bahir_dar_university | Unsorted

Telegram-канал bahir_dar_university - Bahir Dar University,Ethiopia

21305

It is a channel about Bahir Dar University all Campuses! www.bdu.edu.et

Subscribe to a channel

Bahir Dar University,Ethiopia

“የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ልምድ ለIFMIS ትግበራ ስኬት መሠረት ነው”
ዶ/ር መንገሻ አየነ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የፋይናንስ አስተዳደሩን ይበልጥ ግልጽ፣ ቀልጣፋ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት ለማድረግ የሚያስችለውን የተቀናጀ የፋይናንስ አስተዳደር መረጃ ሥርዓት (IFMIS) በይፋ መተግበር ጀመረ። በዩኒቨርሲቲው የፕሬዝዳንት መሰብሰቢያ አዳራሽ በተከናወነው የሲስተም ማስተዋወቂያ መርሃ ግብር ላይ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲው በቴክኖሎጂ ልማትና አጠቃቀም ረገድ የካበተ ልምድ ያለው ተቋም ነው። ዶ/ር መንገሻ አየነ ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ቀደም ለራሱም ሆነ ለሌሎች ተቋማት ዘመናዊ ሲስተሞችን በማልማት ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህ የዳበረ ልምድ አዲሱ የIFMIS ሥርዓት በስኬት እንዲተገበር ትልቅ አቅም እንደሚሆን አረጋግጠዋል።

በፋይናንስ ሚኒስቴር አማካኝነት የቀረበውና በዩኒቨርሲቲው ስራ የጀመረው ይህ ዘመናዊ አሰራር በጀት፣ ግዥ፣ ክፍያ፣ ሂሳብ አያያዝ እና ሪፖርትን ጨምሮ ሁሉንም የመንግስት የፋይናንስ ስራዎች በአንድ የኮምፒውተር መረብ የሚያገናኝ ነው።
የፋይናንስ ሚኒስቴር የቡድን መሪና የክንውን አማካሪ ወ/ት እመቤት መኮነን በበኩላቸው ሲስተሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን የፋይናንስ አስተዳደር ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ገልጸዋል።

ይህ የማስተዋወቅ ስራ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መከናወኑ ሲስተሙ በቀጣይ በሌሎች 43 የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ለሚኖረው ትግበራ እንደ መነሻና ትልቅ ተሞክሮ የሚወሰድ ነው።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ፕሬስ የህትመት ውጤቶች በአውደ ርዕይው ትኩረት ስበዋል
የባሕር ዳር ከተማ ባህልና ቱሪዝም መመሪያ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ከተማ አቀፍ የመጻሕፍት ዐውደ ርዕይ አዘጋጅቷል። በዚህ ዐውደ ርዕይ ከስምንት በላይ የሚኾኑ የመጻሕፍት መሸጫ መደብሮችም ተሳተፈዋል። ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬስም አንዱ ነው። የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ፕሬስ የሽያጭ ባለሙያ አቶ ግስሜ ይችላልም በቅርቡ በፕሬሱ የታተመውን የዐፄ ዘርዐ ያዕቆብን ዜና መዋዕል ይዘው የተገኙ ሲሆን በግማሽ ቀን ውስጥ ብዙ ሽያጭ እንዳከናወኑና መጽሐፉም የአንባቢያን ትኩረት የሳበ መኾኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በፕሬሱ የአርትዖት ሥራቸው ተጠናቆ በህትመት ሂደት ላይ የሚገኙ ሥራዎችን ማለትም የዐፄ ኢያሱ ቀዳማዊ ዜና መዋዕል (አድያም ሰገድ)፣ የዐፄ ምኒልክ ዜና መዋዕል፣ Compendium of Medicinal Plants of Ethiopia Vol. I እና ዘረኝነትና ሳይንስ በአውደ ርዕዩ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ ለተገኙ ታዳሚዎችና የሚዲያ አካላት በሰፊው የማስተዋወቅ ሥራ ተሰርቷል።
ቦታ፦ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ዋና በር አጠገብ፣ ወደ ጣና ሐይቅ መግቢያ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

መልካም የገና በዓል!

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Bahir Dar University Hosts High-Level Strategic Dialogue with Ministries and Embassies on Internationalization

Bahir Dar, Ethiopia
January 1, 2026

Bahir Dar University convened a high-level Strategic Meeting with Representatives of Ministries and Embassies on Thursday, January 1, 2026, bringing together senior government officials, diplomats, and university leaders to deliberate on strengthening international cooperation in higher education.

The strategic dialogue formed part of the University’s broader efforts to advance its internationalization agenda as it continues its transformation toward becoming a research-intensive and internationally engaged autonomous institution.

The meeting was officially opened by Dr. Mengesha Ayene, President of Bahir Dar University, who warmly welcomed participants and underscored the importance of sustained collaboration between universities, government institutions, and diplomatic missions in positioning Ethiopian higher education within the global academic ecosystem.

Following the opening and participant introductions, Dr. Manendante Mulugeta Seyoum, Director of External Relations and Partnership, presented “BDU in Brief: Internationalization in Focus.” The presentation highlighted the university’s key achievements in international engagement, its growing international student and staff profile, and its strategic priorities, including mobility expansion, joint academic programs, and enhanced international student support services.

The session on Stakeholder Perspectives provided a valuable platform for representatives from the Ministry of Foreign Affairs, Ministry of Education, and Embassies to share insights on existing opportunities, emerging challenges, and concrete areas for collaboration.

Notably, Ambassador Nebiyu Tedla, Minister Delegate and Director General of Public Diplomacy at the Ministry of Foreign Affairs, and Ambassador Roza Yerukneh, Deputy Director General of Public Diplomacy, emphasized the role of public diplomacy and education as key instruments for strengthening Ethiopia’s international relations. Contributions from the Ministry of Education further enriched the discussion by highlighting practical cooperation mechanisms in scholarship access, academic exchanges, and student support.

Participants acknowledged that effective internationalization requires not only academic partnerships but also coordinated policy support, facilitation mechanisms, and shared responsibility among stakeholders.

The meeting concluded with an agreement on clear follow-up mechanisms, including continued dialogue, coordination through designated focal points, and joint exploration of actionable initiatives.

The strategic meeting reaffirmed Bahir Dar University’s position as a trusted partner in international education and demonstrated the strong commitment of government institutions and diplomatic missions to advancing Ethiopia’s global academic engagement through collaboration, mobility, and shared vision.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

A New Year of Renewal and Partnership

Around the world, New Year invites reflection, hope, and fresh ambition.

As calendars turn, Bahir Dar University continues its journey of connecting cultures, advancing knowledge, and strengthening international partnerships through education, research, and innovation.

Here’s to a New Year filled with collaboration, shared purpose, and global impact.

