dnhayilemikael | Unsorted

Telegram-канал dnhayilemikael - ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

1867

#መሰረታዊ_የቤተክርስቲያን_ክርስቲያን_ትምህርት / #የተለያዩ_ተከታታይ_ትምህርት ' #ስንክሳር_የቅዱሳን_ገድል_በየዕለቱ ! #ስዕለ_አድህኖ ! #ምስባክ #የየበአላቱ_ዋዜማና_ሥርተ_ማህሌት #መዝሙር #ግጥም #ለመናፍቃን_ጥያቄ_መልስ እና የተለያዩ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ ሌሎች መንፈሳዊ ጽሁፎች ይለቀቁበታል Administration @zearsema_dn

Subscribe to a channel

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

እግዚአብሔር የረሳን ለምን ይመስለናል?
1. እኛ ስለምንረሳው
    የመከራ ጽናት የዘመን ብዛት እግዚአብሔር ረስቶኛል ብቻ ሳይሆን (ሎቱ ስብሐት) እግዚአብሔር የለምም ያስብላል። የሰው ልጅ መከራው ጽኑ በሆነ ጊዜ፣ ዘመን በራቀበት ጊዜ፣ ለጥያቄው መልስ ባጣ ጊዜ በእነዚህ በሦስቱ በሃይማኖት እንቅፋት ይገጥመዋል። ስለዚህ እግዚአብሔር ረስቶኛል፣ አይወደኝም ይልና ቀቢጸ ተስፋ ላይ ሲደርስ ደግሞ እግዚአብሔር ባይኖር ነው እንጂ ቢኖርማ ማለት ይጀምራል። በመጨረሻም የለም ብሎ ይክዳል።
     ሰይጣን ሰውን ወደ ምንፍቅና ወደ ክህደት የሚወስድባቸው 3ቱን መንገዶች መጠንቀቅ ይገባል። ይህንን ይበልጥ ለመረዳትም የሚከተሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ሀሳቦችን እንመልከት:-
👉ሀ. "ስለምን ጦምን? አንተም አልተመለከትከንም? ሰውነታችንንስ ስለምን አዋረድን? አንተን አላወቅህም?" (ኢሳ58÷3)
    እዚህ ላይ ጹመው ለጥያቄያቸው ምላሽ በማጣታቸው እግዚአብሔርን አልተመለከትከንም፣ አላወቅኸንም እስከማለት ደርሰው ነበር። "የእግዚአብሔር ዓይኖች ምን ሆነው አልተመለከቱም?፣ አይወሰኑ ምሉዓን፣ አይሞቱ ሕያዋን፣ አያዳሉ ጻድቃን ናቸው። ታዲያ ለምን አልተመለከትከንም አሉ?" ብንል መልሱ "ጥያቄያቸው ባለመመለሱ እግዚአብሔር የተዋቸው የገፋቸው የረሳቸው መስሏቸዋል" የሚል ይሆናል።
     የፈለጉትን በማጣታቸው በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት እግዚአብሔር የሌለ እየመሰላቸው ወዲያ ወዲህ የሚቅበዘበዙ ወገኖች በዚህ ዘመንም አይታጡም። ግን እግዚአብሔር አላይ ብሎ ሳይሆን እኛ አንታይም አትየን ብለነው ነው። "ገዳም ሄድኩ፣ ንስሐ ገባሁ፣ እጸልያለሁ፣ እጦማለሁ፣ በቅዱሳን አምናለሁ፣ እቆርባለሁ ነገር ግን እስከዛሬ ከነበርኩበት ነኝ ምን ይሻለኛል?" የሚሉ ብዙዎች ናቸው። መልሱን ለእነዚህ ጦመኞች የመለሰውን እንስማ!
    "በውኑ ሴት ከማኅፀንዋ ለተወለደው ልጅ እስከማትራራ ድረስ ሕፃንዋን ትረሳ ዘንድ ትቾላለችን? አዎ እርስዋ ትረሳ ይሆናል፣ እኔ ግን አልረሳሽም" ይላል (ኢሳ 49÷15)። እናት 9 ወር ፀንሳ፣ ከደምዋ ተከፍሎ፣ በምጥ በፃዕር በጭንቅ የወለደችውን፣ 3 ዓመት ያጠባችውን፣ ሁሉን ታግሳ በንጽሕና ያሳደገችውን ልጇን ትረሳለችን? አትረሳም። ዳሩ ግን ቢያንስ ሙቶ እንኳን አልቅሳ አልቅሳ ስታንቀላፋ በዕለቱም ቢሆን ትረሳለች። እግዚአብሔር ግን ይህ ሁሉ በባሕርዩ የለበትምና አይረሳም። "እንግዲያውስ ስለምን አልተመለከትከንም ሰውነታችንንስ ስለምን አዋረድን? አንተም አላወቅኸንም?

ጥያቄ:- ስለምን ጦምን? አንተም አልተመለከትከንም ሰውነታችንንስ ስለምን አዋረድን? አንተም አላወቅኸንም?

መልስ.......
                          ይቀጥላል
ከጸያሔ ፍኖት (በአባ ገብረ ኪዳን) ከገጽ 68-69 የተወሰደ
/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

“ብዙ እናቶች ስቃይ ካለበት የወሊድ ሰዓት በኋላ ልጆቻቸውን ሌሎች እንዲመግቡላቸው ለእንግዶች ይሰጣሉ። ክርስቶስ ግን እኛ ልጆቹን በብዙ መከራ እና ስቃይ በመስቀል ላይ ከወለደን በኋላ ሌሎች እስኪመገቡን ድረስ አይተወንም። በገዛ ሥጋ እና ደሙ እየመገበ ራሱ ያሳድገናል። በዚህ ሁሉ መንገድም ከራሱ ጋር አንድ ያደርገናል።”

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

ስለዚህ ከሥጋውና ደሙ ርቃ በኃጢአት በበደል ተይዛ ተርባ ያለች ነብሳችንን ንስሐ ገብተን ከኃጢአታችን ታጥበን ሥጋውን በልተን ደሙን ጠጥተን እናጠግባት ከክርስቶስ ጋር አንድነትን እናደርግላት ።

ዲን እስራኤል

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ስደክም_ያን_ጊዜ_ኃይለኛ_ነኝና»

ድካም ለሃይማኖት ጌጥ ነው፡፡
ድካሞ ለእምነት ኃይል ነው፡፡
ድካም ለእግዚአብሔር ክብር መገለጫ ነው፡፡
ድካም ለነፍስ ዋጋ የመስጠት ማሳያ ነው፡፡ ድካም ዓለምንና ኃጢአቷን የመናቅ ውጤት ነው፡፡
ድካም የልምድ እስራትን የመበጠሻ መጋዝ ነው፡፡
ድካም መንፈሳዊ ለውጥን የማምጫ የከፍታዎች ደረጃ ነው፡፡
"ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ ነኝና።"
(2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 12፥10)

"ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ ነኝና፡፡" የቃሉን እውነት ከኛ ውስጥ ገልብጦ የሚመራን ዲያቢሎስ ደግሞ፤ "ሳልደከም ያን ጊዜ ልፍስፍስ ነኝና" የሚል ኑሮን ሊያሰለጥነን ስለ ሃይማኖት መድከምን የሚጠየፍ አመለካከትና ተክለ ቁመና ሲቀርጽልን፤ ስንድከም የበለጠ የምንደክም እየመሰለን ከበረከት ተልፈስፍሰን፣
ከጸጋ ተልፈስፍሰን፣ ከመገለጥ ተልፈስፍሰን፣ ከእምነት መፍትሔ ተልፈስፍሰን፣ ከራእይ ተልፈስፍሰን ይኸውና ሁሌ ድካም ያልተለየው ደካማ ጊዜን እንገፋለን፡፡

ሰው በሠራው ልክ ደመወዙን እንደሚቀበል በመንፈሳዊው ሕይወትም እንዲሁ ነው፡፡ እስከ አቅማችን እውነተኛው ጥግ መንፈሳዊ ጠባያችንንና ሥራችንን ቅዱስ ለማድረግ በደከምንበት ልክ፤ እግዚአብሔር ዋጋችንን ይሰጣል፡፡

ስለዚህሳ? "ስለዚህማ ስለ ክርስቶስ በድካም በመንገላታትም በችግርም በስደትም በጭንቀትም ደስ ይለኛል፤ ስደክም ያን ጊዜ ኃይለኛ ነኝና" እያልን ስለ መንፈሳዊ ብርታት መድከም ኃይል እንደሆነ ልናውቅና ልንኖርበት ይገባናል፡፡



/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ልክ በዛሬዋ ቀን ነበር
ዛሬ አመት ሆናችሁ
ጥቁር የለበስንበት ቀን
ወጣቶች በግፍ የተረሸኑት
ልክ የዛሬዋ ቀን ነበር በቤተ ክርስትያን ቅጥር ውስጥ የደም ጅረት የፈሰሰበት
ልክ የዛሬዋ ቀን ነበር ምዕመናን የተጋደሉላት
ልክ በዛሬዋ ቀን ነው የወጣቶቹ ደም የተገበረው
ልክ በዛሬዋ ቀን ነው የጥይት ዝናብ የዘነበባቸው
ልክ የዛሬዋ ቀን ነበር ህገወጦቹ የተዘባበቱበት በደማችሁ
ልክ በዛሬዋ ቀን ነው ሰማዕትነት የተቀበላችሁት

እናንተ በጥይት ደማችሁ ሲፈስ እኔ ግን ዛሬ ላይ ቁሜ ልቤተ ክርስትያን ሸክም ሆንኩባት በእናንተ ሞት በእናንተ ደም ቤተ ክርስትያን ታጠበች ከበረክ አፅዷን በደማችሁ ጠበቃችሁላት በሞታችሁ አገበራችኋት ምንም የምናገረው የለኝም ግን የእናንተ ሞት መከራዋ ህመሟ ይቆማል ብዬ አስቤ ነበር ያልጠርጥር እራሳችሁን አሳልፋችሁ ስለሰጣችሁ ግን አልቆመም እንደውም ብሷል ወንድሞቼ ብቻ ከአምላካችን አሳስቡልን እየሆነ ያለውን ።

ቤተ ክርስትያን መቼም አረሳችሁም
ተዋህዶ መቼም አረሳችሁም
ሁሌም እናንተን ስናስብ እና ስንዘክር እንኖራለን😭😭😭😭
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ነፍስ ይማር ጥር 27/2016
/channel/MoaeTewahedoB

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፲
የእግዚአብሔር ልጅ የሰው ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ
አንዳንዶች ሰውነቱን ብቻ አይተው ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ብቻ (ዕሩቅ ብእሲ) ይመስላቸዋል። አንዳንዶች ደግሞ አምላክነቱን ብቻ አይተው ሰውነቱን ይዘነጉታል። ነገር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የሆነ አምላክ፣ አምላክ የሆነ ሰው ነው። አምላክም ሰውም የሆነ አንድ ልጅ (ወልድ ዋሕድ) ነው።

