bahir_dar_university | Unsorted

Telegram-канал bahir_dar_university - Bahir Dar University,Ethiopia

21305

It is a channel about Bahir Dar University all Campuses! www.bdu.edu.et

Subscribe to a channel

Bahir Dar University,Ethiopia

ቀን፡ 11/06/2018 ዓ.ም
ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ (በድጋሜ የወጣ)
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመካከለኛ አመራር ምርጫና አሰያየምን ለመደንገግ ባወጣዉ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 05/2012 መሰረት  ለInstitute of Land Adminstration  postgraduate, Research and Community Engagement V/Dean ቦታ  በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመሾም በወጣው ማስታወቂያ በቂ አመልካች አልተገኘም። በመሆኑም በድጋሜ ማውጣት አስፈልጓል፡፡
ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡   ለ Institute of Land Administration postgraduate, Research and Community Engagement V/Dean
የማወዳደሪያ መስፈርት፡-
1ኛ. የትምህርት ማእረግ/ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማትወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተ ቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤
3ኛ. በሚያመለክቱበት አካዳሚክ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ አካዳሚክ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ቸማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
4ኛ. የአካዳሚክ ክፍሉ ማህበረሰብ፣ የአካዳሚክ ኮሚሽኑ አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
አመልካቾች፡-
ይህ ማስታወቂያ በዩኒቨርሲቲው ድህረ- ገጽ፣ ፌስቡክና ማስታወቂያ ሰሌዳዎች ከተገለጸበት የካቲት 11 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡
በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 583 20 9653 ወይም +251 583 20 6059 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡
ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

It is with deep sadness that we remember Mr. Aman Fissehatsion, a valued member of Board of Directors of our University. During his time with us, he demonstrated exceptional dedication, professionalism, and integrity. His positive spirit and commitment was contagious to everyone who had the privilege of working with them. Bahir Dar University extends its heartfelt condolences to his family and loved ones. He will be greatly missed and fondly remembered. https://youtu.be/MCY59_EYg5w

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ማስታወቂያ
ለመጀመሪያ ዲግሪ እና PGDT ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በ2ኛው ወሰነ ት/ት ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው የመግቢያ መስፈርት መሰረት በርቀት (Distance) መርሃ ግብር በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በPGDT ተማሪዎችን ተቀብሎ ማሰልጠን ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉና መማር የምትፈልጉ አመልካቾች ከየካቲት 4 ቀን 2018 ዓ/ም እስከ መጋቢት 04 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እያስታወቅን የምታመለክቱባቸውን የትምህርት መስኮች ዝርዝር ከታች መመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
የማመልከቻ መስፈርት፤ በትምህርት ሚኒስቴር የመግቢያ መስፈርት መሰረት
• የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ወስደው በትምህርት ሚኒስቴር የወጣውን የየዘመኑን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ መቁረጫ ነጥብ ያሟሉ፤
• ከዲፕሎማ ወይም ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ወደ ከፍተኛ ትምህርት ለመግባት የተቀመጠውን የመግቢያ መስፈርት ያሟሉ፤
• በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአቅም ማሻሻያ (Remedial program) ተከታትለው የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ፤
ለበለጠ መረጃ የዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ድረ-ገጽ https://bdu.edu.et/registrar/ ይመልከቱ፡፡
ለምዝገባ የሚያስፈልጉ ሰነዶች/ማስረጃዎች፣
• የትምህርት ማስረጃ ዋናውና ፎቶ ኮፒ፤
• የብቃት ማረጋጫ (COC) (ለሚያስፈልጋቸው ብቻ)፣
• ኦፊሻል ትራንስክርፒት (ለሚያስፈልጋቸው ብቻ)፣
• ለማመልከቻ (Application fee) 300 ብር የተከፈለበት ኦሪጅናልና አንድ የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ደረሰኝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
የማመልከቻ ቦታ፤
• በርቀት ትምህርት ማዕከላት ማለትም በባህር ዳር፤ ጎንደር፤ ደሴ፤ ደብረ ብርሃን፤ አዲስ አበባ፤ ደብረ ማርቆስ፤ ፍኖተ ሰላም እና ሞጣ - እነሴ ማዕከላት ምዝገባ ይደረጋል፡፡
ተጨማሪ ማሳሰቢያዎች፡
1. የቀድሞው ትምህርት ፖሊሲ 12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃ ተቀባይነት የለውም፤
2. በዲፕሎማ የሚመዘገቡ አመልካቾች በምዝገባ ወቅት ኦፊሻል ትራንስክርፕት በፖስታ ሳጥን ቁጥር 79 ማስላክ አለባቸው፤
3. በሀገር አቀፍ ደረጃ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ፈተና ላልተዘጋጀላቸው የትምህርት ዘርፎች ዩኒቨርስቲው የሚያዘጋጀውን የመግቢያ ፈተና መውሰድ አለባቸው፡፡ የፈተናው ቀን እና የቅበላ ውጤት ይፋ የሚደረግበትን ቀን በውስጥ ማስታወቂያ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ድረ-ገጽ https://bdu.edu.et ወይም የፌስቡክ ገጽ ወደ ፊት ይገለፃል፤
4. በቂ የተማሪ ቁጥር የማያመለክትባቸው የትምህርት መስኮች አይከፈቱም፡፡
5. ከዚህ በፊት ለመማር ተመዝግበው ባቋረጡት የት/ት መስክ በተመሳሳይ የቅበላ ዓይነት መመዝገብ አይቻልም

የመመዝገቢያ ክፍያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሂሳብ ቁጥር 1000224663378 መክፈልና ደረሰኝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

AI in Action at Bahir Dar University!

Bahir Dar Institute of Technology at Bahir Dar University is excited to host an inspiring and practical workshop by Dr. Mikael Gorsky, AI Researcher at the Holon Institute of Technology (HIT), Israel.

💡 Workshop Title: Agentic Coding – AI in Software Engineering
📅 Date: Monday, 16 February 2026
⏰ Time: 10:30 AM
📍 Venue: Jan Moscov Library, Bahir Dar Institute of Technology

This 90-minute practical session is specially designed for:
👩‍💻 Computer Engineers
👨‍💻 Computer Scientists
🧑‍💼 Software Developers
🚀 Technology Entrepreneurs
🎓 Interested students and faculty

Discover how AI-powered agents and large language models are transforming the way software is developed.

