dnhayilemikael | Unsorted

Telegram-канал dnhayilemikael - ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

1867

#መሰረታዊ_የቤተክርስቲያን_ክርስቲያን_ትምህርት / #የተለያዩ_ተከታታይ_ትምህርት ' #ስንክሳር_የቅዱሳን_ገድል_በየዕለቱ ! #ስዕለ_አድህኖ ! #ምስባክ #የየበአላቱ_ዋዜማና_ሥርተ_ማህሌት #መዝሙር #ግጥም #ለመናፍቃን_ጥያቄ_መልስ እና የተለያዩ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ ሌሎች መንፈሳዊ ጽሁፎች ይለቀቁበታል Administration @zearsema_dn

Subscribe to a channel

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ይህንን የመሰለ ሕንጻ ቤተ መቅደስ 👇
👉• መቅደስ ቢኖረውም ይጎበኛል እንጂ አይቀደስበትም
👉• አሁን ምዩዚዬም ነው
👉• ሁሉ ተሟልቶ የተሠራለት ቢሆንም አምልኮ አይፈጸምበትም
👉• መጠመቂያ ቢኖረውም የሚጠመቅበት የለም
ምክንያቱም የሀገሩ ሰዎች ሃይማኖታቸውን ትተዋል ሃይማኖት አልባ ሆነዋል ....ከሃይማኖት ባዶ መሆናቸውን በኩራት ያስጎበኛሉ...የካቴድራሉን ሕንጻ ከአገልግሎት ባዶ መሆኑን በኩራት ይናገራሉ!!!!

እኛም ይህንን አይተን ጎብኝተን ስለ ራሳችን
👉• ሀገር
👉• ሃይማኖት
👉• ቤተ ክርስቲያን
👉• ባህል ...ተነጋግረን ከመቅደሱ ወጣን
እኔም ይህንን ቃል አስቤ አዘንኩ 👇
ማቴዎስ 23
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁸ እነሆ፥ ቤታችሁ የተፈታ ሆኖ ይቀርላችኋል።
³⁹ እላችኋለሁና፥ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እስክትሉ ድረስ ከእንግዲህ ወዲህ አታዩኝም።"

👉እንደ አማኝና አገልጋይ ሁሌም የሚሰማኝ ይህ ነው !

👉ወደፊት የሚመጣው ትውልድ ቤተክርስቲያኗን ከነሥርዓቷ በምን ያህል መጠን ይረከባታል?

👉እኛ ስለ ዘርና ስለ ብሔር ስለ ሥልጣንና ሢመት ስለ ገንዘብና ኑሮ ስናስብ ትውልዱን ከእጃችን እየተቀማን ቤተ ክርስቲያንን ዝቅ አድርገን የኛን ልዕልና ብቻ ለማሳየት እየተጋን የት እንደርስ ይሆን?....

👉የቤተ ክርስቲያን አምላክ ትውልዳችንን በሃይማኖት ያጽናልን ይጠብቅልን
ተረካቢ አያሳጣን!!!!

መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው

ከ ኖርዌይ ትሮንዳሂም
ግንቦት 5 /2016 ዓ.ም

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ክርስቲያን_የሆነ_ሰው_ሳያነብ_እንዳያልፍ!!!

#ስንት_ዓመት_ተማርን?

❖አሁን የምንሰራው ስራ ለሥጋዊ ኑሮ የሚሆን የሚጠቅም ነው በዚች ምድር ላይ ሳለን እንዳይርበን እንዳይጠማን እንዳይበርድን ኑሮአችን ለማመቻቸት እንወጣለን እንወርዳለለን🤔
✟👉✥ከሕፃንነታችን ጀምሮ እንማራለን
ሶስት ዓመት ጊዜ ወስደን መዋእለ ሕፃናት ተምረናል
👉 አስራ ሁለት ዓመት ጊዜ ሰጥተን 12 ክፍል ጨርሰናል(አቋርጠንም ያለን ልንኖር እንችላለን
👉 አምስት ዓመት በላይ ጊዜ ሰጥተን በድግሪ በማስተር ተመርቀናል
👉ባጠቃላይ የሥጋ ሥራ ለመያዝ ከሃያ ዓመት በላይ ተምረናል
🤔እንደዚህም ተምረን ስራ አጥተን በስራ ፍለጋ ደክመናል ወንድሜ(እህቴ) ሆይ አሁን ከ20 ዓመት በላይ የተማርነው ትምህርት ለስንት ዓመት ያሰራናል ?
🤔ጡረታ እስክንወጣ ነው ከዛ በሇላ የተማርነው ትምህርት አያገለግለንም
ከ20 ዓመት በላይ ስንማር የፈተፈተነው ጊዜ እናስብ ጭንቀቱን ድካሙን እንቅልፍ ማጣቱን
ከትምህርት ቤት ለመድረስ የእግር ጉዞውን ሁሉ አንርሳ ያ ሁሉ ደክመን የተማርከው ስንሞት አይጠቅመንም 🙊
🤔ሥጋችን መቃብር ሲገባ ምድራዊ እውቀታችን አብሮ ይቀበራል
👉በህይወት እያለን ጡረታ የምንወጣው መስራት አትችሉም ተብለን ነው
👉🤔ከ20 ዓመት በላይ በተማርነው ትምህርት ብንሰራበት 30 ዓመት ቢሆን ነው ያም እድሜ ከታደለህ ነው።
👉🤔ወንድሜ(እህቴ) ሆይ እስቲ ልጠይቃችሁ
ለሥጋችን ስራ ለመስራት ከ20 ዓመት በላይ ተምረናል
#ለነፍሳችን ስንት ዓመት ተማርን?
👉ለነፍሳችን የተማርነው ትምህርት ጡረታ የለውም
በሥጋ የተማርነው የመንግሥት ስራ ያስይዘናል
👉በነፍስ የተማርነው የእግዚአብሔር ስራ ያስይዘናል
የነፍስ ትምህርት ምን ይመስለናል ቃለ እግዚአብሔር ነው
✥#የእግዚአብሔርን ቃል በወር ስንት ሰዓት ተምረናል ?
👉✥በዓመት ስንት ቀን ይሆናል የተማርንበትም ጊዜ እስቲ እንደምረው?
✥ባጠቃላይ የተማርንበት ጊዜ እስክንሞትስ ስንት ዓመት ይሆናል?
👉✥ መቼም የሥጋውን የተምህርት ጊዜ አያክልም
✥በነፍስ የተማርነው ትምህርት ስንት ዓመት እንደሚያሰራልን እናውቃለን ?
✥ቁጥር የማይደርስበት ጊዜ ነው
ዘመናት አልፈነው እንሰራበታለን ለዘላለም ጡረታ አያወጣንም
👉✥እኛ ግን ይሄን ረስተናል ቀኑን ሙሉ ለሥጋችን እንሮጣለን ለነፍሳችን የምንማርበት ጌዜ አጥተናል በሚያልፈው ነገር እራሳችንን ቢዚ አድርገናል ::
👉✥ሁለት ሰኣት ቁጭ ብለን የተለያዩ ፊልም እናያለን 30 ደቂቃ ቁጭ ብለን ወንጌል መማር ይሰለቸናል::
👉✥ሁለት ሰአት ቆመን እያጨበጨብን ኳስ እንደግፋለን 2 ሰአት ቆመን ቅዳሴ ማስቀደስ አቅቶን በዕለተ ሰነበት ተኝተን እናረፍዳለህን
👉✥ልብ ወለድ ዝሙታዊ የሆኑ መጻፎችን በየቀኑ እናነባለን የእግዚአብሔር እስትንፋስ የሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍን ለማንበብ ይሰለቸናል
👉✥ለዘፈን የከፈትነውን አፋችንን ለምስጋና ይዘጋል
👉✥ለሀሜት የሚፈጥነው አፋችን ለጸሎት ይዘገያል
👉✥ለእስፓርት የጠነከረው ጉልበታችን ለስግደት ይዝላል
👉✥ለስርቆት የሚላከው እጃችን ለምጽዋት አይታዘዝም
👉✥ወደጭፈራ ቤት የሚገሰግሰው እግራችን ወደ ቤተክርስቲያን ለመሄድ ይተሰሰራል
👉✥ሀሜት የሚሰማው ጆሮአችን ወንጌል ለመስማት ይደነቁራል
👉✥የዝሙት ሸቶ የሚያሸተው አፍንጫችን የመቅደሱን እጣን ሽታ ይፀየፈዋል
👉✥ጫት የለመደው አፋችን ሥጋውን እና ደሙን ረስቶአል
👉✥አልኮል የለመደው አፋችን ፀበሉን ተፀይፎታል
👉✥ ቂም የሚቋጥረው ልባችን ፍቅርን ረስቷል
🤔✥ስናጣ እግዚአብሔርን እንቀርበዋለን ስናገኝ ግን እንርቀዋለን
🤔👉ስንጨነቅ አምላካችንን እንጠራዋለን ስንደሰት እንረሳዋለን
🤔✥ወንድሜ(እህቴ) ሆይ በህይወታችን አንቀልድባት
👉✥ከእኛ በፊት የነበሩት ተዋቂው አዋቂው ሁሉ የት አሉ? 👉✥መቃብር ውስጥ አይደሉምን ?
✟✥✟ይህንን አስበን ከፈጣሪያችን ጋር የሚያገናኝ ስራ እንስራ
✟✥✟ በአዲስ ዓመት አዲስ እቅድ ያስፈልገናል
✟✥✟ወደቤተ ክርስቲያን ሄደን ዘወትር ወንጌል እንማር
✟✥✟ ለማስቀደስ ለመፆም ለመስገድ እንትጋ
✟✥✟ ለንስሐ እንዘጋጅ ቅድሚያ ለነፍሳችን ሁሉን ነገር እናድርግ
❖አንደበታችን ለጸሎት ይትጋ
❖እጅአችን ለምጽዋት ይዘርጋ
❖ልባችን ለምህረት ይነሳሳ
❖ሥጋውን እና ደሙን ለመቀበል እንወስን

👉👉✥ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከአካፈልኩ በኁላ ቻነላችንን ይቀላቀሉ👉 @dnhayilemikael
ሌሎችም እንድማሩበት #ሸር ያድርጉ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔም ጸልዩ!
✥"ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን

#ሌሎች_እንዲያነቡትና_እንድማሩበት_አስተማሪ_ሆኖ_ካገኛችሁ_ሼር_ያድርጉ!
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@dnhayilemikael
@dnhayilemikael
@dnhayilemikael
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#እንኳን_ለኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተ_ክርስቲያን_ታላቁ_ሊቅ_ቅዱስ_ያሬድ_ዓመታዊ_መታሰቢያ_በዓል_አደረሰን!

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲__ አንቀጽ 11 ስለ ሕዝባውያን ይናገራል

፩) ወደ ኃጢአት ሥራ የሚሄድ አንድ ሰው ስንኳ ቢኖር የእግዚአብሔርን ትእዛዝ አፍርሷልና ከዓላዊ ጋር ይቆጠራል።

፪) እግዚአብሔር በሰጠህ መልክ ላይ ሌላ መልክ አትጨምር። አትከተብ፣ አትጠቆር።

፫) ያድግ ዘንድ ጸጉርህን አትንከባከበው። ጺምህ አትላጭ። (ለወንዶች)። ሰው ከባሕርይው ያገኘውን መልክ አይለውጥ።

፬) ረቂቅ (ስስ) ልብስ አትልበስ። ለጣትህም የወርቅ ቀለበት አታድርግ። ይህ ሁሉ የዝሙት ምልክት ነውና።


፭) ከደጋግ ሰዎች ጋር ሕይወት የሚገኝባትን የወንጌልን ነገር ተነጋገር። ሁልጊዜ መልካም ነገርን ሥሩ።


፮) የወንድሞቻችሁን በደል ፈጥናችሁ ይቅር ማለት ይገባችኋል። ብትቆጡ ይቅር ሳትሉ አትደሩ።

፯) በክርስቶስ ያመንን እኛ ሥራ ፈት ሁነን መኖር አይገባንም [ቁጥር ፬፻፴፬]። ምእመናን ሆይ ከሚያሳፍር ነገር ራቁ። የማይረባ የማይጠቅም ነገር አትናገሩ።


፰) በአንድ ሰውስ እንኳ ክፉ ነገር አትናገር። ሁለት አንደበት አትሁን። ክፉ ምክር አትምከር። ቀናተኛ አትሁን። ቁጡ ብስጩ፣ ጠብ ክርክር ወዳጅ አትሁን።


፱) ሰው የሰይጣን ማደሪያ የሚሆነው በነፍስ ጽነት ሲገኝባት ነው።

፲) ያገኘኽውን ሁሉ አመስግነህ ተቀበል።

፲፩ ......ይቀጥላል ....