ሰው እንደመሆኑ በየጥቂቱ አደገ፣ ተራበ፣ ተጠማ፣ ስለእኛ መከራን ተቀበለ። አምላክ እንደመሆኑም የተራቡትን አጠገበ። ከኃጢአት በቀር የሰውነትን ሥራ ሁሉ ሠራ። በዚህም ሰውን አዳነ። ወንጌላዊው ሉቃስ የኢየሱስ ክርስቶስን የትውልድ ሐረግ ሲገልጽ "የእግዚአብሔር ልጅ የአዳም ልጅ" ብሎ ይናገራል (ሉቃ. ፫፣፴፰)። ሙስሊሞች አምላክ አይወልድም አይወለድም ብለው ይናገራሉ። ነገር ግን ይህ እግዚአብሔር የሆነውን ሳይሆን እንዲሆን የሚፈልጉትን ሐሳብ የሚያንጸባርቁበት ንግግር ነው። ቁርኣን ከመጻፉ በፊት የነበሩ የነቢያትና የሐዋርያት መጻሕፍት የሚናገሩት እግዚአብሔር ወልድ የእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጁ መሆኑን ነውና። "ከአጥቢያ ኮከብ አስቀድሞ ከሆድ ወለድኩህ" እንዲል (መዝ. ፻፱፣፫)። እንግዲህ አላህ በቁርኣን ወንጌልንም ኦሪትንም ለዒሣ ገለጥኩ ብሎ ከተናገረ ወንጌልም ኦሪትም የአብ አንድ ልጅ ወልድ እንዳለው ይናገራሉ። ስለዚህ በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ማመን ይገባቸው ነበር።

የሃይማኖት ትምህርት በነጻነት የሚማሩት ነው። ስለዚህ ኅሊናን ነጻ አድርጎ፣ እውነታውን እየመረመሩ መረዳት አስፈላጊ ነው። ስለሆነም ፕሮቴስታንቶችም፣ ሙስሊሞችም፣ ቅባቶችም፣ ካቶሊኮችም፣ ሃይማኖት አልባዎችም ካላችሁ በነጻነት መነጋገር እንችላለን። ኑ።

© በትረማርያም አበባው

/channel/dnhayilemikael
ክፍል ፲፩ ይቀጥላል

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፰
በሥላሴ ዘንድ ያለው አካላዊ ግብር የሚከተለው ነው። የአብ መውለድ ማሥረጽ፣ የወልድ መወለድ፣ የመንፈስ ቅዱስ ደግሞ መሥረጽ ነው። ከዚህ ውጭ መቅባት፣ መቀባት፣ ቅብዕ መሆን የሚል አካላዊ ግብር የለም።

ለግብረ ባሕርይ የተነገረውን ለግብረ አካል፣ ለግብረ አካል የተነገረውን ለግብረ ባሕርይ አድርገው ከተናገሩት ትልቅ ተፋልሶን ያመጣል። በግብረ አካል ሕይወትነት በተለየ የመንፈስቅዱስ ነው። በግብረ ባሕርይ ሲነገር ግን ሦስቱ አንድ የሚሆኑበት አፍኣዊ ግብር ነው። ይህ በሦስቱ ኵነታት ተገናዝቦ የሚገኝ ሕይወትነት ነው እንጂ ከሦስቱ ኵነታት አንዱ አይደለም። ለምሳሌ በሃይማኖተ አበው "አብ ሕይወት፣ ወልድ ሕይወት፣ መንፈስቅዱስ ሕይወት" ሲል ይገኛል። ይህ ሕይወትነት ሦስቱ አካላት አንድ የሚሆኑበት ሕይወትነት ነው እንጂ በግብረ አካል የተጠቀሰው እስትንፋስነት (ሕይወትነት) አይደለም። ምክንያቱም ሦስቱም አካላት በየአካላቸው ጸንተው የሚኖሩ ስለሆነ አብ መንፈስቅዱስን፣ መንፈስ ቅዱስም አብን አይሆኑምና ነው።

በግብረ ባሕርይ አብን አባታችን እንደምንለው ሁሉ ወልድንም አባታችን ሆይ እንለዋለን። እኛን በመንፈሳዊ ልደት መውለድ የአብም፣ የወልድም፣ የመንፈስ ቅዱስም (ሦስቱም አንድ የሚሆኑበት) ሥራ ነው። በዚህኛው ግብረ ባሕርይ አብንም ወልድንም መንፈስቅዱስንም ወላዲ ወላዲ ወላዲ ልንላቸው እንችላለን። በግብረ አካል ወላዲ የሚባል ግን አብ ብቻ መሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል። ለግብረ ባሕርይ የተነገረውን ለግብረ አካል፣ ለግብረ አካል የተነገረውን ለግብረ ባሕርይ መናገር አይገባም ያልነው ይህ ነው።

አፍቀርከ ጽድቀ ወዐመፃ ጸላእከ ወበእንተዝ ቀብዐከ እግዚአብሔር ቅብዐ ትፍሥሕት እምእለ ከማከ ብሎ ቅዱስ ዳዊት የተናገረው በመቅባት ሦስቱም አካላት አንድ ስለሆኑ ስለሦስቱም የተነገረ ቃል ነው። እለ ከማከ ተብለው ("እለ" የሚለው አገባብ በቂ ሆኖ ማለት ነው) ከተገለጹት ነቢያት የሚበልጥ ቅብዐ ትፍሥሕትን ቀባህ ተብሏል። ቅብዐ ትፍሥሕት ክብር ነው። የነቢያት ክብር የጸጋ ክብር ነው። አምላክ የተባሉ ነቢያት እንኳ ቢኖሩ አምላክነታቸው፣ ክብራቸው የጸጋ ነው። ረሰይኩከ አምላኮ ለፈርዖን እንዲል። ሥጋ አምላክነትን (ክብርን) ገንዘብ ያደረገው ግን በጸጋ ሳይሆን በባሕርይ በተዋሕዶ ነው።


/channel/dnhayilemikael
ክፍል ፱ ይቀጥላል

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፮
ኢየሱስ ክርስቶስ በአደገባት ከተማ ምክንያት ናዝራዊ እየተባለ ይጠራል። ማቴ. ፪፣፳፫ "በነቢያት ናዝራዊ ይባላል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ናዝሬት ወደ ምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ" እንዲል። ክርስቶስ በቤተልሔም እንደተወለደ ዕለቱን በአንድ ጊዜ ልደግ አላለም። ሰው እንደመሆኑ እንደሰው በየጥቂቱ አደገ። በበሕቅ ልሕቀ እንዲል። ሥጋ መቼም ቃልን ተዋሕጃለሁ ብሎ በአንድ ጊዜ የሠላሳ ዓመት ጎልማሳ ልሁን አላለም።

ክርስቶስ በሥጋ በቤተልሔም ተወልዶ በናዝሬት አደገ። መድኃኒትነቱ ግን ለዓለም ሁሉ ስለሆነ መድኃኔዓለም እየተባለ ይጠራል። ካህናትም በእርሱ የተሾሙ እርሱን የሚያገለግሉ ስለሆኑ ለሰው ልጅ ሁሉ እኩል ያስባሉ። ለሁሉም ጸሎትን ያቀርባሉ። በብሉይ ኪዳን ናዝራውያን የሚባሉት ለእግዚአብሔር ራሳቸውን የተለየ የሚያደርጉ ሰዎች ነበሩ (ዘኍ. ፮፣፪)። በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ክርስቶድ ናዝራዊ እንደተባለ ሁሉ በጥምቀት ተወልደን ከዓለም ተለይተን ውሉደ እግዚአብሔር የሆንን እኛ ክርስቲያኖች ናዝራውያን እንባላለን።

/channel/dnhayilemikael።

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ክፍል ፭
ኢየሱስ ክርስቶስ የት ተወለደ?
የሕይወት እንጀራ ክርስቶስ በእንጀራ ቤት ተወለደ (ሉቃ. ፪፣፬-፲፭)። ቤተልሔም ማለት የእንጀራ ቤት ማለት ነው። የክርስቶስ መወለድ ድንገት እንደ እንግዳ ደራሽ፣ እንደ ውሃ ፈሳሽ አይደለም። በቅዱሳን ነቢያት የሰውን ሥጋ ተዋሕዶ እንደሚወለድ ትንቢት ሲነገር ነበርና (ኢሳ. ፯፣፲፬)። ከጽድቅ ለተራበው ዓለም መንፈሳዊ ምግብ ይሆን ዘንድ የሕይወት እንጀራ ክርስቶስ በእንጀራ ቤት ተወለደ።

ቤተልሔም በእስራኤል ሀገር ያለች የዳዊት ከተማ የነበረች ቦታ ናት። ነቢያቱ፣ ነገሥታቱ ተወልደውባታል። የነቢያት ሀገር ናት። ከነቢያቱ፣ ከነገሥታቱ ግን የሕይወት እንጀራ ሆኖ የተራበውን ዓለም ማጥገብ የቻለ አልነበረም። ወልደ እግዚአብሔር ግን ከድንግል ማርያም ተወልዶ ዘለዓለማዊ ሕይወትን የሚሰጥ የሕይወት እንጀራ ሆነ። ምእመናን ንሥሓ ገብተው፣ ሥጋውን በልተው፣ ደሙን ጠጥተው በእርሱ ሕያዋን ሆነው ይኖራሉ። እርሱም በእነርሱ ይኖራል።

© በትረማርያም አበባው

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ክፍል ፫
አማኑኤል
አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ (እግዚአብሔር ምስሌነ) ማለት ነው። እግዚአብሔር በአካል ከፍጥረቱ ተለይቶ አያውቅም። እርሱ በአካል የሌለበት ቦታ የለምና። በረድኤትም በብሉይ ኪዳን ከቅዱሳን አበው፣ ከቅዱሳን ነቢያትና፣ ከቅዱሳን ነገሥታት ጋር ነበር። ይህኛው "ምስሌነ" ግን አነጋገሩ ከረድኤት የተለየ "ምስሌነ" ነው። በረድኤት ከእኛ ጋር መኖርን ብቻ የሚገልጽ አይደለም። የእኛን ሥጋ ተዋሕዶ ከእኛ ጋር መኖሩንም የሚገልጽ አነጋገር ነው። አማኑኤል የሚለው ስም ስመ ሥጋዌውን የሚገልጽ ስም ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን እንደእኛ ሰው ሆኖ ክሦ፣ ቤዛ ሆኖ አድኖናል።

እንግዲህ ምንንም፣ ማንንም አንፈራም። የሚያስፈራን ፍጡር የለም። ምክንያቱም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው። በእምቢታችን ጸንተን፣ በራሳችን ፈቃድ ከእግዚአብሔር ጋር መኖር አንፈልግም ብለን ከሰይጣን ጋር ካልተባበርን በስተቀር እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ስለሆነ በእርሱ ሁሉን አሸንፈን እንኖራለን።

እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆኖ ነጻነትን መለሰልን፣ ፍጹም መንፈሳዊ ደስታን ሰጠን። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ሁሉ አለን። ኵሉ ብነ እንዘ አልብነ ኵሉ እንዳለ።