Join us and be part of the conversation shaping the future of technology.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ቀን፡ 03/06/2018 ዓ.ም
ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ (በድጋሜ የወጣ)
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመካከለኛ አመራር ምርጫና አሰያየምን ለመደንገግ ባወጣዉ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 05/2012 መሰረት  ለInstitute of Land Adminstration Academic V/Dean ቦታ  በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመሾም በወጣው ማስታወቂያ በቂ አመልካች አልተገኘም። በመሆኑም በድጋሜ ማውጣት አስፈልጓል፡፡
ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡   ለ Institute of Land Adminstration Academic V/dean
የማወዳደሪያ መስፈርት፡-
1ኛ. የትምህርት ማእረግ/ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማትወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተ ቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤
3ኛ. በሚያመለክቱበት አካዳሚክ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ አካዳሚክ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ቸማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
4ኛ. የአካዳሚክ ክፍሉ ማህበረሰብ፣ የአካዳሚክ ኮሚሽኑ አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
አመልካቾች፡-
ይህ ማስታወቂያ በዩኒቨርሲቲው ድህረ- ገጽ፣ ፌስቡክና ማስታወቂያ ሰሌዳዎች ከተገለጸበት የካቲት 04 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡
በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 583 20 9653 ወይም +251 583 20 6059 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡
ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Bahir Dar University Welcomes AcceDe, Spain for Futsal Training and Sports Development Collaboration

Bahir Dar University warmly welcomed an eight-member delegation from AcceDe, Spain, as part of its ongoing efforts to strengthen international partnerships that contribute to student development and institutional growth. The visit, hosted by the University’s management, the External Relations and Partnership Directorate at Information and Strategic Communication Vice President Office, and Sport Academy, focused on futsal training, capacity building, and material support, reinforcing the University’s commitment to sports as a vital component of campus life.

Throughout the week-long stay, AcceDe’s professional team worked closely with Bahir Dar University coaches, sports staff, and students, delivering intensive, hands-on futsal training sessions. The sessions emphasized modern coaching techniques, tactical game understanding, teamwork, and leadership, skills that extend beyond the playing field and into students’ academic and personal lives.

The collaboration also included material support aimed at enhancing the University’s sports infrastructure and training resources. This contribution reflects a shared vision of empowering young people through sport and strengthening institutional capacity in physical education and athletics.

The visit created an energetic and engaging atmosphere across the Sport Academy, where students and coaches actively participated in training sessions and exchanges. It also offered an opportunity for professional interaction, experience sharing, and mutual learning between the visiting experts and the University’s sports community.

As the visit concluded, Bahir Dar University reaffirmed its commitment to expanding partnerships that support holistic education. The collaboration with AcceDe, Spain stands as a strong example of how international cooperation in sports can foster talent development, promote healthy lifestyles, and build lasting institutional ties.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

እዩሀስ ወርቁ ለባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛውን ወርቅ አሰገኘ!

በጅማ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት በታላቅ ድምቀት እየተካሄደ ባለው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስፖርት ፌስቲቫል የዩኒቨርሲቲያችን ተማሪ የሆነው እዩሀስ ወርቁ የውድድሩ ኮከብ መሆኑን ዳግም አስመስክሯል።

ባለፈው የ100 ሜትር የፍጻሜ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ በማስገኘት የፈጣንነቱን አክሊል የደፋው እዩሀስ፣ ዛሬ በ200 ሜትር የሩጫ ውድድር ተቀናቃኞቹን በአስደናቂ ብቃት በመቅደም ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ለዩኒቨርሲቲው አስመዝግቧል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

@NGAT

@bahir_dar_university
@bahir_dar_university

#SHARE #SHARE

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ቀን፡ 28/05/2018 ዓ.ም
ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመካከለኛ አመራር ምርጫና አሰያየምን ለመደንገግ ባወጣዉ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 05/2012 መሰረት ለ College of Agriculture and Environmental Science የድህረምረቃ ምርምርና ማህበረሰብ ተሳትፎ ም/ዲን ቦታ በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ መሾም ይፈልጋል፡፡
ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡ የድህረምረቃ ምርምርና ማህበረሰብ ተሳትፎ ም/ዲን 
የማወዳደሪያ መስፈርት፡-
1ኛ. የትምህርት ማዕረግ/ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማትወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤
3ኛ. በሚያመለክቱበት አካዳሚክ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ አካዳሚክ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ቸማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
4ኛ. የአካዳሚክ ክፍሉ ማህበረሰብ፣ የአካዳሚክ ኮሚሽኑ አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
አመልካቾች፡-
ይህ ማስታወቂያ በዩኒቨርሲቲው ድህረ- ገጽ፣ ፌስቡክና ማስታወቂያ ሰሌዳዎች ከተገለጸበት ጥር 28 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡
በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 583 20 9653 ወይም +251 583 20 6059 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡
ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ማስታወቂያ
በባሕር ዳር የኒቨርሲቲ ልዩ አማራጭ መምህራን ትምህርት ስልጠና ለመውሰድ የተመረጣችሁ አመልካቾች ሙሉ፤

በልዩ አማራጭ መምህራን ትምህርት ስልጠና ለመሳተፍ ካመለከታችሁት ምሩቃን መካከል በአማርኛ፤ እንግሊዝኛ እና ፊዚክስ ትምህርቶች ዘርፍ የተመረጣችሁ ስልጣኞች የምዝገባ ጊዜ የካቲት 2 እና 3፣ 2018 ዓ፣ም በፔዳ ካምፓስ መምህራን ትምህርት ትምህርት ቤት መሆኑን ቀደም ሲል የገለፅን ሲሆን ለምዝገባ ስትመጡ፡-

1ኛ. የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና የማይመለስ ኮፒ
2ኛ. ሁለት ጉርድ ፎቶ ግራፍ
3ኛ. ኦፊሻል ቀድሞ ከተማራችሁበት ዩኒቨርሲቲ በቅርበት ያላችሁ ተማሪዎች ወደ ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ እንዲላክላችሁ አዛችሁ እንድትመጡ ሩቅ ቦታ ላላችሁ ደግሞ ከመጣችሁ በኋላ በ3 ወር ጊዜ ውስጥ እንድታስልኩ
4ኛ. አንሶላና የትራስ ልብስ ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን፡፡

