስተናጋጁን ሊቀመንበር (መንግሥቱን) እጅግ አስቀያሚ አድረገው ነው የሠሩት» ተብሎ ሰለተተቸ የበዓሉ ዝግጅት ኮሚቴ አባላት በሙሉ በከፍተኛ መደናገጥ ትርምስ ፈጠሩ» ካለ በኋላ ተራኪው ሥዩም የተጠየቀውንና ለማመን የሚከብደውን አስገራሚ መልስ እንዲህ ይመልሳል።

«እንደዚያ አበላሽቶ የሥራውን ሠዓሊ በአስቸኳይ ፈልጌ እንዳቀርብ ታዘዝኩኝ፤ የእምነቱንና አመለካከቱን፤ ፀረ- አብዮተኛ መሆን አለመሆኑ፤ በሊቀመንበሩ ላይ ጥላቻ ያለው ወይም የሌለው መሆኑን ተጠየቅሁ። በበኩሌ አፍራሽ መልስ ከመስጠት በስተቀር የተጠየቀውን ጥያቄ ሁሉ የሚደግፍ መልስ አልሰጠሁም። ነፍሴን ስላስጨነቋት የሰጠውት መልስ አንድ ነገር ነው፤ ለሊቀመንበሩ ተፈጥሮ የሰጠቻቸውን መልክ ሠዓሊው በምንም መንገድ መለወጥ እንዳልነበረበትና ለሥራ እንዲረዳው ሞዴል ሆኖ በተሰጠው ፎቶግራፍ ላይ አሳድጎ ከመሥራት ውጪ ምንም ዓይነት የአሠራር ሰሕተት እነዳልነበረ ያበጠ ይፈንዳ ከሚል አቋም በድፈረት የጭንቄን ሳረጋግጥ «በያሉበት የተሰቀሉት ሁሉ ወርደው በተቻለ መጠን ይስተካከሉ፣ ይመሩ፣ ይቆንጁ እባክህ» ወደሚለው ሐሳብ አዘነበሉ። አራቱም ምስሎች ከየተሰቀሉበት ወርደው ሌሎች ሠዓሊዎች ተፈልገው ተፈጥሮ ያስገኘችው እውነት በጥበብ ተለውጦና ተውቦ እንዲቀርብ ተደረገ።» ይለናል።

በእኔ ትሑት አስተያየት ሥዩም ወልዴ «ለሊቀመንበሩ ተፈጥሮ የሰጠቻቸውን መልክ ሠዓሊው በምንም መንገድ መለወጥ » አይችልም ብሎ ለበዓሉ አዘጋጅ ኮሚቴ ይህንን መልስ በዘመነ ደርግ ይመልሳል ብዬ ለማመን ይቸግረኛል። ለማንኛውም መጽሐፉ ብዙ ለማመን የሚከብዱ ታሪኮች አሉት። አንብቡት።

ፀጋየ ገብረ መድህን ሮበሌ !!!


/channel/azop78

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

አስራ አንደኛው በተሰኛው መጽሐፏ የምናውቃት ይቱስራ ምትኩ ድንቅ መጽሐፍ ይዛ እየመጣች ነው።


በቅርብ ቀን

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ቀደምት እትም የታሪክ መጽሐፍት !!
እነኾ ከኤዞፕ መጽሐፍት !!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ግልጽ ጨረታ በሉት !!!

ይኽንን ፍቅር እስከ መቃብር አይታችኹታል።
እስካኹን ባለኝ የመጽሐፍት ሽያጭ ዘመኔ የመጀመሪያ የኾነውን ምንም ያልተነካካ ያልተበረዘ ያልተከለሰ እትም የ1958 ዓም እትም ገጥሞኝ አያውቅም።

እነኾ ይኽንን የመጀመሪያ እትም መጽሐፍ በደምበኛ ትዕዛዝ መቀበያ ደብተራችን ላይ ያለንን ትዕዛዝ ስመለከተው ከ25 ይበልጣል። በመኾኑም ለማን ሰጥቸ ለማን የለኝም ልበል። ስለዚኽ ይኽንን ጽሑፍ ቀድሞ አይቶ ለደወለልልን፣ ላዘዘን ፣ ደምበኛችን ብቻ የምንሰጠው ይኾናል ።

አስታውሱ ይኽ ቅጅ የ1958 ዓም ነው።

ትዕዛዝ _ እስኪ እጅወ ላይ ያለውን የፍቅር እስከ መቃብር እትም ይመልከቱ ?

