dnhayilemikael | Unsorted

Telegram-канал dnhayilemikael - ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

1867

#መሰረታዊ_የቤተክርስቲያን_ክርስቲያን_ትምህርት / #የተለያዩ_ተከታታይ_ትምህርት ' #ስንክሳር_የቅዱሳን_ገድል_በየዕለቱ ! #ስዕለ_አድህኖ ! #ምስባክ #የየበአላቱ_ዋዜማና_ሥርተ_ማህሌት #መዝሙር #ግጥም #ለመናፍቃን_ጥያቄ_መልስ እና የተለያዩ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ ሌሎች መንፈሳዊ ጽሁፎች ይለቀቁበታል Administration @zearsema_dn

Subscribe to a channel

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ኦያያያያያያያያያ ወልደ እንትና ዐሥር ሺ ብር ሰጥተዋል። ምእመናን ሴቶች በእልልታ ወንዶች በጭብጨባ አመስግኑልን_እልልልልልል_ጨብጨብጨብጨብ_ወዘተ። ጨረታ ዐውደ ምሕረት ላይ ለምን???

በአንድ መግለጫ ብቻ መስተካከል የሚችል ነገር ግን ቸል የተባለ ጉዳይ፦

፩. አዲስ አበባም ሌሎች ከተሞች ላይም ቄሶች ነን የሚሉ፣ መነኮሳት ነን የሚሉ መንገድ ላይ ሰው ከተሳለማቸው በኋላ አስገድደው ውዳሴ ማርያም ወይም ሌላ የጸሎት መጽሐፍ ካልገዛችሁን የሚሉ ብዙ ናቸው። ይህ እኔንም ገጥሞኛል። ይህን ሙሉ በሙሉ ለምእመኑም አሳውቆ ማስቀረት።

፪. ጥላ ዘቅዝቆ በዐውደ ምሕረት ውስጥ መለመን ቢቀር። በተጨማሪ ዐውደ ምሕረት ላይ ጨረታ፣ መጽሐፍ መሸጥና የመሳሰሉ ንግዶች መቅረት አለባቸው። በእግዚአብሔር ቤት ንግድና ጨረታ ማድረግ ታላቅ ኃጢአት አይደለምን????

፫. የገጠሪቷ ቤተክርስቲያን ጧፍ፣ ዘቢብ፣ ዕጣን አጥታ ተቸግራ ሳለ በየዐውደ ምሕረቱ ዝም ብሎ የሚነድ ጧፍ መኖር የለበትም። በፍትሐ ነገሥት እንደተነገረው የሐዋርያት መልእክት ሲነበብ ጧፍ መበራቱ አንትሙ ውእቱ ብርሃኑ ለዓለም ብሏቸዋልና የዚያ ምሳሌ ነው። ወንጌል ሲነበብ ብዙ መብራት እንዲበራ ታዟል። ጌታ አነ ውእቱ ብርሃኑ ለዓለም ብሏልና የዚያ ምሳሌ ነው። በወንጌል ጊዜ ብዙ ይብራ መባሉ የጌታ ብርሃንነት የባሕርይ ስለሆነ ይህንን በሥርዓታችን ለመመስከር ነው።

፬. በበዓላት ወቅት በዓሉን ለማክበር የመጣው ሕዝብ የወንጌልን ትምህርት መማር ሲገባው የስለት ጊዜ እየተባለ ምእመናንን ማሰልቸት ተገቢ አይደለም። ስለት የሚቀበል ለብቻው መድቦ በዐውደ ምሕረቱ ግን ወንጌል ነው መሰበክ ያለበት።

፭. ቤተክርስቲያን አሥራት የምትቀበልበት፣ በውስጧ ላሉ አግልጋዮች ደመወዝ የምትከፍልበት የራሷ ባንክ ለምን አይኖራትም??? ይህ ቢሆን ምእመናንም አሥራታቸውን ቀጥታ በባንክ ይከፍላሉ። ስለታቸውንም ሌላውንም በዚያ ያስገባሉ። ይህ ሆነ ማለት ደግሞ የሙዳየ ምጽዋት ሌቦች ምክንያት ያጣሉ ማለት ነው።

፮. ማዕከላዊ የሆነ የደመወዝ ክፍያ ለምን አይኖርም? ለምንድን ነው መምህራን አዲስ አበባና ከትልልቅ ከተሞች የተከማቹት?? በረሓ የሚሄደው ቀነሰ፣ የገጠር አጥቢያዎች ላይ አገልጋይ እየጠፋ ነው። ይህ እንዳይሆን መምህራንን ወደየቦታው መበተን አስፈላጊ ነው። በረሓ ለሚሄዱት ከተማ ካለው የበለጠ ደመወዝ እንዲከፈላቸው ማድረግ። ይህ ቢደረግ ወንጌል ትሰፋለች።

አንድም ካህን ጎዳና ላይ ሲለምን እንዳይገኝ፣ ከተገኘ ግን ምእመናን ለአቅራቢያ ቤተክህነት አሳውቀው እርምጃ እንዲወሰድበት ማድረግ ይቻላል።

© በትረ ማርያም አበባው

🌹

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

እንኳን አደረሰን!

በዓለ ቅዱሳን፦
❖ዮሴፍ አረጋዊ (ትሩፍ)
❖ወጢሞቴዎስ ሊቀ ጳጳሳት (ዘአልቦ ጥሪት)
❖ፍሬምናጦስ ሰላማ (ከሣቴ ብርሃን)
❖ወሳሙኤል (ዘሃሌ ሉያ)

ሐምሌ ፳፮፦

✝ሰላም ለስዕርተ ርዕስከ ዘአስተርአየ ጸዓዳ፤ ወለገጽከ ውኩይ ከመ ርዕየቱ ለተቅዳ፤ ዮሴፍ ወልደ ዳዊት እምዘርዓ ያዕቆብ ዘይሁዳ፤ ዘጻመውከ ምስለ ማርያም ወምስለ ክርስቶስ ወልዳ፤ በጊዜ ኮነ ስደት እምኀበ ንጉሥ ኄሮዳ!

✝ዮሴፍ አረጋዊ በዓለ ርስእ ሠናይ፤ ዘኢተረክበ በውስቴቱ ኅሊና እኩይ፤ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ለብሔረ አግአዚ ዐባይ፤ ሊቀ ጳጳሳት ክቡር ጢሞቴዎስ ነዳይ፤ ሮዲስ ጻድቅ ወሳሙኤል ኅሩይ!

✝ሰላም ለዮሴፍ ዘተኃርየ በበትር፤ ከመ ይኩን ሐጻኒሁ ለአማኑኤል ሔር፤ ፍሬምናጦስ ሰላማ ሐዋርያዊ ክቡር፤ ወለጢሞቴዎስ ዘይብልዎ ብእሲ ግዩር፤ ወሳሙኤል ዘፈለሰ ውስተ ብሔር ስዑር!

©ዝክረ ቅዱሳን

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
እግዚአብሔር ያልተቀየማቸው ተጠራጣሪዎች        
    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥

❖ አባ ጊዮርጊስ እንዲህ አለ
አረጋዊው ስምዖን ‘እነሆ ድንግል ትጸንሳለች’ የሚለውን ትንቢት ተጠራጠረ፤ ይህ ጥርጣሬው ግን በደል ሆኖ አልተቆጠረበትም ይልቁንም ስሙ አማኑኤል የተባለውን ሕፃን ለማቀፍ አበቃው እንጂ፡፡

✍️"ወኢተኈልቈ ሎቱ ኑፋቄሁ ኀበ ጌጋይ አላ አብጽሖ ኀበ ሑቃፌ ሕፃን ዘስሙ አማኑኤል"

❖ ቶማስም የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠረ፤ ትንሣኤውን መጠራጠሩ ግን የጌታን ጎን ለመዳሰስ በችንካሩ እጁን ለማስገባት አበቃው፡፡

✍️ "ወአብጽሖ ኑፋቄሁ ኀበ ገሢሠ አጽልእቲሁ ለመድኃኔ ዓለም"

✍️ በእውነት ‘መተላለፉ የቀረችለት ኃጢአቱም የተከደነችለት ምስጉን ነው’ እግዚአብሔር የወደደው ሰው ቍስሉ አይመረቅዝም በደሉም አይታሰብም፡፡ 
📖መዝ 32፥1

❖ ጌታ ሆይ እኔንም ስለ መጠራጠሬ አትቀየመኝ ልደትህን የተጠራጠረው ስምዖንን እንዲያቅፍህ ፈቀድክለት፤ ትንሣኤህን የተጠራጠረውን ቶማስ ጎንህን አስነካኸው፤ ያኛው ‘ዓይኖቼ ማዳንህን አዩ’ ብሎ ዘመረልህ ይኼኛው ደግሞ ‘ጌታዬ አምላኬ’ ብሎ መሰከረልህ፡፡

❖ ጌታ ሆይ እኔ እምነተ ቢሱንም መጠራጠሬን አትመልከትብኝ፤ የሚዋዥቅ ሕሊናዬን አጽናልኝ እንደዚያ የልጅ አባት ‘አለማመኔን እርዳው’ እንደ ጴጥሮስ ‘ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ’ በመጠራጠሬ አትቀየመኝ፡፡

❖ መጠራጠሬን አይተህ አትቀየመኝ፤ አንድ ትቢያ ቢጠራጠርህ እንደማይጎድልብህ አውቃለሁ፤ ስለዚህ ራርተህ እምነትን አድለኝ፤ ምናለ ለእኔም ማዳንህን አይቼ እስካምን እንደ ስምዖን ዕድሜ ብትጨምርልኝ? መቼም ላንተ ዘመን አይቸግርህም፤ ሺህ ዓመት ለአንተ አንድ ቀን አይደለች? ቢያንስ አምኜ አሰናብተኝ እስክልህ እስከ ቀትር አቆየኝ፡፡

❖ አንተን በእምነት እንዳቅፍህ እርዳኝ እንጂ ስምዖን አሰናብተኝ እንዳለህ እኔም ደስ ብሎኝ አርፋለሁ፤ ማዳንህን ሳልረዳ ፣ አንተን በእምነት መዳፍ ሳላቅፍህ መሞትን ግን እፈራለሁ፡፡

❖ "አምላኬ ጌታዬ" ብዬ ብዘምርም እንደ ቶማስ ካልዳሰስሁህ ሰውነቴ በእምነት አይኮማተርም፤ ተጠራጣሪውን የማትንቀው ሆይ ጥያቄው የማያባራ ልቤን ጥርጣሬው የማያልቅ ከንቱ ሕሊናዬን እንደ ቶማስ ራራለት፤ ለእኔ የቆሰልከውን ቁስል በእምነት መዳፍ ካልነካሁ ፤ እጄን ከችንካርህ ካላገባሁ የፍቅርህ ጥልቀት አይሰማኝምና እባክህን ‘ና ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን’ በለኝ፡፡

❖ ሳላውቅህ የኖርኩት ጌታዬ ሆይ እንደዚያ መቶ አለቃ ‘ለካስ የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ’ ብዬ ሳልመሰክርልህ አልሙት፤ እንደ ሌንጊኖስ ወግቼህ በፈሰሰው በጎንህ ውኃ ዓይኔን አብርተህ ካለማመን ብታወጣኝ ምናለ? ያላመኑትን የማትንቀው ሆይ ተጠራጣሪዎችን ያልተቀየምከው ሆይ የሚጠራጠርህን ልቤን አትቀየምብኝ፤ የሚያስብ የሚጠይቅ አእምሮ ሠጥተህ ለምን ተጠቀምክበት ብለህ አትቀየምምና ስምዖን አቀፈህ ቶማስም ዳሰሰህ።

"ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ"
📖ኤፌ 4፥29

✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
📖ምሳ 1፥33

✍️ " #ወአንቢበክሙ አንትሙ #ለዘኢያንበበ አይድኡ
➘ #እናንተ_አንብባችሁ_ላላነበበው_ንገሩ"

📌 ምንጭ
✍️ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ 

✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝

🙏 ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ፤ እኔም ለእናንተ ከአዘጋጀው በኃዋላ በድካሜ ብዛት ሳይገባኝና ሳይገባኝ በምጽፈው ድርሳንወ ገድላት መጽሐፍት ላይ የቃላት (የፊደል) ሕፀፅ ቢገኝ በጎደለው እየሞላችሁ በጠመመው እያቃናችሁ አንብቡ በረከት ተካፈሉ እላለሁ ከምንም ጊዜ በላይ ለሀገራችንና ለዓለም ሰላም እንዲሁም ለደካማው ወንድማችሁ እንድበረታ (የተጣልሁ) እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ

✍"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
📚ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

               ወስብሐት ለእግዚአብሔር
                              ይቆየን 

───────────
                    Channel
 🧲  /channel/dnhayilemikael
 ───────────

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

@በእንተ ዲያቆናት(ስለ ዲያቆናት)

