bahir_dar_university | Unsorted

Telegram-канал bahir_dar_university - Bahir Dar University,Ethiopia

21305

It is a channel about Bahir Dar University all Campuses! www.bdu.edu.et

Subscribe to a channel

Bahir Dar University,Ethiopia

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመሬት አስተዳደር ኢንስቲትዩት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ስልጠናና ምዘና በይፋ አስጀመረ።
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመሬት አስተዳደር ኢንስቲትዩት ከከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የከተሞች ገቢ ሪፎርም ፕሮጀክት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር፣ በአማራ ክልል የከተማ መሬት፣ ፕላን ዘርፍ እና የከተማ ፋይናንስ ባለሙያዎች ላይ ያነጣጠረ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ስልጠናና ምዘና ማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት አካሂዷል።

ይህ ስልጠና ከ19/08/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 02/10/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 150 ሰልጣኞች በ5 ዋና ዋና የሙያ ዘርፎች ላይ ስልጠናውን ይወስዳሉ።
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ጉዳዮች ኮርፖሬሽን ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ነጻነት ፈንታሁን፣ ስልጠናው የንድፈ ሀሳብ እውቀት ብቻ ሳይሆን፣ ሰልጣኞች የተማሩትን እውቀትና ልምድ በመጠቀም የመሬት አስተዳደር ስርዓቱን የማዘመንና የመመዝገብ ትልቅ ሀላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የፌዴራል ከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ተወካይ ወ/ሮ ሰሎሜ ጥላሁን፣ ከተሞቻችን ዘመኑ ከሚጠይቀው አንጻር የመሬት አያያዝና ምዝገባን በማዘመን ለነዋሪዎች ግልጽና ምቹ አሰራርን መፍጠር እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል።

የአማራ ክልል የመሬት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አብሬ ከበደ፣ በሀገር ሀብትና ጊዜ ታቅዶ የተዘጋጀው ይህ ስልጠና የዘርፉን ችግሮች ለመፍታት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ ሰልጣኞች በዲሲፕሊንና በትጋት በመሳተፍ የመፍትሔ አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

የመሬት አስተዳደር ኢንስቲትዩት ዲን ዶ/ር ሰይድ ሁሴን፣ ኢንስቲትዩቱ በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ ሆኖ እየሰራ መሆኑን ገልጸው፣ ለሚሰሩበት ተቋም አርአያ የሚሆኑ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት ጥረት እያደረጉ መሆኑን አስረድተዋል።  ስልጠናው በዋናነት የሚያጠነጥነው የመሬት ይዞታ መለኪያና ካርታ ስራ ፣የመሬት ይዞታ ምዝገባ ስርዓት፣ የከተማ ፕላንና የመሬት አስተዳደር፣ የማይንቀሳቀስ ንብረት ዋጋ ግምት፣ የከተማ ፋይናንስ (ወይም የከተማ የገንዘብ አስተዳደር) መሆናቸውን ገልጸዋል። አክለውም ዩኒቨርሲቲያችን ለሀገራችን የከተማ ልማትና የመሬት አስተዳደር ዘርፍ የላቀ ብቃት ያላቸውን ባለሙያዎች በማፍራት የሚያደርገውን አስተዋጽኦ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቀዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Bahir Dar University Hosts 3rd BRICS Think Tank Council Ethiopia Conference

Bahir Dar University, in collaboration with the Institute of Foreign Affairs, successfully hosted the 3rd BRICS Think Tank Council (BTTC) Ethiopia Conference from 22–23 April 2026, under the theme “The Prospect of BRICS and Ethiopia’s Priorities.” The high-level forum brought together diplomats, university presidents, scholars, researchers, and policy experts for two days of rich dialogue and strategic reflection.

In his welcoming remarks, Dr. Zewdu Emiru, Vice President for Information and Strategic Communication at Bahir Dar University, emphasized that the conference aimed to provide vital platform for exchanging ideas, sharing experiences, and generating actionable recommendations on key global and national priorities, thereby strengthening economic, political, and diplomatic cooperation among BRICS member countries and partner nations. He underscored the importance of translating insights and recommendations from policymakers, scholars, and researchers into strategies that advance shared development goals.

H.E. Mr. Mohammedrafi Abaraya, Deputy Director of the Institute of Foreign Affairs, in his opening remarks, highlighted the growing global significance of BRICS, noting that the bloc represents approximately half of the world’s population and over a quarter of global trade. He further emphasized Ethiopia’s emerging leadership role in Africa, particularly in areas such as technology and innovation, green development, agricultural transformation, and climate action.

In his address, H.E. Ambassador Minelik Alemu, Special Policy Advisor to the Minister of Foreign Affairs, described the conference as a vital platform for Ethiopia to expand its economic, research, and diplomatic engagement, while fostering meaningful knowledge exchange with new global partners.

Over the two days, participants engaged in substantive discussions across a range of critical global and national priorities. Parallel breakout sessions enabled deeper engagement, culminating in forward-looking recommendations that will be submitted to the 18th BRICS Academic Forum (2026) and subsequently to the XVIII BRICS Summit.

In his closing remarks, Dr. Mengesha Ayene, Bahir Dar University, reflected on the depth and quality of the discussions, noting that the conference successfully created a platform for critical reflection, knowledge exchange, and strategic alignment between Ethiopia and BRICS partners. He highlighted the importance of addressing global challenges, ranging from climate change and digital transformation to inclusive economic governance, through collaborative, research-driven, and policy-informed approaches.

Dr. Mengesha reaffirmed Bahir Dar University’s strong commitment to supporting such high-level intellectual engagements, positioning the University as a hub for policy dialogue, research collaboration, and international partnership. He further emphasized the University’s readiness to contribute to evidence-based policymaking and regional and global knowledge systems.

Following the conference, participants visited Bahir Dar University’s Ethiopian Institute of Textile and Fashion Technology (EiTEX), where they were introduced to the University’s achievements in textile innovation, research, and industry linkage. The visit, complemented by a brief city tour of Bahir Dar, was met with highly positive reflections from participants, who praised the University’s academic excellence, innovation ecosystem, and the city’s unique cultural and natural appeal.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

U.S. Alumni Engagement Highlights Impact, Innovation, and Community Transformation

The visit of H.E. Ervin Massinga, U.S. Ambassador to Ethiopia, to Bahir Dar University featured an engaging and insightful dialogue with U.S. program alumni hosted at Bahir Dar Institute of Technology (BiT). The session brought together a dynamic group of beneficiaries of U.S.-funded programs, entrepreneurs, scholars, and faculty members who have participated in various academic and professional exchanges.

The discussion provided a powerful platform for alumni to share how their experiences in U.S.-supported programs have translated into meaningful contributions at the local level. Participants highlighted their active roles in transferring knowledge and skills to students and communities, supporting youth entrepreneurship, start-up development, and innovation ecosystems, and driving business development initiatives and community-based solutions.

A key highlight of the session was the role of the U.S. Alumni Bahir Dar Chapter, hosted at BiT, which serves as a growing network for collaboration, mentorship, and sustained engagement among alumni.

The discussion also underscored the importance of strengthening platforms such as the American Corner, recognized as a vital resource for youth learning, access to information, and cross-cultural exchange. Participants emphasized the need to further expand such initiatives to maximize their impact.