Happy New Year from Bahir Dar University, from Ethiopia to the world.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከIUC ፕሮጀክት በተገኘ ድጋፍ በቢዝነስና  ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ቤተ መጻሕፍት ውስጥ የመጀመሪያ የሆነውን Digital Research Lab ስራ አስጀመረ።
    መርሐ ግብሩን መርቀው የከፈቱት የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር እሰይ ከበደ እና የምርምር እና ማህበረሰብ ተሳትፎ ምክትል ፕሬዝዳንት እንዲሁም የIUC ፕሮጀክት አስተባባሪ ፕሮፌሰር እንየው አድጎ ሲሆኑ፡ ለእንግዶች የእንኳን ደህና  መጣችሁ እና የፕሮግራም ገለጻ ያደረጉት የፕሮጀክቱ ማናጀር ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራው ናቸው። ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራውን ተከትሎ ስለ Digital Research Lab ገለጻ ያደረጉት የሳይንስ እና ማሪታይም የአይ ሲቲ መሰረተ ልማትና አገልግሎት ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ውብሸት ስመኘው እንደገለፁት  ለአገልግሎት ዝግጁ የሆኑት 70 ዘመናዊ (High Tech Computing) ኮምፒውተሮች ከቤልጅየም ሃገር በፕሮጀክቱ ተገዝተው የመጡና ከአሁን  በፊት ከነበሩት ኮምፒውተሮች በጣም ፈጣን እና የራሳቸው WiFi supported እንዲሁም 32 RAM ያላቸው  መሆናቸውን ገልጸዋል ። ይህ ዘመናዊ ዲጂታል የምርምር ቤተሙክራ ከፍተኛ አቅም ስላለው ሁሉም የዩኒቨርሲቲው መምህራንና የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች በስፋት እንዲጠቀሙበት ያሳሰቡ ሲሆን ስለ አጠቃቀሙም አስተዳደራዊ ስርዓት እንደሚበጀለት አስገንዝበዋል፡፡ ቤተሙከራውም ሁለት ክፍሎች ኖረውት አንደኛው ለሴቶች ብቻ አገልግሎት ለመስጠት የተዘጋጀ ነው፡፡
       የIUC ፕሮጀክት ማኔጀር የሆኑት ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራው እንደገለፁት ለአሁኑ 70 ኮምፒውተሮች ዝግጁ ይሁኑ እንጂ ተጨማሪ 18 ኮምፒውተሮችን ለአገልግሎት  ለማዋል  በዝግጅት  ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። አክለውም በዚህ ፕሮጀክት መሳካት  አስተዋጽኦ ያደረጉትን የስራ ክፍሎች አመስግነዋል።
      የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቤተ መጻሕፍት ዳይሬክተር አቶ ይበልጣል ታፈረ እንደገለጹት ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት የቤተ  መጻሕፍቱ አስተባባሪ ወ/ሮ የአብስራ ይባቤ፣ የዩኒቨርስቲው የኔትወርክ ቡድን መሪ ቻላቸው መኮነን፣ የሳይንስና የማሪታይም የICT እና መሠረተ ልማት ቡድን መሪ አቶ ውብሸት ስመኘው፣ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ የICTመሠረተ ልማት  ቡድን መሪ አቶ ሲሳይ ቁምላቸው እና ሌሎችም  በኃላፊነት የተሳተፉበት መሆኑን ገልጸዋል ።
     በመጨረሻም ለdigital research lab መሳካት የላቀ አስተዋፃኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅና እና ሰርቲፊኬት ሽልማት መረሃ ግብር ተደርጎ በምርምርና ማህበረሰብ ተሳትፎ ምክትል ፕሬዘዳንት እንዲሁም የIUC ፕሮጀክት አስተባባሪ  የሆኑት ፕሮፌሰር እንየው አድጎ ቤተ-ሙከራው በይፋ መከፈቱን አብስረዋል። በንግግራቸውም IUC ፕሮጀክት ሁለተኛው ምዕራፍ እንደሆነና በመጀመሪያው ምዕራፍ 17 PhD እና 29 MSc ለሚደርሱ የአካዳሚክ ስታፍ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ያደረገ ሲሆን በሁለተኛ ምዕረፍ ደግሞ 15 PhD እና 26  MSc ተማሪዎችን ለማስመረቅ እየሰራን ነው ብለዋል። የፕሮጀክቱ ዋና ዓላማምም የዩኒቨርስቲውን የቀጣይ ትውልድ  ተመራማሪዎች ማፍራት እንደሆነና ከፍተኛ የሆነ የሰው ኃይልና የቤተ-ሙከራዎችን አቅም የማሳደግ እንደሆነ በመግለጽ ተመሳሳይ ከፍተኛ ዳታዎችን ፕሮሰስ ማድረግ የሚችሉ (High Tech computers) በየግቢዎች የሚከፈትበት ዕድል ሊኖር እንደሚችል ገልጸው  ይህንን ለማሳካት የሁላችንንም ርብርብ የሚጠይቅ መሆኑን አሳስበዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የእንስሳት ሕክምና ዘርፉን ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ ነው

ታህሳስ 19/2018ዓ/ም ፣ (ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ)፤ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና ብሩክ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የእንስሳት ቀንን በጋራ አክብረዋል። ዩኒቨርሲቲው ከአጋር ድርጅቶች ጋር በትብብር የእንስሳት ህክምና ዘርፉ እንዲጠናከር እየተጋ ነው።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ሕክምና ትምህርት ቤት ከብሩክ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር "የእንስሳት ደህንነትን መጠበቅ ማህበረሰብንና ተፈጥሮን መጠበቅ ነው" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የእንስሳት ቀንን በዩኒቨርሲቲው ግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አክብሮ ውሏል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የእንስሳት ሕክምና ትምህርት ቤት ዲን ዶ/ር የሸዋስ ፈረደ እንደገለጹት፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከበረው የእንስሳት ቀን የአንድ መቶ ዓመት ታሪክ ያለው ነው። የእንስሳት ደህንነት ማሻሻል የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር ከእንስሳት ወደ ሰው የሚተላለፉ በሽታዎችን ከመከላከል አንጻር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለውም አስገንዝበዋል። ደህንነታቸው ካልተጠበቀ እንስሳት የሚገኝ ምርት ለሰው ልጅ ጤና ጠንቅ መሆኑን የጠቀሱት ዲኑ፣ በዓለም ላይ ካሉ በሽታዎች መካከል ከ60 እሰከ 70 በመቶ የሚሆኑት መነሻቸው ጤንነታቸው ካልተጠበቁ እንስሳት መሆኑን አብራርተዋል።

