#መሰረታዊ_የቤተክርስቲያን_ክርስቲያን_ትምህርት / #የተለያዩ_ተከታታይ_ትምህርት ' #ስንክሳር_የቅዱሳን_ገድል_በየዕለቱ ! #ስዕለ_አድህኖ ! #ምስባክ #የየበአላቱ_ዋዜማና_ሥርተ_ማህሌት #መዝሙር #ግጥም #ለመናፍቃን_ጥያቄ_መልስ እና የተለያዩ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ ሌሎች መንፈሳዊ ጽሁፎች ይለቀቁበታል Administration @zearsema_dn
++ ከእምነት በፊት መዳን ++
( ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ )
የተፈጠርነው በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው። ሰው ሆነን ወደ ምድር የመጣንበትን ዘመን፣ የተገኘነበትን ምድር፣ የወጣንበትን ማኅበረ ሰብእ እና ሌሎችንም ጉዳዮች የመረጠ እርሱ እግዚአብሔር ነው። አዳም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ በራሱ ምርጫ ራሱን ያስገኘ ማን አለ? አጭር ወይም ረዥም፣ ቀጭን ወይም ወፍራም፣ ነጭ ወይም ጥቁር ሆኖ ስለመወለዱ ከእግዚአብሔር ጋር የተማከረስ ማነው? ሁሉም በእግዚአብሔር ፈቃድ የተከናወነ ነው። ገበሬ ዘሩን በምድር ላይ በበተነ ጊዜ ምድሩን ለዘሩ የሚመርጥለት ገበሬው ነው እንጅ ዘሩ እንዳልሆነ ሁሉ የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ምርጫ እንጅ በራሱ ምርጫ ወደ ዓለም ሊመጣ አይችልም።
በዚህ መንገድ ወደ ምድር የመጣ የሰው ልጅ የሚኖረውም የእግዚአብሔርን ፈቃድ መሠረት አድርጎ ነው። በማኅፀን በሠራን ጊዜ ለሕይወታችን የሚያስፈልገንን አንዳች ሳያጎድል ሠርቶ ከማኅፀን ስላወጣን በምድር ላይ ስንኖር የምንኖርበትን ትዕዛዝ ቢያዝዘን አንዳች እንደሚያጎድልብን ሳንጠራጠር አምነን እንታዘዝለታለን። በባሕር የሚኖሩትን በባሕር ለመኖር የሚያበቃቸውን፣ በየብስም የሚኖሩትን በየብስ ለመኖር የሚያስችላቸውን አካል ሰጥቶ ፈጥሯቸዋል። አካላችንን ከሥርዓተ ዓለም ጋር አስማምቶ ምንም የማይጠቅም አካል ሳይጨምር የሚበቃንን እና የሚያስፈልገንን ብቻ ሰጥቶ ወደ ዓለም እንድንመጣ ማድረጉ ለእኛ የሚያስፈልገንን ሁሉ በመስጠት የሚያኖረን እርሱ ብቻ መሆኑን እንድናምን ያስገድደናል።
ከዚህም የተነሣ ነው ሰባኪዎቻችን፥ በሰው እንዳንታመን “ማዳን በማይችሉ በሰው ልጆችና በአለቆችም አትታመኑ ነፍሳቸው ትወጣለች ወደ መሬትም ይመለሳሉ” መዝ 145፥3 ብለው ብለው መታመናችንን በሥጋዊና በደማዊ ፍጥረት ላይ እንዳናደርግ የመከሩን።
ልንኖረው ከተፈቀደልን ሦስት ክፍል ካለው ኑሯችን የመጀመሪያውን ያለ እግዚአብሔር በቀር ከእኛም ሆነ ከሰዎች አንዳች ምክር የሰጠበት የለም። ከማኅፀን ከወጣንም በኋላ የምንኖረው ሁለተኛውን ክፍል ኑሯችንን ሲሆን ከማኅፀን ከወጣንበት ጊዜ ጀምሮ ራሳችንን በሰዎች ዕቅፍ ስለምናገኘው ነው መሰለኝ ከእግዚአብሔር ሀሳብ ይልቅ በራሳችንና በሰዎችም ፈቃድ የመኖር ዝንባሌ ይታይብናል።
በውስጣችን ባለው አድሮብን፣ ተዋሕዶን ከሚኖረው አምላካችን ይልቅ አጠገባችን ከጎናችን ባሉ ሰዎች ተስፋ እናደርጋለን። ይልቁንም በቤተ እግዚአብሔር ለሚኖሩ ሰዎች በሰው መታመን እንዴት ያለ አስቸጋሪ ነገር መሰላችሁ?
ይህንን ያልሁት የዛሬውን መጻጉዕን ጉዳይ ሳስብ ቀድሞ የሚመጣብኝ እግዚአብሔር ሰዎችን ወድ ሚያድንበት ስፍራ ሂዶ ሰው መጠበቁ ስለሚያስገርመኝ ነው። የመጻጉዕን መዳን ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያዘገየበት በሰው ስለሚታመን ሳይሆን አይቀርም። “ጌታ ሆይ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል ብሎ መለሰለት” ዮሐ 5፥5 በሚለው የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ውስጥ የሚታየው ሀሳብ መጻጉዕ በእግዚአብሔር ደጅ እየኖረ በሰው የሚታመን በሽተኛ እንደነበረ የሚያሳይ ነው። ከሩቅ ቦታ አምጥቶ የመጠመቂያው ስፍራ ያደረሰው ማነው? ይሄ ሰው ይህንን ያኽል ዘመን እንዴት አንድ ሰው ወደ መጠመቂያው እንዲወርድ ሊረዳው አልፈቀደም? አብረውት በመጠመቂያው ስፍራ ተኝተው የሚሰነብቱ አንካሶችን በሽተኞች ከዳኑ በኋላ እንኳን ይህንን ሰው ወደ መጠመቂያው ስፍራ አውርደውት ድኖ እንዲመለስ እንዴት አላደረጉትም? እያልሁ ብዙ ጊዜ አስቤ አውቃለሁ።
ይህ ሰው ከመጀመሪያው እምነት የጎደለው ነው። የዳኑት ሁሉ እግዚአብሔር ስለፈቀደላቸው ሳይሆን ሰው ስላላቸው ነው ብሎ የሚያስብ ሰው ነው። የመጣው የእግዚአብሔር መልአክ በወረደ ጊዜ በሚናወጠው ውኃ ውስጥ ገብቶ ተጠምቆ ፈውስ ለማግኘት ነው ነገር ግን በሃይማኖቱ ላይ የሰዎችን እርዳታ ካልተጨመረበት በቀር መዳን እንደማይችል በማሰብ ይሄንን ሁሉ ዘመን ሰው ሲፈልግ ነው የኖረው። በእግዚአብሔር ፊት ሆኖ ሰው መጠበቅ የሚያስገርም ነገር ነው። ለዚህም ነው ኢየሱስ ክርስቶስ ካዳነው በኋላ ራሱን ሳይገልጥለት በሰዎች መካከል ሆኖ የሄደው። እሱም ያዳነው ማን እንደሆነ ሊመረምር አልተመለሰም። ሰው ሲጠብቅ የኖረ ሰው እግዚአብሔር አዳነኝ ማለት እንዴት ይችላል? አይሁድ በጠየቁትም ጊዜ “ያዳነኝ ያ ሰው አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለኝ” ነው እንጅ ያለው እግዚአብሔር አዳነኝ አላለም።
እምነታችን ሳይጸናልን ገንዘብ ብንቀበል፣ ሥልጣን ብናገኝ፣ ጤና ቢኖረን፣ ጉልበታም ብንሆን፣ ውበትና ደም ግባት ቢስማማልን፣ ዓለምን በመላው የእኛ ማድረግ ብንችል ምንም ጥቅም እንደሌለው ተመልከቱ።
መጻጉዕ ያዳነውን ትቶ አልጋውን ተሸክሞ መሄዱ ያሳዝናል። ከዚያች ቀን ጀምሮ ሰይጣን ዝም ብሎ ሊተወው አልወደደም። እስከ ዕለተ ዐርብ ድረስ ተከታትሎ ፍጹም ኃጢአት አሠርቶታል። በሕይወቱ ውስጥ ከሕማሙ ቀጥሎ ሌላ ፈተና ይዞበት የመጣው ፈውሱ ከእምነቱ በመቅደሙ ነው። ከዳነ በኋላ ከዐሥሩ ለምጻሞች እንደ አንዱ እግዚአብሔርን እያመሰገነ በቤተ መቅደስ ሊገኝ ይገባው ነበር እርሱ ግን ይህንን ሲያደርግ አልታየም። ያለ ሃይማኖት የሆነ ነገር ሁሉ ፈተናው ከባድ ነው።
ከሁሉም ነገር በፊት ሃይማኖትህን እንዲያጸናልህ ለምን። ሕይወትህን ከሚገጥምህ ፈተና ሁሉ ጠብቆ ሊያኖራት የሚችል በልብህ ውስጥ ያለው ሃይማኖትህ ነው። ሁሉንም ነገር ከተቀበልህ በኋላ ከሁሉም አስቀድሞ እግዚአብሔርን ለማመስገን ጊዜ ይኑርህ። ንብረትህን ከመሰብሰብህ በፊት ልብህን ሰብስበህ አስብ። ቀጥሎ ለምትጓዝበት መንገድ የሚረዳህ ይህ ነውና። ዳዊት ጎልያድን በማሸነፉ “አቤቱ ጉልበቴ ሆይ እወድሀለሁ” ብሎ ዘመረ እንጅ በራሱ ወይም በሌላ ሰው አልተመካም። ስለዚህም እግዚአብሔር ለሌላ ከፍ ላለ ጸጋ መረጠው። በሰዎች ላይ የጀመረውን ማሸነፍ በአጋንንት ላይ ደገመው። ሳኦልን ከሰዎች እጅ ብቻ ሳይሆን ከመናፍስትም እጅ የሚያድንበትን መንፈሳዊ ጉልበት ከእግዚአብሔር እጅ ተቀበለ። ራሱ ለእግዚአብሔር መዝሙር እያዘጋጀ ስለነበረ ጎልያድን በመግደሉ ሰዎች ስለራሱ የዘመሩትን ዝማሬ አልሰማቸውም።
ወንድሜ ከእግዚአብሔር እጅ ከዚህ የሚበልጥ ሌላ ስጦታ ስለሚጠብቅህ ያዳነህን መርምረህ ሳታውቅ የተሰጠህን አልጋ ብቻ ይዘህ አትውጣ። ከግዚአብሔር ፊት ስትወጣ የሚያገኙህ ሁሉ የሚመለከቱት መዳንህን ሳይሆን የተሸከምኸውን አልጋ ነው። ስንት ዘመን ታመህ እዚህ እንደደረስህ እነሱ አይገባቸውም። ለሕጋቸው እንጅ ለሰው የሚጨነቁ አይደሉም። ስህተቱ፥ ላንተ የሚያስብ እግዚአብሔርን ትተህ እነሱ ወዳሉበት መሄድህ ነው። ሰው አድርጎ በፈጠረህ ጊዜ ለሰውነትህ የሚያስፈልጋትን ሁሉ አስማምቶ የፈጠረህ ጌታ ዛሬም አንተን ለማኖር የሚበቃ ኃይልና ፈቃድ ስላለው ሁልጊዜም ከፊቱ አትጥፋ። ሳታምን ምንም እንዲደረግልህ አትለምን። በእምነት ድል ወደማትነሣው ክብር ለመግባትም አትሞክር።
በጸና እምነት ወስጥ ካልኖርህ፦ ክብር ቢኖርህ ከንቱ ውዳሴ ይጥልሃል። ሀብት ቢኖርህ ጥጋብ ያጠፋሃል። ዝና ቢኖርህ መታበይህ ማዕበል ሆኖ ያሰጥምሃል። ውበት ቢኖርህ ለዝሙት አሳልፎ ይሰጥሃል። ጌጠኛውን ልብስ የመልበስ ዕድል ቢያጋጥምህ ለትውዝፍት ይዳርግሃል። ወንድሜ ያለ እምነት ከሆነ በምንም ነገር እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልምና ከሁሉም ነገር በፊት እግዚአብሔር ሃይማኖትህን እንዲያጸናልህ ለምን።
ፍትሐ ነገስት አንቀጽ 8
ቁጥር 16 ካህናት ከሠርግ አዳራሽ ሄደው ዘፈን መስማት አይገባቸውም። የሚፈክሩት የሚዘፍኑት ሳይመጡ በልተው ጠጥተው መርቀው ይመለሱ እንጂ
የእመቤታችን ዕረፍትና ዕርገት በቅዱስ ያሬድና በአባ ጽጌ ድንግል
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ሊቁ ቅዱስ ያሬድ እንዲኽ እያለ ያወድሳታል፦
╬ “ሐዋርያት አመድበሉ
ሥጋ ድንግል ጠብለሉ
በሰንዱነ ብርሃን ዘላዕሉ
ልብሳ ተካፈሉ”
(ሐዋርያት ተሰበሰቡ፤ ከላይ በመጣ በፍታ (መጐናጸፊያ) የድንግል ሥጋን ጠቀለሉ፤ ልብሷንም ተካፈሉ)
╬ “በደመና ተጋቢኦሙ ሐዋርያት ለድንግል ንጽሕት
ገነዝዋ በክብር ወበስብሐት
ለቀበላሃ ወረዱ ኀይላት
ወቀበርዋ ውስተ ገነት”
(ሐዋርያት በደመና ተሰብስበው ንጽሕት ድንግልን በክብር በምስጋና ገነዟት፤ ለአቀባበሏ ኀይላት ወረዱ፤ በገነት ውስጥም ቀበሯት)
╬ “ተጋቢኦሙ ሐዋርያት እምኲለሄ
በደመናት ዘምሉእ ሡራኄ
ገነዙ በክብር ወበስባሔ
ሥጋ ድንግል ዘይምዕዝ እምርሔ”
(ብርሃንን የተመላ በኾነ በደመናት ሐዋርያት ከአራቱ ማእዝን ተሰብስበው ልብን ከሚመስጥ ሽቱ ይልቅ የሚሸትት የድንግልን ሥጋ በክብርና በምስጋና ገነዙ)
╬ “ተጋቢኦሙ በደመና ሰማይ
ሐዋርያት ሥርግዋን በዕበይ
ገነዝዋ ለድንግል በብዙኅ ግናይ
ዳዊት ዘመራ በመሓልይ”
(በገናንነት የተጌጡ ሐዋርያት በሰማይ ደመና ተሰብስበው ድንግልን በብዙ ምስጋና ገነዟት፤ ዳዊትም በምስጋና አመሰገናት፡፡)
╬“ተጋቢኦሙ አርድዕተ ወልዳ
በደመና ብርሃን ጸዐዳ
ገነዝዋ በስብሐት ለጽርሕ ሳይዳ”
(ጸዐዳ በኾነ በብርሃን ደመና የልጇ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበው፤ ውቢቱ አዳራሽን በምስጋና ገነዟት)
╬ “ተጋብኡ በቅጽበት ለግንዘተ እሙ ቅድስት
ብፁዓን ሐዋርያት
ቦኡ ኀቤሃ በሰላም አምኁ ኪያሃ
በስብሐት ገነዙ ሥጋሃ”
(ንኡዳን ክቡራን ሐዋርያት ቅድስት የምትኾን የጌታ እናቱን ለመገነዝ በቅጽበት ተሰበሰቡ፤ ወደ ርሷ ገብተው በሰላምታ ርሷን እጅ ነሧት፤ ሥጋዋንም በምስጋና ገነዙ)
╬ “ፃኢ እምሊባኖስ ሥነ ሕይወት ርቱዕ አፍቅሮትኪ ቡርክት አንቲ እምአንስት ማኅደረ መለኮት ሰላም ለኪ፤ ማርያም እመ አምላክ ወልድኪ ይጼውዐኪ ውስተ ሕይወት ወመንግሥተ ክብር”