Both the Ambassador and the participants reflected on the importance of sustained partnerships, alumni engagement, and investment in human capital as key drivers of development. The session concluded with a shared vision to further strengthen alumni networks and enhance collaboration between U.S. programs and Bahir Dar University in fostering innovation, leadership, and community transformation.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ቀን፡ 14/08/2018 ዓ.ም
ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመካከለኛ አመራር ምርጫና አሰያየምን ለመደንገግ ባወጣዉ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 05/2012 መሰረት ለ ግሽአባይ ግቢ የጀማሪ መርሃግብር ም/ዲን  በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ መሾም ይፈልጋል፡፡
ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡ ግሽአባይ ግቢ የጀማሪ መርሃግብር ም/ዲን 
የማወዳደሪያ መስፈርት፡-
1ኛ. የትምህርት ማዕረግ/ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማትወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤
3ኛ. በሚያመለክቱበት አካዳሚክ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ አካዳሚክ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ቸማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
4ኛ. የአካዳሚክ ክፍሉ ማህበረሰብ፣ የአካዳሚክ ኮሚሽኑ አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
አመልካቾች፡-
ይህ ማስታወቂያ በዩኒቨርሲቲው ድህረ- ገጽ፣ ፌስቡክና ማስታወቂያ ሰሌዳዎች ከተገለጸበት ሚያዚያ14 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡
በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 Academic V/Dean 20 9653 ወይም +251 583 20 6059 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡
ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር መንገሻ አየነ የተላለፈ የትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

ለዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ፣ ለአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም ለአገር አቀፍና ለዓለም አቀፍ አጋሮቻችን በሙሉ፤

ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን።

የትንሣኤ በዓል ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገርንበትና ተስፋ የታደሰበት ታላቅ የድል በዓል ነው። ይህ በዓል ለእኛ ለባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ እንደ ተቋም የጀመርናቸው ታላላቅ የለውጥ ጉዞዎች ፍሬ አፍርተው የምናይበት አዲስ ምዕራፍ ተደርጎ ይወሰዳል።

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በአሁኑ ወቅት "ርዕይ ጥበብ ቁጥር ፪" የተሰኘውን የ5 ዓመት የስትራቴጂክ ዕቅድ መሠረት በማድረግ ወደ ሙሉ ራስገዝ ዩኒቨርሲቲነት የምናደርገውን ታሪካዊ የሽግግር ጉዞ በቆራጥነት እያከናወነ ይገኛል። ይህ የራስገዝነት ርዕያችን የምርምር ዩኒቨርሲቲነታችንን በጽኑ መሠረት ላይ በማቆም በተግባር የተገለጠ ማኅበረሰባዊ ለውጥ ማምጣትን ያለመ ነው። ከዚህም በተጨማሪ በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ ሥርዓተ-ትምህርታችን ሁሉ ተጨባጭ ማሳያችን እንዲሆን በማድረግ የላቀ የዕውቀትና የጥበብ ማዕከል ለመሆን በትጋት እየሠራን እንገኛለን።

ይህ የ5 ዓመት የሽግግር ጉዞ ስኬታማ ይሆን ዘንድ የዩኒቨርሲቲው መምህራን፣ ሠራተኞች፣ ተማሪዎች እንዲሁም የአካባቢያችን ማኅበረሰብና አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ አጋሮቻችን የምታደርጉት ድጋፍና ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪዬን አቀርባለሁ።

የትንሣኤው ብርሃን በሥራችን ሁሉ እንዲበራና ተቋማችንን ወደ ላቀ ከፍታ እንዲያሸጋግረው እመኛለሁ።
በድጋሚ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ።

ዶ/ር መንገሻ አየነ
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ቀን፡ 28/08/2018 ዓ.ም
ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከአካዳሚክ ዩኒቶች ውጭ በተለያዩ ክፍሎች በኃላፊነት የሚያገለግሉ የመካከለኛ እና ዝቅተኛ አመራር ምርጫ፣ ሹመት/ ምደባን ለመደንገግ ታህሳስ 6 ቀን 2018 ዓ/ም በወጣው መመሪያ’ መሰረት ለስብእና ግንባታ ምክትል ዲን የኃላፊነት ቦታ በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ መሾም ይፈልጋል፡፡
ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡ ለስብእና ግንባታ ምክትል ዲን
የማወዳደሪያ መስፈርት፡-
1ኛ. የትምህርት ማእረግ/ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት፤ በካውንስሊንግ፣ በክሊኒካል ሳይኮሎጂ፣ ወይም በሳይካትሪ እና ተዛማጅ ዘርፎች ሁለተኛ ዲግሪ እና በላይ
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማት ወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤
3ኛ. በሚያመለክቱበት የስራ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ለማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/የምትችል፤
4ኛ. የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራር አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ሌሎች አካላት ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/የምትችል፤
አመልካቾች፡- ከሚያዚያ 28/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በስም በታሸገ ኤንቨሎፕ ፕሬዚደንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡
በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 583 20 9653 ወይም +251 583 20 6059 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡
ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር እያደረገ ያለውን  ጉዞ አጠናክሮ መቀጠሉን አስታወቀ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ  (መጋቢት 28/ 2018 ዓ.ም) — በኢትዮጵያ ቀዳሚ ከሆኑ የትምህርት ተቋማት አንዱ የሆነው ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ፣ አጠቃላይ የአሠራር ዘይቤውን በመቀየር ወደ “ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲነት” ለመሸጋገር የሚያስችለውን የልየታ ሂደት በይፋ ማብሰሩን ገለጸ። ይህ ሽግግር ዩኒቨርሲቲው ሙሉ በሙሉ ወደ “ራስ-ገዝነት” (Autonomy) ለመሸጋገር ለያዘው ብሔራዊ ግብ እንደ ትልቅ መነሻ ተወስዷል።የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት መንገሻ አየነ (ዶ/ር ) በጉዳዩ ላይ እንደገለጹት፣ ተቋሙ ካለበት መደበኛ የመማር-ማስተማር ሂደት ወጥቶ በምርምርና ፈጠራ ላይ የተመሠረተ እንዲሆን መወሰኑ ለሀገራዊ ዕድገት ያለውን ድርሻ ያሳድገዋል ብለዋል። አክለውም ዋናው ግባችን በምርምር ግንባር ቀደም መሆን ብቻ ሳይሆን፣ ራሱን በራሱ የሚያስተዳድርና የፋይናንስና የአካዳሚክ ነፃነቱን ያረጋገጠ ሙሉ በሙሉ ራስ-ገዝ ተቋም መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት እሰይ ከበደ (ፕ/ር)ያቀረቡት ዝርዝር የልየታ ሪፖርት እንደሚያመለክተው፣ ዩኒቨርሲቲው በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተቀመጡትን ጥብቅ መመዘኛዎች ለማሟላት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በተጨማሪም ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ በ“ምርምር-ተኮር” ምድብ ውስጥ እንዲካተት የሚያስችሉ የመምህራን ብቃት፦ ቢያንስ 50 በመቶ የሚሆኑት መምህራን የዶክትሬት (PhD) ዲግሪ ያላቸው መሆን፣የተማሪዎች ስብጥር፦ የድህረ-ምረቃ (ማስተርስና ዶክትሬት) ተማሪዎች ቁጥር አጠቃላይ ከተማሪው ብዛት 30 በመቶ መድረስ፣የበጀት ድልድል፦ ከዓመታዊ በጀቱ ቢያንስ 5 በመቶ ለምርምርና ምርምር ነክ ተግባራት ብቻ መመደብና ዓለም አቀፋዊነት፦ የውጭ የምርምር ፈንድ ማሰባሰብና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ስትራቴጂካዊ ትብብር መፍጠር ዋና ዋና ነጥቦች መሆነቸውን አስገንዝብዋል፡፡  ዩኒቨርሲቲው ከብዛት ይልቅ ለጥራት ትኩረት ለመስጠት ፕሮግራሞቹን በድጋሚ እየፈተሸ መሆኑ ጠቅሰው  በዚህም መሠረት፦ተደጋጋሚና ተመሳሳይ የሆኑ የትምህርት ዘርፎችን በመቀነስ በላቀ ጥራት ላይ ማተኮር፣ዘርፈ-ብዙ (Multidisciplinary) ምርምሮችን በማጠናከር ለሀገራዊ ችግሮች ተግባራዊ መፍትሔ ማመንጨትና በዓለም አቀፍ የጥናትና ምርምር መጽሔቶች ላይ የሚታተሙ የጥናት ውጤቶችን ቁጥርና ጥራት ማሳደግ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በሪፖርቱ ማጠቃለያ ላይ ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ አባላት ጋር ጥልቅ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ ለተነሱ ስጋቶችና ጥያቄዎች በ መንገሻ አየነ (ዶ/ር) መሪነት ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። በውይይቱም ዩኒቨርሲቲው የጀመረው  የለውጥ ጉዞ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን የሚያስችለው እንደሆነ ሀሳብ ተወስዷል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Bahir Dar University Holds the 3rd Stakeholders’ Consultation Forum on the “LINK” Project, Aiming to Transform the Agricultural Sector

[Bahir Dar University – April 04, 2026]

Bahir Dar University, in collaboration with the The Austrian Partnership Programme in Higher Education and Research for Development (APPEAR) and HAUP University in Austria, successfully held the LINK-351 Project’s two-year performance review and stakeholder consultation workshop.

