dnhayilemikael | Unsorted

Telegram-канал dnhayilemikael - ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

1867

#መሰረታዊ_የቤተክርስቲያን_ክርስቲያን_ትምህርት / #የተለያዩ_ተከታታይ_ትምህርት ' #ስንክሳር_የቅዱሳን_ገድል_በየዕለቱ ! #ስዕለ_አድህኖ ! #ምስባክ #የየበአላቱ_ዋዜማና_ሥርተ_ማህሌት #መዝሙር #ግጥም #ለመናፍቃን_ጥያቄ_መልስ እና የተለያዩ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ ሌሎች መንፈሳዊ ጽሁፎች ይለቀቁበታል Administration @zearsema_dn

Subscribe to a channel

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

❖ ወዳጄ እስኪ ልጠይቅህ፤ አንተም አንቺም መልሱልኝ!

❓ጌታችን ዛሬ ቢመጣ የምትመልሰው የምትመልሺው መልስ ምንድን ነው

✍️"ንስሐ ያልገባሁት፣ ሥጋ ወደሙን ያልተቀበልሁት፣ ምግባር ትሩፋት ያልያዝሁት ዕድሜዬ ገና ነው ብዬ አስቤ ነው፤ ሥራ በጣም በዝቶብኝ ስለ ነበረ ጊዜ አጥቼ ነው፤ ዛሬ ነገ እያልኩ እየረሳሁት እንጂ እንደዚያ ማድረግ አቅቶኝ አልነበረም"

❓ምክንያትህ እነዚህ ናቸው
❓እኅቴ! ሰበቦችሽ እነዚህ ናቸው

❖ በዚያ ሰዓት ግን እነዚህ ኹሉ ጥቅም የላቸውም፤ እናት ልጇን በማታድንበት ሰዓት እነዚህ ምክንያቶች ምንም አይረቡም፡፡

❓ ታዲያ ለምን ትዘገያለህ
❓ እኮ ለምን ትዘገያለሽ
❓ያኔ ዋይ ዋይ ከምትዪ... ያኔ የማይጠቅም ጸጸት ከምትጸጸት ለምን ዛሬ አትጠቀምበትም
❓ለምን ራስህን አታድንም

📌 ምንጭ
✍️ከገብረ እግዚአብሔር ኪደ
📚ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ሊቀ መዘምራን ቴድሮስ ዮሴፍ
https://youtube.com/watch?v=ZlJmiQKQAN4&feature=shared

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

እንኳን ለአባ ሳሙኤል ዓመታዊ እረፍት በዓል ለዋዜማ በሰላም አደረሳችሁ ።

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ከፈሪ ሰው ጋር ስለ ጦርነት አትማከር መጋቤ ሐዲስ ፍሬስብሐት ይርጋ የቅኔና የመጽሐፍት መምህር
https://youtube.com/watch?v=Q9RDoxL4bqQ&feature=shared

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ዝጎራ ገፅ 315

" የምሥጢር ሙዳይ ሁን እንጂ የእሳት ማንደጃ ወናፍ አትሁን ። ሰዎች ሊሰሙህ በሚችሉበት ችሎታቸውና ፍላጎታቸው መጠን ብቻ ተናገር ፣ ቁጥብ እንጂ ዝርው አትሁን ። ለዕውቀት ትጋ ። በከፊል በተረዳኸው ነገር ራስክን እንደ አዋቂ አትቁጠር ። በከፊል ከማወቅ አለማወቅ ይሻላል ። ሥራ ስትሠራ ደግሞ ነገ ትቼው ለምሞተው ወይም ብሠራ የሚጠቀመው ሌላ ነው በሚል ተስፋ ቢስ ሆነህ ሳይሆን ዘላለም እንደምትኖር ያክል በመትጋት ነው ። ትጋት ጥሩ ነው ። ችኮላህ ግን ውጤት አያመጣም ፣ በችኮላ መሥራትና በፍጥነት መሥራት የተለያዩ ናቸው ። ርኩሰት የዕውቀትና ስልጣኔ መገለጫ አይደለምና ማንነትንና ሰብዓዊ ክብርን ከሚያጎድፉ ተግባራት መታቀብን ገንዘብ አድርግ ። "

" እናም በየዕለቱ በኑሮህ ጠንቃቃ ሁን ። ያለጸጸት ነገን ለመኖር ዛሬን በቁም ነገር አሳልፍ ፤ ውሳኔዎችህ ትክክለኛ መሆናቸውን መርምር ፤ ልክ እንደገና ሕይወትን የመኖር ዕድል ቢኖርህ ወይም እንደገና ሕይወትን የመኖር ዕድል ቢኖርህ ደግመህ የምትኖረውንና ለማከናዎን የምትመርጠውን ዐይነት ሕይወት ለመኖር ሞክር ። .... "

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

የክርስትና አባትና እናት

✝️ በቤተክርስቲያናችን ወንዶች በ፵ ቀናቸው ሴቶች በ፹ ቀናቸው በተጠመቁ ጊዜ የክርስትና አባት ወይም እናት ይኖራቸዋል

✝️ የክርስትና አባትና እናት ማለት ደግሞ ልጆች በሚጠመቁ ጊዜ ስለ እምነታቸው ባለው ነገር ሁሉ ሀላፊነት ወስደው አስፈላጊውን ትምህርት የሚሰጡ፣ የሚደግፉ ማለት ነው
➻ በጥምቀታቸው ወቅትም ስለ ልጆቹ በእምነታቸው ለለመስከር ቃል የሚገቡ፣ ሀላፊነት የሚወስዱ ናቸው

✝️ ይህ ስርዓት በቤተክርስቲያናችን የተጀመሪያው በ፬ኛው ክፍለ ዘመን በመጀመሪያው የሀገራችን ኢጲስ ቆጶስ በአቡነ ሰላም ከሳቴ ብርሃን ነው

✝️ የመንፈሳዊ ትምህርት ከመስጠትም በዘለለ መንፈሳዊ ዝምድናን (አበ ልጅነትን) ማጠናከሪያ መንገድ ነው

⛪️ ከክርስትና አባትነትና እናትነት የሚከለክሉ ነገሮች፦

➻ የሥጋ ዝምድና መኖር
➻ የጋብቻ ዝምድና ያላቸው መሆን
➻ ዕድሜያቸው ለማስተማር፣ ለማሳመን አለመድረስ
➻ በቂ እምነት፣ መልካም መንፈሳዊ ሕይወት አለመኖር
➻ ሃይማኖታቸው ከተጠማቂው ጋር የተለየ መሆን

✝️ ጾታን ስናይ ወንድ ወንድን ሴት ሴትን ያነሳሉ እንጂ ወንድ ሴትን ሴት ወንድን ክርስትና ማንሳት አይፈቀድም

✝️ የክርስትና አባትና እናት ክርስትና ያነሷቸውን ልጆች በሥጋ ከወለዷቸው ልጆች ሳይለዩ አስፈላጊውን የክርስትና ትምህርት፣ ድጋፍና ክብካቤ ለማድረግ በእግዚአብሔር ፊት ቃል ይገባሉ

