dnhayilemikael | Unsorted

Telegram-канал dnhayilemikael - ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

1867

#መሰረታዊ_የቤተክርስቲያን_ክርስቲያን_ትምህርት / #የተለያዩ_ተከታታይ_ትምህርት ' #ስንክሳር_የቅዱሳን_ገድል_በየዕለቱ ! #ስዕለ_አድህኖ ! #ምስባክ #የየበአላቱ_ዋዜማና_ሥርተ_ማህሌት #መዝሙር #ግጥም #ለመናፍቃን_ጥያቄ_መልስ እና የተለያዩ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ ሌሎች መንፈሳዊ ጽሁፎች ይለቀቁበታል Administration @zearsema_dn

Subscribe to a channel

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ወደ እስራኤል ለሥራ ወይም ለትምህርት መሄድ ይፈልጋሉ⁉️

👇👇
@Hebrewethio
@Hebrewethio

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

🙏ጸሎት የተሰኘ አዲስ ግሩም ኦርቶዶክሳዊ 🙏

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

🙏ጸሎት የተሰኘ አዲስ ግሩም ኦርቶዶክሳዊ 🙏

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ራስን_መግዛት (ክፍል - ፬)

#ዶግማና_ትምህርት

💠መንፈሳዊው ሰው በዶግማና በትምህርት ላይ ራሱን ይገዛል፡፡

❤እርሱ አዘውትሮ ስለሚያነብ ወደ አእምሮው የገባውን ማንኛውንም ዓይነት አሳብ ለማስፋፋት አይጣደፍም:: ለምሳሌ፦ ቀስ ብሎ ሊያስተምረው ወይም አሳጥሮ ሊጽፈው ወይም ደግሞ መጽሐፍ አድርጎ ሊያሳትመው ይችላል፡፡ አንድ ሰው አንድን አሳብ ከመስጠቱም ሆነ ከመቀበሉ በፊት ወይም ጉዳዩን ለሌሎች ሕሊና ከማስተዋወቁ በፊት ለረዥም ጊዜ ሊያብላላውና ከገዛ ራሱ ሕሊና ጋር ሊወያይበት ይገባል፡፡

❤በልብህ ውስጥ ያለው አሳብ በአንተ ቁጥጥር ሥር ነው፡፡ ካወጣኸው ወይም ካስፋፋኸው ግን በሌሎች ሰዎች ቁጥጥር ሥር ነው::
❤ታላቁ አባት ቅዱስ መቃርስ «ወንድሜ ሆይ! ሰዎች በአንተ ላይ ከመፍረዳቸው በፊት በራስህ ላይ ፍረድ!›› ብሎ መናገሩ ምንኛ ትክክል ነው! ምናልባት ይህንን አባባሉን ያገኘው ከሐዋርያው ከቅዱስ ጳውሎስ ሊሆን ይችላል፡፡ «ራሳችንን ብንመረምር ባልተፈረደብንም ነበር . . » 1ኛ ቆሮ. 11፥31።
❤ይህም ማለት መንፈሳዊው ሰው በሌሎች ቁጥጥር ሥር ከመውደቅ ይልቅ ራሱን መቆጣጠር ይመርጣል ማለት ነው፡፡

#ታዛዥነትና_ቃል_መግባት

❤ራሱ ቃል በመግባት፣ በታዛዥነትና በተሸናፊነት ውስጥ ራሱን ይገዛል፡፡
❤ምክንያቱም ዛሬ አንዳንድ ሰዎች በነፃነት፣በግል ክብርና በራስ መተማመን ስም ስለ ሥነ ሥርዓት፣ ስለ ወግና ስለ ሕግ ሳይጨነቁ የወደዱትን ስለሚያደርጉ ነው፡፡
❤በዲሞክራሲ ብናምንም የምናምነው በገደብ ውስጥ ባለ ዲሞክራሲ ነው::
❤ለዚህ አባባል ወንዝ ጥሩ ምሳሌ ሊሆነን ይችላል፡፡ ወንዝ ከግራና ከቀኙ ባሉት ሁለት ከፍ ያሉ የምድር አካላት ተገድቦ ይፈሳል፡፡ ሰዎች ወንዙን ከሚፈስበት አቅጣጫ በማስቆም ነጻነቱን ሊነፍጉት ባይችሉም አፍሳሹ ወጥቶ የጎርፍ አደጋ እንዳያስከትልና አካባቢውን ረግረግ እንዳያደርግ ግን ሊቆጣጠሩት ይችላሉ፡፡

💠መንፈሳዊው ሰው
❤ ቃሉን ይጠብቃል

❤ግብረገብነትን ያከብራል!
❤ሕግጋትን ያጤናል፡፡
❤ሌሎች ሰዎችንም እንዲሁ ያከብራል፡፡ ሐዋርያው የተናገረውን ቃል ሳያንገራግር ይቀበላል:: «ለሁሉ የሚገባውን አስረክቡ፤ግብር ለሚገባው ግብርን፣ቀረጥ ለሚገባው ቀረጥን፣ መፈራት ለሚገባው መፈራትን፣ክብር ለሚገባው ክብርን ስጡ።» ሮሜ 13፥7: የራሱን ምኞትና አስተሳሰብ የሚከተለውና ለሥነ ሥርዓት፣ ለበላዩና ለማንም የማይገዛው ሰው ግን መንፈሳዊ ሰው አይደለም፡፡ እርሱ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረውን ስለማይቀበል ምንም ዓይነት ነገር አይቀበልም።

❤ታዛዥነትን አስመልክቶ መንፈሳዊው ሰው ራሱን ይገዛል፡፡ እርሱ ለወላጆቹ፣ ለንሥሐ አባቱ፤ ለሥነ ሥርዓት ከመታዘዙም በላይ ለእግዚአብሔርም ፍጹም ታዛዥ ነው::
💠መታዘዝ ክብሩን እንደማይቀንሰው ይረዳል:: መታዘዝ የትሕትና ምልክት ሲሆን ትሕትና ደግሞ መልካም ባሕርይ ነው፡፡ ለማንም የማይታዘዝ ሰው ሙሉ ለሙሉ የሚታዘዘው ለትዕቢቱና ለአሳቡ መሆኑ እርግጥ ነው፡፡

ይቀጥላል......

(#በብፁዕ_አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
#መንፈሳዊ_ሰው_መጽሐፍ  ገጽ 122-128
#በአያሌው_ዘኢየሱስ_የተተረጎመ)



#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

MK TV || ዕለታዊ መረጃዎች || የስብከተ ወንጌል ተደራሽነትን ለማስፋት 36 ሰባክያነ ወንጌል ተመሩቁ
https://youtube.com/watch?v=n49JSiqTE-o&feature=shared

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ታኅሣሥ 12
ዕረፍቱ ለአባ ሳሙኤል ዘዋልድባ

💠ታኅሣሥ ፲፪ የከበረ ገድለኛ አባት የዋልድባው አባ ሳሙኤል የአባቱ ስም እስጢፋኖስ የእናቱ ስም ደግሞ ዓመተ ማርያም ነው። እነርሱም በዘመድ የከበሩ ደጋግ ናቸው፤ እነርሱም በአክሱም ሀገር ሲኖሩ ሁለት ልጆችን ወለዱ። አንደኛው ስሙ ገብረ ክርስቶስ ሲሆን ይህ ሁለተኛው ደግሞ የእግዚአብሔር ሰው አባ ሳሙኤል ነው። እርሱንም ለመምህር ሰጥተውት የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እየተማረ በትጋት ኖረ። ከዚህ በኋላም ያስተምረው የነበረ መምህሩ ስለ አባ ሳሙኤል ታላቅነት ትንቢት ተናገረና በመቶ ዓመቱ ዐረፈ።

💠አባ ሳሙኤልም አባትና እናቱ እንዳረፉ ተነሥቶ ወደ አባ መድኃኒነ እግዚእ (አባ አድኃኒ) በመሄድ በደብረ በንኰል መኖር ጀመረ። በዚያም ትጋቱን ያዩ የአባ መድኃኒነ እግዚእ ደቀ መዛሙርት አባ ምንኲስና አስኬማ የሚገባው ደገ’ኛ ነውና እንዲያመነኩሱት ነገሩት። አባ አድኃኒም ትጋቱንና ተአዛዚነቱን ተመልክቶ አመነኰሰው። በዚያም ለሁላቸውም እየታዘዘ እንደመንኰራኲር በመፋጠን ያገለግል ነበር። የራሱን ሥራ ጨርሶ የደከማቸው ካለ ፈጥኖ መሄድ የነርሱንም ሥራ በመሥራት ያግዛቸው ነበር። በዚህም አፍቅሮ ቢጽን በግብር በግልጥ አሳያት። አባ መድኃኒነ እግዚእም በእጅጉ ወደደው። ነገር ግን በዚህ ገዳም ሲቆይ የሻገተ ጎመንና ጥቂት ውኃ ካልሆነ በቀር ምንም ምን ሌላ እህል አይቀምስም። እንዲህ ራሱን ሥጋውን በገድል እየቀጠቀጠ ቢኖርም ዘመዶቹ ግን እየመጡ ስላወኩት ለአባ መድኃኒነ እግዚእ አስፈቅዶ ወደ ሌላ ቦታ ሄዶ እግሮቹ እስኪያብጡ ድረስ እንደመንኰራኲር ይሰግድ፣ እጅግም ብዙ ጊዜ ይጸልይ ነበር። ከዚህም የተነሣ ሊቁ አባታችን ማር አባ ጊዮርጊስ ሲያመሰግነው ‹‹ሰአል ለነ ሳሙኤል አቡነ ሠረገላ ጸሎት፤ የፈጣን የጸሎት ሠረገላ የሆንክ ሳሙኤል ሆይ ለምንልን›› በማለት ተማጽኖታል።

💠ከዚያም ተነሥቶ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ በረኃ ወጥቶ ሲጋደል አናብርትና አናብስት ይሰግዱለትና ይገዙለትም ነበር። አንድ ዕለት አንዲት ለመውለድ የደረሰች አንበሳ ከበዓቱ መጣች። እርሱም ነገሩን አውቆ ቦታ ካስተካከለላት በኋላ መንታ የሆኑ ወንድና ሴት ደቦሎችን ወለደች። ወንዱም ሴቷን እየተጋፋ ሲጠባ አባ ሳሙኤል ግን ተራ በተራ እንዲጠቡ ያደርጋቸው ነበር። በሌላም ጊዜ አንድ አንበሳ እግሩ በእሾህ ተወግቶ አቂሞበት በጽኑዕ ታሞ ከውኃ ዳር ሁኖ ከደቀ መዝሙሩ ጋራ ሲጓዙ አዩት። ደቀ መዝሙሩም ውኃ ጠጥቶ ደክሞት የተኛ መስሎት ነበር። በኋላም ቀረቡና አባ ሳሙኤል ወስፌ አምጥቶ እሾሁን አወጣለት፤ ቂሙንም አፈረጠለት። ያም አንበሳ ከዚያ ልክ እንደእምቦሳ በአባ ሳሙኤል ፊት ይዘል ነበር።

💠አንድ ቀንም መጽሐፉን ሸክፎና የእሳት ማኅቶት ይዞ ሲጓዝ ታላቅ ወንዝ ውኃው እስከ አፉ መልቶ ገጠመው። አባታችንም በእምነት በውስጡ ገብቶ ተጓዘ። ሲገባበትም ውኃው ከራሱም በላይ ሞልቶበት ነበር። ተሻግሮ ሲወጣ ግን የእግዚአብሔር ድንቅ ቅዱስ ክብሩ እንዲገለጽ የቸሩ አምላክ ፈቃዱ ስለነበር እሳቱም አልጠፋ፣ ከመጻሕፍቱም አንዲቱ ቅጠን ስንኳ የውኃ ጠል አላገኛትም።