© በትረማርያም አበባው

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ክፍል ፩
_ኢየሱስ_
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሚጠራባቸው ስሞች አንዱ ኢየሱስ ነው። ኢየሱስ ማለት መድኃኒት ማለት ነው። ዓለም በአዳም በደል ምክንያት ታሞ ይኖር ነበር። ዓለምን መፈወስ የቻለ ሰው ደግሞ እስከ ክርስቶስ ልደት ድረስ አልተገኘም ነበር። ስለዚህ ዓለምን ለማዳን ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ፣ ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ ተዋሐደ። ዓለምን የማዳን ሥራውም ከማኅፀን በተዋሕዶ ጀመረ። በዓለም ላይ ብዙ መድኃኒቶች ቢኖሩም መድኃኒትነታቸው የጸጋ ማዳን ነው። በባሕርይው አዳኝ የሆነ እግዚአብሔር ነው። እርሱ እግዚአብሔር ሥጋን ተዋሕዶ አድኖናልና ኢየሱስ ተብሏል። ሰውን ያዳነው፣ ወደቀደመ ቦታውም የመለሰው ኢየሱስ ነው። ሌሎች ፍጡራን ቢያድኑ ግን ማዳንን ከክርስቶስ በጸጋ ተቀብለው ነው። ኢየሱስ የሚለው ስም በአማርኛ መድኃኒት፣ መድኃኒ ዓለመ፣ መድኃኔ ዓለም ተብሎ ሊገለጽ ይችላል።

የኢየሱስ ስሙ፣ አካሉ፣ ሁለንተናው አዳኝ ነው። ስለሆነም በየጊዜው በየሰዓቱ ከሰይጣን ተንኮል ያድነን ዘንድ ስሙን እንጠራለን። ስለሆነም እንደ ደራሲው ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ሠረፀ እምቤተ ሌዊ፣ ኮሬባዊ መለኮታዊ፣ ቃል ሰማያዊ እምድንግል ተወልደ እንለዋለን።

© በትረማርያም አበባው


/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

የቃናውን ወይን የቃና ሰርገኞች ጠጥተው ጨርሰውታል። ከትውልድ ወደ ትውልድ ሳይተላለፍ በታሪክ ብቻ እንማረዋለን። የቀራንዮውን ወይን ግን እስከ ዕለተ ምጽአት ምእመናን ንሥሓ እየገቡ ይጠጡታል። እርሱም ንጽሐ ሥጋን ንጽሐ ነፍስን ያጎናጽፋቸዋል። ለምእመና ልዩ ቀን (ዕለት ኅሪት) ንሥሓ ገብተው ከዘለዓለማዊው ወይን የሚጠጡበት ቀን ናት።
                #ዕለት #ኅሪት #ዕለተ #መድኃኒት
እስራኤላውያን ከግብፅ የወጡባት ቀን ዕለት ኅሪት ትባላለች። ባሕረ ኤርትራን የተሻጉረባት ቀን ደግሞ ዕለተ መድኃኒት ትባላለች። ጌታ የተፀነሰባት ዕለት ዕለት ኅሪት ትባላለች። የተወለደባት ቀን ደግሞ ዕለተ መድኃኒት ትባላለች። አንድም የተወለደባት ቀን ዕለት ኅሪት ትባላለች። የተሰቀለባት ቀን ዕለተ መድኃኒት ትባላለች። አንድም የተሰቀለባት ቀን ዕለት ኅሪት ትባላለች። ከሙታን የተነሣባት ቀን ዕለተ መድኃኒት ተብላበች። ሰው ንሥሓ የሚገባባት ቀን ዕለት ኅሪት ትባላለች። ሥጋውን ደሙን የሚቀበልባት ቀን ደግሞ ዕለተ መድኃኒት ትባላለች። ዕለት ኅሪት፣ ዕለተ መድኃኒት በንባብ እንጂ በምሥጢር አንድ ናቸው።

ጌታ ጥር ፲፩ በውሃ ተጠመቀ። በዕለተ ዐርብ ከጎኑ በፈሰሰው ንጹሕ ውሃ (ማየ ገቦ) ደግሞ እኛ እንድንጠመቅ አደረገን። ጌታ በቃና ዘገሊላ ውሃውን ወደ ወይን ለውጦ ሠርገኞችን አስደሰታቸው። ወይን ያስተፌሥሕ ልበ ሰብእ ማለትኮ ይህ ነው። ወይን ደመ ክርስቶስ ምእመናንን ያስደስታል። በዕለተ ዓርብ ደሙን አፍስሶ አነጻን። ወይን ክርስቶስ እስከ ዕለተ ምጽአት ለሚነሡ ምእመናን መድኃኒት የሚሆን መጠጥን ሰጠን።

ስለ ቃና ወይን ስንናገር ንሥሓ ገብተን ዋናውን ወይን ደመ ክርስቶስን መቀበል ይገባናል።

/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ጌታ በሌሊት ለምን ተጠመቀ ?
ይቀጥላል ......

ቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ
   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

እንኳን ለወንጌላዊ ሐዋርያ ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ


ሰላም ለከ ዮሐንስ ታኦሎጎስ
ሰላም ለከ ዮሐንስ አቡ ቀለምሲስ
ሰላም ለከ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
ሰላም ለከ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚዕ
ሰላም ለከ ዮሐንስ ነባቤ መለኮት
ሰላም ለከ ዮሐንስ ወንጌላዊ


   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ክርስቲያን መሆንህን በቃል ሳይሆን በተግባር አሳየኝ !

ክርስቲያኖች ግን ክርስቲያኖች ለመሆናቸው መታወቅ የሚገባቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተው ምሥጢራትን ሲቀበሉ ብቻ ሳይሆን የትም ቦታ በሚኖሩት የቅድስና ሕይወት ነው፡፡ በአፍአ የከበሩ ሰዎች በአፍአ ከሚያሳዩት ምልክት እንደሚታወቁ ኹሉ፥ እኛም ልንታወቅ የሚገባን በነፍሳችን ክብር ነው፡፡ በሌላ አገላለጥ አንድ ክርስቲያን መታወቅ ያለበት በተሰጠው ልጅነት ብቻ ሳይሆን ለልጅነቱ እንደሚገባ በሚያሳየው አዲስ ሕይወትም ጭምር ሊሆን ይገባል፡፡ ይህ ክርስቲያን ለዓለም ብርሃንና ጨው ሊኾን ይገባዋል፡፡ ለዓለም ብርሃን መሆንህስ ይቅርና ለራስህ እንኳን ብርሃን መኾን ካልተቻለህ፣ የሚሰፋ ቁስልህን በዘይት ማሰርም ካቃተህ፥ ክርስቲያን መሆንህን የምናውቀው እንዴት ነው? ወደ ተቀደሰው ውኃ ገብተህ በመጠመቅህ ነውን? በዚህስ አይደለም ! ይህስ እንዲያውም ዕዳ ፍዳ ይሆንብሃል [እንጂ ክርስቲያን መሆንህን እንድናውቅህ አያደርገንም]፡፡ ይህ ሀብት (ልጅነት) ታላቅ ነውና ለዚህ ሀብት እንደሚገባ ለማይኖሩት ሰዎች ዕዳ ፍዳ መጨመሪያ ነው፡፡ አዎን፥ ክርስቲያን ለዓለም ብርሃኑን ማብራት ያለበት ከእግዚአብሔር በተቀበለው ጸጋ ብቻ ሳይሆን እርሱ ራሱም ድርሻውን በመወጣት ነውና፡፡ ክርስቲያን ካልሆኑት ይልቅ በኹለንተናው - በአረማመዱ፣ በአተያዩ፣ በአለባበሱ፣ በአነጋገሩ - ብልጫ ሲኖረው ነውና፡፡ ይህንም የምለው ልጅነትን የተቀበሉ ክርስቲያኖች ልጅነትን ተቀበሉ በመባል ብቻ ሳይሆን የሌሎች ሰዎች ረብ ጥቅም ይሆን ዘንድ ለተቀበሉት ልጅነት የሚገባና ሥርዓት ያለው ሕይወት እንዲኖሩ ስለምሻ ነው፡፡

#ይቀጥላል...

   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
     /channel/dnhayilemikael
   ╰═══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

የጌታችንና የመዲሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አከባበር በላሊበላ
ይሄን ይመስል ነበር

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

❖ ወዳጄ እስኪ ልጠይቅህ፤ አንተም አንቺም መልሱልኝ!

❓ጌታችን ዛሬ ቢመጣ የምትመልሰው የምትመልሺው መልስ ምንድን ነው

✍️"ንስሐ ያልገባሁት፣ ሥጋ ወደሙን ያልተቀበልሁት፣ ምግባር ትሩፋት ያልያዝሁት ዕድሜዬ ገና ነው ብዬ አስቤ ነው፤ ሥራ በጣም በዝቶብኝ ስለ ነበረ ጊዜ አጥቼ ነው፤ ዛሬ ነገ እያልኩ እየረሳሁት እንጂ እንደዚያ ማድረግ አቅቶኝ አልነበረም"

❓ምክንያትህ እነዚህ ናቸው
❓እኅቴ! ሰበቦችሽ እነዚህ ናቸው

❖ በዚያ ሰዓት ግን እነዚህ ኹሉ ጥቅም የላቸውም፤ እናት ልጇን በማታድንበት ሰዓት እነዚህ ምክንያቶች ምንም አይረቡም፡፡

❓ ታዲያ ለምን ትዘገያለህ
❓ እኮ ለምን ትዘገያለሽ
❓ያኔ ዋይ ዋይ ከምትዪ... ያኔ የማይጠቅም ጸጸት ከምትጸጸት ለምን ዛሬ አትጠቀምበትም
❓ለምን ራስህን አታድንም

📌 ምንጭ
✍️ከገብረ እግዚአብሔር ኪደ
📚ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ



/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ተስፋ መቍረጥ

ዮሐንስ ዘሰዋስው ስለ ቀቢጸ ተስፋ ሲያስረዳ፦ "ቀቢጸ ተስፋ  የመቀባጠር አንዱ ቅርንጫፍ፣ የእርሱም የበኲር ልጅ ናት። ... ቀቢጸ ተስፋ የነፍስ ልምሾነት (መሰልሰል)፣ የአእምሮ መዛል (መድከም)፣ ተጋድሎን ቸል ማለት፣ ብፅዓትን (ቃል ኪዳንን) መጥላት ነው። ... እግዚአብሔርንም ምሕረት የለሽና ሰዎችን የሚጠላ እንደ ኾነ አድርጋ ትከሳለች። መዝሙራትን ለመዘመር የምትዝል፣ ለጸሎት የምትደክም፣ ለአገልግሎት እንደ ብረት የጸናች (ግትር የኾነች)፣ ለተግባረ እድ የምትተጋ፣ ለመታዘዝ ኹኔታ (ብቃት) ቸልተኛ ናት።" ይላል። (ሳሙኤል ፍቃዱ (ሐተታና ትርጒም)፣ ምዕራግና ድርሳን፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ 173)። ከዚህ ትርጒም ተነሥተን ተስፋ መቍረጥ ለመንፈሳዊ አገልግሎት ያለንን ስልቹነት፣ ወይም ጥላቻ የሚያመለክት ነው ማለት እንችላለን። ልበ አምላክ ዳዊት "ሰነፍ በልቡ እግዚአብሔር የለም ይላል" እንዳለ በንዝኅላልነታችን ምክንያት እግዚአብሔር የለም ብለን እስከ ማመን የምንደርስበት ክፉ አኗኗር በቀቢጸ ተስፋ ኾኖ መኖር ነው። ተስፋ የሚቈርጥ ሰው ስኬት ላይ መድረስ አይችልም። ሕይወቱን በበጎ ጎዳና መምራት አይኾንለትም። ምክንያቱም ማንኛውም ነገር ጥረትንና ተጋድሎን ይሻልና። አንዴ ወደሚፈልገው መንገድ እየሄደ ውድቀት ካገጠመው ኹሉም ነገር ወዲያ ጨለማ መስሎ ይታየዋል።