✝️ ይህንን ቃልም በተግባር የመተርጎም ሀላፊነትን እንዲወጡ ቤተክርስቲያን በሚገባ ታስተምራለች

✝️ የክርስትና አባትነትና እናትነት የተዛመዱ ክርስቲያኖች በፍጹም መጋባት አይችሉም
➻ ይህም በሥጋ ከመዛመድ በላይ መንፈሳዊ ዝምድና ምን ያህል ታላቅ እንደሆነ ያሳየናል

ልዑል እግዚአብሔር በቸርነቱ ይጠብቀን። ሀገራችንና ሃይማኖታችንን ይባርክ።

#

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

እመኑ ብየ
https://youtube.com/watch?v=8NxHAUlTxDg&feature=shared

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን!
መስከረም 21-ብዙኃን ማርያም (የእመቤታችን የበዓሏ መታሰቢያ ነው፡፡)
+ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት አስቀድሞ ኃይለኛ ሥራየኛ ጠንቋይ የነበረውና በኋላም አምኖ ለክርስቶስ ምስክር ሆኖ አንገቱን የተሰየፈው ቅዱስ ቆጵርያኖስ በሰማዕትነት ያረፈበት ዕለት ነው፡፡
+ ቆጵርያኖስን ያሳመነችውና ስሟ በተጠራበት ቦታ ሰይጣናት እንደ ትቢያ በነው የጠፉት ድንግሊቱ ዮስቴናም በሰማዕትነት ያረፈችው በዚሁ ዕለት ነው፡፡
+ ዳግመኛም ይህች ዕለት የከበሩ ሃይማኖታቸው የቀና 318ቱ አበው ሊቃውንት በ325 ዓ.ም አርዮስን አስተምለው ለመመለስ በኒቅያ የተሰበሰቡባት ዕለት ናት፡፡ የጉባኤውም ፍጻሜ ዓመታዊ መታሰቢያ በዓሉ ኅዳር ዘጠኝ ነው፡፡
+ የጌታችን ቅዱስ መስቀል ግሸን ደብረ ከርቤ የገባበት ዕለት ነው፡፡ (የመስከረም ዓሥራ ሰባቱን ይመለከቷል፡፡)
+ ከ72ቱ አርድእት አንዱ የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ጢባርዮስ ዕረፍቱ መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሰዋል፡፡

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

"የክርስቶስ መስቀል ታላቅ በረከትንና ድኅነትን እንድናገኝ ምክንያት እንደ ሆነ እናስተውላለን፡፡ የክርስቶስ መስቀል ስናስበው ሐዘንና ምሬት ነው ነገር ግን እውነታው ደስታና ሐሴትን የሚሞላ ነው፡፡ መስቀል ለቤተ-ክርስቲያን ድኅነት ነው መስቀል ተስፋ ለሚያደርጉት መመኪያ ነው መስቀል የእግዚአብሔር ጠላቶች የነበሩት የታረቁበትና ኃጢአን ወደ ክርስቶስ የቀረቡበት ነው፡፡ በመስቀል ከጠላትነት ወደ እግዚአብሔር ልጅነት ተሸጋግረናል በመስቀል ከዲያብሎስ ቀንበር ወጥተናል ከሞት ወደ ሕይወት መጥተናል፡፡ ስለ መስቀል የማንሰብክ ከሆነ አሁንም በሞትና በፍዳ እንደ ተያዝን ነው ማለት ነው፡፡
            ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ልብሰ ተክህኖን ክህነት የሌለው ሰው መንካትና ማጠብ አይችልም። ሥርዓት አይደለም። በቅንነት አንዳንድ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት አድርጋችሁት ከነበረ ከእንግዲህ እንዳታደርጉ ትምህርት ይሁናችሁ። ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፰ ላይ ከዲያቆናት፣ ከቀሳውስትና፣ ከዚያ በላይ ከሆኑት በስተቀር ንዋየ ቅድሳትን እንዲነኩ አልተፈቀደም። ስለዚህ ካህናት ሆይ ክህነት የሌላቸው ሰዎች ንዋየ ቅድሳትን እንዲነኩና እንዲያጥቡ አታድርጉ።

መ/ር በትረ ማርያም አበባው

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

✓•ወንድሞቼ_ሆይ ወደ ቤተ ክርስቲያን ውድ ስጦታዎችን ይዛችሁ ስትመጡ አያለሁ፡፡ መልካም አድርጋችኋል፡፡ ነገር ግን ስትመለሱ ደግሞ መበለቶችን፣ ደሀ አደጎችንና ሕጻናትን ስትበድሉ አያችኋለሁ፡፡ ታድያ ይህን ሁሉ እያደረጋችሁ በወርቅ የተንቆጠቆጠ ምሥዋዕና ጽዋዕ ብታቅረቡ ምን ይጠቅማችኋል? ለምንስ መሥዋዕቱን ማክበር ስትፈልጉ አስቀድማችሁ ልባችሁን መባ አድርጋችሁ አታቀርቡም? ልባችሁ በጭቃ ተጨማልቆ ምሥዋዑ እንኳን ወርቅ ፕላቲንየምስ ቢሆን ምን ይረባችኋል? ምንስ ይጠቅማችኋል?

✓•ተወዳጆች_ሆይ!
አመጣጣችን በወርቅ የተለበጠ መሠዊያ ለማቅረብ ሳይሆን ይኸን ከልብ በመነጨ ለማቅረብ ይሁን፡፡ ከልባችን የምናቀርበው ነገር ሁሉ ከወርቅ የበለጠ መባ ነው፡፡

✓•ልብ_በሉ!
ቤተ ክርስቲያን የወርቅ ወይም የነሐስ ማቅለጫ ቦታ አይደለችም፤ ለቅድስና የተጠሩ ሁሉ እና የመላእክት ኅብረት እንጂ፡፡ስለዚህ ከስጦታችሁ በፊት ልባችሁን ይዛችሁ ኑ፡፡ እግዚአብሔር እኮ ሥጦታችንን የሚቀበለው ደሀ ሆኖ ሳይሆን ስለ ነፍሳችን ብሎ ነው፡፡

✓•ክርስቶስን_ማክበር_ትወዳላችሁን?
እንግዲያስ ዕራቆቱን ስታዩት ችላ አትበሉት፡፡ እናንተ ወደ ቤተ መቅደስ ስትመጡ እጅግ ውድ በሆኑ ልብሶች አጊጣችሁ ስትመጡ እርሱ በብርድና በመራቆት ሊሞት ነውና ብያንስ ትንሽ እንኳን እዘኑለት፡፡ ቤተ መቅደስ ረግጣችሁ ቤተ መቅደስ አትምጡ፡፡ በቃሉ “ይህ ሥጋዬ ነው” ያለው ጌታ በተመሳሳይ ቃሉ “ተርቤ ስታዩኝ አላበላችሁኝም፤ ከሁሉ ከሚያንሱት ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም” ብሏልና።

ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ይብሰተ_አእምሮ
#የአእምሮ_ድርቀት

የወንጌል አንድምታ ትርጓሜያችን እንዲህ ይላል 👇
"አሥራ ሁለት መሳክወ ነፋሳት አሉ
አራቱ መሳክው (መስኮቶች) የአራት
#ነፋሳተ_ምሕረት መውጫ ሲሆኑ
ስምንቱ መሳክው ደግሞ የስምንቱ ነፋሳተ መዓት መውጫ ናቸው
#ስምንቱ ነፋሳተ መዓት ሲታዘዙ በዓለም ላይ አምስት ዓይነት መቅሠፍት ይወርዳል
ከነዚያ ውስጥ አንዱ
#ይብሰት/ድርቅ ነው ይልና ይብሰት በሁለት እንደሚከፈል ይናገራል
የመጀመሪያው የእህል የውሃ መታጣት ሲሆን
ሁለተኛው ግን
#ይብሰተ_አእምሮ (የአእምሮ ድርቀት) ነው
👉በዚህ ዘመን የገጠመን ዋና በሽታ ይህ ይመስለኛል
በዓለም ላይ እየከተሠቱ የምናያቸውና የምንሰማቸው ችግሮች ሁሉ
#በይብሰተ_አእምሮ የተቀደሙ ናቸው
• የእርስ በእርስ ጦርነት
• የሀገራት ጦርነት
• የኅፃናት መደፈርና መገደል
• የታላላቅ ሰዎች አለመከበር
• የሙስና መስፋፋት
• የተመሳሳይ ፆታ መጋባት
• መተሳሰብና መተዛዘን መጥፋት ...እነዚህ ሁሉ የ
#ይብሰተ_አእምሮ ውጤቶች ናቸው

የሰውነት ልክ የደረቀበት
እውነት የማይታመንበት
እውነት ተናጋሪ የሚሰቀልበት
ውሸት የለመለመበት
ጩኸት የሚቀማበት
ዕውቀትና አዋቂዎች የሚገፉበት ይህ ዘመን ነው
ይኸውም ይብሰተ አእምሮ ነው
ይብሰተ አእምሮ ሲከሠት በሁሉም ቦታ
#ደህና_ሰው ይታጣል
ጽኑ ተስፋ በሚጣልባቸው በሃይማኖት ቦታዎች ሳይቀር
#ደግ_ሰው ይታጣል
ፍርድ ይዛባል፤ ድሃ ይገፋል....መደማመጥ የለም ...ሁሉም አውቃለሁ ይላል...ጫጫታ እንጂ ንግግር የለም!!!
ይህ
#ይብሰተ_አእምሮ ይባላል

መፍትሔው በሃይማኖትና በምግባር መታነጽ ዕውቀት ንባብና መደማመጥ ነው !!!!!

የራስ ቅል ድርቀት በቅባት እንደሚርስ
የዕውቀት ማጣትም በንባብ ይርሳል ይታደሳል!

መጪውን ዘመን የደረቀውን አእምሯችንን በንስሐ አለምልመን
በሥጋ ወደሙ አፍርተን
በንባብና በዕውቀት ታድሰን የምንኖርበት ያድርግልን !!!

ለሀገራችን ሰላምን ይስጥልን!

መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

++ ከእምነት በፊት መዳን ++

( ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ )

የተፈጠርነው በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው። ሰው ሆነን ወደ ምድር የመጣንበትን ዘመን፣ የተገኘነበትን ምድር፣ የወጣንበትን ማኅበረ ሰብእ እና ሌሎችንም ጉዳዮች የመረጠ እርሱ እግዚአብሔር ነው። አዳም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ በራሱ ምርጫ ራሱን ያስገኘ ማን አለ? አጭር ወይም ረዥም፣ ቀጭን ወይም ወፍራም፣ ነጭ ወይም ጥቁር ሆኖ ስለመወለዱ ከእግዚአብሔር ጋር የተማከረስ ማነው? ሁሉም በእግዚአብሔር ፈቃድ የተከናወነ ነው። ገበሬ ዘሩን በምድር ላይ በበተነ ጊዜ ምድሩን ለዘሩ የሚመርጥለት ገበሬው ነው እንጅ ዘሩ እንዳልሆነ ሁሉ የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ምርጫ እንጅ በራሱ ምርጫ ወደ ዓለም ሊመጣ አይችልም።

በዚህ መንገድ ወደ ምድር የመጣ የሰው ልጅ የሚኖረውም የእግዚአብሔርን ፈቃድ መሠረት አድርጎ ነው። በማኅፀን በሠራን ጊዜ ለሕይወታችን የሚያስፈልገንን አንዳች ሳያጎድል ሠርቶ ከማኅፀን ስላወጣን በምድር ላይ ስንኖር የምንኖርበትን ትዕዛዝ ቢያዝዘን አንዳች እንደሚያጎድልብን ሳንጠራጠር አምነን እንታዘዝለታለን። በባሕር የሚኖሩትን በባሕር ለመኖር የሚያበቃቸውን፣ በየብስም የሚኖሩትን በየብስ ለመኖር የሚያስችላቸውን አካል ሰጥቶ ፈጥሯቸዋል። አካላችንን ከሥርዓተ ዓለም ጋር አስማምቶ ምንም የማይጠቅም አካል ሳይጨምር የሚበቃንን እና የሚያስፈልገንን ብቻ ሰጥቶ ወደ ዓለም እንድንመጣ ማድረጉ ለእኛ የሚያስፈልገንን ሁሉ በመስጠት የሚያኖረን እርሱ ብቻ መሆኑን እንድናምን ያስገድደናል።

ከዚህም የተነሣ ነው ሰባኪዎቻችን፥ በሰው እንዳንታመን “ማዳን በማይችሉ በሰው ልጆችና በአለቆችም አትታመኑ ነፍሳቸው ትወጣለች ወደ መሬትም ይመለሳሉ” መዝ 145፥3 ብለው ብለው መታመናችንን በሥጋዊና በደማዊ ፍጥረት ላይ እንዳናደርግ የመከሩን።

ልንኖረው ከተፈቀደልን ሦስት ክፍል ካለው ኑሯችን የመጀመሪያውን ያለ እግዚአብሔር በቀር ከእኛም ሆነ ከሰዎች አንዳች ምክር የሰጠበት የለም። ከማኅፀን ከወጣንም በኋላ የምንኖረው ሁለተኛውን ክፍል ኑሯችንን ሲሆን ከማኅፀን ከወጣንበት ጊዜ ጀምሮ ራሳችንን በሰዎች ዕቅፍ ስለምናገኘው ነው መሰለኝ ከእግዚአብሔር ሀሳብ ይልቅ በራሳችንና በሰዎችም ፈቃድ የመኖር ዝንባሌ ይታይብናል።

በውስጣችን ባለው አድሮብን፣ ተዋሕዶን ከሚኖረው አምላካችን ይልቅ አጠገባችን ከጎናችን ባሉ ሰዎች ተስፋ እናደርጋለን። ይልቁንም በቤተ እግዚአብሔር ለሚኖሩ ሰዎች በሰው መታመን እንዴት ያለ አስቸጋሪ ነገር መሰላችሁ?