#share

ቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ
   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮

    የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን 
              ➡️      መሰረተ ሚዲያ

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
     ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ

👇👇👇👇👇👇👇👇

የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═
/channel/Meseretemedia

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

+ ወደ ኖኅ መርከብ ለመጨረሻ ጊዜ የገባችው እንስሳ +

የኖኅ መርከብ ጉዳይ በጣም አስገራሚ ከሚሆኑብኝ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች አንዱ ነው:: በዓለማችን አሁን ያሉ እንስሳት ሁሉ "ከነ ባለቤትዎ" እንዲገኙልን እንደሚባልበት ሰርግ ጥንድ ጥንድ ሆነው የገቡባት ትልቅ መርከብ ታሪክ : ዳግም ለሰው ልጆች ወላጆች ለመሆን የተመረጡ አራት ወንዶችና አራት ሴቶች ብቻ የተሳፈሩባት ትልቅ መርከብ ሁኔታ ትኩር ብሎ ላየው አስገራሚ እውነቶችን ያዘለ ነው::

ከሁሉም በላይ ግን መርከቢቱ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ መሆንዋ ብዙ ነገር እንድናስብ ያግዘናል:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "ወደ ኖኅ መርከብ ተኩላ ገብቶ ሲወጣም ተኩላ ሆኖ ይወጣል:: ወደ ቤተክርስቲያን ግን ተኩላ ሆነው ገብተው በግ ሆነው የወጡ ብዙዎች ናቸው" ብሎአል::

እውነትም ቤተ ክርስቲያን ወደ እርስዋ የገቡትን መለወጥ የምትችል መርከብ ናት:: ወደ ቤተ ክርስቲያን እንደ ጅብ ሆዳም ሆነው ገብተው ጾመኞች ሆነው የወጡ አሉ:: እንደ የሌሊት ወፍ በቀን መኖር አቅቶአቸው ሌሊቱን የልባቸው ዓይን ታውሮ በኃጢአት ጨለማ ሲደናበሩ የኖሩ ሰዎች ወደ መርከቢቱ ገብተው እንደ ንስር አርቀው አጥርተው ቀኑን የሚያዩ ሆነዋል:: ቤተ ክርስቲያን ወደ እርስዋ የገቡትን የምትለውጥ መርከብ ናት:: ውኃ ወደ እርስዋ ሲገባ ጠበል ይሆናል:: አፈር ወደ እርስዋ ሲገባ እምነት (እመት) ይሆናል:: ዘይት ወደ እርስዋ ሲገባ ቅዱስ ቅባት ይሆናል:: ኅብስትና ወይን ወደ እርስዋ ሲገባ ወደ ቅዱስ ቁርባን ይለወጣል::

ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ያልተለወጠ ሰው ግን ሲገባም ጅብ ሲወጣም ጅብ ሆኖአል:: ኖኅ ከመርከብ መልእክት ልኮት የቀረው የቁራ ነገርስ? ከቤተ ክርስቲያን ወጥተው ስንቶች በዚያው ቀርተዋል? ለዓለም ጨው እንዲሆኑ ተልከው በዚያው ሟሙተው የቀሩ ስንት አሉ:: ርግብ ግን ማረፊያ ስታጣ ተመልሳ ነበር:: ከመርከቢቱ የራቅን ሁላችን "ልባችን በእግዚአብሔር እስካላረፈ ድረስ ዕረፍት የለውም" እንዳለ ሊቁ ወደ መርከቢቱ ፈጥነን መመለስ አለብን::

ሰሞኑን ደግሞ አንድ ጥያቄ በአእምሮዬ ተመላለሰብኝ:: "ወደ ኖኅ መርከብ ለመጨረሻ ጊዜ የገባው እንስሳ ማን ሊሆን ይችላል?" የሚል:: ይህን ጥያቄ በግልም በጉባኤ ላይም ሰዎችን ጠይቄ ነበር:: መቼም ለዚህ ጥቅስ አያስፈልገውም:: ኖኅ ቆሞ እንስሳቱ እስኪገቡ ድረስ እንደጠበቀና ማንንም እንስሳ ጥሎ እንዳልገባ የታወቀ ነው::
በዚህ ምክንያት እንስሳቱ ወደ መርከቢቱ የሚገቡት እንደደረሱበት ቅደም ተከተል ነው:: ክንፍ ያላቸው በርረው ቀድመው ይገባሉ:: እንደ ጥንቸል እንደ ካንጋሮ እንደ ሚዳቁዋ ያሉትም እየዘለሉ ፈጥነው ይገባሉ::

ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ነፍሳቸውን ለማዳን ፈጥነው በርረው የገቡ እንደ ሚዳቋ ዘልለው የደረሱ ብርቱዎች አሉ:: እንደ ፒኮክ ያሉ ባለ ውብ ክንፎች : እንደ ቀጭኔ ያሉ ባለ ረዥም አንገቶች እንደ ጃርት ያሉ ሌላው ላይ የሚሰኩት እሾኽ የለበሱ እንስሳት ወደ መርከብዋ ገብተዋል:: በቤተክርስቲያን እንደ ፒኮክ አምሮ መታየት መዘባነን የሚወዱ ለታይታ የሚገዙ ብዙዎች ገብተዋል:: እንደ ቀጭኔ አንገታቸውን ከፍ አድርገው ሰውን ቁልቁል የሚመለከቱና "አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የዕብራውያን ሴቶች" ዓይነት ሕይወት ያላቸውም ገብተዋል:: እንደ ጃርት በክፉ ንግግር የሰው ልብ ላይ የሚሰኩት ጥላቻ የተላበሱ ሰዎችም ገብተዋል:: የኖኅ መርከብ ያልያዘችው እንስሳ እንደሌለ ቤተ ክርስቲያንም ያልተሸከመችው ዓይነት ሰው የለም::

ወደ ጥያቄው ስመለስ በእኔ ግምት ወደ መርከቡ በጣም ዘግይታ የገባችው ኤሊ ነበረች:: በላይዋ ድንጋይ የተጫናት እጅግ ቀርፋፋዋ ኤሊን የማይቀድም እንስሳ መቼም አይኖርም:: ምንም ብትዘገይም ኖኅ እስከመጨረሻው ጠብቆ አስገብቶ ለዘር አትርፎአታል:: የኤሊ ዘሮችም "ኖኅ ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ዳይኖሰር በጠፋን ነበር" ብለው ኖኅን ማመስገናቸው አይቀርም:: እግዚአብሔር ምንም ብትዘገይ ኤሊ ሳትገባ መርከቡን አልዘጋውም::

የኤሊ በመርከቡ መትረፍ በቤተ ክርስቲያን ልንተርፍ ተስፋ ለምናደርግ ለእኛ ትልቅ መጽናኛችን ነው::

ወዳጄ ወደ ቤተ ክርስቲያን ለመምጣት እንደ ወፍ ትበርራለህ? እንደ ሚዳቋ ትዘልላለህ? ወይንስ እንደ ኤሊ ትጎተታለህ? እግሮችህ ለመንፈሳዊ ነገር ሲሆን አቅም እያጡ አልተቸገርህም?
ልብህ ቢፈልግም እንደ ኤሊዋ የተጫነህ የኃጢአት ድንጋይ አላንቀሳቅስ ብሎህ አልዘገየህም?

እንዲህ ከሆነ አትጨነቅ መርከብዋ ቤተ ክርስቲያን አንተን ሳትይዝ ጥላህ ወዴትም አትሔድም:: ጉዞህን እስካላቆምህ ድረስ ትጠብቅሃለች:: እየተጎተትህም እየተሳብህም ቢሆን አንተ ብቻ ወደ ደጁ ገስግስ::
አንተ ብቻ መንገድ ጀምር እንጂ ፈጣሪ በሩን የሚዘጋው አንተ እስክትገባ ጠብቆ ነው::

ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር እንዲህ ብለህ ለምነው :-
"ብበድልህም እንኳን አሁንም በርህን እያንኳኳሁ ነው:: እየተጎተትሁም ቢሆን አሁንም የምጉዋዘው ወደ አንተ ለመምጣት ነው"

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሚያዝያ 5 2013 ዓ ም

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን አጥብቃችሁ ስለ እኔ ጸልዩልኝ!
በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)

/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ትንሣኤ ልቡና

✟ሰው አስቀድሞ በልቡ ካልተነሣ የኋለኛውን ትንሣኤ ማለትም ትንሣኤ ዘለክብርን ገንዘብ ማድረግ አይችልም።

❖“ዝናቡ እንዴ ነበር?” ለሚለው የአበው ጥያቄ ምላሹ “በየደጅህ እየው” እንደኾነ
ሁሉ በኋለኛው ዘመን በቀኝ የምንቆምበትን፣ “እናንተ የአባቴ ቡሩካን
ኑ ዓለም ከመፈጠሩ በፊት የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ"

የምንባልበትን ትንሣኤ ዘለክብርን ዛሬ በየልቡናችን ማየት አለብን።

ያኔ ለመነሣትና ክብር ለማግኘት አሁን በንስሓና በሥጋ ወደሙ ተወስኖ መጓዝ ያስፈልጋል እሱ ነው ትንሣኤ ልቡና።

✣ ይኽንን ነው አስቀድመን ገንዘብ ማድረግ ያለብን፡፡
❖ዛሬ በቃለ እግዚአብሔር እየተመራን፣ በምክረ ካህን፣ እየተጠበቅን በንስሓ
ሕይወት እየኖርን በቅዱስ ቁርባን ታትመን ልባችንን ለአግዚአብሔር
አያስገዛን ከተገኘን የፊተኛው ትንሣኤ ባለቤት ኾነናል ማለት ነው
“በፊተኛው ትንሣኤ ዕድል ያለው ብፁዕና ቅዱስ ነው፡፡ሁለተኛው ሞት
በእርሱ ላይ ሥልጣን የለውም
፡፡

❖ ማለትም ከትንሣኤ አስድማ በምትሆን
በትንሣኤ ልቡና ከምስጢረ ንስሓ ከምስጢረ ቁርባን ዕድል ፈንታ
ጽዋዕ ተርታ ያገኘ ሰው ንዑድ ክቡር ነው” ራእ. ፳፥፮

ስለኾነም ርስተ መንግሥተ ሰማያትን ለምንወርስበት የትንሣኤ ዘለክብር ባለቤቶች ለመኾን እንድንበቃ ከወደቅንበት ለሚያነሣን ከረከስንበት ለሚያነጻን ከራቅንበት ለሚያቀርበን ለምስጢረ ንስሓ /ትንሣኤ ልቡና/ እንዘጋጅ ዘንድ ፈቃደኞች እንሁን የፊተኛው ትንሣኤ ይኽ ነውና፡፡
አምላክ ቅዱሳን ልዑል እግዚአብሔር ጅማሬያችንንና ፍጻሜያችንን
ሁል ጊዜም ያሳምርልን አሜን፤
ይቆየን።


/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ግንቦት_ልደታ ስናከብር ፈጽሞ ማድረግ የሌለብን ነገሮች

እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልደት ክብረ በአል በሰላም አደረሳችሁ !!!

#ነገር ግን በበጎ ነገሮች #ሰበብ_ክፉ_ዓላማዉቅ ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መካከል መርዝን ከሚጨምርባቸዉ መንፈሳዊ በዓላት አንዱ #የግንቦት_ልደታ (የእመቤታችን የልደት በዓል) ነዉ፡፡

#በዚህ ዕለት አንዳንዶች #ባለማወቅ ሌሎች ደግሞ #በድፍረት ‹‹ለአድባር አዉጋር ነዉ፤ ቆሌዉን ለመለመን ነዉ›› እያሉ ለማያውቁት አምልኮ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቅቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ አሉ፡፡
#እውነታው እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸው፡፡
#እኛ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ግን እነዚህን የሃይማኖት ለዋጮች ሥራቸውን እንጸየፋለን፡፡ ስለሆነም ከእንደዚህ ዓይነቱ ባዕድ አምልኮ በመለየት ይህንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር ልናከብረው ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን በሠራችልን ሥርዓት መሰረት በቀናች በተዋሕዶ እምነት ሆነን፤ በምሕረቱ የጎበኘንን አምላካችንን ብቻ እያመለክን፤ የድኅነታችን ምክንያት የሆነችውን ድንግል ማርያምንም እያመሰገንን ልናከብረው ይገባል፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ከእመቤታችን ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡ አሜን።

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ትንሣኤ #ልቡና
ዛሬ የትንሣኤ በዓልን እያከበርን ነው። ትንሣኤ ማለት መነሣት ማለት ነው። ብዙዎቻችንም እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን እያልን ነው። ፖለቲከኛውም፣ ሰባኪውም፣ ጳጳሱም፣ ዘፋኙም፣ አርቲስቱም፣ አክቲቪስቱም ሁሉም እንኳን አደረሳችሁ እያለ ነው። ጌታ ተነሣ ስንል እኛም ትንሣኤ ልቡናን መነሣት አለብን። ፖለቲከኞች በቂም በቀል እና በሴራ መቃብር ውስጥ ሆናችሁ እንኳን አደረሳችሁ ብትሉን ራሳችሁን የምትዋሹ ትሆናላችሁ። ከመቃብር ውጡ። ትንሣኤያችሁን ሐዋርያት ይመልከቱት። በመቃብር ሆነን ስለ ትንሣኤ ብናወራ አያምርብንም።

ኑ በሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተነሣ እኛም ትንሣኤ ልቡናን እንነሣ። የዘረኝነት፣ የውሸት፣ የጥላቻ፥ የበቀል፣ የሐሜት፣ የከንቱ ውዳሴ፣ የትዕቢት፣ የራስ ወዳድነት መቃብርን ፈንቅለን እንውጣ። ኑ እንነሣ። ስንነሣ ደግሞ ልባችን ብርሃንን ይሞላዋል። ችግሮቻችን ሁሉ ከእኛ በታች ነበሩ። ነገር ግን ትንሣኤ ልቡናን ባልተነሡ ሰዎች ምክንያት እንደ ተራራ የገዘፉ ሆኑብን።

ኑ በትንሣኤው እንነሣ።

በአፋችሁ እንኳን አደረሳችሁ እያላችሁን በልባችሁ ግን ቀጣይ ዓመት እንዳንደርስ እየገደላችሁን ከሆነ ይሁዳነት ነው። ይሁዳ በአፉ ሰላም እያለ ነው ጌታን የሸጠው። ሁሉም ከተንኮልና ከሽንገላ መቃብር ይውጣ እና የፍቅር ትንሣኤን ይነሣ።

© በትረ ማርያም አበባው


/channel/dnhayilemikael🌿

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
           አሜን

✍“ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ፤ ተነሥቶአል እንጂ በዚኽ የለም"
📖ሉቃ 24፥5