የቅድስትና ሐዋርያዊት ኵላዊት ኦርቶዶክሳዊት የተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ቅዱሳት መጻሕፍት ምን ይላሉ?
፩. ዲያቆንም ኾነ ቄስ ሰሞነኛም ይኹን አይኹን፤ ለመቀደስም ኾነ ለጸሎት ቤተ መቅደስ ውስጥ መግባት ያለባቸው ሌሊት ነው። ሥርዐተ ቅዳሴ እንዲህ ይላላ፦
👌 "ሌሊት ለጸሎት ያልመጡ ቀሳውስትና ዲያቆናት ወደ ቤተ መቅደስ ይገቡ ዘንድ ያገለግሉም ዘንድ አይገባቸውም። ይኽን ትእዛዝ ቢደፋፈሩ ግን ከሕግ ትእዛዝ የወጡ ይኾናል።" [ሥርዐተ ቅዳሴ]
፪. ብዙዎቹ ዲያቆናት ልብሰ ተክህኖ ለብሶ መቀደስ፥ ሰዓታትና ማኅሌት መቆምና በንግሥ ሰዓት መስቀልና ቃጭል ይዘው ቅድመ ታቦት መኼድ እንጂ የቅዱሳት መጻሕፍትን ምሥጢር መረዳት የስብከተ ወንጌል ግብር ብቻ ይመስላቸው። ፍጹም ስሕተት ነው።  ከመቀደስ ባለፈ እውነተኛውን የቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት
መማር፥ መረዳት፤ ከክህደት ትምህርት አንጥሮ መገንዘብም የመለየት ኃላፊነት አለባቸው።
➺ቅጥረኛ ስለኾንኩ እንጂ...በሚል ሳይፈልገው የሚቀድስ፦ ከታማኝ አገልጋይ ጋር ምን አንድነት አለው?
➾ቅባት ከተዋሕዶ ጋራ፥ ኑፋቄ ከአሚን(ከእምነት) ጋራ፥ ምርግትና ከጥንቆላ ጋራ፥ አውደ ነገሥት ከፍትሐ ነገሥት ጋር፥ ክህደት ከእውነተኛዋ ኦርቶዶክሳዊት የተዋሕዶ ትምህርት ጋር፤ ምንም ኅብረት እንደሌላቸው አንጥሮ፥ ኵልል አድርጎ የመረዳት የማስረዳትም ግዴታ አለባቸው። ለዚኽም ነው፦
👌"የቤተ ክርስቲያን መብራት አገልጋዮቹዋም የምትኾኑ ዲያቆናት ኾይ ተኵላ ከበግ ጋራ፤ ጭላት(ጭልፊ) ከርግብ ጋራ፤ ክርዳድ ከስንዴ ጋራ እንዳይኖር ከውስጥዋ ንቀሉ፤[ቅዳሴ አትናቴዎስ] እንዲል።
፫. ደጀ ሰላም፦ የሰላም ደጅ ናት። የዲያቆናት አብነት ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ መጽሐፈ ገድሉ ላይ "የቀዳሜ ሰማዕት ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ አምላክ እግዚአብሔርም የዚኽን ሰው የንስሓ እንባ ተመልክቶ ይቅር አለው። ይኽ ሰውም በዚያች ቤተ ክርስቲያን ደጀ ሰላም ተቀምጦ የደረሰበትን ለሚገባውና ለሚወጣው ኹሉ መሰከረ።" [ገድለ ቅዱስ እስጢፋኖስ ዘወርኃ መጋቢት]
✍️ አኹንማ የተጣሉ የሚታረቁባት፦ የሰላም ደጅ የተሰኘችው "ደጀ ሰላም" ድረስ ቢራና ዘር ማንዘሮቹ ገብተው "ምን ይኹንልህ?!" ብለን ግሮሰሪ አደረግነው። በርግጥ መጠጥ ፈጽሞ የተከለከለ ባይኾንም፤ አብዝቶ መጠጣት ግን የተገባ አለመኾኑ ለኹላችንም ግልጽ ነው። ደጀ ሰላም "የሰላም ደጅ" እንጂ 'የቢራዎች ደጅ' አይደለችምና ባይገባ ይመከራል።
✍️በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ተፈቅደው ነገር ግን ከማይበረታቱ ነገሮች አንዱ መጠጥ ነው። ፈጽሞ አይጠጣም፥ ርኵስ ነው ባንልም የማይጠጣ የተሻለ አደረገ።
➣"ከስካር ተጠበቁ ሙሴ በኦሪት ዘሌዋውያን እንዳይሰክሩ አዟቸዋል። እንዲሁ እናንተ ኤጲስቆጶሳት ቀሳውስትና ዲያቆናት መጠጥን ከማብዛትና ከስካር ተጠበቁ፤ መዳራት፣ ዝሙት፣ ስግብግብነት፣ ሰውን መስደብና ማስቀየም፣ መታበይ፣ በሐሰት መማል፣ ብዙ ቁም ነገሮችን መዘንጋትና ሌሎችም ከስካር የሚመነጩ ናቸው።"[መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ዘሮም፤ ምዕራፍ ፲፤ ቍጥር 56]
➛"ከስካርና ወይንን ከማብዛት ተጠበቁ፤ ቃለ እግዚአብሔር የሠፈረባቸውን መጻሕፍት መጠጣትን አዘውትሩ እንጂ።" [ዝኒ ከማሁ(Ibid) ቍጥር 57]
፬. የበቁ ዲያቆናት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በቅድስና ሥጋወደሙን ለመለወጥ ሲወርድ ማየት ይችላሉ።
➤"ካህን የመንፈስ ቅዱስን ፀጋ ላክ ባለጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለመስዋዕትነት በቀረቡ ፅዋዕና ሕብስት ላይ መንፈስ ቅዱስ ይወርዳል፤ ዲያቆናት በቅድስና ሥጋወደሙን ለመለወጥ ሲወርድ ማየት ይችላሉ። የዲያቆናት ክብር በዚህ ብቻ የተወሰነ አይደለም። ቅዱስ እስጢፋኖስ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ የክብር ቦታ ከእግዚአብሔር ዘንድ ሊሠጠው እንደቻለ ለነሱም ይሠጣል።"
[መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ዘሮም፤ ምዕራፍ ፲፩፤ ቍጥር 33]
፭. ዛሬ ላይ ዲያቆናት የት ይገኛሉ? ምን ሲያደርጉ ይገኛሉ? ክቡር ዲያቆን ሆይ! "ዙረታም" ነኝ ካልክ የት መዞር እንዳለብህ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዲህ ይመክሩናል።
➣"ዲያቆናት የክርስቲያኖችን የመኖሪያ ቤት ወዳለበት ኹሉ እየዞሩ የተቸገሩትን ኹሉ ይጎብኙ፤ ችግራቸውንም ይመልከቱ። ጥዋትም ኾነ ማታ ምእመናኑ በስንፍና እንዳይያዙ ለመንፈሳዊ አገልግሎት እንዲተጉ ያነቃቁዋቸዋል። በሠርክ በጧትና በማታም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሁል ጊዜ እየኼዱ ያመስግኑት፤ እግዚአብሔር የዕለት ብርሃን ነው፤ ኹሉንም ይረዳል።" [መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ዘሮም፤ ምዕራፍ ፱፤ ቍጥር 66]
፮. ዲያቆናት ምንም ዓይነት ጉቦ መቀበል፥ በደም ግባት ማዳላት፤ ድሀን አይቶ ባላየ ማለፍ፤ ዝም ብሎ ስለ ሴትና ወንድ በማውራት ዋዛ ፈዛዛ በመስማት- ነገረ ዘርቅ መስማት የለባቸውም።
➤ "እናንተም የመንጋዎች ጠባቆችና ዲያቆናት ሆይ መማለጃ በመቀበልና ፊት አይቶ በማድላት ምክንያት ከቤተ ክርስቲያን ታወጡት ዘንድ በደል በሌለው በንጹህ ሰው ላይ ነገር ሥራንና የሐሰት ነገርን ትሰሙ ዘንድ አይገባም። እንደዚህ ያለ ሥራ የሚሠሩ ሰዎች የዲያብሎስ ወዳጆች ይኾናሉና።" [መጽሐፈ ዲድስቅልያ፤ ምዕራፍ ፲፥ ቍጥር 55]
➣ "ዲያቆናት ድኆች ሳይለምኗቸው ፈቃዳቸውን ሊያደርጉላቸው አገባብ ነው።"[መጽሐፈ ዲድስቅልያ፤ ምዕራፍ ፲፮፥ ቍጥር 55]
፯. ዲያቆን በድቁና የተካነ ካህን ነው። ቄስም በቅስና የተካነ ካህን ነውና በአጠቃላይ ማኅበረ ካህናት አይደለም በfb በሕዝባውያን መዋኛ ገንዳዎች እንዲዋኙና ለሕዝባውያን ገላቸውን እንዲያሳዩና ተገላልጠው እንዲታዩ፥ ቁንጣ፥ ጃፖኒ፣ ጥብቅብቅ የሚያደርጉ አልባሳት አድርጎ ውጭ መታየት ፈጽሞ አይፈቀድላቸውምና....
✍️ "አንተ ግን ትታጠብ ዘንድ በወደድህ ጊዜ የሕፃንነትህን ደም ግባትና  የሰውነትህን ማማር እንዳያዩ በአንተም እንዳይሰናከሉ። አንተም እንዳትበድል፤ በእነርሱም እንዳትሰነካከል፤ ሴቶች ወደሚታጠቡበት መታጠቢያ ቤት አትግባ።"[መጽሐፈ ዲድስቅልያ፤ ምዕራፍ ፪]
👌ጸጉር አቆራረጥንም በተመለከተ ለምዕመናን ሲገልጽ የቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያናችን የሕግና የሥርዓት መጽሐፍ የሆነው ፍትሕ መንፈሳዊ ወሥጋዊ "በተፈጠርህ ጊዜ እግዚአብሔር በሰጠህ መልክ ላይ መልክ አትጨምር። ያድግ ዘንድ ፀጉርህን አትከባከበው ተላጨው እንጂ አታሳድገው። ወጥመዳቸው ቅርብ የሆነ ሴቶችን ወደ አንተ ያመጣብህ ዘንድ አታሳምረው። ረቂቅ ልብስ አትልበስ፤ ይህች ስሕተትን ታመጣለችና፤ ቀለም የተቀባ ጫማ አትጫማ፤ በጣቶችህ የወርቅ ቀለበትን አታድርግ፤ ይህ ሁሉ የዝሙት ምልክት ነውና። ጠጉርህን ግልስልስ ብጥር አታድርገው፤ አትሠራው፤ " [ፍትሕ መንፈሳዊ፤ አንቀጽ ፲፩፤ ገጽ. 123] ካለ ለካህናቱ እንዴት ጥብቅ ይሆን???



💚💛❤     
  ✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
      ❍ㅤ           ⎙ㅤ         ⌲ 
ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ         ˢᵃᵛᵉ          ˢʰᵃʳᵉ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ሺ_ዓመት_አይኖር

🥀ብዙ ጊዜ ለስንፍናችን ምክንያት ወይም ተስፋ ለመቁረጥ ሰበብ ከሚሆኑን ነግሮች አንዱ "ሺ ዓመት አይኖር" የሚለው አባባል ነው በእርግጥ በምድር ሺ ዓመት መኖር የቻለ የለም ረጅም ዓመት እንደኖረ የሚነገርለት ማቱሳላ እንኳን ሺ ዓመት አልኖረም ወዳጄ በተለይ እኛ ባለንበት በዚህ ዘመን ደግሞ እንኳን ሺ ዓመት ሊኖር ቀርቶ መቶ የሞላ እንኳን ቢገኝ የሚድያ የአንድ ወቅት የዜና ሽፋን መሆኑ የማይቀር ነው ስለዚህ ወደ ዘመናችን አባባሉን ማምጣት ከፈለግን መቶ ዓመት አይኖር በሚል ልንቀይረው ያስፈልጋል።

🥀የሚያሳዝነው ሺ ዓመት አይኖር የምንለው ለመዝናናት ለመጨፈር ራስን ለመርሳት ፈቃደ ሥጋን እንደ ልብ ለመፈጸም ብቻ እንጂ ለመንፈሳዊ ሕይወት ለመሰናዳት አይደለም "አንቂ" የሚባሉ አካላት የዕድሜህን አጫርነት የሚነግሩህ ከሞት በኋላ ላለው ረጅሙ ዕድሜ በዚህች በአጭሯ የምድር ዕድሜህ በጎ ሰርተህ እንድታልፍ ሳይሆን እንዳትጨናነቅ ፈታ ብለህ(በእነርሱ አማርኛ) እንድትኖር ለማስታወስ ብቻ ነው።

🥀ወዳጄ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ግን በምድር ስለምትኖርበት ዕድሜህ ሲነግርህ ቢበዛ(ቢበረታ) ሰማንያ ይልሃል ሺ ዓመት አይኖር ሲሉህ ቢበዛ ሰማንያ እርሱም በተገኘ በላቸው ታድያ በምድር የምትኖርበት ዕድሜህ ጥቂት ከሆነ ከዚያ በኋላ በሞት ይህን ምድር ከተሰናበትክ ከሞት በኋላ የት ትሄድ ይሆን?? የዚህ ምድር ኑሮህ በሞት ከተቋጨ በኋላ ሞተህ የምትቀር መስሎ እንዳይሰማህ ከሞት በኋላ ሕይወት አለህ ያውም እንደሰው ኖረህ ከሞትክ የምትነሳው እንደ ሰው ሆነህ የምትኖረውን ሕይወት ለመድገም

🥀እንዳይመስልህ ከትንሣኤ በኋላ የምትኖረው እንደ መላእክት ነው “በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ”ማቴ 22፥30
ስለዚህ አስታውስ የምድር ኑሮህ ቢበዛ ሰማንያ ነው ያ ማለት ጥቂት ነው መጽሐፍ
እንደሚነግርህ