(የሕይወት ደም ግባት የአምላክ እናት ከሊባኖስ ውጪ፤ ፍቅርሽ የቀና ነው፤ ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ፤ የመለኮት ማደሪያ ሰላምታ ላንቺ ይገባል፤ የአምላክ እናት ማርያም ሆይ ልጅሽ ወደ ዘላለማዊ ሕይወትና ወደ ክብር መንግሥት ይጠራሻል)
╬ “ፈለሰት ማርያም በስብሐት ውስተ ሰማያት መላእክት ወሊቃነ መላእክት ወረዱ ለተቀብሎታ”
(እመቤታችን በምስጋና ወደዚያኛው ዓለም በተለየች ጊዜ ለአቀባበሏ መላእክትና ሊቃነ መላእክት ወረዱ)።
☀️☀️☀️
💥 አባ ጽጌ ድንግል እንዲኽ እያለ ያወድሳታል:-
❖ "እንዘ ይፀውረኪ በሐቂፍ ወይስዕመኪ በአፍ
አመ አፍለሰኪ ወልድ ውስተ የማኑ ለዐሪፍ
ጽጌ ዕፀ ገነት ማርያም ዘትጼንዊ ለአንፍ
እንዘ ይትጓድዑ አክናፈ በክንፍ
ለቀበላኪ ወረዱ አእላፍ”
(ለአፍንጫ መዐዛን የምትሰጪ የገነት ዛፍ ማርያም ሆይ፤ ልጅሽ በክንዱ ዐቅፎ በአፉ እየሳመ በቀኙ ሊያሳርፍሽ ባሳረገሽ ጊዜ፤ አንቺን ለመቀበል ክንፍ ለክንፍ እየተጋጩ እልፍ አእላፋት መላእክት ወረዱ)
❖ “ትእምርተ ፍልሰትኪ እምድረ ጽጌ ድንግል በክልኤ
በደመና ሰማይ አርአየ ዘሐዋርያት ጉባኤ
ወእለ ሞቱ አንቅሐ እምከርሠ መቃብር ቀርነ ጽዋዔ
ለነሰ እንዘ ይብሉ ሶበ ሰማዕነ ውዋዔ
መሰለነ ዘበጽሐ ትንሣኤ”
(በኹለት ወገን ድንግል የኾንሽ ማርያም ሆይ አበባ ካለበት ምድር ወደ ሰማይ የማረግሽ ተአምር በሰማይ ደመና የሐዋርያት ጉባኤን አሳየ፤ የሞቱትንም ከመቃብር ውስጥ በተአምር ነጋሪት ድምፅ አስነሣ፤ ለእኛስ የምስጋና ከፍተኛ ድምፅን በሰማን ጊዜ የሙታን መነሣት የደረሰ መሰለን እስኪሉ ድረስ)።
❖ “አመ ነሥኡኪ እምኤዶም አዕላፈ ማሕሌት ጾታ
እንዘ ይጼልሉኪ ድንግል በአክናፈ መባርቅት ከመ ወልታ
ሰራዊተ ሰማይ ይቤሉ ለክብረ ፍልሰትኪ ግርማ ትርሲታ
መኑ ይእቲ ዛቲ ዘገዳመ ጽጌ ዕጥነታ
ወከመ ሠርጸ ጢስ ዘስኂን ይምዕዝ ዕጥነታ”
(ድንግል ወገኖች አመስጋኞች መላእክት በየነገድ በየነገድ ኾነው በመባርቅት ክንፎች እንደ ጋሻ ጋርደው ከኤዶም ገነት በተቀበሉሽ ጊዜ የሚያስደንቅ ክብር ለተገለጸባት ለዕርገትሽ የሰማይ ሰራዊት አበባ ካለበት በረሓ የምትወጣ መዐዛዋም ከነጭ ዕጣን ይልቅ የሚሸትት አወጣጧም እንደ ጢስ አወጣጥ የኾነችይኽቺ ማናት? ይኽቺ ማን ናት ይላሉ (መሓ ፫፥፲፮))።
[የአምላክ እናት ሆይ እወድሻለሁ]
✍️ መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (በድጋሚ የተለጠፈ)
ኦያያያያያያያያያ ወልደ እንትና ዐሥር ሺ ብር ሰጥተዋል። ምእመናን ሴቶች በእልልታ ወንዶች በጭብጨባ አመስግኑልን_እልልልልልል_ጨብጨብጨብጨብ_ወዘተ። ጨረታ ዐውደ ምሕረት ላይ ለምን???
በአንድ መግለጫ ብቻ መስተካከል የሚችል ነገር ግን ቸል የተባለ ጉዳይ፦
፩. አዲስ አበባም ሌሎች ከተሞች ላይም ቄሶች ነን የሚሉ፣ መነኮሳት ነን የሚሉ መንገድ ላይ ሰው ከተሳለማቸው በኋላ አስገድደው ውዳሴ ማርያም ወይም ሌላ የጸሎት መጽሐፍ ካልገዛችሁን የሚሉ ብዙ ናቸው። ይህ እኔንም ገጥሞኛል። ይህን ሙሉ በሙሉ ለምእመኑም አሳውቆ ማስቀረት።
፪. ጥላ ዘቅዝቆ በዐውደ ምሕረት ውስጥ መለመን ቢቀር። በተጨማሪ ዐውደ ምሕረት ላይ ጨረታ፣ መጽሐፍ መሸጥና የመሳሰሉ ንግዶች መቅረት አለባቸው። በእግዚአብሔር ቤት ንግድና ጨረታ ማድረግ ታላቅ ኃጢአት አይደለምን????
፫. የገጠሪቷ ቤተክርስቲያን ጧፍ፣ ዘቢብ፣ ዕጣን አጥታ ተቸግራ ሳለ በየዐውደ ምሕረቱ ዝም ብሎ የሚነድ ጧፍ መኖር የለበትም። በፍትሐ ነገሥት እንደተነገረው የሐዋርያት መልእክት ሲነበብ ጧፍ መበራቱ አንትሙ ውእቱ ብርሃኑ ለዓለም ብሏቸዋልና የዚያ ምሳሌ ነው። ወንጌል ሲነበብ ብዙ መብራት እንዲበራ ታዟል። ጌታ አነ ውእቱ ብርሃኑ ለዓለም ብሏልና የዚያ ምሳሌ ነው። በወንጌል ጊዜ ብዙ ይብራ መባሉ የጌታ ብርሃንነት የባሕርይ ስለሆነ ይህንን በሥርዓታችን ለመመስከር ነው።
፬. በበዓላት ወቅት በዓሉን ለማክበር የመጣው ሕዝብ የወንጌልን ትምህርት መማር ሲገባው የስለት ጊዜ እየተባለ ምእመናንን ማሰልቸት ተገቢ አይደለም። ስለት የሚቀበል ለብቻው መድቦ በዐውደ ምሕረቱ ግን ወንጌል ነው መሰበክ ያለበት።
፭. ቤተክርስቲያን አሥራት የምትቀበልበት፣ በውስጧ ላሉ አግልጋዮች ደመወዝ የምትከፍልበት የራሷ ባንክ ለምን አይኖራትም??? ይህ ቢሆን ምእመናንም አሥራታቸውን ቀጥታ በባንክ ይከፍላሉ። ስለታቸውንም ሌላውንም በዚያ ያስገባሉ። ይህ ሆነ ማለት ደግሞ የሙዳየ ምጽዋት ሌቦች ምክንያት ያጣሉ ማለት ነው።
፮. ማዕከላዊ የሆነ የደመወዝ ክፍያ ለምን አይኖርም? ለምንድን ነው መምህራን አዲስ አበባና ከትልልቅ ከተሞች የተከማቹት?? በረሓ የሚሄደው ቀነሰ፣ የገጠር አጥቢያዎች ላይ አገልጋይ እየጠፋ ነው። ይህ እንዳይሆን መምህራንን ወደየቦታው መበተን አስፈላጊ ነው። በረሓ ለሚሄዱት ከተማ ካለው የበለጠ ደመወዝ እንዲከፈላቸው ማድረግ። ይህ ቢደረግ ወንጌል ትሰፋለች።
አንድም ካህን ጎዳና ላይ ሲለምን እንዳይገኝ፣ ከተገኘ ግን ምእመናን ለአቅራቢያ ቤተክህነት አሳውቀው እርምጃ እንዲወሰድበት ማድረግ ይቻላል።
© በትረ ማርያም አበባው
🌹
እንኳን አደረሰን!
በዓለ ቅዱሳን፦
❖ዮሴፍ አረጋዊ (ትሩፍ)
❖ወጢሞቴዎስ ሊቀ ጳጳሳት (ዘአልቦ ጥሪት)
❖ፍሬምናጦስ ሰላማ (ከሣቴ ብርሃን)
❖ወሳሙኤል (ዘሃሌ ሉያ)
ሐምሌ ፳፮፦
✝ሰላም ለስዕርተ ርዕስከ ዘአስተርአየ ጸዓዳ፤ ወለገጽከ ውኩይ ከመ ርዕየቱ ለተቅዳ፤ ዮሴፍ ወልደ ዳዊት እምዘርዓ ያዕቆብ ዘይሁዳ፤ ዘጻመውከ ምስለ ማርያም ወምስለ ክርስቶስ ወልዳ፤ በጊዜ ኮነ ስደት እምኀበ ንጉሥ ኄሮዳ!
✝ዮሴፍ አረጋዊ በዓለ ርስእ ሠናይ፤ ዘኢተረክበ በውስቴቱ ኅሊና እኩይ፤ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ለብሔረ አግአዚ ዐባይ፤ ሊቀ ጳጳሳት ክቡር ጢሞቴዎስ ነዳይ፤ ሮዲስ ጻድቅ ወሳሙኤል ኅሩይ!
✝ሰላም ለዮሴፍ ዘተኃርየ በበትር፤ ከመ ይኩን ሐጻኒሁ ለአማኑኤል ሔር፤ ፍሬምናጦስ ሰላማ ሐዋርያዊ ክቡር፤ ወለጢሞቴዎስ ዘይብልዎ ብእሲ ግዩር፤ ወሳሙኤል ዘፈለሰ ውስተ ብሔር ስዑር!
©ዝክረ ቅዱሳን
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
እግዚአብሔር ያልተቀየማቸው ተጠራጣሪዎች
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
❖ አባ ጊዮርጊስ እንዲህ አለ
አረጋዊው ስምዖን ‘እነሆ ድንግል ትጸንሳለች’ የሚለውን ትንቢት ተጠራጠረ፤ ይህ ጥርጣሬው ግን በደል ሆኖ አልተቆጠረበትም ይልቁንም ስሙ አማኑኤል የተባለውን ሕፃን ለማቀፍ አበቃው እንጂ፡፡
✍️"ወኢተኈልቈ ሎቱ ኑፋቄሁ ኀበ ጌጋይ አላ አብጽሖ ኀበ ሑቃፌ ሕፃን ዘስሙ አማኑኤል"
❖ ቶማስም የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠረ፤ ትንሣኤውን መጠራጠሩ ግን የጌታን ጎን ለመዳሰስ በችንካሩ እጁን ለማስገባት አበቃው፡፡
✍️ "ወአብጽሖ ኑፋቄሁ ኀበ ገሢሠ አጽልእቲሁ ለመድኃኔ ዓለም"
✍️ በእውነት ‘መተላለፉ የቀረችለት ኃጢአቱም የተከደነችለት ምስጉን ነው’ እግዚአብሔር የወደደው ሰው ቍስሉ አይመረቅዝም በደሉም አይታሰብም፡፡
📖መዝ 32፥1
❖ ጌታ ሆይ እኔንም ስለ መጠራጠሬ አትቀየመኝ ልደትህን የተጠራጠረው ስምዖንን እንዲያቅፍህ ፈቀድክለት፤ ትንሣኤህን የተጠራጠረውን ቶማስ ጎንህን አስነካኸው፤ ያኛው ‘ዓይኖቼ ማዳንህን አዩ’ ብሎ ዘመረልህ ይኼኛው ደግሞ ‘ጌታዬ አምላኬ’ ብሎ መሰከረልህ፡፡
❖ ጌታ ሆይ እኔ እምነተ ቢሱንም መጠራጠሬን አትመልከትብኝ፤ የሚዋዥቅ ሕሊናዬን አጽናልኝ እንደዚያ የልጅ አባት ‘አለማመኔን እርዳው’ እንደ ጴጥሮስ ‘ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ’ በመጠራጠሬ አትቀየመኝ፡፡
❖ መጠራጠሬን አይተህ አትቀየመኝ፤ አንድ ትቢያ ቢጠራጠርህ እንደማይጎድልብህ አውቃለሁ፤ ስለዚህ ራርተህ እምነትን አድለኝ፤ ምናለ ለእኔም ማዳንህን አይቼ እስካምን እንደ ስምዖን ዕድሜ ብትጨምርልኝ? መቼም ላንተ ዘመን አይቸግርህም፤ ሺህ ዓመት ለአንተ አንድ ቀን አይደለች? ቢያንስ አምኜ አሰናብተኝ እስክልህ እስከ ቀትር አቆየኝ፡፡
❖ አንተን በእምነት እንዳቅፍህ እርዳኝ እንጂ ስምዖን አሰናብተኝ እንዳለህ እኔም ደስ ብሎኝ አርፋለሁ፤ ማዳንህን ሳልረዳ ፣ አንተን በእምነት መዳፍ ሳላቅፍህ መሞትን ግን እፈራለሁ፡፡
❖ "አምላኬ ጌታዬ" ብዬ ብዘምርም እንደ ቶማስ ካልዳሰስሁህ ሰውነቴ በእምነት አይኮማተርም፤ ተጠራጣሪውን የማትንቀው ሆይ ጥያቄው የማያባራ ልቤን ጥርጣሬው የማያልቅ ከንቱ ሕሊናዬን እንደ ቶማስ ራራለት፤ ለእኔ የቆሰልከውን ቁስል በእምነት መዳፍ ካልነካሁ ፤ እጄን ከችንካርህ ካላገባሁ የፍቅርህ ጥልቀት አይሰማኝምና እባክህን ‘ና ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን’ በለኝ፡፡
❖ ሳላውቅህ የኖርኩት ጌታዬ ሆይ እንደዚያ መቶ አለቃ ‘ለካስ የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ’ ብዬ ሳልመሰክርልህ አልሙት፤ እንደ ሌንጊኖስ ወግቼህ በፈሰሰው በጎንህ ውኃ ዓይኔን አብርተህ ካለማመን ብታወጣኝ ምናለ? ያላመኑትን የማትንቀው ሆይ ተጠራጣሪዎችን ያልተቀየምከው ሆይ የሚጠራጠርህን ልቤን አትቀየምብኝ፤ የሚያስብ የሚጠይቅ አእምሮ ሠጥተህ ለምን ተጠቀምክበት ብለህ አትቀየምምና ስምዖን አቀፈህ ቶማስም ዳሰሰህ።
"ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ"
📖ኤፌ 4፥29
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
📖ምሳ 1፥33
✍️ " #ወአንቢበክሙ አንትሙ #ለዘኢያንበበ አይድኡ
➘ #እናንተ_አንብባችሁ_ላላነበበው_ንገሩ"
📌 ምንጭ
✍️ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝
🙏 ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ፤ እኔም ለእናንተ ከአዘጋጀው በኃዋላ በድካሜ ብዛት ሳይገባኝና ሳይገባኝ በምጽፈው ድርሳንወ ገድላት መጽሐፍት ላይ የቃላት (የፊደል) ሕፀፅ ቢገኝ በጎደለው እየሞላችሁ በጠመመው እያቃናችሁ አንብቡ በረከት ተካፈሉ እላለሁ ከምንም ጊዜ በላይ ለሀገራችንና ለዓለም ሰላም እንዲሁም ለደካማው ወንድማችሁ እንድበረታ (የተጣልሁ) እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ
✍"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
📚ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን
───────────
Channel
🧲 /channel/dnhayilemikael
───────────
@በእንተ ዲያቆናት(ስለ ዲያቆናት)
የቅድስትና ሐዋርያዊት ኵላዊት ኦርቶዶክሳዊት የተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ቅዱሳት መጻሕፍት ምን ይላሉ?