The University’s Vice President for Information and Strategic Communication, Dr. Zewdu Emiru, attended the forum and delivered a welcome address, reaffirming the university’s commitment to implementing community-based projects as a problem-solving institution.

Dr. Zewdu said the project would modernize the postgraduate Agroforestry curriculum, equipping graduates with the skills needed to better serve farmers as they enter the workforce.

The Dean of the College of Agriculture and Environmental Sciences, Prof. Melkamu Alemayehu, noted that the project effectively integrates the university’s three core missions: teaching, research, and community service. He added that a “Living Lab” involving 10 farmers is currently underway, that the project is enrolling and training Master’s students, and that a student is pursuing PhD studies in Austria, contributing to the development of high-potential scholars.

Project Coordinator Dr. Zerihun Yohannes presented the two-year performance report, stating that the project has successfully completed two-thirds of its planned three-year duration. He explained that the workshop aimed to evaluate progress made so far and to gather input from stakeholders to inform further problem-solving research.

During the forum, group discussions were facilitated by Dr. Habtamu Asaye, Mr. Mekonnen Getachew, and DRMFSS Director Dr. Emiru. Stakeholders, including farmers, researchers, and representatives from executive bodies, actively participated in the discussions.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

PhD Opportunity
Bahir Dar University (BDU) invites applications for one PhD position under the project “Understanding scaling of soil moisture retention practices for climate-resilient food production in semi-arid Ethiopia and Kenya - SMARTSCALE”.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በዲጂታል የታገዘ የሒሳብ ትምህርት (Interactive Digital Mathematics Education) አገራዊ ወርክሾፕ ተካሄደ
መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም | ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ኮሌጅ የሒሳብ ትምህርት ክፍል "National Workshop on Interactive Digital Mathematics Education" በሚል ያዘጋጀው አገራዊ የወርክሾፕና የሶፍትዌር ምርቃት መርሃግብር ተካሂዷል።

ወርክሾፑን በንግግር የከፈቱት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ፕ/ር እሰይ ከበደ፣ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ከኢትዮጵያ የትምህርት ስትራቴጂክ ዕቅድ አንዱና ዋነኛው መሆኑን የጠቀሱት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ መድረኩ ላይ ለተገኙ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የሳይንስ ኮሌጅ ዲን ፕ/ር ብርሃኑ አሳዬ በበኩላቸው፣ ለተጋባዥ እንግዶቹና ለተመራማሪዎቹ ምስጋና በማቅረብ የመድረኩን አስፈላጊነት አስገንዝበዋል።

ስለ ወርክሾፑ ዓላማና ስለ ሶፍትዌሩ ዝርዝር ማብራሪያ የሰጡት የዩኒቨርሲቲያችን መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር አብዱ መሐመድ፣ "Interactive Digital Mathematics" መጽሐፍ/ሶፍትዌር መዘጋጀቱ በሒሳብ ትምህርት ዘርፍ ያለውን የመምህራን እጥረትና የተማሪዎችን የግብረ-መልስ (Feedback) ችግር እንደሚቀርፍ ገልጸዋል።
አክለውም"ይህ ሶፍትዌር እያንዳንዱ ተማሪ ስህተቱንና ጥንካሬውን በራሱ እንዲለይ እንደሚረዳና ይህም ልክ ለእያንዳንዱ ተማሪ አንድ መምህር እንደተመደበለት እንደሚቆጠር እንዲሁም ሶፍትዌሩ የተዘጋጀው በአገራዊ የትምህርት ሥርዓተ መሠረት በመሆኑ፣ ጥቅሙ ለባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን ለመላው የኢትዮጵያ ተማሪዎች እንደሚተርፍ ገልጸዋል።

ከኬንያ ዩኒቨርሲቲ የመጡት መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር ሚካኤል ኦቤሮ  INNODEMS and their Collaboration with Ethiopian Universities" በሚል ርዕስ ልምዳቸውን አጋርተዋል።
ዶ/ር ሚካኤል ተማሪዎች ሒሳብን እንዲወዱ ለማድረግ የማስተማር ዘዴን መቀየር እንደሚገባ አሳስበዋል። ሒሳብን በጨዋታ (Games)፣ በእንቆቅልሾች (Puzzles) እና በካርዶች (Cards) ማስተማር ተማሪዎችን የበለጠ እንደሚያነቃቃ ገልጸው፤ የራሳቸውን ተሞክሮ ሲያካፍሉም፦ "እኔ ራሴ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እያለሁ በሒሳብ ጎበዝ አልነበርኩም፤ ነገር ግን በጨዋታ መልክ መለማመድ  መቻላቸው ፍላጎቱ እንደ ጨመረላቸውና ዛሬ ደግሞ የሒሳብ ምሁር ለመሆን እንዳበቃቸው ልምዳቸውን አካፍለዋል።

በመርሃግብሩ በዶ/ር አብዱ መሪነት የፓናል ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ በውይይቱ የተሳተፉት ከትምህርት ሚኒስቴርና ከክልል ትምህርት ቢሮ የመጡ እንግዶች የሶፍትዌሩን ቀጣይነት ለማረጋገጥና ለማስፋፋት አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል።

በመርሐ-ግብሩ ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት፣ ከትምህርት ሚኒስቴርና ከክልል ትምህርት ቢሮ የመጡ የሥራ ኃላፊዎች፣ ከኬንያ የመጡ መምህርና ተመራማሪ፣ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች ተገኝተዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Bahir Dar University recently hosted a half-day training workshop titled “Avoiding Rejection: How to Successfully Navigate the Publishing Process” as part of its Research Excellence Series 2026. The session was facilitated by Sam Nkosi from Taylor & Francis Group.

The workshop was opened by Prof. Eneyew Adgo, Vice President for Research and Community Engagement at BDU, who emphasized the University’s commitment to strengthening research quality and enhancing global visibility. He highlighted the importance of equipping researchers with practical skills to effectively navigate the academic publishing process. He also expressed appreciation to Taylor & Francis for delivering this targeted training and encouraged participants to actively engage with the facilitator. Dr. Tibebu Anteneh, Director of BDU Press, on his part expressed the importance of exploring opportunities for follow-up initiatives, including discipline-specific manuscript development workshops, editorial training sessions, and continued collaboration with international publishers to support both authors and journal editors.
Participants—including journal editors, faculty members, and postgraduate students—engaged in discussions on key topics such as selecting appropriate journals, understanding editorial expectations, responding to peer review, and maintaining ethical standards in publishing. The session also addressed common challenges such as manuscript rejection, language barriers, and identifying predatory journals.
The interactive nature of the training allowed participants to share experiences and gain practical insights into improving both individual research output and institutional publishing standards.
The workshop reflects Bahir Dar University’s ongoing efforts to enhance research capacity, strengthen its academic journals, and increase its international visibility.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Peter Döhle Senior Officials Visit Bahir Dar University Maritime Academy
Bahir Dar University
March 18, 2026
Senior executives from the German shipping giant, Peter Döhle, a long-standing strategic partner, visited the Bahir Dar University Maritime Academy on March 18, 2026. The visit aimed to further strengthen the enduring partnership between the two institutions and explore new areas of collaboration.
Mr. Gezu Gibramu, the Academy’s Liaison Officer and Logistics Coordinator, welcomed the delegation and guided them on a tour of the Academy’s key facilities. The visitors toured the medical training facilities, where students receive hands-on instruction in first aid to help save lives at sea and manage emergencies. They also visited the modern mechanical and electrical workshops, which play a crucial role in delivering high-quality practical training to marine graduates.
Peter Döhle currently employs over 500 personnel, of whom 120 (nearly 25%) are Ethiopians trained at the Bahir Dar University Maritime Academy. This figure stands as a strong testament to the Academy’s role in producing internationally competitive and qualified maritime professionals.
“This visit will not only create internship opportunities for our students but will also open doors for expanded employment and accelerated technology transfer,” said Mr. Bizu.
It was also noted during the visit that such international partnerships contribute significantly to enhancing training quality in line with global standards. They also increase the competitiveness of Ethiopian marine graduates in the international shipping industry, support the growth of the country’s foreign exchange earnings, and broaden students’ exposure to modern maritime technologies.
Bahir Dar University Maritime Academy will continue to strengthen its collaboration with international institutions to enhance Ethiopia’s presence in the global maritime transport sector, Mr. Bizu, Liaison Officer and Logistics Coordinator of the Academy, affirmed.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

📢 Call for Papers: EAI-ICAST 2026

The 14th International Conference on the Advancement of Science and Technology (EAI-ICAST 2026), hosted by Bahir Dar Institute of Technology, invites submissions. It gathers global researchers to explore engineering and sustainable tech.