🥀ሕይወታችሁ ምንድር ነው ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና”
ያዕ 4፥14

🥀ስለዚህ በምድር የምትቆየው ጥቂት ጊዜ ነውና:-*
ዛሬ የንስሐ አባት ያዝ
ዛሬ ንስሐ ግባ
ዛሬ ከተጣላሃቸው ታረቅ
ዛሬ ያስቀየምካቸውን ይቅር በል
ዛሬሥጋ ወደሙን ተቀበል

ነገ ሳይሆን ዛሬ መልካም ነገሮችህን ሁሉ ጀምር ምክንያቱም
“እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።”
2ኛ ቆሮ 6፥2   የሞዐ
     Join  ቴሌግራም ቻናል

  አምላከ ቅዱሳን ለንስሐ የተዘጋጀ ልብ ያድለን
ለንስሃ ሞት ያብቃን🙏

❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮

    የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን 
              ➡️      መሰረተ ሚዲያ

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
     ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ


👇👇👇👇👇👇👇👇

የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═
/channel/Meseretemedia

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

† የድፍረት ኃጢአት በእግዚአብሔር ቤት †

"በመገናኛው ድንኳን ደጅ ከሚየገለግሉ ሴቶች ጋር እንደተኙ ሰማ።"(1ኛ ሳሙ 2፡22)

★ የአገልጋዮች ማመንዘርና ውጤቱ ★

34 ሺህ እስራኤላውያን በጦርነት ከሞቱበትና ታቦተ ጽዮን ከተማረከችበት የድፍረት ኃጢአቶች መካከል አንዱ የእግዚአብሔርን ቃል የሚያውቁና በውስጥና በውጭ የሚገለግሉ ወንዶችና ሴቶች ያደረጉት ማመንዘር ነው፡፡

ማመንዘር ኃጢአት ነው፡፡ ማመንዘር ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጪ ሲሆን ደግሞ ቅጣቱ እጅግ የከፋ ነው ማለትም ወንድ ከወንድና ሴት ከሴት ጋር ሲሆን ሀገርን ከነሙሉ ሀብትና ንብረቷ በእሳት ተቃጥላ እንድትጠፋ ያደርጋል፡፡ ግብሩም ግብረ ሰዶም ይባላል፡፡ (ዘፍ 19፡24)
አንድ ተራ ግለሰብ ከሕግ አግባብ ውጪ ቢያመነዝር ኃጢአቱ በራሱ ላይ ይሆናል፡፡
ኃይልንና ሥልጣንን ተtመክቶ በትዳር ያለችን ሴት ቢመነዝር በደሉ ከፍ ያለ ቅጣትን ያስከተላል፡፡ ቅጣቱም ከራስ ወደ ልጅ ይወርዳል፡፡ (2 ሳሙ 12፡10)

በቤተ እግዚአብሔር ቃሉን እየሰሙ ኖረው እያገለገሉ ያሉ፣ እግዚአብሔርን መፍራት ትተው በድፍረት ከሌሎች አገልጋዮች ጋር ቢያመነዝሩ ለኃጢአታቸው የሚከፈላቸው ደመወዝ ቤተ ክርስቲያንን ሁሉ አደጋ ውስጥ ይጥላል፡፡
ከላይ በርዕሱ ለመጠቀስ እንደተሞከረው ሁለቱ የሊቀ ካህኑ የዔሊ ልጆች አፍኒንና ፊንሐስ ከክህነታቸው በተጨማሪ በትዳራቸው ላይ ይማግጡ፣ ያመነዝሩ የነበሩት በእግዚአብሔር ቤት ከሚያገለግሉ እግዚአብሔርን ከሚያውቁ ሴቶች ጋር ነበር፡፡ በየአብያተ ክርስቲያናቱ የንግስ በዓልን ምክንያት አድርጎ በሰንበት ትምሕርት ቤቶች አዘጋጅነት የሚካሄዱ የአዳር መርሐ ግብሮች ፈተና እየሆኑብን አይደለ ?፣ የጉዞ መርሐ ግብሮችስ ከመንፈሳዊ ዓላማቸው እያፈነገጡብን አይደለ?

አሁን ይህን ቃል ሰምተንና አንብበን በነ አፍኒንና ፊንሐስ ላይ ለመፍረድ አንነሳ በዘመናችንስ እንደዚህ ዓይነት የድፍረት ኃጢአቶች በአገልጋዮች ዘንድ የሉም? . . . የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪዎች፣ የሰንበት ትምሕርት ቤት አመራሮች ቃሉን ከማወቅ በዘለለ በዲያቆናትና በሰንበት ትምሕርት ቤት ወጣት ሴቶች፣ በሰንበት ትምሕርት ቤት ወጣት ሴቶችና ወንዶች መካከል የሚታዩና የሚሰሙ አዝማሚያዎችን በዝምታ ማለፍ እንደ ዔሊ አያስቀስፈንም ብላችሁ ታምናላችሁ? ቤተ ክርስቲያንን አደጋ ውስጥ አይከታትም ብላችሁ ታስባላችሁ? . . . በሀገራችን እየደረሰ ላለው ብዙ ምስቅልቅሎችስ የአገልጋዮች በቤተ መቅደስ የሚደረጉ ዘርፈ ብዙ የድፍረት ኃጢአቶች ምክንያት አይደለም ብላችሁ ታስባላችሁ? ይህንን የማስጠንቀቂያ ደውል የሰማን ሁላችን ዛሬ ንስሐ እንግባ።

ለሌሎችም ሼር አድርጉት

መምህር ኢንጂነር ታርኩ አበራ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

+"+ እንኩዋን ለአጋእዝተ ዓለም #ሥላሴ እና ለቅዱሳን
አበው
#አብርሃም: #አባ_ሲኖዳ እና #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ
ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ +"+

+"+
#ሥሉስ_ቅዱስ +"+

=>በአንድነቱ ምንታዌ (ሁለትነት): በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት)
የሌለበት የዘለዓለም አምላክ: የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ
#እግዚአብሔር ነው:: #አብ : #ወልድ : #መንፈስ_ቅዱስ
በስም: በአካል: በግብር ሦስትነት: በባሕርይ: በሕልውናና
በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው:: በዚህ ጊዜ ተገኙ: በዚህ ጊዜ
ያልፋሉ አይባሉም:: መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና::

+ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት " #ቅድስት_ሥላሴ "
እንላቸዋለን:: የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም::
የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል:: በቤቱም መጥተው
ያድራሉ::

+ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል
በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም:: አባታችን
#ቅዱስ_አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን
በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል:: ሥላሴ
አኀዜ ዓለም (ዓለምን በእጁ የያዘ) ነው:: ነገር ግን በፍቅር
ለሚሻው በፍቅር ይመጣል::

+አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ: እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ
ሥላሴን በድንኩዋናቸው አስተናገዱ:: አብርሃም እግራቸውን
አጠበ:: (ወይ መታደል!) በጀርባውም አዘላቸው:: (ድንቅ አባት!)
ምሳቸውንም አቀረበላቸው:: እንደሚበሉ ሆኑለት:: በዚያው
ዕለትም የይስሐቅን መወለድ አበሠሩት:: #ቅድስት_ሣራ ሳቀች::
እንደ ዘንድሮ ወገኖቻችን የማሾፍ አይደለም:: ደስታና ጉጉት
የፈጠረው እንጂ:: ሥላሴ "ምንት አስሐቃ ለሣራ በባሕቲታ"
ብለው ነበርና በዚህም ምክንያት ነው " #ይስሐቅ" የተባለው::

+ሥላሴን ያስተናገደች ድንኩዋን (ሐይመት) የድንግል
እመቤታችን ማርያም ምሳሌ ናት:: በድንግል ላይ #አብ
ለአጽንኦ: #መንፈስ_ቅዱስ ለአንጽሖ: #ወልድ በተለየ አካሉ
ለሥጋዌ በእርሷ ላይ አርፈዋል / አድረዋልና::

+"+ #ታላቁ_አባ_ሲኖዳ +"+

=>የባሕታውን ሁሉ አለቃቸው ታላቁ ቅዱስ ሲኖዳ:-
¤በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን የተወለደ
¤በእናቱ ማሕጸን ሳለ መላእክት በሰይፈ እሳት ይጠብቁት የነበረ
¤የታላቅነት ትንቢት የተነገረለት
¤ገና ሳይወለድ ሥውራን አበው የሰገዱለት
¤በሕጻን ሰውነቱ ጾምና ጸሎትን የጀመረ
¤የልጅነት ቁርስና ምሳውን ለነዳያን ያካፍል የነበረ
¤በ9 ዓመቱ ወደ በርሃ የመነነ
¤የአባ አብጐል ደቀ መዝሙር የሆነ አባት ነው::

+ሲመነኩስም በእግዚአብሔር ትእዛዝ #የሠለስቱ_ደቂቅ
አስኬማ: #የኤልያስ ቆብዕ እና የመጥምቁ #ዮሐንስ ቅናትን
(መታጠቂያ) ከያሉበት መላእክት አምጥተውለት የመነኮሰ
¤ዓለምን በሙሉ በጸሎቱ ይጠብቅ የነበረ
¤የግብፅን በርሃ በብርሃን የሞላ
¤በርካታ ድርሰቶችን የደረሰ
¤ያለ ማቇረጥ በየቀኑ ከ100 ዓመታት በላይ ከጌታችን ክርስቶስ
ጋር የተነጋገረ
¤ደመናትን ተጭኖ ይሔድ የነበረና
¤ያለ ዕረፍት ለ111 ዓመታት ከ2 ወራት ፈጣሪውን ያገለገለ
አባት ነው::

+በዚህም ምክንያት አንድ ቀን ገዳማውያን ሁሉ እየሰሙ
እንዲህ የሚል ቃል ከሰማይ መጣ:: "ሲኖዳ ተሠይመ
#አርሲመትሪዳ " (ሲኖዳ አርሲመትሪዳ ሆኗል:: ማለትም
ለባሕታውያን ሁሉ አለቃ ሁኖ ተመርጧል ማለት ነው:: )

+ቅዱሱ የጌታችንን እግር እያጠበም ይጠጣ ነበር::
+በዚህች ዕለት በ120 ዓመቱ ጌታችን ወርዶ ሲያሳርገው
#አቡነ_ኪሮስ "ታላቅ ምሰሶ (ታላቅ ዛፍ) ወደቀ" ብለው
አልቅሰዋል:: #ሲኖዳ ማለት "ደግ ሰው" ማለት ነው::

+"+ #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ ( #GIYORGIS_OF_SEGLA )
+"+


=>ታላቁ ኢትዮዽያዊ ሊቅና ጻድቅ የተወለደው ወሎ #ጋስጫ
ውስጥ በ1358 ዓ/ም ነው:: ከልጅነቱ ትምሕርት አልገባሕ
ቢለውም በልቡናው ግን ቅን እና ታዛዥ ነበር:: መምሕሩ
"ትምሕርት አይገባውምና ውሰዱት" ቢላቸው "የእግዚአብሔር
ነውና ያገልግላችሁ" ብለው መለሱት:: መገፋቱን የተመለከተ
#አባ_ጊዮርጊስ #እመቤታታችንን ከልቡ ይወዳት ነበረና
ይማጸናት ገባ::

+ቀን ቀን ገዳሙን ሲረዳ: እሕል ሲፈጭና ሲከካ: ላቡንም
ሲያፈስ ውሎ ሌሊት ደግሞ ሲጸልይ ያነጋ ነበር:: ድንግል
እመቤታችን ጸሎቱን ሰምታለችና #ቅዱስ_ዑራኤልን አስከትላ
መጣችለት:: በንጹሐት እጆቿ ባርካው ምሥጢርንም ነገረችው::
"ወነገረቶ ሐምስተ ቃላተ" እንዲል:: ጽዋዐ ልቡናን አጠጥታው
ተሠወረችው::

+ከዚህች ሰዓት ጀምሮ አባ ጊዮርጊስ ፍጹም ተለወጠ:: በጽድቁ
ላይ የሊቅነትን ካባ ደረበ:: ቅዱሳት መጻሕፍትን ይተነትናቸው:
መናፍቃንንም ምላሽ ያሳጣቸው ገባ:: የተረጐማቸውና
ያተታቸውን ሳይጨምር 41 ድርሰቶችን ደረሰ:: (መጽሐፈ
ሰዓታት: መጽሐፈ ምሥጢር: አርጋኖን: ኆኅተ ብርሃን: ውዳሴ
መስቀል: ወዘተ . . . የእርሱ ድርሰቶች ነበሩ)

+ስለ ሃይማኖትም ጠበቃ ነበር:: ስለ ቅድስናውና ውለታው የኢ/
ኦ/ተ/ቤ እንዲህ ትጠራዋለች:-
1. #ሊቀ_ሊቃውንት
2. #በላዔ_መጻሕፍት
3. #ዓምደ_ሃይማኖት
4. #ዳግማዊ_ቄርሎስ
5. #ጠቢብ_ወማዕምር

+ጻድቁ ሊቅ በተወለደ በ60 ዓመቱ በ1418 ዓ/ም በዚህች ቀን
ዐርፏል:: አባ ጊዮርጊስ የተወለደውም ያረፈውም ሐምሌ 7 ቀን
ነው::