ዶ/ር የሸዋስ አክለውም ሁሉም የሰው ልጅ ለእንስሳት የሚገባውን እንክብካቤ ሊያደርግና በአስተሳሰብ ደረጃም ለውጥ ሊያመጣ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ሀገራት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የእንስሳት ጤናና ደህንነት አያያዝን ማሻሻል፣ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን መስራት እንዲሁም የህግ ማዕቀፎችን ማበጀትና ተግባራዊነታቸውን መከታተል እንደሚኖርባቸው ጠቁመዋል። ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲም በተግባር የታገዘ ትምህርት ከመስጠት ባለፈ ማህበረሰቡ ለእንስሳት ያለውን አመለካከት እንዲቀይርና በዘመናዊ መንገድ በማርባት ተጠቃሚ እንዲሆን በትጋት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በብሩክ ኢትዮጵያ በኩል በዓሉን አስመልክቶ ጽሁፍ ያቀረቡት ዶክተር ገበየሁ ድልነሳ በበኩላቸው፣ ድርጅታቸው ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር የእንስሳት ህክምና ተማሪዎች የተግባር ልምምድ እንዲያገኙና ዘመናዊ የእንስሳት አያያዝ ጥበብን እንዲቀስሙ እያገዘ መሆኑን ገልጸዋል። ድርጅቱ በዋናነት የወደፊት የእንስሳት ሐኪሞች ለስራ እንስሳት የሚሰጡትን የህክምና ጥራት ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራና በገበያ ቦታዎች እንዲሁም በገጠር መንደሮች የሚገኙ የእንስሳት ባለቤቶች እንስሳቶቻቸውን በተሻለ ሁኔታ እንዴት መመገብና ማሳረፍ እንዳለባቸው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ የእንስሳት ደህንነት ህግና ፖሊሲ እንዲጸድቅና በተግባር ላይ እንዲውል እየሰራ መሆኑን ዶክተር ገበየሁ ጠቁመዋል።

በመጨረሻም የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች በብሩክ ኢትዮጵያና በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትብብር የተገነባውን የእንስሳት ህክምና ማዕከልና ሞዴል ላብራቶሪ የጎበኙ ሲሆን፣ የተገነባው ማዕከል የመማር ማስተማር ሂደቱን ከንድፈ-ሀሳብ ወደ ተግባር ተኮር ዘዴ የቀየረ መሆኑን በመታዘባቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የዓለም የእንስሳት ቀን የፓናል ውይይት የተደረገ ሲሆን የእንስሳት ደህንነት ኮሙኒኬሽን፣ የእንስሳት ደህንነት የሚሰሩ አካላት በተመለከተ የጋራ ህብረት፣ የተማሪዎች ክበባት እና መሠል ስራዎች መሠራት እንዳለባቸው ተጠቁሟል።

ዩኒቨርስቲውም ይህን መሰል ተግባር ተኮር ስራዎች ይበልጥ እንዲያሰፋፋ በጉብኝቱ ወቅት ተሳታፊዎች ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

#አሁን ​#HappeningNow
​World Animal Day is currently being celebrated at Bahir Dar University. The event is being held at the Zenzelma Campus, organized by Ethiopia in collaboration with the Bahir Dar University School of Veterinary Medicine.

​We will return with further details.

የዓለም የእንስሳት ቀን በባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ እየተከበረ ነው። Brooke Ethiopia  ከባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ሕክምና ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር በዘንዘልማ ግቢ እየተከበረ ነው።
በዝርዝር እንመለሳለን።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Invitation to a training
**
https://docs.google.com/forms/d/1UCsvW6WDA0mVh4hNTcGn25alMMl7Oj9jVoa1bTcRzW4/edit

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለህግ ባለሙያዎቹ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀመረ
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማእከል ከዩኒቨርሲቲው የህግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ለህግ ባለሙያዎች ያዘጋጀው የሁለት ቀን ስልጠና  ተጀመረ።
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው የስልጠና ዳይሬክተር አቶ ወርቁ አበበ እንደገለጹት፤ ስልጠናው የባለሙያዎችን የስራ አፈጻጸም ክፍተት ለመሙላትና የተሻለ የዜጎች አገልግሎት አሰጣጥን ለማጎልበት ታስቦ የተዘጋጀ ነው። "ስልጠናው መሰረታዊ ከመሆኑም ባለፈ፣ ከፍተኛ ልምድ ያላቸውን አንጋፋ የህግ ባለሙያዎች በመጋበዝ የልምድ ልውውጥ እንዲደረግበት ታቅዷል" ያሉት አቶ ወርቁ፣ ሰልጣኞች በቀጣይነት ለሌሎች መምህራን፣ ሰራተኞችና ተማሪዎች እውቀታቸውን እንዲያካፍሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የህግ አገልግሎት ዳይሬክተሩ አቶ ተመስገን ሲሳይ በበኩላቸው፣ ስልጠናው በተለይ በቅርቡ የተቀጠሩ አዳዲስ ሰራተኞች ተገቢውን እውቀት እንዲጨብጡና ነባር ሰራተኞችም አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
የስልጠናው ዋና ዋና ትኩረቶች የፍትሐብሔር ስነ-ስርዓት ህግና፣የውል ህግ እና ግንባታ፡  በተለይም ዩኒቨርሲቲው እያከናወናቸው ያሉ በርካታ የግንባታ ስራዎችን ተከትሎ የሚነሱ የህግ ክርክሮችንና ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል ግንዛቤ በግንባታ ህግ ዙሪያ እንደሚሰጥ የህግ አገልግሎት ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። አክለውም ይህ ስልጠና ዩኒቨርሲቲው በህግ አገልግሎት ዘርፍ ያለውን ተወዳዳሪነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከጀመራቸው ተከታታይ ስልጠናዎች መካከል የመጀመሪያው መሆኑንም ገልጸዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የሙዝ ችግኝ ልማት ተስፋ ሰጪ ውጤት እያሳየ መሆኑ ተገለጸ
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከአረንጓዴ ልማት ሥራዎቹ ጎን ለጎን በዋናው ግቢ፣ በዘንዘልማና በይባብ ግቢዎች የጀመረው የሙዝ ችግኝ ተከላ የሚጨበጥ ለውጥ እያመጣ መሆኑን አስታወቀ።
በዩኒቨርሲቲው የእንግሊዝኛ ትምህርት ክፍል መምህርና የደንገልና ሙዝ ልማት ፕሮጀክት አስተባባሪ የሆኑት ንብረት አስራደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ቀደም ሲል የተጀመረው የደንገል ችግኝ ልማት ከተማውን ማዳረስ ከመቻሉም በላይ ማህበረሰቡ በራሱ አልምቶና ተንክብክቦ ተጠቃሚ እንዲሆን አስችሏል ብለዋል።
ከ2016 ዓ.ም. መጨረሻ ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ የተከናወነው የሙዝ ችግኝ ተከላም አሁን ላይ የሚጨበጥ ውጤት እያሳየ እንደሚገኝና ፕሮጀክቱ በዩኒቨርሲቲው ግቢዎች ብቻ ሳይወሰን፣ በመንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች የሚገኙ አትክልተኞችን በማሳተፍ የከተማዋን አየር ንብረትና አፈር የተላመደ የሙዝ ልማት እንዲስፋፋ እየተሰራ መሆኑን አስተባባሪው ገልጸዋል።