🗓️ Deadlines

- Full Paper: April 30, 2026
- Acceptance: June 20, 2026
- Camera-ready: July 30, 2026
- Conference: October 2–4, 2026

🔬 Tracks
- AI, Machine Learning
- Electrical, Electronics, Computer Engineering
- Manufacturing & Mechanization
- Materials Science
- Process Industries for Sustainability
- Renewable & Green Energy
- Sustainable Infrastructure

📍 Venue & Submission

Location: Bahir Dar University, Ethiopia
Submit: icast-conf.eai-conferences.org/2026/
Contact: repubbit@gmail.com
Sponsors welcome! Join us in October to share research and connect globally.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በልዩ ድምቀት ተከበረ

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ “Give to Gain” በሚል፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ “50 ዓመት የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ "ጥበብ" የመሰብሰቢያ አዳራሽ በልዩ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል።
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ከአብክመ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዴኤታ ነቢያ መሀመድ እና  የሴቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዘዳንት ጦይባ ሀሰንን እንዲሁም የባህር ዳር ከተማ ም/ከንቲባ አቶ አስሜ ብርሌ ጨምሮ  ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣የዩኒቨርሲቲው ተመራማሪና ምሁራን፣ተማሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ (ዶ/ር) የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ በንግግራቸውም የሴቶችን የታሪክ ተጋድሎና ጥንካሬ አውስተዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም
በዓሉ የሴቶችን ተጋድሎ የምናስታውስበት ብቻ ሳይሆን፣ ላለፉት 50 ዓመታት የሴቶች ድምፅ ለሀገራዊ ለውጥና ለታሪክ መታደስ ያበረከተውን አስተዋጽኦ የምናከብርበት ነው ብለዋል።
በተለይም በዩኒቨርሲቲው ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሠለጠኑትና የተመረቁት 27 ሴት መርከበኞች የሴቶችን ብቃትና አቅም በተግባር ያሳዩ የዘመኑ የጥንካሬ ተምሳሌቶች መሆናቸውን በመጥቀስ፣ "ሴት ስትሠራ ሀገር ትሠራለች፤ የሴቶች ውጤታማነት የሀገር ውጤታማነት ነው" ሲሉ የሴቶችን ሚና አጉልተዋል።

መርሐ ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ ክብርት  ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በዓሉ ከጥቁር ሕዝቦች ኩራት "ዐድዋ" ድል ማግስት መከበሩ ለየት ያለ ትርጉም እንደሚሰጠው ገልጸዋል። እናቶቻችን በዐድዋ ያሳዩት ጀግንነትና ጥበብ ዛሬም ለሴቶች መብት መከበርና ለፖለቲካዊ ተሳትፎ መጎልበት መሠረት መሆኑን አስገንዝበዋል።
ባለፉት 50 ዓመታት ሴቶች በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በጤና እና በትምህርት ዘርፎች ያመጡት ለውጥ የሚደነቅ መሆኑ በዝርዝር ተመላክቷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የዘርፉ ምሁራን የውይይት የመነሻ ጽሑፎችን አቅርበዋል፦ ዶክተር ሙሉጎጃም ወንድይፍራው (የዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር) እና ወ/ሮ ሰገድ አሻግሬ (የስርዓተ ጾታ ትምህርት ክፍል መምህርት)፦ ምሁራዊ ትንታኔ ያዘለ የመወያያ ፅሁፍ ሰነድ አቅርበዋል። እንዲሁም ወይዘሮ ሰብለ ዘውዱ (የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ሕጻናትና ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ)፦ የኢትዮጵያ ሴቶች የ50 ዓመታት የለውጥ ጉዞና የማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ታሪካዊ ዳራን የሚዳስስ ጽሑፍ አቅርበዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ በክብር እንግዶች የዳቦና የኬክ ቆረሳ ስነስርዓት፣በግሽ ዓባይ የባህል ቡድን የተለያዩ ጡዕመ ዜማዎች የቀረቡ ሲሆን ከመድረክ ባሻገር የሴቶችን ጥንካሬ የሚያመላክቱ የተለዩ አኩሪ ተግባራትን በመስክ ጉብኝት መመልከት የተቻለ ሲሆን ዕለቱን ለመዘከር የዩኒቨርሲቲውን ስፖርት አካዳሚ ተማሪዎች ጨምሮ የሩጫ ውድድር ተካሂዷል፡፡
ሌላኛው የበዓሉ ድምቀት የሆነው የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዴኤታ ነቢያ መሀመድ፣የሴቶች ክንፍ ምክትል ፕሬዘዳንት ጦይባ ሀሰን እና በዶ/ር ሙሉነሽ አዋያይነት በሴቶች ምሁራን በቀረቡት ፅሁፍ መነሻነት ታዳሚው  የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን አቅርበው ለቀረቡት ጥያቄዎች ምላሽ ተሠጥቶባቸው ሰፊ ውይይት ተካሂዷል፡፡
         ሚኒስቴር ዴኤታዋ ነቢያ መሀመድ በማጠቃለያቸው አንድ አገር ልትለማም ልትፈርስም የምትችለው በምሁራኑ ምክንያት ስለሆነ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በመተባበር ሀገር በቀል እውቀቶችን በመጠቀም ሸልፍ የሚያሞቁ ሳይሆን መሬት የነካ ለማህበረሰቡ ጉልህ ፋይዳ ያለው የምርምር ውጤት በመስራት እጅ ለእጅ ተያይዘን የበለፀገች ኢትዮጲያን እንፍጠር የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የምርምር ውጤቶችን ወደ ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል ውይይት ተደረገ 
    
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስራ ፈጠራ ልማት እና ኢንኩቤሽን ማዕከል ከሳይንስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር
የፈጠራ የመጨረሻው መዳረሻ፦ ምርምርን ለገበያ ዝግጁ ማድረግ"The Last Mile of Innovation: Making Research Market-Ready” በሚል መሪ ቃል መረጃ የሰጠና የወደፊቱን አቅጣጫ የጠቆመ የውይይት መድረክ አካሄደ።

ይህ መድረክ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የሚሰሩ ምርምሮች በላቦራቶሪ እና በቤተ-መጻሕፍት ብቻ ተወስነው ሳይቀሩ፣ እንዴት ወደ ተጨባጭ የገበያ ምርቶች እና አገልግሎቶች ሊቀየሩ እንደሚችሉ አቅጣጫ አመላክቷል።


የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ የስራ ፈጠራ ልማት እና ኢንኩቤሽን ማዕከል ኃላፊ ሲሳይ ገረመው (PhD) እንደገለጹት፤ የውይይቱ ዋነኛ ዓላማ በዩኒቨርሲቲው ለረጅም ጊዜ ምርምር ሲያደርጉ የቆዩ ምሁራን ተሞክሯቸውን እንዲያካፍሉ እና ምርምርን ወደ ገንዘብ (Commercialization of knowledge) የመቀየር ሂደትን ማፋጠን ነው።

የሳይንስ ኮሌጅ ዲን ፕሮፌሰር ብርሃኑ አሳየ በበኩላቸው፣ በአካዳሚክ እውቀት እና በተግባራዊው ዓለም መካከል ያለውን ልዩነት ማጥበብ እንደሚገባ አሳስበዋል። "ምርምር የማህበረሰብን ችግር የሚፈታ እና ለሀገር ኢኮኖሚ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆን አለበት" ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ ይህ ሴሚናር እውቀትን ወደ እሴት ለመለወጥ ትልቅ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።

በዕለቱ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶክተር አማረ ካሳው ሰፊ ገለጻና ውይይት የመሩ ሲሆን፣ የምርምር ውጤቶችን ከገበያ ፍላጎት ጋር ማጣጣም (Aligning research with market needs)፣የገንዘብ ድጋፍ እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር ጥምረት መፍጠር (Funding and partnerships)፣የአእምሮአዊ ንብረት መብት (IP) እና የስታርት አፕ ድጋፎችን ማጠናከር እና ተመራማሪዎች የንግድ ስራ ክህሎት እና የስራ ፈጠራ አስተሳሰብ እንዲያዳብሩ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