=>የሥላሴ ቸርነት: የአብርሃም ደግነት: የአበው አባ ጊዮርጊስና
አባ ሲኖዳ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን::

=>ሐምሌ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱሳን አብርሃምና ሣራ (ሥላሴን ያስተናገዱ)
2.ብሥራተ ልደተ ይስሐቅ
3.ታላቁ አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን ሁሉ አለቃ)
4.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (ሊቀ ሊቃውንት: ኢትዮዽያዊ
የሃይማኖት ምሰሶ)
5.ቅዱስ አግናጥዮስ ዘአንጾኪያ (ምጥው ለአንበሳ)
6.አባ መቃቢስ
7.አባ አግራጥስ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
2.አባ ባውላ ገዳማዊ
3.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ

=>+"+ እግዚአብሔርም ለአብርሃም ተስፋ በሰጠው ጊዜ:-
'በእውነት እየባረክሁ እባርክሃለሁ:: እያበዛሁም አበዛሃለሁ'
ብሎ ከእርሱ በሚበልጥ በማንም ሊምል ስላልቻለ በራሱ ማለ::
እንዲሁም እርሱ ከታገሠ በሁዋላ ተስፋውን አገኘ:: +"+ (ዕብ.
6:13)
=>+"+ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ: የእግዚአብሔርም ፍቅር:
የመንፈስ ቅዱስም ሕብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን:: አሜን:: +"+
(ቆሮ. 13:14)

+++ ስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር +++
©ዝክረ ቅዱሳን


•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮

    የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን 
              ➡️      መሰረተ ሚዲያ

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
     ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ


👇👇👇👇👇👇👇👇

የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═
/channel/Meseretemedia

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

በቤትህ ያለው ዳቦ ለተራበው ሰው የሚውል(ንብረቱ) ነው፥ በልብስ ማስቀመጫህ ውስጥ ያለው የማትጠቀመው ኮት የችግረኛው ገንዘቡ ነው፥ በጫማ ማስቀመጫህ ውስጥ አልፈልገውም ብለህ ሊበላሽብህ የሆነው ጫማ የደሃው ጫማ (ጫማ ለሌለው ገንዘቡ) ነው ፥ ያከማቸኸው ገንዘብ ለድሃው የሚገባው ነው....

ዛፍ በፍሬው ይታወቃል፥ ሰውም በድርጊቱ፡፡ መልካም ስራ መቼም አይጠፋም፡፡ መልካም እርዳታን የሚዘራ፥ ወዳጅነትን ያጭዳል፡፡ ደግነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል፡፡

"ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ብቻ የለብንም፥ ነገር ግን ካነበብነው ተምረን ማደግ አለብን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም የማይጠቅም ነገር እንዳልተጻፈ ተገንዘብ፡፡

አሁንም ለጥንካሬ፣ ለመታገስ፣ ለመዳን፣ ለመለወጥ ጊዜ አለህ! ተኝተሃልን? ንቃ! ኃጢአት ሰርተሃልን? እንግዲያውስ  መስራቱን አቁም፡፡

#ቅዱስ_ባስልዮስ_ዘቂሳርያ

/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

" ራስህን ከቤተክርስቲያን ፈፅሞ አትለይ፤ ቤተክርስቲያን ተስፋህ ናት፤ ቤተክርስቲያን ደኅንነትህ ናት፤ ቤተክርስቲያን መጠጊያህ ናት።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

" ወደ ተቀደሰ ተራራዬ አመጣቸዋለሁ፥ በጸሎቴም ቤት ደስ አሰኛቸዋለሁ፤ ቤቴ ለአሕዛብ ሁሉ የሚሆን የጸሎት ቤት ይባላልና..."
ኢሳ. ፶፮፥፯ /56፥7/

❤ ቤተክርስቲያን ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኝበት የጸሎት ቤት ነው። በእዚያም እርሱ አለና።

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ጊዜ የለኝም መምህራኑ ገዳማውያኑ ያንብቡ !!!

❖ "ሰው ወደሚበዛበትና የዚህን ዓለም ፍርድ ወደሚሰጡ ቦታዎች አለመኼድ ስለማልችል፣ የምመራው ትልቅ የንግድ ድርጅት ስላለኝ፣ ሥራዬ ጥበበ እድ ስለሆነ፣ ጊዜ ስለሌለኝ፣ ትዳር ስላለኝ፣ ልጆችን ስለማሳድግ፣ የቤተሰብ አስተዳዳሪ ስለሆንኩ፣ እኔ የዓለም ሰው ስለሆንኩ መጻሕፍትን ማንበብ አይጠቅመኝም፤ "መጻሕፍትን ማንበብ በገዳም ለሚኖሩ መነኮሳት ነው" ብለህ አትንገረኝ።

❖ "አንተ ሰው! ምን ማለትህ ነው?" "ብዙ የዚህ ዓለም አሳብ ስላለብኝ መጻሕፍት ማንበብ ለእኔ አይደለም" ትለኛለህን? እንዲያውም ልንገርህ! አንተም ስማኝ! ከእነዚያ መነኮሳት ይልቅ ማንበብ ያለብህ አንተ ነህ፤ መጻሕፍትን በብዛት ማንበብ  የሚገባቸው ብዙ የዓለም አሳብ ያላቸው ሰዎች እንጂ በምግባር በትሩፉት የተጠመዱ መነኮሳት አይደሉምና::

📌 ምንጭ
✍️ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (ገብረ እግዚአብሔር ኪደ)
📚"የክርስቲያን መከራ"



═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮

    የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን 
              ➡️      መሰረተ ሚዲያ

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
     ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ


👇👇👇👇👇👇👇👇

የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═
/channel/Meseretemedia

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ሰው ሃይማኖቱን መጠበቅ የሚችለው ስለ ሃይማኖቱ አምስት ነገሮች ሲያውቅ ነው ፡፡

💠 1/ ምን እንደሚያምን
💠 2/ ለምን እንደሚያምን
💠 3/ ያመነውን እንዴት መፈጸም እንዳለበት
💠 4/ ያመነውን እንዴት ለሌሎች ማሳወቅ እንዳለበት
💠 5/ እምነቱን የሚፈተን ነገር ሲመጣ እንዴት መከላከል እንዳለበት

ማወቅ አለበት

ሃይማኖታችንን ለመጠበቅና በሃይማኖታችን ጸንተን ለመኖር መንፈሳዊ ትምህርትእንማር


መሰረተ ሚዲያ


የቴሌግራም አድራሻ/channel/Meseretemedia

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

+• የእንባችን ዋጋ ምን ያህል ነው? •+
               አንብቡት🙏

🥀አባ አንቶኒ ኮኒያሪስ የተሰኙ የግሪክ ኦርቶዶክስ ካህን በጻፉት "ፊሎካሊያ: የኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነት ቅዱስ መጽሐፍ" (Philokalia: The Bible of Orthodox Spirituality) በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ ለማስተማሪያነት ያሰፈሩት እንዲህ የሚል አንድ ጥንታዊ አፈታሪክ አለ:-

🥀እግዚአብሔር ከዕለታት በአንዱ ቀን ቅዱሳን መላእክቱን "ወደ ምድር ወርዳችሁ ከሁሉ ይልቅ እጅግ ብርቅዬ የሆነውን ነገር ይዛችሁልኝ ኑ" ብሎ ያዛቸዋል::

🥀አንድ መልአክ ሌላ ሰው ለማዳን ብሎ ራሱን መስዋእት ያድረገን ሰው የደም ጠብታን ይዞ ተመለሰ:: እግዚአብሔርም "መልአክ ሆይ ፥ በእርግጥ ይህ በእኔ ዓይን እጅግ የተወደደ ነው:: በዓለም ያለው እጅግ ብርቅዬ ነገር ግን አይደለም::" አለው::

🥀ሌላኛው መልአክ ደግሞ ሌሎችን ስታስታምም በያዛት በሽታ ምክንያት ያረፈችን የአንዲት ነርስ የመጨረሻ እስትንፋስ ይዞ መጣ:: እግዚአብሔርም "መልአክ ሆይ ፥ በእርግጥ ስለሌሎች የሚከፈል መስዋእትነት በእኔ ዓይን እጅግ ታላቅ ዋጋ አለው:: ሆኖም ግን በዓለም ያለው እጅግ ብርቅዬው ነገር ይህ አይደለም" አለው::

🥀በመጨረሻም አንድ መልአክ ንስሃ ገብቶ ወደ እግዚአብሔር የተመለሰን ኃጢአተኛ አንድ ዘለላ እንባ ይዞ መጣ:: እግዚአብሔርም "መልአክ ሆይ ፥ በዓለም ላይ ያለውን እጅግ ብርቅዬ ነገር አመጣህ - ይኸውም የገነትን በር የሚከፍት የንስሃ እንባ ነው!" በማለት ተናገረ::

🥀የጌታ ቃል “እንዲሁ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል።"(ሉቃ 15:10) ብሎ ስለ ንስሃ ዋጋ ይነግረናል:: ንስሃ ደግሞ በተሰበረ ልብና በእንባ ሲሆን ይሰምራልና ፥ በዚህ መንገድ ሆነን ንስሃ ለመግባት እንፋጠን፤ እርሱ ይቅር ይለን ዘንድ ሁሌም ዝግጁ ነውና::

🥀   አምላከ ቅዱሳን ለንስኃ የተዘጋጀ ልብ ይፍጠርልን  
ለንስኃ ሞት ያብቃን🙏 
           ተቀላቀሉ ቴሌግራም
/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ (በዓለ ሃምሳ )
በሰላም አደረሳችሁ ።


በዓለ ጰራቅሊጦስ ወይም በዓለ ጰንጠቆስጤ ከዘጠኙ የጌታችን ዐበይት በዓላት አንዱ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደበትን ቀን የምናስብበት በዓል ነው።

ጰራቅሊጦስ፡- ቃሉ የግሪክ ነው። “ጰራቅሊጦስ” የሚለው ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ ለኾነው ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስሙ ሲኾን፣ ትርጕሙም

👉መጽንኢ (በእምነት የሚያጸና)፣
❖መንጽሒ (ከኃጢአት የሚያነጻ)፣
❖ናዛዚ (ያዘኑትን የሚያረጋጋ)፣
❖መስተፍስሒ (የተጨነቁትን የሚያስደስት)፣
❖ከሣቲ (ምስጢርን የሚገልጽ) ማለት ነው

ከበዓሉ በረከት ረድኤት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ያሳትፈን።

/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

*በዓለ ጰራቅሊጦስ*

❖ጰንጠቆስጤ ቃሉ የግሪክ ቃል ነው፡፡ ትርጓሜውም ሃምሳኛ ማለት ነው፡፡

❖ ጰራቅሊጦስ ማለትም የሚረዳ፤ የሚያጽናና ማለት ነው፡፡
❖በብሉይ ኪዳን በዓላት ለምሳሌ የአይሁድ የፋሲካ በዓላቸውን ካከበሩ በኋላ አምሳውን ቀን የነጻነት በዓላቸው አድርገው ከሰነበቱ በኋላ ኃምሳኛውን ቀን በተለየ ሁኔታ በዓለ ሰዊት ብለው ያከብራሉ፡፡

❖ በእነርሱ ሀገር ከመጋቢት እስከ ግንቦት ያለው ወቅት ጸደይ /የእሸት ወራት/ ነው፡፡
ጌታችን እርሱ ባወቀ ይህን በዓል /በዓለ ሠዊትን/ ለሐዲስ ኪዳን በዓላችን ፪ ጥቅሞችን እንዲያስገኝ አድርጓል””

✢ የመጀመሪያ ለበዐለ ጰራቅሊጦስ
ምሳሌ መንገድ ጠራጊ፤ መተርጐሚያ ፤ ማሳመኛ መሆኑ ነው፡፡

ሁለተኛው በዓሉ እንዲከበር ምክንያት የሆነው ርደተ-መንፈስ ቅዱስ /የመንፈስ ቅዱስ መውረድ/ ጌታችን በዐረገ በዐሥረኛው ቀን በተነሳ በአምሳኛው ቀን በወረደበት ዕለት በዝርዎት የነበሩ አይሁድ ሁሉ ለበዓለ ፋሲካና ከዚሁ ተያይዞ ለሚከበረው ለበዓለ ሠዊት እንደተሰበሰቡ የተፈጸመ መሆኑ ነው፡፡

❖ ሰዎቹም በጸሎት የተጉ መሆናቸውና ከእግዚአብሔር የሆነውን ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸው በክርስቶስ አምላክነት አምነው የቤተክርስቲያን መሠረት እንዲጣል ምክንያት ሆኖአል፡፡ ማስረጃ፡- ሐዋ.፪÷፭-፮ “ከሰማይም በታች ካሉ ሕዝብ ሁሉ በጸሎት የተጉ አይሁድ በኢየሩሳሌም ይኖሩ ነበር፤ ይህም ድምጽ በሆነ ጊዜ ሕዝብ ሁሉ ተሰበሰቡ ….” ሕዝቡም እንደተጻፈውም ነገሩ ከእግዚአብሔር መሆኑን ለመመርመር ጊዜ አልፈጀባቸውም፡፡ሐዋ.፪÷፯-፲፩ “ ተገርመውም ተደንቀውም እንዲህ አሉ፡- ❖እነሆ እነዚህ የሚናገሩት ሁሉ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን?
❖እኛም እያንዳንዳችን የተወለድንበትን የገዛ ቋንቋችንን እንዴት እንሰማለን?... እግዚአብሔርን ታላቅ ሥራ በልሳኖቻችን ሲናገሩ እንሰማቸዋለን፡፡”