ዶ/ር ንብረት አክለውም ፕሮጀክቱ አበረታች ውጤቶችን እያስመዘገበ መሆኑንና ለልማቱ ተነሳሽነት ላላቸው 175 የዩኒቨርሲቲው ሰራተኞች የሙዝ ችግኝ በመስጠት በአንድ ዓመት ውስጥ የሚታይ የተግባር ለውጥ መመዝገቡ እንዲሁም በአማራ ክልል ያለውን ሰፊ የልማት አቅም በመጠቀም፣ በተለይም እንደ ፍኖተ ሰላም፣ ሜጫ እና ወረታ ባሉ ቆላማ አካባቢዎች የሙዝ ልማትን በማስፋፋት በምግብ ራስን ለመቻል ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ይህ ተነሳሽነት የአካባቢ ጥበቃን ከምግብ ዋስትና ጋር በማቀናጀት ለከተማ ግብርና ተምሳሌት የሚሆን ተግባር መሆኑ ተመላክቷል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማኅበርን ለማጠናከር እንደሚሠራ አስታወቀ

የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማኅበር ፕሬዚዳንት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በመገኘት ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ጋር ውይይት አድርገዋል።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ በቅርቡ አዲስ ስራ አስፈጻሚ በማቋቋም የዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማኅበር ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ዶ/ር ደመላሽ መንግሥቱ ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱም ዶ/ር መንገሻ የዩኒቨርሲቲ መምህራን የራሳቸው ማኅበር ስራ አስፈጻሚ በአዲስ መልክ መደራጀቱን በማድነቅ፤ ማኅበሩ ለሀገርና ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚጠበቅበትን ጠቃሚ ሚና እንዲወጣ እንዲሁም ማኅበሩ ይበልጥ ሊጠናከር ስለሚገባባቸው ሁኔታዎች መክረዋል።
በውይይቱ ላይ የተገኙት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማኅበር ፕሬዚዳንት ዲያቆን ውቤ እንግዳው በበኩላቸው፤ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በአገር አቀፉ ማኅበር ውስጥ የዋና ጸሐፊነት ሚናውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።

ዶ/ር መንገሻ አየነ ማኅበሩ በኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚያስተምሩና የሚመራመሩ መምህራንን፣ ተመራማሪዎችንና ፕሮፌሰሮችን በአባልነት ያቀፈ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለሀገር ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች የላቀ ሙያዊ አበርክቶ ለማድረግ አቅዶ መሥራት እንዳለበት መክረዋል። አክለውም የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማኅበር (ኢዩመማ) ለሀገር ዕድገት፣ ለዩኒቨርሲቲዎች ራስ-ገዝ (Autonomy) እንቅስቃሴና ለመምህራን ሁለንተናዊ ሕይወት መሻሻል ትልቅ ፋይዳ ያለው ተቋም በመሆኑ በጥንካሬ ሊመራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በመጨረሻም ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ማኅበሩ አገራዊ ተልዕኮውን እንዲወጣ፣ የዩኒቨርሲቲዎችን ክብርና ድርሻ በማስጠበቅ ረገድ የአስተባባሪነት ሚናውን እንዲያጠናክር አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግና አብሮ ለመሥራት ያለውን ቁርጠኝነት ፕሬዚዳንቱ አረጋግጠዋል።
የማኅበሩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ደመላሽ መንግሥቱ በቆይታቸው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን የሥራ እንቅስቃሴና የግቢዎቹን ወቅታዊ ሁኔታ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

https://euraxess.ec.europa.eu/worldwide/africa/events/horizon-europe-info-day-and-grant-writing-workshop-bahir-dar-university

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ቀን፡ 06/04/2018 ዓ.ም
ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመካከለኛ አመራር ምርጫና አሰያየምን ለመደንገግ ባወጣዉ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 05/2012 መሰረት ለ College of Business and Economics Dean ቦታ በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ መሾም ይፈልጋል፡፡
ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡ Dean for College of Business and Economics
የማወዳደሪያ መስፈርት፡-
1ኛ. የትምህርት ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማትወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤
3ኛ. በሚያመለክቱበት አካዳሚክ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ አካዳሚክ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ቸማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
4ኛ. የአካዳሚክ ክፍሉ ማህበረሰብ፣ የአካዳሚክ ኮሚሽኑ አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
አመልካቾች፡-
ይህ ማስታወቂያ በዩኒቨርሲቲው ድህረ- ገጽ፣ ፌስቡክና ማስታወቂያ ሰሌዳዎች ከተገለጸበት ታህሳስ 06 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡
በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 583 20 9653 ወይም +251 583 20 6059 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡
ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

BDU Establishes Advanced Technology Partnership with Russia

BDU, ADDIS ABABA (Late Post) – Bahir Dar University (BDU) is seeking to substantially enhance its international collaborations following a high-level meeting at the recent Russian Culture Day in Addis Ababa. The focus is on critical and emerging technological sectors.

Dr. Mengesha Ayene, President of Bahir Dar University, delivered a keynote speech at the event, emphasizing the longstanding bilateral relationship between Ethiopia and Russia and advocating for its expansion into strategic, high-impact areas.

President Dr. Mengesha Ayene specifically identified four vital high-tech fields with significant potential for collaboration, which are integral to Ethiopia's national development plans and BDU's capacity-building initiatives: Data Science and Cyber Security, essential for the country's digital transformation and safeguarding critical infrastructure; Aerospace Engineering, a fundamental area for advancing technological innovation and research; and Nuclear Engineering, which promotes energy independence and supports advanced scientific exploration.

Dr. Mengesha Ayene stated, “Ongoing cooperation in these fields is imperative for enhancing BDU's capabilities and directly contributing to Ethiopia's developmental objectives.”

Following the cultural exhibition, a high-level Russian delegation engaged in constructive discussions with the BDU team. The deliberations focused on establishing concrete, impactful partnerships with significant influence, including collaborative research and innovation projects, student and staff exchange programs, and joint PhD initiatives aimed at developing high-level national expertise.

The meeting concluded with a mutual consensus to develop a Memorandum of Understanding (MoU) to formally establish and govern the partnership with prominent Russian universities, representing a significant milestone in BDU's strategic internationalization efforts. Dr. Mengesha Ayene expressed sincere appreciation for the Russian delegation's invitation and facilitation, underscoring the success of the fruitful discussions.