በዋናነት ብዙ ሰዎች በተስፋ መቍረጣቸው ምክንያት ራሳቸውን ለማጥፋት ይወስናሉ። ተስፋ መቍረጥ የእግዚአብሔርን ምሕረት የመርሳትና ይሁዳን የመምሰል ሕይወት ነው። ተስፋ የሚቈርጥ ሰው ከዚህ ሐሳቡ ለመውጣት ሲል ወደ ሱስ ይጓዛል። በጽኑ ሱስ ሲያዝ ደግሞ የበለጠ የሕይወትን ጣዕም እያጣ ይሄዳል፤ ኋላም ራስን ማጥፋትን እንደ ቀላል ነገር አድርጎ ሊመለከት ይችላል። ቅዱስ ይስሐቅ ዘሶርያ "በመሰናክልህ ምክንያት ተስፋ አትቍረጥ። ይኸውም ኃጢአትህን በማሰብ አትጸጸት ማለቴ ሳይኾን፥ ነገር ግን የማይድኑ አድርገህ አታስብ ማለቴ ነው።" በማለት የገለጸው ብዙውን ጊዜ ተስፋ መቁረጥ ከኃጢአቴ አልነጻም፣ መዳን አልችልም ብሎ ከማሰብ የሚመጣ ስለ ኾነ ነው። The Ascetical Homilies of St. Isaac the Syrian, Homily 64, “On Prayer, Prostrations, Tears, Reading, Silence, and Hymnody”። ወንድሜ ሆይ! ምንም ዓይነት መሰናክል ሊገጥምህ ይችላል፤ ነገር ግን ከልብህ ተጸጽተህ ንስሓ ከገባህ የሚድን መኾኑን አትዘንጋው። ከማንኛውም ውድቀትህ በላይ እግዚአብሔር የሚያዝንብህ አይምረኝም ብለህ ማመን ስትጀምር ነው። ንስሓ ከተገባበት የማይድን ምንም ዓይነት አደገኛ የኃጢአት በሽታ የለምና። የደማስቆው ጴጥሮስ "ነፍስን የሚገድለውን ተስፋ መቍረጥን፥ ጽኑ ተአጋሲነት ይገድለዋል።" በማለት ያስረዳል። St. Peter of Damaskos, “Book II: Twenty-Four Discourses,” V Patient Endurance, The Philokalia: The Complete Text (Vol. 3)።  እንግዲህ ይህ የሊቁ አገላለጽ በአንድ በኩል ተስፋ መቍረጥ ነፍስን የሚገድል መርዝ መኾኑን የሚጠቁም ሲኾን፥ በሌላ በኩል በትዕግሥት ሊነቀል የሚችል መኾኑን ያስረዳል። ስለዚህ ተስፋ መቍረጥ ትዕግሥትን በማጣት የሚበቅል ክፉ አረም መኾኑን በዚህ እናስተውላለን።

ዮሐንስ ዘካርፓቶስ እንዲህ ይላል "ፈርዖን ፈርቶ እንዲህ አለ፦ "ፈርዖንም ሙሴንና አሮንን በፍጥነት ጠራ፦ አምላካችሁን እግዚአብሔርን እናንተንም በደልሁ፥ አኹን እንግዲህ በዚህ ጊዜ ብቻ ኃጢአቴን ይቅር በሉኝ፥ ይህንም ሞት ብቻ ከእኔ ያነሣልኝ ዘንድ አምላካችሁን እግዚአብሔርን ለምኑ፣ አላቸው። ሙሴም ከፈርዖን ፊት ወጣ ወደ እግዚአብሔር ለመነ።"  ፈርዖንም ተሰማለት። በተመሳሳይ ኹኔታ አጋንንትም ጌታችንን ወደ ገደል እንዳይከታቸው ለመኑ፥ ጥያቄያቸው ተመለሰላቸው። ሉቃ 8፡31። እንግዲያው አንድ ክርስቲያን ከመንፈሳዊ ሞት ይወጣ ዘንድ ቢለምን ምን ያህል የበለጠ ይሰማለት ይኾን?" በማለት በምንም መንገድ ተስፋ ወደ መቍረጥ መሄድ እንደ ሌለብን ነው።(St. John of Karpathos, For the Encouragement of the Monks in India who had Written to Him: One Hundred Texts (69)። ያን ጨካኙን ፈርዖንን የሰማ አምላክ አንተን እንዴት አይሰማህም? በመስቀል ላይ የሚሰቅሉትን እኒያን አይሁድን የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ብሎ የምሕረት ድምፁን ያሰማ እርሱ አይምረኝም ብለህ ስለምን ትጨነቃለህ? ይልቅስ ኃጢአትህን አምነህ ይቅር ይልህ ዘንድ ወደ ፈጣሬ ዓለማት ወደ ኾነው ጌታ በአንብዓ ንስሓ ብትቀርብ አይሻልህምን? ተስፋ ስንቈርጥ ሁሉንም ነገር አጥርተን ማየት አንችልም። ልክ በጨለማ ውስጥ ያለ ሰው በብርሃን አለመኖር ምክንያት ከፊት ለፊቱ ያሉ ነገሮችን አጥርቶ ማየት እንደ ማይችል፥ ተስፋ በመቍረጥ ጨለማ ውስጥ ያለም ሰውም  እንዲሁ አጥርቶ ማየት አይችልም።
/channel/dnhayilemikael
/channel/dnhayilemikael
/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ብዙዎቻችን ለምን እንደምንኖር አላወቅንም። በዚህ ምድር ሳለን የምንናገረው፣ የምናስበው፣ የምናደርገው ነገር ሁሉ ከሞት በኋላ ለምንኖረው ዘለዓለማዊ ሕይወት ግብዓት የሚሆን መሆን ሲገባው በቀልድ፣ ለማንም በማይጠቅም ንግግር፣ ጊዜያችንን ስናባክን ይስተዋላል። እያንዳንዱ ድርጊታችን ከፈጣሪ ዘንድ እንጠይቅበታለን። መልካም ከሆነ እንሸለምበታለን። ክፉ ከሆነ ለዘለዓለም እንሰቃይበታለን።

ስለዚህ ያለንበትን ሁኔታ ቆም ብለን አስበን በክፉ መንገድ ካለን ንስሓ ገብተን ወደ መልካም መመለስና በመልካም መንገድ ካለን ደግሞ በዚሁ ለመጽናት መጣር አለብን።

© በትረ ማርያም አበባው


                        
/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

አንተ ሰው እስኪ ንገረኝ!

አንድን የሥጋ ቁስል ለመፈወስ ለእያንዳንዱ ሰው ከባድ ነው፤ የነፍስን ቁስል መፈወስ ግን ለኹሉም ቀላል ነው፡፡ የሥጋ ቁስል ለመፈወስ መድኃኒት ብሎም ገንዘብ ያስፈልጋል፤ ነፍስን ለመፈወስ ግን ቀላል ብሎም ወጪን የማይጠይቅ ነው፡፡ ሥጋን ከዚያ ከሚያሰቃይ ቁስሉ ለመፈወስ አድካሚ ነው፡፡ ምክንያቱም በቀዶ ጥገና ምላጭ መቀደድ አለበት፤ መራራ መድኃኒቶችም ሊጨመሩበት ይገባል፡፡ ነፍስን ለመፈወስ ግን እንዲህ ዓይነት ነገር አያስፈልግም፡፡ ፈቃደኛ መኾን ብቻ በቂ ነው፤ ፍላጎቱ ካለ ኹሉንም ነገር ለማድረግ ቀላል ነው፡፡ የእግዚአብሔር መግቦቱም እስከ አሁን ድረስ ይህ ነው፡፡ ሥጋ ቢቆስል ያን ያህል ከባድ ጉዳትን አያመጣብንም፤ ምክንያቱም ምንም ባንታመምም እንኳን ሞት መጥቶ ይህን ሥጋችን ያፈርሰዋል፤ ያበሰብሰዋልምና፡፡ ነፍሳችን ብትታመም ግን ጉዳቱ ብዙ ነው፡፡ እግዚአብሔር የነፍስን ሕመም ለመፈወስ መድኃኒቱ ቀላል፣ ምንም ወጪና ስቃይ የሌለበት ያደረገውም ስለዚሁ ነው፡፡ ታዲያ ምንም እንኳን በሕመሙ ምክንያት የሚያገኘን ጉዳት ያን ያህል ብዙ ባይኾንም የገንዘብ ወጪን የሚጠይቀው፣ ሐኪም የሚያስፈልገው፣ ብዙ ስቃይ ያለበት ሥጋችን ሲታመም እርሱን ለማከም እጅግ የምንደክም ኾነን ሳለ፥ እጅግ ብዙ ጉዳት የሚያመጣውን፣ እርሱን ለመፈወስ ወጪ የማይጠይቀውን፣ ለማስታመም ሌሎች ሰዎች የማያስቸግረውን፣ እንደ ምላጩና እንደ መራራ መድኃኒቱ ስቃይ የሌለበትን ይልቁንም ከእነዚህ አንዱስ እንኳን ሳይፈልግ በእኛ ኃይል ባሉ ምርጫና ፈቃድ ብቻ መዳን የሚችለውን፣ ይህን ማድረግ ሳንችል ስንቀርም ከባድ ፍርድና ቅጣት ስቃይም እንደሚያገኘን በእርግጥ እያወቅን የነፍሳችንን ቁስል ችላ የምንል ከኾነ ሊደረግልን የሚችል ምሕረት እንደ ምን ያለ ምሕረት ነው? እኮ የምናገኘው ይቅርታ እንደ ምን ያለ ይቅርታ ነው?