💠ጸላኤ ሠናያትም እጅግ ብዙ ጊዜ ይፈታተነው ነበር። አባ ሳሙኤል ግን በጸሎቱ ኃይል ድል ያደርገዋል። አንድ ዕለትም ጥልቅ ጉድጓድ አስቆፍሮ ለዐራት ወራት እህል ውኃ ሳይቀምስ ቆዳው ከአጥንቱ እስኪጣበቅ ሥጋውን አስጨንቆ ሲጋደል ከቆየ በኋላ ጌታችን ከአእላፍ መላእክት ከእመቤታችን እና ከቅዱሳን ጋር መጥቶ ባረከው፤ በምራቁም መላ ሰውነቱን ቀብቶ ኃይልን አሳደረበት። እንዲሁ ጣቱንም ሦስት ጊዜ ቢያጠባው ረኃብ የሚባል ነገር ሁሉ እልም ብሎ ጠፋለት። ከዚያችም ዕለት አንሥቶ እግሮቹን እያሠረ ማቅንም ለብሶ በየዕለቱ ከባሕር እየሰጠመ መዝሙረ ዳዊትን አምስት ጊዜ እየመላለሰ ቁጥር በሌለውም ግርፋት ራሱን ሥጋውን ይቀጣ ነበር። አናብስቱንም ልክ እንደፈረስ ለዕቃም ለመጓጓዝም ይገለገላቸው ነበር። እነርሱም እጅጉን ይታዘዙለታል።

💠ብዙ ደቀ መዛሙርትም ወደርሱ መጥተው የርሱ ልጆች ሆኖ። አንድ ዕለትም አባ ገብረ መስቀል ከሚባል ደገ’ኛ ጻድቅ አባት ጋር ተገናኝየው ሲጨዋወቱ አመሹ። ከዚያም በፊት ተያይተው አያውቁም ነበር። የእራትም ሰዓት ሲደርስ ተነሥተው በጸሎት ቢተጉ ከሰማይ የተዘጋጀ ማዕድ ወርዶላቸው አብረው ተመግበዋል። በሌላም ጊዜ ከአንድ ገዳማዊ አባት ሲነጋገሩ አባ ሳሙኤል ለዚያ ደግ ሰው ሲናገር ‹‹እነሆ እኔ በአርያም ቁሜ ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር የአምላክን መንበር ሳጥን ዐሥራ ሁለት ዓመት ሆነኝ›› አለው። ጻድቁ አባ ሳሙኤል አባታችን ለመቀደስ ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ የሚቀድስበት ጽዋዕ እና ኅብስት ከሰማይ የሚወርድለት ነበር።

💠ከዚህ ሁሉ ላይ ከዚህ ደገ’ኛ ጻድቅ የምናነሳለት ነገር ለንጽሕት የአምላክ እናት ለእመቤታችን ያለውን ጽኑዕ ፍቅር ነው። እርሱም ውዳሴዋን ከቅዳሴዋ አስተባብሮ የሚደግም ነበር። በሚጸልይበትም ጊዜ ከመሬት ክንድ ከስንዝር ከፍ ይል ነበር። እመቤታችንም በእጅጉ የምትወደው ንጹሕ ድንግል ተጋዳይ መነኰስ አባት ነው። ተያይዞም የሚነሣው አባታችን ምግብ ባሻቸው ጊዜ በውኃው ላይ ውዳሴዋን ከቅዳሴዋ አድርጎ ቢጸልይ ኅብስት ሁኖላቸው ይመገቡት ነበር። ንጽሕት እመቤታችንም አንድ ዕለት ተገልጻለት በክብር ታየችውና ንጹሕ ዕጣንን ከሚያበራ ዕንቊ ጋራ ሰጥታዋለች።

💠ዕረፍቱ በደረሰ ጊዜም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በብርሃናውያን አክናሱ ተሸክሞ ኢየሩሳሌም ሰማያዊትን አሳየውና ወደ ልዑል እግዚአብሔር አቀረበው። ቸሩ አምላካችንም በማይታበለው ቃሉ ጽኑዕ ቃልኪዳንን ሰጠው። ወደ ቀደመ አኗኗሩም በተመለሰ ጊዜ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው፤ ከዚህም ሁሉ በኋላ በሰላም ዐረፈ።

💠እግዚአብሔር አምላካችን በዚህ ኃያል ገድለኛ ጻድቅ ጸሎት ይማረን፤ በረከቱም ትደርብን፤ ለዘላለሙ አሜን።


#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

🥀በሰው ልጅ አፈጣጠር ትልቁ የማይዳሰስና ዋጋ የሚሰጠው አካል ህሊና ነው ። 💝
ቴሌግራም ቻናል⤵️

➯ ህሊና የአምላክ መቀመጫ ነው
➯ ህሊና ልክ እንደ አምላክ ነው
➯ ህሊና የሌለው ሰው አምላክ የሌለው ሰው ነው
➯በህሊናችን በኩል የሚያነጋግረን አምላክ ነው
መልካሙንና ክፉውን ሁሉ ይነግረናልና

💝ስንዋሽ
💝ውሸታምነታችንን
💝አድርባይነታችንን
💝ስግብግብነታችንን
💝ጨካኝ መሆናችችን
💝ኀጢያታችንን
💝 አስመሳይነታችንን ..... ሁሉ ሁልጊዜ ዝክዝክ አድርጎ ይነግረናል ።

💝ጥሩ ከሠራንም በዛውል ልክ መልካም መስራታችን ይመሰክርልናል ሀሴትም ያደርጋል ።
ህሊናችንን ብንሰማው መልካሙን መንገድ ይመራናል ። ባልሰማነው መጠን ደግሞ እየደከሞ ሂዶ መልካም ማድረግ ይሳነዋል የሰይጣን መጫወቻም ሆኖ ይኖራል ።

💝የህሊና ወቀሳ ከሰዎች ወቀሳ በእጅጉን ይለያል
ሰው ቢወቅስህ ለጊዜው ነው ህሊና ግን እረፍት የለሽ ነው ።

💝ህሊና ሲኖረን የኛ ምርጥ ጠላቶች
ውሸት ፣ ክፋት ፣ ማታለል ፣ ስግብግብነት ...... ይሆናሉ ።

💝ህሊና ሲኖረን በሰዎች ውስጥ ለመቀመጥ ማስመሰልንንና በሰዎች እንባ መደሰትን እንጠየፋለን ።

💝ህሊና ሲኖረን በሰዎች መቸገር ፣ መውደቅና መንከራተት ተባባሪ መሆንን አንጠላለን

💝ህሊና ቢስነት በየዋህ ሰዎች መጫወትን ፣  በተቸገሩ መጠቀምን ፣ በፈሪ ሰዎች መዘባበትን.....የምንወድ ለሆድ ያደርን ክፉ ሰው ያደረገናል ።

🥀አስተሳሰባችን ከአለባበሳችን ሲያምር
መልካምነታችን ከምንቀባው ሽቶ በላይ ሲያውድ
ምግባራችን በተግባር ሲገለጥ በሰብአዊነትና በህሊና መንገድ ስንሄድ
ለሰው ምናወራውን መልካም ነገር ስንኖረው ያኔ ህሊናችን ለራሳችን ምቹ ትራስ ሆኖ ያገለግለናል ። /ፍቅርተ ኢየሱስ /
            አምላከ ቅዱሳን ማስተዋልን ይስጠን🙏
     ቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ
   


#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ለሦስት ወራት ትምርህታቸውን በሀገረ ስብከቱ የካህናት ማሠልጠኛ ስከታተሉ የነበሩ የመጀመሪያ ዙሪ ደቀመዛሙርት ተመረቁ

መሠረተ ሚዲያ

በጉጂ ምዕራብ ጉጂ ቦረና ሊበን ዞኖች ሀገረ ስብከት ከሀገረ ስብከቱ ከተለያየ 13 ወረዳ ቤተ ክህነት የተወጣጡ ቤተ ክርስቲያንን በተለያየ ቋንቋ (አፋን ኦሮሞ ፣ አማርኛ ፣ ኮንሰኛ ፣ገደኤኛ፣ እና ሱማለኛ)
የሚያገለግሉ
ከመስከረም 12 እስከ ታኅሣሥ 7  ትምህርታቸውን በሀገረ ስብከቱ የካህናት ማሠልጠኛ ስማሩ የነበሩ  35 ደቀመዛሙርት በዛሬ ዕለት ተመርቀዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ በተመራቅ ደቀ መዛሙርቱ የተለያየ ወረብ ዝማረ እንድሁ የዕለቱ ወንጌል ተሰብኳል

መምህር አለምቀር ማኅበረ ቅዱን የነጌሌ ማዕከል ሰብሳቢ ለተመራቂ ተማርዎች መልእክት አስተላልፎ በመጨረሻም የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ለደቀመዛሙርቱ የምስክር ወረቀት በመስጠት
ምክር መልእከት በማስተላለፍና ቃለ ቡራከ በመስጠት መርሐ ግብሩ ተፈጽሟል


መርሐ ግብሩ የተካሄደው የነጌሌ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ጠዋት በሰንበት መርሃ ግብር ላይ ነው ።



╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮

    ሰንበት ትምህርት ቤት ሚዲያ(መሠረተ ሚዲያ )
➡️      መሰረተ ሚዲያ


👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
     ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ


👇👇👇👇👇👇👇👇

የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️
⤵️ ⬇️
/channel/Meseretemedia

   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ዕለታዊ_መልዕክት

“አንድ ገበሬ ዘር መዝራት ስላለበት ብቻ እንዲሁ አይዘራም፡፡ አስቀድሞ መሬቱን ማረስ፣ ማለስለስ አለበት፡፡ ካረሰ ካለሰለሰ በኋላ ዘሩን ይዘራዋል፡፡ አሁንም ግን መዝራቱ ብቻ በቂ አይደለም፡፡ የዘራውን ዘር አፈር ሊያለብሰው ይገባዋል፡፡ እንዲያ ካላደረገ ወፎች መጥተው ይለቅሙታልና፡፡ ልክ እንደዚሁ እኛ ክርስቲያኖችም በእኛ ላይ የተዘራውን ዘር (ቃለ እግዚአብሔር) በየጊዜው እንደ ገበሬው የማንከታተለው ከሆነ በአየር ላይ እንደተዘራ ዘር ይሆንብናል፡፡ ሰይጣን ይለቅምብናል፤ የራሳችን ስንፍና እንዲጠወልግ ያደርጓል፤ ፀሐይ ያደርቋል፤ ጐርፍ ይወስዷል፤ እሾክ አንቆ ይይዟል፡፡

ስለዚህ ዘር ዘርቶ ዞር ማለት አያስፈልግም ማለት ነው፡፡ በየጊዜው መኮትኮት፣ ወፎችን ማባረር፣ የበቀለ አረም ካለ ማረም፣ ጭንጫ የበዛበት አከባቢ ካለ የለሰለሰ አፈር መጨመር፣ በየጊዜው መከታተል፣ አጥር ማጠር፣ እንዲሁም ማንኛውም የተዘራውን እህል ሊያበላሹ የሚችሉ ነገሮችን ማስወገድ ያስፈልጋል፡፡ ምናልባት በሰብሉ እርሻ የገበሬው ትጋት ብቻ አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱም መሬቱ ግዑዝ ነገር ስለሆነ፡፡ በመንፈሳዊው እርሻ ግን እንዲህ አይደለም፡፡ ኃላፊነቱ የገበሬው ማለትም የመምህሩ ብቻ አይደለም፡፡ ከግማሽ ወይም ከዚያ በላይ የደቀመዝሙሩ (የምእመኑ) ኃላፊነት ነው፡፡ በርግጥ መምህሩ ዘሩን መዝራት አለበት፡፡ ነገር ግን ደቀ መዝሙሩ የተነገረውን ቃል ሁል ጊዜ መስማት ብቻ ሳይሆን ማድረግም አለበት፤ በግብር ፍሬ ማፍራት አለበት፤ የበቀሉ አረሞች ካሉ በየጊዜው መንቀል አለበት፡፡

የገበሬ ልጆች በሰብሉ መካከል የበቀለ አረም ካለ እንዲሁ ጫፍ ጫፉን ብቻ አይቈርጡትም፡፡ ከሥር ይነቅሉትና በመጨረሻም በእሳት ያቃጥሉታል እንጂ፡፡ በእኛ ላይ የበቀሉ አረሞችም (ጥርጥሮች፣ ክሕደቶች፣ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ማነቆ የሆኑብንን ነገሮች…) ከሥራቸው ነቅለን ልናቃጥላቸው ይገባናል፡፡”