፩. ዲያቆንም ኾነ ቄስ ሰሞነኛም ይኹን አይኹን፤ ለመቀደስም ኾነ ለጸሎት ቤተ መቅደስ ውስጥ መግባት ያለባቸው ሌሊት ነው። ሥርዐተ ቅዳሴ እንዲህ ይላላ፦
👌 "ሌሊት ለጸሎት ያልመጡ ቀሳውስትና ዲያቆናት ወደ ቤተ መቅደስ ይገቡ ዘንድ ያገለግሉም ዘንድ አይገባቸውም። ይኽን ትእዛዝ ቢደፋፈሩ ግን ከሕግ ትእዛዝ የወጡ ይኾናል።" [ሥርዐተ ቅዳሴ]
፪. ብዙዎቹ ዲያቆናት ልብሰ ተክህኖ ለብሶ መቀደስ፥ ሰዓታትና ማኅሌት መቆምና በንግሥ ሰዓት መስቀልና ቃጭል ይዘው ቅድመ ታቦት መኼድ እንጂ የቅዱሳት መጻሕፍትን ምሥጢር መረዳት የስብከተ ወንጌል ግብር ብቻ ይመስላቸው። ፍጹም ስሕተት ነው። ከመቀደስ ባለፈ እውነተኛውን የቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት
መማር፥ መረዳት፤ ከክህደት ትምህርት አንጥሮ መገንዘብም የመለየት ኃላፊነት አለባቸው።
➺ቅጥረኛ ስለኾንኩ እንጂ...በሚል ሳይፈልገው የሚቀድስ፦ ከታማኝ አገልጋይ ጋር ምን አንድነት አለው?
➾ቅባት ከተዋሕዶ ጋራ፥ ኑፋቄ ከአሚን(ከእምነት) ጋራ፥ ምርግትና ከጥንቆላ ጋራ፥ አውደ ነገሥት ከፍትሐ ነገሥት ጋር፥ ክህደት ከእውነተኛዋ ኦርቶዶክሳዊት የተዋሕዶ ትምህርት ጋር፤ ምንም ኅብረት እንደሌላቸው አንጥሮ፥ ኵልል አድርጎ የመረዳት የማስረዳትም ግዴታ አለባቸው። ለዚኽም ነው፦
👌"የቤተ ክርስቲያን መብራት አገልጋዮቹዋም የምትኾኑ ዲያቆናት ኾይ ተኵላ ከበግ ጋራ፤ ጭላት(ጭልፊ) ከርግብ ጋራ፤ ክርዳድ ከስንዴ ጋራ እንዳይኖር ከውስጥዋ ንቀሉ፤[ቅዳሴ አትናቴዎስ] እንዲል።
፫. ደጀ ሰላም፦ የሰላም ደጅ ናት። የዲያቆናት አብነት ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ መጽሐፈ ገድሉ ላይ "የቀዳሜ ሰማዕት ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ አምላክ እግዚአብሔርም የዚኽን ሰው የንስሓ እንባ ተመልክቶ ይቅር አለው። ይኽ ሰውም በዚያች ቤተ ክርስቲያን ደጀ ሰላም ተቀምጦ የደረሰበትን ለሚገባውና ለሚወጣው ኹሉ መሰከረ።" [ገድለ ቅዱስ እስጢፋኖስ ዘወርኃ መጋቢት]
✍️ አኹንማ የተጣሉ የሚታረቁባት፦ የሰላም ደጅ የተሰኘችው "ደጀ ሰላም" ድረስ ቢራና ዘር ማንዘሮቹ ገብተው "ምን ይኹንልህ?!" ብለን ግሮሰሪ አደረግነው። በርግጥ መጠጥ ፈጽሞ የተከለከለ ባይኾንም፤ አብዝቶ መጠጣት ግን የተገባ አለመኾኑ ለኹላችንም ግልጽ ነው። ደጀ ሰላም "የሰላም ደጅ" እንጂ 'የቢራዎች ደጅ' አይደለችምና ባይገባ ይመከራል።
✍️በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ተፈቅደው ነገር ግን ከማይበረታቱ ነገሮች አንዱ መጠጥ ነው። ፈጽሞ አይጠጣም፥ ርኵስ ነው ባንልም የማይጠጣ የተሻለ አደረገ።
➣"ከስካር ተጠበቁ ሙሴ በኦሪት ዘሌዋውያን እንዳይሰክሩ አዟቸዋል። እንዲሁ እናንተ ኤጲስቆጶሳት ቀሳውስትና ዲያቆናት መጠጥን ከማብዛትና ከስካር ተጠበቁ፤ መዳራት፣ ዝሙት፣ ስግብግብነት፣ ሰውን መስደብና ማስቀየም፣ መታበይ፣ በሐሰት መማል፣ ብዙ ቁም ነገሮችን መዘንጋትና ሌሎችም ከስካር የሚመነጩ ናቸው።"[መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ዘሮም፤ ምዕራፍ ፲፤ ቍጥር 56]
➛"ከስካርና ወይንን ከማብዛት ተጠበቁ፤ ቃለ እግዚአብሔር የሠፈረባቸውን መጻሕፍት መጠጣትን አዘውትሩ እንጂ።" [ዝኒ ከማሁ(Ibid) ቍጥር 57]
፬. የበቁ ዲያቆናት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በቅድስና ሥጋወደሙን ለመለወጥ ሲወርድ ማየት ይችላሉ።
➤"ካህን የመንፈስ ቅዱስን ፀጋ ላክ ባለጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለመስዋዕትነት በቀረቡ ፅዋዕና ሕብስት ላይ መንፈስ ቅዱስ ይወርዳል፤ ዲያቆናት በቅድስና ሥጋወደሙን ለመለወጥ ሲወርድ ማየት ይችላሉ። የዲያቆናት ክብር በዚህ ብቻ የተወሰነ አይደለም። ቅዱስ እስጢፋኖስ በመንግሥተ ሰማያት ታላቅ የክብር ቦታ ከእግዚአብሔር ዘንድ ሊሠጠው እንደቻለ ለነሱም ይሠጣል።"
[መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ዘሮም፤ ምዕራፍ ፲፩፤ ቍጥር 33]
፭. ዛሬ ላይ ዲያቆናት የት ይገኛሉ? ምን ሲያደርጉ ይገኛሉ? ክቡር ዲያቆን ሆይ! "ዙረታም" ነኝ ካልክ የት መዞር እንዳለብህ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዲህ ይመክሩናል።
➣"ዲያቆናት የክርስቲያኖችን የመኖሪያ ቤት ወዳለበት ኹሉ እየዞሩ የተቸገሩትን ኹሉ ይጎብኙ፤ ችግራቸውንም ይመልከቱ። ጥዋትም ኾነ ማታ ምእመናኑ በስንፍና እንዳይያዙ ለመንፈሳዊ አገልግሎት እንዲተጉ ያነቃቁዋቸዋል። በሠርክ በጧትና በማታም ወደ ቤተ ክርስቲያን ሁል ጊዜ እየኼዱ ያመስግኑት፤ እግዚአብሔር የዕለት ብርሃን ነው፤ ኹሉንም ይረዳል።" [መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ ዘሮም፤ ምዕራፍ ፱፤ ቍጥር 66]
፮. ዲያቆናት ምንም ዓይነት ጉቦ መቀበል፥ በደም ግባት ማዳላት፤ ድሀን አይቶ ባላየ ማለፍ፤ ዝም ብሎ ስለ ሴትና ወንድ በማውራት ዋዛ ፈዛዛ በመስማት- ነገረ ዘርቅ መስማት የለባቸውም።
➤ "እናንተም የመንጋዎች ጠባቆችና ዲያቆናት ሆይ መማለጃ በመቀበልና ፊት አይቶ በማድላት ምክንያት ከቤተ ክርስቲያን ታወጡት ዘንድ በደል በሌለው በንጹህ ሰው ላይ ነገር ሥራንና የሐሰት ነገርን ትሰሙ ዘንድ አይገባም። እንደዚህ ያለ ሥራ የሚሠሩ ሰዎች የዲያብሎስ ወዳጆች ይኾናሉና።" [መጽሐፈ ዲድስቅልያ፤ ምዕራፍ ፲፥ ቍጥር 55]
➣ "ዲያቆናት ድኆች ሳይለምኗቸው ፈቃዳቸውን ሊያደርጉላቸው አገባብ ነው።"[መጽሐፈ ዲድስቅልያ፤ ምዕራፍ ፲፮፥ ቍጥር 55]
፯. ዲያቆን በድቁና የተካነ ካህን ነው። ቄስም በቅስና የተካነ ካህን ነውና በአጠቃላይ ማኅበረ ካህናት አይደለም በfb በሕዝባውያን መዋኛ ገንዳዎች እንዲዋኙና ለሕዝባውያን ገላቸውን እንዲያሳዩና ተገላልጠው እንዲታዩ፥ ቁንጣ፥ ጃፖኒ፣ ጥብቅብቅ የሚያደርጉ አልባሳት አድርጎ ውጭ መታየት ፈጽሞ አይፈቀድላቸውምና....
✍️ "አንተ ግን ትታጠብ ዘንድ በወደድህ ጊዜ የሕፃንነትህን ደም ግባትና የሰውነትህን ማማር እንዳያዩ በአንተም እንዳይሰናከሉ። አንተም እንዳትበድል፤ በእነርሱም እንዳትሰነካከል፤ ሴቶች ወደሚታጠቡበት መታጠቢያ ቤት አትግባ።"[መጽሐፈ ዲድስቅልያ፤ ምዕራፍ ፪]
👌ጸጉር አቆራረጥንም በተመለከተ ለምዕመናን ሲገልጽ የቅድስትና ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያናችን የሕግና የሥርዓት መጽሐፍ የሆነው ፍትሕ መንፈሳዊ ወሥጋዊ "በተፈጠርህ ጊዜ እግዚአብሔር በሰጠህ መልክ ላይ መልክ አትጨምር። ያድግ ዘንድ ፀጉርህን አትከባከበው ተላጨው እንጂ አታሳድገው። ወጥመዳቸው ቅርብ የሆነ ሴቶችን ወደ አንተ ያመጣብህ ዘንድ አታሳምረው። ረቂቅ ልብስ አትልበስ፤ ይህች ስሕተትን ታመጣለችና፤ ቀለም የተቀባ ጫማ አትጫማ፤ በጣቶችህ የወርቅ ቀለበትን አታድርግ፤ ይህ ሁሉ የዝሙት ምልክት ነውና። ጠጉርህን ግልስልስ ብጥር አታድርገው፤ አትሠራው፤ " [ፍትሕ መንፈሳዊ፤ አንቀጽ ፲፩፤ ገጽ. 123] ካለ ለካህናቱ እንዴት ጥብቅ ይሆን???