ይህንን ያልሁት የዛሬውን መጻጉዕን ጉዳይ ሳስብ ቀድሞ የሚመጣብኝ እግዚአብሔር ሰዎችን ወድ ሚያድንበት ስፍራ ሂዶ ሰው መጠበቁ ስለሚያስገርመኝ ነው። የመጻጉዕን መዳን ለሠላሳ ስምንት ዓመታት ያዘገየበት በሰው ስለሚታመን ሳይሆን አይቀርም። “ጌታ ሆይ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል ብሎ መለሰለት” ዮሐ 5፥5 በሚለው የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ውስጥ የሚታየው ሀሳብ መጻጉዕ በእግዚአብሔር ደጅ እየኖረ በሰው የሚታመን በሽተኛ እንደነበረ የሚያሳይ ነው። ከሩቅ ቦታ አምጥቶ የመጠመቂያው ስፍራ ያደረሰው ማነው? ይሄ ሰው ይህንን ያኽል ዘመን እንዴት አንድ ሰው ወደ መጠመቂያው እንዲወርድ ሊረዳው አልፈቀደም? አብረውት በመጠመቂያው ስፍራ ተኝተው የሚሰነብቱ አንካሶችን በሽተኞች ከዳኑ በኋላ እንኳን ይህንን ሰው ወደ መጠመቂያው ስፍራ አውርደውት ድኖ እንዲመለስ እንዴት አላደረጉትም? እያልሁ ብዙ ጊዜ አስቤ አውቃለሁ።

ይህ ሰው ከመጀመሪያው እምነት የጎደለው ነው። የዳኑት ሁሉ እግዚአብሔር ስለፈቀደላቸው ሳይሆን ሰው ስላላቸው ነው ብሎ የሚያስብ ሰው ነው። የመጣው የእግዚአብሔር መልአክ በወረደ ጊዜ በሚናወጠው ውኃ ውስጥ ገብቶ ተጠምቆ ፈውስ ለማግኘት ነው ነገር ግን በሃይማኖቱ ላይ የሰዎችን እርዳታ ካልተጨመረበት በቀር መዳን እንደማይችል በማሰብ ይሄንን ሁሉ ዘመን ሰው ሲፈልግ ነው የኖረው። በእግዚአብሔር ፊት ሆኖ ሰው መጠበቅ የሚያስገርም ነገር ነው። ለዚህም ነው ኢየሱስ ክርስቶስ ካዳነው በኋላ ራሱን ሳይገልጥለት በሰዎች መካከል ሆኖ የሄደው። እሱም ያዳነው ማን እንደሆነ ሊመረምር አልተመለሰም። ሰው ሲጠብቅ የኖረ ሰው እግዚአብሔር አዳነኝ ማለት እንዴት ይችላል? አይሁድ በጠየቁትም ጊዜ “ያዳነኝ ያ ሰው አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለኝ” ነው እንጅ ያለው እግዚአብሔር አዳነኝ አላለም።
እምነታችን ሳይጸናልን ገንዘብ ብንቀበል፣ ሥልጣን ብናገኝ፣ ጤና ቢኖረን፣ ጉልበታም ብንሆን፣ ውበትና ደም ግባት ቢስማማልን፣ ዓለምን በመላው የእኛ ማድረግ ብንችል ምንም ጥቅም እንደሌለው ተመልከቱ።

መጻጉዕ ያዳነውን ትቶ አልጋውን ተሸክሞ መሄዱ ያሳዝናል። ከዚያች ቀን ጀምሮ ሰይጣን ዝም ብሎ ሊተወው አልወደደም። እስከ ዕለተ ዐርብ ድረስ ተከታትሎ ፍጹም ኃጢአት አሠርቶታል። በሕይወቱ ውስጥ ከሕማሙ ቀጥሎ ሌላ ፈተና ይዞበት የመጣው ፈውሱ ከእምነቱ በመቅደሙ ነው። ከዳነ በኋላ ከዐሥሩ ለምጻሞች እንደ አንዱ እግዚአብሔርን እያመሰገነ በቤተ መቅደስ ሊገኝ ይገባው ነበር እርሱ ግን ይህንን ሲያደርግ አልታየም። ያለ ሃይማኖት የሆነ ነገር ሁሉ ፈተናው ከባድ ነው።

ከሁሉም ነገር በፊት ሃይማኖትህን እንዲያጸናልህ ለምን። ሕይወትህን ከሚገጥምህ ፈተና ሁሉ ጠብቆ ሊያኖራት የሚችል በልብህ ውስጥ ያለው ሃይማኖትህ ነው። ሁሉንም ነገር ከተቀበልህ በኋላ ከሁሉም አስቀድሞ እግዚአብሔርን ለማመስገን ጊዜ ይኑርህ። ንብረትህን ከመሰብሰብህ በፊት ልብህን ሰብስበህ አስብ። ቀጥሎ ለምትጓዝበት መንገድ የሚረዳህ ይህ ነውና። ዳዊት ጎልያድን በማሸነፉ “አቤቱ ጉልበቴ ሆይ እወድሀለሁ” ብሎ ዘመረ እንጅ በራሱ ወይም በሌላ ሰው አልተመካም። ስለዚህም እግዚአብሔር ለሌላ ከፍ ላለ ጸጋ መረጠው። በሰዎች ላይ የጀመረውን ማሸነፍ በአጋንንት ላይ ደገመው። ሳኦልን ከሰዎች እጅ ብቻ ሳይሆን ከመናፍስትም እጅ የሚያድንበትን መንፈሳዊ ጉልበት ከእግዚአብሔር እጅ ተቀበለ። ራሱ ለእግዚአብሔር መዝሙር እያዘጋጀ ስለነበረ ጎልያድን በመግደሉ ሰዎች ስለራሱ የዘመሩትን ዝማሬ አልሰማቸውም።

ወንድሜ ከእግዚአብሔር እጅ ከዚህ የሚበልጥ ሌላ ስጦታ ስለሚጠብቅህ ያዳነህን መርምረህ ሳታውቅ የተሰጠህን አልጋ ብቻ ይዘህ አትውጣ። ከግዚአብሔር ፊት ስትወጣ የሚያገኙህ ሁሉ የሚመለከቱት መዳንህን ሳይሆን የተሸከምኸውን አልጋ ነው። ስንት ዘመን ታመህ እዚህ እንደደረስህ እነሱ አይገባቸውም። ለሕጋቸው እንጅ ለሰው የሚጨነቁ አይደሉም። ስህተቱ፥ ላንተ የሚያስብ እግዚአብሔርን ትተህ እነሱ ወዳሉበት መሄድህ ነው። ሰው አድርጎ በፈጠረህ ጊዜ ለሰውነትህ የሚያስፈልጋትን ሁሉ አስማምቶ የፈጠረህ ጌታ ዛሬም አንተን ለማኖር የሚበቃ ኃይልና ፈቃድ ስላለው ሁልጊዜም ከፊቱ አትጥፋ። ሳታምን ምንም እንዲደረግልህ አትለምን። በእምነት ድል ወደማትነሣው ክብር ለመግባትም አትሞክር።

በጸና እምነት ወስጥ ካልኖርህ፦ ክብር ቢኖርህ ከንቱ ውዳሴ ይጥልሃል። ሀብት ቢኖርህ ጥጋብ ያጠፋሃል። ዝና ቢኖርህ መታበይህ ማዕበል ሆኖ ያሰጥምሃል። ውበት ቢኖርህ ለዝሙት አሳልፎ ይሰጥሃል። ጌጠኛውን ልብስ የመልበስ ዕድል ቢያጋጥምህ ለትውዝፍት ይዳርግሃል። ወንድሜ ያለ እምነት ከሆነ በምንም ነገር እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልምና ከሁሉም ነገር በፊት እግዚአብሔር ሃይማኖትህን እንዲያጸናልህ ለምን።