#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ

 
#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ዕለታዊ_መልዕክት

ሕፃናት የእናታቸውን ጡት ለመጥባት ምን ያህል እንደሚጓጉ አስተውላችኋልን? እኛም ወደ ቅዱሱ ማዕድ መቅረብ ያለብን፣ ከመንፈሳዊው ጽዋ ጡትም ለመጠጣት መጓጓት ያለብን እንደዚህ ነው፡፡

ሕፃናቱ የእናታቸውን ጡት ሲያዩ እንዴት ደስ እንደሚሰኙም ተመልክታችኋል! እኛም የመንፈስ ቅዱስን ፍቅር ስንመለከት ደስ ሊለን የሚገባው እንደዚህ ነው፡፡

ሕፃናቱ የእናታቸው ጡት ሲከለከሉ ምርር ብለው እንደሚያለቅሱ ኹሉ፥ እኛም ከዚህ ማዕድ (ከቅዱስ ቁርባን) ስንርቅ ምርር ብለን ልናለቅስ ይገባናል
::


#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

"እነሆ መቅደሱ ይቀደስ ዘንድ አማናዊቷ ቤተመቅደስ ወደ ቤተ መቅደሱ ገባች"


🌹🌹🌹ባዕታ ለማርያም❤🌹🌹🌹

እንኳን (ለባዕታ ለማርያም) እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተመቅደስ ለገባችበት አመታዊ የንግስ በዓል በሰላም አደረሳችሁ🙏🙏🙏

ነገ ታህሳስ 3 /4/2016 በዓሉ በደማቁ ይከበራል

❤️ዓመ ሰሉሱ ለታህሳስ በአታ ለማርያም ውስተቤተ መቅደስ❤
መልካም በዓለ ማርያም🙏

የባዕታ ማርያም ምልጃዋ አይለየን
መልካም በዓለ ዋዜማ ይሁንላቸሁ።🙏



#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

++++እናስተውል በድጋሜ የዘላለም ቁጣ ሳይመጣ++++

ልጄ ሆይ ዛሬን ብትወድቅ ተስፋ አትቁረጥ ተነስ እንጂ ዛሬ እንደ ቃሉ በፍቅር መኖር ቢያቅትህ መፍትሔው ተስፋ መቁረጥ አይደለም፡፡ በእግዚአብሔር ተስፋ ማድረግ እንጂ ዛሬ በአገልግሎትህ ብትደክም ተስፋ ቆርጠህ ከቤቱ ከቶ አትውጣ፡፡ ከሐዋርያት ጋር ሆነህ ጌታ ሆይ ወደ ማን እሄዳለሁ?  አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ በለው፡፡ ዮሐ 6፡68 ከዳዊት ጋርም ሆነህ አሁንስ ተስፋዬ ማነው አንተ እግዚአብሔር አይደለህምን በለው መዝ 38፡7 ፍሬ ለማፍራትም በእርሱ ተስፋ አድርግ፡፡ በተስፋ ለምትጠባበቀው ለምትሻውም ነፍስ ጌታ ቸር የሚራራም ነውና፡፡ ልጄ ሆይ አዳም ከገነት ቢሰደድ ይዞ የወጣው ሌላ አይደለም ተስፋን ነው፡፡ በጌታ ቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ እድሜ ልኩን በክፉ ስራ ቢኖርም ተስፋን ግን አልጣለም በመጨረሻ ትንፋሽ ላይ ሳለ ወደ ሕይወት ያደረሰችው ይህች ተስፋ አለመቁረጥ ናት፡፡ በግራ ያለውማ ተስፋ በመቁረጡ የእምነትና የፍቅር ሻማዎቹ ሊበሩለት አልቻሉም፡፡ እንግዲህ ልጄ ሆይ በጊዜውም ያለጊዜውም እርሱን ተስፋ አድርገህ ኑር፡፡ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ።

:ምናልባት ለመፆም፣ ለመፀለይ፣ ለማስቀደስ፣ ለመስገድ፣ የተለያዩ መንፈሳዊ ተግባራትን ለማከናወን ፍላጎታችን ፍቅራችን ጠፍቶ ይሆናል። እነዚህን መንፈሳዊ ተግባራትን ለማከናወንም እምነት አጥተን ይሆናል ግን ተስፋ ልንቆርጥ አይገባም በእግዚአብሔር። ፍቅር እንዲጨምርልን እንለምነው። አለማመኔን እርዳው እምነትን ጨምርልኝ፣ ትእዛዛቶችህን ለመፈፀም እምነት ይጎድለኛል። በመፆም በመፀለይ የሚገኘውን በረከት አላስብም እንዲሁ ለማድረግ ያክል ብቻ ነው። ዋጋም ያለው አይመስለኝም። አምላኬ ፍቅርህን አብዛልኝ አንተን ማመንንም ጨምርልኝ ብለን እንለምነው። የመበለቲቱን ሁለት ዲናር ሳይንቅ አክብሮ የተቀበለ አምላካችን ይለመነናል። 

‹‹እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን እነርሱ ምድርን ይወርሳሉ›› መዝ 36፡9                                                                                   



#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ሆድ_አምላክ_ይሆናልን?

የሰው ልጅ ወደድኳቸው በሚላቸው ነገሮች ሕይወቱ ይወሰናል። ሰይጣንም በምንወዳቸው ነገሮች ቀዳዳ በኩል ገብቶ ነው በውንብድና የጸጋችንን መዝገብ የሚበረብር።

ለእግዚአብሔርም ያለንን ፍቅር የምንገልጠው በምንወዳቸው ነገሮች ነው።  እርሱ አንድ ልጁን በመስጠት ፍቅሩን እንደገለጠልን እኛም የምንወዳቸውን ለእግዚአብሔር ብለን ይቅርብን ብለን በመተው በዚህ ፍቅራችንን እንገልጣለን።

የምንወዳቸው ሁሉ በእግዚአብሔር ፍቅር ፋንታ ከገቡብን፥ እነዚያ በእርግጥ የምንወዳቸው ነገር ግን በፍቅረ እግዚአብሔር የተካናቸው የወዳጅ ጠላት የሆኑበትን ጠዖታት ናቸው። ከእነዚህም ሳይገባን ጣዖታት አደርገን ከምናመልካቸው መካከል አንዱ ሆድ ነው።

እግዚአብሔር አትብሉ ብሎ የከለከለንን ነገርና አትብሉ ባለን ሰአት የምንበላ ከሆነ በእርግጥ ከእግዚአብሔር ይልቅ ሆዳችንን እየወደድን ስለሆነ ሆዳችንን አመለክን ማለት ነው።

ይህ ብቻ አይደለም፤ እግዚአብሔር እውነት ነው እቸገራለሁ ብሎ አስቦ መዋሸትም ጣዖት ማምለክ ነው። ለሆዱ ብሎ የሚዋሽ ሰው ከእግዚአብሔር ባሕርይ ጋር ይቃረናልና። የእግዚአብሔር ባሕርይው እውነት ነው። 

ድኻ እየተቸገረ እያዩ ለነገ በማሰብ የማይመጸውቱ ሰዎችም በሁለት መንገድ ጣዖት አምልከዋል፦
#አንደኛ አስቀድመን እንደ ገለጥነው ከፍቅር ይልቅ ገንዘብን በማስቀደም፤
#ሁለተኛ ደግሞ እግዚአብሔር ያኖረኛል ከማለት ይልቅ ራሳቸውን ለራሳቸው ጠባቂ መጋቢ አድርጎ በመሾም መግቦተ እግዚአብሔርን በመካድ ነው።

እንግዲህ እናስተውል ሆድ በሦስት መሠረታዊ ምክንያቶች ጣዖት ሊሆንብን እንደሚችል፦
#መጀመሪያ እግዚአብሔር የከለከለንን በመመገብ ጊዜ ከእግዚአብሔር ይልቅ መብልን በመውደድ፤
#ሁለተኛ ለቅዳሴ መላእክት የተፈጠርን ክቡራን አገልጋዮቹ ስንሆን መላ ዘመናችን ሆዳችንን በማገልገል ራሳችንን የራሳችን ባርያዎች በማድረግ፤
#ሦስተኛ እግዚአብሔር እንደፈጠረኝ ያኖረኛል ከማለት ይልቅ ለነገ በመስገብገብ ለድኾች አለመራራት ናቸው። 

ጾም ፍቅር እንጅ ቀመር አይደለም። የምንጾመው ከምንወደው መብል መጠጥ በመከልከል ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር ለመግለጥ እንጅ ሰባት ጾም የጾምን ሰዎች ነን የሚል መስፈርት ለማሟላት አይደለም።

የሰው ልጆች ሁሉ እናትና አባት የመጀመሪያዎቹ ሰዎች አንዲት የእንጨት ፍሬ የተከለከሉት ያችን በመተው ፍቅረ እግዚአብሔርን እንዲገልጡ እንጅ ለአንዲት እንጨት ፍሬ ነፍጓቸው አይደለም። እርሱማ እንኳን የበለስ ፍሬ ሊነፍገን  ሥጋውን ደሙን በለጋሥነት የሰጠ የባሕርይ ቸር አይደለምን?

ክርስትና የፍቅር ሃይማኖት ነው። እግዚአብሔር ፍቅር ነውና ስለ ፍቅር ትጾማለህ፤ ስለ ፍቅር ትጸልያለህ፤ ሰለ ፍቅር ትሰደዳለህ፤ ስለ ፍቅር ትታሰራለህ፤ ስለ ፍቅር ትናቃለህ፤ ስለ ፍቅር ግፍን ሁሉ ተቀብለህ ትሞታለህ፤ በፍቅር ብርሃን ደምቀህ ትነሣለህ።

ፍቅር ደግሞ ስለ ፍቅር በመማር የምታውቃት አይደለችም ስለ ፍቅር በመኖር እንጂ። ፍቅር በልቡናህ ዛፍ ሆኖ የተተከለ እንደሆነ ሥሩ እስከ ተረከዝህ ይወርዳል፤ ቅርንጫፎቹ ወደ ራስህ ያድጋሉ፤ አበባቸው በአንደበትህ ይፈነድቃሉ፤ የፍቅር ፍሬዎችም እነ ጾምና ጸሎት ምጽዋት ከአንተ በመላእክት እጅ እየተለቀሙ በሰማይ ጎተራ ይከማቻሉ፤ የፍቅርን ፍሬ እየበላህም ለዘለዓለም ትኖራለህ።

እግዚአብሔርን የምትወደው ከሆነ እንኳን ሰባቱን አጽዋማትን ሁሉንም ቀን ትጾማለህ።  ፍቅረ እግዚአብሔር ያነሰህ ፍቅረ መብልዕ የበዛልህ ስትሆን ደግሞ ጾም ይቀነስልኝ ብለህ ክተት ሠራዊት ትወጣለህ፤ ነጋሪት ትጎስማለህ። እንዳትጾም የሚረዱህ የሚመስልህን ጥቅሶችም በመብራት እየፈለግህ ትለኩሳለህ። በጅብ ቆዳ የተለጎመ ከበሮ ሲመቱት 'እንብላው' ብሎ ይጮኻል እንዲሉ አበው፤ የሆድ ጠበቃ የሆኑ የጅብ ስብከት የሚያመሰጥሩ የእንብላው መጽሐፍ ሊቃውንትንም አታጣም።

እናም ወዳጄ ሆይ "እለ ከርሦሙ ያመልኩ" "ሆዳቸው አምላካቸው ነው" እንደለ ቅዱስ ጳውሎስ (ፊልጵ. ፫፥፲፰ )የምትወደው ሆድህ ጠላት ሆኖ በግራ እንዳያቆምህ በእግዚአብሔር  ፍቅር ሰይፍነት የስስትን ገመድ ቆርጠህ ጥለህ ከምጽዋትና ከተገራ ሰውነት ጋር ጹም!