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ዘወትር፣ ፍቅር ዕውር ነው ብላችሁ ስታወሩ እሰማለሁ፡፡ አዎን፣ አፍቃሪ በተፈቃሪው ላይ አንዳችም እንከን አያይም ማለታችሁ ነው፡፡ እኔ ግን እላችኋለሁ … ይሄ ዓይነት አለማየት የማየት ከፍታ ጫፍ ነው፡፡

በምንም ነገር ላይ እንከን አታዩ ዘንድ ምነው ሁሌ በታወራችሁ፡፡

አይይ … የፍቅር ዓይኖችማ … ንጹህ፣ የጠሩና ሰርስረው የሚያዩ ብሌኖች ናቸው፡፡ ስለዚህም ምንም እንከን አያዩም፡፡

አዎን … ፍቅር ዓይናችሁን ሲያበራው … ያኔ … ለፍቅራችሁ ያልተገባ ምንም ነገር አታዩም፡፡ በእርግጥም፣ ፍቅር አልባ የተንሸዋረረ ዓይን ብቻ ነው በሌሎች ላይ ስህተት ፍለጋ የሚተጋ፡፡ የትኛውም የሚያያቸው እንከኖችም … የሌላም ሳይሆን የራሱ ናቸው፡፡

ፍቅር አንድ ያደርጋል፡፡ ጥላቻ ይበትናል፡፡ ይህ የመሠዊያው ጫፍ የምትሉት ግዙፍ የአለት ክምር እንኳ፣ በፍቅር እጅ ባይያያዝ ተበታትኖ በበረረ ! ይሄ በስባሽ ገላችሁ፣ መፍረስን የመከተው፣ እያንዳንዷን የአካል ሕዋስ በጥልቅ ፍቅር ብትወዱ ነው !!! ፍቅር፣ በሕይወት ማራኪ ዜማ የሚደንስ ሰላም ነው፡፡  ጥላቻ … ጨካኝ የሞት ጥላ ያጠላበት የተቅበዘበዘ ጦርነት ነው፡፡ የቱን ትመርጣላችሁ - ፍቅርና ዘላለማዊ ሰላምን ወይንስ ጥላቻን እና ማለቂያ የለሽ ጦርነትን ? መላዋ ምድር እናንተ ውስጥ ሕያው ነች፡፡ ሰማየ ሰማያቱ እና የሰማየ ሰማያቱ አለቆች እናንተ ውስጥ ሕያው ናቸው፡፡ ስለዚህም ራሳችሁን የምትወዱ ከሆነ፣ ምድርን እና መላ ፍጡራኖቿን ውደዱ፡፡ እናም ራሳችሁን የምትወዱ ከሆነ ሰማያቱን እና አገልጋዮቹን በመላ ውደዱ፡፡

ከ“መጽሐፈ ሚርዳድ”

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ቆየት ያሉ በእንግሊዝኛ የተፃፉ የታሪክ መጽሐፍት እጃችን ላይ ይገኛሉ። !!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

የካህሊል አማልዕክትን
ማንበብ ላላነበባችኹት !!!
እነሆ እንደ መግቢያ!!