መምህራን ትምህርት ትምህርት ቤት
ባሕር ዳር የኒቨርሲቲ
To all applicants of Bahir Dar University Special Alternative Teacher Education Training:
In our previous notice regarding Bahir Dar University Special Alternative Teacher Education Training applicants, we have notified the selected applicants, and the place and dates of registration. Please also note that, when you come for registration, you should bring/arrange:
1. Your original and non-returnable copy of your educational credentials
2. Two recent photographs
3. Sending of your Official Educational Credentials to Bahir Dar University from the university you attended your previous study within 3 months of your arrival.
4. Last but not least a bed sheet and pillowcase.
School of Teacher Education
Bahir Dar University

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሐዘን መግለጫ

​የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ቦርድ፣ አመራሮች፣ መምህራን፣ ሠራተኞችና ተማሪዎች በተወዳጁና እንቁው የኪነ-ጥበብ ባለሙያ እንዲሁም የሥነ-መዝናኛ ፕሮግራም አቅራቢ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት መለየት የተሰማንን ጥልቅና መራር ሐዘን እንገልጻለን።

​አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ በሙያው ለዘመናት ኢትዮጵያውያንን ሲያዝናና፣ ሲያስተምርና በክፉም በደጉም ጊዜ ከሕዝብ ጎን በመቆም ላበረከተው ዘመን ተሻጋሪ አስተዋጽኦ ትልቅ ክብር አለን። የእርሱ ማለፍ ለሀገራችን የጥበብ ዘርፍ ትልቅ የሐዘን ጠባሳን ጥሎ አልፏል።

​በመሆኑም ለታዋቂው አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶችና ለመላው የጥበብ አፍቃሪ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ፈጣሪ መጽናናትን እንዲሰጥልን እንመኛለን።

​የአርቲስቱ ነፍስ በሰላም ትረፍ!
​ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችና ለክፍሉ ሰራተኞች የአቅም ማሻሻያ ሥልጠና ሰጠ

[ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ - ጥር 2018 ዓ.ም] የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተቋሙን ገጽታና የኮሙኒኬሽን ስራዎችን በላቀ ደረጃ ለማከናወን ይረዳ ዘንድ፣ አዲስ ለተመደቡና ለነባር የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ለሦስት ቀናት ሲሰጥ የነበረውን የአቅም ግንባታ ሥልጠና ዛሬ በስኬት አጠናቋል። በሥልጠናው ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር መንገሻ፣ ባለሙያዎች የተቋሙን ትክክለኛ መልክና አንደበት በመሆን ሙያዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

ሥልጠናው በተለያዩ የዩኒቨርሲቲው ግቢዎች ማለትም በጥበበ ግዮን ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ በባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት እና በሰላም ግቢ የኢት/ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የተመደቡ 35 የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችና የክፍሉ ሠራተኞችን ያሳተፈ ነበር። ባለሙያዎቹ ባለፉት ሦስት ቀናት በተቋም ትውውቅ፣ በመሠረታዊ የኮሙኒኬሽን ክህሎት፣ በዘገባ አጻጻፍ፣ በቃለመጠይቅ ስልቶችና ለሕዝብ ግንኙነት ግብ በሚውሉ የዜና ዝግጅት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ተደርጓል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር መንገሻ በሥልጠናው መርሃ-ግብር ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መመሪያ፤ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ በሙያው ብቁ፣ ታታሪ፣ በተክለ ቁመና፣ በክህሎትና ዘርፉ በሚፈልገው እውቀት እንዲሁም በአለባበስም ሆነ በተቋማዊ የባለቤትነት ስሜት ለሌሎች አርአያ መሆን እንደሚገባው ገልጸዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ ዩኒቨርሲቲው ለዘርፉ ስኬታማነት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል። በተመሳሳይ መልኩ የጥራት ሥራ አስፈጻሚው አቶ ወርቁ አበበ፣ ጥራትና ሕዝብ ግንኙነት ተደጋጋፊ መሆናቸውን ጠቁመው፣ ተቋሙ በትንታኔና በጥራት የታጀበ ዘገባ የሚሰሩ ባለሙያዎች እንዲኖሩት በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
ሥልጠናው በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ተግባቦት መምህራን በሆኑት በዶ/ር ነገሰ በላይና በአቶ አዝዛቸው ወንዴ፣ እንዲሁም በውስጥ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ በአቶ ግርማው አሸብር የተመራ ሲሆን፣ በንድፈ-ሀሳብና በተግባራዊ ልምምድ የታጀበ እንደነበር ታውቋል።

የሥልጠናው ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት፣ ሥልጠናው በተለይ ለአዲስ ሠራተኞች ክፍሉን ከማስተዋወቅና ለቀጣይ ተልዕኮ ራስን ከመዘጋጀት አኳያ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። በቀጣይም እንደየሥራ መደባቸው የካሜራ፣ የግራፊክስና የዲዛይን ተጨማሪ የተግባር ሥልጠናዎች እንዲመቻቹላቸው የጠየቁ ሲሆን፤ የውስጥ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ አቶ ግርማው አሸብር በበኩላቸው፣ ዩኒቨርሲቲው ክፍተቶችን መሠረት ያደረጉ ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስራዎችን አቅዶ እንደሚሰራ አረጋገጠዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

“የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ልምድ ለIFMIS ትግበራ ስኬት መሠረት ነው”
ዶ/ር መንገሻ አየነ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የፋይናንስ አስተዳደሩን ይበልጥ ግልጽ፣ ቀልጣፋ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት ለማድረግ የሚያስችለውን የተቀናጀ የፋይናንስ አስተዳደር መረጃ ሥርዓት (IFMIS) በይፋ መተግበር ጀመረ። በዩኒቨርሲቲው የፕሬዝዳንት መሰብሰቢያ አዳራሽ በተከናወነው የሲስተም ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው በቴክኖሎጂ ልማትና አጠቃቀም ረገድ የካበተ ልምድ ያለው ተቋም ነው። ዶ/ር መንገሻ አየነ ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ቀደም ለራሱም ሆነ ለሌሎች ተቋማት ዘመናዊ ሲስተሞችን በማልማት ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህ የዳበረ ልምድ አዲሱ የIFMIS ሥርዓት በስኬት እንዲተገበር ትልቅ አቅም እንደሚሆን አረጋግጠዋል።

በፋይናንስ ሚኒስቴር አማካኝነት የቀረበውና በዩኒቨርሲቲው ስራ የጀመረው ይህ ዘመናዊ አሰራር በጀት፣ ግዥ፣ ክፍያ፣ ሂሳብ አያያዝ እና ሪፖርትን ጨምሮ ሁሉንም የመንግስት የፋይናንስ ስራዎች በአንድ የኮምፒውተር መረብ የሚያገናኝ ነው።
የፋይናንስ ሚኒስቴር የቡድን መሪና የክንውን አማካሪ ወ/ት እመቤት መኮነን በበኩላቸው ሲስተሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የፋይናንስ አስተዳደር ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ገልጸዋል።