💚💛❤
✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲
ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ
#ሺ_ዓመት_አይኖር
🥀ብዙ ጊዜ ለስንፍናችን ምክንያት ወይም ተስፋ ለመቁረጥ ሰበብ ከሚሆኑን ነግሮች አንዱ "ሺ ዓመት አይኖር" የሚለው አባባል ነው በእርግጥ በምድር ሺ ዓመት መኖር የቻለ የለም ረጅም ዓመት እንደኖረ የሚነገርለት ማቱሳላ እንኳን ሺ ዓመት አልኖረም ወዳጄ በተለይ እኛ ባለንበት በዚህ ዘመን ደግሞ እንኳን ሺ ዓመት ሊኖር ቀርቶ መቶ የሞላ እንኳን ቢገኝ የሚድያ የአንድ ወቅት የዜና ሽፋን መሆኑ የማይቀር ነው ስለዚህ ወደ ዘመናችን አባባሉን ማምጣት ከፈለግን መቶ ዓመት አይኖር በሚል ልንቀይረው ያስፈልጋል።
🥀የሚያሳዝነው ሺ ዓመት አይኖር የምንለው ለመዝናናት ለመጨፈር ራስን ለመርሳት ፈቃደ ሥጋን እንደ ልብ ለመፈጸም ብቻ እንጂ ለመንፈሳዊ ሕይወት ለመሰናዳት አይደለም "አንቂ" የሚባሉ አካላት የዕድሜህን አጫርነት የሚነግሩህ ከሞት በኋላ ላለው ረጅሙ ዕድሜ በዚህች በአጭሯ የምድር ዕድሜህ በጎ ሰርተህ እንድታልፍ ሳይሆን እንዳትጨናነቅ ፈታ ብለህ(በእነርሱ አማርኛ) እንድትኖር ለማስታወስ ብቻ ነው።
🥀ወዳጄ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ግን በምድር ስለምትኖርበት ዕድሜህ ሲነግርህ ቢበዛ(ቢበረታ) ሰማንያ ይልሃል ሺ ዓመት አይኖር ሲሉህ ቢበዛ ሰማንያ እርሱም በተገኘ በላቸው ታድያ በምድር የምትኖርበት ዕድሜህ ጥቂት ከሆነ ከዚያ በኋላ በሞት ይህን ምድር ከተሰናበትክ ከሞት በኋላ የት ትሄድ ይሆን?? የዚህ ምድር ኑሮህ በሞት ከተቋጨ በኋላ ሞተህ የምትቀር መስሎ እንዳይሰማህ ከሞት በኋላ ሕይወት አለህ ያውም እንደሰው ኖረህ ከሞትክ የምትነሳው እንደ ሰው ሆነህ የምትኖረውን ሕይወት ለመድገም
🥀እንዳይመስልህ ከትንሣኤ በኋላ የምትኖረው እንደ መላእክት ነው “በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ”ማቴ 22፥30
ስለዚህ አስታውስ የምድር ኑሮህ ቢበዛ ሰማንያ ነው ያ ማለት ጥቂት ነው መጽሐፍ
እንደሚነግርህ
🥀ሕይወታችሁ ምንድር ነው ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና”
ያዕ 4፥14
🥀ስለዚህ በምድር የምትቆየው ጥቂት ጊዜ ነውና:-*
ዛሬ የንስሐ አባት ያዝ
ዛሬ ንስሐ ግባ
ዛሬ ከተጣላሃቸው ታረቅ
ዛሬ ያስቀየምካቸውን ይቅር በል
ዛሬሥጋ ወደሙን ተቀበል
ነገ ሳይሆን ዛሬ መልካም ነገሮችህን ሁሉ ጀምር ምክንያቱም
“እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።”
2ኛ ቆሮ 6፥2 የሞዐ
Join ቴሌግራም ቻናል
አምላከ ቅዱሳን ለንስሐ የተዘጋጀ ልብ ያድለን
ለንስሃ ሞት ያብቃን🙏
❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን
➡️ መሰረተ ሚዲያ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ
👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═/channel/Meseretemedia
† የድፍረት ኃጢአት በእግዚአብሔር ቤት †
"በመገናኛው ድንኳን ደጅ ከሚየገለግሉ ሴቶች ጋር እንደተኙ ሰማ።"(1ኛ ሳሙ 2፡22)
★ የአገልጋዮች ማመንዘርና ውጤቱ ★
34 ሺህ እስራኤላውያን በጦርነት ከሞቱበትና ታቦተ ጽዮን ከተማረከችበት የድፍረት ኃጢአቶች መካከል አንዱ የእግዚአብሔርን ቃል የሚያውቁና በውስጥና በውጭ የሚገለግሉ ወንዶችና ሴቶች ያደረጉት ማመንዘር ነው፡፡
ማመንዘር ኃጢአት ነው፡፡ ማመንዘር ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጪ ሲሆን ደግሞ ቅጣቱ እጅግ የከፋ ነው ማለትም ወንድ ከወንድና ሴት ከሴት ጋር ሲሆን ሀገርን ከነሙሉ ሀብትና ንብረቷ በእሳት ተቃጥላ እንድትጠፋ ያደርጋል፡፡ ግብሩም ግብረ ሰዶም ይባላል፡፡ (ዘፍ 19፡24)
አንድ ተራ ግለሰብ ከሕግ አግባብ ውጪ ቢያመነዝር ኃጢአቱ በራሱ ላይ ይሆናል፡፡
ኃይልንና ሥልጣንን ተtመክቶ በትዳር ያለችን ሴት ቢመነዝር በደሉ ከፍ ያለ ቅጣትን ያስከተላል፡፡ ቅጣቱም ከራስ ወደ ልጅ ይወርዳል፡፡ (2 ሳሙ 12፡10)
በቤተ እግዚአብሔር ቃሉን እየሰሙ ኖረው እያገለገሉ ያሉ፣ እግዚአብሔርን መፍራት ትተው በድፍረት ከሌሎች አገልጋዮች ጋር ቢያመነዝሩ ለኃጢአታቸው የሚከፈላቸው ደመወዝ ቤተ ክርስቲያንን ሁሉ አደጋ ውስጥ ይጥላል፡፡
ከላይ በርዕሱ ለመጠቀስ እንደተሞከረው ሁለቱ የሊቀ ካህኑ የዔሊ ልጆች አፍኒንና ፊንሐስ ከክህነታቸው በተጨማሪ በትዳራቸው ላይ ይማግጡ፣ ያመነዝሩ የነበሩት በእግዚአብሔር ቤት ከሚያገለግሉ እግዚአብሔርን ከሚያውቁ ሴቶች ጋር ነበር፡፡ በየአብያተ ክርስቲያናቱ የንግስ በዓልን ምክንያት አድርጎ በሰንበት ትምሕርት ቤቶች አዘጋጅነት የሚካሄዱ የአዳር መርሐ ግብሮች ፈተና እየሆኑብን አይደለ ?፣ የጉዞ መርሐ ግብሮችስ ከመንፈሳዊ ዓላማቸው እያፈነገጡብን አይደለ?
አሁን ይህን ቃል ሰምተንና አንብበን በነ አፍኒንና ፊንሐስ ላይ ለመፍረድ አንነሳ በዘመናችንስ እንደዚህ ዓይነት የድፍረት ኃጢአቶች በአገልጋዮች ዘንድ የሉም? . . . የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪዎች፣ የሰንበት ትምሕርት ቤት አመራሮች ቃሉን ከማወቅ በዘለለ በዲያቆናትና በሰንበት ትምሕርት ቤት ወጣት ሴቶች፣ በሰንበት ትምሕርት ቤት ወጣት ሴቶችና ወንዶች መካከል የሚታዩና የሚሰሙ አዝማሚያዎችን በዝምታ ማለፍ እንደ ዔሊ አያስቀስፈንም ብላችሁ ታምናላችሁ? ቤተ ክርስቲያንን አደጋ ውስጥ አይከታትም ብላችሁ ታስባላችሁ? . . . በሀገራችን እየደረሰ ላለው ብዙ ምስቅልቅሎችስ የአገልጋዮች በቤተ መቅደስ የሚደረጉ ዘርፈ ብዙ የድፍረት ኃጢአቶች ምክንያት አይደለም ብላችሁ ታስባላችሁ? ይህንን የማስጠንቀቂያ ደውል የሰማን ሁላችን ዛሬ ንስሐ እንግባ።
ለሌሎችም ሼር አድርጉት
መምህር ኢንጂነር ታርኩ አበራ
+"+ እንኩዋን ለአጋእዝተ ዓለም #ሥላሴ እና ለቅዱሳን
አበው #አብርሃም: #አባ_ሲኖዳ እና #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ
ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ +"+
+"+ #ሥሉስ_ቅዱስ +"+
=>በአንድነቱ ምንታዌ (ሁለትነት): በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት)
የሌለበት የዘለዓለም አምላክ: የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ
#እግዚአብሔር ነው:: #አብ : #ወልድ : #መንፈስ_ቅዱስ
በስም: በአካል: በግብር ሦስትነት: በባሕርይ: በሕልውናና
በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው:: በዚህ ጊዜ ተገኙ: በዚህ ጊዜ
ያልፋሉ አይባሉም:: መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና::
+ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት " #ቅድስት_ሥላሴ "
እንላቸዋለን:: የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም::
የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል:: በቤቱም መጥተው
ያድራሉ::
+ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል
በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም:: አባታችን
#ቅዱስ_አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን
በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል:: ሥላሴ
አኀዜ ዓለም (ዓለምን በእጁ የያዘ) ነው:: ነገር ግን በፍቅር
ለሚሻው በፍቅር ይመጣል::
+አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ: እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ
ሥላሴን በድንኩዋናቸው አስተናገዱ:: አብርሃም እግራቸውን
አጠበ:: (ወይ መታደል!) በጀርባውም አዘላቸው:: (ድንቅ አባት!)
ምሳቸውንም አቀረበላቸው:: እንደሚበሉ ሆኑለት:: በዚያው
ዕለትም የይስሐቅን መወለድ አበሠሩት:: #ቅድስት_ሣራ ሳቀች::
እንደ ዘንድሮ ወገኖቻችን የማሾፍ አይደለም:: ደስታና ጉጉት
የፈጠረው እንጂ:: ሥላሴ "ምንት አስሐቃ ለሣራ በባሕቲታ"
ብለው ነበርና በዚህም ምክንያት ነው " #ይስሐቅ" የተባለው::
+ሥላሴን ያስተናገደች ድንኩዋን (ሐይመት) የድንግል
እመቤታችን ማርያም ምሳሌ ናት:: በድንግል ላይ #አብ
ለአጽንኦ: #መንፈስ_ቅዱስ ለአንጽሖ: #ወልድ በተለየ አካሉ
ለሥጋዌ በእርሷ ላይ አርፈዋል / አድረዋልና::
+"+ #ታላቁ_አባ_ሲኖዳ +"+
=>የባሕታውን ሁሉ አለቃቸው ታላቁ ቅዱስ ሲኖዳ:-
¤በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን የተወለደ
¤በእናቱ ማሕጸን ሳለ መላእክት በሰይፈ እሳት ይጠብቁት የነበረ
¤የታላቅነት ትንቢት የተነገረለት
¤ገና ሳይወለድ ሥውራን አበው የሰገዱለት
¤በሕጻን ሰውነቱ ጾምና ጸሎትን የጀመረ
¤የልጅነት ቁርስና ምሳውን ለነዳያን ያካፍል የነበረ
¤በ9 ዓመቱ ወደ በርሃ የመነነ
¤የአባ አብጐል ደቀ መዝሙር የሆነ አባት ነው::
+ሲመነኩስም በእግዚአብሔር ትእዛዝ #የሠለስቱ_ደቂቅ
አስኬማ: #የኤልያስ ቆብዕ እና የመጥምቁ #ዮሐንስ ቅናትን
(መታጠቂያ) ከያሉበት መላእክት አምጥተውለት የመነኮሰ
¤ዓለምን በሙሉ በጸሎቱ ይጠብቅ የነበረ
¤የግብፅን በርሃ በብርሃን የሞላ
¤በርካታ ድርሰቶችን የደረሰ
¤ያለ ማቇረጥ በየቀኑ ከ100 ዓመታት በላይ ከጌታችን ክርስቶስ
ጋር የተነጋገረ
¤ደመናትን ተጭኖ ይሔድ የነበረና
¤ያለ ዕረፍት ለ111 ዓመታት ከ2 ወራት ፈጣሪውን ያገለገለ
አባት ነው::
+በዚህም ምክንያት አንድ ቀን ገዳማውያን ሁሉ እየሰሙ
እንዲህ የሚል ቃል ከሰማይ መጣ:: "ሲኖዳ ተሠይመ
#አርሲመትሪዳ " (ሲኖዳ አርሲመትሪዳ ሆኗል:: ማለትም
ለባሕታውያን ሁሉ አለቃ ሁኖ ተመርጧል ማለት ነው:: )
+ቅዱሱ የጌታችንን እግር እያጠበም ይጠጣ ነበር::
+በዚህች ዕለት በ120 ዓመቱ ጌታችን ወርዶ ሲያሳርገው
#አቡነ_ኪሮስ "ታላቅ ምሰሶ (ታላቅ ዛፍ) ወደቀ" ብለው
አልቅሰዋል:: #ሲኖዳ ማለት "ደግ ሰው" ማለት ነው::
+"+ #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ ( #GIYORGIS_OF_SEGLA )
+"+
=>ታላቁ ኢትዮዽያዊ ሊቅና ጻድቅ የተወለደው ወሎ #ጋስጫ
ውስጥ በ1358 ዓ/ም ነው:: ከልጅነቱ ትምሕርት አልገባሕ
ቢለውም በልቡናው ግን ቅን እና ታዛዥ ነበር:: መምሕሩ
"ትምሕርት አይገባውምና ውሰዱት" ቢላቸው "የእግዚአብሔር
ነውና ያገልግላችሁ" ብለው መለሱት:: መገፋቱን የተመለከተ
#አባ_ጊዮርጊስ #እመቤታታችንን ከልቡ ይወዳት ነበረና
ይማጸናት ገባ::
+ቀን ቀን ገዳሙን ሲረዳ: እሕል ሲፈጭና ሲከካ: ላቡንም
ሲያፈስ ውሎ ሌሊት ደግሞ ሲጸልይ ያነጋ ነበር:: ድንግል
እመቤታችን ጸሎቱን ሰምታለችና #ቅዱስ_ዑራኤልን አስከትላ
መጣችለት:: በንጹሐት እጆቿ ባርካው ምሥጢርንም ነገረችው::
"ወነገረቶ ሐምስተ ቃላተ" እንዲል:: ጽዋዐ ልቡናን አጠጥታው
ተሠወረችው::
+ከዚህች ሰዓት ጀምሮ አባ ጊዮርጊስ ፍጹም ተለወጠ:: በጽድቁ
ላይ የሊቅነትን ካባ ደረበ:: ቅዱሳት መጻሕፍትን ይተነትናቸው:
መናፍቃንንም ምላሽ ያሳጣቸው ገባ:: የተረጐማቸውና
ያተታቸውን ሳይጨምር 41 ድርሰቶችን ደረሰ:: (መጽሐፈ
ሰዓታት: መጽሐፈ ምሥጢር: አርጋኖን: ኆኅተ ብርሃን: ውዳሴ
መስቀል: ወዘተ . . . የእርሱ ድርሰቶች ነበሩ)
+ስለ ሃይማኖትም ጠበቃ ነበር:: ስለ ቅድስናውና ውለታው የኢ/
ኦ/ተ/ቤ እንዲህ ትጠራዋለች:-
1. #ሊቀ_ሊቃውንት
2. #በላዔ_መጻሕፍት
3. #ዓምደ_ሃይማኖት
4. #ዳግማዊ_ቄርሎስ
5. #ጠቢብ_ወማዕምር
+ጻድቁ ሊቅ በተወለደ በ60 ዓመቱ በ1418 ዓ/ም በዚህች ቀን
ዐርፏል:: አባ ጊዮርጊስ የተወለደውም ያረፈውም ሐምሌ 7 ቀን
ነው::
=>የሥላሴ ቸርነት: የአብርሃም ደግነት: የአበው አባ ጊዮርጊስና
አባ ሲኖዳ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን::
=>ሐምሌ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱሳን አብርሃምና ሣራ (ሥላሴን ያስተናገዱ)
2.ብሥራተ ልደተ ይስሐቅ
3.ታላቁ አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን ሁሉ አለቃ)
4.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (ሊቀ ሊቃውንት: ኢትዮዽያዊ
የሃይማኖት ምሰሶ)
5.ቅዱስ አግናጥዮስ ዘአንጾኪያ (ምጥው ለአንበሳ)
6.አባ መቃቢስ
7.አባ አግራጥስ
=>ወርሐዊ በዓላት
1.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
2.አባ ባውላ ገዳማዊ
3.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
=>+"+ እግዚአብሔርም ለአብርሃም ተስፋ በሰጠው ጊዜ:-
'በእውነት እየባረክሁ እባርክሃለሁ:: እያበዛሁም አበዛሃለሁ'
ብሎ ከእርሱ በሚበልጥ በማንም ሊምል ስላልቻለ በራሱ ማለ::
እንዲሁም እርሱ ከታገሠ በሁዋላ ተስፋውን አገኘ:: +"+ (ዕብ.