የካህሊል ሴቶች
‹‹Beloved prophet››
(ያዕቆብ ብርሃኑ)
*


… የካህሊል ጅብራን ነፍስ ሁሉንም በመፈለግና ሁሉንም በማጣት ቅዝምዝም መሀል ተሰንቅራ የጠፋች የቅጽበት ብልጭታ ትመስላለች፡፡ በማይረካ ጥማትና በማያባራ ሽሽት መካከል ተወጥራ ሲነካኳት ስቃይን የምትዘምር አንዲት ፍሬ የክራር ክር፡፡ ሕይወቱን የምታተርፍለትን አንዲት የጉበት ቀዶ ጥገና ማድረግን ችላ ብሎ ሞትን በጨበጣ የታገለ…
ካህሊል ጅብራን የአባቱን ሕልፈት ተከትሎ በ1895 እ.ኤአ ከእህቱና እናቱ ጋር በስደት አሜሪካ ገባ፡፡ በዚያ ወቅት ራሱን እንኳን በቅጡ መግለፅ የማይችል አይናፋር ልጅ ነበረ፡፡ ድንገት ግን የ21 ዓመት ልጅ እያለ በአስር ዓመታት የምትበልጠውን ሜሪ ሐስከልን ተዋወቀ፡፡ ሜሪ ካህሊልን ዘግቶ ከተቀመጠባት ጠባብ የጭለማ ክፍሉ ጎትታ አውጥታ ከዓለም ጋራ አስተዋወቀችው፡፡ ፓሪስ ድረስ ልካ ስነ-ስዕል አስተማረችው፡፡ እርሱም በምላሹ እንደጣዖት አመለካት፡፡ የነፍስ ጓደኛው አደረጋት፡፡ የሴቶች ሁሉ መስፈሪያ ትልቋ ሔዋን እንደሆነች በነፍሱ ዘመረላት፡፡ እስከመጨረሻው ብቸኛ አርታኢውም እሷው ነበረች፡፡
የሜሪና የካህሊል ጓደኝንት ብዙ ጊዜ ተፈትኖ እየታደሰ የቀጠለ ከምናውቃቸው ጉድኝቶች የተለየና ሊገልፁት የሚያስቸግር ይመስላል፡፡ ሜሪ ሐስከል ሲበዛ ደግ ሴት ነበረች፡፡ ከካህሊል በፊት ቢሆን ለራሷ የሚላስ ሳይኖራት እየቆጠበች የምታስተምራቸው የግሪክ ታዳጊዎች ነበሯት፡፡ ይኸው መልካምነቷ ከአፈር ላይ አንስታ በዓለም ላይ ከዊሊያም ሸክስፒርና ላኦ ትዙ ቀጥሎ በሦስተኝነት በሰፊው የተነበበውን ደራሲ እንድትፈጥር አስችሏታል፡፡
ለ27 ዓመታት ይህን ሁሉ ስታደርግ ከካህሊል የምትጠብቀው ብቸኛ ነገር ቢኖር ለሚያገኛቸው ሰዎች ሁሉ የምወዳት ፍቅረኛዬ ናት ብሎ እንዲያስተዋውቃት ብቻ… በግል ማስታዎሻ ደብተርዋ ላይ አስፍራው እንደተገኘችው በዓለም ለእርሷ ካህሊል ጅብራንን ከመውደድ የሚበልጥ ነገር አልነበረም፡፡
ያለ ሜሪ ሐስከል ካህሊል ከትንኝ ያነሰ፣ ከላባ የቀለለ ለቁምነገር የማይጠራ ሰው በሆነ ነበር፡፡ ትልቁ ካህሊል ሜሪን አለመተዋወቅ ቀርቶ ከእርሷ ጋር የነበረው ጓደኝነት በሆነ ምክኒያት ተቋርጦ ቢሆን ኖሮ በተወዳጁ ፋንታ ዕድገቱ የቀነጨረውን ነብይ የማየት ዕድላችን የሚያጠራጥር አይደለም፡፡ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚነሆነኝ ይመስለኛል። ሜሪ ሐስከል ግን ባደረገችው ነገር ለአፍታም ሳትኩራራ አንዲት ሴት በእህትነት፣ በእናትነት፣ በፍቅረኝነት፣ በጓደኝነት፣ በሰውነት ልትሰጠው የምትችለውን ፍቅር ሁሉ ቅንጣት ታህል ሳትሸራርፍ እየለገሰች በሐምራዊ የንቃት ክንፎች እየበረረ እልፍ መሻገሮችን እንዲያስስ አስችላዋለች፡፡ በ1914 እ.ኤ.አ ክረምት በጻፈላት ደብዳቤ እንዲህ ይላል፡፡
“The day will come when I shall be able to say, ‘I became an artist through Mary Haskell… You have the great gift of understanding, beloved Mary. You are a life-giver, Mary. You are like the Great Spirit, who befriends man not only to share his life, but to add to it. My knowing you is the greatest thing in my days and nights, a miracle quite outside the natural order of things.››
ሜሪ በኪናዊ ምጥቀቱ ከፍ ባለበትም ይሁን በሞራል በተሸመደመደባቸው ጊዜያት ሁሉ ያለማመንታት ከጎኑ ነበረች፡፡ ይህንን ደብዳቤዋን ተመልከቱ፡፡
‹‹I don’t even want you to be a poet or painter: I want you to be whatever you are led or impelled to become… Your work is not only books and pictures. They are but bits of it. Your work is You, not less than you, not parts of you… These days when you “cannot work” are accomplishing it, are of it, like the days when you “can work.” There is no division. It is all one. Your living is all of it; anything less is part of it. — Your silence will be read with your writings some day, your darkness will be part of the Light.››
ካህሊል ለትዳር የጠየቃት ብቸኛዋ ሴት ሜሪ ሐስከል ነበረች፡፡ ባይሳክም ቅሉ… ምናልባት ያለመሳካቱ ምክንያት ካህሊል ትዳርን አጥብቆ የማይፈልግ ሰው በመሆኑ ሊሆን ይችላል፡፡
‹‹አብሮነታችሁ የመሰናዘሪያ ቦታ አይንፈጋችሁ፡፡ በአንድነት ቁሙ። ነገርግን መተዛዘል እስቲሆን ድረስ አትደራረቡ፡፡ የቤተ መቅደስ አዕማድ ሲቆሙ ራቅ ራቅ ብለው ነው፡፡›› ይላልና፡፡
እስኪ ይሄኛውንም ካህሊል ለሜሪ የጻፈላትን ደብዳቤ ተመልከቱ
‹‹I wish I could tell you, beloved Mary, what your letters mean to me. They create a soul in my soul. I read them as messages from life. Somehow they always come when I need them most, and they always bring that element which makes us desire more days and more nights and more life. Whenever my heart is bare and quivering, I feel the terrible need of someone to tell me that there is a tomorrow for all bare and quivering hearts and you always do it, Mary.››
የማግኘት አድሉ ያለችሁ ‹‹Beloved prophet›› በሚል ርዕስ በ416 ገጾች ተቀንብቦ የቀረበውን የሁለቱ ጓደኛሞች ደብዳቤዎች የተጠናቀሩበት መጽሐፍ እንድታነቡ እጋብዛችኋለሁ፡፡
ካህሊል ግን አሁንም ከፍታው ቀጥሏል፡፡ ሜሪም አስከ ዘለዓለም አብራው ከፍ የምትል ይመስላል፡፡ መጻሕፍቱ ዛሬም በሁሉም የዓለም ማዕዘናት በስፋት ይነበባሉ፤ ይተረጎማሉ፡፡ እንደ ጥናቶች ጥቁምታ ከሆነ ካህሊል አሁን በሚነበብበት ፍጥነት ከቀጠለ ከሃያ ወይም ሠላሳ ዓመታት በኋላ በሰፊው በመነበብ ሸክስፒርንም ሆነ ላኦትዙን የሚያስከነዳበት እድል አለው፡፡
ተፅዕኗቸው ከሜሪ ጋር ለንጽጽር የሚቀርብ ባይሆንም እንኳን ሌሎች በርካታ ሴቶች በካህሊል ሕይወት ውስጥ ነበሩ፡፡ እርሱም ስለ ሴቶች እንዲህ ብሏል ‹‹የዓይኔን መስኮት እና የመንፈሴን በሮች የሚከፍቱት ሴቶች ናቸው፡፡ እናቴ፣ እህቴና ጓደኛዬ የምላቸው ሴቶች ድጋፍ ባያደርጉልኝ ኖሮ ዛሬ እኔም የዓለምን ጸጥታ እና እርጋታ በማንኮራፋት ድምጽ ከሚረብሹት ሰዎች መካከል ተጋድሜ ሳንጎላንጅ እገኝ ነበር፡፡››