#ክርስቶስ_ተንስአ_እሙታን
በዐቢይ ኃይል ወስልጣን፤
#አሠሮ_ለሰይጣን
አግዐዞ ለአዳም፤
#ሰላም
እምይእዜሰ፤
#ኮነ
ፍሥሐ ወሰላም።

    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
      ድርሳን ዘበዓለ ፋሲካ
    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥

✍ "እግዚአብሔርን የሚያምንና የሚወድ ቢኖር፤ እርሱ በዚህ  አንፀባራቂና የደስታ በዓል ደስ ይበለው"

✍ "ብልህ አገልጋይ ቢኖር፤ እርሱ ወደ ጌታው ሐሴት ገብቶ ዕልል ይበል፤ በጾም የደከመ ቢኖር፤ አሁን ደመወዙን ይቀበል፡"

✍ "በመጀመሪያው ሰዓት ወደ አምላኩ የቀረበ ቢኖር፤ ዛሬ ሽልማቱን ይውሰድ"

✍ "በሦስተኛው ሰዓት የመጣ ቢኖር፤ እርሱ በዓሉን በምስጋና ያክብር፤ በስድስተኛው ሰዓት የደረሰ ቢኖር፤ አይጎድልበትምና አይጠራጠር፤ እስከ ዘጠነኛ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፤ ሳይጠራጠር ይቅረብ፤ እስከ ዐሥራ አንደኛዋ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፤ ስለ መዘግየቱ አይደንግጥ፤ ጌታ ቸር ነውና፤ በመጨረሻ የመጣውንም እንደ መጀመሪያው አድርጐ ይቀበሏልና"

✍ "በዐሥራ አንደኛው ሰዓት ለመጣው ከመጀመሪያው ሰዓት አንሥቶ ሲደክም ከነበረው ጋራ እኩል ይሰጧልና፤ መጨረሻ ለመጣው ጌታ ምሕረቱን ይለግሰዋል፤ መጀመሪያ ለመጣውም ያስብለታል፡፡

✍ "ለአንደኛው ይሰጠዋል፤ ለሌላኛውም ጸጋውን ያድለዋል፤ ለአንደኛው መልካም ምግባሩን ይቀበልለታል፤ ለሌላኛውም መልካም ፍቃዱን ይቀበልለታል፤ ለአንዱ ምግባሩን ያከብርለታል፤ ለሌላኛውም በቅን ልቡና የሚያደርገውን ጥረት ያደንቅለታል"

✍ "ስለዚህ ኹላችሁም ወደ ጌታችሁ ደስታ ግቡ፤ ፊተኞች ኋለኞችም ሆይ እኩል ደመወዛችሁን ተቀበሉ፤ ባለጸጐች ድኾችም ሆይ በአንድነት ዘምሩ"

❖ እናንተ ብርቱዎች ደካሞችም ሆይ በዓሉን አክብሩት፡፡

✍እናንተ የጾማችሁ መጾም ያልቻላችሁም ሆይ ዛሬ ላይ ደስ ይበላችሁ፤ መሠዊያው ሙሉ ነውና ኹሉም በማዕዱ ደስ ይበለው፤ ፍሪዳው የሰባ ነውና አንድ ሰው ስንኳ እንደ ተራበ እንዳይሔድ፤ ኹላችንም የእምነት በዓሉን እንካፈል፤ ከቸርነቱና ከፍቅሩ ሀብትም እንቋደስ፡፡

✍ማንም ስለ ድኽነቱ አይዘን፤ ኵላዊቷ መንግሥት ተገልጣለችና፤ ማንም በኃጢአቱ አያንባ፤ ከመቃብሩ የይቅርታ ብርሃን ተንቦግቧልና፤ ማንም ሞትን አይፍራ የመድኃኒታችን ሞት ከዚህ ነጻ አውጥቶናልና፤ ለእርስዋ በመታዘዝም ጌታ አጥፍቷታልና፡፡

✍በሞቱ ሞትን ገደለው፤ ወደ ሲዖል በመውረድ ሲዖልን በዘበዘው፤ ኢሳይያስም አሰምቶ እንደ ተናገረ ሲዖል ከጌታችን ጋር ፊት ለፊት ተገናኘች፤

❖ መረራትም ከንቱ አድርጓታልና መረራት
❖ ሸንግሏታልና መረራት
❖ ሽሯታልና መረራት
❖ ነፍሳትን ይዛ እንዳታስቀር አስሯታልና መረራት
❖ መቃብር የዕሩቅ ብእሲ ሥጋ አገኘሁ ብላ ዋጠችው፤ስትውጠው ግን እግዚአብሔር ኾኖ አገኘችው መረራትም

❓ሞት ሆይ መውጊያህ ወዴት አለ
❓ሲዖል መቃብርም ሆይ ድል መንሣትህ ይዞም ማስቀረትህ ወዴት አለ

❖ ክርስቶስ ተነሣ፤
❖ ሞት ሆይ አንተም ጠፋህ
❖ ክርስቶስ ተነሣ፣ አጋንንትም አዘኑ
❖ ክርስቶስ ተነሣ፤ መላእክትም ሐሴት አደረጉ
❖ ክርስቶስ ተነሣ፤ የሰው ሕይወትም ነጻ ወጣች
❖ ክርስቶስ ተነሣ፤ መቃብርም ባዶ ኾነች
❖ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለአንቀላፉት ኹሉ በኵር ኾኖላቿልና፡፡

❖ ለእርሱም ክብርና ጽንዕ ዛሬም ዘወትርም እስከ ዘለዓለሙ ድረስ ይኹን

✍ "ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ
ተሐጺባ በደመ ክርስቶስ"

👉"ምድር ጸዳች ሐሴት አደረገች
በክርስቶስ ደም በእውነት ታጠበች"

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን መልካም በዓል

✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
📖ምሳ 1፥33

📌ምንጭ
✍ቅዱስ ዩሐንስ አፈወርቅ እንደፃፈው

✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝

🙏 ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ፤ እኔም ለእናንተ ከአዘጋጀው በኃዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ     

✍"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
📚ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

               ወስብሐት ለእግዚአብሔር
                              ይቆየን 

───────────
                    Channel
 🧲 
/channel/dnhayilemikael🌿

        FB
/channel/dnhayilemikael🌿

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

የሰሙነ ሕማማት ዕለታት ስያሜዎች

፩ .ዕለተ ሰኑይ
መርገመ በለስ
፡- ጌታችን የሆሣዕና ዕለት ቢታንያ አድሮ በማግስቱ ከቢታንያ ሲወጣ ተራበ፤ በመንገድም ሲያልፍ ቅጠል ያላት በለስን ከሩቁ ተመለከተ፡፡ ወደ በለሲቱም በቀረበ ጊዜ ከቅጠል በቀር አንዳች ፍሬ አላገኘባትም፡፡ ያንጊዜም ‹‹ከእንግዲህ ወዲህ ለዘለዓለም ከአንቺ ፍሬ የሚበላ አይኑር›› ሲል በለሲቱን ረገማት፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ይህንን ሰሙት፡፡ በዚህም ምክንያት ይህች ዕለት በለሲቱ የተረገመችባት ቀን ናትና መርገመ በለስ ተብላ ትጠራለች፡፡ (ማር.፲፩፥፲፩-፲፬)
በዚህ አገላለጽ በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ስትሆን ፍሬ የተባለ ደግሞ ሃይማኖትና ምግባር ነው፡፡ መድኃኒታችን ክርስቶስ ከእስራኤል ፍቅርን፣ ሃይማኖትን፣ ምግባርን ፈልጎ አላገኘባቸውም፡፡ እስራኤል፦ ሕዝበ እግዚአብሔር፣ የአብርሃም ዘር መባልን እንጂ የአብርሃምን ሥራ በመሥራት በምግባር በሃይማኖት ጸንተው መኖር አይፈልጉምና ደግ ሰው አልተገኘባቸውም፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ በለስ የተባለች ኦሪት ናት፡፡ ኦሪት በዚህ ዓለም ሰፍና ቢያገኛትም አማናዊ ድኅነትን የምታሰጥ ሆና አላገኛትም፡፡ ይሁን እንጂ በእርሷ ድኅነት ባይገኝባትም ‹‹ኦሪትና ነቢያትን ከመፈጸም በቀር ልሽር አልመጣሁም ልፈጽም እንጂ›› በማለት ሕገ ኦሪትን ፈጽሟታል፡፡ ከዚህም ባሻገር በለስ የተባለች ኃጢአት ናት፡፡ የበለስ ቅጠል ሰፊ እንደሆነች ሁሉ ኃጢአት በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፍና አግኝቷታል፡፡ በለስ ሲበሉት ይጣፍጣል፤ ቆይቶ ግን ይመራል፤ ኃጢአትም ሲሠሩት ለጊዜው ደስ ያሰኛል ኋላ ግን ያሳዝናል፡፡ በአንቺ ፍሬ አይገኝ የሚለውም በአንቺ በኃጢአት ፍዳ ተይዞ የሚቀር አይኑር ሲል ነው፡፡ በለሲቱ ስትረገም ፈጥና መድረቋም በአዳም ምክንያት ያገኘን በደል በእርሱ እንደጠፋልን ለመግለጽ ነው፡፡

/channel/dnhayilemikael🌿

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

5 ነገሮችን በደንብ ያዙ።
    1, 🛑አላማ

    2 ,🛑እምነት

    3,🛑ጥረት

    4 🛑ጥንቃቄ

     5🛑ጽናት
=>እነዚህን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።

❇️9ኙ የቅድስና መንገዶች❇️

፩👉ሃይማኖት
፪👉ጾም
፫👉ጸሎት
፬👉ስግደት
፭👉ምጽዋት
፮👉ፍቅር
፯👉ትህትና
፰👉ትዕግስት
፱👉የዋህነት

✝ንስሐ የተጣመመውን ያቀናል።በኃጥያት የቆሸሸውን ያነጻል፤ንስሐ ለሚገቡ ሁሉ የመላዕክት ንጹሕ ልብስ ይሰጣችኃል።
        (ቅዱስ መቃርስ )
/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ኃጢአት እንዳይሰለጥንብን ሁልጊዜ ወደ ሥጋ ወደሙ እንቅረብ

💠ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም የኩራትና የማንኛውም ዓይነት ክፉ ድርጊት
አንዳይሠለጥንብን ኹል ጊዜ ወደ ሥጋውና ደሙ ልንቀርብ ይገባናል ይለናል::
ሥጋውንና ደሙን ስንቀበል👉 ኃይል ሰማያዊን ገንዘብ እናደርጋል ይህ ደግሞ
ጠንካራ እንድንኾን ያደርገናል
ስንፍናችንን ያጠፋልናል በማለት ራስን
ለመቆጣጠር እንድንችል ምሰሶ የሚኾነን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን
እንድንቀበል ወደ ድግሱ ይመራናል፡፡

💠በእርግጥ በሥጋውና ደሙ የክርስቶስ አካል እንኾናለን በእርሱም ኃይል የጠላትን ወጥመድ ሰባብረን እንጥላለን፡፡



መጽሔተ ወራዙት ዘኦርቶዶክስ ገጽ 226


/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

🌹🌹🌹🌹🌹#ዐይን_ይጹም🌹🌹🌹🌹🌹
               

ቤተክርስቲያናችን ሥርዓተ ጾምን ስትሠራ ከእህልና ውኃ እንዲሁም ከእንስሳት ተዋጽኦ ብቻ  እንድንከለከል ሳይሆን የስሜት ሕዋሳቶቻችን ሁሉ ከልዩ ልዩ ገቢረ ኃጢአት መጾም እንዳለብን ታስተምረናለች፡፡  በአጠቃላይ  የስሜት ሕዋሳቶቻችን ዐሥር ሲሆኑ አምስቱ ሕዋሳት በአፍኣ (የሚታዩ የሚዳሰሱ) ሲሆኑ ዐይነ ሥጋ፤ እዝነ ሥጋ፤ እግረ ሥጋ፤ እደ ሥጋና አንፈ ሥጋ ናቸው። 

አምስቱ ደግሞ ውሳጣዊ ( የማይታዩ የማይጨበጡ ) ሲሆኑ እግረ ኅሊና፤ እደ ኅሊና፤ ዐይነ ኅሊና፤ አንፈ ኅሊናና እዝነ ኅሊና ናቸው አፋዊ ሕዋሳቶቻችን ከውሳጣዊው ሕዋሳቶቻችን ጋር ተናበዉ ከክፉ ነገር ሲርቁ ጾሙ እንላለን፡፡

ሥጋዊ ዐይናችን የሰውነታችን መብራት ሲሆን ኅሊናዊ ዐይናችን ደግሞ የኅሊናችንና የነፍሳችን መብራት ነው፡፡ በሥጋዊ ዐይናችን ዓለማዊ ነገሮችን ማየት ስንችል በኅሊናዊ ዐይናችን ደግሞ መንፈሳዊውን ረቂቁን ነገር መመልከት እንችላለንና፡፡ የሰውነታችን መብራት ዐይናችን እንደሆነ አምላካችን እግዚአብሔር በቅዱስ ወንጌል
"የሰውነት መብራት ዐይን ናት ዐይንህ ጤናማ ብትሆን ሰውነት ሁሉ ብሩህ ይሆናል ዐይንህ ግን ታማሚ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል፡፡ " ( ማቴ 6:22) በማለት አስተምሮናል፡፡

የሰው ልጅ የሕዋሳቱ ሁሉ መብራት በሆነችው ዐይኑ አይቶ መልካም ነገሮችን ከማድረግ ባሻገር ክፉ ነገሮችን ተመልክቶ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያጣሉ ነገሮችን ከማድረግ እንዲከለከል ( እንዲጾም) ቅዱሳት መጻሕፍት ያስተምራሉ፡፡