Bahir Dar University, one of Ethiopia's largest institutions, is actively dedicated to enhancing its capacity through global partnerships. The historical friendship between Russia (formerly the USSR) and Ethiopia extends over more than a century. Notably, the former USSR played a pivotal role in founding Bahir Dar University and establishing the current Bahir Dar Institute of Technology. The university's main library, Jan Moskov, bears the name in recognition of this historical connection.

Russian Foreign Ministry - МИД России
Bahir Dar Institute of Technology, Bahir Dar University, Ethiopia
Ministry of Education Ethiopia

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመሠረተ-ልማት ግንባታዎችን አስረከበ
ባህር ዳር — የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ልማት ማዕከል (ECDD) ጋር በመተባበር፣ የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን እና ሰራተኞችን ተደራሽነት የሚያረጋግጡ የተለያዩ ግንባታዎችን አጠናቆ አስረከበ።

የዩኒቨርሲቲው የአካል ጉዳተኞች ጉዳይ ዳይሬክተር ዶክተር ዘላለም ተመስገን እንደገለጹት፣ ተቋሙ ከECDD ጋር በአራት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ ደርሷል። ከእነዚህም መካከል ዋነኛው "የአካባቢ ማሻሻያ" (Environmental Modification) ሲሆን፣ ለዚህም ተግባራዊነት በሁለት ግቢዎች ውስጥ አራት ተጨባጭ ስራዎች ተከናውነዋል። በፔዳ ግቢ፡ ሶስት የተለያዩ ቦታዎች ላይ የነበሩ ደረጃዎች ወደ ተዳፋት (Ramp) ተቀይረዋል። ይህም አካል ጉዳተኞች ያለ ማንም ድጋፍ በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ ያስችላቸዋል። እንዲሁም በቴክኖሎጂ ግቢ፡ የአካል ጉዳተኞችን ፍላጎት ያማከለ ዘመናዊ መጸዳጃ ቤት ተገንብቷል። ቀደም ሲል የነበሩት መጸዳጃ ቤቶች ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ባለመሆናቸው ሲፈጠር የነበረውን ከፍተኛ ችግር ይህ ግንባታ እንደሚቀርፈው ተገልጿል።
የECDD የተደራሽነት መሐንዲስ ወይዘሮ ኤደን የወንድወሰን እንደገለጹት፣ ግንባታዎቹ ከዚህ ቀደም ከሚሰሩ መሰል ስራዎች በልዩ ሁኔታ ተለይተው የተሰሩ ናቸው። ራምፖቹ (Ramps) የዊልቸር እንቅስቃሴን በሚያሳልጥ መልኩ ምቹ ሆነው የተሰሩ ሲሆን፣ ጥቅም ላይ የዋሉ ቁሳቁሶችም ደረጃቸውን የጠበቁና ተጠቃሚዎችን ለአደጋ የማያጋልጡ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የECDD የክልል አስተባባሪ ወይዘሮ አልማዝ መኮንን በበኩላቸው፣ ይህ ተግባር እንደ መጀመሪያ ሙከራ ወይም ማሳያ (Showcase) የሚወሰድ መሆኑን ጠቁመው፣ በቀጣይም አካል ጉዳተኞች እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መሰል ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ስታፍ አባል የሆኑት ዶክተር ሰለሞን ደምሴ፣ ግንባታው የተማሪዎችንና የሰራተኞችን የቆየ ችግር የፈታ መሆኑን ገልጸው፣ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ፕሮጀክቱ በሌሎችም የግቢው ክፍሎች ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የመጀመሪያውን የክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በይፋ አስመረቀ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ጥር 1፣ 2018 ዓ.ም) - የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ (ESA) ከተመሠረተ 15 ዓመታት በኋላ ከአዲስ አበባ ውጭ የመጀመሪያ የሆነውን የክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ በኢትዮጵያ ጨርቃጨርቅና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) ውስጥ በዛሬው ዕለት መርቆ ስራ አስጀምሯል። ይህ የባሕር ዳር ቻፕተር ጽሕፈት ቤት በኢንስቲትዩቱ ግቢ ውስጥ በሚገኘውና ለተማሪዎች፣ ለምሁራንና ለተመራማሪዎች ምቹ አገልግሎት በሚሰጠው ዘመናዊው "ግሪን ዲጂታል ላይብረሪ" ውስጥ ተደራጅቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

በምርቃቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ የአካዳሚው ሥራ አስፈጻሚ ፕ/ር ተከተል ዮሐንስና የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር መንገሻ አየነ የጽሕፈት ቤቱን ቁልፍ በመረካከብና ሪቫን በመቁረጥ በጋራ መርቀው የከፈቱ ሲሆን፣ በዕለቱም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የአካዳሚው አባላት የሆኑ ፕሮፌሰሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር መንገሻ አየነ በምርቃቱ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አካዳሚው የመጀመሪያውን ቅርንጫፍ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መክፈቱ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸው ዩኒቨርሲቲው ከአካዳሚው ጋር በቅንጅት በመሥራት ለአማራ ክልልም ሆነ ለሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የሳይንስ እድገት የሚጠበቅበትን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል። ፕሬዚደንቱ አክለውም በአሁኑ ወቅት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ 11 የአካዳሚው አባል የሆኑ ፕሮፌሰሮች ቢኖሩም፣ ተቋሙ ካሉት 43 ፕሮፌሰሮችና ከ850 በላይ ረዳት ፕሮፌሰሮች አንጻር ይህ የተደራጀ አቅም ለሀገርና ለሕዝብ ጠቃሚ የሆኑ ሳይንሳዊ ሥራዎችን ለማከናወን ትልቅ ዕድል መሆኑን አብራርተዋል።

የአካዳሚው ሥራ አስፈጻሚ ፕ/ር ተከተል ዮሐንስ በበኩላቸው፣ አካዳሚው በስድስት የሳይንስ ዘርፎች ማለትም በኢንጅነሪንግ፣ በጤና፣ በተፈጥሮ ሳይንስ፣ በጥበባት ዘርፎች ሁሉ ከፍተኛ የምርምርና የማማከር ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን አስታውሰዋል። አካዳሚው ተደራሽነቱን ለማስፋት ባደረገው እንቅስቃሴ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚውን ሚና በመውሰድ ደረጃውን የጠበቀ የጽሕፈት ቤት አገልግሎት በማመቻቸቱ የተሰማቸውን ኩራት ገልጸዋል።

ፕ/ር ተከተል አክለውም አካዳሚው ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቅርበት በመሥራት በሀገራዊ የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ ሳይንሳዊ ምላሾችን እንደሚሰጥና በማማከር፣ በመገምገምና አዳዲስ ሳይንሳዊ እሳቤዎችን በማመንጨት በኩል የላቀ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ገልጸዋል። በመጨረሻም በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሚገኙና ተፈላጊውን መስፈርት የሚያሟሉ ምሁራን የአካዳሚው አባል በመሆን ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Bahir Dar University Celebrates the New Year with a Vibrant International Gathering of Cultures

Bahir Dar, Ethiopia
January 1, 2026

Bahir Dar University (BDU) marked the beginning of the New Year with a colorful and vibrant International New Year Gathering on Thursday, January 1, 2026, bringing together international students and staff, senior government officials, diplomats, and members of the university community in a joyful celebration of diversity, unity, and shared aspirations.