❖ተገርመው ተደንቀውም አልቀሩም -
👉አለ -የቅ/ጴጥሮስን ስብከትሰምተው አምነው የተጠመቁ ብዙዎች ናቸውና ይህንን ሲያጠይቅ ነው፡፡ ሐዋ.፪÷፵፩-፵፪ “ ቃሉንም የተቀበሉ ተጠመቁ በዚያም ቀን ሦስት ሺህ የሚያህል ነፍስ ተጨመሩ፤በሐዋርያትም ትምህርትና በኀበራት እንጀራውንም በመቁረስ በጸሎትም ይተጉ ነበር”

ይህዊ ዕለት፤ የቤተክርስቲያን የልደት ቀን የምትባለውም ለዚህ ነው፡፡
መንፈስ ቅዱስ የወረደበት፤ በሦስት ሺህ ✢ሰዎች ጥምቀት መስፋፋት የጀመረችበት፤ ሐዋርያትም ፍሩሃኑ ጥቡዓን /ደፋሮች/ ሆነው፤ በዕውቀት በልጽገው፣በአእምሮ ታድሰው ዓለሙን ለመለወጥ ኃይል ያገኙባት ዕለት ናት፡፡

❖ቅ/ዮሐንስ አፈወርቅ እነዚህን ነገሮች አስታውጦ ሲናገር “መንፈስ ቅዱስ ባይወርድላት ኑሮ የቤተክርስቲያን ሕልውና ከስሞኖ ቀጭጮ ይቀር ነበር፤ ስለዚህም በሚገባ አነጋገር ይህች ዕለት የቤተክርስቲያን የልደት ቀን ትባላለች” ብሎአል፡፡

👉ከዚህም የተነሳ ሌሎች ሊቃውንትም ዕለቲቱን የበዓላት ሁሉ እመቤት እንደሚሏት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ገልጸውታል፡፡
በዓሉ ጌታችን በመዋዕለ ሥጋዌው ለቤተክርስቲያን “ ከእናንተ ጋር ስኖር ይህን ነግሬአችኋለሁ፤ እኮ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል፤ እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል” እና “ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሏቸዋል፤በስሜ አጋንንትን ያወጣኑ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤…” ሲል የገባው ኪዳን የተፈጸመበት ተደርጎም ይከበራል፡፡

👉 በእኛ በቤተክርስቲያን ሊቃውንት በፍትሐነገሥት የገለጹትን በማሰብ ለመንፈሳዊ ሐሴት በቃለ -እግዚአብሔር ይከበራል ፡፡ ፍትሐ ነገሥታችን “ ትንሣኤን በአከበራችሁ በአምሳኛው ቀን ዕርገቱን በአከበራችሁ በዐሥረኛው ቀን በዓለ ጰራቅሊጦስን አክብሩ በዓል ይሁንላችሁ" እንዳለ ቤ/ክ ታከብራለች!



ቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ
   ╭═
/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

‹‹ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ››

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

†††እንኳን ለቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ : ቅዱስ ዋርስኖፋ እና አባ ዮሐንስ ዘጐንድ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። †††

†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

††† ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ †††

††† ቅዱሳን ሐዋርያት አባቶቻችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በተከተሉበት ሰዓት እድሜአቸው በ3 ደረጃ የተከፈለ እንደ ነበር የቤተ ክርስቲያን ትውፊት ያሳያል:: እንደ ዮሐንስ ወንጌላዊ ያሉት በ20ዎቹ ውስጥ : ቅዱስ ታዴዎስን የመሰሉት ደግሞ በ30ና በ40ዎቹ ውስጥ የነበሩ ሲሆን እነ ቅዱስ ዼጥሮስ ደግሞ በ50ዎቹ ውስጥ የሚገኙ ነበሩ::

ደቀ መዛሙርቱ ከወጣቶችም : ከጐልማሶችም : ከአረጋውያንም የተዋቀሩ ነበሩ ማለት ነው:: ቅዱስ ታዴዎስ በቀደመ ስሙ ልብድዮስ ይባል የነበረ ሲሆን በአንዳንድ መጻሕፍት ውስጥ (በተለይ በምሥራቅ ኦርቶዶክሶች) ስምዖን እና ይሁዳ እየተባለም ተጠርቷል::

ቅዱሱ ጌታችን ተከትሎ : ከ12ቱ አንዱ ሆኖ በፈጣሪው ተመርጦ : 3 ዓመት ከ3 ወር ከጌታ እግር ተምሮ : በዕርገቱ ተባርኮ : በበዓለ ሃምሳም 71 ልሳናትን ተቀብሎ : ሐዋርያት ዕጣ ሲጣጣሉ የበኩሉን አሕጉረ ስብከት ተካፍሎ ዓለምን ዙሯል::

ቅዱስ ታዴዎስ እስከ እርጅናው ድረስ ለወንጌል ሲተጋ ኑሯል:: ጌታችንም በየጊዜው በአካል እየተገለጸ አጽናንቶታል:: ከብዙ የድካምና የመከራ ዘመናት በሁዋላም ሐምሌ 2 ቀን ዐርፏል::

ቅዱሱ ሐዋርያ ያረፈው ሶርያ ውስጥ ሲሆን ከ250 ዓመታት በሁዋላ ቤተ ክርስቲያኑ ታንጾለት በዚህች ቀን ወደ ቁስጥንጥንያ ፈልሷል:: ይህንን ያደረገው ደግሞ ታላቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ነው:: ከሐዋርያው ዘንድም ብዙ ተአምራት ተደርገዋል::

††† ቅዱስ ዋርስኖፋ ሰማዕት †††

††† ቅዱሱ በትውልድ ግብፃዊ ሲሆን ገና ከልጅነቱ ጣዕመ ክርስትና የገባው ነበር:: መጻሕፍትን በማንበብ: ክርስትናንም በመለማመድ ስላደገ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት የመወደድ ሞገስ ነበረው:: በእድሜው እየጐለመሰ ሲሔድ በተጋድሎውም እየበረታ ሔደ::

በወቅቱ እርሱ የነበረባት ሃገር ዻዻስ በማረፉ ሊቃውንቱና ሕዝቡ ተሰብስበው አምላክን ጠየቁ:: እንደሚገባም መከሩ:: በደንብ አስተውለዋልና እንደ አንድ ልብ መካሪ: እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሁነው ሁሉም ቅዱስ ዋርስኖፋን መረጡ::

ዛሬን አያድርገውና በአባቶቻችን ዘመን ሕዝቡም ሆነ ሊቃውንቱ መሪ መምረጥን ያውቁ ነበር:: ተመራጮቹ ደግሞ እንኩዋን እንደ ዘመናችን "ሹሙኝ : ምረጡኝ" ሊሉ በአካባቢውም አይገኙም ነበር::

ቅዱስ ዋርስኖፋ ለዽዽስና እንደ መረጡት ሲያውቅ "ጐየ" እንዲል መጽሐፍ: ጨርቄን ማቄን ሳይል በሌሊት ጠፍቶ በርሃ ገባ:: (እንዲህ ነበሩ አበው) በገባበት በርሃ ውስጥ በዓት ሠርቶ በጾም: በጸሎትና በስግደት በርትቶ ዓመታትን አሳለፈ:: እርሱ በበርሃ እያለ ዘመነ ሰማዕታት ጀምሮ ብዙ ክርስቲያኖች አልቀው ነበር::

እርሱ ግን ከዓለም ርቁዋልና ይህንን አላወቀም ነበር:: አንድ ቀን መልአከ እግዚአብሔር መጥቶ "አንተ በስሙ ደማቸውን ለሚያፈሱ አክሊላት እየታደለ : ሰማያዊ ርስትም እየተካፈለ ነውኮ! አልሰማህም?" አለው::

ቅዱስ ዋርስኖፋም "ለካም እንዲህ ያለ ክብር አምልጦኛል" ብሎ: በርሃውን ትቶ ወደ ከተማ ወጣ:: መልአኩ እንዳለውም ክርስቲያኖች ሲሰቃዩ ደረሰ:: ቅዱሱም ሳያመነታ ስመ ክርስቶስን ሰብኮ: ብዙ ተሰቃይቶ በዚህች ቀን አክሊለ ሰማዕትን በአክሊለ ጻድቃን ላይ ደርቧል::

††† እጨጌ አባ ዮሐንስ ዘጐንድ †††

††† ጻድቁ ተወልደው ያደጉት በኢየሩሳሌም ሲሆን ነገዳቸውም እሥራኤላዊ ነው:: ነገር ግን ተጋድሏቸውን የፈጸሙት በሃገራችን ኢትዮዽያ ውስጥ ነው:: እጨጌ አባ ዮሐንስ ከአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቀጥሎ ባለ ረዥም እድሜ ጻድቅ መሆናቸው ይነገራል::

አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ያረፉት በ562 ዓመታቸው ሲሆን እጨጌ አባ ዮሐንስ ደግሞ በ500 ዓመታቸው ነው:: የሚገርመው ጻድቁ የታላላቁ ጻድቃን ገብረ መንፈስ ቅዱስ : ተክለ ሃይማኖት: ሳሙኤል: ዜና ማርቆስ እና ሌሎችም ባልንጀራ ነበሩ::

በዛ ዘመን ዘረኝነት በቅዱሳኑ ዘንድ አልነበረምና ነጭ ሆነ ጥቁር : ከየትም ይምጣ የሰው ልጅ መሆኑ ብቻ በቂ ነበር:: እጨጌ አባ ዮሐንስ በሃገራችን 5 በዓቶች የነበሯቸው ሲሆን በአንድ በዓት የሚኖሩት ለ50 ዓመት ነበር::

በዚህም በኢየሩሳሌም ለ50 ዓመት : በኢትዮዽያ ደግሞ ለ450 ዓመታት ኑረዋል:: ከበዓቶቻቸው አንዱ ደብረ ሊባኖስ ሲሆን በገዳሙ ለ50 ዓመታት አበ ምኔት(እጨጌ) ሆነው አገልግለዋል:: "እጨጌ" የሚባሉትም በዚህ ምክንያት ነው::

ጻድቁ የመጨረሻ ዘመናቸውን ያሳለፉት በጐንድ (ጉንድ) ተክለ ሃይማኖት ገዳም ነው:: ገዳሙ የሚገኘው በሰሜን ጐንደር ዞን : በለሳ ወረዳ ውስጥ ሲሆን የመሠረቱትም ራሳቸው ናቸው:: ነገር ግን በራሳቸው እንዲጠራ አልፈለጉምና ገዳሙ የሚጠራው በወዳጃቸው በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ስም ነው::

ጐንድ እኛ ኃጥአን ሳይገባን ያየነው ገዳም ነው:: ዛሬም ድረስ ድንቅ የሆኑ አበው የሚኖሩበት : ተአምራትም የማይቋረጥበት : ፈዋሽ ጠበል ያለው ደግ ገዳም ነው:: ጻድቁ እጨጌ አባ ዮሐንስ ግን አስታዋሽ አጥተው እየተዘነጉ ካሉ ቅዱሳን አንዱ ናቸው:: ምንም ዛሬ አጽማቸው ፈልሶ ወደ ደቡብ ኢትዮዽያ አካባቢ ቢሔድም እርሳቸው በ500 ዓመታቸው ያረፉት በዚህ ገዳም ውስጥ ነው::

††† እግዚአብሔር ከሐዋርያው : ከሰማዕቱና ከጻድቁ ክብርን : በረከትን ያሳትፈን::

††† ሐምሌ 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ (ፍልሠቱ)
2.ቅዱስ ዋርስኖፋ ሰማዕት
3.እጨጌ አባ ዮሐንስ (ዘጐንድ)

††† ወርኀዊ በዓላት
1.የፈጣሪያችንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት
2.ቅድስት አርሴማ ድንግል
3.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት
4.ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
5.ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት
6.ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ (ጻድቅና ሰማዕት)

††† "ለመንጋው ምሳሌ ሁኑ እንጂ ማሕበሮቻችሁን በኃይል አትግዙ:: የእረኞችም አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብርን አክሊል ትቀበላላችሁ:: እንዲሁም ጐበዞች ሆይ! ለሽማግሌዎች ተገዙ:: ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ:: እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና:: ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል::" †††
(1ዼጥ. 5:3)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

🌧☔️
በአንድ ሀገር ዝናብ ጠፋና ህዝቡ ሁሉ ተጨነቀ በመጨረሻም ምህላ እንዲደረግ ተወሰነ።
ህዝቡ ሁሉ ወደ ቤተክርስትያን ጉዞ ጀመረ አንዲት ህፃን ግን በጉዞው መሃል ዣንጥላ ይዛ ነበር። ለምን እንደያዘች ስትጠየቅ ወደ ቤተክርስትያን እምንሄደው ዝናብ እንዲዘንብ ለመለመን አይደለም? ታዲያ ስንመለስ በምን እንጠለላለን ስትል መለሰች።
ስለዚህች ህፃን እምነት በዛች ቀን ዝናብ ዘነበ ህዝቡ ሁሉ በዝናብ ሲደበደብ እርሷ ግን በያዘችው ዣንጥላ ተጠልላ ነበር።

ብዙዎቻችን የዚችን ህፃን ያህል ቅንጣት ታህል እምነት የለንም፣ ብዙ ነገር እንጠይቃለን የጠየቅነው ነገር እንደሚሰጠን ግን እርግጠኛ ሆነንና ተዘጋጅተን አንጠብቅም።

ከአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ የተወሰደ

አምላከ ህጻናት ክብር ምስጋና ይድረሰው!!