አባታችን አዳም እና እናታችን ሔዋን ዕፀ በለስን በልተው ከገነት ለመባረራቸው ምክንያቱ ዐይናቸው ነበር በዐይናቸው ተመልክተው በመጎምጀታቸው ነው በተጨማሪም የሴት ልጆች መላእክትን መስለው ፈጣሪያቸውን እያመሰገኑ ከሚኖሩበት ከተቀደሰውና ከታላቁ ደብር ቅዱስ ወጥተው ከዘፋኞቹ ከቃኤል ልጆች ጋር በኃጢአት ለመውደቅ ያደረሳቸው ዐይናቸው ነው ምክንያቱም የኃጢአተኞቹን የቃኤልን ልጆች አስከፊ ዝሙት በዐይናቸው ከተመለከቱ በኋላ ነውና ወደ ገቢረ ኃጢአት የገቡት፡፡

በመሆኑም ዐይናችን ለሕዋሳቶቻችን ብርሃን ሆኖ የተሰጠን ሥነ ፍጥረትን እየተመለከትን ፈጣሪያችንን ልናደንቅበትና ልናመሰግንበት ጨለማውንና ብርሃኑን ገደሉንና ሜዳውን የምንመገበውንና የማንመገበውን የሚጠቅመንንና የማይጠቅመንን ልንለይበት የሚጠቅመንን እያየን ልንሠራበት እንጂ የምናየውን ክፉ ነገር ሁሉ እየሠራን ከፈጣሪያችን ጋር ልንጣላበት አይደለም፡፡

በዕለት ከዕለት ኑሮአችን በዐይናችን የምናየው ለኃጢአት ለርኩሰት ለሞት የሚጋብዝ ብዙ ጠቃሚ ያልሆኑ ነገሮች አሉ ለአብነት ያህል ብንመለከት እንኳን በማኅበራዊ ሚድያው የምናየው ነገር ዘግናኝና መንፈሳዊነታችንን የሚገዳደር ጉዳይ ነው ትውልዱም በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በመገናኛ ብዙኃን ያየውን ነገር በመሥራት ራሱን እያረከሰና ከፈጣሪው ጋር እየተጣላ መሆኑን በየዕለቱ የምናየው ጉዳይ ነው፡፡

የዐይን ጾም ማለት ከእነዚህ ጠቃሚ ያልሆኑ ነገሮችን ከማየት መከልከል ማለት ነው፡፡ አምላካችን በቅዱስ ወንጌል " ዐይንህ ብታሰናክልህ ከአንተ አውጥተህ ጣላት" ያለበት ምክንያት የምታየውን ክፉ ሥራ ከመሥራት ተከልከል ማለቱ ነው፡፡ ምክንያቱም በምድር ላይ ዐይን ኖሮን ከገነት መንግሥተ ሰማያት ከምንባረር በምድር ላይ ዐይን ሳይኖረን ገነት መንግሥተ ሰማያትን ብንወርስ ይሻላልና፡፡ ጫማ ሰፊው ስምዖን ጫማ በሚሰፋበት ወስፌ ዐይኑን አውጥቶ የጣለበት ምክንያትም ይኸው መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያቱ ባስተማረው መጽሐፈ ኪዳን " አዑሩ አዕይንቲክሙ ዐይናችሁን ከልክሉ" አለ፡፡ አምላካችን ዐይናችሁን ከልክሉ ሲለን ግኡዝ ሆኖ ማራኪ መስሎ ኃጢአትን ይዞ የሚመጣ ነገርን እንዳያይ ሥጋዊ ዐይናችሁን ከልክሉት ክፉውን ነገር አይታችሁ እንዳላያችሁ ሁናችሁ ተውት የሚያስጎመጅ መስሎ የታያችሁን እንዳላያችሁ እለፉት ያያችሁትን ክፉ ነገር ሁሉ እናድርግ ፡ እንፈጽመው ከማለት ተቆጠቡ ሲል ታላቁ አባት አረጋዊ መንፈሳዊም ዐይናችን ከክፉ ነገሮች መጾም እንዳለበት እንዲህ በማለት ይመክረናል " ክላእ ንጻሬከ እምኩሉ ሥን ኀላፊ እንዘ ትኔጽሮ ለእግዚአብሔር ወትኄልዮ በልብከ በልብህ እግዚአብሔርን እያሰብህ ኃላፊውንና ጠፊውን ነገር ከማየት ዐይንህን ከልክል በማለት ያስተምረናል፡፡ ኃላፊውንና ጠፊውን ነገር በዐይናችን ዐይተን ወደ ልባችን ባመላለስነው ቁጥር እግዚአብሔርን ማሰብ አይቻልምና ነው፡፡

ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድም " ይጹም ዐይን እምርእየ ኀሡም ዐይን ክፉ ነገርን ከማየት ይጹም " በማለት የዐይናችን ጾም ክፉ ነገር ከማየት መሆን እንዳለበት ገልጾልናል፡፡ በመሆኑም ዐይናችን ጠቃሚ ያልሆኑ ፊልምችን ድራማዎችን ማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃንን በአጠቃላይ ለኃጢአት የሚጋብዙ ነገሮችን ከማየት ይልቅ መንፈሳውያን መጻሕፍትን በመመልከት ነፍሳችንን የማይጎዱትን መገናኛ ብዙኃን በማየት የመዝሙር ምስሎችን በማዘውተር ወዘተ መጾም ያስፈልጋል፡፡

  ይቆየን።

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘን_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ

/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

መኑ ውእቱ ገብር ኄር : በጎ ቸር አገልጋይ ማን ነው?››
-----------------------------

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስያሜ የዐቢይ ጾም ስድስተኛው እሑድ ወይም ሳምንት ገብር ኄር ይባላል፤ ስያሜውን የሰጠውም ኢትዮጵያዊ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ ከአምስቱ መጻሕፍቶቹ አንዱ በሆነው ጾመ ድጓ የዐቢይ ጾም ሳምንታት ስያሜዎች ከነሥርዓተ ማኅሌቱ አዘጋጅቷል፡፡ ስለዚህ በስድስተኛው የዐቢይ ጾም ሳምንት ከዋዜማው ቅዳሜ ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን የሚዘመረው ዝማሬ፣ የሚሰበከው ስብከት፣ የሚሰጠው ትምህርት ገብር ኄርን ወይም ታማኝ አገልጋይን የሚያወሳ ነው፡፡

ለዚህም ምሳሌ እንዲሆነን በማቴዎስ ወንጌል ላይ የተጻፈው ታሪክ እናነሳለን፤ አንድ ባለ ጸጋ ሰው ባሪያዎችን ጠርቶ ለአንዱ አምስት መክሊት ሰጠው፣ ሁለት መክሊት የሰጠውም አለ፣ አንድ መክሊትም የሰጠውም አለ፡፡ ከዚህ በኋላ ወደሩቅ አገር ሄደ፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለውም ወጥቶ ወርዶ ሌላ አምስት አትርፎ ዐስር አደረገ፡፡ ሁለት የተቀበለውም አትርፎ አራት አደረገ፡፡ አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ መሬቱን ቆፍሮ በሻሽ ጠቅልሎ የጌታውን መክሊት ቀበራት፡፡

ከብዙ ጊዜ በኋላ ጌታቸው መጥቶ ተቆጣጠራቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለው ቀርቦ ‹‹ጌታዬ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ አምስት አተረፍኩ አለው፡፡ ‹‹ገብር ኄር ወምእመን ዘበሁድ ምእምነ ኮንከ ዲበ ብዙህ እሰይመከ ባዕ ውስተ ፍስሐሁ ለእግዚእከ፤ አንተ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል፤ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ›› አለው፡፡ ሁለት የተቀበለውም ቀርቦ ‹‹ጌታዬ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ወጥቼ ወርጄ ሌላ ሁለት አትርፌ አራት አድርጌአለሁ፡፡ አንተ ታማኝ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃል፤ በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ›› አለው፡፡

አንድ መክሊት የተቀበለው ግን ቀርቦ ‹‹ጌታዬ አንተ ክፉና ጨካኝ ካልዘራህበት የምታጭድ ካልበተንህበት የምትሰበስብ እንደሆንክ ስለአወቅሁ መሬቱን ቆፍሬ ቀበርኋት እነኋት መክሊትህ አለው፡፡ አንተ ሰነፍ ባሪያ መክሊቴን በጊዜ ልትሰጠኝ በተገባህ ነበር፤ እኔም ወጥቶ ወርዶ ለሚያተርፍ በሰጠሁት ነበር፡፡

የዚህን መክሊት ውሰዱና አስር መክሊት ላለው ስጡት፡፡ላለው ይሰጡታል ይጨመርለታል፤ለሌለው ግን ያለውን ይቀሙታል፡፡ይህን ሰነፍ ባሪያ እጅ እግሩን አሥራችሁ ጽኑዕ ጨለማ ወደአለበት ውሰዱት፤ጩኸትና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበትም ጨምሩት››አለ፡፡(ማቴ.፳፭፥፲፬-፳፭)

ባለ ጸጋ የተባለው ጌታ ነው፤ መክሊት የተባለው ልዩ ልዩ የአገልግሎት ጸጋ ነው፡፡ ያተረፉት በሚገባ በታማኝነት ያገለገሉ ቅዱሳን ሰዎች ናቸው፤ መክሊቱን የቀበረው ደግሞ በታማኝነት በተሰጠው ጸጋ ማገልገል ሲገባው ያላገለገለ ነው፡፡ ጌታቸው ሊቆጣጠራቸው መጣ ማለት በዕለተ ምጽአት ለሁሉም በአገለገለው አገልግሎት ዋጋ ለመስጠት እንደሚመጣ ያሳየናል፡፡

ያገለገሉትን ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አላቸው ማለት ታማኝ አገልጋዮች መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉና፡፡ ሰነፎች ደግሞ ጥርስ ማፋጨት ስቃይ ጽኑዕ ጨለማ ባለበት ሲዖል መግባታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡

ከላይ ያነሳነው የቅዱስ ወንጌል ቃል ‹‹ታማኝ አገልጋይ ማነው?›› ይህ እያንዳንዱ በአርዓያ እግዚአብሔር የተፈጠረ የሰው ልጅ ጥያቄ ነው፤ የዚህን አምላካዊ ጥያቄ መልስ መስጠት ከሰው ልጆች ይጠበቃል፡፡

ታማኝ አገልጋይ ማነው?

፩. ታማኝ አገልጋይ ነቢዩ ሙሴ

ሙሴ ታማኝ አገልጋይ እንደነበር ቅዱሳት መጻሕፍት ይመሠክራሉ፡፡ ‹‹በመካከላችሁ ነቢይ ቢኖር እኔ እግዚአብሔር በራእይ እገለጥለታለሁ ወይም በህልም አናግረዋለሁ፤ ባሪያዬ ሙሴ ግን እንዲህ አይደለም፤ እርሱ በቤቴ ሁሉ የታመነ ነው››፡፡ (ዘኁ.፲፪፥፮) ይህ የፍጡር ምስክርነት ሳይሆን በፈጣሪው የተሰጠ ምስክርነት ነው፡፡ በእውኑ በዘመናችን እንኳን ፈጣሪ ፍጡራን ታማኝነቱን የሚመሰክሩለት አጋልጋይ ይኖር ይሆን? የሙሴን ታማኝ አገልጋይነት በረሃ፣ ስደት፣ መከራ እና ቁጣ ያልበገረው አርባ ዓመት ስለ ወንድሞቹ በመሰደድ፣ አርባ ዓመት ደግሞ የተሰደደላቸው ወንድሞቹን በመምራት ባሕር በመክፈል፣ ጠላት በመግደል፣ መና በማውረድ፣ ደመና በመጋረድ ውኃ ከዓለት አፍልቆ በማጠጣት፣ መከራውን ከወገኖቹ ጋር በመቀበል፣ የቀኑ ሀሩር የሌሊቱን ቁር /ብርድ/ ታግሶ በታማኝነት አገልግሏል፤ ታማኝነቱ እስከሞት ነበር፡፡

‹‹ሙሴም ወደ እግዚብሔር ተመልሶ ወዮ እኒህ ሕዝብ ታላቅ ኀጢአት ሠርተዋል፡፡ ለራሳቸውም የወርቅ አማልክት አድርገዋል፡፡ አሁን ይህን ኀጢአታቸውን ይቅር በላቸው፤ ያለዚያ ግን ከጻፍከው መጽሐፍ እባክህ ደምስሰኝ፤ ከባለሟልነትህ አውጣኝ››፡፡(ዘጸ.፴፪፥፴፩) ታማኝ አገልጋይ ‹‹እኔ ልሙት፤ ሌሎች ይዳኑ የሚል ነው፤ አሁን የምናየው ግን ፈጽሞ ከዚህ የተለየ ነው፡፡ ሰዎች ይሙቱ፤ እኔ ልኑር፤ ሰዎች ጾም ይደሩ፤ እኔ ልብላ፤ ሰዎች ይራቆቱ እኔ ልልበስ፤ ሰዎች ይዘኑ፤ እኔ ልደሰት›› ነው፡፡