Held at the Wisdom Tower Garden, the gathering was more than a celebration of the New Year; it was a celebration of community, connection, and shared purpose. The event reflected the university’s commitment to internationalization and its belief that meaningful global engagement is built through human connection and mutual respect.

The program began with arrival and a cultural welcome, setting a festive tone that carried through the evening. The formal opening featured the Ethiopian National Anthem and the East African Anthem, symbolizing national pride and regional solidarity.

Participants were warmly welcomed by Dr. Zewdu Emiru, Vice President for Information and Strategic Communication of Bahir Dar University, who emphasized the importance of fostering an inclusive and supportive environment for international students and staff.

In his opening remarks, Dr. Mengesha Ayene, President of Bahir Dar University, highlighted the university’s vision of becoming a globally engaged, research-intensive, and autonomous institution where diversity is embraced as a core strength.

The celebration was further enriched by key remarks from Ambassador Nebiyu Tedla, Minister Delegate and Director General of Public Diplomacy at the Federal Democratic Republic of Ethiopia Ministry of Foreign Affairs, who underscored the role of education and cultural exchange in advancing public diplomacy and strengthening people-to-people relations.

Mr. Getu Abdissa, Scholarship and Internationalization Desk Officer at the Ministry of Education, also delivered key remarks, reaffirming the Ministry’s commitment to supporting international students and expanding scholarship and internationalization opportunities.

A brief overview of the purpose of the gathering was presented by Dr. Manendante Mulugeta Seyoum, Director of External Relations and Partnership at Bahir Dar University, who noted that the event was designed around three key purposes: as a moment of welcome and appreciation, to strengthen bonds, and celebrate shared values of diversity, inclusiveness, cooperation, and peace.

The heart of the evening unfolded through student-led cultural expressions, where international students showcased the richness of their cultures through music, dance, and interactive performances. Student groups from all East African countries filled the evening with color, rhythm, and energy, creating moments of joy and mutual appreciation.

The event also featured goodwill messages from distinguished guests, including Ambassador Roza Yerukneh, Deputy Director General of Public Diplomacy at the Ministry of Foreign Affairs, Mulki Mohammed Hussein, Assistant Education Attaché at the Embassy of Somalia, and student representatives, who spoke on behalf of the international student body. Their messages conveyed sincere appreciation to the university leadership and organizing team for hosting such an inclusive and memorable celebration.

As Bahir Dar University advances toward becoming a research-intensive and autonomous institution, international engagement remains a core pillar of its vision. Events such as this New Year Gathering serve as powerful reminders that global engagement begins at home, through dialogue, respect, shared experiences, and a strong sense of community.

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ቀን፡ 23/04/2018 ዓ.ም
ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ  ከአካዳሚክ ዩኒቶች ውጭ በተለያዩ ክፍሎች በኃላፊነት የሚያገለግሉ የመካከለኛ እና ዝቅተኛ አመራር ምርጫ፣ ሹመት/ ምደባን  ለመደንገግ ታህሳስ  6 ቀን 2018 ዓ/ም በወጣው መመሪያ’ መሰረት ለአስተዳደር እና ልማት ጉዳዮች ኮርፖሬት ዳይሬክተር እና ለተማሪዎች ዲን የኃላፊነት ቦታ በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ መሾም ይፈልጋል፡፡
ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡  1. ለአስተዳደር ጉዳዮች ኮርፖሬት ዳይሬክተር
                         2. ለተማሪዎች ዲን 
የማወዳደሪያ መስፈርት፡-
1ኛ. የትምህርት ማእረግ/ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማት ወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤
3ኛ. በሚያመለክቱበት የስራ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ለማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/የምትችል፤
4ኛ. የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራር አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ሌሎች አካላት ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/የምትችል፤
አመልካቾች፡- ከታህሳስ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በስም በታሸገ ኤንቨሎፕ ፕሬዚደንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡
በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 583 20 9653 ወይም +251 583 20 6059 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡
ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

HAPPY NEW YEAR!!!

2026

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Call for Papers

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

"ራስገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን ተገቢው ዝግጅት ተደርጓል። "
ዶ/ር መንገሻ አየነ
የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት

የዩኒቨርሲቲያችን ፕሬዚደንት ዶ/ር መንገሻ አየነ ከአሚኮ ወቅታዊ ጋር ስለራስገዝነት ቆይታ አድርገዋል።

በቆይታቸውም ከእራስ ገዝነት አስተሳሰብ እና ሳይንሳዊ ምልከታ፣ የሌሎች ዓለማት ተሞክሮ፣ የዩኒቨርሲቲዎች አፈጣጠርና አሁናዊ ቁመናቸው፣ የራስገዝነት ትርጓሜና ሊያስገኘው ስለሚችለው ነጻነት ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ፕሬዚዳንቱ ዩኒቨርስቲያችን ራስገዝ መሆን የሚችልባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች ማጠናቀቁንም ተናግረዋል።

ማስፈንጠሪያውን በመንካት ሙሉውን ይከታተሉ።
https://youtu.be/ij8LNMFrgAI?si=V27f94fNFVePJaa_

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Merry Christmas!

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

🌍ዓለም ለእኛ ሰበብ ቦታ የላትም!!!