ተወዳጆች ሆይ እኛስ በእምነታችን ምን ትሩፋት አገኘን?

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል አሁናዊ ሥርዓተ ዋዜማ በዚህ መልኩ ቀጥሏል

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ቅዱሳንን ማክበር ጥቅሙ ለማን ነው?

ፀሐይን የሚያይ ሰው የፀሐይቱን ብርሃን ይበልጥ ብሩህ እንዲኾን
አያደርገውም፤ የገዛ ራሱን የማየት ዓቅሙን እንዲጨምር ያደርጋል
እንጂ፡፡ ልክ እንደዚሁ፡ ሰማዕታትን (ቅዱሳንን) የሚያከብር ሰውም
ሰማዕታቱን ይበልጥ እንዲከበሩ አያደርጋቸውም፤ እርሱ
ከሰማዕታቱ (ከቅዱሳኑ) የሚቀድስ በረከትን ይቀበላል እንጂ፡፡

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ሺ_ዓመት_አይኖር

🥀ብዙ ጊዜ ለስንፍናችን ምክንያት ወይም ተስፋ ለመቁረጥ ሰበብ ከሚሆኑን ነግሮች አንዱ "ሺ ዓመት አይኖር" የሚለው አባባል ነው በእርግጥ በምድር ሺ ዓመት መኖር የቻለ የለም ረጅም ዓመት እንደኖረ የሚነገርለት ማቱሳላ እንኳን ሺ ዓመት አልኖረም ወዳጄ በተለይ እኛ ባለንበት በዚህ ዘመን ደግሞ እንኳን ሺ ዓመት ሊኖር ቀርቶ መቶ የሞላ እንኳን ቢገኝ የሚድያ የአንድ ወቅት የዜና ሽፋን መሆኑ የማይቀር ነው ስለዚህ ወደ ዘመናችን አባባሉን ማምጣት ከፈለግን መቶ ዓመት አይኖር በሚል ልንቀይረው ያስፈልጋል።

🥀የሚያሳዝነው ሺ ዓመት አይኖር የምንለው ለመዝናናት ለመጨፈር ራስን ለመርሳት ፈቃደ ሥጋን እንደ ልብ ለመፈጸም ብቻ እንጂ ለመንፈሳዊ ሕይወት ለመሰናዳት አይደለም "አንቂ" የሚባሉ አካላት የዕድሜህን አጫርነት የሚነግሩህ ከሞት በኋላ ላለው ረጅሙ ዕድሜ በዚህች በአጭሯ የምድር ዕድሜህ በጎ ሰርተህ እንድታልፍ ሳይሆን እንዳትጨናነቅ ፈታ ብለህ(በእነርሱ አማርኛ) እንድትኖር ለማስታወስ ብቻ ነው።

🥀ወዳጄ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ግን በምድር ስለምትኖርበት ዕድሜህ ሲነግርህ ቢበዛ(ቢበረታ) ሰማንያ ይልሃል ሺ ዓመት አይኖር ሲሉህ ቢበዛ ሰማንያ እርሱም በተገኘ በላቸው ታድያ በምድር የምትኖርበት ዕድሜህ ጥቂት ከሆነ ከዚያ በኋላ በሞት ይህን ምድር ከተሰናበትክ ከሞት በኋላ የት ትሄድ ይሆን?? የዚህ ምድር ኑሮህ በሞት ከተቋጨ በኋላ ሞተህ የምትቀር መስሎ እንዳይሰማህ ከሞት በኋላ ሕይወት አለህ ያውም እንደሰው ኖረህ ከሞትክ የምትነሳው እንደ ሰው ሆነህ የምትኖረውን ሕይወት ለመድገም

🥀እንዳይመስልህ ከትንሣኤ በኋላ የምትኖረው እንደ መላእክት ነው “በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ”ማቴ 22፥30
ስለዚህ አስታውስ የምድር ኑሮህ ቢበዛ ሰማንያ ነው ያ ማለት ጥቂት ነው መጽሐፍ
እንደሚነግርህ

🥀ሕይወታችሁ ምንድር ነው ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና”
ያዕ 4፥14

🥀ስለዚህ በምድር የምትቆየው ጥቂት ጊዜ ነውና:-*
ዛሬ የንስሐ አባት ያዝ
ዛሬ ንስሐ ግባ
ዛሬ ከተጣላሃቸው ታረቅ
ዛሬ ያስቀየምካቸውን ይቅር በል
ዛሬሥጋ ወደሙን ተቀበል

ነገ ሳይሆን ዛሬ መልካም ነገሮችህን ሁሉ ጀምር ምክንያቱም
“እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።”
2ኛ ቆሮ 6፥2   የሞዐ
     Join  ቴሌግራም ቻናል

  አምላከ ቅዱሳን ለንስሐ የተዘጋጀ ልብ ያድለን
ለንስሃ ሞት ያብቃን🙏

❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮

    የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን 
              ➡️      መሰረተ ሚዲያ

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
     ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ


👇👇👇👇👇👇👇👇

የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═
/channel/Meseretemedia

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

📌 "አስታውስ"

➯ ደካማነትህን አስታውስ፣ ያንጊዜ በጣም ጠንቃቃ ትሆናለህ፣ ሊጎዱህ በሚችሉ በትምክህትና በውዳሴ ከንቱም አትሸነፍም፡፡

➯ የተሰጠህን በፍቅር የተሞላ የእግዚአብሔርን ቸርነት አስታውስ፣ ይህም በምስጋና የተሞላ ሕይወት እንድትመራ ያደርግሃል፤ በእግዚአብሔር ፍቅርና ሥራ ላይ ስትታመን ፍጹም የሆነ እምነት በልብህ እያደገ ይመጣል፤ ከእግዚአብሔር ጋር ያሳለፍከው ጊዜ ደግሞ በእምነት እንድትኖር ያበረታታሃል፡፡

➯ የሰዎችን ፍቅርና ካንተ ጋር ያሳለፉትን መልካም ጊዜ አስታውስ፤ የሰዎችን ቀናነት ትጠራጠር ዘንድ ወይም ያደረጉብህን ክፉ ነገር ታስብ ዘንድ ይገባሃልን? የቀደመ ፍቅራቸው ስለ እነርሱ ይማልዳል ያንተንም ቁጣ ያበርዳል፡፡

➯ ሞት እንዳለ አስታውስ፣ እንዲሁ በዓለም ያለ ፈተናም እንደሚያልፍ
✍️"ሁሉ ከንቱ ነው፣ ነፋስንም እንደመከተል ነው፡፡" ማለትን ትረዳለህ፡፡
📖መኬ 1፥14

➯ በእግዚአብሔርፊት መቆምህንና እርሱም እንደሚመለከትህ አስታውስ፣ ያኔ ኃጢአት አትሰራም እግዚአብሔርን ታየዋለህና፡፡

➯ ስለ አንተ የፈሰሰውን የክርስቶስን ክቡር ደም አስታውስ፤ በዚህም ሕይወትህ ያለውን ዋጋ በእርግጥ ታውቃለህ፤ በዓይኖችህ ፊት የከበረ ይሆናል፣ ስለዚህም በከንቱ በመኖር አታጠፋውም፣
✍️"በዋጋ ተገዝታችኋልና"  እንዲል ቅዱስ ጳውሎስ፡፡
📖1ኛ ቆሮ 6፥20

➯ በወላጆችህ እምነት በተጠመቅህባት ቦታ ለእግዚአብሔር የገባኸውን ቃል አስታውስ፤ ዲያብሎስን፣ ሥራዎቹን ሁሉ፣ ሐሳቦቹንና ጥበቡን፣ ኃይሉንም ትክድ ዘንድ፡፡

➯ በዚህ ዓለም እንግዳመሆንህንና ወደ ሰማያዊው ቤትህ እንደምትመለስ ዘወትር አስታውስ፤ ያን ጊዜ በዚህ ዓለምና በደስታው ተስፋ ማድረግን ትተዋለህ፡፡

➯ በጠባቡ በር መጓዝ ወደ መንግስተ ሰማያት እንደሚያደርስህ አስታውስ፤ ሰፊው ደጅ ፊት ለፊትህ ተከፍቶ ብታየው፣ አልፈኸው ሂድ ከእሱም ራቅ፣ በእርሱ የሄዱ እንዳሉ አልቀዋልና፤ ዘላለማዊው ሕይወትህን አስታውስ፣ ሁልጊዜም ስለዚህ ትጋ፡፡

➯ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህንና እርሱን መምሰል እንዳለብህ አስታውስ፤ እውነተኞች ከሆኑት ከእግዚአብሔር ልጆች ጋር አካሄድህን አስተካክል፡፡

➯ የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ መሆንህን አስታውስ፡፡ በውስጥህ ያለውንም ቅዱሱን የእግዚአብሔር መንፈስ አታሳዝን፤ ዘወትርም ቅዱስ የእግዚአብሔር ማደሪያ ሁን፡፡

📌 ምንጭ
✍️አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

አባታዊ ምክር

✥እኔ አባታችሁና መምህራችሁ ነኝ፥ ሁላችሁ ልጆቼ ትእዛዜን አዳምጡ፤ በቅድስት ሥላሴ ማመንን እንድትከተሉና እንድትጸኑ እነግራችኋለሁና፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ እርስ በእርሳችሁ በእውነተኛ ፍቅር ትዋደዱ ዘንድ እለምናችኋለሁ።

✥የተወደዳችሁ ልጆቼ በፍጹም ሰብአዊነት መልካምን አንድታደርጉ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ ዓለም እንድታታልላችሁ አትፍቀዱላት፤ በእግዚአብሔር አገልግሎት ዳተኞችና ቸልተኞች አትሁኑ ብዬ እለምናችኋለሁ።

✥የተወደዳችሁ ልጆቼ ፡ እና ያለ መታከት እንድትጸልዩ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ መለያየትን ከሚያመጣ ንግግር አንደበታችሁን እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።፡

✥የተወደዳችሁ ልጆቼ የተጠመቃችሁባትን ቅድስቲቱን ጥምቀት እንድትጠብቋት እለምናችኋለሁ፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ ሰውነታችሁን ለጌታ ንጹሕ አድርጋችሁ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።

✥ልጆቼ መብራታችሁ ፈጽሞ እንዲጠፋ አትፍቀዱ ይልቅስ ብርሃንን እንዲሰጥ እንድታደርጉት እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ እግዚአብሔር የሰጣችሁን ትእዛዝ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።

✥ልጆቼ  እግዚአብሔርን መፍራት ከእናንተ ጋር እንዲሆን እለምናችኋለሁ፤ የነገርኳችሁን ሁሉ ከጠበቃችሁ የእባቡንና የዘንዶውን ራስ ትቀጠቅጣላችሁ፤ ያልኋችሁን ካደረጋችሁ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ ብርሃናዊያን ኪሩቤል ይጠብቋችኋል፡፡

✥ ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ✥

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ሰኔ ፴ ልደቱ ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ

👉በንጉሥ ሄሮድስ ዘመን ዘካርያስ የሚባል ካህን ነበር፤ ሚስቱም ኤልሣቤጥ መካን ስለነበረች ልጅ አልነበራቸውም፤ እርሷም የመውለጇ ዘመን አልፎ ነበር፡፡ ሆኖም ሁለቱም በእግዚአብሔር የታመኑ ጻድቃን ነበሩ፡፡ 
👉ከዕለታት በአንድ ቀንም ካህኑ ዘካርያስ ወደ ቤተ መቅደስ ለአገልግሎት በገባበት ሰዓት በዕጣን መሠውያው በቀኝ በኩል የእግዚአብሔር መልአክ ቆሞ ታየው፤  እንዲህም አለው ‹‹ዘካርያስ ሆይ፥ አትፍራ፤ ጸሎትህ በእግዚአብሔር ፊት ተሰምቷልና፤ ሚስትህ ኤልሣቤጥም ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልድልሃለች፤ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ፡፡ ደስታና ሐሤትም ይሆንልሃል፤ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል፡፡ እርሱ በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ ይሆናልና የወይን ጠጅና የሚያሰክርም መጠጥ ሁሉ አይጠጣም፤ ከእናቱ ማሕፀን ጅምሮም መንፈስ ቅዱስ ይመላበታል፡፡ ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎቹን ወደ አምላካቸው ወደ እግዚአብሔር ይመልሳቸዋል፡፡ እርሱም የአባቶቻችን ልብ ወደ ልጆች፥ የከሓዲያንንም ዐሳብንም ለእግዚአብሔር የተዘጋጀ ያደርግ ዘንድ በኤልያስ መንፈስ ቅዱስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል፡፡›› ዘካርያስም መልአኩን እንዲህ አለው፤ ‹‹ይህ እንደሚሆን በምን አውቃለሁ? እነሆ፥ እኔ አርጅቻአለሁ፤ የሚስቴም ዘመንዋ አልፏል፡፡›› መልአኩም እንዲህ ብሎ መለሰለት፤ ‹‹እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፤ ይህንም እነግርህና አበሥርህ ዘንድ ወደ አንተ ተልኬአለሁ፡፡ አሁንም በጊዜው የሚሆነውንና የሚፈጸመውን ነገሬን አላመንኽኝምና ይህ እስኪሆን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ፤ መናገርም ይሳንሃል፡፡›› (ሉቃ.፩፥፲፫-፳)
👉ከዚህም በኋላ ሚስቱ ኤልሣቤጥ ፀነሰች፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ፀንሳ እናቱ ኤልሣቤጥን ለመጠየቅ በሄደችበት ወቅት በማሕፀኗ ውስጥ ሳለ ሕፃኑ ለእግዚአብሔር ልጅ ሰገደ፡፡ (ሉቃ.፩፥፴፱-፵፩)
👉ኤልሣቤጥ የመውለጃዋ ጊዜ በደረሰ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች፡፡ መውለዷን የሰሙ ዘመዶቿና ጎረቤቶቿም ደስ ተሰኙ፤ ልጁንም ስምንት ቀን በሞላው ጊዜ ሊገረዙት መጡ፤ ስሙንም በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ሊሰይሙት ወደዱ፤ ነገር ግን እናቱ ዮሐንስ ተብሎ መጠራት እንዳለበት ተናገረች፡፡ ሆኖም ግን ከዘመዶቿ መካከል ስሙ ዮሐንስ የሚባል ባለመኖሩ አባቱ እንዲወስን ካህኑ ዘካርያስን በጠየቁት ጊዜ መናገር የተሣነው ዲዳ ነበርና ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ሲጽፍ ሁሉም ተደነቁ፤ በዚያን ጊዜም የዘካርያስ አንደበት ተፈታ፤ እግዚአብሔርንም አመሰገነ፡፡
👉ካህኑ ዘካርያስም መንፈስ ቅዱስ በመላበት ጊዜ እንዲህ ብሎ ትንቢት መናገር ጀመረ፤  ‹‹ይቅር ያለን፥ ለወገኖቹም ድኅነትን ያደረገ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ይመስገን፤ ከባርያው ከዳዊት ቤት የምንድንበትን ቀንድ አስነሣልን፤ ከጥንት ጀምሮ በነበሩ በቅዱሳን በነቢያት አፍ እንደ ተናገረ፡፡ ከጠላቶቻችን እጅ፥ ከሚጠሉንም ሁሉ እጅ ያድነን ዘንድ፤ ቸርነቱን  ከአባቶቻችን ጋር ያደርግ ዘንድ፤ ቅዱስ ኪዳኑንም ያስብ ዘንድ፤ ለአባታችን ለአብርሃም የማለውን መሐላ ያስብ ዘንድ፤ ከጠላቶቻችን እጅ ያድነን ዘንድ ያለ ፍርሃት፥ በቅድስናና በጽድቅ በፊቱ በዘመናችን ሁሉ እንድናመልከው ይሰጠን ዘንድ፤ አንተም ሕፃን፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፡፡ መንገዱንም ትጠርግ ዘንድ በፊቱ ትሄዳለህና፡፡ ኃጢአታቸው ይሰረይላቸው ዘንድ መድኃኒታቸውን እንዲያውቁ ለአሕዛብ ትሰጣቸው ዘንድ፤ ከአርያም በጎበኘን በአምላካችን በይቅርታውና በቸርነቱ፤ በጨለማና በሞት ጥላ ለነበሩት ብርሃኑን ያሳያቸው ዘንድ፥ እግሮቻቸውንም ወደ ሰላም ጎዳና ያቀና ዘንድ ወጣ፡፡›› ሉቃ.፩፥፷፰-፸፱
የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አማላጅነት እና ተራዳኢነት አይለየን፤ ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን!


/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

                    ቀናችንን በጸሎት እንጀምር

    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
ማንም ኋለኛ ነኝ ብሎ ተስፋ አይቁረጥ
    ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥

❖ ከመጀመሪያ ጀምሮ መልካም ነገርን መምረጥ መልካም ነው፤ በመልካምነት አለመቀጠል ግን ብዙ ወቀሳን ያመጣል፤ የብዙ ሰዎች ክፉ መኾን በዚሁ የሚመደብ ነው ፤ ብዙዎች ሕይወታቸውን በመልካም ጀምረው በኋላ ግን በክፋት መርዝ ተጠምቀው ሲሰክሩ ተመልክቻለሁ፡፡

❖ እናንተ ግን እንዲህ አትሁኑ ምንም እንኳን አሁን ወደ ክፋት ጥልቅ ወርዳችሁ ቢኾንም

✍️"ከዚሁ ተመልሰን መውጣት አይቻለንም ፤ መለወጥም አይኾንልንም" በማለት ተስፋ የምትቆርጡ አትኹኑ፤ እናንተ ስትፈቅዱ እግዚአብሔርም ሲረዳችሁ ከክፋት ዐዘቅት መውጣት በእጅጉ ቀላል ነውና፡፡

❖ ከኹሉም በላይ አመንዝራ ተብላ በከተማው ትታወቅ የነበረችውን ሴት በመልካምነቷ እንዴት እንደምትወደስ አልሰማችሁምን? እየነገርኳችሁ ያለሁት በወንጌለ ዮሐንስ ስለተጠቀሰችው ሴት አይደለም ፤ በእኛ ዘመን ስላለችውና ፍኒሳ ከተባለችው ክፉ ከተማ ስለተገኘችው ሴት እንጂ ይህቺ ሴት አስቀድማ በመካከላችን በአመንዝራነቷ ትታወቅ ነበር፤ በክብር ቦታ ሁሉ የመጀመሪያውን ስፍራ የምትይዝ ሴት ነበረች፤ ስሟ በሀገሩ ሁሉ የገነነ ነበር በእኛ ዘንድ ብቻ ሳይሆን በሲልስያና በቀጰዶቅያም የታወቀ ነበር፡፡

❖ ይህቺ ሴት ብዙ ከተሞችን አፍርሳለች ፤ የብዙ ወላጅ አልባ ሕፃናትን ንብረት በልታለች፤ ብዙዎች "መተተኛ ናት" ይሏታል ውበቷን ብቻ ሳይኾን መድኃኒትም ጭምር ትጠቀም ነበርና፡፡

❖ ከዚሁ የተነሣ በአንዱ ቀን የንግሥቲቱን ልጅ እስከ ማማለል ደርሳለች፤ ጭካኔዋ ክፉ የክፉ ክፉ ነበር፤ ከዕለታት በአንዲቱ ቀን ግን ማመን እስኪያቅተኝ ድረስ ተለውጣ አየኋት፤ ራሷን በእግዚአብሔር የጸጋው ዙፋን ፊት ድፍት ብላ ስታለቅስ አየኋት አሁን የቀድሞ ክፉ ሥራዎቿ ኹሉ ርግፍ አድርጋ ትታለች በእርሷ ላይ ከነበሩት አጋንንት ጭፍራ ተፋትታ የክርስቶስ ሙሽሪት ኾናለች፡፡

❖ በእውነት ከእርሷ የሚከፋ ሰው በዓይኔ አላየሁም አሁን ግን ራሷን ከእንደዚህ ዓይነቱ ክፉ ሥራ ከልክላለች፤ ከዚህ በፊት ስትለብሳቸው የነበሩት የምንዝር ጌጦች ስፍር ቁጥር የላቸውም አሁን ግን እነዚህን ኹሉ አወላልቃ ጥላ ለእግዚአብሔር በሚገባ የማቅ ልብስ ራሷን የክርስቶስ ደቀ መዝሙር አድርጋለች፡፡

❖ ይህቺን ሴት ወደ ቀድሞ ሕይወቷ ለመመለስ የሀገሪቱ መኳንንት ከዙፋናቸው ወርደው ለምነዋት ነበር ወታደሮች ከነትጥቃቸው መጥተው አስፈራርተው ሊወስዷት ሞክረው ነበር፤ ነገር ግን ወደ ቀድሞ ሕይወቷ ይመልሷት ዘንድ አልተቻላቸውም፡፡

❖ ይህቺ ሴት ከዚያ አስነዋሪ ሕይወቷ ተመልሳ ለቅዱስ ቁርባን በቅታለች፤ ለእግዚአብሔር ጸጋ የተገባች ኾና ተገኝታለች ኃጢአቷን ኹሉ በጸጋው አጥባለች ከተጠመቀች በኋላ ራሷን መግዛት ችላለች፤ ይህቺ ሴት የቀድሞ ሕይወቷን ፣ ገላዋን ለብዙ ወዳጆቿ ያሳየችበትን ሕይወት "የእስር ቤት ሕይወት" ብላ ትጠራዋለች፤ በእውነት "ኋለኞች ፊተኞች ይኾናሉ ፤ ፊተኞችም ኋለኞች ይኾናሉ" የሚለው የከበረ ቃለ ወንጌል በእርሷ ሲፈጸም አየነው፤ መለወጥ ከፈለግን እኛን ማሰናከል የሚቻለው ኃይል እንደሌለ ዐወቅን ፤ ተረዳን፡፡

❖ እንኪያስ እኛም ተስፋ በመቁረጥ ፥ በኃጢአት ዐዘቅት ሰምጠን የምንቀር አንኹን፤ ከእኛ መካከል በጽድቅ በረኻነት የሚኖር ማንም አይገኝ ፊተኛ ነኝ የሚል ማንም አይገኝ ፤ ብዙ አመንዝሮች እርሱን አልፈውት ሊሔዱ ይችላሉና፤ ማንም ኋለኛ ነኝ ብሎ ተስፋ አይቁረጥ ፤ ከልቡ ከተጸጸተና ከተመለሰ ፊተኛ መኾን ይቻለዋልና፡፡

✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
📖ምሳ 1፥33

📌 ምንጭ
✍️ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝

🙏 ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ፤ እኔም ለእናንተ ከአዘጋጀው በኃዋላ በድካሜ ብዛት ሳይገባኝና ሳይገባኝ በምጽፈው ድርሳንወ ገድላት መጽሐፍት ላይ የቃላት (የፊደል) ሕፀፅ ቢገኝ በጎደለው እየሞላችሁ በጠመመው እያቃናችሁ አንብቡ በረከት ተካፈሉ እላለሁ ከምንም ጊዜ በላይ ለሀገራችንና ለዓለም ሰላም እንዲሁም ለደካማው ወንድማችሁ እንድበረታ (የተጣልሁ) እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ

✍"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
📚ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ

               ወስብሐት ለእግዚአብሔር
                              ይቆየን 

───────────
                    Channel
 /channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ብሒለ አበው

❖እግዚአብሔር የአንተን ድካም ስህተት ጉድለት እንደተሸከመ ሁሉ አንተም የሌሎችን ተሸከም᎓᎓

❖እግዚአብሔር በራሱ ሁሉን ማድረግ ይችላል፤ አንተ ግን አብረኸው ትሠራ ዘንድ ይሻል፣ እንድትሠራ ብቻ አይደለም
እንድትለፋ እንድትጥርም ነው እንጂ።


እግዚአብሔር ከእርሱም በፊት ሓላፊነት እንድትወስድባት ነፍስህን አደራ ሰጥቶሃል፤ ታዲያ ለአደራው ታማኝ እንደሆነ ባለአደራ ለዚህ ጊዜ ሰጥተሃል ወይስ በሌላ ተይዘሃል!


❖እግዚአብሔር ለምን ኃጢአት ሠራችሁ ብሎ አይጠይቀንም፤ ለምን ንስሓ አልገባችሁም ብሎ እንጂ፡፡

❖በጎልጎታ የተሰቀለው እርሱ እንደ ኃጢአተኛ ተቆጠረ፤ ብዙ
ስድብና ንቀትን ታገሠ፤ ከሞት በክብር ተነሣ፤ በክብርም ወደ
ሰማይ ዐረገ፤ በአብም ቀኝ በክብር ተቀመጠ፡፡

❖አንዳንዴ ስለ እግዚአብሔር ብለን በመልካም ቁጣ ውስጥ
ልናልፍ እንችላለን፤ ነገር ግን እንዲህ ሲሆን መረበሽና ራስን ያለመግዛት ነገር አይኖርበትምና በዚህ ጊዜ መንፈሳዊ ቅናት
ነው።

❖ አንተ ታማኝ ሆነህ በሰዎች ላይ በቃልህ የማትፈርድ ከሆነ እግዚአብሔር ደግሞ እጅግ ፈታኝ ከሆነው በሐሳብ መፍረድ
ይጠብቅሃል።

❖ሌሎችን አመስግን ያለህን አድናቆት ግለጽላቸው፤ መልካም
ሥራቸውን እንዳወቅህ እንዲረዱ አድርግ፤ አክብራቸውም።


ሠናይ ሰንበት



╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮

    የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን 
              ➡️      መሰረተ ሚዲያ

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
     ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ


👇👇👇👇👇👇👇👇

የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═
/channel/Meseretemedia

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

1፣3፣6፣16፣21 የቅድስት ድንግል ማርያም ቀኖች ናቸው፡፡
የእርሷ የኾኑት በዙ ብለህ እንዳታስብ!
ዕንኳን ዕለታቱ የዕለታቱ ፈጣሪ ክርስቶስም የእርሷ ኾኗል፡፡

በ፶፪ ዐ/ም በዛሬው ዕለት ከሦስት ድንጋዮች አንድ መቅደስ በእመቤታችን ስም በፊልጵስዩስ ተሠራ፡፡
ወራሴ ተአምራት ቅዱስ ላሊበላ ደግሞ ከሺ ዐመት በኋላ በኢትዮጵያ ከአንድ ድንጋይ አንድ ሙሉ መቅደስ ገነባ፡፡