#መጋቤ_ብሉይ_ወሐዲስ_አባ_ገብረ_ኪዳን



#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

አንድ ሰው መጥቶ እናንተ የምትለብሱትን አንዲት ቁራጭ ልብስ እንኳ ሳይሰጣችሁና ሰውነታችሁ በብርድና በዋዕየ ፀሐይ እየተቆራመደ ሳለ ቤታችሁን በወርቅና በተንቆጠቆጠ የመጋረጃ ዓይነት ቢያስጌጥላችሁ ምን ጥቅም አለው? እኛስ ነፍሳችን ዕራቁቷን ሳለች ሥጋችንን ወርቅ ብናለብሰው በወርቅ ብናስተኛው ምን ትርጉም አለው? ነፍሳችን በመሬት ላይ እየተንፏቀቀች ሳለ ሥጋችን በከበሩ ሠረገላዎችና የተለያዩ ማጓጓዣዎች ብትንፈላሰስ ምን ጥቅም አለው?

ልጆቼ ! እውነተኛውን ልብስ ልበሱ ብዬ እመክራችኋለሁ። እዚህ የሚቀረውን ሳይኾን ዘለዓማዊውን ልብስ ልበሱ። የሰርጉን ልብስ ልበሱ።

እስኪ በየገዳማቱ ሒዱና ይህን ከቅዱሳን አበው ወእማት ተማሩ። እነዚህ ቅዱሳን በእልፍ ወትእልፊት ዕንቁ የተሽቆጠቆጠ ልብስ ብትሰጥዋቸው አይቀበሏችሁም። ለምን? እነርሱ ጋር ያለው ልብስ እናንተ ይዛችሁት ከሔዳችሁት ይልቅ በእጅጉ እንደሚበልጥ ስለሚያውቁ! ይኸውም የነፍሳቸው ልብስ ማለቴ ነው።

ለእነርሱ ይዛችሁት የሔዳችሁት ልብስ ለአንድ ምድራዊ ንጉሥ ብትሰጡት እጅግ ያመሰግናችኋል። እነርሱ ግን ከዚህ ንጉሥ በላይ በከበረ ልብሱ ያጌጡ ናቸውና አይቀበሏችሁም። ወርቃቸውን ወደሚያስቀምጡበት መዝገብ (ልቡናቸው) ገብታችሁ ስታዩ'ማ ራሳችሁን ስታችሁ ትወድቃላችሁ ። የሀብታቸውን (ምግባር ትሩፋታቸውን) ብዛት የወርቃቸውን ንጻት እንዲህ ነው ተብሎ የሚነገር አይደለም ። እናንተም ከእነርሱ ተማሩና እውነተኛውን ልብስ ለመልበስ ተሽቀዳደሙ ።

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

(ሰማዕትነት አያምልጣችሁ መጽሐፍ)


#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

መድኃኔዓለም

💠«መድኃኔዓለም ማለት ዓለምን ያዳነ የዓለም መድኃኒት  ማለት ነው።
💠ሰው በመበደሉ ምክንያት ከክብር ተዋርዶ ይኖር ነበር።ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የተዋረደውን ሰው እርሱ በመስቀል ተሰቅሎ ወደ ቀደመ ክብሩ መለሰው።

ምን ዓይነት ፍቅር ነው?????
👉 ወንድሜ/እህቴ አስባችሁታል ግን ስለእኛ ብሎ እኛን ለማዳን ብሎኮ ነው የተሰቀለው።
💠ራቁትን መሰቀል ምን ያህል አሳፋሪ ነገር እንደሆነ እናውቀዋለን።ጌታ ግን እኛን ለማዳን ብሎ ራቁትን መሰቀልን ናቀው።
👉 በፈጠራቸው ፍጥረታት ተሰቃየ ተተፋበት መከራ ጸናበት ሰቀሉት ።እኛን ትእግስት ሊያስተምረን እነርሱን ማጥፋት እየቻለ እርሱ ግን በፍቅር እያየ የማያውቁትን አያውቁምና አባት ሆይ ይቅር በላቸው ይል ነበር።
💠ክርስቶስ እኛን ለማዳን ሲሰድቡት አልተሳደበም ሲንቁት አልናቃቸውም ሲታበዩበት ሁሉ እርሱ ግን በትሕትና ያያቸው ነበር።
ታድያ
     💠 እኛ ደግሞ መንግሥቱን ለመውረስ ሲንቁን ሲሰድቡን ሲታበዩብን በፍቅር በዝምታ ማለፍ ይጠበቅብናል።

💠ይህን ካደረግን የክርስቶስ ደቀመዝሙር እንባላለን። በ5 ችንካር ነበር የቸነከሩት።በመስቀል የተገኙ ድንግል ማርያምና ሐዋርያው ዮሐንስ ነበሩ።
አንተም በመስቀሉ ስር ለመገኘት ከፈለግህ ትዕግስትን ፍቅርን ትሕትናን ገንዘብ አድርግ።

መድኃኔዓለም በቸርነቱ ይቅር ይበለን።



/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

🙏ጸሎት የተሰኘ አዲስ ግሩም ኦርቶዶክሳዊ 🙏

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

🙏ጸሎት የተሰኘ አዲስ ግሩም ኦርቶዶክሳዊ 🙏

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#የመጨረሻ_ክፍል

#ራስን_መግዛት (ክፍል- ፭)

#ምኞትና_የበላይነት

መንፈሳዊው ሰው ምኞቱን፣ ደስታውን መውደዱንና የበላይነቱን አስመልክቶ ራስን መግዛት አለው:: በራሱ ዓይኖች ፊት ራሱን አዋቂ አድርጎ ሲያገኘው ወይም በአመለካከቱ ውስጥ ራሱን አጽድቆ ሲመለከት ወይም ደግሞ ራሱን ከሚያስበው በላይ ከፍ አድርጎ ሲያስብ ራሱን ለመግዛት ይጥራል፡፡ ሮሜ 12፥3

ከዚህ በተጨማሪ እግዚአብሔር ከሰጠው ጸጋ በላይ ራሱን ሊያልቅ አይሞክርም፡፡ ዲያብሎስ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ ብሎ በትዕቢት የተነሣው ራሱን መግዛት ባለመቻሉ ስለሆነ ወድቋል። ኢሳ. 14፥14

መንፈሳዊው ሰው ራሱን የሚገዛው ውዳሴ ከንቱን አስመልክቶ ብቻ ሳይሆን ስጦታዎችንም በተመለከተ ነው:: ወይም ደግሞ ሰውየው ራሱን ከፍ ከፍ እንዳያደርግ እግዚአብሔር እርሱነቱን የሚገዛበትን መንገድ ያመቻችለታል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን አስመልክቶ የተናገረውን ቃል አትርሱ! «ስለዚህም በመገለጥ ታላቅነት እንዳልታበይ የሥጋዬ መውጊያ እርሱም የሚጎስመኝ የሰይጣን መልእክተኛ ተሰጠኝ፤ ይኸውም እንዳልታበይ ነው።» 2ኛ ቆሮ. 12፥7።

#ወንድሜ_ሆይ! አሳብህ ከፍ ከፍ ባለብህ ጊዜ ሁሉ ተቆጣጠረው። ራስህን ከተሰጠህ በላይ አድርገህ አትገምት፡፡ አንተነትህን ከሌሎች ጋር አነጻጽረህ ወደምትመለከትበት ደረጃ የሚመሩህ ምኞቶችህን ግታቸው፡፡ ራስህን ከፍ ከፍ ብሎ ስታየው ወይም ደግሞ በፊትህ ታላቅ ሆኖ ስታገኘ ው ታዛዥነትህን፣ ትሕትናህን፣ ለሌሎች ያለህን ክብር በማጣት ላይ መሆንህን እወቅ፡፡ በማንኛውም ጊዜ ከፊት ለፊትህ የሚከተለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል አኑር። «ትዕቢት ጥፋትን ኵሩ መንፈስም ውድቀትን ይቀድማል።» ምሳ. 16፥18::

#በሕይወት_ዙሪያ

ራስን መግዛት መላ ሕይወትን ያጠቃልላል፡፡ መንፈሳዊው ሰው ምቾትንና ድሎትን አስመልክቶ ራስን መግዛት አለው፡፡ እርሱ ሰዓቱን በትክክል ይጠቀማል፡፡ በመሆኑም ጊዜውን ለሚሠራው መንፈሳዊ ሥራ ያከፋፍላል። ቀጠሮ ያከብራል:: በተሰደበ ወይም በተጠቃ ጊዜ ሰራሱ ሊበቀል እንዳይነሳሳ ራሱን ይገዛል፡፡ ገንዘብን በተመለከተም ስለሚቀበለውና ስለሚስጠው ገቢና ወጪ ላይ ራሱን ይገዛል። ከሌሎች ጋር የሚያደርገው ግንኙነት እስከ ምን ድረስ መሆን እንዳለበት ይረዳል:: ወደ ግራ ወይም ወደ ቀኝ እንዳያጋድል የልቡን ስሜታዊነትና ፍላጎት ይቆጣጠራል:: ሌላው ቢቀር በአምልኮ፣ በአገልግሎት፣ሌሎችን በመቆጣጠርና ሌሎችም ባሉበት ኃላፊነቶች ውስጥ ራሱን ይገዛል::

#ለማጠቃለል
በዚህ ጉዳይ ላይ የምስጠው ጠቃሚ አስተያየት ራሱን ከውስጥ መቆጣጠር የማይችል ስው ከውጪ የሌሎች ቁጥጥር እንደሚያስፈልጉት የሚገልጽ ነው:: እርሱ ራሱን ከውስጥ መቆጣጠር ካልቻለ ቁጥጥሩ ያለ ፈቃዱ ከውጪ ይመጣል። ከውጪ የሚመጡት ኃይላትም አመሉን በቅርብ የሚያውቀውና ኃላፊነቱን የሚጠይቀው ኅብረተሰብ አንዱ ሲሆን የሚመለከቱት ዓይኖችና የሚሰሙት ጆሮዎች ተጠያቂ ያደርጉታል። ከዚህ በኋላ በፍርሃት ይገዛል ወይም በእፍረት ይሸማቀቃል፡፡ በመጨረሻም በሕግና ከበላይ አካላት በሚመጡ ውሳኔዎች እንዲቆጣጠሩት ይሆናል::

ወይም ደግሞ በመንፈሳዊ ምክሮች ከገደቡ እንዳያልፍ አድርገው ያቆሙታል፡፡ ከዚህ ካለፈ ስህተቱን እንዳይደግም በሚያደርጉት ውጪያዊ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር ይወድቃል:: ነቢዩ ዳዊት ራሱን ባለመግዛቱ ብቀላ ከመውሰድ ራሱን ሊከለክል አለመቻሉ በጣም ያስደንቀኛል። በዚያን ወቅት ለእርሱ ውጪያዊ ኃይል ስላስፈለገው አቢግያ በጥበብና በእውቀት እንድትገሥጸው ሆኗል። 1ኛ ሳሙ. 25::

አንድ ሰው ያለራሱ ፈቃድ በሌላ ቁጥጥር ውስጥ ከሚገባ ወይም በውጪያዊ ኃይል ከሚገዛ ይልቅ ራሱን በመንፈሳዊነት ገዝቶ መለኮታዊውን ዋጋ ቢያገኝ ይሻለዋል ይበጀዋልም:: መንፈሳዊው ሰው ግን ራሱን የሚገዛው ከውስጥ ነው:: በዚህ ጊዜ ውጊያዎች ከመጡበትም ምንጊዜም ቢሆን የሚፈልገው የልቡን ንጽሕና እና የተቀደሱ ሥራዎቹን ስለሆነ የተለያዩ መንፈሳዊ እርምጃዎችን ይወስዳል::

(#በብፁዕ_አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
#መንፈሳዊ_ሰው_መጽሐፍ  ገጽ 122-128
#በአያሌው_ዘኢየሱስ_የተተረጎመ)


#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ራስን_መግዛት  (ክፍል-፫)

#መብላትና_መጠጣትን_መግዛት

ብዙ ሰዎች «ዳይት» በሚለው አካሄድ ምግብን ከወትሮው በመቀነስ ራሳቸውን ተቆጣጥረው ክብደታቸውን ይቀንሳሉ፡፡ ይህን የሚደርጉትም ለስኳር በሽታ፣ ለልብ ሕመም፣ ለደም ብዛትና ስብ (ውፍረት) ለመቀነስ ሲሉ ነው:: መንፈሳዊው ስው ግን ምግቡንና መጠጡን የሚቆጣጠረው ለመንፈሳዊ ምክንያቶች ነው፡፡ ይህም ጾምንና መከልከልን ያካትታል፡፡ እርሱ እዚህ ላይ ራሱን የሚገዛው ሥጋውን አድክሞ ለመንፈሱ የትጋት ጊዜ ለመስጠት ነው::

ምግብን አስመልክተን ስንናገር እናታችን ሔዋን ራስዋን መግዛት እንዳልቻለች እናስታውሳለን። እርሷ ራስዋን መግዛት ስላልቻለች የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በመተላለፍ እንዳትበላ ከተከለከለችው ዛፍ ፍሬዋን ቆርጣ በልታለች:: አባታችን አዳምም እንዲሁ ተቀብሎ በልቷል:: በዚህም የመጀመሪያው ኃጢአት ወደ ዓለም ገባ፡፡

እዚህ ላይ ከውድቀት በፊት ቀድሞ የመጣው ስሜትን ለመቆጣጠር አለመቻል ነው:: በመሆኑም የመጀመሪያው ኃጢአት የተፈጸመው ሔዋን እባቡን በመስማቷ ወይም ደግሞ «ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነና ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ . . » አይታ ስለጎመጀች ነው:: ዘፍ. 3፥5:: በእርግጥም አንዱ ኃጢአት ወደ ሌላኛው ኃጢአት ስለሚመራ በመጀመሪያ ከስሜት ወደ አሳብ፤ ቀጥሎም ወደ ልብ፤ ከዚያም ወደ ድርጊት ያሸጋግራል፡፡

#ቁጣን_በተመለከተ ...