ይህ የማስተዋወቅ ስራ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መከናወኑ ሲስተሙ በቀጣይ በሌሎች 43 የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ለሚኖረው ትግበራ እንደ መነሻና ትልቅ ተሞክሮ የሚወሰድ ነው።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ፕሬስ የህትመት ውጤቶች በአውደ ርዕይው ትኩረት ስበዋል
የባሕር ዳር ከተማ ባህልና ቱሪዝም መመሪያ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ከተማ አቀፍ የመጻሕፍት ዐውደ ርዕይ አዘጋጅቷል። በዚህ ዐውደ ርዕይ ከስምንት በላይ የሚኾኑ የመጻሕፍት መሸጫ መደብሮችም ተሳተፈዋል። ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬስም አንዱ ነው። የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ፕሬስ የሽያጭ ባለሙያ አቶ ግስሜ ይችላልም በቅርቡ በፕሬሱ የታተመውን የዐፄ ዘርዐ ያዕቆብን ዜና መዋዕል ይዘው የተገኙ ሲሆን በግማሽ ቀን ውስጥ ብዙ ሽያጭ እንዳከናወኑና መጽሐፉም የአንባቢያን ትኩረት የሳበ መኾኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በፕሬሱ የአርትዖት ሥራቸው ተጠናቆ በህትመት ሂደት ላይ የሚገኙ ሥራዎችን ማለትም የዐፄ ኢያሱ ቀዳማዊ ዜና መዋዕል (አድያም ሰገድ)፣ የዐፄ ምኒልክ ዜና መዋዕል፣ Compendium of Medicinal Plants of Ethiopia Vol. I እና ዘረኝነትና ሳይንስ በአውደ ርዕዩ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ ለተገኙ ታዳሚዎችና የሚዲያ አካላት በሰፊው የማስተዋወቅ ሥራ ተሰርቷል።
ቦታ፦ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ዋና በር አጠገብ፣ ወደ ጣና ሐይቅ መግቢያ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

መልካም የገና በዓል!

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

The school welcomed new students
Bahir Dar University School of Teachers’ Education welcomed new candidates today with a warm orientation for those joining the Alternative Teacher Education Program in Amharic, English, and Physics departments. Led by the college deans, the kickoff program emphasized teaching as a calling and encouraged students to see themselves as future change makers in classrooms across Ethiopia.
The orientation gave participants an opportunity to get to know one another, asking questions and starting to create cooperation that will support them throughout their journey.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

High-Level Seminar Explores AI and the Future of Society and Education

February 16, 2026

Bahir Dar University hosted a high-level seminar titled “AI and the Future of Society and Education” at the President’s Office, bringing together members of the University’s top management, deans and directors of academic programs, and senior officials from Bahir Dar City Administration.

The seminar was delivered by Dr. Mikael Alemu Gorsky, an international strategist and academic researcher specializing in the societal and institutional implications of artificial intelligence. Born and educated in Moscow and drawing on Ethiopian and Israeli heritage, Dr. Gorsky currently lives and works in Israel. He serves as a lecturer and researcher at the Holon Institute of Technology near Tel Aviv, where his work focuses on how emerging technologies reshape governance systems, higher education, and long-term development trajectories.

In the seminar, Dr. Mikael addressed the rapidly evolving global landscape of artificial intelligence and examined its transformative implications for society at large. Particular emphasis was placed on how AI is reshaping governance systems, public administration, and the strategic direction of higher education institutions.

During the session, participants raised questions on the need for institutional policy on AI, curriculum redesign, emerging global AI trends, the integration of AI into institutional decision-making and medical sciences, and the ethical and regulatory challenges associated with technological acceleration. The presenter underscored the urgency for universities and public institutions to proactively position themselves within this transformation by investing in digital capacity, research innovation, and adaptive leadership.

While the discussion reflected a shared recognition of both the opportunities and strategic challenges AI presents for Ethiopia’s higher education and governance frameworks, the event concluded with a strong call for forward-looking institutional strategies and deeper collaboration to ensure that AI becomes a tool for inclusive growth and sustainable transformation.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Bahir Dar University Launches Student-Created Research Publication Management System (RPMS)

Bahir Dar University (BDU) has achieved a key milestone in its digital transformation with the launch of the Research Publication Management System (RPMS). Created entirely by a talented team of BDU students, the new system was officially presented to university leadership, including deans and directors, during a ceremony on February 13, 2026.

The RPMS is an advanced digital platform designed to centralize, monitor, and showcase the university’s extensive research outputs. Moving away from scattered and manual data entry, the university aims to reduce redundancies and establish a single, reliable source of academic contributions.

In a step toward greater self-reliance, the software was developed by graduates of the Bahir Dar Institute of Technology (BiT) in 2025. This project underscores the university's commitment to solving administrative challenges by utilizing the knowledge and technical skills of its students and alumni.

Prof. Enyew Adgo, Vice President for Research and Community Service, explained that this system is more than a tool—it acts as a bridge to national and international recognition. After thorough evaluation by technical experts, the university found this homegrown solution to surpass previous methods, marking a significant shift toward a modern, data-driven research environment.

The RPMS is expected to bring numerous benefits. By organizing research within a single database, it makes scholarly work more accessible to the global academic community and reduces the administrative burden on researchers and department heads.