ታማኝ አገልጋይ ለሚያገለግላቸው ሰዎች ጥቅም ቅድሚያ የሚሰጥ እንጂ የራሱን ጥቅም የሚያስቀድም አይደለም፡፡ ዛሬ በዓለማችን የምንመለከተው ግን ‹‹ጩኸት ለአሞራ መብል ለጅግራ›› የሚባለውን መሰል ነው፡፡ በታማኝ አገልጋዮች ድካም የሚሸለሙ ታማኝ አገልጋዮች በሠሩት ሥራ የሚያቀርቡ፣ የሚወደሱ፣ ከጥቅሙ እንጂ ከድካሙ መክፈል የማይሹ እንቅፋት የሚመታው እግርን ነው፡፡ አክሊል የሚቀዳጀው ግን ራስ ነው፡፡ ታማኝ አገልጋይ ማለት እንደራስ አክሊል ዘውድ የሚጸፋ ብቻ ሳይሆን እንደ እግር እንቅፋቱን፣ እሾሁን፣ መከራውን፣ ውጣ ውረዱንና ድካሙን የሚቀበል ነው፡፡ በጥቅም ጊዜ ለራሱ በአካፋ የሚዝቅ ወይም በጭልፋ የሚጨለፍ አይደለም፡፡ ሙሴ ባሕር የከፈለው፣ መና ያወረደው፣ ደመና የጋረደው፣ ወይም ውኃ ያፈለቀው ለራሱ አልነበረም፤ ለሚመራቸው ሕዝብ ነበር እንጂ፡፡ ታማኝ አገልጋይ ያሰኘውም ይኸው ነው፤ በዚህ ከብሮበታል፤ ተመስግኖበታልም፡፡

፪. ታማኝ አገልጋይ ነቢዩ ዳዊት

ዳዊት ዘመነ መሳፍንት አልፎ ዘመነ ነገሥት ሲተካ እስራኤልን በንጉሥነት እንዲያገለግል እግዚአብሔር ከበግ ጥበቃው ወስዶ ሥልጣን ሰጠው፤ ያልተመነ የሳዖልን በትረ መንግሥት በሳሙኤል እጅ ተቀብቶ ተቀብሏል፡፡

በተሰጠው ሥልጣን በታማኝነት ሕዝበ እስራኤልን መርቷል፡፡ ታማኝነቱንም እግዚአብሔር ለሙሴ እንደ መሰከረለት ለእርሱም መስክሮለታል፡፡ ‹‹እግዚአብሔር እንደልቡ የሆነ ሰው መርጧልና››፤ ‹‹የዘይቱን ቀንድ ሞልተህ በልጆቹ መካከል ለእኔ ንጉሥ አዘጋጅቻለሁና ወደ እሴይ ወደ ቤተልሔም እልክሃለሁ›› እንደተባለው፡፡ (፩ ሳሙ.፲፫፥፲፫፣ ፲፮፥፪)

‹‹ወረከብክዎ ለዳዊት ገብርየ ወቀባዕክዎ ቅብዐ ቅዱስ›› እንዲል፡፡(መዝ.፹፰፥፳) ‹‹ባሪያዬ ዳዊትን አገኘሁት፤ የተቀደሰ ዘይትንም ቀባሁት›› ይህን አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሰዓታት በተባለው ድርሰቱ፡- ‹‹ረከብክዎ ለዳዊት ገብርየ ብዕሴ ምእመነ ዘከመልብየ›› አገልጋዬ ዳዊትን እንደ ልቤ የታመነ ሰውን ሆኖ አገኘሁት›› ሲል ተርጉሞታል፡፡ የተገኘው በታማኝነት ነበር፤ ከነገሠ በኋላም ታማኝ ነበር፤ አሁን በዚህ ዓለም የምንኖር እኛ ግን በድኅነት ታማኝ እንሆንና ሀብት ሹመት ሥልጣን ሲመጣ ታማኝነትን እናጣለን፤ እንዲያውም ታማኝነትን እንንቀዋለን፡፡ መስረቅ ጀግንነት፣ መዋሸት ሥልጣኔ ይመስለናል፡፡ ዳዊት ሳይሾም በጎቹን በመጠበቅ ታማኝ ነበር፡፡ በጎቹን የሚነጥቅ ተኩላ አንበሳ ቢመጣ በኋላው ተከትሎ ነብሩን በጡጫ አንበሳውን በእርግጫ ብሎ በጎቹን ያስጥለው ነበር፡፡

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ይህን ያህል ቀን ጾምኩ አትበሉኝ፡፡

💠 ይህን አልበላሁም ወይም ያንን አልበላሁም፣
💠የወይን ጠጅ አልጠጣሁም አትበሉኝ።

👉ይልቁንስ ከግልፍተኝነት ወደ ገርነት፣
👉 ከጭካኔ ወደ ደግነት የተሸጋገርኽ እንደሆነ አሳየኝ፡፡
👉በአንተ ውስጥ ጥላቻና ቂም ቢኖሩ፣
👉 በወይን ፋንታ ውኃ ብትጠጣ ምን ይጠቅማል?
👉ጾም ብቻውን ስማያዊ ምንዳ አያስገኝምና፤
👉 ትርጉም በሌለው በባዶ የፆም ሥርአት ራስህን አታስገዛ።

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ኦርቶዶክሳዊ  ሚዛን

ኦርቶዶክሳዊው  ሚዛን    ክፍል  ፩

ብዙው  ሰው  እጁ  እስኪላጥ  ሲያጨበጭብ  ከርሞ  አሁን  ደግሞ  ላንቃው  እስኪሰነጠቅ  እየጮኽ ነው።  በእርግጥ  የመንጋነት  ፍጻሜው  ውድቀት  እና  ማፈር  እንዲሁም  ፀፀት  ነው።  አብዛኛው ሰው  መንጋ  ነው።  የሰባኪ  መንጋ  አለ።  የአጥማቂ  ነኝ  ባይ  መንጋ  አለ።  የፖለቲከኛ  መንጋ  አለ። የአክቲቪስት  መንጋ  አለ።  አንዳንዱ  አሁንም  ከመንጋነት  ወደ  መንጋነት  የተዘዋወረ  አለ።  የሆነ ሰው  መንጋ  ሆኖ  ይከርምና  የተከዳ  ሲመስለው  እገሌ  ግን  ያን  ጊዜም  ትክክል  ነበር  ብሎ  ለዚያ ሰው  ወዶ  ገብ  መንጋ  ይሆናል።  እኒህ  ሁሉ  መንጋቸውን  እንደፈለገ  ይነዱታል።  መንጋው ደግሞ  አያሰላስልም።  መንጋ  እንደ  ሸንበቆ  ነው።  ሸንበቆ  ነፋስ  ወደነፈሰበት  ነው  ሁል  ጊዜም የሚያዘነብለው።  ነገር  ግን  ነፋሱ  በጣም  አይሎ  ነቃቅሎ  ሲጥለው  ያን  ጊዜ  ያማርራል።  አብዛኛው ሰው  መለኪያ  የለውም።  መስማት  የሚፈልገውን  እየነገሩ  የሚወስዱት  ሰዎች  ብዙ  ናቸው። በርበሬ  ተወዶ  ከሆነ  ቤተክርስቲያን  ሰባኪው  አስተምሮ  ሲጨርስ  "ፈጣሪያችን  የበርበሬን  ዋጋ ይቀንስልን"  ሲል  "አሜን"  የሚለውን  መንጋ  ብዛት  አስተውልማ።  ደንበኛው  ሊቅ  መጥቶ አስተምሮ  ሲጨርስ  "ንሥሓ  ገብተን  ሥጋውን  ደሙን  ለመቀበል  ያብቃን"  ሲል  አሜን  የሚለው ይቀንሳል።  ይሄ  በጣም  አሳዛኙ  ክስተት  ነው።  ሰው  መስማት  ያለበትን  ከሚሰማ  ይልቅ  መስማት የሚፈልገውን  መስማትን  እየመረጠ  ነው።  ቤተ  ክርስቲያን  በክርስቶስ  ደም  የተዋጀችው የክርስቶስ  ሙሽራ  የሆነችው  ስለበርበሬ  እንዲወራ  ነው  እንዴ!?።  ማንኛውም  ሰው  ፕሮፌሰርም፣ ዶክተርም፣  ኢንጂነርም፣  ሳይንቲስትም፣  ፖለቲከኛም፣  ፓትርያርክም፣  ቄስም፣  ጳጳስም፣ መምህርም፣  ምእመንም፣  ዲያቆንም  ሁሉም  ፍጡራን  ናቸው።  እንደፍጡርነታቸው  የሚለኩበት መለኪያም  አንድ  ነው።  አንተ  ሰው  ለምን  የፖለቲከኛ  መንጋ  ትሆናለህ!?  ፖለቲከኛም  እንደ አንተ  ሰው  መሆኑን  ዘነጋሃው  እንዴ!?  እንደ  አንተ  ሰው  ከሆነ  አንተም  እርሱም  የምትዳኙበት መለኪያ  አንድ  ዓይነት  ነው።  አንድ  ዓይነት  ከሆነ  ደግሞ  ለምን  ራስህን  የፖለቲከኛና  የሰባኪ መንጋ  ታደርጋለህ!?  የማንም  መንጋ  አትሁን።  እግዚአብሔር  ራስህን  አስችሎ  ስለፈጠረህ ራስህን  ችለህ  አስብ።  በሌሎች  ጭንቅላት  ካልተመራሁ  አትበል።  ሩጥ  ሲሉህ  የምትሮጥ  ቁጭ በል  ሲሉህ  ቁጭ  የምትል  ከሆነ  ፈጣሪ  በነጻነት  ራስህ  ተመራምረህ  እንድትመርጥ  የሰጠህን እድል  መንጋ  ለሆንክለት  አካል  አሳልፈህ  ሰጠኽው  ማለት  ነው።  ይህ  ደግሞ  እገሌ  አይሳሳትም ወደማለት  ጽንፍ  ያወርድሀል።  ከዚያ  ያ  ሰው  ሲሳሳት  አንተ  ማፈሪያ  ሆነህ  ትቀራለህ። ኦርቶዶክሳዊው  ሰው  ግን  ሁሉን  የሚመረምርበት  አእምሮ  ከፈጣሪ  ስለተሰጠው  በራሱ  መንገድ በራሱ  መለኪያ  ነገሮችን  ይመረምራል  እንጂ  የማንም  መንጋ  አይሆንም።  ታድያ  በዓለማችን የሚደረጉ  ነገሮችን  ለመመርመር  ኦርቶዶክሳዊው  ሚዛን  ያስፈልገናል።  ኦርቶዶክሳዊው  ሚዛን ሁልጊዜም  ትክክል  ነው።  አያጸጽትም።  ዘመናትን  ተሻጋሪ  ነው።  ልበ  ሙሉ  ያደርጋል። ምክንያቱም  የኦርቶዶክሳዊው  ሚዛን  ባለቤት  እግዚአብሔር  ነው።  ስለዚህ  ኦርቶዶክሳዊው  ሚዛን ምንድን  ነው?!  ከመንጋነት  እንዴት  እንላቀቅ  የሚሉ  ጉዳዮችን  በ7  ክፍል  እንመለከታለን።

ይከታተሉ። ክፍል 2  ይቀጥላል ..

መ/ር በትረ ማርያም

#share

/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ግንቦት 11 በዓሉ ለቅዱስ ያሬድ ማሕሌታይ

" ከመ ተሰወርከ ያሬድ እምቅድመ ዓይኑ ለሞት
አድህነነ በጸሎትከ እምእለተ እኪት
ወባለሐነ እምኩሉ መንሱት"

ቅዱስ ያሬድ ሆይ ከሞት ፊት እንደተሰወርክ ሁሉ በጸሎትህ እኛን ከክፉ ቀን እና ከክፉ ነገር አድነን

የቤተ ክርስቲያን ጌጥ የዜማ አባት የመጻሕፍት ትርጓሜ መምህር የቅኔ እና የሥነ መለኮት ሊቅ ማሕሌታይ ቅዱስ ያሬድ ደብረ ሐዊ በተባለ ቅዱስ መካን በምናኔ ለብዙ ዘመን ከኖረ በኃላ ሞት ሳይቀምስ በሰባ አምስት አመቱ የተሰወረው ግንቦት 11 ቀን ነው

በገድለ ቅዱስ ያሬድ ተጽፎ እንደምናገኘው በዘመኑ የነበሩ ሁሉ እንደ መበረቅ የሚደምቅ፣ ምሥጢሩ እንደ መስታወት የሚያንጸባርቅ ጥበብ የተሞላበትን ድንቅ ዜማውን ለመስማት ከህጻናት እስከ ንጉሡ ድረስ ይከቡት የነበረ ማሕሌታይ ነው

" ንጉሥ ገብረ መስቀል ይህን ታላቅ ጣዕም ያለው ዜማ በሰማ ጊዜ ጫማውን ከእግሩ አልጨመረም ንግሥቲቱም አገልጋዮቿን ተወች ያንን ጥዑም ዜማ ትሰማ ዘንድ በአንድነት ሮጡ ጳጳሳት ካህናት የቤተ መንግሥቱ ወይዛዝርት ሹማምንት ወደ ቅዱስ ያሬድ መጡ ሲሰሙት ዋሉ፤ ከድምፀ ቃናው ጣዕም የተነሣ አጥንትን የሚያለመልም ልቡናን የሚያስደስት ነገር አግኝተዋልና፤ የቃሉን ድምፅ በሰሙ ጊዜ ሮጡ ወደ እርሱ ደረሱ ንጉሡም ንግሥቲቱም ከካህናቱ ጋር፣ ከመንግሥት ሹማምንትና ከሕዝቡ ጋር በመኾን ሲያዳምጡት ዋሉ›› እንዲል ገድለ ቅዱስ ያሬድ

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ሆይ የክብርህ ምስጋና ሰማያትንና ምድርን የመላ ነው እያሉ በስማይ ከሚኖሩ ከቅዱሳን መላእክት የሰማሁት ዜማ ምን ይረቅ ምን ይጠልቅ እንደምን ያለ ረቂቅ ነው ለዚህ አንክሮ ይገባል እያለ በምስጋና ሥርዓታቸው ሲደነቅባቸው ከነበሩ ከቅዱሳን መላእክት ጋራ ሊያመስገን ከዚህ ዓለም መከራ እና ድካም ሊያርፍ ሞትን ሳይቀምስ ተሰወረ በድርሣነ ቅዱስ ዑራኤል የስኔ ወር ምንባብ ላይ " ከሰው ዓይን ተሰወረ አኗኗሩም ከሰማይ መላእክት ጋር ሆነ " እንዲል