ይኼኛውን «ነርቭን መግዛት» ልንለው እንችላለን፡፡ እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ቃል መንፈሳዊው ሰው ዘወትር ከቁጣ ለመራቅ ይሞክራል:: «...የሰው ቁጣ የእግዚአብሔርን ጽድቅ አይሠራምና።» ያዕ. 1፥20:: እርሱ ንዴት በልቡ ውስጥ መንቀሳቀስ መጀመሩን ሲያውቅ ምላሱንና ነርሹን እንዲቆጣጠሩበት አይተዋቸውም:: ስለሆነም በቁጣ ጊዜ ቃላቱን በሚገባ ለመቆጣጠር እንዲችል ወይ ዝም ማለትን ይመርጣል አሊያም ንግግሩ እንዲዋጥ ያደርጋል፡፡

ከሁሉ በላይ ደግሞ ቁጣን ከልቡ ውስጥ ያባርራል:: በዚህም በሚችለው ሁሉ በቁጣ እንዳይቀጣጠልና ድምፁ ከፍ ብሎ እንዳይወጣ ያደርጋል። በተጨማሪም ገጹን አያጨፈግግም:: በዚህ ጊዜ አኳኋኑ ሁሉ የሐዋርያውን ቃል የተከተለ ይሆናል፡፡ «ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ ለመናገርም የዘገየ ይሁን . . » ያዕ. 1፥19:: ለቁጣ የፈጠነ ሰው በጥድፊያ ስለሚወድቅ ብዙ ኃጢአት ይፈጽማል: በተረጋጋ ጊዜ በወሰደው የተሳሳተ እርምጃው አብዝቶ ይጸጸታል። በመጨረሻም መስኮታዊውን መልክ ስለሚያጣ ለብዙዎች የማሰናከያ በቁጣው ውስጥ ድንጋይ ይሆናል።

መንፈሳዊው ሰው በቁጣ ውስጥ እያለ ደብዳቤ አይጽፍም:: ብስጭት ውስጥ እያለም ውሳኔ አይወስንም:: ምናልባት ግን በቁጣ ውስጥ እያለ ደብዳቤ ከጻፈ ተጣድፎ ወደ ፖስታ ቤት አይልከውም ለአንድ ለሁለት ቀን እንዳለ ያስቀምጠዋል:: ከዚህ በኋላ በድጋሚ ያነበውና ወይ ቀዶ ይጥለዋል አለበለዚያም ሌላ ይጽፋል:: ይህን በማድረጉም ይህ ነገር በእርሱ ላይ የኃጢአት መረጃ እንዳይሆንበትና ውጤቱም የማያስደስት ሆና እንዳይቀር ያደርጋል:: በተናደደ ጊዜ ውሳኔዎቹን የሚወስደውም ባለማስተዋል ነው:: እንደነዚህ ዓይነቶቹ ውሳኔዎች «ስሜታዊ ውሳኔዎች» ተብለው ይጠራሉ:: ብዙዎቹ የተሳሳቱና ተገቢ ያልሆኑ ውሳኔዎች ናቸው:: ከዚህ ጋር በተያያዘ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል:: «በነፍስህ ለቁጣ ችኩል አትሁን፤ ቁጣ በሰነፍ ብብት ያድራልና: መክ. 7፥9::

ይቀጥላል....

(#በብፁዕ_አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
#መንፈሳዊ_ሰው_መጽሐፍ  ገጽ 122-128
#በአያሌው_ዘኢየሱስ_የተተረጎመ)


#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

የስብከተ ወንጌልን ተደራሽነት ለማስፋት 36 ሰባኪያነ ወንጌል ተመረቁ ፡፡

በጉጂ፣ ምዕራብ ጉጂ ፣ ቦረና ፣ ምሥራቅ ቦረና እና ሊበን ዞኖች ሀገረ ስብከትና በማኅበረ ቅዱሳን ትብብር  የአገልጋይ እጥረት ካለባቸው ከተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ  36 ሠልጣኞች ለ 3 ወራት  የተለያዩ ሥልጠናዎችን ሲከታተሉ  ቆይተው  ታኅሣሥ 7 ቀን 2016 ዓ.ም  ሊቀ ማዕምራን ጌታሁን ሞርኪ የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅና የተለያዩ የሀ/ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና ምእመናን በተገኙበት ተመርቀዋል፡፡

     በሀገረ ስብከቱ የሚታየውን የሰባኪያነ ወንጌል እጥረት መቅረፍና ስብከተ ወንጌልን ማስፋት ዓላማውን ያደረገው ሥልጠና  ትምህርተ ወንጌልን በተለያዩ ቋንቋዎች ተደራሽ ለማድረግ ሠልጣኞቹ የኦሮምኛ፣ጌድዮኛ፣ ኮንሶኛ፣ ሶማልኛና አማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ  በመሆናቸው የቤተክርስቲያንን ሐዋርያዊ ተልእኮ ከማስፈጸም አንጻር ጉልህ ሚና እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል።  

በሥልጠናውም ነገረ ሃይማኖት ፣ የቤተክርስቲያን ታሪክ፣ የስብከት ዘዴ ፣ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣ ነገረ ቅዱሳን፣ ነገረ ድኅነት እና ሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች የተካተቱ ሲሆን  ሥልጠናው በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት ከ 6 ዓመታት በፊት በነገሌ ቦረና ለሀ/ስብከቱ በተሠራው  አዳሪ አብነት ት/ቤት የተሰጠ መሆኑም ተገልጿል፡፡

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

   አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ

የሚያየውን ዓለም ለውጦ ባላየው
ሳሙኤል በትኅርምት ስላገለገለው
የሰማዩን መንግስት አምላክ አወረሰው
ከሀገሩ ወጥቶ ተከዚን መሻገር
ኮሮጆ አልያዘም አልያም ወርቅ ብር
የርሱ ወርቅ እንቁ በገዳሙ ሲኖር
የድንግል ቅዳሴ ውዳሴዋ ነበር
በጽድቅ በትሩፋት ብርሃን ቢሆን ለዓለም
ለእርሱ ተገዙለት አናብስተ ገዳም
አምላኩ በሰጠው ክቡር ቃልኪዳን
ጻድቁ ሳሙኤል እንዲያማልደን
በስሙ እናስብ ችግረኛውን
በጻድቁ ስም በጎ የሠራ በፍቅር
ያገኘዋልና የጻድቁን ክብር




#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ራስን መግዛት (ክፍል -፩)

መንፈሳዊው ሰው ካሉት ብቃቶች መካከል አንዱና ዋነኛው ራስን መግዛት ነው፡፡ እርሱ ራሱን ለሥጋ ምኞትና ለፍላጎቶቹ አሳልፎ አይሰጥም፡፡ ሕሊናው የኃጢአትን ምኞት ሲናፍቅ ይህን አሳቡን በመቃወም መንፈሱ እንድትመራው በማድረግ ራሱን አጥብቆ ይገዛል:: መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል:- «በመንፈሱ ላይ የሚገዛ (መንፈሱን የሚገዛ) ከተማ ከሚወስድ ይበልጣል፡፡» ምሳ. 16፥32

እንደ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት ራሱን የሚገዛ ወይም የሚመራ ማለት ሥጋው የጠየቀውን ሁሉ የማይሰጥ ይልቁኑ የሚቃወም ማለት ነው:: «ነፍሱን የሚወድ ያጠፋታል፤ነፍሱን በዚህ ዓለም የሚጠላ ለዘላለም ሕይወት ይጠብቃታል፡፡» ዮሐ. 12፥25።

ራስን መግዛት በውስጡ የተለያዩ ክፍሎች እንዳሉት እርግጥ ነው፡፡ እነርሱም፤-

1. #ምላስን_መግዛት፡፡
2. #አሳብን_መግዛት::
3. #ልብን_መግዛት፡፡ (ፍላጎትንና ምኞትን በመግዛት)
4. #ስሜትን_መግዛት::
5. #ሆድን_መግዛት (ምግብን በተመለከተ) ናቸው፡፡

ራሱን የሚመራ ሰው እርሱነቱን ለእሴትና ለዓላማ እንዲሁም ለሕግና ደንብ ያስገዛል፡፡ ራሱን መምራት የማይችል ሰው ግን በእርግጥ እርሱነቱን ለጥፋት ይጋብዛል፡፡ ራሱን የሚገዛ ሰው ነፍሱን በእውነተኛ ፍቅር ይወዳታል:: ራሱን የሚያቀናጣ ግን ነፍሱን ከማጣቱም በላይ ሌሎችም ከእርሱ ጋር አብረው እንዲጠፉ ያደርጋል፡፡ ራሱን አጥብቆ የሚጠብቀው በትጋቱ ነፍሱን ስለሚጠብቃትና በመልካም ሁኔታ ስለሚይዛት ያድናታል፡፡ አልፎ ተርፎም ሌሎችን ለማዳን ምክንያት ይሆናል፡፡ የራሱን አመለካከትና ግንኙነት በቅደም ተከተል ያደራጃል፡፡ በመጀመሪያ እግዚአብሔርን ያስቀድማል፤ በመቀጠል ሰዎችን ያስከትላል፤ በመጨረሻም ራሱን።

#ምላስን_መግዛት፡፡

መንፈሳዊው ሰው ቃላት ወይም አሳቦች ያቀበሉትን ወደ አእምሮው የመጡትን ሁሉ በአንደበቱ አይናገራቸውም፡፡ እያንዳንዱን ቃል ከአንደበቱ ከማውጣቱ በፊት ይመዝናል:: የእርሱ ሚዛን የሚለካው የቃሉን ፍሬ ነገር ብቻ ሳይሆን ትክክል መሆኑንና አለመሆኑንም ጭምር ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የእርሱ ዋና ዓላማው ቃሉ በሌሎች ሰዎች ላይ የሚያመጣውን ተጽዕኖ፣አፀፋና ውጤቱን ጭምር ነው::

የምላስ ወይም የአንደበት ስህተት ውጤት ሥጋን ማሳደፉንና የፍጥረትንም ሩጫ ማቃጠሉን የሚያውቅ ሰው ከመናገሩ በፊት ከፍተኛ ጥንቃቄ ያደርጋል:: ያዕ. 3፥5-6:: ከነቢዩ ከዳዊት ጋር ሆኖም:- «አቤቱ ለአፌ ጠባቂ አኑር፤ የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ፡፡» ይላል፡፡ እርሱ አንዴ ከአፉ የወጣው ቃል ተመልሶ ሊገባ እንደማይችል ያውቃል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ከአፉ የወጣው ቃል አድማጮቹ ጆሮ ከደረሰ በኋላ የተናገረውን መልሶ ሊውጠው፣ ወይም ይቅርታ ሊያገኝበት እንደማይችል አስቀድሞ ያውቃል:: ከዚህ በኋላ ስህተቱን ለማስተካከል ቢጥርም ጥፋቱ በእርሱ ላይ ዕዳ ሆኖ እንደሚቆጠር አጥብቆ ይረዳል፡፡ ከሁሉ በላይ ደግሞ ጌታ እንደተናገረው እንደሚኮነንበት ያውቃል፡ . . . ከቃልህ የተነሣ ትጸድቃለህና፤ ከቃልህም የተነሣ ትኮነናለህ፡፡» ማቴ. 12፥37::

#ይቀጥላል...