6:13)
=>+"+ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ: የእግዚአብሔርም ፍቅር:
የመንፈስ ቅዱስም ሕብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን:: አሜን:: +"+
(ቆሮ. 13:14)
+++ ስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር +++
©ዝክረ ቅዱሳን
•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን
➡️ መሰረተ ሚዲያ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ
👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═/channel/Meseretemedia
በቤትህ ያለው ዳቦ ለተራበው ሰው የሚውል(ንብረቱ) ነው፥ በልብስ ማስቀመጫህ ውስጥ ያለው የማትጠቀመው ኮት የችግረኛው ገንዘቡ ነው፥ በጫማ ማስቀመጫህ ውስጥ አልፈልገውም ብለህ ሊበላሽብህ የሆነው ጫማ የደሃው ጫማ (ጫማ ለሌለው ገንዘቡ) ነው ፥ ያከማቸኸው ገንዘብ ለድሃው የሚገባው ነው....
ዛፍ በፍሬው ይታወቃል፥ ሰውም በድርጊቱ፡፡ መልካም ስራ መቼም አይጠፋም፡፡ መልካም እርዳታን የሚዘራ፥ ወዳጅነትን ያጭዳል፡፡ ደግነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል፡፡
"ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ብቻ የለብንም፥ ነገር ግን ካነበብነው ተምረን ማደግ አለብን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም የማይጠቅም ነገር እንዳልተጻፈ ተገንዘብ፡፡
አሁንም ለጥንካሬ፣ ለመታገስ፣ ለመዳን፣ ለመለወጥ ጊዜ አለህ! ተኝተሃልን? ንቃ! ኃጢአት ሰርተሃልን? እንግዲያውስ መስራቱን አቁም፡፡
#ቅዱስ_ባስልዮስ_ዘቂሳርያ
/channel/dnhayilemikael
" ራስህን ከቤተክርስቲያን ፈፅሞ አትለይ፤ ቤተክርስቲያን ተስፋህ ናት፤ ቤተክርስቲያን ደኅንነትህ ናት፤ ቤተክርስቲያን መጠጊያህ ናት።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
" ወደ ተቀደሰ ተራራዬ አመጣቸዋለሁ፥ በጸሎቴም ቤት ደስ አሰኛቸዋለሁ፤ ቤቴ ለአሕዛብ ሁሉ የሚሆን የጸሎት ቤት ይባላልና..."
ኢሳ. ፶፮፥፯ /56፥7/
❤ ቤተክርስቲያን ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኝበት የጸሎት ቤት ነው። በእዚያም እርሱ አለና።
ጊዜ የለኝም መምህራኑ ገዳማውያኑ ያንብቡ !!!
❖ "ሰው ወደሚበዛበትና የዚህን ዓለም ፍርድ ወደሚሰጡ ቦታዎች አለመኼድ ስለማልችል፣ የምመራው ትልቅ የንግድ ድርጅት ስላለኝ፣ ሥራዬ ጥበበ እድ ስለሆነ፣ ጊዜ ስለሌለኝ፣ ትዳር ስላለኝ፣ ልጆችን ስለማሳድግ፣ የቤተሰብ አስተዳዳሪ ስለሆንኩ፣ እኔ የዓለም ሰው ስለሆንኩ መጻሕፍትን ማንበብ አይጠቅመኝም፤ "መጻሕፍትን ማንበብ በገዳም ለሚኖሩ መነኮሳት ነው" ብለህ አትንገረኝ።
❖ "አንተ ሰው! ምን ማለትህ ነው?" "ብዙ የዚህ ዓለም አሳብ ስላለብኝ መጻሕፍት ማንበብ ለእኔ አይደለም" ትለኛለህን? እንዲያውም ልንገርህ! አንተም ስማኝ! ከእነዚያ መነኮሳት ይልቅ ማንበብ ያለብህ አንተ ነህ፤ መጻሕፍትን በብዛት ማንበብ የሚገባቸው ብዙ የዓለም አሳብ ያላቸው ሰዎች እንጂ በምግባር በትሩፉት የተጠመዱ መነኮሳት አይደሉምና::
📌 ምንጭ
✍️ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (ገብረ እግዚአብሔር ኪደ)
📚"የክርስቲያን መከራ"
═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን
➡️ መሰረተ ሚዲያ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ
👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═/channel/Meseretemedia
ሰው ሃይማኖቱን መጠበቅ የሚችለው ስለ ሃይማኖቱ አምስት ነገሮች ሲያውቅ ነው ፡፡
💠 1/ ምን እንደሚያምን
💠 2/ ለምን እንደሚያምን
💠 3/ ያመነውን እንዴት መፈጸም እንዳለበት
💠 4/ ያመነውን እንዴት ለሌሎች ማሳወቅ እንዳለበት
💠 5/ እምነቱን የሚፈተን ነገር ሲመጣ እንዴት መከላከል እንዳለበት
ማወቅ አለበት
ሃይማኖታችንን ለመጠበቅና በሃይማኖታችን ጸንተን ለመኖር መንፈሳዊ ትምህርትእንማር
መሰረተ ሚዲያ
የቴሌግራም አድራሻ/channel/Meseretemedia
+• የእንባችን ዋጋ ምን ያህል ነው? •+
አንብቡት🙏
🥀አባ አንቶኒ ኮኒያሪስ የተሰኙ የግሪክ ኦርቶዶክስ ካህን በጻፉት "ፊሎካሊያ: የኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነት ቅዱስ መጽሐፍ" (Philokalia: The Bible of Orthodox Spirituality) በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ ለማስተማሪያነት ያሰፈሩት እንዲህ የሚል አንድ ጥንታዊ አፈታሪክ አለ:-
🥀እግዚአብሔር ከዕለታት በአንዱ ቀን ቅዱሳን መላእክቱን "ወደ ምድር ወርዳችሁ ከሁሉ ይልቅ እጅግ ብርቅዬ የሆነውን ነገር ይዛችሁልኝ ኑ" ብሎ ያዛቸዋል::
🥀አንድ መልአክ ሌላ ሰው ለማዳን ብሎ ራሱን መስዋእት ያድረገን ሰው የደም ጠብታን ይዞ ተመለሰ:: እግዚአብሔርም "መልአክ ሆይ ፥ በእርግጥ ይህ በእኔ ዓይን እጅግ የተወደደ ነው:: በዓለም ያለው እጅግ ብርቅዬ ነገር ግን አይደለም::" አለው::
🥀ሌላኛው መልአክ ደግሞ ሌሎችን ስታስታምም በያዛት በሽታ ምክንያት ያረፈችን የአንዲት ነርስ የመጨረሻ እስትንፋስ ይዞ መጣ:: እግዚአብሔርም "መልአክ ሆይ ፥ በእርግጥ ስለሌሎች የሚከፈል መስዋእትነት በእኔ ዓይን እጅግ ታላቅ ዋጋ አለው:: ሆኖም ግን በዓለም ያለው እጅግ ብርቅዬው ነገር ይህ አይደለም" አለው::
🥀በመጨረሻም አንድ መልአክ ንስሃ ገብቶ ወደ እግዚአብሔር የተመለሰን ኃጢአተኛ አንድ ዘለላ እንባ ይዞ መጣ:: እግዚአብሔርም "መልአክ ሆይ ፥ በዓለም ላይ ያለውን እጅግ ብርቅዬ ነገር አመጣህ - ይኸውም የገነትን በር የሚከፍት የንስሃ እንባ ነው!" በማለት ተናገረ::
🥀የጌታ ቃል “እንዲሁ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል።"(ሉቃ 15:10) ብሎ ስለ ንስሃ ዋጋ ይነግረናል:: ንስሃ ደግሞ በተሰበረ ልብና በእንባ ሲሆን ይሰምራልና ፥ በዚህ መንገድ ሆነን ንስሃ ለመግባት እንፋጠን፤ እርሱ ይቅር ይለን ዘንድ ሁሌም ዝግጁ ነውና::
🥀 አምላከ ቅዱሳን ለንስኃ የተዘጋጀ ልብ ይፍጠርልን
ለንስኃ ሞት ያብቃን🙏
ተቀላቀሉ ቴሌግራም
/channel/dnhayilemikael
"ለነፍስህ የምታደርግላት ታላቅ ነገር አለ ይኼውም ራስህን በሚገባ መርምረህ ማወቅ ነው።"
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ
#ፍኖተ #እንድርያስ
ብዙዎቻችን ለብዙ ደቂቃ ስላወራን የሰበክን ሊመስለን ይችላል። ለስብከት አርዓያ ብናደርጋቸው ብዬ የማስባቸው አራት ዓይናውን ሊቅ አቡነ እንድርያስን ነው። ብዙ ጊዜ ሲሰብኩ በቦታ ተገኝቼ ሰምቻለሁ። እኔ በተሳተፍኩባቸው ስብከቶች ረጅም ደቂቃ የሰበኩት 21 ደቂቃ ነው። ነገር ግን ከዐሥር ዓመት በፊት በአጭር ደቂቃ የሰበኩትን ስብከት እስካሁን አስታውሰዋለሁ።
በግሌ ስብከት ከ30 ደቂቃ ባይበልጥ ባይ ነኝ። በሠላሳው ደቂቃ ግን ቧልት፣ ፌዝ፣ ቀልድ ያልተቀላቀለበት ጉዳይ ተኮር፣ ሕይወት ተኮር ስብከት ቢሰበክ መልካም ነው። ስብከት እንዲህ ከሆነ ሥልጠና ግን ቀኑን ሙሉም ቢሰጥ ለውጥ ያመጣል ብየ አስባለሁ። ሥልጠና አንድን ጉዳይ አጥርቶ የማሳወቅ አቅሙ ከፍተኛ ነው።
ዓውደ ምሕረቶች ነገረ ክርስቶስ፣ ነገረ ቅዱሳን፣ ነገረ ማርያም፣ ነገረ ሃይማኖት፣ የሥርዓትና የሥነ ምግባር ትምህርቶች ቢሰጥባቸው አትራፊ እንሆናለን። የሙገሣ የጭብጨባ የግርግር ሰዓት ባይሆኑ ይመረጣል። ብፁዕ አባታችን አቡነ እንድርያስ በስብከት መካከል ጭብጨባንና እልልታን አጥብቀው ይቃወማሉ። እንኳንስ መንፈሳዊ ማዕድ ሥጋዊ ማዕድ ቀርቦ ምግቡ ቢጣፍጠን እንኳ ጣፈጠን ብለን መካከል ላይ እልል አንልም አናጨበጭብም። ምግቡን እያጣጣምን በሥርዓት እንመገባለን። በስብከት ሰዓት ጭብጨባና እልልታ ተገቢ አይደለም።
የጭብጨባና የእልልታ ሰዓት ማኅሌት ነው እንጂ ስብከት አይደለም። ፍኖተ እንድርያስን እንከተል ስል
፩ኛ ስብከታችን አንድን ጉዳይ ዓለማዊ ፍልስፍና ሳንቀላቅልበት እንደእርሳቸው መንፈሳዊውን ጉዳይ አሥርፀን ማጠቃለል ብንችል።
፪ኛ ሰዓት ማርዘም ሳይሆን ማስተማር የፈለግነውን ጉዳይ ግልጽ በሆነ አቀራረብ እስከ ሠላሳ ደቂቃ ባለው መጨረስ ብንችል። ከሠላሳ ደቂቃ በኋላኮ አብዛኛው የመስማት አቅሙ ይቀንሳል።
፫ኛ በስብከታችን መካከል ቧልት፣ ፌዝ፣ ቀልድ ባንቀላቅል።
ማለቴ ነው። የክርስትና ሕይወትና ትምህርት የሚሰለች አይደለም። በሕይወት እየተረጎምነው ስንሄድ ሁልጊዜ አዲስ (እንደገና አዲስ)፣ እያደር አዲስ ነው። የምናውቀውን ታሪክ መምህሩ ሲደግመው ብንሰማ እንኳ በዚህ ታሪክ ምን ያህል እንደተለወጥን ራሳችንን መመርመር ይገባናል።
© በትረ ማርያም አበባው
ደብረ ታቦር