Additionally, university leaders can now access real-time analytics to support decisions on research funding and strategic development.
Dr. Ababay Ketema, Director of Publication, Documentation, and Dissemination, highlighted that the system will help enhance the university's ranking and visibility. He noted that by improving how research findings are shared, the university is ensuring its researchers receive deserved recognition. The unveiling event included a technical presentation and a discussion session led by Professor Netsanet Fentahun, Corporate Director for Research Affairs, alongside the student developers.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ቀን፡ 04/06/2018 ዓ.ም
ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ  ከአካዳሚክ ዩኒቶች ውጭ በተለያዩ ክፍሎች በኃላፊነት የሚያገለግሉ የመካከለኛ እና ዝቅተኛ አመራር ምርጫ፣ ሹመት/ ምደባን  ለመደንገግ ታህሳስ  6 ቀን 2018 ዓ/ም በወጣው መመሪያ’ መሰረት ለ የማህበረሰብ አሳታፊነት ዳይሬክተር የኃላፊነት ቦታ በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ መሾም ይፈልጋል፡፡
ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡  የማህበረሰብ አሳታፊነት ዳይሬክተር
የማወዳደሪያ መስፈርት፡-
1ኛ. የትምህርት ማዕረግ/ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማት ወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤
3ኛ. በሚያመለክቱበት የስራ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ለማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/የምትችል፤
4ኛ. የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራር አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ሌሎች አካላት ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/የምትችል፤
አመልካቾች፡- የካቲት 05/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በስም በታሸገ ኤንቨሎፕ ፕሬዚደንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡
በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 583 20 9653 ወይም +251 583 20 6059 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡
ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የምርምር ስራዎችን ጥራት ለማረጋገጥ የሚያስችል የ"Turnitin" ሶፍትዌር አጠቃቀም ስልጠና መሰጠት ጀመረ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፤ ጥር 02/2018 ዓ.ም
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዘዳንት ጽ/ቤት አስተባባሪነት ለዲኖች፥ ዳይሬክተሮችና ትምህርት ክፍል ኃላፊዎች የTurnitin ሶፍትዌር አጠቃቀም ስልጠና እየተሰጠ ነው።
በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምርምር ጉዳዮች ኮርፖሬት ዳይሬክተር  የሆኑት ፕሮፌሰር ነፃነት ፈንታሁን በዩኒቨርሲቲው የሚካሄዱ የምርምር ስራዎችን ጥራት ለመጠበቅ እና ከስርቆት (Plagiarism) የፀዱ እንዲሆኑ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝና ሶፍትዌሩ በከፍተኛ ወጪ በግዢ የቀረበ መሆኑን ጠቁመው፣ በአሁኑ ወቅት እስከ 1,500 ለሚደርሱ ተመራማሪዎችና መምህራን አካውንት የመክፈት አቅም እንዳለው ገልጸዋል። ፕሮፌሰሩ አክለውም "ይህንን ሶፍትዌር ስንጠቀም በተፈቀደልን ልክ እና እጅግ በአግባቡ ሊሆን ይገባል" በማለት አሳስበዋል።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የህትመት፥ዶክመንቴሽንና ስርጭት ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር አባባይ ከተማ፣ ስለ ሶፍትዌሩ ምንነት እና አጠቃቀም ሰፊ ገለፃ አቅርበዋል። በገለጻቸውም፦አዲስ አካውንት እንዴት መክፈት እንደሚቻል፤የምርምር ሰነዶችን እንዴት መመርመር (Check) ማድረግ እንደሚቻል፤እና ውጤቱን እንዴት መተንተን እንደሚቻል በዝርዝር አሳይተዋል።
ዶ/ር አባባይ ከተማ አክለውም፣ ሶፍትዌሩ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውጭ መጠቀም እንደማይቻልና ሰልጣኞች በአጠቃቀም ሂደት ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በተጨማሪም የዩኒቨርሲቲው የአብያተ መጸሃፍት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ይበልጣል ታፈረ  ሶፍትዌሩን እንዴት ማስተዳደር (Manage) ማድረግ እንደሚቻል እና ተቋሙ የከፈለውን ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ እያንዳንዱ ተጠቃሚ በራሱ ትክክለኛ መረጃ አካውንት መክፈት እንዳለበት በተግባር አስረድተዋል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ከሰልጣኞች ለተነሱ ጥያቄዎች በዶ/ር አባባይ ከተማ አማካኝነት ዝርዝር ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። ይህ ስልጠና ዩኒቨርሲቲው በምርምር ዘርፍ የጀመረውን የጥራት ማረጋገጫ ጉዞ አንድ እርምጃ ወደፊት እንደሚያስኬደው ይታመናል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

በባሕር ዳር ከተማ የሚስተዋለውን የኢ-መደበኛ አሰፋፈር ችግር ለመፍታት የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሄደ

በባሕር ዳር ከተማ ጣና ክፍለ ከተማ የሚስተዋሉ የኢ-መደበኛ አሰፋፈር (Informal Settlements) ተግዳሮቶችን ለመለየትና ዘላቂ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያለመ የውይይት መድረክ ተካሄደ።

መድረኩ የኦስትሪያ መንግስት ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ባከናወኑት ጥናት ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ ነው።

የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት በዩኒቨርሲቲው መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም የፕሮጀክቱ አባል የሆኑት ፕሮፌሰር አማረ ሰውነት ሲሆኑ  ይህ ወርክ ሾፕ በጣና ክፍለ ከተማ በሚገኙ ባታ እና ወራሚት ቀበሌዎች ላይ የሚኖሩ ኢ-መደበኛ ሰፈሮች ላይ  ትኩረት ያደረገ እንደሆነና በኢ-መደበኛ ሰፈራ ላይ ያለውን ችግር ለይቶ ማውጣት እንዲሁም ለፖሊሲ አውጭዎችና አስተግባሪዎች የሚሆን ግባት መስጠትን ዋና ተልኳቸው መሆኑንና ለዚህ ጥናት /ምርምር/ ስራ አምስት የዩኒቨርስቲው መምህራንና ተመራማሪዎች ተመድበው ጥናቱን እያካሄዱ እንደሆነ ገልጸዋል።


እንደ ጥናቱ ግኝት፣ ላለፉት 20 ዓመታት በከተማዋ ያለው የኢ-መደበኛ አሰፋፈር ከሦስት እጥፍ በላይ መጨመሩን የገለጹት በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርስቲው መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዶ/ር አጸደ ደስታ ናቸው። አከለውም በዚህ ጉዳይ ከዚህ በፊት የተናጥል ውይይት መደረጉንና ያሉ ችግሮችን ለመለየት ብዙ ሂደት እንደሄዱና ይህም ወርክ ሾፕ የዚያ አካል እንደሆነና በዚህ ውይይት የጋራ የመፍትሄ አቅጣጫ ለማምጣት ከማህበረሰቡ፣ ከመንግስት አካላትና መንግስታዊ ካልሆኑ አካላት ጋር በጋራ ለመወያየት እንደሆነ ገልጸዋል።