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ፍትሐ ነገስት አንቀጽ 8

ቁጥር 16 ካህናት ከሠርግ አዳራሽ ሄደው ዘፈን መስማት አይገባቸውም። የሚፈክሩት የሚዘፍኑት ሳይመጡ በልተው ጠጥተው መርቀው ይመለሱ እንጂ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

የእመቤታችን ዕረፍትና ዕርገት በቅዱስ ያሬድና በአባ ጽጌ ድንግል
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ሊቁ ቅዱስ ያሬድ እንዲኽ እያለ ያወድሳታል፦
╬ “ሐዋርያት አመድበሉ
ሥጋ ድንግል ጠብለሉ
በሰንዱነ ብርሃን ዘላዕሉ
ልብሳ ተካፈሉ”
(ሐዋርያት ተሰበሰቡ፤ ከላይ በመጣ በፍታ (መጐናጸፊያ) የድንግል ሥጋን ጠቀለሉ፤ ልብሷንም ተካፈሉ)

╬ “በደመና ተጋቢኦሙ ሐዋርያት ለድንግል ንጽሕት
ገነዝዋ በክብር ወበስብሐት
ለቀበላሃ ወረዱ ኀይላት
ወቀበርዋ ውስተ ገነት”
(ሐዋርያት በደመና ተሰብስበው ንጽሕት ድንግልን በክብር በምስጋና ገነዟት፤ ለአቀባበሏ ኀይላት ወረዱ፤ በገነት ውስጥም ቀበሯት)

╬ “ተጋቢኦሙ ሐዋርያት እምኲለሄ
በደመናት ዘምሉእ ሡራኄ
ገነዙ በክብር ወበስባሔ
ሥጋ ድንግል ዘይምዕዝ እምርሔ”
(ብርሃንን የተመላ በኾነ በደመናት ሐዋርያት ከአራቱ ማእዝን ተሰብስበው ልብን ከሚመስጥ ሽቱ ይልቅ የሚሸትት የድንግልን ሥጋ በክብርና በምስጋና ገነዙ)

╬ “ተጋቢኦሙ በደመና ሰማይ
ሐዋርያት ሥርግዋን በዕበይ
ገነዝዋ ለድንግል በብዙኅ ግናይ
ዳዊት ዘመራ በመሓልይ”
(በገናንነት የተጌጡ ሐዋርያት በሰማይ ደመና ተሰብስበው ድንግልን በብዙ ምስጋና ገነዟት፤ ዳዊትም በምስጋና አመሰገናት፡፡)

╬“ተጋቢኦሙ አርድዕተ ወልዳ
በደመና ብርሃን ጸዐዳ
ገነዝዋ በስብሐት ለጽርሕ ሳይዳ”
(ጸዐዳ በኾነ በብርሃን ደመና የልጇ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበው፤ ውቢቱ አዳራሽን በምስጋና ገነዟት)

╬ “ተጋብኡ በቅጽበት ለግንዘተ እሙ ቅድስት
ብፁዓን ሐዋርያት
ቦኡ ኀቤሃ በሰላም አምኁ ኪያሃ
በስብሐት ገነዙ ሥጋሃ”
(ንኡዳን ክቡራን ሐዋርያት ቅድስት የምትኾን የጌታ እናቱን ለመገነዝ በቅጽበት ተሰበሰቡ፤ ወደ ርሷ ገብተው በሰላምታ ርሷን እጅ ነሧት፤ ሥጋዋንም በምስጋና ገነዙ)

╬  “ፃኢ እምሊባኖስ ሥነ ሕይወት ርቱዕ አፍቅሮትኪ ቡርክት አንቲ እምአንስት ማኅደረ መለኮት ሰላም ለኪ፤ ማርያም እመ አምላክ ወልድኪ ይጼውዐኪ ውስተ ሕይወት ወመንግሥተ ክብር”
(የሕይወት ደም ግባት የአምላክ እናት ከሊባኖስ ውጪ፤ ፍቅርሽ የቀና ነው፤ ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ፤ የመለኮት ማደሪያ ሰላምታ ላንቺ ይገባል፤ የአምላክ እናት ማርያም ሆይ ልጅሽ ወደ ዘላለማዊ ሕይወትና ወደ ክብር መንግሥት ይጠራሻል)

╬ “ፈለሰት ማርያም በስብሐት ውስተ ሰማያት መላእክት ወሊቃነ መላእክት ወረዱ ለተቀብሎታ”
(እመቤታችን በምስጋና ወደዚያኛው ዓለም በተለየች ጊዜ ለአቀባበሏ መላእክትና ሊቃነ መላእክት ወረዱ)።
                 ☀️☀️☀️
💥 አባ ጽጌ ድንግል እንዲኽ እያለ ያወድሳታል:-
❖ "እንዘ ይፀውረኪ በሐቂፍ ወይስዕመኪ በአፍ
አመ አፍለሰኪ ወልድ ውስተ የማኑ ለዐሪፍ
ጽጌ ዕፀ ገነት ማርያም ዘትጼንዊ ለአንፍ
እንዘ ይትጓድዑ አክናፈ በክንፍ
ለቀበላኪ ወረዱ አእላፍ”
(ለአፍንጫ መዐዛን የምትሰጪ የገነት ዛፍ ማርያም ሆይ፤ ልጅሽ በክንዱ ዐቅፎ በአፉ እየሳመ በቀኙ ሊያሳርፍሽ ባሳረገሽ ጊዜ፤ አንቺን ለመቀበል ክንፍ ለክንፍ እየተጋጩ እልፍ አእላፋት መላእክት ወረዱ)

❖ “ትእምርተ ፍልሰትኪ እምድረ ጽጌ ድንግል በክልኤ
በደመና ሰማይ አርአየ ዘሐዋርያት ጉባኤ
ወእለ ሞቱ አንቅሐ እምከርሠ መቃብር ቀርነ ጽዋዔ
ለነሰ እንዘ ይብሉ ሶበ ሰማዕነ ውዋዔ
መሰለነ ዘበጽሐ ትንሣኤ”
(በኹለት ወገን ድንግል የኾንሽ ማርያም ሆይ አበባ ካለበት ምድር ወደ ሰማይ የማረግሽ ተአምር በሰማይ ደመና የሐዋርያት ጉባኤን አሳየ፤ የሞቱትንም ከመቃብር ውስጥ በተአምር ነጋሪት ድምፅ አስነሣ፤ ለእኛስ የምስጋና ከፍተኛ ድምፅን በሰማን ጊዜ የሙታን መነሣት የደረሰ መሰለን እስኪሉ ድረስ)።

❖ “አመ ነሥኡኪ እምኤዶም አዕላፈ ማሕሌት ጾታ
እንዘ ይጼልሉኪ ድንግል በአክናፈ መባርቅት ከመ ወልታ
ሰራዊተ ሰማይ ይቤሉ ለክብረ ፍልሰትኪ ግርማ ትርሲታ
መኑ ይእቲ ዛቲ ዘገዳመ ጽጌ ዕጥነታ
ወከመ ሠርጸ ጢስ ዘስኂን ይምዕዝ ዕጥነታ”
(ድንግል ወገኖች አመስጋኞች መላእክት በየነገድ በየነገድ ኾነው በመባርቅት ክንፎች እንደ ጋሻ ጋርደው ከኤዶም ገነት በተቀበሉሽ ጊዜ የሚያስደንቅ ክብር ለተገለጸባት ለዕርገትሽ የሰማይ ሰራዊት አበባ ካለበት በረሓ የምትወጣ መዐዛዋም ከነጭ ዕጣን ይልቅ የሚሸትት አወጣጧም እንደ ጢስ አወጣጥ የኾነችይኽቺ ማናት? ይኽቺ ማን ናት ይላሉ (መሓ ፫፥፲፮))።
[የአምላክ እናት ሆይ እወድሻለሁ]
✍️ መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (በድጋሚ የተለጠፈ)