ተዓምረ ኢየሱስ የተሰኘው የቤተ ክርስቲያናችን መጽሐፍም

" ካህኑ ያሬድ ከዚህ ዓለም የሚለይበት ሰአት በደረሰ ጊዜ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ወዳጄ ሆይ ቀድሞ በሰማይ ያለ የመላእክትን ሥርዓት እንድታይ እና ወደ ምድር አስተላልፈህ ይህንኑ ዜማ እንድትመሠርት እንደ ወደድኩ ሁሉ አሁንም ከዚህ ዓለም በምትለይበት ሰዓት እኔ ዳግም ተመልሼ በምመጣበት ጊዜ ከካህናተ ሰማይና ሄሮድስ ደማቸውን ካፈሰሳቸው ህጻናት ጋር በደብረ ጽዮን ትዘምር ዘንድ ሰማያዊ የክብር አክሊል እና የብርሃን ልብስ ተዘጋጅቶልሃል ብሎት ወደ ሰማይ ዐረገ " ሲል ሞትን ሳይቀምስ መሰወሩን ይገልጻል

+ የቅዱስ ያሬድ በረከት በሁላችን ይደር በምልጃው ሀገራችንን ከክፉ ነገር ይሰውርልን

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ሃሌ ሉያ
ርኢክዋ፣ አእመርክዋ፣ አፍቀርክዋ ለቤተ ክርስቲያን

ሃሌ ሉያ
ቤተ ክርስቲያንን አየኋት፣ አወቅኋት፣ ወደድኋት።
"ቅዱስ ያሬድ"

የቅዱስ ያሬድ በረከት አይለየን ።



#share

ቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ
   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮

    የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን 
              ➡️      መሰረተ ሚዲያ

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
     ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ

👇👇👇👇👇👇👇👇

የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═
/channel/Meseretemedia

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ለኤማሁስ መንገደኞች የቀረበው ጥያቄ

ሐዋርያት ቤት ዘግተው ተቀምጠው ሳለ ፥ ነገሩን ለማየት አንዳንዶችም ወደ ኢየሩሳሌም በሚመጡበት ዕለት ሁለት ሰዎች ደግሞ ኢየሩሳሌምን ለቀው ወደ መንደራቸው መንገድ ጀምረዋል ፤ እኒህ ሁለቱ ወደ ባላገር ሲሄዱ የነበሩት ሰዎች ሉቃስና ቀለዮጳ ሲባሉ መዳረሻቸውም ኤማሁስ የምትባል መንደር ነበረች። (ማር16፥12 |ሉቃ 24፥13) አስቀድሞ ሁለት ሁለት አድርጎ ለአገልግሎት ልኳቸው ነበር በዚህ መንገድ ግን ሁለት ሆነውና ጠውልገው ተልዕኮ የሌለውን ጉዞ እያደረጉ ነው።

ከእኛ ዘንድም እንደነዚህ መንገደኞች ለአገልግሎትና ለድኅነት ተጠርተው እስከመጨረሻው ጸንተው እንዲቆዩ ከታዘዙባት ኢየሩሳሌም ተስፋ ማድረግ ተስኗቸው በዚህ መሆን ለኛ መልካምነቱ ምኑ ላይ ነው ? ብለው ፥ ልቡናቸው ደክሞ መንገድ የጀመሩ ግን ሁለት ሳይሆኑ ብዙዎች ናቸው ።

እኔ መንገድ ነኝ ያለ ከሦስቱ አካል አንዱ የሆነ ጌታ በመንገዳቸው ሦስተኛው ሰው ሆኖ ፤ ስለሚነጋገሩት ነገር ጠየቃቸው መንገደኞቹ በእነዚያ ዕለታት ስለሆነውና ስለእምነታቸው ተስፋ ያደረጉት ባለመሆኑም ማዘናቸውን ነገሩት። (ሉቃ 24፥17)

እኒህን የ 60 ምዕራፍ መንገደኞችን ነገር ገታ እናድርግና ፤ እኛስ በመንገዳችን ስለምን እየተነጋቨገርን አለን ? ብለን ራሳችንን እንጠይቅ

ወደ ኢየሩሳሌም ስንመጣ እንደ ሰብአ ሰገል እርሱን ለማየት ወደን የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው ? ብለን ከልባችን እየፈለግነው ወይስ እንደእነዚህ መንገደኞች በመንገድ ደክመን በሥራና በቃል ግን ብርቱ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየሱስ እየተጠያየቅንና እየተመራመርን ነን ?
እንጀራውን {ሥጋውን} በልተን ያንንም ጽዋ {ደሙን} ጠጥተን ስንመለስ ሐዋርያው እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁ እንዳለን ስለኛ መሞቱን እየተናገርን ነው ? (1ኛ ቆሮ 11 ፥26) በመጓጓዣ ተቀምጠን ስንሳፈርስ የሀገራችን ሰው እንደሆነው ጃንደረባ ነቢዩ ይህን ስለማን ይናገራል ? ብለን ስለክርስቶስ ሰው መሆን ለማወቅ እየወደድን ይሆን ? እንጀራ ቆርሰን እየተመገብን ሳለን ስለሕይወት እንጀራ ስለሆነው እርሱ ፥ እንጀራን አበርክቶ መመገቡንም እያደነቅን በልባችን እናንግሰው ብለንስ መክረናል ? መዝሙርና ዝማሬ መንፈሳዊም ቅኔን እየተቀኘንስ ዘምረናል ?

በሕይወታችና በውሏችን በምናደርጋቸው ነገራት ሁሉ መንፈሳዊ ጉዳዮችን እርስበእርስ ለመነጋገር ብዙ ምርጫዎች ቢኖሩም እኛ ግን "ከሁሉ የሚበልጥ ማን ይሆን ?" እየተባባልን እርስበርስ ምንፎካከር ፥ ርስት ለመውሰድ እንደ ገበሬዎቹ ኃጢአት ለማድረግ የምንማከር ፥ " እያንዳንዳችሁ ከባልንጀራችሁ ጋር እውነትን ተነጋገሩ" (ዘካ 8፥16) ብንባልም ሐሰትና ሽንገላን ስለሰውም በሹክሹክታ የምነጋገር ነን ፤ የታዘዝነውን ቃል መናገር ትተን በመንገዳችን ዱላ የምናነሳ በለዓሞች ሆነናል ።

እንዳናውቀው የልባችን ዓይን ተይዞ የማናስተውል ፥ መጻሕፍትና መምህራን የተናገሩትን ሁሉ ከማመን ልባችን የዘገየ ፥ በሩቅ በምናያት በሰማይ ብቻ ያለን መሰለን እንጂ እርሱ በሁሉ የመላ ጌታ ነውና በእኛ መካከልም ተገኝቶ እንደ ሁለቱ መንገደኞች እንዲህ ሲል ይጠይቀናል < እርስ በርሳችሁ የምትነጋገሯቸው እነዚህ ነገሮች ምንድን ናቸው ? > (ሉቃ 24፥17)

✍ ዲያቆን ኃይለሚካኤል ዳንኤል
ግንቦት 7፥ 2016 ዓ.ም

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ዕለታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ መልእክት 1

1ኛ ቆሮንቶስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁶ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?
¹⁷ ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ።



ቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ
   ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮

    /channel/dnhayilemikael
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
     ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ

👇👇👇👇👇👇👇👇

የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═
/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ፋሲካ አልባ ፋሲካ

ለሃምሳ ቀናት ጾመን  ደርሰን ከኀዘን አጽናፍ
በስግደት በለቅሶ ከርመን ቆመን ከሰቆቃ ጫፍ
እንደ ሐዲስ ኪዳንናዊ ሰው ከርመን ወንጌል ስናጠና
እግዚኦ መሐረነ ጌታ ብለን ጮኸን ሆሳዕና

ሕማምህ መከራህ አልፎ ትንሣኤህ ሲመጣ ፋሲካ
ልክ እንደ ኦሪት ሰው ሆንን ሮጥን እንስሳ ፍለጋ
እንደ ክርስቲያኖች ወግ ሥጋህንበልተን እንደመዳን
በግና ዶሮ ልናሳድድ ሔድን ወደ ብሉይ ኪዳን

ስንት ሰዓት ልቁረብ ማለት ትተን የእርዱ ነገር አስጨነቀን
ከትንሣኤህ ዕለት ቆመን የልብ ትንሣኤ ራቀን
የመቃብርህን ውጪ ቆመው ደጅ ደጁን ከጠበቁ
ሕያው ጌታ መሆንህን  ክብርህን ጭራሽ ካላወቁ
ከሮማውያን ወታደሮች በምን ተለየን እኛ
ሥጋህን ተቀብለን ካልሆነን የነፍስ መዳኛ

ከቶ እንዴት ይከበራል ወደ አንተ ሳይቀርቡ ትንሣኤ?
ለእኛ አልነበረም ወይ ያ ዕንባ ያ ሁሉ ኤሎሄ ኤሎሄ
የከበረው ሥጋህ ዛሬ በእኛ ውስጥ ካልተቀበረ
ምኑን ትንሣኤ ተበሰረ ምኑን ፋሲካ ተከበረ?

ይቅር በለን ጌታችን ሆይ በዶሮ ሥጋ ላከበርንህ
የሥጋችንን ስናሳድድ በትንሣኤህ ቀን ለቀበርንህ
በሞትህ ሙት ያስነሣህ ሆይ እኛንም አስነሣን ዛሬ
ደርቀን አንቅር በኃጢአት አድርገን የትንሣኤህ ፍሬ

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ቀዳም ስዑር
ሚያዝያ 2016 ዓ.ም.
🌿


/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ከትንሳኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡-

#ሰኞ
#ማዕዶት_ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡

#ማክሰኞ
#ቶማስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29

#ረቡዕ
#አልአዛር_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡

#ሐሙስ
#አዳም_ሐሙስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡

#አርብ
#ቅድስት+ቤተክርስቲያን_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡

#ቅዳሜ
ቅዱሳት_አንስት_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡

#እሁድ
#ዳግም_ትንሳኤ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ፋሲካ አልባ ፋሲካ

ለሃምሳ ቀናት ጾመን ደርሰን ከኀዘን አጽናፍ
በስግደት በለቅሶ ከርመን ቆመን ከሰቆቃ ጫፍ
እንደ ሐዲስ ኪዳንናዊ ሰው ከርመን ወንጌል ስናጠና
እግዚኦ መሐረነ ጌታ ብለን ጮኸን ሆሳዕና

ሕማምህ መከራህ አልፎ ትንሣኤህ ሲመጣ ፋሲካ
ልክ እንደ ኦሪት ሰው ሆንን ሮጥን እንስሳ ፍለጋ
እንደ ክርስቲያኖች ወግ ሥጋህንበልተን እንደመዳን
በግና ዶሮ ልናሳድድ ሔድን ወደ ብሉይ ኪዳን

ስንት ሰዓት ልቁረብ ማለት ትተን የእርዱ ነገር አስጨነቀን
ከትንሣኤህ ዕለት ቆመን የልብ ትንሣኤ ራቀን
የመቃብርህን ውጪ ቆመው ደጅ ደጁን ከጠበቁ
ሕያው ጌታ መሆንህን ክብርህን ጭራሽ ካላወቁ
ከሮማውያን ወታደሮች በምን ተለየን እኛ
ሥጋህን ተቀብለን ካልሆነን የነፍስ መዳኛ

ከቶ እንዴት ይከበራል ወደ አንተ ሳይቀርቡ ትንሣኤ?
ለእኛ አልነበረም ወይ ያ ዕንባ ያ ሁሉ ኤሎሄ ኤሎሄ
የከበረው ሥጋህ ዛሬ በእኛ ውስጥ ካልተቀበረ
ምኑን ትንሣኤ ተበሰረ ምኑን ፋሲካ ተከበረ?

ይቅር በለን ጌታችን ሆይ በዶሮ ሥጋ ላከበርንህ
የሥጋችንን ስናሳድድ በትንሣኤህ ቀን ለቀበርንህ
በሞትህ ሙት ያስነሣህ ሆይ እኛንም አስነሣን ዛሬ
ደርቀን አንቅር በኃጢአት አድርገን የትንሣኤህ ፍሬ

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ቀዳም ስዑር
ሚያዝያ 2016 ዓ.ም.


/channel/dnhayilemikael🌿

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያምገዳም ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት ተከናወነ !

ሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክሃይማኖት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በመገኘት የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት አከናውነዋል።

ዕለተ ሐሙስ እንደሚታወቀው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፍጹም ትህትና የደቀ መዛሙርቱን እግር ያጠበበት ከሐዋርያት ጋር ግብር የገባበትና የክርስትና ሕይወት ማኅተም የሆነውን ምስጢረ ቁርባን ያከናወነበት ዕለት ነው።

ስነ ሥርዓቱም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ቆሞሳት ፣ ካህናት እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ሃይማኖታዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ተከናውኗል ።

ምንጭ ተዋሕዶ ሚዲያ





/channel/dnhayilemikael🌿

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿✍#ሆሳዕና_ማለት_ምን_ማለት_ነው ??
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
#በሆሳዕና_ለምን_ቀለበት_እናስራለን ?
#በሆሳዕና_ጌታችን_ለምን_በአህያ_ላይ_ተቀመጠ

#በሆሳዕና_ለምን_ዘንባባ_አነጠፉ ?
................................................................
እና ሌሎች በደንብ ይነበብ ሼር!

=> ሆሳዕና ማለት ምን ማለት ነው??