ጥናቱ በኢ-መደበኛ ሰፈራዎች ውስጥ የሚስተዋሉ ችግሮች መኖራቸው በተለይም የቤቶች ደረጃቸውን አለመጠበቅና ለኑሮ ምቹ አለመሆን፣  የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የመንገድ፣ የጤና እና የትምህርት ተደራሽነት እጅግ አነስተኛ መሆን፣ በነዋሪዎች ላይ የሚስተዋለው የኢኮኖሚ አቅም ማነስና የተረጋጋ የገቢ ምንጭ እጥረት ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑንና ለእነዚህ ችግሮች እንደ ዋና ምክንያት የተጠቀሰው የከተማ አስተዳድሩ የኑሮ ደረጃቸውን የሚመጥን የመኖሪያ ቤት ቦታ አለመስጠቱ መሆኑ በመድረኩ ላይ ተገልጿል ። ይህም ነዋሪዎች ወደ ኢ-መደበኛ አሰፋፈር እንዲያመሩ አስገዳጅ ሁኔታዎችን ፈጥሯል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉ ኢ-መደበኛ ሰፋሪዎች
እንደገለጹት፣ ሰፈራው ከመሠረተ ልማት እጥረት ባለፈ መጠነ ሰፊ ማህበራዊ ችግሮችን እያስከተለ እንደሚገኝ በተለይም፦ ሴቶች በመሠረታዊ አገልግሎቶች እጥረት ምክንያት ለከፍተኛ እንግልትና ለኢኮኖሚ ጥግኝነት መጋለጣቸው እንዲሁም የተፋፈገ አሰፋፈርና የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓት አለመኖር ለበሽታዎች መስፋፋት ምክንያት መሆኑ ተጠቁሟል።

የጥናቱ ውጤት በቀጣይ ለፖሊሲ አውጭዎችና ለሥራ አስፈጻሚ አካላት ግብዓት እንዲሆን የሚቀርብ ሲሆን፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የመንግስት መስሪያ ቤት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት መጡ ባለሙያዎች በበኩላቸው፣ የጥናቱ ውጤት ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለመረዳት ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግና በቀጣይ የከተማዋን ፕላን በጠበቀ መልኩ ችግሩን ለመቅረፍ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

“የፋሽን ተደራሽነትን በማስፋት ባሕር ዳርን የፋሽን ከተማ ለማድረግ ጠንክረን እየሰራን ነው፡፡” አቶ ቢኒያም ሶሎሞን የአፓረል ፋካሊቲ ዲን
የአፓረል ፋካሊቲ “Sustainable Fashion” በሚል መሪ ቃል 2ኛውን አገር አቀፍ ጉባኤ አካሄደ፡፡
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቴክስታይል እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የአፓረል ፋካሊቲ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች፣ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ጥናታዊ ጽሑፍ አቅራቢዎች፣ ስራ ፈጣሪዎች፣ ተጋባዥ እንግዶች እና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት “Sustainable Fashion (ዘላቂ ፋሽን)” በሚል መሪ ቃል 2ኛውን አገር አቀፍ ጉባኤ አካሄደ፡፡
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቴክስታይል እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ታምራት ተስፋዬ ይህ ጉባኤ ወሳኝ አጋር አካላትን በማገናኘት ስለ ዘላቂ ፋሽን እንድንወያይ እና የፋሽኑ ዘርፍ በኢትዮጵያ ደረጃ እንዲስፋፋ ጉልህ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡
ዘላቂ ፋሽን ለአንድ ሀገር እድገት የጀርባ አጥንት ስለሆነ ፋሽንን ማበረታታት እና ማስፋፋት ይጠበቅብናል ሲሉ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዘዳንት ፕሮፌሰር እንየው አድጎ ተናግረዋል፡፡
ፕሮፌሰሩ አክለውም ጉባኤው ተመራማሪዎች የምርምር ውጤቶችን የሚያቀርቡበት፣ ከኢንዱስትሪ ዘርፉ ከመጡ አካላት ልምድ በመቅሰም የምርምር አድማሳችንን የምናሰፋበት፣ አካባቢን በማይበክል መልኩ ምርትን ለማምረትና ችግሮችን ተረድተን መፍትሄ ለማበጀት ያግዛል ብለዋል፡፡
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቴክስታይል እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የአፓረል ፋካሊቲ ዲን አቶ ቢኒያም ሶሎሞን የዚህ ጉባኤ ዓላማ ዘላቂ ፋሽንን ከአካዳሚው፣ ከኢንዱስትሪ እና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በማስተሳሰር የፋሽን ኢንዱስትሪውን ከፍ ማድረግ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡ ጉባኤው አካባቢያዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘላቂነትን በማስተዋወቅ ፋሽን ኢንዱስትሪው በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ ነውም ብለዋል፡፡
በጉባኤው ላይ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፤ ከተለያዩ ቦታ የመጡ ስራ ፈጣሪዎች እና አምራች ድርጅቶች ምርቶቻቸውን አስተዋውቀዋል፡፡

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ለሁሉም የብሔራዊ ድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ተፈታኞች በሙሉ

የ2018 ዓ.ም የግማሽ ዓመት የብሔራዊ ድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) የሚሰጠው የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ስለሆነ ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳውቃለን፡፡

To all National Graduate Admission Test (NGAT) candidates

The 2018 National Graduate Admission Test (NGAT) mid-year exam will be held on February 11, 2026. We would like to inform you that you should start preparing.

@bahir_dar_university
@bahir_dar_university

#SHARE #SHARE

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የእጅ ኳስ እና የባድመንተን ቡድን የነሃስ ሜዳሊያ ባለቤት ሆነ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት ልዑክ በጅማ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ስፖርት ፌስቲቫል ላይ ድሎችን ማስመዝገቡን ቀጥሏል።

የዩኒቨርሲቲያችን የእጅ ኳስ ቡድን ከመከላከያ ጋር ባደረገው እልህ አስጨራሽ ጨዋታ ውጤታማ በመሆን በቡድን የነሐስ ሜዳሊያ በድል ተቀዳጅቷል። እንዲሁም በተለይ በባድመንተን ዘርፍ ተማሪዎቻችን የላቀ ብቃታቸውን በማሳየት በአጠቃላይ 8 የነሐስ ሜዳሊያዎችን ለዩኒቨርሲቲያቸው አስገኝተዋል፦ተማሪ ፍቅርተ ጌታሁን፦ በነጠላና በጥንድ (2 ነሐስ)፣ተማሪ ያብስራ ፀጋየ፦ በጥንድና በድብልቅ (2 ነሐስ) ፣ተማሪ አምላኩ ዘውዱ፦ በድብልቅና በጥንድ (2 ነሐስ) እንዲሁም ተማሪ ናሁም አበበ፦ በነጠላና በጥንድ (2 ነሐስ)  ለዩኒቨርሲቲያቸው አስገኝተዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳቾሁ።

መልካም በዓል

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Announcement
Fourth Round of GAT Training

(Tir 18–19, 2018 E.C./26-27 January 2026)
To: All Interested Postgraduate Applicants
The College of Science and the Faculty of Humanities at Bahir Dar University are pleased to announce the Fourth Round of Graduate Admission Test (GAT) Training, which will be conducted over two days in a hybrid mode (online and face-to-face).