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ክቡር የሚሆን የወንጌል ቃል እንሰማ ዘንድ እንሳለመው ዘንድ በእርሱም ደስ ይለን ዘንድ በዚህ የበቃን ያድርገን  ሁሉን የያዘ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ ለአንተ ምስጋና ይገባል ዳግመኛም ክቡር የሚሆንን የወንጌልን ቃል በልቦናችን ትጽፍ ዘንድ እንለምንሃለን እንማልድሃለንም

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ዕለታዊ_መልዕክት

1, ጠንካራ ሰው ሁን ማለት አትውደቅ ማለት አይደለም ወድቀህ መነሳትንም ልመድ ማለት እንጂ!
2. ዝም በል ማለት አትናገር ማለት አይደለም ሌሎችን ለመስማት ጆሮ ስጥ ማለት እንጂ!
3. ሆዳም አትሁን ማለት አትብላ ማለት አይደለም በሰው ሀቅ አትለፍ ማለት እንጂ!
4. አትቆጣ ማለት ስሜት አይኑርህ ማለት አይደለም ከቁጣ ቶሎ ተመለስ ማለት እንጂ!

5. ይቅርታ አድርግ ማለት አልተጎዳህም ፣ አልተናደድክም ማለት አይደለም በሆድህ ቂም መያዝ ሌላ ጉዳት ስለሆነ ነው እንጂ!
6. ጠላትህን ውደድ ማለት ጠላት ጥሩ ነው ማለት አይደለም ከጥላቻ ይልቅ ፍቅር ስለሚያሸንፍ ነው እንጂ!
7. ደስተኛ ሁን ማለት ሁሉ ይኑርህ ምን አይጉደልብህ ማለት አይደለም ባለህ ትንሽ ነገር ቢሆን ደስ ይበልህ ማለት እንጂ!
8. ሥራህን ውደድ ማለት የምትሰራው ሥራ ጥሩ ነው ማለት አይደለም ነገ ጥሩ ሥራ እንዲኖርህ ዛሬ ላይ የምትሰራውን ሥራ ውደድ ማለት እንጂ!


እግዚአብሔር አምላክ ይርዳን !


[ወልደ ሚካኤል]


#ለሌሎች_ሼር_ማድረግ_አትዘንጉ

JOIN /channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

“አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል" / ኤፌ 5÷14/

ወዳጆቼ ብዙዎቻችን ስልክ ስናወራ ሳንቲሜ ቆጠረ እንጂ ዕድሜዬ ቆጠረ አንልም ከዕድሜው ይልቅ ለሳንቲም ዋጋ እንሰጣለን። በስልክ ከወዳጆቻችን ጋር የምናወራውን ያክል እንኳ ከፈጣሪያችን ጋር ማውራት ሸክም ሆኖብናል።

በመንፈሳዊ ህይወት ላይ ለውጥ ለማምጣት በፕሮግራም ሳይሆን በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው መኋዝ ያለብን።  ነገ እጀምራለው ነገ ይህን አደርጋለው እያልን ቆጠሮ ብንሰጥ ትርፉ መሰላቸት ነው ማድረግ ያለብንን ዛሬ አሁኑን እንጀምረው። የእግዚአብሔር ፈቃዱም አሁኑኑ እንድንድን ነው።

ነቢያት ስላልመጣው ዘመን ያውቁ ነበር ፤ እኛ ግን የምንኖርበት ዘመን ምንነት እንኳ ተሰውሮብናል። ሐዋርያት ሄደው ዓለምን ዞረው ይሰብኩ ነበር ፣ እኛ ግን በተመቻቸ ቦታ መጥታችሁ ተሰበኩ እንላለን። ሰማዕታት ለክርስቶስ ፍቅር ሞቱ ፣ እኛ ግን ለጥቅማችን ፣ ለምኞታችን ፣ ለኃጢያታችን እንሞታለን። ጻድቃን የዚህን ዓለምን ጣዕም ንቀው መነኑ ፣ እኛ ግን ዓለም መራራ ሆናብንም እንኳ ደግመን ደጋግመን እንፈልጋታለን።

ቅዱሳን አባቶቻችን ከሕግ አልፈው በትሩፋት ኖሩ ፣ እኛ ልጆቻቸው ግን የታዘዝነውን እንኳ መፈጸም ተስኖናል። ደናግል መነኮሳት የክርስቶስ ሙሽሮች ሆኑ ፣ እኛ ግን በአንድ ሃይማኖታችን ጸንተን ክርስቶስን መከተል (ማምለክ) አቅቶናል። ሊቃውንት አባቶቻችን አህያ እንኳ የማትሸከመውን መጽሐፍ በቃላቸው አጠኑ ፣ እኛ ግን አንድ ጥቅስ ለማጥናት ያዙኝ ልቀቁኝ እንላለን።

ጌታ ሆይ እባክህን እኛን እንቅልፋሞቹን ከእንቅፋችን አንቃን !


ለተዋሕዶ ልጆች👇
                •➢ ሼር // SHARE
  /channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ጾም ሙሽሪትን ትመስላለች፤ ሙሽሪትን በሠርግ አዳራሽ ኾነው የሚቀበሏት ሰዎች ቤቱን ያስጌጡታል፤ ይሸልሙታል፡፡ ወደ ሠርጉ አዳራሽ የሚገባውን ሰው የሠርግ ልብስ ለብሶ እንደኾነ፣ የቆሸሸ እንዳልኾነ አይተው ያስገቡታል፡፡ እኛም እንዲኽ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ልቡናችንን በማንጻት፣ ልል ዘሊል ከመኾን በመራቅ፣ የክፋት እርሾን በማስወገድ፣ ከጾም ጋር አብረው የሚመጡትን የሚያጅቧትን መልካም ምግባራትንም ለመቀበል የልቡናችንን ውሳጤ በመክፈት የምግባር እናት፣ የማስተዋል እንዲኹሉም ለሌሎች ምግባራት ኹሉ ንግሥት የምትኾን ጾምን ልንቀበላት ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ይኽን ያደረግን እንደኾነ ታላቅ ሐሴት እናደርጋለን፤ ርሷም ቁስለ ነፍሳችንን ትፈውስልናለች፡፡