❖በዓለ ደብረ ታቦር የሚውለው በነሐሴ 13 ቀን በመሆኑ ለጾመ ፍልሰታ ሱባዔ ልዩ ምዕራፍ ሆኖ በታላቅ መንፈሳዊ ተመስጦና ማኀሌት ይከበራል። ከዘጠኙ ዐበይት የጌታችን በዓላት አንዱ ነው። ምን አድርጎበታል ቢሉ ብርሃነ መለኮቱን ለሐዋርያት በደብረ ታቦር ገልጾበታል። ደብር ተራራ ታቦር የተራራ ስም ነው። ጌታ በመዋዕለ ስብከቱ ብዙውን ጊዜ የሚያስተምረው ተአምራት የሚያደርገው በተራራ ላይ ነበር። በዚህም ዕለት ዘጠኙን ከእግሩ ደብር ትቶ ሶስቱ ጴጥሮስን ዮሐንሰንና ያዕቆብን አስከትሎ ከርእሰ ደብር ወጣ። ወተወለጠ ራዕዩ በቅድሜሆሙ ወአብርሀ ገጹ ከመ ፀሐይ ወአልባሲሁኒ ኮነ ጸዓዳ ከመ በረድ ይላል መልኩ ተለውጦ ፊቱ እንደ ጸሐይ አብርቶ ልብሱ እንደ በረድ ነጽቶ ሙሴና ኤልያስ በቀኝ ሆነው ታዩአቸው። ሙሴንና ኤልያስን መምረጡ ስለምንድነው ቢሉ ሙሴ 570 ጊዜ ቃል በቃል ተነጋግሮ ባይህ እወዳለሁ አለው ፊቴን አይቶ አንድ ሰዓት እንኳ መቆም መቆየት የሚቻለው የለም አለው ። ይህማ ካልሆነማ ባለሟል መባሌ ምኑ ላይ ነው። ቢለው ኃላ ሰው ሆኜ ስመጣ እታይሃለው ብሎት ነበርና ዘጸ 33:18-23 ነው። ያን ለመፈጸም ኤልያስም እንዲሁ ተስፋ ነበረውና አንድም ጌታ ዕውር ቢያበራ ሙት ቢያነሳ ሙሴ ነው ኤልያስ ነው ብለውት ነበርና የኛን ጌታ ማን ሙሴ ማን ኤልያስ ይልሀል የሙሴ የኤልያስ ጌታ ይበሉህ እንጂ ብለው እንዲመሰክሩ አምጥቷቸዋል። ፍጻሜው ግን ደብረ ታቦር የመንሥተ ሰማያት ምሳሌ ናት። ሕጋውያንም ደናግልም እንዲወርሷት ለማጠየቅ ከሕጋውያን ሙሴን ከደናግል ኤልያስን አመጣ። ጴጥሮስ እመሰ ትፈቅድ ንንበር ዝየ ወንግበር ሠለስተ ማኅደረ አሐደ ለከ አሐደ ለሙሴ ወአሐደ ለኤልያስ ብትወድስ አንዱን ላንተ አንዱን ለሙሴ አንዱን ለኤልያስ ሶስት ጎጆ ሠርተን በዚህ እንኑር አለው። መጽአ ደመና ብሩህ ወጸለሎሙ ይላል ። ይህን ሲናገር ብሩህ ደመና መጥቶ ጋረዳቸው ወዲያውም ዝንቱ ውእቱ ዘአፈቅር ወሎቱ ስምዕዎ ቢሉ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው። እሱን ስሙት የሚል ድምፅ ከወደ ላይ ተሰምቷል ።እነ ጴጥሮስ ደንግጠው ወደቁ ተንሥኡ ወኢትፍርሁ ብሎ አንስቷቸዋል ። ከርእሰ ደብር ሲወርዱም ያዩትን የሰሙትን እስከ ትንሳኤው ለማንም እንዳይናገሩ አዟቸዋል ።ማቴ 17 :3-9 ዘጠኙን በእግረ ደብር ትቶ ሶስቱን አስከትሎ መውጣቱ ስለምንድነው ቢሉ ከዘጠኙ ብርሃነ መለኮት ሊያይ የማይገባው ይሁዳ ነበርና ትቶትም ቢሄድ ለየኝ ባለ ነበርና አንድም ጴጥሮስ እሞታለሁ እነሣለሁ ቢለው ካንተ ይራቅ ብሎት ነበርና እሱን ስሙት የሚለውን እንዲሰማ አምጥቶታል። ዮሐንስና ያዕቆብንም በመንግሥቱ በመጣ ጊዜ በቀኝ በግራ መቀመጥን ሽተው ነበርና ነው። ያስ ቢሆን ከተራሮች ሁሉ ታቦርን ስለምን መረጠ ቢሎ ዳዊት ታቦር ወአርሞንኤም በስመ ዚአከ ይትፌስሑ መዝ 87:12ብሎ ያን ለመፈጸም ነው።
†††እንኳን ለቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ : ቅዱስ ዋርስኖፋ እና አባ ዮሐንስ ዘጐንድ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን። †††
†††በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
††† ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ †††
††† ቅዱሳን ሐዋርያት አባቶቻችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በተከተሉበት ሰዓት እድሜአቸው በ3 ደረጃ የተከፈለ እንደ ነበር የቤተ ክርስቲያን ትውፊት ያሳያል:: እንደ ዮሐንስ ወንጌላዊ ያሉት በ20ዎቹ ውስጥ : ቅዱስ ታዴዎስን የመሰሉት ደግሞ በ30ና በ40ዎቹ ውስጥ የነበሩ ሲሆን እነ ቅዱስ ዼጥሮስ ደግሞ በ50ዎቹ ውስጥ የሚገኙ ነበሩ::
ደቀ መዛሙርቱ ከወጣቶችም : ከጐልማሶችም : ከአረጋውያንም የተዋቀሩ ነበሩ ማለት ነው:: ቅዱስ ታዴዎስ በቀደመ ስሙ ልብድዮስ ይባል የነበረ ሲሆን በአንዳንድ መጻሕፍት ውስጥ (በተለይ በምሥራቅ ኦርቶዶክሶች) ስምዖን እና ይሁዳ እየተባለም ተጠርቷል::
ቅዱሱ ጌታችን ተከትሎ : ከ12ቱ አንዱ ሆኖ በፈጣሪው ተመርጦ : 3 ዓመት ከ3 ወር ከጌታ እግር ተምሮ : በዕርገቱ ተባርኮ : በበዓለ ሃምሳም 71 ልሳናትን ተቀብሎ : ሐዋርያት ዕጣ ሲጣጣሉ የበኩሉን አሕጉረ ስብከት ተካፍሎ ዓለምን ዙሯል::
ቅዱስ ታዴዎስ እስከ እርጅናው ድረስ ለወንጌል ሲተጋ ኑሯል:: ጌታችንም በየጊዜው በአካል እየተገለጸ አጽናንቶታል:: ከብዙ የድካምና የመከራ ዘመናት በሁዋላም ሐምሌ 2 ቀን ዐርፏል::
ቅዱሱ ሐዋርያ ያረፈው ሶርያ ውስጥ ሲሆን ከ250 ዓመታት በሁዋላ ቤተ ክርስቲያኑ ታንጾለት በዚህች ቀን ወደ ቁስጥንጥንያ ፈልሷል:: ይህንን ያደረገው ደግሞ ታላቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ነው:: ከሐዋርያው ዘንድም ብዙ ተአምራት ተደርገዋል::
††† ቅዱስ ዋርስኖፋ ሰማዕት †††
††† ቅዱሱ በትውልድ ግብፃዊ ሲሆን ገና ከልጅነቱ ጣዕመ ክርስትና የገባው ነበር:: መጻሕፍትን በማንበብ: ክርስትናንም በመለማመድ ስላደገ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት የመወደድ ሞገስ ነበረው:: በእድሜው እየጐለመሰ ሲሔድ በተጋድሎውም እየበረታ ሔደ::
በወቅቱ እርሱ የነበረባት ሃገር ዻዻስ በማረፉ ሊቃውንቱና ሕዝቡ ተሰብስበው አምላክን ጠየቁ:: እንደሚገባም መከሩ:: በደንብ አስተውለዋልና እንደ አንድ ልብ መካሪ: እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሁነው ሁሉም ቅዱስ ዋርስኖፋን መረጡ::
ዛሬን አያድርገውና በአባቶቻችን ዘመን ሕዝቡም ሆነ ሊቃውንቱ መሪ መምረጥን ያውቁ ነበር:: ተመራጮቹ ደግሞ እንኩዋን እንደ ዘመናችን "ሹሙኝ : ምረጡኝ" ሊሉ በአካባቢውም አይገኙም ነበር::
ቅዱስ ዋርስኖፋ ለዽዽስና እንደ መረጡት ሲያውቅ "ጐየ" እንዲል መጽሐፍ: ጨርቄን ማቄን ሳይል በሌሊት ጠፍቶ በርሃ ገባ:: (እንዲህ ነበሩ አበው) በገባበት በርሃ ውስጥ በዓት ሠርቶ በጾም: በጸሎትና በስግደት በርትቶ ዓመታትን አሳለፈ:: እርሱ በበርሃ እያለ ዘመነ ሰማዕታት ጀምሮ ብዙ ክርስቲያኖች አልቀው ነበር::
እርሱ ግን ከዓለም ርቁዋልና ይህንን አላወቀም ነበር:: አንድ ቀን መልአከ እግዚአብሔር መጥቶ "አንተ በስሙ ደማቸውን ለሚያፈሱ አክሊላት እየታደለ : ሰማያዊ ርስትም እየተካፈለ ነውኮ! አልሰማህም?" አለው::
ቅዱስ ዋርስኖፋም "ለካም እንዲህ ያለ ክብር አምልጦኛል" ብሎ: በርሃውን ትቶ ወደ ከተማ ወጣ:: መልአኩ እንዳለውም ክርስቲያኖች ሲሰቃዩ ደረሰ:: ቅዱሱም ሳያመነታ ስመ ክርስቶስን ሰብኮ: ብዙ ተሰቃይቶ በዚህች ቀን አክሊለ ሰማዕትን በአክሊለ ጻድቃን ላይ ደርቧል::
††† እጨጌ አባ ዮሐንስ ዘጐንድ †††
††† ጻድቁ ተወልደው ያደጉት በኢየሩሳሌም ሲሆን ነገዳቸውም እሥራኤላዊ ነው:: ነገር ግን ተጋድሏቸውን የፈጸሙት በሃገራችን ኢትዮዽያ ውስጥ ነው:: እጨጌ አባ ዮሐንስ ከአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቀጥሎ ባለ ረዥም እድሜ ጻድቅ መሆናቸው ይነገራል::
አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ያረፉት በ562 ዓመታቸው ሲሆን እጨጌ አባ ዮሐንስ ደግሞ በ500 ዓመታቸው ነው:: የሚገርመው ጻድቁ የታላላቁ ጻድቃን ገብረ መንፈስ ቅዱስ : ተክለ ሃይማኖት: ሳሙኤል: ዜና ማርቆስ እና ሌሎችም ባልንጀራ ነበሩ::
በዛ ዘመን ዘረኝነት በቅዱሳኑ ዘንድ አልነበረምና ነጭ ሆነ ጥቁር : ከየትም ይምጣ የሰው ልጅ መሆኑ ብቻ በቂ ነበር:: እጨጌ አባ ዮሐንስ በሃገራችን 5 በዓቶች የነበሯቸው ሲሆን በአንድ በዓት የሚኖሩት ለ50 ዓመት ነበር::
በዚህም በኢየሩሳሌም ለ50 ዓመት : በኢትዮዽያ ደግሞ ለ450 ዓመታት ኑረዋል:: ከበዓቶቻቸው አንዱ ደብረ ሊባኖስ ሲሆን በገዳሙ ለ50 ዓመታት አበ ምኔት(እጨጌ) ሆነው አገልግለዋል:: "እጨጌ" የሚባሉትም በዚህ ምክንያት ነው::
ጻድቁ የመጨረሻ ዘመናቸውን ያሳለፉት በጐንድ (ጉንድ) ተክለ ሃይማኖት ገዳም ነው:: ገዳሙ የሚገኘው በሰሜን ጐንደር ዞን : በለሳ ወረዳ ውስጥ ሲሆን የመሠረቱትም ራሳቸው ናቸው:: ነገር ግን በራሳቸው እንዲጠራ አልፈለጉምና ገዳሙ የሚጠራው በወዳጃቸው በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ስም ነው::
ጐንድ እኛ ኃጥአን ሳይገባን ያየነው ገዳም ነው:: ዛሬም ድረስ ድንቅ የሆኑ አበው የሚኖሩበት : ተአምራትም የማይቋረጥበት : ፈዋሽ ጠበል ያለው ደግ ገዳም ነው:: ጻድቁ እጨጌ አባ ዮሐንስ ግን አስታዋሽ አጥተው እየተዘነጉ ካሉ ቅዱሳን አንዱ ናቸው:: ምንም ዛሬ አጽማቸው ፈልሶ ወደ ደቡብ ኢትዮዽያ አካባቢ ቢሔድም እርሳቸው በ500 ዓመታቸው ያረፉት በዚህ ገዳም ውስጥ ነው::
††† እግዚአብሔር ከሐዋርያው : ከሰማዕቱና ከጻድቁ ክብርን : በረከትን ያሳትፈን::
††† ሐምሌ 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ (ፍልሠቱ)
2.ቅዱስ ዋርስኖፋ ሰማዕት
3.እጨጌ አባ ዮሐንስ (ዘጐንድ)
††† ወርኀዊ በዓላት
1.የፈጣሪያችንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት
2.ቅድስት አርሴማ ድንግል
3.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት
4.ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
5.ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት
6.ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ (ጻድቅና ሰማዕት)
††† "ለመንጋው ምሳሌ ሁኑ እንጂ ማሕበሮቻችሁን በኃይል አትግዙ:: የእረኞችም አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብርን አክሊል ትቀበላላችሁ:: እንዲሁም ጐበዞች ሆይ! ለሽማግሌዎች ተገዙ:: ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ:: እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና:: ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል::" †††
(1ዼጥ. 5:3)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
🌧☔️
በአንድ ሀገር ዝናብ ጠፋና ህዝቡ ሁሉ ተጨነቀ በመጨረሻም ምህላ እንዲደረግ ተወሰነ።
ህዝቡ ሁሉ ወደ ቤተክርስትያን ጉዞ ጀመረ አንዲት ህፃን ግን በጉዞው መሃል ዣንጥላ ይዛ ነበር። ለምን እንደያዘች ስትጠየቅ ወደ ቤተክርስትያን እምንሄደው ዝናብ እንዲዘንብ ለመለመን አይደለም? ታዲያ ስንመለስ በምን እንጠለላለን ስትል መለሰች።
ስለዚህች ህፃን እምነት በዛች ቀን ዝናብ ዘነበ ህዝቡ ሁሉ በዝናብ ሲደበደብ እርሷ ግን በያዘችው ዣንጥላ ተጠልላ ነበር።
ብዙዎቻችን የዚችን ህፃን ያህል ቅንጣት ታህል እምነት የለንም፣ ብዙ ነገር እንጠይቃለን የጠየቅነው ነገር እንደሚሰጠን ግን እርግጠኛ ሆነንና ተዘጋጅተን አንጠብቅም።
ከአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ የተወሰደ
አምላከ ህጻናት ክብር ምስጋና ይድረሰው!!