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ውድ የኤዞፕ መጽሐፍት ደንበኞቻችን
በተደጋጋሚ ስትጠይቁን የነበረውን #የባስሊቆስ #እንባ በ100 ብር በሽያጭ ላይ ነን ጎራ ብለው ይሸምቱ

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

🌼🌻🌼🌻*የኔ*ጌታ*<በቸርነትህ*አመታትን* 🌻🌼ታቀዳጃለህ>*መዝ*64:11

*ይህ* 🌼አዲሱ*አመት🌻*የሰላም*የደስታ*🌼የፍቅር*🌻ያንድነት*የስኬት*ዘመን*🌻🌼 ያድርግልዎት 🌻*ሰላም*🌼 ለሀገራችን*ይሁንልን*መልካም*🌼🌻 አዉዳመት*🌼🌻 መጪው አዲስ ዓመት የሀገራችን እና የሕዝቦቿ ሰቆቃ የሚያበቃበት እውነተኛ ሰላም የሚሰፍንበት ተድላና ፍሰሃ የተትረፈረፈበት ዓመት ይሁንልን።
መልካም አዲስ አመት. *🌼🌻


ኤዞፕ መጽሐፍት

/channel/azop78

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

እንደ ወሸባ ከአንድ ቤትና ከhንድ ቤተሰብ የማይወጣ ትርክትመሆኑን ያጤኩት መጽሐፉን ጨርሼ ካጠፍኩት በኋላ አባትቶ እስደንቆኛል:

አንዳንዴ ብቻ እንዲህ ይገጥማል:: እንደ ውሃ አሳስቆ የሚወስድ ትርክት ማረፊያውን ለጥ ያለ ሜዳ ላይ ሲያደርግ ያኔ ጥያቄ ያስከትላል::

"የዚህ ቤተሰብ አባል አልነበርኩም? ታዲያ የተዘጋ ደጃፋቸውን አልፌ እንዴት ወደ ቤታቸው ዘለቅሁ? እንደ መርፌ የወጋኝ ስጋነት
ከየት መጣ? _ ሲስቁ አላጀብኩም? ሲያለቅሱ አልተንሰቀሰኩም? ይሄ ሁሉ ከት መጣ?"