🔑 Training Focus Areas

Verbal Reasoning: Reading comprehension, vocabulary development, and analysis of written materials
Quantitative Reasoning: Arithmetic, algebra, geometry, and data interpretation
Analytical Writing: Critical thinking and structured expression of complex ideas

📅 Training Schedule
Mode: Hybrid (Online + Face-to-Face)
Duration: Two days (Tir 18–19, 2018 E.C./26-27 January 2026)
Training Registration link: https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdUBEDSA4MbiJ1OqGUypIZeh5ZSLDDD78zgGfi6eVvVcvI_Dg/viewform?usp=header

Online training links:
English session: https://meet.google.com/jqf-tjyh-gug
Mathematics session: https://meet.google.com/zic-cnze-zze
Face-to-Face Venues:
Smart Room 401, College of Science, Peda Campus
NEL-1, Faculty of Humanities, Peda Campus
💵 Training Fee
Fee: 300 Birr per applicant
Payment Method: Commercial Bank of Ethiopia (CBE)
Account Number: 1000012881968
Account Name: Human Rights and Legal Aid, BDU
Payment Reference: 4th Round NGAT Training
Please ensure that payment is made before the start of the training.
Attach the payment receipt during online registration.

👥 Coordinators
Prof. Tsegaye Kassa: 0920 761 042
Dr Ayenew Guadu: 0967 610 008

👨‍🏫 Trainers

Experts from the Departments of Mathematics and English Language and Literature
All interested postgraduate applicants are strongly encouraged to take advantage of this opportunity to enhance their preparation for the National Graduate Admission Test (NGAT).

Training Coordination Team
Bahir Dar University

@bahir_dar_university
@bahir_dar_university

#SHARE #SHARE

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Consultation on Education in Emergencies Held

The Office of the Dean of the College of Education, Research and Community Service, in collaboration with the Institute of Pedagogy and Education Research (IPER), jointly organized a half-day workshop on Education in Emergencies in Amhara region. The workshop focused on the damage inflicted on the education sector as a result of conflicts in the Amhara region and explored possible ways forward. The consultation brought together representatives from the Regional Education Bureau, non-governmental organizations (NGOs), the Department of Education of the Bahir Dar City Administration, as well as teachers and leaders from Bahir Dar University.

Mr. Atinkut Yalew, UNICEF Education Specialist for the Amhara region, made a thought provoking presentation on the current status of education in the region under conflict conditions. In his evidence-based presentation, he highlighted the impact of the crisis on education and outlined possible strategies for ensuring continuity of learning during emergencies. He also invited participants to reflect on the potential roles of university academics in such contexts.Dr. Dereje Taye, who facilitated the discussion, provided a brief overview of priority areas for future engagement. 

Finally, Dr. Asnakew Tagele, CEO of the College, delivered the closing remarks, calling on all stakeholders to play their part in supporting the young who are out of school due to recurring conflicts in the region.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመሠረተ-ልማት ግንባታዎችን አስረከበ
ባህር ዳር — የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ልማት ማዕከል (ECDD) ጋር በመተባበር፣ የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን እና ሰራተኞችን ተደራሽነት የሚያረጋግጡ የተለያዩ ግንባታዎችን አጠናቆ አስረከበ።

የዩኒቨርሲቲው የአካል ጉዳተኞች ጉዳይ ዳይሬክተር ዶክተር ዘላለም ተመስገን እንደገለጹት፣ ተቋሙ ከECDD ጋር በአራት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ ደርሷል። ከእነዚህም መካከል ዋነኛው "የአካባቢ ማሻሻያ" (Environmental Modification) ሲሆን፣ ለዚህም ተግባራዊነት በሁለት ግቢዎች ውስጥ አራት ተጨባጭ ስራዎች ተከናውነዋል። በፔዳ ግቢ፡ ሶስት የተለያዩ ቦታዎች ላይ የነበሩ ደረጃዎች ወደ ተዳፋት (Ramp) ተቀይረዋል። ይህም አካል ጉዳተኞች ያለ ማንም ድጋፍ በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ ያስችላቸዋል። እንዲሁም በቴክኖሎጂ ግቢ፡ የአካል ጉዳተኞችን ፍላጎት ያማከለ ዘመናዊ መጸዳጃ ቤት ተገንብቷል። ቀደም ሲል የነበሩት መጸዳጃ ቤቶች ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ባለመሆናቸው ሲፈጠር የነበረውን ከፍተኛ ችግር ይህ ግንባታ እንደሚቀርፈው ተገልጿል።
የECDD የተደራሽነት መሐንዲስ ወይዘሮ ኤደን የወንድወሰን እንደገለጹት፣ ግንባታዎቹ ከዚህ ቀደም ከሚሰሩ መሰል ስራዎች በልዩ ሁኔታ ተለይተው የተሰሩ ናቸው። ራምፖቹ (Ramps) የዊልቸር እንቅስቃሴን በሚያሳልጥ መልኩ ምቹ ሆነው የተሰሩ ሲሆን፣ ጥቅም ላይ የዋሉ ቁሳቁሶችም ደረጃቸውን የጠበቁና ተጠቃሚዎችን ለአደጋ የማያጋልጡ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የECDD የክልል አስተባባሪ ወይዘሮ አልማዝ መኮንን በበኩላቸው፣ ይህ ተግባር እንደ መጀመሪያ ሙከራ ወይም ማሳያ (Showcase) የሚወሰድ መሆኑን ጠቁመው፣ በቀጣይም አካል ጉዳተኞች እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መሰል ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ስታፍ አባል የሆኑት ዶክተር ሰለሞን ደምሴ፣ ግንባታው የተማሪዎችንና የሰራተኞችን የቆየ ችግር የፈታ መሆኑን ገልጸው፣ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ፕሮጀክቱ በሌሎችም የግቢው ክፍሎች ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የመጀመሪያውን የክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በይፋ አስመረቀ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ጥር 1፣ 2018 ዓ.ም) - የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ (ESA) ከተመሠረተ 15 ዓመታት በኋላ ከአዲስ አበባ ውጭ የመጀመሪያ የሆነውን የክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ በኢትዮጵያ ጨርቃጨርቅና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) ውስጥ በዛሬው ዕለት መርቆ ስራ አስጀምሯል። ይህ የባሕር ዳር ቻፕተር ጽሕፈት ቤት በኢንስቲትዩቱ ግቢ ውስጥ በሚገኘውና ለተማሪዎች፣ ለምሁራንና ለተመራማሪዎች ምቹ አገልግሎት በሚሰጠው ዘመናዊው "ግሪን ዲጂታል ላይብረሪ" ውስጥ ተደራጅቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ የአካዳሚው ሥራ አስፈጻሚ ፕ/ር ተከተል ዮሐንስና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር መንገሻ አየነ የጽሕፈት ቤቱን ቁልፍ በመረካከብና ሪቫን በመቁረጥ በጋራ መርቀው የከፈቱ ሲሆን፣ በዕለቱም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የአካዳሚው አባላት የሆኑ ፕሮፌሰሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር መንገሻ አየነ በምርቃቱ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አካዳሚው የመጀመሪያውን ቅርንጫፍ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መክፈቱ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸው ዩኒቨርሲቲው ከአካዳሚው ጋር በቅንጅት በመሥራት ለአማራ ክልልም ሆነ ለሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የሳይንስ እድገት የሚጠበቅበትን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። ፕሬዚደንቱ አክለውም በአሁኑ ወቅት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ 11 የአካዳሚው አባል የሆኑ ፕሮፌሰሮች ቢኖሩም፣ ተቋሙ ካሉት 43 ፕሮፌሰሮችና ከ850 በላይ ረዳት ፕሮፌሰሮች አንጻር ይህ የተደራጀ አቅም ለሀገርና ለሕዝብ ጠቃሚ የሆኑ ሳይንሳዊ ሥራዎችን ለማከናወን ትልቅ ዕድል መሆኑን አብራርተዋል።