የፕሮግራሙ ማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር እንየው አድጎ፣ የምርምር እውነተኛ ተፅዕኖ የሚለካው በሰው ልጅ ህይወት ላይ በሚያመጣው ለውጥ መሆኑን ገልጸዋል። "ምርምር ህይወትን ሲያሻሽል እና ምርታማነትን ሲጨምር ያኔ ወደ ፈጠራ (Innovation) ይቀየራል" በማለት ተመራማሪዎች ትኩረታቸውን ወደ ተጨባጭ መፍትሄዎች እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሙሉ የ4.00 ውጤት (perfect 4:00) ላስመዘገቡ 111 ተማሪዎች እውቅና እና ሽልማት ሰጠ

(ሚያዝያ 17/2018 ዓ.ም - ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ) ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማፍራት በሚያደርገው ጥረት፣ በዩኒቨርሲቲው ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ መንፈቀ ዓመት ሙሉ የ4.00 CGPA ውጤት ያስመዘገቡ 111 ተማሪዎችን የክብር ዕውቅናና ሽልማት ሰጥቷል። በዚህ ደመቅ ባለ መርሃ ግብር ላይ ከተሸለሙት ተማሪዎች መካከል 11ዱ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ ለተሸላሚዎቹ ባስተላለፉት ልዩ መልዕክት፣ ውጤቱ የአካዳሚክ ስኬት ብቻ ሳይሆን ራስን የማክበር መገለጫ መሆኑን ገልጸዋል። ተማሪዎቹ ይህንን ውጤታማ ልምድ አዳብረው እንዲቀጥሉ ያሳሰቡት ፕሬዝዳንቱ፣ ብቃትና ስኬት ለግለሰብ ብቻ ሳይሆን ለሀገርም ትልቅ ሀብት መሆኑን አስምረውበታል። አክለውም "ኢትዮጵያ የነገ የኖቤል ሎሬቶች ከእናንተ መካከል ትጠብቃለች" በማለት፣ ተማሪዎቹ በየተሰማሩበት የሙያ መስክ አገርን የሚያስጠሩ ባለሙያዎች እንዲሆኑ የሞራል ጥሪ አቅርበዋል።

የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር እሰይ ከበደ በበኩላቸው በእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸው እንደገለጹት፣ የዕውቅና መርሃ ግብሩ ዋነኛ ዓላማ ተማሪዎች ያላቸውን ዕውቀት ይዘው እንዲቀጥሉና ለበለጠ ትጋት እንዲነሳሱ ለማድረግ ነው። ይህ ታሪካዊ ውጤት በአመራሩና በተማሪዎች መካከል በተደረገ የተቀናጀ የቅርብ ክትትል የተመዘገበ መሆኑንም ፕሮፌሰሩ ጠቁመዋል። ምክትል ፕሬዚደንቱ አክለውም የተማሪዎቹ ስኬት ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለትምህርት ጥራት እና አካዳሚያዊ ልሕቀት ለሚሰጠው ትኩረት ማዕከል መሆኑን ገልጸው፣ ውጤቱ በተለያዩ ፈተናዎች፣ አለመረጋጋቶችና ግጭቶች መካከል ሆኖ የተገኘ፣ በዲሲፕሊን የታጀበ ጥናት፣ የጠንካራ ቁርጠኝነትና የማያቋርጥ ጥረት ውጤት መሆኑን አስገንዝበዋል። "ይህንን ስኬት በድንገት ያገኛችሁት ሳይሆን በመስዋዕትነት፣ በጽናትና በዓላማችሁ ላይ በማተኮር ያመጣችሁት ነው" ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ ውጤቱ ተማሪዎች ቁርጠኛ ከሆኑ የላቀ የትምህርት ስኬት ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ መሆኑን ገልጸው እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል። የቤተሰቦቻቸው ድጋፍ፣ ማበረታቻና ምክር በትምህርት ጉዟቸው ወቅት ተነሳሽነትን፣ ዲሲፕሊንን እና በራስ መተማመንን እንድታዳብሩ ትልቅ እገዛ ማድረጉንም አድናቆታቸውን ችረዋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ የተማሪዎች ህብረት ምክትል ፕሬዝዳንት ተማሪ ብርሃነመስቀል የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፈ ሲሆን፣ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው በሳይንሳዊ ምርምር እንዲሳተፉ የሚያግዙ አዳዲስ ፕሮጀክቶች መጀመራቸውን ገልጾ፤ ዕውቀትና መሪነት አብረው የሚሄዱ በመሆናቸው አገርና ሕዝብን የማስከበር ኃላፊነት ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስቧል። ከተሸላሚዎች መካከል አስተያየቷን የሰጠችው የሁለተኛ ዓመት የሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ተማሪ በለጡ ደረስ፣ የተሰጣት ዕውቅና ውጤቷን ለማስቀጠል ትልቅ ጉልበት እንደሚሆናት ገልጻለች። ተማሪዋ አክላም የላቀ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች በጋራ ተሰባስበው ዕውቀትና ልምድ የሚለዋወጡበት ምቹ ሁኔታ ቢፈጠር ያላቸውን አቅም ይበልጥ እንደሚያሳድገው ጠቁማለች።

"ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ" በሚለው መሪ ቃሉ የሚታወቀው ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ በአሁኑ ወቅት በዘጠኝ ግቢዎችና በ18 የአካዳሚክ ክፍሎች ከ26,000 በላይ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው በአፍሪካ ቀዳሚ የምርምር ተቋም ለመሆን በሚያደርገው ጉዞ ውስጥ እንዲህ ያሉ የላቀ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑ በዕለቱ ተገልጿል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

6ኛው ዓለም አቀፍ የጤና ምርምር ኮንፈረንስ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በድምቀት ተካሄደ
ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ፤ [ሚያዚያ 15/2018 ዓ.ም]
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 6ኛውን ዓለም አቀፍ የጤና ምርምር ኮንፈረንስ በዩኒቨርሲቲው  ጥበብ ህንፃ አዳራሽ በታላቅ ድምቀት አስጀመረ።
ኮንፈረንሱ በዘርፉ ያሉትን ወቅታዊ የጤና ችግሮች በመለየት፣ በሳይንሳዊ ጥናት የተደገፉ መፍትሄዎችን በማፍለቅ እና የባለሙያዎችን የዓመታት ተሞክሮ በመለዋወጥ ረገድ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ታምኖበታል። በስነ-ስርዓቱ ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ ከተለያየዩ ዓለም አቀፍና የሀገራችን ክፍሎች የመጡ ምሁራን፣ ተመራማሪዎች፣ የአማራ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለሙያዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በመክፈቻው መርሃ ግብሩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር በቃሉ ዉበሸት፣ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የጤናው ዘርፍ በውስጣዊና ውጫዊ ተግዳሮቶች ውስጥ ሆኖም አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገቡን ገልጸዋል።
በተለይም የእናቶችና የህፃናትን ሞት በመቀነስ ረገድ የተመዘገበው ስኬት ተቋሙ ለኅብረተሰቡ ያለው የላቀ አስተዋጽኦ ማሳያ መሆኑን አንስተዋል። "የህክምና ሳይንስን ከምርምር ጋር አቀናጅተን በመስራታችን፣ የማህበረሰብ አገልግሎታችንን ወደ ተሻለ ደረጃ ማድረስ ችለናል፤ ይህ ኮንፈረንስም ይህንኑ ተሞክሮ ለማስቀጠል ትልቅ አጋጣሚ ነው" ብለዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ በበኩላቸው፣ ዩኒቨርሲቲው በአገራችን ከሚገኙ የጥናትና ምርምር ማዕከላት መካከል ግንባር ቀደም መሆኑን አስታውሰዋል። ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለክልሉ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ለሀገር አቀፍ የህክምና አገልግሎት ያለውን ፋይዳ በመጠቆም፣ ኮንፈረንሱ እንዲሁ የውይይት መድረክ ብቻ ሳይሆን ሳይንሳዊ ግኝቶች የሚቀመጡበት መድረክ መሆኑን አስገንዝበዋል።
"ይህ መድረክ የኅብረተሰባችንን የጤና ችግሮች ለመቅረፍ የሚረዱ፣ በምርምር የተረጋገጡ ሳይንሳዊ መፍትሄዎችን በማፍለቅ ፖሊሲ አውጪዎችና የጤና ባለሙያዎች የሚመሩበትን አቅጣጫ ይጠቁማል" ሲሉም አክለዋል።