ተወዳጆች ሆይ እኛስ በእምነታችን ምን ትሩፋት አገኘን?
ቅዱሳንን ማክበር ጥቅሙ ለማን ነው?
ፀሐይን የሚያይ ሰው የፀሐይቱን ብርሃን ይበልጥ ብሩህ እንዲኾን
አያደርገውም፤ የገዛ ራሱን የማየት ዓቅሙን እንዲጨምር ያደርጋል
እንጂ፡፡ ልክ እንደዚሁ፡ ሰማዕታትን (ቅዱሳንን) የሚያከብር ሰውም
ሰማዕታቱን ይበልጥ እንዲከበሩ አያደርጋቸውም፤ እርሱ
ከሰማዕታቱ (ከቅዱሳኑ) የሚቀድስ በረከትን ይቀበላል እንጂ፡፡
#ሺ_ዓመት_አይኖር
🥀ብዙ ጊዜ ለስንፍናችን ምክንያት ወይም ተስፋ ለመቁረጥ ሰበብ ከሚሆኑን ነግሮች አንዱ "ሺ ዓመት አይኖር" የሚለው አባባል ነው በእርግጥ በምድር ሺ ዓመት መኖር የቻለ የለም ረጅም ዓመት እንደኖረ የሚነገርለት ማቱሳላ እንኳን ሺ ዓመት አልኖረም ወዳጄ በተለይ እኛ ባለንበት በዚህ ዘመን ደግሞ እንኳን ሺ ዓመት ሊኖር ቀርቶ መቶ የሞላ እንኳን ቢገኝ የሚድያ የአንድ ወቅት የዜና ሽፋን መሆኑ የማይቀር ነው ስለዚህ ወደ ዘመናችን አባባሉን ማምጣት ከፈለግን መቶ ዓመት አይኖር በሚል ልንቀይረው ያስፈልጋል።
🥀የሚያሳዝነው ሺ ዓመት አይኖር የምንለው ለመዝናናት ለመጨፈር ራስን ለመርሳት ፈቃደ ሥጋን እንደ ልብ ለመፈጸም ብቻ እንጂ ለመንፈሳዊ ሕይወት ለመሰናዳት አይደለም "አንቂ" የሚባሉ አካላት የዕድሜህን አጫርነት የሚነግሩህ ከሞት በኋላ ላለው ረጅሙ ዕድሜ በዚህች በአጭሯ የምድር ዕድሜህ በጎ ሰርተህ እንድታልፍ ሳይሆን እንዳትጨናነቅ ፈታ ብለህ(በእነርሱ አማርኛ) እንድትኖር ለማስታወስ ብቻ ነው።
🥀ወዳጄ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት ግን በምድር ስለምትኖርበት ዕድሜህ ሲነግርህ ቢበዛ(ቢበረታ) ሰማንያ ይልሃል ሺ ዓመት አይኖር ሲሉህ ቢበዛ ሰማንያ እርሱም በተገኘ በላቸው ታድያ በምድር የምትኖርበት ዕድሜህ ጥቂት ከሆነ ከዚያ በኋላ በሞት ይህን ምድር ከተሰናበትክ ከሞት በኋላ የት ትሄድ ይሆን?? የዚህ ምድር ኑሮህ በሞት ከተቋጨ በኋላ ሞተህ የምትቀር መስሎ እንዳይሰማህ ከሞት በኋላ ሕይወት አለህ ያውም እንደሰው ኖረህ ከሞትክ የምትነሳው እንደ ሰው ሆነህ የምትኖረውን ሕይወት ለመድገም
🥀እንዳይመስልህ ከትንሣኤ በኋላ የምትኖረው እንደ መላእክት ነው “በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ”ማቴ 22፥30
ስለዚህ አስታውስ የምድር ኑሮህ ቢበዛ ሰማንያ ነው ያ ማለት ጥቂት ነው መጽሐፍ
እንደሚነግርህ
🥀ሕይወታችሁ ምንድር ነው ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና”
ያዕ 4፥14
🥀ስለዚህ በምድር የምትቆየው ጥቂት ጊዜ ነውና:-*
ዛሬ የንስሐ አባት ያዝ
ዛሬ ንስሐ ግባ
ዛሬ ከተጣላሃቸው ታረቅ
ዛሬ ያስቀየምካቸውን ይቅር በል
ዛሬሥጋ ወደሙን ተቀበል
ነገ ሳይሆን ዛሬ መልካም ነገሮችህን ሁሉ ጀምር ምክንያቱም
“እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።”
2ኛ ቆሮ 6፥2 የሞዐ
Join ቴሌግራም ቻናል
አምላከ ቅዱሳን ለንስሐ የተዘጋጀ ልብ ያድለን
ለንስሃ ሞት ያብቃን🙏
❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን
➡️ መሰረተ ሚዲያ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ
👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═/channel/Meseretemedia
📌 "አስታውስ"
➯ ደካማነትህን አስታውስ፣ ያንጊዜ በጣም ጠንቃቃ ትሆናለህ፣ ሊጎዱህ በሚችሉ በትምክህትና በውዳሴ ከንቱም አትሸነፍም፡፡
➯ የተሰጠህን በፍቅር የተሞላ የእግዚአብሔርን ቸርነት አስታውስ፣ ይህም በምስጋና የተሞላ ሕይወት እንድትመራ ያደርግሃል፤ በእግዚአብሔር ፍቅርና ሥራ ላይ ስትታመን ፍጹም የሆነ እምነት በልብህ እያደገ ይመጣል፤ ከእግዚአብሔር ጋር ያሳለፍከው ጊዜ ደግሞ በእምነት እንድትኖር ያበረታታሃል፡፡
➯ የሰዎችን ፍቅርና ካንተ ጋር ያሳለፉትን መልካም ጊዜ አስታውስ፤ የሰዎችን ቀናነት ትጠራጠር ዘንድ ወይም ያደረጉብህን ክፉ ነገር ታስብ ዘንድ ይገባሃልን? የቀደመ ፍቅራቸው ስለ እነርሱ ይማልዳል ያንተንም ቁጣ ያበርዳል፡፡
➯ ሞት እንዳለ አስታውስ፣ እንዲሁ በዓለም ያለ ፈተናም እንደሚያልፍ
✍️"ሁሉ ከንቱ ነው፣ ነፋስንም እንደመከተል ነው፡፡" ማለትን ትረዳለህ፡፡
📖መኬ 1፥14
➯ በእግዚአብሔርፊት መቆምህንና እርሱም እንደሚመለከትህ አስታውስ፣ ያኔ ኃጢአት አትሰራም እግዚአብሔርን ታየዋለህና፡፡
➯ ስለ አንተ የፈሰሰውን የክርስቶስን ክቡር ደም አስታውስ፤ በዚህም ሕይወትህ ያለውን ዋጋ በእርግጥ ታውቃለህ፤ በዓይኖችህ ፊት የከበረ ይሆናል፣ ስለዚህም በከንቱ በመኖር አታጠፋውም፣
✍️"በዋጋ ተገዝታችኋልና" እንዲል ቅዱስ ጳውሎስ፡፡
📖1ኛ ቆሮ 6፥20
➯ በወላጆችህ እምነት በተጠመቅህባት ቦታ ለእግዚአብሔር የገባኸውን ቃል አስታውስ፤ ዲያብሎስን፣ ሥራዎቹን ሁሉ፣ ሐሳቦቹንና ጥበቡን፣ ኃይሉንም ትክድ ዘንድ፡፡
➯ በዚህ ዓለም እንግዳመሆንህንና ወደ ሰማያዊው ቤትህ እንደምትመለስ ዘወትር አስታውስ፤ ያን ጊዜ በዚህ ዓለምና በደስታው ተስፋ ማድረግን ትተዋለህ፡፡
➯ በጠባቡ በር መጓዝ ወደ መንግስተ ሰማያት እንደሚያደርስህ አስታውስ፤ ሰፊው ደጅ ፊት ለፊትህ ተከፍቶ ብታየው፣ አልፈኸው ሂድ ከእሱም ራቅ፣ በእርሱ የሄዱ እንዳሉ አልቀዋልና፤ ዘላለማዊው ሕይወትህን አስታውስ፣ ሁልጊዜም ስለዚህ ትጋ፡፡
➯ የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህንና እርሱን መምሰል እንዳለብህ አስታውስ፤ እውነተኞች ከሆኑት ከእግዚአብሔር ልጆች ጋር አካሄድህን አስተካክል፡፡
➯ የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ መሆንህን አስታውስ፡፡ በውስጥህ ያለውንም ቅዱሱን የእግዚአብሔር መንፈስ አታሳዝን፤ ዘወትርም ቅዱስ የእግዚአብሔር ማደሪያ ሁን፡፡
📌 ምንጭ
✍️አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
አባታዊ ምክር
✥እኔ አባታችሁና መምህራችሁ ነኝ፥ ሁላችሁ ልጆቼ ትእዛዜን አዳምጡ፤ በቅድስት ሥላሴ ማመንን እንድትከተሉና እንድትጸኑ እነግራችኋለሁና፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ እርስ በእርሳችሁ በእውነተኛ ፍቅር ትዋደዱ ዘንድ እለምናችኋለሁ።
✥የተወደዳችሁ ልጆቼ በፍጹም ሰብአዊነት መልካምን አንድታደርጉ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ ዓለም እንድታታልላችሁ አትፍቀዱላት፤ በእግዚአብሔር አገልግሎት ዳተኞችና ቸልተኞች አትሁኑ ብዬ እለምናችኋለሁ።
✥የተወደዳችሁ ልጆቼ ፡ እና ያለ መታከት እንድትጸልዩ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ መለያየትን ከሚያመጣ ንግግር አንደበታችሁን እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።፡
✥የተወደዳችሁ ልጆቼ የተጠመቃችሁባትን ቅድስቲቱን ጥምቀት እንድትጠብቋት እለምናችኋለሁ፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ ሰውነታችሁን ለጌታ ንጹሕ አድርጋችሁ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።
✥ልጆቼ መብራታችሁ ፈጽሞ እንዲጠፋ አትፍቀዱ ይልቅስ ብርሃንን እንዲሰጥ እንድታደርጉት እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ እግዚአብሔር የሰጣችሁን ትእዛዝ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።
✥ልጆቼ እግዚአብሔርን መፍራት ከእናንተ ጋር እንዲሆን እለምናችኋለሁ፤ የነገርኳችሁን ሁሉ ከጠበቃችሁ የእባቡንና የዘንዶውን ራስ ትቀጠቅጣላችሁ፤ ያልኋችሁን ካደረጋችሁ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ ብርሃናዊያን ኪሩቤል ይጠብቋችኋል፡፡
✥ ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ✥
ሰኔ ፴ ልደቱ ለመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ
👉በንጉሥ ሄሮድስ ዘመን ዘካርያስ የሚባል ካህን ነበር፤ ሚስቱም ኤልሣቤጥ መካን ስለነበረች ልጅ አልነበራቸውም፤ እርሷም የመውለጇ ዘመን አልፎ ነበር፡፡ ሆኖም ሁለቱም በእግዚአብሔር የታመኑ ጻድቃን ነበሩ፡፡
👉ከዕለታት በአንድ ቀንም ካህኑ ዘካርያስ ወደ ቤተ መቅደስ ለአገልግሎት በገባበት ሰዓት በዕጣን መሠውያው በቀኝ በኩል የእግዚአብሔር መልአክ ቆሞ ታየው፤ እንዲህም አለው ‹‹ዘካርያስ ሆይ፥ አትፍራ፤ ጸሎትህ በእግዚአብሔር ፊት ተሰምቷልና፤ ሚስትህ ኤልሣቤጥም ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልድልሃለች፤ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ፡፡ ደስታና ሐሤትም ይሆንልሃል፤ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል፡፡ እርሱ በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ ይሆናልና የወይን ጠጅና የሚያሰክርም መጠጥ ሁሉ አይጠጣም፤ ከእናቱ ማሕፀን ጅምሮም መንፈስ ቅዱስ ይመላበታል፡፡ ከእስራኤልም ልጆች ብዙዎቹን ወደ አምላካቸው ወደ እግዚአብሔር ይመልሳቸዋል፡፡ እርሱም የአባቶቻችን ልብ ወደ ልጆች፥ የከሓዲያንንም ዐሳብንም ለእግዚአብሔር የተዘጋጀ ያደርግ ዘንድ በኤልያስ መንፈስ ቅዱስና ኃይል በፊቱ ይሄዳል፡፡›› ዘካርያስም መልአኩን እንዲህ አለው፤ ‹‹ይህ እንደሚሆን በምን አውቃለሁ? እነሆ፥ እኔ አርጅቻአለሁ፤ የሚስቴም ዘመንዋ አልፏል፡፡›› መልአኩም እንዲህ ብሎ መለሰለት፤ ‹‹እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፤ ይህንም እነግርህና አበሥርህ ዘንድ ወደ አንተ ተልኬአለሁ፡፡ አሁንም በጊዜው የሚሆነውንና የሚፈጸመውን ነገሬን አላመንኽኝምና ይህ እስኪሆን ድረስ ዲዳ ትሆናለህ፤ መናገርም ይሳንሃል፡፡›› (ሉቃ.፩፥፲፫-፳)
👉ከዚህም በኋላ ሚስቱ ኤልሣቤጥ ፀነሰች፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ፀንሳ እናቱ ኤልሣቤጥን ለመጠየቅ በሄደችበት ወቅት በማሕፀኗ ውስጥ ሳለ ሕፃኑ ለእግዚአብሔር ልጅ ሰገደ፡፡ (ሉቃ.፩፥፴፱-፵፩)
👉ኤልሣቤጥ የመውለጃዋ ጊዜ በደረሰ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች፡፡ መውለዷን የሰሙ ዘመዶቿና ጎረቤቶቿም ደስ ተሰኙ፤ ልጁንም ስምንት ቀን በሞላው ጊዜ ሊገረዙት መጡ፤ ስሙንም በአባቱ ስም ዘካርያስ ብለው ሊሰይሙት ወደዱ፤ ነገር ግን እናቱ ዮሐንስ ተብሎ መጠራት እንዳለበት ተናገረች፡፡ ሆኖም ግን ከዘመዶቿ መካከል ስሙ ዮሐንስ የሚባል ባለመኖሩ አባቱ እንዲወስን ካህኑ ዘካርያስን በጠየቁት ጊዜ መናገር የተሣነው ዲዳ ነበርና ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ሲጽፍ ሁሉም ተደነቁ፤ በዚያን ጊዜም የዘካርያስ አንደበት ተፈታ፤ እግዚአብሔርንም አመሰገነ፡፡
👉ካህኑ ዘካርያስም መንፈስ ቅዱስ በመላበት ጊዜ እንዲህ ብሎ ትንቢት መናገር ጀመረ፤ ‹‹ይቅር ያለን፥ ለወገኖቹም ድኅነትን ያደረገ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ይመስገን፤ ከባርያው ከዳዊት ቤት የምንድንበትን ቀንድ አስነሣልን፤ ከጥንት ጀምሮ በነበሩ በቅዱሳን በነቢያት አፍ እንደ ተናገረ፡፡ ከጠላቶቻችን እጅ፥ ከሚጠሉንም ሁሉ እጅ ያድነን ዘንድ፤ ቸርነቱን ከአባቶቻችን ጋር ያደርግ ዘንድ፤ ቅዱስ ኪዳኑንም ያስብ ዘንድ፤ ለአባታችን ለአብርሃም የማለውን መሐላ ያስብ ዘንድ፤ ከጠላቶቻችን እጅ ያድነን ዘንድ ያለ ፍርሃት፥ በቅድስናና በጽድቅ በፊቱ በዘመናችን ሁሉ እንድናመልከው ይሰጠን ዘንድ፤ አንተም ሕፃን፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፡፡ መንገዱንም ትጠርግ ዘንድ በፊቱ ትሄዳለህና፡፡ ኃጢአታቸው ይሰረይላቸው ዘንድ መድኃኒታቸውን እንዲያውቁ ለአሕዛብ ትሰጣቸው ዘንድ፤ ከአርያም በጎበኘን በአምላካችን በይቅርታውና በቸርነቱ፤ በጨለማና በሞት ጥላ ለነበሩት ብርሃኑን ያሳያቸው ዘንድ፥ እግሮቻቸውንም ወደ ሰላም ጎዳና ያቀና ዘንድ ወጣ፡፡›› ሉቃ.፩፥፷፰-፸፱
የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አማላጅነት እና ተራዳኢነት አይለየን፤ ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን!