'ወድቆ የተገኘ ሐገር' ካዳንዶቹ ትርክቶች አንዱ ነው:: ወድቀን እንደተገኘን ሁሉ ጉዲፈቻ ለመቀበል ቀድሞ እጆቹን ይዘረጋል::
በሂደት 'ስጋነትን' በውስጣችን ያኖራል:: ከዚያ ወዲያማ ለቤተሰባዊ ጥቃት 'ቤተሰባዊ መብከንከን ገጥሞን ባላለፍን' ስንል ራሳችንን እናገኘዋለን::
እስቲ አንብቡና ፍረዱኝ:

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

« አንድዋ ልጅ እምቢ አላትና፣ ተቀሚሷ ሥር መአት ጨርቅ ጐዝጉዛ ባሏን አርግዣለኹ እያለች ስትዋሽለት መክረም»

«ማታ ሲተኙ አያያትም?» ስትል ታንጉት ጠየቀች፣ ነገሩ አስገረሟት።

« ያመኛል እያለች ለብቻዋ እየተኛች ነዋ! ዘጠኝ ወር ተሞላት በኋላ ምን ታርገው። አውራ ዶሮዋን አርዳ ደሙን ታልጋው ላይ አፈሰሰችና «አስወረደኝ» አለች ይባላል። ታዲያ ምን ተብሎ ተዘፈነላት መሰለሽ?
ጌጤ ነው ስሟ፣ እንግዲህ፦

የጌጤ አውራ ዶሮ ዘንድሮ ከበረ
ዘጠኝ ወር ተረግዞ ዐልጋ ላይ ሠፈረ

« እኔን ይንገሩኝ የምለው ገብርዬ መካን ቢሆንስ? ብለው የጀመሩትን ነው። ምን አለ እርሶማ የልጅ ልጅ አይተዋል» ስትል በመከፋት አንገቷን አቀረቀረች።

« ታልሽ ምን ቸገረኝ! አየሽ፣አንድ ልጅ እናቱ እንጂ አባቱ በእርግጠኛነት የሚታወቅ አይደለም። አባቱ ማን መሆኑን ምንአልባት በእርግጠኛነት የምታውቅለት እናቱ ብቻ ነች። አሁን ለምሳሌ እኔ ልጆቹን ለአባታቸው ልጆችህ ናቸው አልኩት እንጂ ተሌላ አርግዤአቸው ቢሆን በምን ያውቅ ነበር? እና አሁንም የሆነ እንደሆነ ፞ · ·» መጨረሱ የከበዳቸው ይመስል ተውት።

ወይዘሮ ደብሬ እንደሰጉት ሐሳቡን ታንጉትን በጣም አላስደነገጣትም። «እና ለገብርዬ ልጅ ተሌላ ወንድ ላርግዘለት ማለት ነው? » ስትል ከመገረም ጋር ጠየቀች።

«አንቺን አርጊው አላልኩሽም፤ ንገሪኝ ስላልሽ ነው፤ ባላቸው መካን ተሆነ የሚያደረጉ ሴቶች ግን አሉ።»

—ከብርሃኑ ዘርይሁን ፣«የታንጉት ምስጢር» 1979 ዓ.ም

ኤዞፕ መጽሐፍት የምንጊዜም ምርጥ ሙጽሐፍት አቅራቢ !!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ዛሬ ሞት ተፈርዶብኛል፧ በቃ በሰይፍ ተቀልቼ እንድሞት፣ በሕይወት ከሚኖሩት ወገን እንድስረዝ ተበይኗል፡፡ እሺ መሞቱን ልሙት ለምን ስይፉን አይስሉትም? ይኼም ተንኮል እኮ ነው፧ቶሎ ሲጥ እንዳልል የተሸረበ ሴራ፤ በህይወት እና በሞት መካከል ያለን በግ እያየ የሚስቅ በግ አራጅ አለ? እኔን የገጠሙኝ ግን እየገዘገዙ የሚገድሉ ሰው አራጆች ናቸው፡፡

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

.
....💚...💛..❤.....