@necktop3
@necktop3

ራስ ላይ ለውጥ የሚፈልግ
contact @seen311
        SHARE

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህራን ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ እና ማሪታይም ኮሌጅ ጋር የልምድ ልውውጥ አደረጉ።

የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ መምህራን በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ እና ማሪታይምኮሌጅ በመገኘት የልምድ ልውውጥ እና የመስክ ምልከታ አደረጉ። በጉብኝቱ ወቅት የሁለቱ ተቋማት መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች በሰው ኃይል ልማት፣ በቁሳቁስ አቅርቦት እና በአስተዳደራዊ መዋቅሮች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።
የልዑካን ቡድኑ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ደረጃቸውን የጠበቁ የቤተሙከራ መሣሪያዎችንና የምርምር ማዕከላትን የጎበኘ ሲሆን፣ በተለይም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርገው የዋሸራ ምርምር ማዕከል የሥራ እንቅስቃሴ የልዑካን ቡድኑን ትኩረት ስቧል።
የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ እና ማሪታይምኮሌጅ ዲን የሆኑት ፕሮፌሰር ብርሀኑ አሳየ ሁለቱ ዩኒቨርሲቲዎች በጋራ ለመስራት እና እርስ በእርስ ለመተዋወቅና አዳዲስ ሀሳቦችን በማመንጨት ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ፣የተለያዩ የቤተሙከራ መሳሪያዎች በጋራ መጠቀም እንዲሁም ለማህበረሰብ እድገት የሚያገለግሉ ቴክኖሎጂዎችን በጋራ መስራት ጥቅሙ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል ።
የሀረማያ ዩኒቨርስቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን የሆኑት ዶ/ር ስለሽ እንደገለጹት በጉብኝቱ ያዩት እና ትኩረታቸውን የሳበው ደረጃቸውን የጠበቁ የቤተሙከራ መሳሪያዎች እና አጠቃቀማቸው ትልቅ ተሞክሮ የቀሰሙበት እንደሆነ ገልጸው ዩኒቨርሲቲዎች በጋራ ለመሰራት መስማማታቸው የአቅም ውስንነትን ለመቅረፍ ፣ፕሮጀክት በመክፈት የመማር ማስተማር ሂደቱ ምቹ እንዲሆን ፣ለተማሪዎች ልውውጥ ፣ለማህበረሰብ እድገት ፣ለሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች የማማከር አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችል ገልጸዋል።
ስምምነቱን ለማጠናከርም በሁለቱም ዩኒቨርሲቲዎች በኩል ኮሚቴ ተቋቁሞ የጋራ ስምምነት"MOU" እንደሚፈራረሙ ገለጸዋል፡፡

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ቀን፡ 10/04/2018 ዓ.ም
ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ (በድጋሜ የወጣ)
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመካከለኛ አመራር ምርጫና አሰያየምን ለመደንገግ ባወጣዉ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 05/2012 መሰረት  ለ School of Earth Sciences ዲን ቦታ በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ ለመሾም በወጣው ማስታወቂያ በቂ አመልካች ባለመገኘቱ በድጋሜ ማውጣት ይፈልጋል፡፡
ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡   ለ School of Earth Sciences  ዲን
የማወዳደሪያ መስፈርት፡-
1ኛ. የትምህርት ማእረግ/ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማትወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተ ቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤
3ኛ. በሚያመለክቱበት አካዳሚክ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ አካዳሚክ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ቸማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
4ኛ. የአካዳሚክ ክፍሉ ማህበረሰብ፣ የአካዳሚክ ኮሚሽኑ አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
አመልካቾች፡-
ይህ ማስታወቂያ በዩኒቨርሲቲው ድህረ- ገጽ፣ ፌስቡክና ማስታወቂያ ሰሌዳዎች ከተገለጸበት ታህሳስ 10 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡
በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 583 20 9653 ወይም +251 583 20 6059 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡
ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና ፕላን ኢንተርናሽናል 16 ወጣት ስራ ፈጣሪዎችን አሰልጥነው አስመረቁ
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (BiT) ከፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ለ15 ቀናት ሲሰጥ የነበረውን የስራ ፈጠራ ስልጠና በማጠናቀቅ ለወጣት ሰልጣኞች የእውቅና መርሀ ግብር አከናወነ።
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በገላ፣ ልብስ ፣ ፈሳሽ ላቫ ፣ የእጅ መታጠቢያ፣ የዕቃ፣ የዱቄት ሳሙና እና በመዋቢያ ምርቶች ከሰቆጣ፣ ላሊበላ እና ባሕር ዳር  ለተመለመሉ 16 ሰልጣኞች ባለፉት 15 ቀናት ላሰለጠናቸው ስራ ፈጣሪ ወጣቶች እውቅና የሚሰጥበት መርሀ ግብር የተከናወነ ሲሆን በአውደ ጥናቱና በእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር ለተሳተፉ አካላት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ምክትል ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር አማረ ካሰው እንደገለጹት ሰልጣኞች ከማምረት ባለፈ የገበያ ትስስር በመፍጠር ለሌሎች ወጣቶችም ሰፊ የስራ እድል መፍጠር አለባችው ብለዋል፡፡ 
በእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር ለታደሙ አካላት ስልጠናውን አስመልክተው ማብራሪያ የሰጡት  በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ኬሚካልና ምግብ ምህንድስና ፋኩሊቲ  መምህርና ተመራመሪ እንዲሁም ዲን የሆኑት ፕሮፌሰር ሰሎሞን ወርቅነህ ተቋሙ ከ50 በላይ ላቦራቶሪዎች ያሉት መሆኑን ገልፀው፣ እነዚህን በመጠቀም ዩኒቨርሲቲው በርካታ የስራ ፈጠራ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ መሆኑን አብራርተዋል። ፕሮፌሰሩ አያይዘውም፣ ተቋሙ ከማሰልጠን ባሻገር ሰልጣኞች ለስራቸው የሚሆን የዕውቅና ሰርተፍኬት የሚያገኙበት መንገድ እንደተመቻቸ ገልጸዋል።
ከሰልጣኞች መካከል ስራ ፈጣሪ ፊቨን አብዲ በበኩሏ የተገኘው እውቀትና ክህሎት ልዩ መሆኑን እና እነሱ የሚያመርቷቸው ምርቶች ከሌሎች የሚለዩት "ለእጅ፣ ለልብስ እና ለገላ መታጠቢያ የሚያስፈልገውን ኬሚካል መጠን ከጤና አንፃር ተለይቶ መወሰን የሚያስችል" ሳይንሳዊ እውቀት ያገኘችበት ስልጠና መሆኑን ገልጥጻለች።
በስልጠናውም አስራ አምስት ሴቶች እና አንድ ወንድ በድምሩ አስራ ስድስት ወጣቶች በደረቅና ፈሳሽ ሳሙና አመራረት ዙሪያ ስልጠናውን ወስደው ያጠናቀቁ ሲሆን በሰልጣኞች የተሰሩ ምርቶችም በተሳታፊዎች ተጎብኝተዋል፡፡
መርሀ ግብሩ ሲጠናቀቅ የላቀ አፈፃፀም እና ቁርጠኝነት አሳይተው ላጠናቀቁ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች፤ ከፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ባሕር ዳር ቅርንጫፍ ተወካይ እና ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አመራሮች ጋር በመሆን የእውቅና ሰርተፍኬት ለሰልጣኞች ተሰጥቷል።

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

The Poly Journal of Engineering and Technology (PJET) is a peer-reviewed, open-access, and multidisciplinary journal published biannually by the Bahir Dar Institute of Technology, Bahir Dar University.