/channel/dnhayilemikael
ቀናችንን በጸሎት እንጀምር
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
ማንም ኋለኛ ነኝ ብሎ ተስፋ አይቁረጥ
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
❖ ከመጀመሪያ ጀምሮ መልካም ነገርን መምረጥ መልካም ነው፤ በመልካምነት አለመቀጠል ግን ብዙ ወቀሳን ያመጣል፤ የብዙ ሰዎች ክፉ መኾን በዚሁ የሚመደብ ነው ፤ ብዙዎች ሕይወታቸውን በመልካም ጀምረው በኋላ ግን በክፋት መርዝ ተጠምቀው ሲሰክሩ ተመልክቻለሁ፡፡
❖ እናንተ ግን እንዲህ አትሁኑ ምንም እንኳን አሁን ወደ ክፋት ጥልቅ ወርዳችሁ ቢኾንም
✍️"ከዚሁ ተመልሰን መውጣት አይቻለንም ፤ መለወጥም አይኾንልንም" በማለት ተስፋ የምትቆርጡ አትኹኑ፤ እናንተ ስትፈቅዱ እግዚአብሔርም ሲረዳችሁ ከክፋት ዐዘቅት መውጣት በእጅጉ ቀላል ነውና፡፡
❖ ከኹሉም በላይ አመንዝራ ተብላ በከተማው ትታወቅ የነበረችውን ሴት በመልካምነቷ እንዴት እንደምትወደስ አልሰማችሁምን? እየነገርኳችሁ ያለሁት በወንጌለ ዮሐንስ ስለተጠቀሰችው ሴት አይደለም ፤ በእኛ ዘመን ስላለችውና ፍኒሳ ከተባለችው ክፉ ከተማ ስለተገኘችው ሴት እንጂ ይህቺ ሴት አስቀድማ በመካከላችን በአመንዝራነቷ ትታወቅ ነበር፤ በክብር ቦታ ሁሉ የመጀመሪያውን ስፍራ የምትይዝ ሴት ነበረች፤ ስሟ በሀገሩ ሁሉ የገነነ ነበር በእኛ ዘንድ ብቻ ሳይሆን በሲልስያና በቀጰዶቅያም የታወቀ ነበር፡፡
❖ ይህቺ ሴት ብዙ ከተሞችን አፍርሳለች ፤ የብዙ ወላጅ አልባ ሕፃናትን ንብረት በልታለች፤ ብዙዎች "መተተኛ ናት" ይሏታል ውበቷን ብቻ ሳይኾን መድኃኒትም ጭምር ትጠቀም ነበርና፡፡
❖ ከዚሁ የተነሣ በአንዱ ቀን የንግሥቲቱን ልጅ እስከ ማማለል ደርሳለች፤ ጭካኔዋ ክፉ የክፉ ክፉ ነበር፤ ከዕለታት በአንዲቱ ቀን ግን ማመን እስኪያቅተኝ ድረስ ተለውጣ አየኋት፤ ራሷን በእግዚአብሔር የጸጋው ዙፋን ፊት ድፍት ብላ ስታለቅስ አየኋት አሁን የቀድሞ ክፉ ሥራዎቿ ኹሉ ርግፍ አድርጋ ትታለች በእርሷ ላይ ከነበሩት አጋንንት ጭፍራ ተፋትታ የክርስቶስ ሙሽሪት ኾናለች፡፡
❖ በእውነት ከእርሷ የሚከፋ ሰው በዓይኔ አላየሁም አሁን ግን ራሷን ከእንደዚህ ዓይነቱ ክፉ ሥራ ከልክላለች፤ ከዚህ በፊት ስትለብሳቸው የነበሩት የምንዝር ጌጦች ስፍር ቁጥር የላቸውም አሁን ግን እነዚህን ኹሉ አወላልቃ ጥላ ለእግዚአብሔር በሚገባ የማቅ ልብስ ራሷን የክርስቶስ ደቀ መዝሙር አድርጋለች፡፡
❖ ይህቺን ሴት ወደ ቀድሞ ሕይወቷ ለመመለስ የሀገሪቱ መኳንንት ከዙፋናቸው ወርደው ለምነዋት ነበር ወታደሮች ከነትጥቃቸው መጥተው አስፈራርተው ሊወስዷት ሞክረው ነበር፤ ነገር ግን ወደ ቀድሞ ሕይወቷ ይመልሷት ዘንድ አልተቻላቸውም፡፡
❖ ይህቺ ሴት ከዚያ አስነዋሪ ሕይወቷ ተመልሳ ለቅዱስ ቁርባን በቅታለች፤ ለእግዚአብሔር ጸጋ የተገባች ኾና ተገኝታለች ኃጢአቷን ኹሉ በጸጋው አጥባለች ከተጠመቀች በኋላ ራሷን መግዛት ችላለች፤ ይህቺ ሴት የቀድሞ ሕይወቷን ፣ ገላዋን ለብዙ ወዳጆቿ ያሳየችበትን ሕይወት "የእስር ቤት ሕይወት" ብላ ትጠራዋለች፤ በእውነት "ኋለኞች ፊተኞች ይኾናሉ ፤ ፊተኞችም ኋለኞች ይኾናሉ" የሚለው የከበረ ቃለ ወንጌል በእርሷ ሲፈጸም አየነው፤ መለወጥ ከፈለግን እኛን ማሰናከል የሚቻለው ኃይል እንደሌለ ዐወቅን ፤ ተረዳን፡፡
❖ እንኪያስ እኛም ተስፋ በመቁረጥ ፥ በኃጢአት ዐዘቅት ሰምጠን የምንቀር አንኹን፤ ከእኛ መካከል በጽድቅ በረኻነት የሚኖር ማንም አይገኝ ፊተኛ ነኝ የሚል ማንም አይገኝ ፤ ብዙ አመንዝሮች እርሱን አልፈውት ሊሔዱ ይችላሉና፤ ማንም ኋለኛ ነኝ ብሎ ተስፋ አይቁረጥ ፤ ከልቡ ከተጸጸተና ከተመለሰ ፊተኛ መኾን ይቻለዋልና፡፡
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"
📖ምሳ 1፥33
📌 ምንጭ
✍️ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝
🙏 ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ፤ እኔም ለእናንተ ከአዘጋጀው በኃዋላ በድካሜ ብዛት ሳይገባኝና ሳይገባኝ በምጽፈው ድርሳንወ ገድላት መጽሐፍት ላይ የቃላት (የፊደል) ሕፀፅ ቢገኝ በጎደለው እየሞላችሁ በጠመመው እያቃናችሁ አንብቡ በረከት ተካፈሉ እላለሁ ከምንም ጊዜ በላይ ለሀገራችንና ለዓለም ሰላም እንዲሁም ለደካማው ወንድማችሁ እንድበረታ (የተጣልሁ) እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ
✍"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን"
📚ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን
───────────
Channel
/channel/dnhayilemikael
ብሒለ አበው
❖እግዚአብሔር የአንተን ድካም ስህተት ጉድለት እንደተሸከመ ሁሉ አንተም የሌሎችን ተሸከም᎓᎓
❖እግዚአብሔር በራሱ ሁሉን ማድረግ ይችላል፤ አንተ ግን አብረኸው ትሠራ ዘንድ ይሻል፣ እንድትሠራ ብቻ አይደለም
እንድትለፋ እንድትጥርም ነው እንጂ።
❖እግዚአብሔር ከእርሱም በፊት ሓላፊነት እንድትወስድባት ነፍስህን አደራ ሰጥቶሃል፤ ታዲያ ለአደራው ታማኝ እንደሆነ ባለአደራ ለዚህ ጊዜ ሰጥተሃል ወይስ በሌላ ተይዘሃል!
❖እግዚአብሔር ለምን ኃጢአት ሠራችሁ ብሎ አይጠይቀንም፤ ለምን ንስሓ አልገባችሁም ብሎ እንጂ፡፡
❖በጎልጎታ የተሰቀለው እርሱ እንደ ኃጢአተኛ ተቆጠረ፤ ብዙ
ስድብና ንቀትን ታገሠ፤ ከሞት በክብር ተነሣ፤ በክብርም ወደ
ሰማይ ዐረገ፤ በአብም ቀኝ በክብር ተቀመጠ፡፡
❖አንዳንዴ ስለ እግዚአብሔር ብለን በመልካም ቁጣ ውስጥ
ልናልፍ እንችላለን፤ ነገር ግን እንዲህ ሲሆን መረበሽና ራስን ያለመግዛት ነገር አይኖርበትምና በዚህ ጊዜ መንፈሳዊ ቅናት
ነው።
❖ አንተ ታማኝ ሆነህ በሰዎች ላይ በቃልህ የማትፈርድ ከሆነ እግዚአብሔር ደግሞ እጅግ ፈታኝ ከሆነው በሐሳብ መፍረድ
ይጠብቅሃል።
❖ሌሎችን አመስግን ያለህን አድናቆት ግለጽላቸው፤ መልካም
ሥራቸውን እንዳወቅህ እንዲረዱ አድርግ፤ አክብራቸውም።
ሠናይ ሰንበት
╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮
የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን
➡️ መሰረተ ሚዲያ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ቻነሉን share በማድረግ
መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ
👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═/channel/Meseretemedia
1፣3፣6፣16፣21 የቅድስት ድንግል ማርያም ቀኖች ናቸው፡፡
የእርሷ የኾኑት በዙ ብለህ እንዳታስብ!
ዕንኳን ዕለታቱ የዕለታቱ ፈጣሪ ክርስቶስም የእርሷ ኾኗል፡፡
በ፶፪ ዐ/ም በዛሬው ዕለት ከሦስት ድንጋዮች አንድ መቅደስ በእመቤታችን ስም በፊልጵስዩስ ተሠራ፡፡
ወራሴ ተአምራት ቅዱስ ላሊበላ ደግሞ ከሺ ዐመት በኋላ በኢትዮጵያ ከአንድ ድንጋይ አንድ ሙሉ መቅደስ ገነባ፡፡
ጌታ ኾይ ድንጋዩን ልብ የአንተ መቅደስ አድርገው
አንድ በጣም ትልቅ ቆሻሻ የጫነ ጋሪ የሚገፋ ሰው ወደ ቤትህ መጥቶ "እባክህ በርህን ክፈትልኝና ይህን ቆሻሻ አንተ ቤት ላራግፈው?" ቢልህ፣ "ውይ የሚጥልበት ቢያጣ ነው። ባይቸገር ወደ እኔ አይመጣም ነበር" ብለህ ደጅህን ከፍተህ ታስገባዋለህ? በፍጹም፤ እንደውም "እንዴት ብታስበኝ ነው? ምነው ስታየው ቤት አልመሰለህም? እንዴት ሰው በሚኖርበት ቤት ቆሻሻ ካልደፋሁ ትላለህ? ስትል ለጠብ ትጋበዛለህ። መደፈርህ እያንገበገበህ "እምቢ!" ብለህ ትቆጣለህ። በእርግጥም ያስቆጣል።
ግን ሌላ የሚከፋ ሽታ ያለው ቆሻሻን ጭኖ ለመጣ ባላጋራ እኮ በፈቃድህ የከፈትከው ቤት አለ። "የምን ቤት?" ብለህ ብትጠይቀኝ "ልብህ ነዋ" ብዬ እመልስልሃለሁ፤ "ማን ይኖርበታል?" ካልኸኝም "እግዚአብሔር ነዋ" እልሃለሁ።
አንተ ለመኖሪያ ቤትህ ጽዳት የምትጠነቀቀውን ያህል የያዕቆብ አምላክ ለሚያርፍበት ኅሊናህ ተጠንቅቀህ ታውቃለህ? ሰይጣን ጭኖ የሚያመጣውን የኃጢአት ቆሻሻ ሁሉ እሺ ብለህ ወደ ልብህ በማስገባት የፈጣሪህን መቅደስ ለምን ታቆሽሻለህ? ንጹሑ እግዚአብሔር የሚያድርበትን ቤት ሊያቆሽሽ በመጣ ሰይጣን ላይ እንዴት አልተቆጣህም? ድፍረቱ ለምን አላብከነከነህም?
እግዚአብሔር አንተ ልትኖርበት ከምትፈልገው ንጹሕ ቤት የበለጠ ጽዱ መቅደስ የማይፈልግ ይመስልሃል?
(Dn Abel Kassahun Mekuria )
@MoaeTewahedoB