" ጥ ሩ : መ ጽ ሐ ፍ ቶ ች : ማ ን በ ብ : ካ ለ ፉ ት : መቶ : ዘ መ ና ት : ም ር ጥ : አ ዕ ም ሮ ዎ ች : ጋ ር: እ ን ደ መ ወ ያ የ ት : ነ ው ::"

ኢማኑኤል ካንት

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

#ወደ_ኢነርጂ_ባህር_ለመጥለቅ_የሚያስችሉህ_4_መንገዶች

#አንድ
• ብቻህን ስትሆን ለጥቂት ደቂቃዎች ያህል ለመዝፈን ሞክር

#ሁለት
• ከውሃ ጋር በፍቅር ውደቅ። በወንዝ አቅራቢያ የእግር ጉዞን አድርግ፣ ረዘም ላለ ጊዜ ሰውነትህን ውሃ ውስጥ ንከረው፤ የራስህን ነጸብራቅ በውሃ ውስጥ ተመልከት፤ ውሃ ውስጥም የሚፈጠሩ ሽክርክሮታዊ ቅርጾችን አስተውላቸው። ይህን ማድረግህ በዩኒቨርስ ውስጥ ያለው የኢነርጂ ፍሰት ምን እንደሚመስል ማስታወሻ ይሆንሃል።

#ሶስት
• በጽሞና ውስጥ ሁን። ከጫጫታ ራቅ። ምንም አይነት ሙዚቃም ሆነ ዜናዎችን ለአንድ ሳምንት ያህል ላለመስማት ሞክር። የራስህን አእምሮ ብቻ አዳምጥ። ይህን ልምምድ ለአንድ ሳምንት ያህል አድርገው። ቀስ በቀስም እያሳደግከው ሂድ፡፡

#አራት
• የምታየውን እና ባንተ ላይ የተከሰተውን ለውጥ ሁሉ በማስታወሻ ደብተርህ ላይ አስፍር።

አሁን ላይ ያለህበት የሕይወት ወቅት ላንተ የጨለመ ክረምት እንደሆነ ሊሰማህ ይችላል፤ ሆኖም ግን የጸደይ ወቅት መምጫው ተቃርቧልና ብርታትህን ጨምር። በራስህ እምነት ይኑርህ። አትወድቅምም!

ጥሩ የስነልቦና መጽሐፍ አንብቢት

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

አንድ ሺ ከአንድ ሌሊት እነሆ በመደብራችን ተገኝታለች ብቅ ብለው ለወዳጅ ዘመድ ስጦታ ይሸምቱ።

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

ቀደምት ትግርኛ አማርኛ መዝገበ ቃላት
1948

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

እውነትም “ጠቢበ ጠቢባን”!
===+++===
ዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው በግሩም ኹኔታ ተርጉሞ ያሳተመውን “ጠቢበ ጠቢባን” መጽሐፍ ፈርሞ ልኮልኝ አነበብኩት። ከገመትኩትም ከጠበኩትም በላይ ሆኖ አገኘሁት። ወንድማችን ዲያቆን ኤፍሬም የሠራው ከትርጉምም በላይ ነው። (ስለ ሥራው ያለኝን ምልከታ ከታች በመጠኑ አነሳለሁ፤) በጣም የደነቀኝ ነገር ቅድሚያ ስለ መጽሐፉ ሕትመት ጥቂት ላንሣ።

የመጽሐፉ ጥራዙ የተመጠነ፤ መጠኑ መካከለኛ፣ ባለ ሙሉ ቀለም፣ ወረቀቱ ብራና አከል እና መሰል ነው። ሲገልጡት ለዓይን ተስማሚ መሆኑ አንባቢን በግድ ይጋብዛል። የሽፋን ገጹ መስሕብነት አለው፣ የውስጥ ገጾቹ ሐረጋት ጥበብ ልዩ ነው። በዘመናዊ ሕትመት ያልተለመደውን ስመ አምላክን እንዲሁም አርዕስቶችን በቀይ ቀለም በወጥነት ማስቀመጥ ምን ያህል አድካሚ ሊሆን እንደሚችል በበተለይ በሥራው ያለፈ ሰው የሚረዳው ነው። እንኳን ይዘቱ (ውስጡ) አምሮ ተሠርቶ ይሄ በራሱ ትልቅ ምሥጋና የሚያሻው ነውና ወንድማችን ኤፍሬም የኔሰው  ና ምሥጋናህን ውሰድ። ማተሚያ ቤቱም ሊመሠገን ይገባዋል።