ሆሳዕና ማለት፦ የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ
የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
=> በሆሣዕና ዕለት በእጃችን እደ ቀለበት ማሰራችን የምን ምሳሌ ነው??

1.ጌታ ለአዳም የሰጠው ቃል ኪዳን ለማስታወስ፡-ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድነሃለሁ ያለውን የተስፋ ቃል ለማስታወስ፡፡
2.ጌታ ለእመቤታችን የገባላትን ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው።
3.ጌታ ለእስራኤላውያን የሰጣቸው ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው።
4.ጌታ ለአዳም ከሰይጣን ግዛት ነጻ እንዳወጣው ሁሉ እኛም ከሰይጣን ግዛት ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ከክፋት ከኃጢአት አውጣን ማረን ለንስኃ ሞት አብቃን ከቤትህ አትለየን እንደ ቸርነትህ ይቅር በለን ስንል ለጌታ ዳግም ላናጠፋ ቃል የምንገባበት ነው፡፡
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
=> ጌታችን በዕለተ ሆሳዕና ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም??

ትንቢቱንና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ "
አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ
ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል።(ትንቢተ ዘካርያስ 9:9)

=> በአህያ መቀመጡ

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
•ትህትናን ለማስተማር
•የሰላም ዘመን ነው ሲል
•ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል በንጽህና በየዋህነት ለሚኖሩ ምዕመናን አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል፡፡

•አህያዎች ትሁታን ናቸው ረጋ ብለው ነው
የሚሄዱት፤በቀላሉ ትወጣበታለህ፤በቀላሉ
ትይዘዋለህ፤እንደፈለክም ታዝዋለህ።

=> ጌታችን ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ ዘንባባ የመነጠፉ ሚስጢር የምን ምሳሌ ነው???

1.ዘንባባ፡- ይስሃቅ በተወለደ ጊዜ ደስ ብሎት አብርሃምን ዘንባባ ይዞ እግዚአብሔር አመስግነዋል፡፡
2.ዘንባባ ደርቆ እንደገና ሂይወት ይዘራል፡- የደረቀ የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
3.ዘንባባ የሰላም ምልክት ነው፡- የሰላም አምላክ ነህ ሲሉ ነው።
4.ዘንባባ የደስታ መግለጫ ነው፡- አንተ ደስ የምታሰኝ ሃዘናችንም የምታርቅልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
5.ዘንባባ እሾሃማ ነው፡- አንተ ህያው አሸናፊ አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
6.ዘንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጂ፡፡ ጌታም አንተ ባህሪህን የማይመረመር ነው ሲሉ ነው፡፡

ህዝቡ ከልብሳቸው ሌላ ስንት አይነት ቅጠንል አነጠፉለት ምን ምን??
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
=> ልብሳቸውን ማንጠፋቸው፡-
ለክብሩ መግለጫ ነው፡፡
ሌሎችም ሦስት አይነት ቅጠል አነጠፉለት ዘንባባ፤የቴመር ዛፍ፤የወይራ ዛፍ አነጠፉለት፡፡

=> ትልቅዋ አህያ በምን ትመሳለለች ውርጭለዋስ???

ትልቅዋ አህያ የኦሪት ምሳሌ ነው።

1.ትልቅዋ አህያ ሸክም የለመደች ናት ህገ ኦሪትም የተለመደች ህግ ናትና፡፡
2.የእስራኤል ምሳሌ ነው፡-ትልቅዋ አህያ ሸክም እንደለመደች ሁሉ እስራኤልም ህግ ለመፈጸም በህግ ለመራመድ የለመዱ ናቸው፡፡
3.የአዳም ምሳሌ ነው፡- አዳም ሸክም የበዛበት ነበርና።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ውርጭላዋ
1.በህገ ወንጌል ትመሰላለች፡-ምክንያቱም ወንጌል ኢየሱስ ክርስቶስ የመሰረታት የሰራት አዲስዋ ህግ ናትና፡፡
2.በአህዛብ ትመሰላለች፡-ትንሽዋ አህያ ሸክም የለመደች አይደለችም እንዲሁም አህዛብም ህግህን የመቀበል የመቀበል የለመደ አይደሉም፡፡ ለህግህ አዲስ ናቸውና፡፡
3.የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡- የዓለም ሸክም አቅልላለችና በእመቤታችን ትመሰለላለች፡፡ እመቤታችን ድህነተ ምክንያታችን ጌታን የተሸከመች ንጽህት እንከን የሌላት እናት ናትና፡፡



መልካም በአል
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
።።።።ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።
🌿/channel/dnhayilemikael🌿

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ሮሜ 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁹ ፍቅራችሁ ያለ ግብዝነት ይሁን። ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ፤
¹⁰ በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ፤
¹¹ ለሥራ ከመትጋት አትለግሙ፤ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ለጌታ ተገዙ፤
¹² በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ፤
¹³ ቅዱሳንን በሚያስፈልጋቸው እርዱ፤ እንግዶችን ለመቀበል ትጉ።
¹⁴ የሚያሳድዱአችሁን መርቁ፥ መርቁ እንጂ አትርገሙ።
¹⁵ ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፥ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ።
¹⁶ እርስ በርሳችሁ በአንድ አሳብ ተስማሙ፤ የትዕቢትን ነገር አታስቡ፥ ነገር ግን የትሕትናን ነገር ለመሥራት ትጉ። ልባሞች የሆናችሁ አይምሰላችሁ።
¹⁷ ለማንም ስለ ክፉ ፈንታ ክፉን አትመልሱ፤ በሰው ሁሉ ፊት መልካም የሆነውን አስቡ።
¹⁸ ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ።
¹⁹ ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና።
²⁰ ጠላትህ ግን ቢራብ አብላው፤ ቢጠማ አጠጣው፤ ይህን በማድረግህ በራሱ ላይ የእሳት ፍም ትከምራለህና።
²¹ ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ።

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

‹‹ጌታውን ያስደሰተው አገልጋይ ታማኝና ቸር አገልጋይ ነው››
ቅዱስ ያሬድ



💠ከማንም አስቀድሞ አገልግሎት ለአምላካችን እግዚአብሔር ይገባል፤ በጥንተ ተፈጥሮ በመጀመሪያው ቀን የተፈጠሩት መላእክት ፈጣሪያቸውን ዘወትር ያለማቋረጥ ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያሉ እንደሚያመሰግኑት ሊቁ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ በመጽሐፈ አክሲማሮስ ገልጾልናል፡፡ (አክሲማሮስ ዘእሑድ) በዕለተ ዓርብ ሰው ሲፈጠር እንደ መላእክቱ የፈጠረውን ጌታውን እንዲያመሰግን፣ እንዲያገለግል እንዲሁም ስሙን እንዲቀድስና ክቡርን እንዲወርስ በመሆኑም የቀደመ ሰው አዳምም አምላኩን እያመሰገነና በገነትም በጸሎት እየተጋ ኖሯል፡፡

በመጽሐፍ ቅዱስና በሌሎች ቅዱሳት መጻሕፍት ተመዝግቦ እንደምናገኘው ጥንተ ጠላት ዲያብሎስ አምላኩን ለማመስገን ባለመፍቀዱ ተረግሞ ወደ ምድር ከተጣለ በኋላ የሰውን ዘር በተለያዩ መንገዶች በማሳት፣ ከቀናው መንገድና ከጽድቁ ጎዳና በማስወጣት ፈጣሪያቸውን እንዳያገለግሉ ያደርጋል፡፡ (ዘፍ.፩-፰፣ አክሲማሮስ ዘዓርብ)

ይህ በእርግጥ አስከፊና አሳዛኝ ቢሆንም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያት ‹‹በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ›› በማለት እንደ ነገራቸው ምንም እንኳን ጠላታችን መከራ አጽንቶና ተስፋ አስቆርጦ ብኩንና ከንቱ ሊያደርገን ቢጥርም መከራውን አልፈን፣ ሥቃያችንን ተቋቁመንና ችግራችን ተወጥተን በመልካም አገልግሎት ወደ አምላካችን መንግሥት መግባት ይቻለናል፡፡ (ዮሐ.፲፮፥፴፫)

መልካም አገልግሎት ለእግዚአብሔር አምላክ በሰውነታችን በበጎነታችን፣ በቅንነታችን፣ በትሕትናችን፣ በዕውቀታችንና በጉልበታችን የምናቅርበው የጸሎት፣ የጾም፣ የምጽዋት፣ የትሩፋትና የፍቅር አገልግሎት ነው፡፡ አምላካችንን ከማመስገን በተጨማሪ ዘወትር እርሱን በመፍራት በዕለት ኑሮአችን ልናስበውና ልናገለግለው ይገባል፡፡ ፈሪሃ እግዚአብሔር ያለው ሰው በምንም ዓይነት ሁኔታ ውስት ቢሆን ክፋትና ኃጢአት ከመሥራት ርቆ ይኖራልና፡፡ በቅንነትና በትሕትና የተሞላ የማኅበራዊ ሕይወትም ይኖረዋልና፡፡ ለሌሎች ሰዎችም መልካም ከማድረግ አይቦዝንም፡፡ ከዚህም አልፎ ተርፎ ባካበተው የመንፈሳዊ እና ዓለማዊ ዕውቀት እንዲሁም ባለው ጉልበት አምላኩን ዘወትር ያገለግላል፤ ይህም ተግባሩ ለጌታው የታመነ ታማኝና ቸር አገልጋይ ያሰኘዋል፡፡

በመጽሐፍ ቅዱስ የሐዲስ ኪዳን ክፍል ወንጌል ላይ ቅዱስ ማቴዎስ የጻፈውን አንድ ታሪክ እናንሣ፤ ‹‹አንድ ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ባለጸጋ ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደ ሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤ ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት፣ ለአንዱ ሁለት፣ ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ። አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፤ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ። አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድር ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ።››

ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው። አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ “ጌታ ሆይ፥ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት” አለ። ጌታውም “መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው።

ሁለት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ “ጌታ ሆይ፥ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት” አለ። ጌታውም “መልካም፥ አንተ በጎ፥ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፥ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው።

አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ “ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህበት የምታጭድ፣ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ” አለ። ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፦ “አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ፥ ካልዘራሁበት እንዳጭድ ካልበተንሁበትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፤ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር። ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት፤ ዐሥር መክሊትም ላለው ስጡት፤ ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳን ይወሰድበታል።

የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።›› (ማቴ.፳፭፥፲፬-፴)
ባለ ጸጋ የተባለው ጌታችን ነው፡፡ መክሊት የተባለው ደግሞ ከአምላካችን የተጠን የተለያዩ የአገልግሎት ጸጋዎች ናቸው፡፡ በታማኝነት ያገለገሉት ሰዎች ምሳሌ በምድራዊ ሕይወታቸው በተሰጣቸው ጸጋ በትጋት አምላካቸውን አገልግለው በመልካም ዕረፍት ገነት የገቡት ቅዱሳን ሰዎች ናቸው፤ መክሊቱን የቀበረው ሰነፍ አገልጋይ ደግሞ በተሰጣቸው ጸጋ በታማኝነት ማገልገል ሲገባቸው ያላገለገሉ ሰዎች ምሳሌ ነው፡፡

ጌታቸው ሊቆጣጠራቸው የመምጣቱ ነገር ጌታችን በዕለተ ምጽአት ለፍርድ ሲመጣ ለሁሉም በሠራው ሥራ መጠን ዋጋ ለመስጠት እንደሚመጣ የሚያመለክት ነው፡፡ ያገለገሉትን ታማኝ አገልጋየችም ለእያንዳንዱ ‹‹ወደ ጌታህ ደስታ ግባ!›› ማለቱ ታማኝ አገልጋዮች መንግሥተ ሰማያትን እንደሚወርሱ የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ሰነፉ አገልጋይ ወደ ጨለማና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ቦታ መወርወሩም ኀጥአን ወደ ገሃነመ እሳት መጣላቸውን የሚያሳይ ነው፡፡

ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ጌታውን ያስደሰተው አገልጋይ ታማኝና ቸር አገልጋይ ነው›› በማለት የተናገረው ይህን የወንጌል እውነት የሚገልጽ ነው፡፡ ታማኝነትና ቸርነት ለአገልግሎታችን እጅጉን አስፈላጊዎች ናቸው፡፡ ታማኝ መሆን ያለ ጥርጥርና በፍጹም እውነት ለአምላካችን መገዛት፣ መታዘዝና መኖር እንዲሁም በሕጉ መኖር ነው፡፡ ይህም ለእርሱ ታምነን ያለ ሐሰት፣ ያለ ስርቆት፣ ያለ አመንዝራነት እና ያለ ክህደት ወዘተ. እንድንኖር ይረዳናል፡፡ በተሰጠንም ክሂሎት፣ ተሰጥኦና ትሩፋት ማገልገል ያስችለናል፡፡ በአንደበታችን እንድናመሰግናው፣ በእጆቻችን አጨብጭበን፣ በጣቶቻችን በገና ደርድረንና መሰንቆ መትተን እንድንዘምርለት፣ በጉልበታችን እንድንሰግድለት በልባችን እንድናፈቅረው አስተምሮናል፡፡

ቸር በመሆን ለሌሎች በለጋስነት ካለን ነገር በመስጠትና በማካፈል መኖርን አሳይቶናል፡፡ አንድ ዳቦ ያለው ግማሹን ለሌላው እንዲያካፈል፣ ሁለት ልብስ ወይም ጫማ ያለው ለሌለው እንዲሰጥ፣ ከማዕዳችን ለተራቡ እንድናበላ፣ ከማድጋችን ለተጠሙ እንድናጠጣ፣ ለተቸገሩትና ላዘኑት ቸርነት በማድረግ እንድናስተዛዝን፣ የታመሙትን እንድናስታምም የአምላካችን ቅዱስ ቃል ያዘናል፡፡ እኛም እንደ መልካም ልጆቹ ለእርሱ በመታዘዝ ታማኝና ቸር አገልጋይ እንሁን!

የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነትና ረድኤት አይለየን፤ አሜን!

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

‹‹እኔ ባሪያህ የአባቴን በጎች ስጠብቅ አንበሳ ወይም ድብ ይመጣ ነበር፤ ከመንጋውም ጠቦት ይወሰድ ነበር፤በኋላውም እከተለውና እመታው ነበር፤ ከአፉም አስጥለው ነበር፤ በተነሳብኝም ጊዜ ጉሮሮውን አንቄ እመታውና እገድለው ነበር፡፡ይህም ፍልስጥኤማዊ ከነዚያ እንደ አንዱ ይሆናል፤ እንግዲህ እገድለው ዘንድ ከእስራኤል ተግዳሮትን አስወግድ ዘንድ ዛሬ አልሄድምን? የሕያው አምላክ ጭፍሮችን ይገዳደር ዘንድ ይህ ቆላፍ ምንድን ነው? ከአንበሳና ከድብ ያስጣለኝ እግዚአብሔር ከዚህ ያልተገረዘ ፍልስጥኤማዊ እጅ ያስጥለኛል››አለ፡፡ (፩ ሳሙ. ፲፯፥፴፬)

ዛሬስ ቢሆን በእስራኤል ዘነፍስ በምእመናን ላይ የሚገዳደሩ ብዙ ፍልስኤማውያን ተሰልፈዋል፤ እነዚህን ድል የሚነሣ በጎቹን ምእመናን ከተኩላ ከአንበሳና፣ ከድብ አፍ የሚታደግ ታማኝ አገልጋይ ማነው? ‹‹ከምእመናን ተግዳሮት የሚያርቅ ፈጣሪዬ ከመከራ ያድነኛል›› ብሎ የሚታመን የኢ-አማንያን ብዛት የማያስፈራው ማን ነው? ከትንሽነቱ እስከ ታላቅነቱ የታመነ አገልጋይ ማነው? ለተሾመበት ሓላፊነት ታማኝ ማነው? አሁንም ዓለማችን ከሥጋውያን ባለ ሥልጣናትም ሆነ ከመንፈሳዊያን መሪዎች የምትሻው ታማኝ ሰው ነው፡፡ በሙስና ያልተዘፈቀ ጉቦ አይኑን ያላጨለመበት ለመንጋው አርአያና ምሳሌ የሚሆን ሰው ታማኝ አገልጋይ ነው፡፡ በመኀላ የተቀበለውን የአገልግሎት ሓላፊነት የማይዘነጋ ታማኝ መሆን አለበት፡፡

መንጋው በክህደት ሲጠፋ ዝም ብሎ የሚያይ ጳጳስ፣ ቄስ፣ ዲያቆን፣ መምህር፣ ሰባኪ፣ አገልጋይ አይደለም፤ ታማሚው እየተሰቃየ የሚዝናና፣ ቆይ ሻይ ልጠጣ የሚል፣ ሐኪም ታማኝ አይደለም፡፡ ፍርድ የሚያጎድል ድሆችን የሚበድል ለደሃ አደጎች የማይፈርድ ዳኛ ታማኝ አገልጋይ አይደለም፡፡

ቅቤ በሙዝ እና በድንች ቀላቅሎ፣ በርበሬ በገል ጨምሮ ሌሎችን አጭበርብሮ የሚሸጥ ነጋዴ ታማኝ አገልጋይ አይደለም፡፡ እየነገደ ያለው በሰው ሕይወት መሆኑን መዘንጋት የለበትም፡፡ እንደየ አቅሙ በተሰጠው የአገልግሎት ዘርፍ ታማኝ መሆን አለበት፡፡

፫. ታማኝ አገልጋይ ቅዱስ ዮሴፍ

ዮሴፍ ለወንድሞቹ ምግባቸውን ተሸክሞ፣ የእርሱ ስንቅ ቢያልቅ የወንድሞቹን ስንቅ ሳይበላ በትንሽ የታመነ ሰው ነበር፤ ወንድሞቹ ሸጠውት በቤተ ጴጥፋራ በሚያገለግልበት ጊዜም ታማኝ ነበር፤ ታማኝነቱ በጲጥፋራ ቤት ጌታ አድርጎታል፡፡

‹‹ዮሴፍ ተሸጠ፤ አገልጋይም ሆነ፤ እግሮቹ በእግር ብረት ስለሰሉ ሰውነቱም ከብረት አመለጠች፤ ቃሉ ሳይደርስ የእግዚአብሔር ቃል ፈተነው፤ ንጉሥ ላከ፤ ፈታውም፤ የሕዝብ አለቃ አድርጎ ሾመው፤ የቤቱም ጌታ አደረገው፤ በገንዘቡ ሁሉ ላይ ገዢ አደረገው፡፡ አለቆቹን እንደ እርሱ ይገስጽ ዘንድ፣ ሽማግሌዎችን እንደ እርሱ ጥበበኞች ያደርጋቸው ዘንድ››፡፡ (መዝ.፻፬፥፲፯) በዚህ ሁኔታ የነበረው ዮሴፍ የጌታው ሚስት ሲወጣና ሲገባ ዐይኗን ጣለችበት በዝሙት አዐይን ተመለከተችው፡፡

‹‹የጌታውም ሚስት በዮሴፍ ላይ ዐይኗን ጣለችበት፤ ከእኔም ጋር ተኛ አለችው፤ እርሱም እምቢ አለ፡፡ ለጌታው ሚስቱ እንዲህ አላት፤ እነሆ ጌታዬ በቤቱ ያለውን ሁሉ ለእኔ በእጄ አስረክቦኛል፡፡ በቤቱ ያለውን ምንም የሚያውቀው የለም፤ በዚህ ቤት ከአኔ የሚበልጥ ሰው የለም፡፡ ሚስት ስለሆንሽ ከአንቺ በቀር ያልሰጠኝ ነገር የለም፤ እንዴት ይህን ትልቅ ክፉ ነገር አደርጋለሁ? እንዴትስ በእግዚአብሔር ፊት ኀጢአትን እሠራለሁ?››፡፡ (ዘፍ.፴፱፥፯)

በዮሴፍ ታማኝነት የጌታው ቤት ተባርኳል፤ ሀብቱ በዝቷል፡፡ በታማኝነቱ በቤቱ ያለውን ሁሉ ተረክቦ ነበር፤ የቀረበለት ፈተና ግን ከባድ ነበር፤ ይህን በታማኝነቱ ማለፍ ችሏል፡፡ ዛሬ በእያንዳንዱ ጓዳ ልጅ ብዙ ክፋት እንዲሁም በደል ይፈጸማል፡፡ ልጅ በፈላ ውኃ የሚቀቅሉም ሰዎች አሉ፤ ሥርቆትም የሚፈጽሙ በርካታ ናቸው፡፡ በጥቃቅን ዕቃዎች እንኳን የሚታመን ጠፍቷል፡፡ ዮሴፍ ግን በታማኝ አገልጋይነቱ በመጣበት መከራ ቢታሰር እንኳ ያለ ሹመት አላደረም፤ የእስረኞች አለቃ ነበር፡፡ ከእስር ቤት ሲወጣም ግብፅን በሙሉ መርቷታል፡፡ በግብፃውያን በሙሉ ተሾሟል፤ በጥቂቱ ታምኗልና፡፡ ‹‹በጥቂቱ የታመነ በብዙ ይሾማል›› እንዲል፡፡ (ማቴ.፳፭፥፳፬)

ከሦስቱ ታማኝ አገልጋዮች ሕይወት ሁሉም የሰው ልጅ ታማኝ አገልጋይነት የሚያሰጠውን ክብርና ጸጋ ተመልክቶ በታማኝነት ማገልገል ይገባዋል፡፡ ታማኝ መሆን መጀመሪያ የሚጠቅመው ለራስ ነው፤ ከዚያም ለሀገር፣ ለወገን፣ ለቤተ ክርስቲያን፣ ላመኑት፣ ላላመኑት ሁሉ ይጠቅማል፡፡ በመጨረሻም የጽድቅ አክሊልን ያቀዳጃል፤ መንግሥተ ሰማያትን ያወርሳል፤ በሰውም በእግዚአብሔርም ፊት ያስከብራል፡፡

ጻድቃን፣ ሰማዕታትና ቅዱሳን በታማኝ አገልግሎታቸው ፈጣሪያቸውን ደስ አሰኝተው ከብረዋል፡፡ በሓላፊው ገንዘብ ያልታመኑት ይሁዳ፣ ሐናንያ፣ ሰጲራ፣ የደረሰባቸውን ጉዳት አይተናል፤ በአካንረ ወልደ ከርሚንም ተመሳሳይ ቅጣት ደርሶበታል፡፡ (ሐዋ.፭፥፩፣ ፩፥፳፭)

ለዚህ ነበር ቅዱስ ዳዊት ‹‹አቤቱ፥ አድነኝ፥ ደግ ሰው አልቆአልና፥ ከሰው ልጆችም መተማመን ጎድሎአልና››ያለው፡፡ (መዝ.፲፩፥፩) ስለዚህ ሁሉም በአለበት የአገልግሎት መስክ ታማኝ አገልጋይ ሆኖ ‹‹አንተ በጎ ታማኝ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃል፤ በብዙ እሾምሀለሁ›› የሚለውን የጌታውን የምስጋና ቃል መስማት ይገባዋል፡፡ መልካም አገልግሎት አገልግለን መንግሥቱን እንድንወርስና ‹‹ገብር ኄር›› እንድንባል አምላካችን ይርዳን፤ አሜን፡፡

ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ( አዳማ- ኢትዮጵያ)
ሚያዝያ 5 /2016ዓ.ም

ሼር በማድረግ አገልግሎታችንን ያሳልጡ ፔጁን ላይክ ያላደረጋችሁ ላይክ አድርጉ፡!

የTelegram:- ቻናሉን ይቀላቀሉ /channel/hameretewahedo

የYoutube:- ሰብስክራይቭ ያድርጉ https://www.youtube.com/channel/UCosQ9gywx0VAqiUm80oJ3rA

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

"ጾምን አጋመስነው አትበሉ"

ገብረ እግዚአብሔር ኪደ
ብዙ ሰዎች ደስ ተሰኝተውና እርስ በእርሳቸው፡- ግማሹን ጾም ፈጽመናል፤ የጾሙ እኩሌታ አለፈ ሲባባሉ ተመልክቻለሁ፡፡

💠እኔ ግን እነዚህ ሰዎች በዚሁ ምክንያት ደስ ሊላቸው እንደማይገባ እመክራቸዋለሁ፤

👉የጾሙ እኩሌታ ማለፉን ሳይኾን የኃጢአታቸው እኩሌታ መኼዱን መወገዱን ያስቡ፤ እንደዚያ ከኾነም ሐሴት ያድርጉ፡፡

👉ደስ ልንሰኝበት የተገባው ነገር ይኼ ነውና፡፡ ሊታይ የሚገባው ይኼ ነው፤ ጥንቱም እነዚህን ኹሉ ነገሮች የምናከናውናቸው ስሕተቶቻችንን እንድናስተካክል፣
👉ጾሙ ሲጀምር እንደ ነበርንበት ሳይኾን እንድንነጻበት፣
👉 ክፉ ልማዶቻችንን ወደ ጎን አድርገን የተቀደሰውን ምግባር ገንዘብ እንድናደርግ ነው

👉እንደዚህ ካልኾነ ግን ጾሙን መጨረሳችን በራሱ ለእኛ ታላቅ ጉዳትን ይዞ ከመምጣት ውጪ ሌላ ምንም ረብ ጥቅም አይሰጠንም፡፡

👉ስለዚህ ብዙ ጊዜ መጾማችንን ብቻ አንመልከት፤ ይህ ምንም ትልቅ ነገር አይደለምና፤ ይልቁንስ በዚህ ጾም ራሳችንን አሻሽለን እንደ ኾነ፣ ጾሙ ከተፈታ በኋላም የዚሁ ፍሬ ጎምርቶ ይታይብን እንደ ኾነ ሐሴት እናድርግ፡፡

👉የክረምት ጥቅሙ ይበልጥ የሚታወቀው ወራቱ ካለፈ በኋላ ነውና፡፡

👉የዚያን ጊዜ የአበባው ማበብ፣ የአዝመራው ማፍራት፣ ሌሎች ዕፅዋትም በቅጠላቸውና በፍሬያቸው በወርሐ ክረምት ያገኙትን ጥቅም ግልጽ አድርገው ይናገራሉና! በእኛም ዘንድ ልክ እንደዚህ ይኹን፡፡

👉በወርሐ ክረምቱ በብዛትም በዓይነትም የተለያየ ዓይነት የዝናብ ጠብታዎችን ተቀብለናል፤ ብዙ ተከታታይ ትምህርቶችን ተምረናል፤ መንፈሳዊ አዝርእት ተዘርተዉብናል፤ የቅምጥልነት እሾኽም ቈርጠን ጥለናል፡፡

👉ስለዚህ ጾሙ በተፈታ ጊዜ የጾሙ ፍሬ ይከብበን ዘንድ፣ ከጾሙ የሰበሰብናቸውን መልካም ነገሮችም ጾሙን ራሱን እናስታውሰው ዘንድ የሰማነውን ነገር አጽንተን በመያዝ እንትጋ።

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

"የተባረከ ሰው ማለት የራሱን ድክመት የሚያው ሰው ነው። ምክንያቱም ይሄ የእውቀቱ መሠረትና የሁሉም መልካም ነገሮች መጀመሪያ ይሆንለታልና፡፡"
(ማር ይስሐቅ)

Читать полностью…
Subscribe to a channel