የአማራ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ፣ በበኩላቸው የኢንስቲትዩቱንና የዩኒቨርሲቲውን የትብብር ስራ አድንቀዋል። በጤናው ዘርፍ ውጤታማ ለመሆን ተቋማዊ ትብብር ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ኮንፈረንሱ በጤናው ዘርፍ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት እና የህዝብ ጤና ችግሮችን ለመፍታት የሚኖረው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

በዛሬው ዕለት በተካሄደው የውይይት መድረክ፡-በጤናው ዘርፍ የተሰሩ አዳዲስ ዓለም አቀፍና አገር በቀል ምርምሮች፣ከምርምር የተገኙ ውጤቶች ወደ ተግባር የሚለወጡበት  እንዲሁም በተመራማሪዎችና በተግባር አራማጆች መካከል የልምድ ልውውጥ የተካሄደበት ሲሆን ይህ መድረክ በአካዳሚክ ማህበረሰቡ እና በጤና ባለሙያዎች መካከል የዕውቀት ሽግግር በማድረግ፣ በማስረጃ የተደገፈ የጤና አሰራርን (Evidence-based practice) በስፋት ለማስረጽ ትልቅ ፋይዳ አለው ተብሏል።
ኮንፈረንሱ ነገም ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን፣ የጤናው ዘርፍ ባለሙያዎች የነገውን የጤና ስርዓት ለመቅረጽ የሚያስችሉ ሀሳቦችን እንደሚያንሸራሽሩ ይጠበቃል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ልማት ማህበር (ECDD) አካል ጉዳተኞችን በዘላቂነት ለመደገፍ የሚያስችል የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ሚያዝያ 14/2018 ዓ.ም)
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከአገር በቀሉ የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ልማት ማህበር (Ethiopian Center for Disability and Development/ECDD) ጋር ለአካል ጉዳተኞች የገንዘብ፣ የሙያ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ፣ የዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሉጎጃም ወንዲፍራው፣ የECDD ፕሮግራም ዳይሬክተር አቶ ለጋሱ ልዑልሰገድ እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን በመቀበልና ምቹ የመማር ማስተማር ሁኔታን በመፍጠር ረጅም ልምድ ያለው ተቋም እንደሆነ ግልጸው ECDD እኛን አምኖ ይህን ትልቅ ኃላፊነት በመስጠቱ እናመሰግናለን ብለዋል ዶ/ር መንገሻ፡፡ አክለውም ስምምነቱ ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን በክልሉ ለሚገኙ አካል ጉዳተኞች ሁሉ ተስፋ የሚሰጥ ነው ብለዋል።
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን የመረጥነው በአካል ጉዳተኞች ጉዳይ ላይ ከፍተኛ ግንዛቤ ያላቸው ምሁራን ስላሉት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ተቋም በመሆኑና ለምናከናውናቸው የሥልጠናና የጥናት ሥራዎች የዩኒቨርሲቲውን ምሁራን ለመጠቀም እንደሆነ የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ልማት ማህበር ፕሮግራም ዳይሬክተር አቶ ለጋሱ ልዑልሰገድ ገልጸዋል። ዳይሬክተሩ አክለውም ለዚህ ታላቅ ተቋም የራሳችንን ጠብታ አስተዋፅዖ ማበርከታቸው ትልቅ ኩራት እንደሚሰማቸውና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡

ስምምነትቱ በተለይ በአካል ጉዳተኞች ዙሪያ የሚሰሩ ሥራዎችን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ያለመ ሲሆን፣ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አካቷል፦ አካል ጉዳተኞች አስፈላጊውን መረጃና ድጋፍ የሚያገኙበት ማዕከል በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ማቋቋም፣አካል ጉዳተኞችን ያካተተ የጤና አገልግሎት እና የኑሮ ማሻሻያ (Livelihood) ሥራዎች ላይ በትኩረት መሥራት፣ አካል ጉዳተኞች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ ትምህርትና ሥልጠና እንዲያገኙ ማስቻል እና በዩኒቨርሲቲው የሚገኙ ምሁራን ያላቸውን ዕውቀት በመጠቀም ለአካል ጉዳተኞችና ለባለሙያዎች ሥልጠና መስጠትን የሚያካትት እንደሆነ በመርሃ ግብሩ ላይ ተገልጿል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ንጹህ ሀሳብ (Positive / Clean thinking) መያዝ
@necktop3
@necktop3
👍ነገሮችን በግልጽና በጥንቃቄ ማየት ያስችላል
👍ሰላምና ደስታ ያመጣል
👍ውስጣዊ ሰላምና ደስታ ይጨምራል
👍ከሰዎች ጋር በፍቅርና በክብር ያስኖራል
👍ስኬትን ይደግፋል
👍ጤናን ይጠብቃል
👍ጭንቀትን ይቀንሳል
👍ራስን መቆጣጠር ያስችላል
👍ሰው ስሜቱን እንዲቆጣጠር ይረዳል
ንጹህ ሀሳብ ለመልካም ሕይወት፣ ለስኬት እና ለሰላም መሠረት ነው!

@necktop3
@necktop3
contact @seen311
        SHARE

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለሴት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች የህይወት ክህሎት ስልጠና ሰጠ።
ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ፦ ሚያዚያ 01/2018 ዓ.ም
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ከ ፀሐይ መታሰቢያ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በዩኒቨርሲቲው ለሚገኙ ሴት አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች  የህይወት ክህሎት የስልጠና መርሀግብርከመጋቢት 29-30/2018 ዓ.ም አካሂዷል።

በስልጠናው መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሙሉጎጃም ወንድይፍራው (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በአገሪቱ ውስጥ አካታች የትምህርት ስርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ግንባር ቀደም ተቋም መሆኑና ዩኒቨርሲቲው አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች በትምህርታቸው ስኬታማ እንዲሆኑና በተለያዩ ማህበራዊና ስነ-ልቦናዊ ጫናዎች ምክንያት ወደ ኋላ እንዳይቀሩ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ዳይሬክተሯ አክለውም፦ከዚህ ቀደም ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር የቁሳቁስ እና የገንዘብ ድጋፎች ሲደረጉ መቆየታቸውን፤ከኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ማህበር ጋር በመተባበር በግቢው ውስጥ ያሉ መሰረተ ልማቶች ለአካል ጉዳተኞች ምቹ እንዲሆኑ መደረጉንና አሁን እየተሰጠ ያለው ስልጠና ደግሞ ተማሪዎቹ በራስ መተማመናቸው እንዲጎለብትና ካደጉበት ማህበረሰብም ሆነ ከራሳቸው የሚመጡ ተጽዕኖዎችን አሸንፈው እንዲወጡ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል።

ስልጠናውን እየሰጡ የሚገኙት የብሩህ ዜጋ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ዳይሬክተር አቶ እስክንድር ካሳ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ምንም እንኳ አሁን ላይ ትኩረቱን አይነ ስውራን ተማሪዎች ላይ ቢያደርግም፣ ይዘቱ ግን ማንኛውም ሰው ተፈጥሯዊ ማንነቱን ተጠቅሞ በህይወቱ የሚያጋጥሙትን ፈተናዎች በውስጣዊ ጥበብ እንዲፈታ የሚያስችል ነው ብለዋል።
"ተማሪዎቹ ያሉባቸውን ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች በፀጋ እንዲቀበሉ፣ ጠንካራ የሰብእና እንዲኖራቸው እና ለማንኛውም ውጫዊ ፈተና የማይበገሩ እንዲሆኑ ለማድረግ እየሰራን ነው" ሲሉ አቶ እስክንድር ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲው በቀጣይም በተማሪዎች ዘንድ የሚታዩ የክህሎት ክፍተቶችን በመለየት መሰል ስልጠናዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል። ይህ ስልጠና ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ ከምረቃ በኋላም በህይወታቸው ስኬታማ ዜጋ እንዲሆኑ መሰረት የሚጥል መሆኑ ታምኖበታል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Study in Japan Opportunity: MEXT Scholarship Briefing (2027 Intake)

Bahir Dar University, in collaboration with the Embassy of Japan in Ethiopia, invites all students to attend an online briefing session on the prestigious Japanese Government (MEXT) Scholarship 2027.