ጌታ ኾይ ድንጋዩን ልብ የአንተ መቅደስ አድርገው

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

አንድ በጣም ትልቅ ቆሻሻ የጫነ ጋሪ የሚገፋ ሰው ወደ ቤትህ መጥቶ "እባክህ በርህን ክፈትልኝና ይህን ቆሻሻ አንተ ቤት ላራግፈው?" ቢልህ፣ "ውይ የሚጥልበት ቢያጣ ነው። ባይቸገር ወደ እኔ አይመጣም ነበር" ብለህ ደጅህን ከፍተህ ታስገባዋለህ? በፍጹም፤ እንደውም "እንዴት ብታስበኝ ነው? ምነው ስታየው ቤት አልመሰለህም? እንዴት ሰው በሚኖርበት ቤት ቆሻሻ ካልደፋሁ ትላለህ? ስትል ለጠብ ትጋበዛለህ። መደፈርህ እያንገበገበህ  "እምቢ!" ብለህ ትቆጣለህ። በእርግጥም ያስቆጣል።

ግን ሌላ የሚከፋ ሽታ ያለው ቆሻሻን ጭኖ ለመጣ ባላጋራ እኮ በፈቃድህ የከፈትከው ቤት አለ። "የምን ቤት?" ብለህ ብትጠይቀኝ "ልብህ ነዋ" ብዬ እመልስልሃለሁ፤ "ማን ይኖርበታል?" ካልኸኝም "እግዚአብሔር ነዋ" እልሃለሁ።

አንተ ለመኖሪያ ቤትህ ጽዳት የምትጠነቀቀውን ያህል የያዕቆብ አምላክ ለሚያርፍበት ኅሊናህ ተጠንቅቀህ ታውቃለህ? ሰይጣን ጭኖ የሚያመጣውን የኃጢአት ቆሻሻ ሁሉ እሺ ብለህ ወደ ልብህ በማስገባት የፈጣሪህን መቅደስ ለምን ታቆሽሻለህ? ንጹሑ እግዚአብሔር የሚያድርበትን ቤት ሊያቆሽሽ በመጣ ሰይጣን ላይ እንዴት አልተቆጣህም? ድፍረቱ ለምን አላብከነከነህም?

እግዚአብሔር አንተ ልትኖርበት ከምትፈልገው ንጹሕ ቤት የበለጠ ጽዱ መቅደስ የማይፈልግ ይመስልሃል?

(Dn Abel Kassahun Mekuria )
@MoaeTewahedoB

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

2ኛ ቆሮንቶስ ምዕራፈ 5

6 እንግዲህ ሁልጊዜ እመኑ ጨክኑሞ በዚህ ሥጋ ሳላችሁም እናንተ እንግዶች እንደ ሆናችሁ ታውቃላችሁ ከሥጋችሁ ተለይታችሁ በሄዳችሁ ጊዜ ወደ ጌተችን ትሄዳላችሁ ።
7 በእምነት እንሄዳለን በማየትም አይደለም
8 ታምነናል ይልቁንም ከሥጋችን ተለይተን ወደ ጌታችን እንሄዳለንና ደስ ይለናል ።
9 አሁንም ብንኖርም ብንሞትም እርሱን ደስ ለማሰኘት እንጥራለን ።
10 መልካም ቢሆን ክፉም ቢሆን በሥጋችን እንደ ሠራነው ዋጋችንን እንቀበል ዘንድ ሁላችን በክርስቶስ የፍርድ ዙፋን ፊት እንሰማለንና

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖


❖❖❖❖ ታማኝነት ❖❖❖


መጽሐፍ : ቅዱስ : እንዲህ : ይላል :- «በጥቂቱ : ታምነሃል : በብዙ : እሾምሃለሁ፤..." (ማቴ. 25 ፥ 2።)

ይህም ፡ ማለት ፡ በምድራዊ ፡ ነገሮች ፡ ላይ ፡ ታማኝ ፡ ሆነህ ፡ ስትገኝ ፡ በሰማያዊ ፡ ነገሮች ፡ ላይ ፡ እሾምሃለሁ ፡ ማለት ፡ ነው። በዚህኛው ፡ ዓለም ፡ ውስጥ ፡ ታማኝ ፡ ሆነህ ፡ ከቆየህ ፡ በዘላለማዊነት ፡ ውስጥ ፡ እሾምሃለህ ፡ ማለትም ፡ ነው።

ይህ ፡ መመሪያ ፡ በብዙ ፡ መስኮች ፡ ላይ ፡ ተግባራዊ ፡ ሊሆን ፡ ይችላል . . .

༒ ዘመዶችህን ፡ በመውደድ ፡ ላይ ፡ ታማኝ ፡ ሆነህ ፡ ከተገኘህ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጠላቶችህንም ፡ በመውደድ ፡ ላይ ፡ ይሾምሃል፡፡ ጠላትህን ፡ የምትወድበትን ፡ ጸጋ ፡ ያድልሃል ፡ ማለት ፡ ነው፡፡

༒ በትርፍ ፡ ጊዜዎችህ ፡ እግዚአብሔርን ፡ የምታገለግል ፡ ከሆንህ ፡ በሕይወትህ ፡ ጊዜ ፡ ሙሉ ፡በእርሱ ፡ ላይ ፡ ትኵረት ፡ የምታደርግበትን ፡ ፍቅር ፡ ያድልሃል፡፡

༒ የፈቃድ ፡ ኃጢአቶችን ፡ ከአንተ ፡ በማስወገድ ፡ ላይ ፡ ታማኝ ፡ ሆነህ ፡ ከተገኘህ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ፈቃድህ ፡ ከሚመጡ ፡ ኃጢአቶች ፡ ነጻ ፡ ያወጣሃል።

༒ ንቁ ፡ ኅሊናህን ፡ ከክፉ ፡ ሀሳቦች ፡ የምትጠብቅ ፡ ከሆንህ ፡ እግዚአብሔር ፡ ንቁ ፡ ያልሆነው ፡ ኅሊናህን ፡ ንጽሕና ፡ ይጠብቅልሀል። ከዚህ ፡ በተጨማሪ ፡ የሕልሞችህን ፡ ንጽሕናም ፡ ይጠብቅልሀል።

༒ ልጅ ፡ እያለህ ፡ ታማኝ ፡ ከሆንህ ፡ እግዚአብሔር ፡ ውጊያዎች ፡ በሚበዙበት ፡ በወጣትነት ፡ ዘመንህ ፡ ውስጥም ፡ ታማኝነትን ፡ ያድልሃል፡፡

༒ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ ላይ ፡ በቃላት ፡ ብቻ ፡ የማትፈርድባቸው ፡ ሆነህ ፡ ለመገኘት ፡ ታማኝ ፡ ከሆንህ ፡ ይበልጥ ፡ አስቸጋሪ ፡ በሆነው ፡ በሀሳብ ፡ እንዳትፈርድባቸው ፡ ያስችልሃል፡፡

༒ ልክ ፡ እንደዚሁ ፡ ራስህን ፡ ከውጪያዊ ፡ ንዴት ፡ በመጠበቅ ፡ ላይ ፡ ታማኝ ፡ ሆነህ ፡ ከተገኘህ ፡ እግዚአብሔር ፡ ከውስጣዊ ፡ ቁጣ፣ ንዴትና ቅናት ፡ ነጻ ፡ ያወጣሃል።

༒ በተለመዱ ፡ መንፈሳዊነቶች (በመንፈስ ፡ ፍሬዎች) ፡ ላይ ፡ ታማኝ ፡ ሆነህ ፡ ከተገኘህ ፡ እግዚአብሔር ፡ የመንፈስ ፡ ስጦታዎችን ፡ ያድልሃል!

በመጀመሪያው ፡ ላይ ፡ ታማኝ ፡ ሆነህ ፡ ካልተገኘህ ፡ ሁለተኛውን ፡ ፈጽሞ ፡ ልታገኘው ፡ አትችልምና፡፡ እግዚአብሔር ፡ በመጀመሪያ ፡ የሚፈትሽህ ፡ በጥቂት ፡ ነገር ፡ ነው:: በዚህች ፡ በጥቂቷ ፡ ነገር ፡ ላይ ፡ ታማኝ ፡ መሆንህን ፡ ካረጋገጥህ ፡ እርሱ ፡ በሚበልጠው ፡ ነገር ፡ ላይ ፡ ይሾምሃል፡፡ ውድቀትህንና ፡  አለመታመንህን ፡ በጥቂቷ ፡ ነገር ፡ ላይ ፡  ከገለጽህ ፡ ግን ፡ እግዚአብሔር ፡ በሚበልጠው ፡ ነገር ፡ ላይ ፡ አይሾምህም። መጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ እንዲህ ፡ ይላልና:- «ከእግረኞች ፡ ጋር ፡ በሮጥህ ፡ ጊዜ ፡ እነርሱ ፡ ቢያደክሙህ ፡ ከፈረሶች ፡ ጋር ፡ መታገል ፡ እንዴት ፡ ትችላለህ?» (ኤር. 12 ፥ 5።)

ብዙ ፡  ሰዎች ፡ ዝቅተኛውን ፡ ኃላፊነት ፡ መወጣት ፡ ሳይችሉ ፡ ከፍተኛውን ፡ ኃላፊነት ፡ ለመቀበል ፡ ማሰባቸው ፡ እጅግ ፡ አስደናቂ ፡ ነገር ፡ ነው። እነዚህ ፡ ሰዎች ፡ በተሰጣቸው ፡ ጸጋ ፡ ሳይጠቀሙ ፡ ተጨማሪ ፡ ጸጋ ፡ እንዲሰጣቸው ፡ የሚጠይቁ ፡ ናቸው። ይህን ፡ ሲያደርጉም ፡ «በጥቂቱ ፡ ታምነሃል ፡ በብዙ ፡ እሾምሃላሁ፤...» የሚለውን ፡ የእግዚአብሔር ፡ ቃል ፡ በመዘንጋት ፡ ነው። ይህ ፡ ቃል ፡ ለእነርሱ ፡ እንደ ፡ ሁኔታው ፡ የሚወሰንበት ፡ ነው ፡ የሚሆነው፡፡


════•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ════
  ✞❀
/channel/dnhayilemikael ❀✞
════•ೋ•✧๑♡๑✧•  ════

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

✝ስለ ምሥጢራተ ቅድሳት ✝

✝✝✝ ከኢትዮዽያ #ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ ምዕመናን አብዛኛው #ከቅዱስ_ሥጋውና_ክቡር_ደሙ የራቀ መሆኑን ሳስብ በጣም አዝናለሁ! ✝✝✝

✝ ግን ለምን ??? ✝

✝ ለምን ብዙዎቻችን #ሕይወት_መድኃኒት ከሆነው ማዕድ ተለየን ??? ✝

✝ ከቅዱስ ሥጋው ሳይበሉ: ከክቡር ደሙ ሳይጠጡ መዳን ይኖር ይሆን ??? ✝

✝ በሰማያዊው ዙፋን #በዘለዓለም_አምላክ_በክርስቶስ ፊትስ በቂ መልስ ይኖረን ይሆን ??? ✝

✝ሁልጊዜ ባልረባ ምክንያት ሕይወት ከሆነው #ማዕደ_ክርስቶስ እስከ መቼ እንርቃለን ???

+እርሱ ግን አሰምቶ ይጠራናል:: "ኑ! ሥጋየን ብሉ: ደሜንም ጠጡ" ይለናል:: "ሥጋየን የሚበላ: ደሜንም የሚጠጣ የዘለዓለም ሕይወት አለው:: እኔም በእርሱ አድሬበት እኖራለሁ" ይለናል:: (ዮሐ. 6:56)

+ሌላ መንገድ አለ እንዳይመስለን ደግሞ "የሰውን ልጅ (የክርስቶስን) ሥጋውን ካልበላችሁ: ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም" (ዮሐ. 6:53) የሚል ተግሣጽን ልኮልናል::

+ቤተ ክርስቲያን እኛን ወደ #ምስጢረ_ቁርባን ለማድረስ ከእነዚህ የተረፈ ነገር አልጫነችብንምኮ!

¤በሃይማኖት መኖር (መመላለስ)
¤ከክርስቶስ (ከጌታችን) ጋር ለመኖር ቁርጥ ውሳኔ
¤በመምሕረ ንስሃ ሥር መጠለል
¤በንስሃ ሕይወት መመላለስና
¤ቀዋሚ የሕይወት መሥመር (ጋብቻ ወይ ምናኔ) መያዝን ትሻለች እንጂ መቼ ሌላ ቀንበር ጫነችብን!

+እናም የመንፈስ ወንድሞቼና እህቶቼ . . .
¤የራቅን እንቅረብ!
¤የቀረብንም እንበርታ!
¤የበረታንም እንጽና!
¤የጸናንም ደካሞቹን እንርዳ! (ይህ በጌታ ዘንድ ዋጋው ትልቅ ነውና!)

☞#የምሕረት_ጌታ #ለምሥጢራተ_ቅድሳት የምንበቃበትን የምሕረት ዘመን ያምጣልን::

☞ግን እናስብበት!!!

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

. Dn Yordanos Abebe
/channel/Meseretemedia

Читать полностью…
Subscribe to a channel