በሌላ አገላለጽ ብነግራችኁ ሐኪሞች በአንድ ታማሚ ሰውነት ውስጥ ያለውን ቆሻሻ፣ መርዘኛ ፈሳሽን ማስወገድ ሲፈልጉ መጀመሪያ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር ታማሚው ምግብ ከመውሰድ እንዲቈጠብ ነው፡፡ ታማሚው ለጊዜው ምግብን ከመብላት ካልተከለከለ ሓኪሞቹ የሚሰጡት መድኃኒት እንደተፈለገው ውጤት አይሰጥም፡፡ እኛም ቁስለ ነፍስ ቁስለ ሥጋ የምትፈውሰውን ጾም ስንቀበላት ከዚኽ በላይ ልንኾን ይገባናል ብዬ እነግራችኋለኹ፡፡ ድኅነተ ሥጋ ድኅነተ ነፍስን የምንሻ ከኾነ ልቡናችንን ንጹሕና ንቁ በማድረግ ልንወስዳት ይገባናል፡፡ እንዲኽ ካልኾነ ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ያመዝናል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ጾመ ነቢያት (የገና ጾም)
ነገ ኅዳር 15/2017 ዓ.ም
(Nov 24/2024 G.C) ይገባል፡፡

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

"ቤተክርስቲያንን የሚያስቀጥሉ ሦስት ሰንሰለቶች አሉ እነርሱም:---
ትዳር ፣ ምንኩስና እና ክህነት ናቸው።

እነዚህ እክል ስለገጠማቸው ነው ቤተክርስቲያን እየተቸገረች ያለቸው እንጂ ሌሎች ሰዎች ወይም አህዛብ ክፉ ስለሆኑ አይደለም። እነሱ ደግ የሚሆኑበት ዘመን ነገም እኔ አልጠብቅም ሰይጣን ባለበት መልካም ነገር አይመጣም።

እኛ ግን የጎደለን ይህ ነው፣ በተከበረ ትዳር ፣በተከበረ ምንኩስና እና በተከበረ ክህነት ቤተክርስቲያን ትቀጥላለች።

ምሳሌ እንዴት ካልን፦
የተከበረ ትዳር:- የተከበረ መነኩሴ ይወልዳል።
የተከበረ መነኩሴ:- የተከበረን ጵጵስናን ያመጣል።
የተከበረ ጳጳስ:- የተከበረን ክህነትን ይሾምና
የተከበረው ክህነት:- የተከበረ ትዳርን ባርኮ ያጋባል። የተከበረው ትዳር መልሶ እንደገና የተከበረ ካህንን ይወልዳል።

በዚህ ዑደት ነው ቤተክርስቲያን ተጠብቃ የምትኖረው። አሁን ግን ምንጩ ደፍርሷል። ለዚህም ሁላችንም መስተካከል አለብን። አሁን እኔ ሁሉም ሥርዓት እየፈረሰ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ! ተምረን ማግባትና፣ተምረን መመንኮስም ሆነ ክህነት መያዝን ማስቀጠል አለብን።"

ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ተግሣፅ ዘቅዱስ ኤፍሬም

ሕይወትህን በአግባቡ መምራት ትፈልጋለህን? እንግዲያውስ ትሕትናን ተለማመድ፤ ያለ ትሕትና ተገቢውን ሕይወት መምራት አይቻልም፡፡ ሥራህን ሁሉ በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ጀምር፡፡ ያን ጊዜ ፍሬዎችህ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይደርሳሉ።

ሰው ከትሕትና ከራቀ ከትክክለኛው መንገድ ርቋል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔርን የተወ ሰውን ርኵስ መንፈስ እንደ ሳውል ያስጨንቀዋል። የጠላት ወጥመድ በማር የተቀባ ነው፡፡ በማር ጣዕም የሚማረክ ሰው ሐዘንን ሁሉ በያዘ ወጥመድ ይያዛል። ትሕትናን ውደዱ፤ ያን ጊዜ ከሰይጣን ወጥመድ ውስጥ አትወድቁም፡፡ በትሕትና ክንፍ በበረራችሁ ቁጥር ሁል ጊዜ ከጠላት ወጥመድ በላይ ትሆናላችሁ።

ግልፍተኝነት እንደ በሰበሰ ረጅም ዛፍ ነው፤ ቅርጫፎቹ ሁሉ በቀላሉ የሚሰበሩ ናቸው᎓᎓ አንድ ሰው በወጣባቸው ጊዜ ከወጣበት ከፍታ ወዲያውኑ ይወድቃል፡፡ በመልካም ሐሳብ ልቡናው የበራ ሰው ግን ምስጉን ነው፤ ክብሩም ታላቅና ዘላለማዊ ነው።

እንግዲህ ራሳችንን ለመቆጣጠር እንጣር ያን ጊዜ ኃጢአታችንን እንረዳለን፡፡ ያን ጊዜም ሁል ጊዜ ራሳችንን ዝቅ እናደርጋለን፤ እንደ እባብ በእብሪት መወጠርን እና ራሳችንን ከፍ ከፍ ከማድረግ እንቆጠባለን፡፡ እንግዲህ ራሳችንን ዝቅ ዝቅ ማድረግን እንውደድ፤ በንጹሕ ልቡና ሆነን ምናልባት የተሰጠንን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በኃጢአት ከማቆሸሽ እንታደግ ይሆናል።

መልካም ጸሎት በሳግ እና በዕንባ የታጀበ ነው፤ በተለይ ደግሞ በምሥጢር የሚፈስ ዕንባ፣ በልቡናው ከፍታ ሆኖ የሚጸልይ ጌታውን በፊቱ ያያል። እኛ የምንኖረውና የምንሔደው በእርሱ ፈቃድ ነውና። ልቡናችሁ ከጠነከረ በጌታችን ፊት አልቅሱ እርሱ የዕውቀትን ብርሃን ይገልጥላችኋል፤ ወደ እርሱ የሚወስዳችሁ አዲስ ልብንም ይሰጣችኋል።

ንስሓ የገቡና ምሕረት የለመኑ ሰዎች ዕዳቸው ተሰረዘላቸው፤ ነገር ግን ለሠራኸው በደል ምሕረት ስትለምን ወንጀልን እና በደልን፤ በወንድምህም ላይ ቂም መያዝን መተው ይገባሃል። ፍቅር ሳይኖርህ ወደ እግዚአብሔር የምታደርገው ልመና ከተዘጋው በር ውጭ ይቀራል፡፡ የጸሎትን በር የሚከፍት ፍቅር ብቻ ነው፡፡

ወንድምህን ብታስቀይም እግዚአብሐርን ታሳዝናለህ፤ ካንተ ጋር ካለው ከወንድምህ ጋር ሰላምን ከፈጠርህ ግን በሰማይ ካለው ከእግዚአብሔር ጋር ትታረቃለህ፡፡ ወንድምህን በፍቅር ብትቀበለው፣ በደሉንም ይቅር ካልከው እግዚአብሔርን ተቀበልክ፡፡

ስለዚህ በተናደዱ ሰዎች በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ታረቅ፤ እንግዲህ የተበሳጩትን በማስደሰት እግዚአብሔርን አስደስተው፣ በታሰሩት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን ጎብኘው፣ በተራቡት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አብላው፤ በታረዙ ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አልብሰው፣ መንገደኛን በመቀበል እግዚአብሔርን በአልጋህ ላይ አስተኛው፤ እግሮቹንም እጠበው፣ በማዕድህም አስቀምጠው፣ እንጀራህንም ከእርሱ ጋር ተካፈል፤ ጽዋህንም ስጠው᎓᎓ እርሱ ታላቅ ፍቅሩን አሳይቶሃልና፤ እርሱ ስለ አንተ ብሎ ትበላው ዘንድ ሥጋውን ቆርሶልሃል፣ ትጠጣው ዘንድም ደሙን አፍስሷል።