ከወራት በፊት “ጠቢበ ጠቢባንን እየተረጎምኩ ነው” ብሎ ዲ/ኤፍሬም ሲጽፍልኝ ደስታዬ ብዙ ነበር፤ አሁን አልቆ ሳየው ከመደሰቴ የተነሣ ይህን የመሰለ፣ ጥንቅቅ ያለ ሥራ ነፍስ ሔር ፕ/ር ጌታቸው በሕይወት በኖሩና በመረቁት ብዬ ከልቤ ተመኘሁ። የትርጉም ሥራ ከባድ ጥንቃቄን የሚፈልግ እና በኮሌጅ ደረጃ ራሱን የቻለ ትምህርትም የሚሰጥበት የሙያ ዘርፍ ነው። የመገኛ ቋንቋውን እና ተቀባይ ቋንቋውን ማውቅ ብቻ በቂ አይደለም። እኔ እንደተመለከትኩት ከሆነ ዲያቆን ኤፍሬም ይህን “ጠቢበ ጠቢባን” መጽሐፍ ተረጎመው ብቻ ሳይሆን አመሠጠረው፣ ተነተነው፣ አብራራው እና የመጽሐፉን ክብር በተገቢ መልኩ ገለጠው ቢባል ማጋነን ሊሆን አይችልም። እንዲህ ያልኩበትን በሦስት ነጥብ ላሥረዳ፦

አንደኛ የተስተካከለ ትርጉም ነው፦
የመልክእ ምሥጋናን መተርጎም እንደሌሎች ጽሑፎች አይደለም። ይልቁንም ደግሞ መልክኡ በተዘጋጀበት ጥበብ በሥነ ግጥም ሲቀርብ ለጥንቱ የተጠጋ ይሆናል። በዚህ ረገድ ዲያቆን ኤፍሬም የግዕዙን መሠረት ሳይለቅ ምሥጢሩንም ዘይቤውንም ጠብቆ መስመር በመስመር ተርጉሞታል። ይህ ከፍተኛ የሆነ የሥነ ጽሑፍ ችሎታን የሚጠይቅ እና በግዕዝ ቋንቋ መዋኘትን ያጠይቃል። በዚያውም ላይ እናቱን (የግዕዙን ዘር) በተጓዳኝ ገጽ፣ አቻ ትርጉሙን (የአማርኛን) በትይዩ ማቅረቡ አንባቢውን ለዳኝነትም ለምርጫም ይጋብዛል፤ ማለፊያ ሥራ!

ኹለተኛ ጥንቅቅ ያለ አርትዖት፦
ታትሞ ለሕዝብ የሚቀርብ ነገር ከፍተኛ የአርትዖት ሥራ ያሻዋል። አንዳንድ መጽሕፍት (እንዲሁም ጋዜጦች) በሳል መልዕክት በውስጣቸው ይዘው በርካታ የፊደል ግድፈት፣ የሥርዓተ ነጥብ አለመስተካከል፣ እንዲሁም የጽሑፍ ፎርማቱ የተዘበራረቀ ስለሚሆን ጥራታቸውን ዝቅ ያደርገዋል። ዲ/ኤፍሬም የቀደመ የአርትዖት ሥራ ልምዱን በበለጠ በዚህ መጽሐፉ ላይ እንዳዋለው በግልጽ ይታያል። የፊደላቱ ለቀማ፣ የቃላቱ አመራረጥ፣ የቁጥሮች አጠቃቀሙ፣ ሥርዓተ ነጥብ አጠባበቁ ወዘተ ... የተዋጣለት ስለሆነ ይበል ወንድማችን ያሰኛል።

ሦስተኛ ማብራሪያና ትንታኔ የያዘ ሥራ፦
አብዛኞቻችን ስለ “ጠቢበ ጠቢባን” ምንነት ያለን ግንዛቤ አናሳ ነው፤ የመጽሐፉን ይዘት የሚያውቁት ደግሞ ጥቂቶች እንደሆኑ ይገመታል። “ጠቢበ ጠቢባን”ን የመሰለ ለፈጣሪ የቀረበ ልዩ ምሥጋና አለማወቅ ምን ያህል እንደሚያስቆጭ አሁን ስናነበው ይገባናል። መጽሐፉ መቼ እና በማን እንደተደረሰ የቀደሙ ሥራዎችን አመሳክሮ፣ የራሱንም ንባብ ጨምሮበት ወንድማችን ኤፍሬም ሰፊ ማብራሪያ አቅርቦልናል። በግዕዙ ድርሰት ላይ አማራጭ ቃላትን ሲጠቀም በምክንያት መሆኑን ለማወቅ በየገጹ ያሉትን የግርጌ ማስታዎሻዎች መመልከት ነው።  “እንዲህ የሚል ዘርም ይገኛል” ብሎ ይገልጻል።  ይህ ዓይነቱ ሥራ በፊሎሎጂ (የጥንታውያን ጽሑፎች ጥናት) ባለሙያዎች የተመሳከረ ሕትመት (critical edition) የሚሉት ዓይነት ነው። ይህን ሥራ ይበልጥ የተደከመበት እንደሆነ የሚያሳየው ዐሥር የሚያህሉ ተመሳሳይ የብራና ቅጂዎችን መዘርዘሩ፣ የታተሙ የጸሎት መጻሕፍትንም ማካተቱ ነው። ይህም ለሌሎች ተርጓሚዎች በጎ ምሳሌ ነው፤ (በእርግጥ ይህም የተሻለ እንዲሆን በቀጣይ ቢጨምራቸው የምላቸውን ሁለት ያህል ነጥቦች ከታች እገልጻለሁ)።