የአካዳሚው ሥራ አስፈጻሚ ፕ/ር ተከተል ዮሐንስ በበኩላቸው፣ አካዳሚው በስድስት የሳይንስ ዘርፎች ማለትም በኢንጅነሪንግ፣ በጤና፣ በተፈጥሮ ሳይንስ፣ በጥበባት ዘርፎች ሁሉ ከፍተኛ የምርምርና የማማከር ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን አስታውሰዋል። አካዳሚው ተደራሽነቱን ለማስፋት ባደረገው እንቅስቃሴ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚውን ሚና በመውሰድ ደረጃውን የጠበቀ የጽሕፈት ቤት አገልግሎት በማመቻቸቱ የተሰማቸውን ኩራት ገልጸዋል።

ፕ/ር ተከተል አክለውም አካዳሚው ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቅርበት በመሥራት በሀገራዊ የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ ሳይንሳዊ ምላሾችን እንደሚሰጥና በማማከር፣ በመገምገምና አዳዲስ ሳይንሳዊ እሳቤዎችን በማመንጨት በኩል የላቀ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በመጨረሻም በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሚገኙና ተፈላጊውን መስፈርት የሚያሟሉ ምሁራን የአካዳሚው አባል በመሆን ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Bahir Dar University Celebrates the New Year with a Vibrant International Gathering of Cultures

Bahir Dar, Ethiopia
January 1, 2026

Bahir Dar University (BDU) marked the beginning of the New Year with a colorful and vibrant International New Year Gathering on Thursday, January 1, 2026, bringing together international students and staff, senior government officials, diplomats, and members of the university community in a joyful celebration of diversity, unity, and shared aspirations.

Held at the Wisdom Tower Garden, the gathering was more than a celebration of the New Year; it was a celebration of community, connection, and shared purpose. The event reflected the university’s commitment to internationalization and its belief that meaningful global engagement is built through human connection and mutual respect.

The program began with arrival and a cultural welcome, setting a festive tone that carried through the evening. The formal opening featured the Ethiopian National Anthem and the East African Anthem, symbolizing national pride and regional solidarity.

Participants were warmly welcomed by Dr. Zewdu Emiru, Vice President for Information and Strategic Communication of Bahir Dar University, who emphasized the importance of fostering an inclusive and supportive environment for international students and staff.

In his opening remarks, Dr. Mengesha Ayene, President of Bahir Dar University, highlighted the university’s vision of becoming a globally engaged, research-intensive, and autonomous institution where diversity is embraced as a core strength.

The celebration was further enriched by key remarks from Ambassador Nebiyu Tedla, Minister Delegate and Director General of Public Diplomacy at the Federal Democratic Republic of Ethiopia Ministry of Foreign Affairs, who underscored the role of education and cultural exchange in advancing public diplomacy and strengthening people-to-people relations.

Mr. Getu Abdissa, Scholarship and Internationalization Desk Officer at the Ministry of Education, also delivered key remarks, reaffirming the Ministry’s commitment to supporting international students and expanding scholarship and internationalization opportunities.

A brief overview of the purpose of the gathering was presented by Dr. Manendante Mulugeta Seyoum, Director of External Relations and Partnership at Bahir Dar University, who noted that the event was designed around three key purposes: as a moment of welcome and appreciation, to strengthen bonds, and celebrate shared values of diversity, inclusiveness, cooperation, and peace.

The heart of the evening unfolded through student-led cultural expressions, where international students showcased the richness of their cultures through music, dance, and interactive performances. Student groups from all East African countries filled the evening with color, rhythm, and energy, creating moments of joy and mutual appreciation.

The event also featured goodwill messages from distinguished guests, including Ambassador Roza Yerukneh, Deputy Director General of Public Diplomacy at the Ministry of Foreign Affairs, Mulki Mohammed Hussein, Assistant Education Attaché at the Embassy of Somalia, and student representatives, who spoke on behalf of the international student body. Their messages conveyed sincere appreciation to the university leadership and organizing team for hosting such an inclusive and memorable celebration.

As Bahir Dar University advances toward becoming a research-intensive and autonomous institution, international engagement remains a core pillar of its vision. Events such as this New Year Gathering serve as powerful reminders that global engagement begins at home, through dialogue, respect, shared experiences, and a strong sense of community.

Читать полностью…
Subscribe to a channel