This scholarship, offered by the Government of Japan through MEXT, supports outstanding international students to pursue undergraduate and graduate studies at leading universities in Japan.

Date: 28 April 2026
Time: 3:30 PM – 4:30 PM
Venue: Online

The session will provide:
Clear guidance on the application process
Practical tips for applying
Insights into studying and living in Japan

Students from all faculties and colleges are highly encouraged to attend!

👉 Register here: https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdXkv2gxHtdXVNWbk6rKVLMt9Fmt4HFnaKWxbvckB0dH_sIMQ/viewform?usp=publish-editor

Don’t miss this valuable opportunity to take your academic journey global!

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Call for Poly-BDU Alumni Association Meeting!

ለመላው የቀድሞ ፖሊ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ምሩቃን በሙሉ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30ጀምሮ መካኒሳ በሚገኘው በብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ አዳራሽ አጠቃላይ ዓመታዊ ስብሰባ ስለሚደረግ ማንኛውም የቀድሞ ምሩቅ በስብሰባው ላይ እንዲገኝ ጥሪያችንን እያቀረብን ስብሰባውን ከነ ሙሉ ወጪው Sponser ያደረገን ብሔራዊ አልኮል ለምሳ ግብዣው ዝግጅት እንዲረዳው የሚገኙትን የሰው ቁጥር ከወዲሁ ስለጠየቀን ስብሰባው ላይ የምትገኙ  "እኔ እገኛለሁ" የሚል መልዕክት በመላክ አረጋግጡልን::

Calll +251911636363

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

#ማስታወቂያ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ/ጥበበ ግዮን ስፒሻላይዝድ ሆስፒታል  መደበኛ አገልግሎቱን በላቀ ደረጃ እየሰጠ ይገኛል።

ለሰራተኞች የሚሰጠው የትራንስፖርት አገልግሎትም የሚቀጥል ሆኖ  ኮሌጁ ሲሰጠው የነበረውን የትራንስፖርት አገልግሎት እንዳቋረጠ ተደርጎ በተያለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ የሚዘዋወረው ደብዳቤ ከኮሌጁ እውቅና ውጭ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቤተሰባዊ ትስስር መርሃ-ግብር መመዝገቢያ ቅጽ 
ውድ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች:-

ዩኒቨርሲቲያችን በ 2011 ዓ.ም ጀምሮት የነበረውና በአሁኑ ወቅት በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በተለያየ ስያሜ ተስፋፍቶ በመተግበር ላይ የሚገኘውን “የባሕር ዳር እንደ-ቤቴ” ቤተሰባዊ ትስስር መርሃ-ግብር ተማሪዎቻችን ከከተማችን ማህበረሰብ ጋር ጥብቅ ወዳጅነት እንዲመሰርቱ እና የዩኒቨርሲቲው አምባሳደር እንዲሆኑ የሚያስችል ተግባራዊ ጽንሰ-ሀሳብ ነው።
በመርሃ-ግብሩ ውስጥ ራቅ ካሉ የአገራችን ክፍሎች የሚመጡ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው በሚኖራቸው ቆይታ ወቅት ቤተሰባዊ ትስስር በመፍጠር በትምህርታቸው እንዲበረቱ፣ ስነ-ልቦናዊ ጫናዎችንና አቻ ግፊቶችን እንዲቋቋሙ እና ባህልና እሴቶቻቸውን እንዲያስተዋውቁ እድል ይፈጥርላቸዋል።
እርስዎም የቃል ኪዳን ወላጅ በመሆን በተማሪዎች ሕይወት ውስጥ አይረሴ አስተዋጾ በማበርከት ትርጉምና ደስታን ያግኙ!

የመርሃ-ግብሩ ተሳታፊ ለመሆን መልካም ፈቃድዎ ከሆነ እባክዎን ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ቅጹን ይሙሉ::

https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfZQMNXEa-xLpr5ENqYvzUJ7UQs1LOKntpLcITHiKKNONPGTA/viewform

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Training on Stress and Trauma Management Given for Journalists

Bahir Dar University, in partnership with the Fojo Media Institute, successfully conducted a three-day stress and trauma management training in Bahir Dar town for mid-career journalists.

The training brought together professionals from Amhara Media Corporation and BDU Community Radio Station, with a strong representation of 15 dedicated female journalists.

This important initiative is part of a broader project supported by UNESCO’s International Programme for the Development of Communication (IPDC), which is also being implemented in Rwanda and Somalia.

By equipping journalists with tools to manage stress and trauma, the program helps strengthen resilient, ethical, and impactful media professionals.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለሴት ተመራማሪዎች የ"Grant Proposal Writing" ስልጠና መሰጠት ተጀመረ
ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ (መጋቢት 12/2018 ዓ.ም)

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈጻሚ በዩኒቨርሲቲው ለሚገኙ 42 ሴት የፒ.ኤች.ዲ (PhD) ተመራማሪዎች ለስድስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የፈንድ ማሰባሰቢያ የጥናት ፕሮፖዛል ጽሑፍ (Grant Proposal Writing) ስልጠና መስጠት ጀመረ።

የስልጠናውን መርሃ-ግብር በንግግር የከፈቱት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር እንየው አድጎ ሲሆኑ ዩኒቨርሲቲው በሴት የፒ.ኤች.ዲ ምሁራን ብዛት ቀዳሚ በመሆኑ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። ሴት ተመራማሪዎችን ማብቃት "ሴት-ነክ" የሆኑ ችግሮች በራሳቸው በሴቶች እንዲፈቱ ከማድረጉም በላይ፣ ሴቶች በስራቸው ላይ ያላቸውን ታማኝነትና የሀብት አጠቃቀም ብቃት ለምርምር ውጤታማነት ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው አጽንኦት ሰጥተዋል።
"የሴቶች የምርምር ፈንድ መቋቋሙ ተመራማሪዎቹ የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱ የምርምር ስራዎችን እንዲሰሩና የመፍትሔ ሃሳብ እንዲያቀርቡ ያግዛል" ያሉት ፕሮፌሰር እንየው፤ ስልጠናው ተመራማሪዎቹ ከአገር ውስጥ ባለፈ ከትላልቅ ዓለም አቀፍ የፕሮጀክት አጋሮች ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥርላቸውም ጠቁመዋል።
የሴት ተመራማሪዎች ማህበር የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቻፕተር ፕሬዝዳንት ዶክተር እሌኒ አድማሱ በበኩላቸው፤ ስልጠናው ተወዳዳሪ የሆኑ የፕሮጀክት ጽሑፎችን በማዘጋጀት ፈንድ (Fund) ማግኘት የሚቻልባቸውን ጥበቦች ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸዋል። ዶክተር እሌኒ አክለውም፦ፕሮጀክቶችን እንዴት መጻፍ እንደሚቻል፣ከሌሎች ተማሪማሪዎች ጋር ተወዳድሮ አሸናፊ መሆን የሚቻልባቸው ስልቶች፤የበጀት አጠቃቀምና አስተዳደር እና ሌሎች ተያያዥ የአቅም ግንባታ ጉዳዮች በስልጠናው እንደሚሸፈኑ አስረድተዋል። ይህንን ከፍተኛ ጥራት ያለው ስልጠና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጡ አንጋፋ ምሁራን ማለትም በፕሮፌሰር ያለምጸሀይ መኮንን፣ በዶክተር ሉሊት ጥላሁን እና በዶክተር ትዕግስት ታደሰ እየተሰጠ ይገኛል።
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሴት ተመራማሪዎችን ተሳትፎ በማሳደግ እና የምርምር ባህልን በማዳበር የላቀ የትምህርትና የምርምር ተቋም የመሆን ራዕዩን አጠናክሮ ይቀጥላል።


Bahir Dar University Launches Grant Proposal Writing Training for Female Researchers
Bahir Dar University (March 19, 2026)
The Institutional Change Office at Bahir Dar University has launched a six-day training program on grant proposal writing for 42 female PhD researchers.
Opening the program, the University’s Vice President for Research and Community Service, Professor Enyew Adgo, expressed his satisfaction that the university is leading in the number of female PhD scholars. He emphasized that empowering female researchers not only enables women to address gender-based challenges independently, but also enhances the overall effectiveness of research through their integrity and efficient use of resources.
“The establishment of the Women’s Research Fund will support researchers in conducting studies that address societal problems and generate practical solutions,” said Professor Enyew. He also noted that the training would enable participants to engage with major international research partners, both domestically and globally.
Dr. Eleni Admasu, President of the Bahir Dar University Chapter of the Association of Women Researchers, stated that the training focuses on equipping participants with the skills and knowledge required to secure funding through competitive project proposals. She added that the program covers key areas such as proposal writing, strategies for successful competition, budget management, and other capacity-building components.
The training is being delivered by senior scholars from Addis Ababa University, including Professor Yalemtsehay Mekonnen, Dr. Lulit Tilahun, and Dr. Tigist Tadesse.
Bahir Dar University continues to advance its vision of becoming a leading institution in education and research by promoting the participation of female researchers and strengthening its research culture.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Invitation to a lecture

We are pleased to announce a special event featuring the renowned playwright, poet, actor, and director Getnet Eneyew.