ይህን የመሠለ ውብ ሥራ ስላቀረበልን ወንድማችን ዲያቆን ኤፍሬም ከልብ መመሥገን ይገባዋል።  መጽሐፉም በሚገባ ሊተዋወቅና ሥራው ሊነገርለት ይገባል፤ ከምር በሆነ አስተያየት ብዙ ሊባልለት የሚገባው ነውና። ይህን ካልኩ ዘንድ to be fair እንዲል ፈረንጅ በሚቀጥለው ቢያሟላቸው የምላቸውን ሁለት አስተያየቶች ላቅርብ።
  -የመጀመሪያው የተረጎመልን የየትኛውን ቅጂ ጠቢበ ጠቢባን እንደሆነ ግልጽ ቢያደርገው? ያደገበትን የፍኖተ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስን ቅጂ ነውን ከሆነስ የመቼ ዘመን? ወይስ የጎንደሩን? የጣናውን? ወይስ ከውጭ ሀገር ከሚገኙት የቱን? እርግጥ ነው ይሄ ሃሣብ ይበልጥ ትርጉም የሚሰጠው በጥናትና ምርምር ለሚሠማሩ ቢሆንም ለጠቅላላ አንባቢም ቢሆን ማለፊያ ነው።  
  -ኹለተኛው ነጥብ ያሉን በርካታ የጠቢበ ጠቢባን ቅጂዎች መሆናቸው ይታወቃል፤ ሁሉንም መዘርዘር ባይጠበቅበትም ግን በርካቶች እንዳሉ ቢገልጽና እሱ ግን የተረጎመልን ይሄን እሱ ያገኘውን መሆኑን ቢጠቁመን ጥሩ እንደነበር ይሰማኛል።

ወንድማችን ዲያቆን ኤፍሬም ሆይ፦
ጠቢበ ጠቢባን የሆነ ልዑል እግዚአብሔር ዕውቀቱን፣ ጥበቡን ገልጾልህ፣ ትጋቱንም አድሎህ ወደ ፊትም ሌሎች መጻሕፍትን በነካ እጅህ ጽፈህ፣ ተርጉመህ እንድታደርሰን አደራ እንልሀለን
/channel/azop78

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

የመጀመሪያው እትም
ፍቅር እስከ መቃብር ጨረታ በሚያስደንቅ ኹኔታ ተጠናቃላች !!!

ሀሳባችን ብዡ ይጠይቁን የነበሩትን ወዳጆቻችንን ማስደሰት ነበር ከልብ ከሚፈልጋት ሰው እጅ ገብታለች!!!!



ይኽ መጽሐፍ እጃችኹ ላይ ካለ እስኪ በድጋሜ እናሳስባችኹ የትኛው ቅጅ ነው ያለዎት !!!!


ካለውት እሰየው ብለናል !!!

ከሌለዎትም ድጋሜ ጨረታ እናወጣለን !!!
ይጠብቁን !!!

Читать полностью…

ኤዞፕ መጽሐፍት

በገበያ ላይ



የሃያኛው ክፍለ ዘመን  መግቢያን የኢትዮጵያ ታሪክ ያወሳል።

የልጅ ኢያሱ፣ የንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ እና የተፈሪ መኮንን ታሪክ
ሀገራችን አሁን ያለችበት በቅጡ ለመረዳት የሃያ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ጀምረን ማጥናት እንደሚጠበቅብን ምሁራን ያስረዳሉ ለዚህም ይረዳን ዘንድ በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ትእዛዝ ተሰንዶ የነበረው መጽሐፍ ተዘጋጅቶ ቀርቦልናል።

Читать полностью…
Subscribe to a channel