(#በብፁዕ_አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
#መንፈሳዊ_ሰው_መጽሐፍ  ገጽ 122-128
#በአያሌው_ዘኢየሱስ_የተተረጎመ)



#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ቁጣ_ድል_አይንሣህ
(#ምክር_ወተግሣጽ_ዘማር_ይስሐቅ)

ወንድምህን ከሚገባው ይልቅ ለማክበር ሰውነትህን አትጋት። ባገኘህውም ጊዜ እጁን እግሩን ሳመው፤ በጎ አድርግለት አክብረህ ወደህ እየው፡፡ ሥራው ባይደለ ሥራ አመስግነው፣ ከአንተም በተለየ ጊዜ የእሱን ነገር ተናገር፡፡ ከበጎ ሥራው ወገን መናገር በሚቻልህ ገንዘብ በጎ በጎ አድርግለት፡፡

በጎ ነገር በመናገርህ ወደ በጎ ሥራ ትስበዋለህ ታነቃቀዋለህ፡፡ አንተ ባመሰገንከው ምስጋና፣ አንተ ባከበርከው ክብር የተነሣ ያፍር ዘንድ እንዳመሰገንከው ያልሆነ እንደሆነ ያፍራል፤ እንዲህ የሆነ እንደሆነ ዘርአ ትሩፋትን ትዘራበታለህ፡፡

ነፍስህ ከለመደችው ባልንጀራህን ከማክበር የተነሣ በጎ ነገርን መውደድ በልቡናህ ይቀርጻል፡፡ ፍጹም ትሕትናን ገንዘብ ታደርጋለህ ሳትጥር ብዙ ሥራ ትሠራልህ፡፡ የምታከብረው በጎውን ሰው ብቻ አይደለም ነውር ያለበትም ቢሆን አክብረው እንጂ፡፡ እንዲህ የሆነ እንደሆነ አንተ ካከበርከው ክብር የተነሣ አፍሮ ካንተ ድኅነትን ያገኛል።

ገንዘብህ የምትሆን ይህችን ጥበብ ለሁሉ አድርጋት፤ ጥበብም የተባለች ሰውን ማክበር ለሰው ማዘን መራራት ናት። አንዱንስ እንኳን አትቈጣ፣ ተቈጥተህ አታሳዝነው፣ ቍጣ ድል አይንሳህ፡፡ ስለ ሃይማኖትም ቢሆን፣ ሥራው ክፉ ስለሆነም ቢሆን ሰው እንዳታማ ተጠበቅ እንጂ አትፍረድበት፡፡ በልዕልና ፊት አይቶ ሳያዳላ የሚፈርድ ዳኛ ክርስቶስ አለንና፡፡ ወደ በጎ ሥራም ልትመልሰውም ብትወድ እዘንለት፤ እያለቀስህ የለዘበ ነገር ንገረው፤ በቍጣ አትናደድበት፤ ጸብ ያለህ ይመስለዋል ፍቅር ውስጣዊ ቍጣን አይሻምና።

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

+++ የአንድ ኃጢአተኛ ሰው ጸሎት ++


ይህሄን ድንቅ ምክር ትምህርት እና ጸሎት በትእግስት ከቻላችሁ ደጋግማችሁ አንብቡ ባይቻላችሁ አንደ ታነቡ ዘንድ አደራ እላችኋለሁ



        ( ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ )

አቤቱ “በጎውን ነገር ማን ያሳየናል?” የምንልበት ዘመን አይደለም፤ እንኳን በእኛ ዘንድ ይቅርና ወንጌል በአሕዛብ ዘንድ ሳይቀር የተሰበከበት ዘመን ነውና። ነገር ግን የተሰበከውን ቃል በልቤ አኑሬ ሕይወቴን ሳልለውጥበት ብዙ ዘመናትና ዓመታት አለፉ። ቃልህን ሰምቶ አለማድረግ በአንተ መዘባበት መሆኑን አውቃለሁ፤ ቃልህን የምሰማ እንጅ የምፈጽም ባለመሆኔም ምክንያት በድቡሽት ላይ እንደተሠራ ቤት ሆኛለሁ። ጥልቀት በሌለው አኗኗር ላይ የተገነባው መንፈሳዊነቴ ጎርፍ በጎረፈ፣ ነፋስ ባለፈ ጊዜ የሚናወጥ ደካማ ሆኖብኛል።

ዓለምን ለማሳለፍ ዳግመኛ መምጣትህን ባሰብሁ ጊዜ እደነግጣለሁ። ጻድቃን “አሜን ጌታ ኢየሱስ ሆይ ቶሎ ና” እያሉ የምትመጣበትን ቀን ሙሽራዋን እንደምትጠብቅ ሴት በተስፋ ይጠባበቃሉ፤ እኔ ግን አሁንም ለንስሐ ዕድሜ እንድትጨምርልኝ እለምናለሁ። ለንስሐ ብየ የለመንሁትን ዕድሜ አሁንም ማለቂያ ለሌለው ፍላጎቴ ባውለውም አንተ ግን የለመንሁትን ዕድሜ ሰጥተህ አጠገብኸኝ። ሰው ምን ቢቸግረው ነው የሠርጉን ቀን የሚያራዝመው? የደስታ ቀኑ እንዳትደርስ የሚከላከል ሰው ማለት እኔ ነኝ። አንተ የምትመጣበት ቀን ከዓለም አስቀድሞ ያጨኻትን የጻድቃንን ነፍስ እንደ ሴት ሙሽራ በአፍህ መሳም ስመህ መኃ 1፥2 የምትቀበልበት ቀን ነው።

ፀሐይና ጨረቃ በማያስፈልጓት ከተማ ለመኖር ጻድቃን ራሳቸው እንደ ፀሐይና ጨረቃ የሚያበሩበትን ያንን ቀን በቶሎ እንዲመጣ አለመለመን እንዴት ያለ ሞኝነት ነው? ያንጊዜ ታላቅ ደስታ ይደረጋል፤ ሙታንን የሚያነቃቸው ታላቁ ዝማሬ በሰማያውያን መላእክት ይጀመራል፤ መላእክት “ቅዱስ እግዚአብሔር” ሲሉ ምድራውያን ጻድቃንም “ቅዱስ ኃያል.......”  እያሉ ያንን ዝማሬ ሊቀበሉ ከመቃብራቸው ይወጣሉ። ሞት ያንን ምስጋና ሰምቶ ይደነግጣል። ዲያብሎስ ይገሠጻል።

በእውነት የዚያን ቀን የሚደረገው ተድላ ደስታ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እስካሁን አልተደረገም። እመቤታችን “ተፈሥሒ” የሚለውን የምስጋና ቃል በሰማች ጊዜ ያገኘችውን ደስታ ጻድቃን ያንጊዜ ያገኙታል። ያችን የደስታ ቀን ባለመዘጋጀቴ መድረሷን እየቸኮሉ ከሚጠባበቁት ውስጥ አይደለሁምና አዝናለሁ።

ጌታዬና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ያንን ቀን በደስታ እንድጠብቅ እንጅ ባሰብሁት ጊዜ ከመደንገጥ አውጣኝ። አውቃለሁ ጌታዬ ዛሬ ቃልህን ሰምተው ደስ የማይላቸው ሰዎች ያንጌዜ “ንዑ ኀቤዬ” የሚለውን ቃልህን ሰምተው ደስ አይላቸውም። ያንጊዜም ደስታን የሚሰጠን ዛሬ የምንሰማው ቃልህ ነው።

ይህንንማ በመካከላችን ስብከትን በጀመርህባት ቀን “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” ባልኸን ጊዜ ገልጠህልን ነበር። መንግሥተ ሰማያት ብለህ የጠራሃት ቃልህን መሆኑን መምህራኖቻችን፥ “መንግሥተ ሰማያት፡− ሕገ ወንጌል፣ ሕገ ወንጌል፡− ተስፋ፣ ተስፋ፡− እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው” ብለው ተርጉመው ነግረውን ተረድተን ነበር። መንግሥተ ሰማያትን በመካከላችን ያኖርህልን ሆይ! ቃልህን በሰሙ ጊዜ የማር ወለላ እንዳቀረቡላቸው ሕጻናት ሳስተው እንደሚሰሙህ ወዳጆችህ እንድሆን እርዳኝ።

ደፍሬ ስምህን መጥራቴን ሳስብ አንዳንድ ጊዜ ፍርሃት ይይዘኛል፤ ደግሞ “ሰውን የምትወድ ሆይ” ብለው ካህኑ በቅዳሴ ጊዜ ሲጠሩህ ስሰማ ፍርሀቴን ያርቅልኛል። አንተ በምትከብርበት መቅደስ ውስጥ ገብቼ መቆሜንም ሳስብ በቅዱሳን ጉባኤ መካከል የአንድ ኃጢአተኛ የእኔ መገኘት ያስጨንቀኛል፤ ነገር ግን ካህኑ በቅዳሴው መካከል “ወንጌል” ብለው ወጥተው “ኃጥአንን ለንስሐ እንጅ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም” የሚለውን ቃልህን ሲያነቡ በሰማሁ ጊዜ በሰጠኸኝ ዕድል ድምጼን ከፍ አድርጌ አመሰገንሁህ።

ሰዎች እስኪገርማቸው ድረስ በእኔ በቀራጩ ቤት መዋልህ ለምንድነው? በፊትህ በድለው ከማያውቁ መላእክት ይልቅ የእኔን ምስጋና ለመስማት መምጣትህ ለምንድነው? ሰውን መውደድህ ያስደንቃል!
ከተግሣጽህ ይልቅ ፍቅርህ ማርኮኝ መጥቻለሁ። ደዌ ከጸናበት ሰው በቀር ሀኪሙን በብርቱ ፍለጋ ማን ይፈልገዋል? እኔም ደዌ ነፍስ ቢጸናብኝ ኃጢአት ቢያስጨንቀኝ መጥቻለሁና ፈውሰኝ። ላገለግልህ ብወድም እንደ ሐማተ ጴጥሮስ ሳልፈወስ ላገለግልህ አልፈቀድሁም። ለአንተ ምን ይሳንሃል? ከለምጼ ልታነጻኝ ብትወድ ይቻልሃል።

ከአልጋዬ ልታነሣኝ ብትወድስ ማን ይከለክልሃል? ፈውሰኝና ዕድሜዬን በሙሉ አገልጋይህ አድርገኝ። ሳልፈወስ ባገለግል ደዌዬ ወደ ሌሎችም እየተዛመተ ብዙዎችን ይበክላል። ይሁዳ ባዛመተው ገንዘብ መውደድ፣ አፍኒንና ፊንሐስ በጀመሩት የመቅደስ ውስጥ ድፍረት፣ ዳታንና አቤሮን ባቀጣጠሉት ዘረኝነት፣ ሲሞናውያን ባሳዩት ጉቦኛነት ተይዘው ያልተፈወሱ ብዙ ናቸው፤ የእኔም ተጨምሮ የፈውስ ጊዜአችንን እንዳያርቅብን ስለምፈራ ፈውሰኝና አገልጋይህ ልሁን።

እኔ ሥጋህንና ደምህን የምቀበለው ዝቅ ብለህ አጥበህ እንዳነጻሓቸው እንደ ሐዋርያት ንጹሕ ሆኜ አይደለም፤ እንዲያውም ስቆርብ ያዩኝ ሰዎች ገርሟቸው “ይሄ ኃጢአተኛ ሰው ቆራቢ ለመባል ብሎ ነው እንጅ አምኖበት ነው?” ብለው ተሳለቁብኝ። በሽታ የጸናበት ሰው መድኃኒቱን የሚወስደው ደዌው እንዲለቀው እንጅ ደዌው ከለቀቀው በኋላ ነውን? እኔስ ይህ ቍርባን ፈራጅ እንደሆነ ባውቅም ማኅየዊ እንደሆነም አምናለሁ።