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ትምህርት በእንተ ሐውልታት መጽሐፍ #በገብረ_እግዚአብሔር_ኪደ የተተረጎመ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፱
ወልደ እግዚአብሔር በከዊን ስሙ ቃል ይባላል። ሥላሴ በባሕርይ አንድ ናቸው። ባሕርይ የሚባለው የሦስቱ ኵነታት ማለትም የቃል፣ የልብ፣ የእስትንፋስ መገናዘብ ነው። ባሕርይ አካላዊ ይባላል እንጂ አካል አይባልም። ባሕርየ ሥላሴ በቃል ከዊነ ሰው ሆነ ይባላል እንጂ በልብ ከዊን ወይም በእስትንፋስ ከዊን ሰው ሆነ አይባልም። ቃል ሰው ሲሆነ ከልብነት ከእስትንፋስነት ተገናዝቦ ሳይለይ ነው። ሥጋ የቃልን ገንዘብ ሲወርስ አብ ልቡ፣ መንፈስቅዱስ እስትንፋሱ ሆነዋል። ሥጋም በቃል ርስት የአብ ቃል፣ የመንፈስ ቅዱስ ቃል ተባለ።

ሥላሴ ስንል አብን፣ ወልድን፣ መንፈስ ቅዱስን ለማመልከት ነው። አብ የራሱ የሆኑ ፍጹም አካል አለው። ወልድም የራሱ ፍጹም አካል አለው። መንፈስቅዱስም የራሱ ፍጹም አካል አለው። እነዚህ አካላት አንዱ አካል በአንዱ አካል ህልው ሆነው ይኖራሉ። ህልው መሆን ብቻ ሳይሆን አንዱ ከአንዱ ተገነዛዝበው ይኖራሉ። ለምሳሌ ከምድር በላይ የፀሐይ ብርሃን በአየር ላይ ህልው ሆኖ ይኖራል። መገነዛዘብ ግን የለውም። አብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ፣ ወልድ በአብና በመንፈስ ቅዱስ፣ መንፈስ ቅዱስ በአብና በወልድ አለ (ህልው ሆኖ ይኖራል) ስንል ግን መገነዛዘብ ያለበት ህልውና ነው።

ሦስቱ አካላት የሚገነዛዘቡት ደግሞ በከዊን ነው። አብ በልብ ከዊኑ የወልድም የመንፈስቅዱስም ልብ ነው። ወልድ በቃል ከዊኑ የአብም የመንፈስቅዱስም ቃል ነው። መንፈስቅዱስ በእስትንፋስነት ከዊኑ የአብም የወልድም ሕይወት ነው። ስለዚህ አብን ልብ፣ ለባዊ፣ አለባዊ፣ ነባቢ፣ አንባቢ፣ ሕያው፣ ማሕየዊ እንለዋለን። ወልድን ቃል፣ ነባቢ፣ አንባቢ፣ ለባዊ፣ አለባዊ፣ ሕያው፣ ማሕየዊ እንለዋለን። መንፈስቅዱስን ደግሞ እስትንፋስ፣ ሕያው፣ ማሕየዊ፣ ለባዊ፣ አለባዊ፣ ነባቢ፣ አንባቢ እንለዋለን። የእነዚህ የሦስቱ ኵነታት ተገናዝቦ ባሕርይ ይባላል። ወልድ ሰው ሲሆን አካለ ቃል ከአካለ ትስብእት ጋር ተዋሕዷል። ባሕርየ ወልድ (ቃልነት) ከባሕርየ ትስብእት ተዋሕዷል ማለታችን ነው።

© በትረማርያም አበባው

/channel/dnhayilemikael
ክፍል ፲ ይቀጥላል

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፯
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንደጻፈው በመሢሕ መሢሓውያን እንባላለን። ክርስቶስ ማለት መሢሕ ማለት ነውና። ይህንን ቅድስት ቤተክርስቲያን ስታስተምረው የኖረችውና ወደፊትም እስከ ዕለተ ምጽአት የምታስተምረው ትምህርት ነው። ሥጋ የአምላክነትን ክብር ሲያገኝ ክብር የሆነው ማን ነው የሚለውን ጠንቅቆ ማወቅ ያስፈልጋል። የቅባት እምነት አራማጆች ለሥጋ ቅብዕ (ክብር) የሆነው መንፈስ ቅዱስ ነው ይላሉ። ነገር ግን ቅዱስ አትናቴዎስ የሚነግረን ለሥጋ ክብር የሆነው ራሱ ቃል መሆኑን ነው። ይህንንም "ሥጋ ረከበ ዕበየ ወብዝኀ ፍድፍድና በተሳትፎቱ ወበተዋሕዶቱ ምስለ ቃል" ብሎ በማያሻማ ቃል ነግሮናል (ሃይ. አበ. ፴፫፣፳፱)። ሥጋ የአምላክነትን ክብር ያገኘው ከቃል ጋር በመዋሐዱ ነው እንጂ መንፈስ ቅዱስ ክብር ሆኖት አይደለም።

መቀባት (ማክበር) ግን የሦስቱም የአንድነት ሥራ ስለሆነ አብ ቀባው፣ መንፈስ ቅዱስ ቀባው ቢል አንድ ነው። በመንፈስ ቅዱስ ቀባው ሲል ቢገኝ መንፈስ ቅዱስ ቅብዕ ነው የሚል ትርጉምን አይሰጥም። ቅዱሳት መጻሕፍት ረቂቅ ሥራዎችን ሁሉ ለመንፈስ ቅዱስ አድለው መናገር ልማዳቸው ነው። ይሁን እንጂ በዚህ ጊዜ ለመንፈስቅዱስ የተጠቀሰው ከአካላዊ ግብር በስተቀር ለአብም ለወልድም ይሆናል። ለምሳሌ "ከውሃና ከመንፈስቅዱስ ያልተወለደ መንግሥተ ሰማያት አይገባም" ይላል። የተጠቀሰው መንፈስቅዱስ ስለሆነ የምንወለደው ከመንፈስቅዱስ ብቻ ነው አንልም። ከወልድም ከአብም ያልተወለደ ማለት እንደሆነ ልብ ማድረግ ያስፈልጋል።

በዚህ አግባብ የተነገሩትን ቃላት ለመንፈስቅዱስ አካላዊ ግብር አድርጎ መውሰድ የጠማማ ኅሊና ሥራ ነው። ግብረ ባሕርይን ከግብረ አካል ጋር ማቀላቀል ትልቅ በደል ነው። ወልድ ዋሕድ በተዋሕዶ ከበረ ስንል ምንጫችን ታላቁ ሊቅ ቅዱስ አትናቴዎስ ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ ሥጋ ከቃል ጋር በመዋሐዱ ክብርን አገኘ በማለቱ ምንታዌ ነው አንልም። ምክንያቱም ሲከፈልም፣ ሲዋሐድም፣ ሲቀባም አንድ ጊዜ ነውና። ስለዚህ በምንም ተአምር ምንታዌ አያሰኝም። ቃል አክባሪ ሥጋ ከባሪ ካላችሁ የካቶሊክ ትምህርት ነው የሚሉ ሰዎች አሉ። ይህ አስቂኝ ነው። የካቶሊክ ትምህርት አንድ አካል ሁለት ባሕርይ የሚል ነው። የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ግን አንድ አካል አንድ ባሕርይ የሚል ነው። ከተዋሕዶ በፊት ቃል በቃልነቱ በክብሩ ጸንቶ ይኖር ነበር። ሥጋ ቃልን በተዋሐደበት ቅጽበት ደግሞ መምህረ ዓለም ቅዱስ ቄርሎስ "እንቲኣሁ ለቃል ኮነ ለሥጋ ዘእንበለ ኃጢአት ወእንቲኣሁ ለሥጋ ኮነ ለቃል" ብሎ እንደተናገረው የቃል ገንዘብ ሁሉ ለሥጋ ሆነ የሥጋ ገንዘብ ሁሉ ደግሞ ለቃል ሆነ። ከቃል ገንዘቦች አንዱ ክቡርነት ነው። የቃል ክቡርነት ለሥጋ ሆነ። ስለዚህም በጊዜ ተዋሕዶ ቅዱስ አትናቴዎስ እንደተናገረው ሥጋ በቃል ከበረ እንላለን።

© መ/ር በትረማርያም አበባው (የመጻሕፍተ ሊቃውንት፣ የመጻሕፍተ ብሉያትና የመጻሕፍተ መነኮሳት ትርጓሜ መምህር)


/channel/dnhayilemikael
ክፍል ፰ ይቀጥላል።

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ተከታታይ የኮርስ መርሐ ገብር

የመሠረተ ተዋሕዶ ሰ/ት ቤት ለመላው የቤተ ክርሰቲያን ልጆች

💠ከ1ኛ-8ኛ ክፍል ላሉ በሕጻናትና አዳግ መርሃ ግብር

💠ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ላሉ በschool መርሐ ግብር

💠በተለያየ ሥራና ትምህርት ዘርፍ ላሉ በአዋቂ መርሃ ግብር

ከጥር እስከ ነሐሴ በሳምንት ለአንድ ቀን ተከታታይ
የቤተክርስቲያን ትምህርት (ዶግማ ቀኖና ሥርዓት ሥነ ምግባር ታርክ...) ለመስጠት ዝግጅቱን ጨርሷል


በመሆኑ ዉድ የተዋሕዶ ልጆች መጥታችሁ የቤተክርስቲያን ትምህርቷን ትማሩ ዘንድ እያሳሰብን ወላጆችም ልጆቻችሁ እንዲማሩ እንድትልኩ በአክብሮት እንጠይቃለን ።



<<ልጄ የቤተ ክርስቲያንን ነገር አደራ

ቤተ ክርስቲያን ሰው የላትምና(ተምረ እርሷን አውቀ በተማርከው ኖረህ) ሰው ሁንላት
>> አቡነ ጎርጎርዮስ ካልእ




የምዝገባ ቦታ =የሰ/ት ቤቱ ሱቅ

የምዝገባ ጊዜ-እስከ ጥር 27

ቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ
   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮

    ሰንበት ትምህርት ቤበቦታ ሚዲያ(መሠረተ ሚዲያ )
➡️      መሰረተ ሚዲያ


👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
     ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ


👇👇👇👇👇👇👇👇

የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️
⤵️ ⬇️═╯

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ክፍል ፬
ቃለ እግዚአብሔር
ወልድ ዋሕድ በተዋሕዶ ከበረ ዋነኛ ትምህርታችን ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ በሃይማኖተ አበው እንደተናገረው ሥጋ መክበሩ ቃል ስለተዋሐደው ነው እንጂ መንፈስ ቅዱስ ክብር ሆኖት አይደለም።
ኢየሱስ ክርስቶስ ቃለ እግዚአብሔር ነው። ይህም ማለት ቃለ አብ፣ ቃለ መንፈስ ቅዱስ ነው ማለታችን ነው። በአንድ ህልውና በአንድ ባሕርይ ለሚኖሩ ሦስቱ አካላት ቃላቸው እርሱ ነው። ይህ ቃል ከሰው፣ ከእንስሳት፣ ከመላእክት ቃል (ድምፅ) የተለየ ነው። እነዚህ ቃላት (ድምፆች) ዝርዋን ናቸው እንጂ አካላውያን አይደሉም። ቃለ እግዚአብሔር አአትሪኮን፣ አተርጋዎን፣ ቦርፎሪኮን ከሚባሉት ቃላት የተለየ ቃል ነው።

ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር የሰሙት ድምፅ እንኳ ዝርው ነው። አካላዊ ቃል የሚባለው ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል ነው። ከንባብ (ንግግር) የተለየ አካላዊ ቃል ነው። ይህ ቃል ሥጋ ሆነ። ይህም ማለት ረቂቁ አካለ ቃል ግዙፉን አካለ ሥጋ በተዋሕዶ ገንዘቡ አደረገው ማለታችን ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር እየተመላለሰ ሲያስተምር ለሕዝቡ ጆሮ ይሰማ የነበረው ድምፅ ዝርው ስለሆነ አካላዊ አይደለም። ራሱ ክርስቶስ ግን አካላዊ ቃል ነው። እርሱ የተናገረው ንግግር ግን ከእርሱ ከአካላዊ ቃል የተገኘ ንግግር (ንባብ) ነው እንጂ ራሱ ንግግሩ አካላዊ አልነበረም።

© መ/ር በትረማርያም አበባው

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ክፍል ፪
ክርስቶስ
ክርስቶስ በዕብራይስጥ ማስያስ፣ በዐረብ መሢሕ፣ በግሪክ ክርስቶስ፣ በግእዝ ቅቡዕ ማለት ነው። ቅቡዕ ማለትም የተቀባ ማለት ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የሆነ አምላክ፣ አምላክ የሆነ ሰው ነው። ወልደ እግዚአብሔር ከድንግል ማርያም የነሣውን ሥጋ ሲዋሐድ በአምላክነት አከበረው። ሥጋም ቃልን ስለተዋሐደ ከብረ። ስለዚህም ቅቡዕ ተባለ። ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መባሉ በሰውነቱ እንደሆነ ሁሉ ቅቡዕ መባሉም በሰውነቱ ነው። በአምላክነቱ ክብርን (ቅብዕን) የሚሻ አይደለምና። ክርስቶስ ለተዋሐደው ሥጋ ክብር የሆነውም ራሱ ቃል ነው። እንጂ የቅባት እምነት አራማጆች እንደሚሉት መንፈስቅዱስ ቅብዕ (ክብር) አልሆነውም። በሥላሴ ዘንድ ቅብዕ፣ ተቀባዒ፣ ቅቡዕ የሚል አካላዊ ግብር የለምና። በማክበር፣ በክብር አንድ ስለሆኑ አብ አከበረው፣ ወልድ አከበረው፣ መንፈስ ቅዱስ አከበረው ቢል አንድ ነው። ለሥጋ ክብር የሆነው በተለየ አካሉ ቃል ነው። ምክንያቱም ሥጋ ቃልን ሆነ እንጂ ልብን ወይም እስትንፋስን አልሆነምና ነው። ሥጋ ከበረ መባሉ እንኳ ቃልን ሆነ ማለት ነውና።

ክፍል ፫ ይቀጥላል።

© በትረማርያም አበባው

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

🌹🌹🌹🌹🌹ወይን እኮ የላቸውም🌹🌹🌹🌹🌹

የቃና ዘገሊላ ታሪክ ውስጥ አስደናቂ ከኾኑ ክስተቶች ውስጥ አንዱ የወይን ማለቅ ጉዳይ ነው። በእርግጥ ቃና ዘገሊላ ውስጥ የተፈጸመው የሰርግ ጉዳይ ጥልቅ መልእክቶችን የተሸከመ መኾኑ በብዙ የሚብራራ ነው። ታሪኩን በጥልቀት ለመረዳት ግን ወደ ታሪኩ ጥልቀት ውስጥ የምንገባበትን በር ማግኘት አለብን። የዮሐንስን ወንጌል ምሥጢራዊነት ወደ መረዳት ከፍታ እስካልወጣን ድረስ በወንጌሉ ውስጥ የተፈጸሙትን አስደናቂ ክስተቶች በአግባቡ መረዳት አንችልም። ማክሲመስ ተናዛዚው መጽሐፍ ቅዱስን በጥቅሉ በቤተ ክርስቲያን ይመስልና የዮሐንስን ወንጌል ደግሞ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለችውን ቅድስተ ቅዱሳን ትመስላለች ይላል። ይህ የሚያመለክተው ወንጌሉ የተሸከመውን ጥልቅ ምሥጢር ነው። እንዲያውም ቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያ ሦስቱን ወንጌላት በሥጋ የዮሐንስን ወንጌል ደግሞ በመንፈስ ይመስላል። የሌሎቹ ወንጌላት እስትንፋሳቸው የዮሐንስ ወንጌል ነውና!!

ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ የዮሐንስን ወንጌል ለመረዳት ሊቁ ኦሪገን እንዳለው ወደ ጌታ ደረት ጋር ጠጋ ብሎ እንደ ዮሐንስ ከጌታ እመቤታችንን መቀበልን ይጠይቃል። ይህ ኹሉ የሚያመለክተው በወንጌሉ ላይ የተጻፉ ክስተቶችን በችኩልነትና በለብ ለብ ስሜት አልፈን እንዳንሄድና በጥልቀት እንድንመረምር ነው። ሰርግ የተፈጸመባት የገሊላዋ ቃና ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያምን በመያዟ ከሚመጣባት ጉድለት ስትድን እንመለከታለን። ከክርስቶስ ጋር ለምናደርገው ግንኙነት የእመቤታችን ልመና እጅግ አስፈላጊ ነው። እርሷ ቀድማን ጉድለታችንን ባታሰማልን ኖሮ መሽራው ክርስቶስ እንዴት ይቀበለን ነበር!!

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከቤተ አይሁድ ወገን ስለ ኾነች የአይሁድን ጉድለት በእጅጉ ታውቀዋለች፤ ስለዚህ የሚጠቅማቸውን ወይን ይሰጣቸው ዘንድ ትለምናለች። በመጽሐፍ እንዲህ ተብሏል “እናንተ ሰካራሞች ንቁ ለመስከርም ወይን የምትጠጡ እናንተ ሁላችሁ! ተድላና ደስታ ከአፋችሁ ጠፍተዋልና አልቅሱ፤ እዘኑም።" ኢዩ 1፥5። በመኾኑም አይሁድ የድኅነትን ደስታ በማጣት በኀዘን ውስጥ ናቸው፤ ይህ ነውና የወይን ማጣት!! ወይን እኮ የላቸውም የድኅነት ደስታ ከደጃቸው ጠፍታለችና ስጣቸው ማለቷ ነበር። በተራው ምድራዊ ወይን ሰክረው የድኅነትን ወይን በማጣት ጨለማ ውስጥ ገብተው ነበርና ጉድለታቸውን የምታውቅ ፈጣኗ እናት ለመነችላቸው።

ወይን እኮ የላቸውም ርቱዕ እምነት የላቸውም። አኹንም በኦሪታቸው ውስጥ የምትታየውን አንተን ወደ ማወቅ አልመጡምና አይኖቻቸውን ከፍተህ ብርሃነ ወንጌልህን ግለጥላቸው። በጨለማ ውስጥ ያለን ነገር ለማየት የግድ ብርሃን እንዲያስፈልግ በእምነት ጨለማ ውስጥ ያሉትን ወይን ርቱዕ እምነትን ሰጥተህ አድናቸው ማለቷ ነው። ያለ እምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ተናገረው በሐዲስ ኪዳኗ ትክክለኛዋ እምነት በኩል ከእግዚአብሔር ጋር እስካልተገናኘን ድረስ በእርግጥም ወይን እኮ የለንም!!

እመቤታችን ወይን እኮ የላቸውም ማለቷ ሰዎች ከፈሪሓ እግዚአብሔር በመራቃቸው ምክንያት የደረሱበትን መልከ ጥፉነት ለማመልከትና ከዚያ እንድንፈወስ ለማስደረግ ነው። መዝ 127 “ብፁዐን ኩሎሙ እለ ይፈርሕዎ ለእግዚአብሔር ወለ እለ የሐውሩ በፍናዊሁ። ፍሬ ጻማከ ተሴሰይ፣ ብፁዕ አንተ ወሠናይ ለከ፤ ብእሲትከ ከመ ወይን ሥሙር ውስተ ጽርዓ ቤትከ - እግዚአብሔርን የሚፈሩ ኹሉ የተመሰገኑ ናቸው፣ የድካምህን ዋጋ ትበላለህ፤ ምስጉን ነህ መልካምም ይኾንልሀል፤ ምስትህም በቤትህ ውስጥ እንደ ወይን የተወደደች ናት።" በማለት በብዙ አንቀጽ ጀምሮ በአንድ አንቀጽ ወደ ማውራት ይመጣል። ይህ የሚያመለክተው የክርስቶስንና የእርሱ የኾነችውን ቤተ ክርስቲያን ግንኙነት ነው። በቤትህ እንደ ወይን የተወደደች ናት በማለት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ውበት ያነሣል። ስለዚህ በፈሪሓ እግዚአብሔር ውስጥ የሚኖሩ የቤተ ክርስቲያን አካሎች የምግባር ውበታቸውን ሳያጡት እንደሚኖሩ፤ ወይን እኮ የላቸውም የተባሉት በዚህ ዓለም ፍልስፍናና ፍቅር የነጎዱትን ነው። የጠፉትን ወደ በረቱ ለመሰብሰብ የተደረገ የፍቅር ጥሪ ነው!!

ወይን እኮ የላቸውም። ፍቅረ ቢጽ ወፍቅረ እግዚአብሔር የላቸውም። የራሳቸውን ስሜት በመውደድ የሠለጠኑ ናቸውና ወይን ፍቅር የላቸውም!! ወይን ጣዕሟ እንደሚያረካ ነፍሳቸው የምትረካባቸው ቃለ እግዚአብሔር የላቸውም!! ቃልህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴ ብርሃን ነው ተብሏል እነርሱ ግን ይህ በአንተ ቃል የመመራት ሐሳብ የላቸውምና  በቃልህ የመመራት ኃይልን ሙላባቸው!! እንግዳ ክፉ ፈቃድ ተነሥቶባቸዋልና ይህን ድል የሚያደርጉበትን ወይን ትዕግሥትን ስጣቸው። መናፍቃን ለሚያቀርቡባቸው ጥያቄዎች መልስ ሰጥተው ሰውነታቸውን በእውነት መሠረት ላይ ይገነቡት ዘንድ ወይን ማስተዋል የላቸውምና ማስተዋሉን አድላቸው!!