As PJET advances toward international visibility and academic excellence, we invite accomplished scholars to help steer our mission of publishing pioneering research in engineering, technology, and applied sciences. Serving on the PJET editorial team presents a unique opportunity to shape scholarly discourse, expand global networks, and make meaningful contributions to the advancement of engineering and technology research.

Hence, you could apply either as 1. Editor-in-Chief or 2. Associate Editors position as outlined in the attached call.

@bahir_dar_university
@bahir_dar_university

#Share   #Share

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

ቀን፡ 06/04/2018 ዓ.ም
ክፍት የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመካከለኛ አመራር ምርጫና አሰያየምን ለመደንገግ ባወጣዉ ማሻሻያ መመሪያ ቁጥር 05/2012 መሰረት ለ Science College የ Research and Community Services V/Dean ቦታ በመመሪያው በወጣው መስፈርት መሰረት ብቁ አመልካቾችን አወዳድሮ መሾም ይፈልጋል፡፡
ክፍት የኃላፊነት ቦታ፡ V/Dean for RCS, Science College
የማወዳደሪያ መስፈርት፡-
1ኛ. የትምህርት ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት
2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማትወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተ ቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤
3ኛ. በሚያመለክቱበት አካዳሚክ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ አካዳሚክ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ቸማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
4ኛ. የአካዳሚክ ክፍሉ ማህበረሰብ፣ የአካዳሚክ ኮሚሽኑ አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/ምትችል፤
አመልካቾች፡-
ይህ ማስታወቂያ በዩኒቨርሲቲው ድህረ- ገጽ፣ ፌስቡክና ማስታወቂያ ሰሌዳዎች ከተገለጸበት ታህሳስ 06 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡
በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 583 20 9653 ወይም +251 583 20 6059 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል፡፡
ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

@bahir_dar_university
@bahir_dar_university

#Share   #Share

Читать полностью…

Bahir Dar University,Ethiopia

Bahir Dar University Commits to Excellence: Launches Major Faculty Training to Improve Assessment Skills and Educational Quality

Bahir Dar University in Ethiopia – December 12, 2025 – has officially started a four-day, impactful training program for its faculty, highlighting its proactive effort to improve academic standards. Organized by the Training Directorate and the Examination Center, this initiative aims to boost the professional skills of BDU's teaching staff, ultimately enhancing student assessment and the overall quality of education.

The training concentrates on two key areas: Basic Test Construction (covering the principles of designing valid True/False, Multiple Choice, Matching, and Essay questions) and Performance-Based Assessment (PBA). The latter includes intensive practical work on creating accurate Rubrics for the evaluation of hands-on and skill-based learning.

Building on last year's success, BDU plans to train 300 faculty members across its colleges and institutes during the 2025/2026 academic year. This effort is crucial for ensuring that student assessments accurately measure knowledge, critical thinking, and skills, thereby maintaining a high standard of education for all BDU students.

~~~~~~

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ ያለመ የመምህራን ስልጠና አስጀመረ

ታህሳስ 03/2018 ዓ.ም(ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ) –የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የትምህርትና ምርምር ጥራትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኝነቱን በተግባር ለማረጋገጥ፣ ለመምህራኑ ሙያዊ ብቃት ማጎልበቻ የተዘጋጀ የአራት ቀናት ልዩ ስልጠና ተጀምሯል። ስልጠናው በዩኒቨርሲቲው የስልጠና ዳይሬክቶሬት እና የፈተና ማዕከል ተብብር የተዘጋጀ ነው።

ስልጠናው ከታህሳስ 03/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አራት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን፣ የትምህርት ጥራት መሻሻል ወሳኝ መሠረት በሆኑት በሁለት ዋና ዘርፎች ያተኮረ ሲሆን፣ መሠረታዊ የፈተና አዘገጃጀት (Basic Test Construction) አንዱ የስልጠናው ትኩረት ነው። በዚህም የተለያዩ የንድፈ ሐሳብ ትምህርቶችና የፈተና አይነቶች (እውነት/ሐሰት፣ ምርጫ፣ አዛምድ እና አብራራ) አዘገጃጀት መርሆዎች ላይ ጥልቅ ትንተና በማድረግ፣ የፈተና ጥራትን የማሳደግ ዘዴዎችን የሚያካትቱ መሆኑ በስልጠናው መጀመሪያ ተብራርቷል።

ሁለተኛውና የስልጠና ትኩረት ተግባር ተኮር ምዘና (Performance-Based Assessment) ሲሆን ተግባር ተኮር ትምህርቶችን በትክክል ለመመዘን የሚያገለግለውን ሩብሪክ (Rubric) ዝግጅት ላይ ትኩረት በማድረግ፣ ተግባራዊ ልምምዶችና የልምድ ልውውጦች በማድረግ እንደሆነ ግንዛቤ ተሰጥቷል።

የስልጠና ዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ወርቁ አበበ እንዳብራሩት፣ ይህ ስልጠና የመምህራን የፈተና ዝግጅት አቅም በማሳደግ የተማሪዎችን እውቀት፣ ክህሎት፣ የማሰብ ችሎታና አመለካከት በትክክል የሚመዝን የፈተና ሂደት ተግባራዊ እንዲሆን ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ትክክለኛ የፈተና አዘገጃጀትና ሂደት መከተል ለአጠቃላይ የትምህርት ጥራት መሻሻል እጅግ አስፈላጊ በመሆኑ፣ ዩኒቨርሲቲው ይህንን ቅድሚያ ሰጥቶ እየሰራበት ይገኛል።
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል ዳይሬክተር ዶ/ር ጥሩወርቅ ታምሩም በበኩላቸው፣ ስልጠናው በተማሪ ምዘና መሳሪያ ዝግጅት ላይ በማተኮር የተሻለ የትምህርት ምዘና ሥርዓት ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።

ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ም ለ180 መምህራን ስልጠና በመስጠት ውጤታማነት በማስመዝገቡ፣ በ2018 ዓ.ም ደግሞ ለ300 መምህራን ስልጠናውን ለመስጠት አቅዷል። በአሁኑ ጊዜ በመጀመርያው ዙር 180 መምህራን ከአካዳሚክ ክፍሎች ተውጣጥተው ስልጠናውን እየተከታተሉ ነው። በመሆኑም የግብርናና አካባቢ ሳይንስ፣ የሂውማኒቲ ፋኩልቲ፣ የስፖርት አካዳሚ፣ የሳይንስ ኮሌጅ፣ የኢትዮጵያ ቴክስታይልና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (EiTEX) እና የባሕር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (BiT) መምህራን የስልጠናው ተካፋዮች ናቸው።

በዚህም ስልጠናውን በተሳካ ሁኔታ ላጠናቀቁ መምህራን በዩኒቨርሲቲው የምስክር ወረቀት የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።

@bahir_dar_university
@bahir_dar_university

#Share   #Share

Читать полностью…
Subscribe to a channel