He will be joining us to share insights drawn from his extensive experience in the world of art.
We warmly invite you to attend and benefit from this enriching event.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ለአካል ብቃት አሰልጣኞች የክህሎት ማሳደጊያ ስልጠና ሰጠ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፤ መጋቢት 02/2018 ዓ.ም
የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ በባሕር ዳር ከተማ ለሚገኙ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አሰልጣኞች የሙያ ክህሎታቸውን ለማሳደግና ሳይንሳዊ አሰራርን ለማስረፅ የተዘጋጀ ስልጠና በዩኒቨርሲቲው የቀድሞው ሴኔት አዳራሽ ሰጥቷል።
ስልጠናው በዋናነት አሰልጣኞች ለማህበረሰቡ የሚሰጡትን የአካል ብቃት አገልግሎት ይበልጥ ውጤታማ እና ደህንነቱ የተጠበቀ እንዲሆን ለማስቻል ያለመ ነው።

የስፖርት አካዳሚው ዲን አቶ ሲሳይ አዱኛ  ስልጠናውን ሲከፍቱ እንደገለጹት፣ ይህ መርሃ-ግብር በማህበረሰቡ ውስጥ የአካል ብቃት ባህልን ለማጠናከር እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል ትልቅ ሚና ይጫወታል። አክለውም ስልጠናው በሦስት ዙር የሚሰጥ ሲሆን፣ በሁሉም ክፍለ-ጊዜዎች ተገኝተው ብቃታቸውን ላረጋገጡ አሰልጣኞች የዕውቅና የምስክር ወረቀት እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
የአካዳሚው መምህር ዘመኑ ተሾመ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ አሰልጣኞች ሳይንስንና የአመጋገብ ስርዓትን መሰረት አድርገው በመስራት ጤናማና አምራች ዜጋን ለመቅረጽ በትጋት መንቀሳቀስ እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

ስልጠናው በሁለት ዋና ዋና ምዕራፎች ተከፍሎ የቀረበ ሲሆን፣ ሰልጣኞች በንድፈ-ሃሳብና በተግባር የታገዘ ግንዛቤ አግኝተዋል።
አሰልጣኝ ደጀኔ ብዙነህ ውጤታማ የአካል ብቃት ስልጠና ሊከተላቸው የሚገቡ ሰባት ወርቃማ መርሆችን በዝርዝር አቅርበዋል፦ እነርሱም ማሟሟቂያና ማቀዝቀዣ (Warming up & Cooling down): ጉዳትን ለመከላከልና ሰውነትን ለማዘጋጀት፣ልዩነት/እንቅስቃሴን መወሰን (Specificity): እንደ ግቡ አይነት የሚመረጥ ልምምድ፣ተከታታይነት ያለው ጫና (Progressive Overload): በሂደት የልምምድ መጠንን መጨመር፣ወደ ነበረበት መመለስ (Reversibility): ልምምድ ሲቋረጥ የሚከሰት የብቃት መቀነስ፣ተለዋዋጭነት (Variability): መሰላቸትን ለመከላከልና ሁሉንም የሰውነት ክፍል ለማሳተፍ፣ግላዊነት (Individuality): እንደ እያንዳንዱ ሰው አቅምና ፍላጎት ልምምድን ማዘጋጀት እንዲሁም እረፍትና ማገገሚያ (Rest & Recovery): የሰውነት ጡንቻዎች እንዲገነቡና ኃይል እንዲያገኙ የሚያደርጉ መርሆዎች መሆናቸውን አሰልጣኙ ገልጸዋል።
የስርዓተ-ምግብ መምህሩ ዳንኤል ክብረት (ዶ/ር) አመጋገብና እንቅስቃሴን የማይነጣጠሉ መሆናቸውን አብራርተዋል። "ያለ ትክክለኛ አመጋገብ የሚደረግ እንቅስቃሴም ሆነ ያለ እንቅስቃሴ የሚደረግ አመጋገብ የተሟላ ጤናን ሊያመጡ አይችሉም" ያሉት መምህሩ፣ ካርቦሃይድሬት፣ ፕሮቲንና ቫይታሚኖችን አመጣጥኖ መውሰድ ለተሻለ ውጤት ቁልፍ መሆኑን ጠቁመዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Call for Abstracts
School of Veterinary Medicine

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ትላንት የተገኘ ድል፤ ለዛሬ ስንቅ!”፦ 130ኛው የአድዋ ድል በዓል በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በድምቀት ተከበረ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የጥቁር ሕዝቦች ኩራት እና የነፃነት ተምሳሌት የሆነውን 130ኛውን የአድዋ ድል በዓል፣ የአባት አርበኞች፣ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ መምህራን፣ የአስተዳድር ሰራተኞችና ተማሪዎች በተገኙበት በታላቁ የጥበብ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።

የዩኒቨርሲቲው የኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሙኒኬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ዘውዱ እምሩ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ሲያስተላልፉ፤ አድዋ የኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን የመላው ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ቀን መሆኑን ገልጸዋል። "አባቶቻችን በዘመናዊ መሣሪያ የታጠቀውን ወራሪ ኃይል በጀግንነትና በአንድነት ድል በማድረግ የነፃነትን ችቦ አቀብለውናል፤ ይህ ታሪክ ለትውልድ የሚተላለፍ የማይደበዝዝ አኩሪ አሻራችን ነው" ብለዋል።


የጥንታዊት ኢትዮጵያ አባት አርበኞች ማህበር ሊቀመንበር አቶ ዳኝነት አያሌው፣ ዩኒቨርሲቲው ለአርበኞች ለሚሰጠው ክብርና እንክብካቤ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አክለውም ታሪክን ለትውልድ ለማጋራት "የታሪክ ክበባት" እንዲጠናከሩና ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ የታሪክ ትምህርት ትኩረት እንዲሰጠው ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። አዳራሹም በአርበኞች ፉከራ እና ሽለላ ደምቆ ውሏል።

የበዓሉን ታሪካዊ፣ ፖለቲካዊና ባህላዊ ፋይዳ የሚያትት ሰፊ የፓናል ውይይት በዶ/ር ገረመው እስከዚያ፦ የታሪክ ድርሳናትን ዋቢ በማድረግ የአድዋን ድል አመጣጥ፤በአቶ ወርቅነህ ገነት፦ ድሉ በፖለቲካዊ ዲፕሎማሲ ረገድ የፈጠረውን ተፅዕኖና በዶ/ር ሞገስ ሚካኤል፦ አድዋ በቋንቋ እና በባህል ግንባታ ላይ ያለውን ሚና በተመለከተ ሙያዊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የሲኒማና ቴአትር ጥበባት ተማሪዎች በአድዋ ጦርነት ዙሪያ የሚያጠነጥን አጭር ድራማ ያቀረቡ ሲሆን፣ በተማሪዎች የቀረቡ ግጥሞችና የባህል ማዕከል የሙዚቃ ቡድን ዝግጅቶች ለበዓሉ ልዩ ድምቀት ሰጥተውታል።
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአባቶቻችን ታሪክ በመዘከርና ለትውልድ በማስተላለፍ ረገድ የበኩሉን ስራ አጠናክሮ ይቀጥላል።

Читать полностью…
Subscribe to a channel