ወይን ሕገ ወንጌል ናት። በሕገ ወንጌል ወይን ውስጥ ገብተው ይኖሩ ዘንድ ወይን የወንጌል ምሥጢራትን የሚረዱበት ሀብተ ትርጓሜ የላቸውም። በወንጌል ውስጥ የተዘገበው ሰላም ቀድሞ ባለበሳቸው ጥላቻ ምክንያት አልተገኘላቸውምና “ወይን እኮ የላቸውም" ። የሕይወት ወይን አንተን ራስህን በማጣት ሕማም ውስጥ ገብተው ቆስለዋልና አምላክነትህን ገልጠህ አሳያቸው። በሕይወት ውጣ ወረድ ውስጥ የሚገጥማቸውን መከራ በጽናት ይቀበሉ ዘንድ ወይን እኮ የላቸውም። በእርግጥ የእመቤታችን ድምጿ በልጇ ዘንድ ይሰማል። የእኛ ጉድለትም ስለ እርሷ ሲባል ይሟላል። ብቻ እናችን ቅድስት ኾይ ከመዝሙር ይልቅ ዘፈን ደስ የሚያሰኘንን እኛን ወይን እኮ የላቸውም በይልን!! ጌታ ሆይ ወይን ደምህን ጠጥተን ምሬተ ኃጢአታችንን ታስወግድ ዘንድ ስለ እናትህ ብለህ ወይንህን ስጠን!! አሜን።

#ከዲያቆን_ዮሐንስ_ጌታቸው

/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ጥር_10

#ጾመ_ገሃድ

ጥር አስር በዚህች ዕለት ምንም ምን መብልን ሰይቀምሱ ምእመናን ሁሉ እስከ ምሽት ይጾሙ ዘንድ ከእኛ አስቀድመው የነበሩ ታላላቅ ሊቃውንት የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሥርዓትን ሠሩ በምሽትም ቢሆን በታላቁ ጾም ከሚበላው በቀር ጥሉላትን እንዳይቀምሱ። በዚች ዕለት ምእመናን እስከ ምሽት እንደመጾሙን ያዘዙበት ምክንያቱ ይህ ነው የልደትና የጥምቀት በዓል በዓል በረቡዕ ወይም በዓርብ ቀን ቢሆን በበዓለ ኃምሳ የሚበላውን የጥሉላት መብል በጥዋት በመብላት ምእመናን ሁሉ በዓሉን እንዲአከብሩ የከበሩ አባቶቻችን ሐዋርያት አዝዘዋል እሊህ ሁለቱ የእግዚአብሔር ታላላቅ በዓላቶቹ ናቸውና።

እኛ በዚህ በኅላፊው ዓለም ተድላ ደስታ ደስ የሚለን ለሌሎች እንዳይመስላቸው እንደ አይሁድና እንደ አረማውያን በዓል በመብልና በመጠጥ ብቻ እንዳናደርግ ስለዚህ ከልደትና ከጥምቀት በዓል በዋዜማ ያሉትን ሁለቱን ዕለታት እንድንጾም አዘዙን የልደትና የጥምቀት በዓል በረቡዕና በዓርብ ላይ በሚሆን ጊዜ በረቡዕና በዓርብ ፈንታ እንድንጾማቸው ይገባልና በዚህም ሁለት ሥራ ይፈጸምልናል የጾም ሥራና የበዓል ማክበር ሥራ ነው። እንዲሁም በግብፃውያን አብያተ ክርስቲያን የተሠራ ነው።

በይረሙን በእሑድ ወይም በአይሁድ ሰንበት ቀን ቢሆን ይህም ጌታ የተገለጸበት ጥር ዐሥራ ቀን ነው በዋዜማው ዐርብ እስከ ምሽት ይጹሙ አስቀድመን እንደተናገርን ጥሉላት አይብሉ የልደትና የጥምቀት በዓልም ሰኞ ቀን ቢሆን በሰንበት ቀን ይጾም ዘንድ አይቻልም ነገር ግን ጥሉላትን ከመብላት ይጠበቁ።

በጥምቀትም ዕለት ከእኵለ ሌሊት በፊት ተነሥተው በውኃው ላይ ይጸልዩና ይጠመቁ ሕፃናትም በሚጠመቁ ጊዜ በውኃ እንዳይገድፉ ካህናቱም ከመንጋቱ በፊት ቀድሰው ቊርባኑን ያሳርጉ እጅግም ማልደው በጥዋት ከቤተ ክርስቲያን ይውጡ በከበረ ሥርዓታቸው ጌቶቻችን ሐዋርያት እንዳዘዙ።

የመለካውያን ወገኖች ግን የልደትና የጥምቀት ዋዜማ በቅዳሜ ቀን ወይም በእሑድ ቀን ቢሆን በሦስት ሰዓት ይቀድሳሉ ከወደዱም የተባረከ ኅብስት ተመግበው ውኃ ይጠጣሉ ከዚህም በኋላ ካህናቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሁነው በየሰዓቱ በመጸለይ ለበዓሉ የሚገባውን የነቢያትን ትንቢቶች ያነባሉ በዚያች ቀን በምሽት ይኸውም ጥር ዐሥር ነው በውኃው ላይ ይጸልያሉ ይህም አባቶቻችን ሐዋርያት እንዳዘዙት አልሆነም። እርሳቸው የኤጲፋንያን በዓል እንዲአክብሩ አዘዋል ይኸውም መድኃኒታችን የተገለጠበት ካኑን በሚባል በሮም ሁለተኛ ወር በሰባት ይህም ጥር ዐሥራ አንድ ቀን ነው።

መለካውያን ግን የከበሩ አባቶች የቤተ ክርስቲያን መምህራን ያዘዙትን ይተላለፋሉ በልደትና በጥምቀት በዓል ዓርብም ረቡዕም ቢሆን አስቀድመው በርሱ ፈንታ ሳይጾሙ በጥዋት ተነሥተው ይበላሉና። እኛንም ከበደላችን ያነጻን ዘንድ በዮርዳኖስም ወንዝ እንደ ተገለጸ የጌትነቱን ክብር በልቡናችን ይገልጥልን ዘንድ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እንለምነው።

ጌትነት ክብር ስግደት ለእርሱ ይገባልና ከቸር አባቱ ጋር ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)

/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#በጥምቀት_ዙሪያ_የሚነሱ_ጥያቄዎች_እና_መልሶቻቸው
#ጌታችን_ለምን_ተጠመቀ?
1. ምሥጢርን ለመግለጥ፡-
ጌታችን በፈለገ ዮርዳኖስ ሲጠመቅ ምስጢረ ሥላሴ ግልፅ ሆኗል፡፡ አብ በደመና “የምወደው የምወልደው ልጄ ይህ ነው” በማለቱ አብ የወልድ አባት መሆኑ ታወቀ፡፡ መንፈስ ቅዱስም የባሕርይ ሕይወቱ መሆኑን ሲያስረዳ በአምሳለ ርግብ በራሱ ላይ ተቀመጠ ወልድም በተለየ አካሉ በዮርዳኖስ ሲጠመቅ ታየ፡፡ ስለዚህ ምሥጢርን ለመግለጥ ስንል የአንድነት የሦስትነት ምስጢር በጐላ ሁኔታ እንዲታወቅ ተጠመቀ ማለት ነው፡፡ /ማቴ. 3፥16/

2. ትንቢቱን ለመፈፀም፡-
በመዝሙር 46/47/፥16 ላይ “አቤቱ ውሆች አዩህ፣ ውሆችም አይተውህ ፈሩ ጥልቆች ተነዋወጡ ውሆችም ጮኹ፡፡” ተብሎ በቅዱስ ዳዊት የተነገረውን ትንቢት ለመፈፀም ተጠመቀ፡፡

3. አርአያ ሊሆነን፡-
ተጠምቆ እንድንጠመቅ አደረገን ሥርዓትን ሠራልን ቀድሞ በአርአያውና በአምሳሉ እንደፈጠረን አሁንም አርአያ ምሳሌ ሆነን፡፡ ለዚህም ነው ምሳሌን ከእኔ ተማሩ ያለን፡፡ /ማቴ 11፥29/ ለትምህርት ለአርአያ /ዮሐ. 13፥1-17/

4. የዕዳ ደብዳቤያችንን ለመደምሰስ፡-
አዳምና ሔዋን ፍዳው በፀናባቸው መከራው በበዛባቸው ጊዜ የሚያቃልልላቸው መስሏቸው ዲያብሎሰ ስመ
ግብርናችሁን ጽፋችሁ ስጡኝ ባላቸው ጊዜ አዳም ገብሩ ለዲያቢሎስ (አዳም የዲያብሎስ የወንድ አገልጋይ) ሔዋን ዓመቱ ለዲያብሎስ (ሔዋን የዲያብሎስ ሴት አገልጋይ) ብለው ጽፈው ሰጡት፡፡ ዲያብሎስም ይህንን ደብዳቤ አንዱን በሲኦል አንዱን በዮርዳኖስ አስቀመጠው፡፡ በዮርዳኖስ ያስቀመጠውን ጌታችን ሲጠመቅ እንደሰውነቱ ረግጦ ደምስሶታል፡፡ ይህንን ጽሕፈት ለመደምሰስ ነው ጌታችን በዮርዳኖስ የተጠመቀው፡፡ ለዚህም ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተፃፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፡፡” ያለው ቆላ 2፥14

#ጌታችን_መች_ተጠመቀ?

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀው በ5531 ዓመተ ዓለም ዘመነ ሉቃስ ማክሰኞ ጥር 11 ቀን ከሌሊቱ በ10ኛው ሰዓት ነበር፡፡ ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 19 በተጠመቀም ጊዜ ዕድሜው 30 ዓመት ከ13 ቀን ነበር፡፡ /ሉቃ. 3፥23/

#ጌታችን_ስለምን_በ30_ዓመት_ተጠመቀ?
በብሉይ ኪዳን ሥርዓትና ልማድ ካህናት ለቤተ እግዚአብሔር ተልእኮ እና መንፈሳውያን አገልግሎቶች ከ30 ዓመት ዕድሜ በፊት አደባባይ አይወጡም ነበር፡፡ እጅግ አስፈላጊ እንኳ ቢሆን ከ20 እና 25 ዓመት አስቀድሞ ለአገልግሎት መሰየም ልማድ አልነበረም፡፡ የቤተ እግዚአብሔር አገልጋዮች በዕድሜና በዕውቀት የበሰሉ፣ በጠባይና በሥራ ልምድ የተፈተኑ ተልዕኳቸውን በብቃት ለመወጣት በተገልጋዩ ሕዝብ ዘንድ የተመሰከረላቸው መሆን ነበረባቸው፡፡ /ዘፀ. 4፥3፤1ዜና መዋ. 23፥24፤ 1ጢሞ.  3፥6-10/ ያንን ሥርዓት ለመፈጸም ጌታችን የተጠመቀውና ለትምህርተ ወንጌል የተገለጠው በ30 ዓመቱ ነበር፡፡

ዮሐንስ መጥምቅም የጌታን መምጣት ለማወጅ በዮርዳኖስ ይሁዳ ምድረ በዳዎች ወጥቶ የታየው ከ30 ዓመት ዕድሜው በኋላ ነው፡፡ ሌላው ዐቢይ ምክንያት የሰው ሁሉ መጀመሪያ አዳም የ30 ዓመት ጎልማሳ ሆኖ ተፈጥሮ በ40ኛ ቀን ተሰጥቶት ኋላም በኃጢአት ምክንያት ያስወሰደውን ልጅነት ለማስመለስ ነው፡፡

ክርስቶስ የተጠመቀው ክብር ሽቶ ሳይሆን የአብ የባሕርይ ልጅነቱን (የባሕርይ አምላክነቱን) ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ለማስመስከር፣ ውኃውን ለመቀደስ፣ የአዳምን ልጆች የእዳ ደብዳቤ ለመደምሰስና በስህተት የጠፋውን የልጅነት ክብር ለመመለስ ነው፡፡ ጌታ ተጠምቆ ከውኃው ከወጣ በኋላ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ በማረፍ አብ በደመና ‹‹ይህ ልጄ ነው›› ብሎ ሲመሰክርለት ምሥጢረ ሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በጉልህ ተረጋግጧል፡፡ /ማቴ. 3፥16/

#ጌታችን_በዮሐንስ_እጅ_ለምን_ተጠመቀ?

ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ ሲሆን በአገልጋዩ በቅዱስ ዮሐንስ እጅ ይጠመቅ ዘንድ በፍጹም ትሕትና ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ ይህንንም ያደረገልን አብነት ሊሆነን ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታችን ቅዱስ ዮሐንስን ‹‹መጥተህ አጥምቀኝ ›› ብሎት ቢሆን ኖሮ ነገ ነገሥታቱና መኳንንቱ ካህናቱን መጥታችሁ አጥምቁን ባሉ ነበር ስለዚህ እንዲህ እንዳይሆን ነው፡፡ ጌታችን ‹‹ጌታ ስሆን በባርያዬ እጅ እንደተጠመቅሁ እናንተም ወደ ቤተክርስቲያን ሄዳችሁ በካህናት እጅ ተጠመቁ›› ሲል ነው፡፡

ጌታችን በዮርዳኖስ የተጠመቀው ልጅነትን የምታሰጥ ጥምቀትን ባርኮ ቀድሶ ሊሰጠን እንጂ ክብር እንዲሆነው አይደለም፡፡ ምክንያቱም፡- እርሱ እከብር አይል ክቡር እጸድቅ አይል ጻድቅ ነውና፡፡

#ቅዱስ_ዮሐንስ_ጌታችንን_በማን_ስም_አጠመቀው?

ጌታችን ዮሐንስን አጥምቀኝ ባለው ጊዜ "ሌላውን በአንተ ስም አጠምቃለሁ አንተን በማን ስም ላጥምቅህ? በአብ ስም እንዳላጠምቅህ አብ አባትህ ባንተ ሕልው ነው በወልድ ስም እንዳላጠምቅህ ወልድ አንተ ነህ በመንፈስ ቅዱስ ስም እንዳላጠምቅህ መንፈስ ቅዱስ ሕይወትህ ባንተ ሕልው ነው ታዲያ በማን ስም ላጥምቅህ?" ብሎ ቢጠይቀው ጌታም ‹‹እንደ መልከጼዴቅ ሥርዓት አንተ የዓለም ካህን ብርሃንን የምትገልጥ የአብ የባሕርይ ልጅ ሆይ ይቅር በለኝ›› ብለህ አጥምቀኝ አለው፡፡

#ዮሐንስ_ጌታን_ሲያጠምቀው_እጁን_ለምን_አልጫነበትም?
- ዮሐንስ በጥምቀት አከበረው /ልዕልና ሰጠው/ እንዳይባል፡፡
- መለኮትን በእጅ መንካት ስለማይቻል

#ጌታችን_ጥምቀቱን_ለምን_በዮርዳኖስ_አደረገው?
በኢየሩሳሌም አካባቢ ብዙ ወንዞች ኩሬዎችና ሐይቆች መኖራቸው የታወቀ ነው፡፡ ጌታ ጥምቀቱን በዮርዳኖስ ያደረገው ስለዚሁ አስቀድሞ የተነገረውን ትንቢት መፈጸሙን ለማረጋገጥ ነው፡፡ ‹‹ባሕር አይታ ሸሸች ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ›› /መዝ.113፥3/ ከዚህም ጋር ከላይ ምንጩ አንድ የሆነው ዮርዳኖስ ዝቅ ብሎ በደሴት ተከፍሎ እንደገና እንደሚገናኝ በግዝረት በቁልፈት (በመገዘርና ባለመገዘር) ተለያይተው የነበሩ ሕዝብና አሕዛብ መላው የአዳም ልጆች በጌታችን ጥምቀት አንድ መሆናቸውን የሚገልጽ ትርጉም አለው፡፡ እስራኤል ዮርዳኖስን ተሻግረው ምደረ ርስት ገብተዋል፡፡ ያመኑ የተጠመቁ ምዕመናንም በጥምቀት ገነት መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉ፡፡ ሌላው በዮርዳኖስ ተጥሎ የነበረውን የዕዳ ደብዳቤ ይደመስስልን ዘንድ /ቈላ. 2፥14/

#ጌታችን_ለምን_በውሃ_ተጠመቀ?
እግዚአብሔር አምላክ በዘመነ ኦሪት ሰብዐ ትካትን በንፍር ውሃ ፈርኦንና ሰራዊቱን በኤርትራ ባሕር ካጠፋ በኋላ ሰዎች ውሃ ለመዓት እንጂ ለምሕረት አልተፈጠረም ይሉ ነበርና ለምሕረት እንደተፈጠረ ለማጠየቅ በውሃ ተጠመቀ ( ዘፍ 7÷17፤ ዘጸ 14÷1-29)

አንድም ውሃ እሳትን ያጠፋል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ከገሃነመ እሳት ትድናላችሁ ሲል ነው፡፡

አንድም ውሃ መልክን ያሳያል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ መልክዓ ሥላሴን የአምላክን ቸርነት ርህራሔ ታያላችሁ ሲል ነው፡፡

አንድም በማር በወተት ቢጠመቅ ኖሮ እነዚህ ለባለጸጎች እንጂ ለድሆች አይገኝም ውሃ ግን በሁሉ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ጥምቀት የታዘዘ ለሁሉ ነው ሲል ነው፡፡

አንድም ማርና ወተት ቢታጠብበት ያቆሽሻል እንጂ አያነጣም ውሃ ግን እድፍን ያስለቅቃል እናንተም በማየ ገቦ ብትጠመቁ ከኃጢአት ትጠራላችሁ ሲል ነው፡፡

አንድም ማርና ወተት ተክል ላይ ቢያፈሱት ያደርቃሉ እንጂ አያለመልሙም ውሃ ግን ያለመልማል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ልምላሜ ሥጋ ወነፍስ ታገኛላችሁ ሲል ነው፡፡ (ዮሐ 19÷35)

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ልዩ የመንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ዝግጅት
በሀ/ማ/ደ/ገ/ቅ/ማ/ቤ/ክ በቀን 5/5/2016 ከቀኑ 10 ሰዓት

በታቦት ዙሪያ ለሚነሱ ጥያቄዎች በሊቃውንተ ቤተ መልስክርስቲያን መልስ ስለሚሰጥበት ሁላችሁም ምዕመናን ተጋብዛችኋል



አዘጋጅ መሠረተ ተዋህዶ ሰ/ት/ቤት

ቦታ= ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን :ዓውደ ምህረት

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ጥር_1_ቅዱስ_እስጢፋኖስ_የተወለደበት_እና_የሰማዕትነት_አክሊል_የተቀበለበት_ዕለት_ነው ።

#እስጢፋኖስ፦የስሙ ትርጉም በግሪክ ቋንቋ አክሊል ማለት ነው፡፡ በግብሩ የቀን ሃሩር የሌሊት ቁር የማይለውጠው፣ መብራት ማለት ነው፡፡

አባቱ ስምኦን፣ እናቱ ሃና ይባላሉ፡፡ የተወለደው - ጥር 1 ቀን በእስራኤል ሃገር ውስጥ በብፅዓት / በስለት/ ነው፡፡ ልዩ ስሟ ሐኖስ በተባለ ቦት ተወለደ ከመጥምቁ ዮሐንስ እግር ሥር በመሆን ተምሯል፡፡

በደሙ የመሠረታት የክርስቶስ ቤተክርስቲያን በጽርሐ-ጽዮን ከመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከተቀበለች በኋላ የትንሣኤውን ወንጌል ለትውልድ ማድረስ ጀመረች፡፡ ወንጌል እየተስፋፋ አማኞች እየበዙ መጡ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት የሚያግዟቸው ሰባት ጠቢባን ወጣቶችን መርጠው የዲቁና ሥልጣን ሰጡአቸው፡፡
ከተሾሙት ዲያቆናት መካከል ቅዱስ እስጢፋኖስ አንዱ ነው፡፡ ሐዋ. 6÷5. ቅዱስ እስጢፋኖስ ጥቅምት 17 ቀን የዲያቆናት አለቃ ሆኖ ሊቀ ዲያቆናት ተብሏል፡፡

ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር፡፡ ከግሪክ አገር የመጡ አይሁድ በተከራከሩት ጊዜ በመንፈስና በጥበብ መለሰላቸው፡፡ አይሁድም ዳኞች በተሰየሙበት ሸንጎ ፊት አቅርበው በሐሰት ከሰሱት፤ ሸንጎውም በድንጋይ እንዲወገር ፈረደበት፡፡ እስጢፋኖስ ግን በታላቅ ኃይልና በብዙ መረዳት ከአባቶቻቸው ታሪክ ተነሥቶ የዓለም መድኃኒት የሆነውን ክርስቶስን ሰበከላቸው፡፡ ጥላውን ከአካሉ ጋር እያጋጠመ ወደ ፍጹማን ጥበብ በጽድቅ ቃል መራቸው፡፡ አይሁድ በጣም ተቆጡ፤ ሁሉም በአንድነት ሆነው በድንጋይ ወገሩት፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሰውነቱ ቆስሎና ዝሎ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ባነሣ ጊዜ የልዑልን ክብር ተመለከተ፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአባቱ ቀኝ ቆሞ አየ፡፡ ሐዋ. 7÷55፡፡

ቅዱስ አሰስጢፋኖስ “እነሆ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅ (ኢየሱስ ክርስቶስ) በአባቱ ቀኝ ቆሞ አያለሁ” አላቸው፡፡ አይሁድ ግን ልበ-ደንዳኖች (የማይራራ ጨካኝ ልብ ያላቸው) ስለሆኑ እስጢፋኖስን ከከተማ ወደ ውጭ አውጥተው ደበደቡት፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሰውነቱ ደከመ፤ ነፍሱ ከሥጋው ልትለይ በደረሰች ጊዜ በሞት ጣር ሆኖ “ጌታ ኢየሱስ ሆይ ይህን ኃጢአት አትቁጠርባቸው፤ ነፍሴን ተቀበል” ብሎ ጸለየ፡፡ ነፍሱንም ለታመነው ፈጣሪ አደራ ሰጥቶ ጥር 1 ቀን በ34 ዓ.ም በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡

የሰማዕትነት ሕይወትን በመጀመሩ ስለ ክርስቶስ ፍቅር መራራ ሞትን በመታገሡ ቀዳሜ ሰማዕት ተብሏል፤ የቤተክርስቲያን የመጀመሪያው ሰማዕት ነውና፡፡

ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን እኛንም በሰማዕቱ ጸሎት ይማረን አሜን !!!



@dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

የአእላፋት ዝማሬ ይሄን ይመስል ነበር

Читать полностью…
Subscribe to a channel