ሐዋርያት “የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል” 1ዮሐ 1፥7 ብለው ያስተማሩት ትዝ ይለኛል። የምትፈርድብኝ ፍርድ ሳይሆን “እንካችሁ ብሉ ሥጋዬን፣ እንካችሁ ጠጡ ደሜን” ብለህ ወደ እኔ የዘረጋሃት እጅህን አያታለሁ። ስለዚህም አፌን ከፍቼ እቀበልሃለሁ።

ዛሬ “በምሕረትህ ብዛት ወደ ቤትህ እገባለሁ አንተን በመፍራትም ወደ ቅድስናህ መቅደስ እሰግዳለሁ” ዳግመኛ በምትመጣ ጊዜም በምሕረትህ ብዛት በሚያስፈራና በሚያስደነግጥ ዙፋንህ ፊት እቆማለሁ። ጭብጥ አፈር ወደ ባሕሩ ቢወረወር ባሕሩን ያደፈርሰዋልን? የእኔ የኃጢአተኛው ወደ መቅደስህ መግባትስ ያንተን ባሕርይ ያሳድፈዋልን? በእውነት በስምዖን ቤት መዋልህ ስምዖንን ያነጻዋል እንጅ አንተን አያረክስህም። ማርያም ኃጥዕት እግርህን ያጠበችበት እንባ እሷን አነጻት እንጅ አንተን አላረከሰህም። ደም የሚፈሳት ሴት ልብስህን በመንካቷ ካንተ የወጣው ኃይል እሷን ጎበኛት እንጅ አንተን አልለወጠኸም። እኔም ወደ ቤትህ የምገባው ይህንን እያሰብሁ ነው።

በተራራው ስብከት ጊዜ ተገኝቼ ስታስተምር ባልሰማህም፤ በደብረ ታቦር በተገለጥህ ጊዜ ክብርህን ካዩት መካከል ባልሆንም፤ በደብረ ዘይት እጅህን ጭነህ ከሾምኻቸው ውስጥ ባልመደብም አንተ ግን ለእኔ ምሕረት ማድረግን አትሰለችም። ወደ አንተ ባልመጣ እንኳን በተኛሁበት መጥተህ “ልትድን ትወዳለህ?” ማለትህ አይቀርም።

ከሰማይ የወረድህልኝ ሆይ! ኢያሱ ለእስራኤል ርስታቸውን እስኪያወርሳቸው ፀሐይን እንዳቆምህለት በምድር ላይ ያለን ኃጥአን ልጆችህ ሰማያዊት ርስትህን ሳንወርሳት ፀሐይ አትጥለቅብን፤ ዕድሜአችን አይለቅብን።  አሜን!
 
@ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ


     #ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

[

የእመቤታችን ወደ ቤተ መቅደስ መግባት
✍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
♥❖♥ ኢያቄምና ሐና ቃል ኪዳናቸውን ለመፈጸም ዘመዶቻቸውን ባልንጀሮቻቸውን ከነልጆቻቸው በመጥራት ሕፃን ልጃቸውን እመቤታችንን ልዩና ንጹሕ ልብስን አልብሰው በመንፈሳዊ ዝማሬ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ መብራትን በእጆቻቸው ይዘው እያበሩ ኢየሩሳሌም ወዳለው ቤተ መቅደስ ወሰዷት፤ ያን ጊዜም ሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ በካህናቱ ታጅቦ የምስጋና ዝማሬን ከልኡካኑ ጋር እያሰማ እነርሱን ለመገናኘት ከመቅደስ ወጣ።

♥❖♥ በዚያም ሊቀ ካህናቱ ብቻ ወደሚገባበት ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ የሚያስወጡ ፲፭ ደረጃዎች ሲኖሩ በየደረጃዎቹም መዝሙረ ዳዊት ተደጋግሞ ሲደረስባቸው ከሚጸለዩት የዳዊት መዝሙራት ውስጥ መዝ ፻፲፰(፻፲፱)-፻፴፪ (፻፴፫) የሚገኙ ሲኾኑ እነዚኽንም የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት አጥኚዎች “Psalms of Ascent” (የመውጣት መዝሙራት) ይሏቸዋል::

♥❖♥ እናትና አባቷም ሊቀ ካህናቱን ካለበት ቅዱስ ቦታ ወደነርሱ እስኪመጣ ለመቆየት ልጃቸው ማርያምን ከአንደኛው ደረጃ ላይ ቢያኖሯትም ርሷ ግን በድንቅ አምላካዊ ሥራ መንፈሳዊ ኀይልን ተመልታ የሦስት ዓመቷ እመቤታችን ያለምንም ረዳት ብቻዋን ደረጃዎቹን በመውጣት በእጅጉ ወደተቀደሰው ሊቀ ካህናቱ ብቻ ወዳለበት ስፍራ ኼደች ርሱም በእጅጉ ተደንቆ ባረካት፤ ያን ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ለሊቀ ካህናቱ የሰው ዘርን በመላ ወደ ገነት የሚያስገባ ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት የእግዚአብሔር ልጅን የምትወልደው ርሷ እንደኾነች ገልጾለት ቦታዋም በጣም የተቀደሰውና ርሱ መሥዋዕት ለማቅረብ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ የሚገባበት ከርሱ በቀር ማንም ሰው የማይገባበት ቅድስት ቅዱሳን ውስጥ መኾኑን ገልጾለታል ፡፡

♥❖♥ ርሱም ይኽነን የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራን በማድነቅ ይኽቺን የመሰለች ልጅ ምን እናደርጋታለን? ምን እናበላታለን? ምንስ እናጠጣታለን? ምን እናነጥፍላታለን? ብሎ ሲጨነቅ ለእስራኤል ደመና ጋርዶ መናን አውርዶ የመገበ፤ ለኤልያስም በመልአኩ እጅ በመሶበ ወርቅ ኅብስት የመገበ፤ ለዕዝራ ሱቱኤልም በመልአኩ በቅዱስ ዑራኤል እጅ መልኩ እሳት የሚመስል ጽዋዐ ልቡና ያጠጣው ልዑል እግዚአብሔር ለእናትነት ወደ መረጣት ወደ እናቱ መልአኩ ፋኑኤልን ላከላት (ዘፀ ፲፮፥፴፩፤ ፩ነገ ፲፱፥፮፤ ዕዝ. ሱቱ. ፲፫፥፴፰-፵፩)::

♥❖♥ ከዚያም “ወሶቤሃ ወረደ ፋኑኤል ሊቀ መላእክት ወጸለላ በአክናፊሁ ወተለዐለ ላዕለ መጠነ ቆመ ብእሲ ወወሀባ ወመጠዋ ወዐርገ ውስተ ሰማይ” ይላል በዚያን ጊዜ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል ኅብስት ሰማያዊን፤ በብርሃን ጽዋዕ ስቴ ሕይወትን ይዞ ረብቦ በመውረድ አንድ ክንፉን አንጽፎ አንዱን ክንፉን አጐናጽፎ ከመሬት የሰው ቁመት ያኽል ከፍ አድርጓት ኅብስቱን መግቧት ጽዋውን አጠጥቷት ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡

♥❖♥ ስላዩትና ስለተደረገው ነገር ኹሉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ አማናዊት የአምላክ መቅደስ የአካላዊ ቃል ታቦት እመቤታችንን ምሳሌዋ ወደሚኾነው ቤተ መቅደስ ታኅሣሥ ፫ በ፭ሺሕ ፬፻፹፰ (5488) ዓመተ ዓለም በሦስት ዓመቷ አስገብተዋታል፤ ከዚያም ኢያቄምና ሐና ወደ ቤታቸው ተመልሰዋል፡፡

♥♥♥ የቅድስት ድንግል ማርያም የቤተ መቅደስ ሕይወት በእጅጉ አስደናቂ ሲኾን የቤተ ክርስቲያናችን ቅዱስ ትውፊት (Holy Tradition) እንደሚያስረዳን ቤተ መቅደስ በኖረችባቸው 12 ዓመታት የእግዚአብሔርን ሕግ በማጥናት ቅዱሳት መጻሕፍትን በማንበብ ለቤተ መቅደስ የሚያስፈልገውን ነገር በእጆቿ እየሠራች በፍጹም ንጽሕና ቅድስና ኾና እግዚአብሔርን በማመስገን መላእክት እያገለገሏት ኖራለች፡፡

ይኽነን በቤተ መቅደስ የነበራትን ቆይታ ቀደምት የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በጥልቀት ጽፈዋል እነሆ የሊቃውንቱ ቃል፦

፩) [አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታ በማሕሌተ ጽጌ]
“የሐዝነኒ ማርያም ዘረከበኪ ድክትምና
አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ እንዘ ትጠብዊ ሐሊበ ሐና
ወያስተፌሥሐኒ ካዕበ ትእምርተ ልህቀትኪ በቅድስና
ምስለ አብያጺሁ ከመ አብ እንዘ ይሴስየኪ መና
ፋኑኤል ጽጌ ነድ ዘይከይድ ደመና”
(ማርያም የሐናን ወተት እየጠባሽ ወደ ቤተ መቅደስ በገባሽ ጊዜ ያገኘሽ ብቸኝነት ያሳዝነኛል፤ ዳግመኛም በደመና የሚመላለስ ደመናን የሚረግጥ የእሳት አበባ ፋኑኤል ከጓደኞቹ መላእክት ጋር መናን እየመገበሽ በንጽሕና የማደግሽ ተአምር ደስ ያሰኘኛል)♥

♥“ከመ ታቦት ሥርጉት በወርቀ ዐረብ ወተርሴስ
በድንግልና ማርያም ስርጉተ ሥጋ ወነፍስ
ተአምረ ነቢር አርአይኪ በቤተ መቅደስ
ኢያቄም ወሐና ቀንሞስ ቀናንሞስ
እምዘጸገዩኪ ለጳጦስ በዓመት ሠላስ”
(በዐረብና በተርሴስ ወርቅ እንዳጌጠች ታቦት በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ያጌጥሽ ማርያም፤ ቀንሞስ ቀናንሞስ የሚባሉ ሽቱዎች ኢያቄምና ሐና ለጳጦስ ምሳሌ የኾንሽ አንቺን ከአስገኙሽ ዘንድ በሦስት ዓመት በቤተ መቅደስ የመኖር ተአምርን አሳየሽ)
       ++++++++++++++
፪) [ሊቁ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም]
♥♥♥ “ኦ ድንግል አኮ በተላህዮ ዘልሕቂ ከመ አዋልደ ዕብራውያን እለ ያገዝፋ ክሣዶን አላ በቅድስና ወበንጽሕ ውስተ ቤተ መቅደስ ነበርኪ…” (ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም፤ በንጽሕና በቅድስና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ፤ ድንግል ሆይ ምድራዊ ኅብስትን የተመገብሽ አይደለም፤ ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ኅብስትን ነው እንጂ፤ ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም፤ ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን ነው እንጂ፤ ድንግል ሆይ ከአንቺ አስቀድሞ ከአንቺም በኋላ እንዳሉ ሴቶች መተዳደፍን የምታውቂ አይደለም፤ በንጽሕና በቅድስና ያጌጥሽ ነሽ እንጂ፤ ድንግል ሆይ የሚያታልሉ ጐልማሶች ያረጋጉሽ አይደለም የሰማይ መላእክት ጐበኙሽ እንጂ እንደተነገረ ካህናትና የካህናት አለቆች አመሰገኑሽ እንጂ)
          +++++++++++++++++++
፫)  [በ፭፻፭ (505) ዓ.ም የተወለደው ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድም በአንቀጸ ብርሃን]

♥“አንቲ ውእቱ ንጽሕት እም ንጹሓን ድንግል ኅሪት ዘነበርኪ ውስተ ቤተ መቅደስ ከመ ታቦት ዘግቡር እምዕፅ ዘኢይነቅዝ…” (ከንጹሓን ይልቅ ንጽሕት የኾንሽ አንቺ ነሽ፤ ከማይነቅዝ ዕንጨት እንደተሠራ በወርቅ እንደተጌጠና ዋጋው ብዙ በኾነ በሚያበራ ዕንቊ እንደተለበጠ ታቦት በቤተ መቅደስ ውስጥ የኖርሽ የተመረጥሽ ድንግል ነሽ፤ እንዲኽ ኾነሽ በቤተ መቅደስ ውስጥ ኖርሽ፤ መላእክት ዘወትር ምግብሽን ያመጡ ነበር፤ መላእክት እየጐበኙሽ እንዲኽ ዐሥራ ኹለት ዓመት ኖርሽ፤ መጠጥሽም የሕይወት መጠጥ ነበር፤ ምግብሽም የሰማይ ኅብስት ነበር)

♥ “መላእክት እመቤታችንን እኅታችን ይሏታል፤ በክንፋቸው ይጋርዷታል፤ በማር ወለላ የተመሰለ የእግዚአብሔር ቃል ከከንፈሮቿ ይፈስሳል፤ ጒንጮቿ እንደ ሮማን ቅርፍት ናቸው፤ ልዑል ወደዳት፤ ዳዊት በመዝሙሩ አመሰገናት፤ በቤተ መቅደስ ተቀበሏት) (ቅዱስ ያሬድ፤ መጽሐፈ ድጓ)

 ♥ ጌታ የመረጠሽ ማርያም ሆይ ለምኝልን፤ ዕፀ ጳጦስ ተብላ የተጠራችውን እመቤታችን ዘካርያስ በቤተ መቅደስ ተቀበላት፤ ኹላቸውም ቅዱሳን ዐዲሲቱ እንቦሳ ይሏታል)


#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

💧💦💧💦💧💦💧💦💧💦💧💦
     ጾምና ጸሎት በአበው አንደበት

👉  "ነፍስ የሌለው ሥጋ የሞተ እንደሆነ እንዲሁ ጸሎትን የማታደርግ ነፍስ ሕይወት የላትም።" 
                             ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

👉  "ጾም የነፍስን ቁስል ትፈውሳለች ፣ የሥጋ ምኞትንም ታሥታግሳለች ለወጣቶች ትዕግሥትን ታስተምራቸዋለች።"            ቅዱስ ያሬድ

👉  "ጾም ጸሎት ከስግደትና ከምጽዋት ጋር ከሆነ የጦር ዕቃ ነው።"   ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ

👉  "ጸሎት የእኛን ፈቃድ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር አስማምተን የምንመራበት ነው።"    
                                            ቅዱስ ኤፍሬም

👉  "የማይጸልይ ሰው ቅጽር የሌላትን ሀገር ይመስላል ያን ማንም እየገባ እንዲዘርፈው እርሱም የተሰጠውን ጸጋ ያጣል።"  
                                       ማር ይስሐቅ

#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

እንኳን ለነቢየ ልዑል ለቅዱስ አልያስ ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ! አደረሰን!

💠ቅዱስ አልያስ ማለት በአጭሩ፦
አክአብና ኤልዛቤል ጣዖት በማምለከታቸው ኤልያስ 3 ዓመት ከ6 ወር ዝናብን እንዳይዘንብ በጸሎቱ ያቆመ፤

💠የሰራጵታዋን መበለት የሞተ ልጇን ከሞት ያስነሣ፤
💠 የአቀረበውን መሥዋዕት እሳት ከሰማይ ወርዶ0 ስለበላለት መሥዋዕቱን እግዚአብሔር የተቀበለለት፤
💠ከ3 ዓመት ከ6 ወር በኋላ ቀርሜሎስ ወጥቶ በመጸለይ ዝናብ እንዲዘንብ ያደረገ፤
💠አካዝያስ የላካቸውን 50 አለቃዎችን እሳት ከሰማይ አውርዶ ያቃጠለ፤

💠በመጐናጸፊያው የዮርዳኖስን ወንዝ የከፈለ፤
💠በእሳት ሠረገላ በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ የዐረገ፤
በደብረ ታቦር ጌታ ምሥጢረ መንግሥቱን ሲገልጽ ከሙሴ ጋር አብሮ የተገኘ፤

💠ዳግመኛ በመምጣት በሐሳዌ መሲሕ ጊዜ መጥቶ ሰማዕትነትን የሚቀበል እጅግ ክቡር ነቢይ ነው።

ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ "ቴስቢያዊ፣ ኮሬባዊ (ወደ ኮሬብ ተራራ የወጣ)፤ ታቦራዊ (በታቦር ተራራ የተገኘ)፤ ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን የለጐመ ለኾነ፤ የጸሎቱ ቃልም በአዶናይ ጆሮ ውስጥ ለተሰማ፤ ውኃውን እስኪበላ ደርሶ እሳትን ከሰማይ ያወረደ ለኾነ፤ በእሳት ሠረገላ ተጭኖ ወደ ተድላ ደስታ ቦታ ለገባ ለነቢዩ ለኤልያስ ሰላምታ ይገባል) ሲል አወድሶታል።

ሊቁ አርከ ሥሉስም በአርኬ መጽሐፉ ላይ፦ "ምድራዊ የሆነ የዓም ሕይወትን አራግፈህ ለማረፍ ወደ ሰማያት ያረግህ ለሆንክ ለአንተ ለኤልያስ ሰላም እላለሁ፡፡ አክአብን ለተናቀ ሥራው እየዘለፍከው ጣዖታትን የቀጠቀጥክ ማምለኪያዎቹን ያፈረስክ በምስጋናህ ምንኛ ተመሰገንህ) ብሎ አመስግኖታል።




የነቢዩ ቅዱስ ኤልያስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፤ በጸሎቱ ይማረን።



#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

💠ጊዜ ለመቆጠብ የሚባክን ጊዜ!💠
.................   ......................
🛐ብዙ ጊዜ በአገልግሎት የምናውቃቸው፣ነግህ ለኪዳን ሠርክ ለጸሎት ከአውደ ምሕረቱ የማይጠፉ። በጎደለው በኩል ቆመው የሚሞሉ፣ ለአገልግሎት የማይታክቱ ብዙ እህትና ወንድሞች ከሆነ ጊዜ በሗላ ሥራ ጀምረው፣ትዳር መስርተው...ወዘተ በአጋጣሚ አግኝታችሁ "ምነው ጠፋችሁ ከቤተክርስቲያን ?" ብላችሁ ስትጠይቋቸው። መልሳቸው ጊዜ አጣሁ ነው።
👉ብዙዎቻችን ለእግዚአብሔር ጊዜ የምንሰጠው በችግር ጊዜ፣ባጣን ጊዜ፣ተስፋ በቆረጥን ጊዜ፣ በጎደለብን ጊዜ እንጂ በበረታን፣ በተሳካልን፣ በሆነልን ጊዜ አይደለም። የሚገርመው ለጸሎት ጊዜ፣ለቤተክርስቲያን ጊዜ መስጠት በማቆማችን ባናውቅም ፣ባይገባንም ጊዜ ለመቆጠብ ብለን ከእግዚአብሔር ቤት በመራቃችን በሕይወታችን ብዙ ነገር ይባክናል። ጥቂት ጊዜ ከአምላክ ፊት በመቆም የምናገኘው መልስ በአቅም ስንደክም ዘመናትን እናስቆጥራለን።

አንድ  ታሪክ አለ ማሳያ የሚሆን" በአንድ ወቅት ሰውየው በደነዘ መጥረቢያ የዛፉን ግንድ ለመቁረጥ ይታገላል። መጥረቢያው እየነጠረ ከመመለስ ውጪ የተፈጠረ ነገር የለም። ይህን ሁኔታ ያስተዋለ አንድ መንገደኛ ሰው ጠጋ ይልና  << ወንድሜ መጥረቢያዉ እኮ ደንዟል አንድ ጊዜ አረፍ ብለህ ሳል ሳል ብታደርገው ጥሩ ነው " አለው። በደነዘ መጥረቢያ  እየታገለ ያለው ምስኪን ሠው መንገደኛውን ዞር ብሎ አየውና "እርሱን የምስልበት ጊዜ  የለኝም" በማለት በደነዘው መጥረቢያ መደብደቡን ቀጠለ ይባላል፡፡

💠ይኼ ሰው እኛን ይመስላል። መጥረቢያ ለመሳል የቆጠበውን ጊዜ ግንዱን ለመቁረጥ የወሰደበትን ጊዜ ተመልከቱ። 👉መጥረቢያውን ለመሳል የሚወስድበት ጊዜ 10 ደቂቃ ሊሆን ይችላል።👉 ባልተሳለ መጥረቢያ ቢቆርጥ ግን ሰዓታትን ይፈጅበታል።ጊዜውንም ጉልበቱንም ያባክናል።
💠ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ፣በመጸለይ፣ቅዱሳት መጻሕፍን በማንበብ፣ በማገልገል የምናባክነው ጊዜ የለንም።
💠በቀናችን ውሎ ካለን ጊዜ በቤተክርስቲያን የሚኖረን ቆይታችንም ጥቂት ጊዜ ነው።ያውም በብዙ የምናተርፍበት።
💠ለጸሎትና ለአገልግሎት
የምናውለውን ጊዜ እንደባከነ ልንቆጥረው አይገባም። ምክንያቱም በዓለም ሀሳብ እንዳንባክን፤የተሰጠን ነገር እንዲባረክ፣ በስራና በትዳር ሕይወታችን እንዳንዝል፤እግዚአብሔር ካዘጋጀልን መልካም ስጦታ እንዳንዘገይ ይረዳናል ይረዳናልና።

ጊዜ ለመቆጠብ ብለን ከሕይወት ምእራፍ እንዳናረፍድ እንጠንቀቅ። ጊዜ የእግዚአብሔር ነውና

#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ዕለታዊ_መልዕክት

"አንተ በየዕለቱ ጠዋት ጠዋት ከእንቀልፍ ስትነቃ የምትጨነቀው ስለ ምንድርን ነው፣ የምትጨነቀው ፊትህን መታጠብህ፣ ቁርስህን መብላትህ፣ ልብስህን መልበስህና ለመሄድ መዘጋጀትህ የቀን ተቀን ሕይወትህ ነውን ወይስ የመጀመሪያ ጉዳይህ ዕለቱን በጸሎት በንባብና በተመስጦ ከእግዚአብሔር ጋር መጀመር ነው... እንደዚህ ዓይነቱ ጉዳይ ላይ አንዳንዶች 'ለመጸለይ ጊዜ የለኝም' ይላሉ። እኔ ግን እውነተኛ ምክንያት ነው ብዬ አልቀበለውም። አንተ ግን ጸሎትህንና ተመስጦህን ካስቀደምክ ያ አጣሁት የምትለው ጊዜህን ታገኘዋለህ። ስለሆነም በሁሉም ነገር ላይ ለእግዚአብሔር ቅድሚያ ስጥ።

🙏 የጸሎት ህይወት ይኑረን 🙏


#ለሌሎች_ሼር_ማድረጎን_አይዘንጉ !

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ═══╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ብዙዎቻችን ለምን እንደምንኖር አላወቅንም። በዚህ ምድር ሳለን የምንናገረው፣ የምናስበው፣ የምናደርገው ነገር ሁሉ ከሞት በኋላ ለምንኖረው ዘለዓለማዊ ሕይወት ግብዓት የሚሆን መሆን ሲገባው በቀልድ፣ ለማንም በማይጠቅም ንግግር፣ ጊዜያችንን ስናባክን ይስተዋላል። እያንዳንዱ ድርጊታችን ከፈጣሪ ዘንድ እንጠይቅበታለን። መልካም ከሆነ እንሸለምበታለን። ክፉ ከሆነ ለዘለዓለም እንሰቃይበታለን።

ስለዚህ ያለንበትን ሁኔታ ቆም ብለን አስበን በክፉ መንገድ ካለን ንስሓ ገብተን ወደ መልካም መመለስና በመልካም መንገድ ካለን ደግሞ በዚሁ ለመጽናት መጣር አለብን።

© በትረ ማርያም አበባው


                        
/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…
Subscribe to a channel