(ድርሳነ ቅዱስ ኤፍሬም ገጽ 334 - 336  በዲ/ን መዝገቡ ከፍያለው የተተረጎመ)


የሀገረ ማርያም የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት ሚዲያ(መሠረተ ሚዲያ )

                  ⬇️

➡️      መሰረተ ሚዲያ   ⬅️

                  ⬆️

የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️
⤵️ ⬇️
/channel/Meseretemedia

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#መጽሐፍ_ቅዱስን_የሚያነቡ_ሰዎች_በ፭ ይመደባሉ

በ፭ የመደብኳቸው እራሴ በተለያየ ምክንያት ያገኘኋቸውን ሰዎች ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ያላቸውን ልምድ በመጠየቅ ካገኘሁት መልስ የተነሳ ነው።

አጭር ስለሆነ እስከ መጨረሻ አንብባችሁ ሐሳብ ስጡበት።

በዚህ አጋጣሚ የመምህር #በትረ_ማርያምን ምክረ ሐሳብ እንከተል እላለሁ።
የእኔም ልምዴ ሁሌም ጧት ጧት ከጸሎት በኋላ ከመጽሐፍ ቅዱስ
ከብሉይ ኪዳን ፫ ምዕራፍ ፣ ከሐዲስ ኪዳን ፪ ምዕራፍ ከዚያ ቀጥሎ የዕለት ስንክሳር ሳላነብ አልወጣም።
ምናልባት ልምዱ ከጠቀማችሁ ብየ ነው እንጂ ይህን ማውራት ፈልጌ አይደለም ።
ግን ማልዶ መነሣትን ይጠይቃል።

✝️፩ኛ, በአጋጣሚ የሚያነቡ፦ እነዚህ መጽሐፍ ቅዱስን የሚያነቡት እንደ ማንኛውም መጽሐፍ በአጋጣሚ ካገኙትና እጃቸው ከገባ ምን እንደሚል ሳያስተውሉ የሚያነቡ ናቸው።
ለምሳሌ፦አንዱ ጓደኛው ጋዜጣ ሲያነብ ሲያየው ቀበል ብሎ አንዳንድ ነገሮችን አንብቦና ፎቶ አይቶ ጋዜጣውን እንደሚመልስ ሰው ናቸው።
በአጋጣሚ ስለሚያነቡትም አይጠቀሙበትም።

✝️፪ኛ, ለጥናትና ለዕውቀት የሚያነቡ፦ እነዚህ ሃይማኖት ከየት መጣ? ማን ጀመረው? ወዘተ የሚለውንና ሌሎች ተዛማጅ ነገሮችን ለማጥናትና ለማወቅ የሚያነቡ ናቸው።
ስለሆነም ለጥናትና ለዕውቀት ብቻ ስለሚያነቡት አይጠቀሙበትም።

✝️፫ኛ, ለትችት የሚያነቡ ፦ እነዚህ ደግሞ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ሕይወት እንደሆነ ለማወቅና እንደ ቃሉ ለመኖር ሳይሆን ለመተቸትና የሚቀበሉትን ሰዎች ለማወናበድ የሚያነቡ ናቸው።
ለትችት ስለሆነ የሚያነቡት በቃሉ አማካኝነት በእግዚአብሔር አምነው ወደ ሕይወት አይደርሱም።

✝️፬ኛ, በመስማት የሚያነቡ፦ እነዚህ ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል ሲባል ይሰሙና ውይ ደስ ሲል ብለው ማንበብ ብቻ ስለሚወዱ ያነቡታል።
ነገር ግን የማይገባቸውና ለሕይወት የማይበቁ ናቸው።
ተግተውና ደጋግመው ቢያነቡት ልባቸው ተለውጦ ሊድኑ ይችላሉ።

✝️፭ኛ, ለሕይወት የሚያነቡ ፦ እነዚህ የእግዚአብሔር ቃል ሕይወት እንደሆነና ቃሉን በመስማት ድኅነት እንደሚገኝና ወደ ድኅነት እንደሚያደርስ በማመን የሚያነቡ ናቸው።
"ወዝኒ ቃል ዘአነ ነገርኩክሙ መንፈስ ውእቱ ወሕይወት ውእቱ = ይኽ እኔ የነገርኋችሁ ቃል መንፈስ ነው ሕይወት ነው" እንዲል (ዮሐ፮፥፷፫)።
✔️እነዚህ አንባቢዎች ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ
"ዘዳዕሙ ሕገ እግዚአብሔር ሥምረቱ
ወዘሕጎ ያነብብ መዓልተ ወሌሊተ
ወይከውን ከመ ዕፅ እንተ ትክልት ኀበ ሙኃዘ ማይ
እን ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ
ወቈጽላኒ ኢይትነገፍ
ወኵሎ ዘገብረ ይፌጽም (መዝ፩፥፪-፫) በማለት እንደነገረን ነው የሚሆኑት።

እኛስ መጽሐፍ ቅዱስን የምናነበው ለምን ዐላማ ነው❓
✔️በአጋጣሚ
✔️ለጥናትና ለዕውቀት ብቻ
✔️ለትችት
✔️በመስማትና ጥቅሱ ደስ ስላለን
✔️ለሕይወት
ወይስ ሰባኪና አስተማሪ ለመሆንና ተቀጥሮ ደሞዝ ለማግኘት ለምን❓

እንደእኔ ፭ኛውን ብንመርጥ በነፍስም በሥጋም ተጠቃሚዎች እንሆናለን።
እናንተስ❓
ሌላም ከአምስቱ ውጪ ቢጨመሩ የምትሉትን መጨመር ትችላላችሁ እኔ ግን አንዳንድ ሰዎችን ስጠይቅ ያገኘሁት መልስ ባብዛኛው በአምስቱ የሚጠቃለል ነው።

መልካም ንባብ።

ወጣቱን መጽሐፍ ቅዱስ እንዲያነብ እያበረታቱ ለሚገኙት ለመምህር #በትረ_ማርያም እድሜና ጤና ይስጥልን።

@መምህር ዳንኤል አለባቸው

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ቅዱስ መስቀል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

በመስቀል ከጠላትነት ድነናል፤ በመስቀል ወደ እግዚአብሔር አንድነት ተመልሰናል፡፡ በመስቀል ዲያብሎስ አርነት ወጥተናል፤ በመስቀል ከሞትና ከጥፋት ድነናል፡፡

ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን በሞት ጥላ ሥር ተይዘን ነበር፤ አሁን ብሥራተ መስቀል በተገለጠበት ጊዜ ግን ህልውና እንኳን እንደሌለው አድርገን ቈጥረን የዘለዓለም ሕይወትን እየናፈቅን ሞትን ንቀነዋል፡፡ ብሥራተ መስቀል ባልተነገረበት ዘመን ለገነት እንግዶች ነበርን፤ መስቀል በተገለጠ ጊዜ ግን ወንበዴስ እንኳን ለገነት የተገባ ሆኖ ተገኘ፡፡

የሰው ልጅ እንደዚህ ካለ ጨለማ መጠን ወደ ሌለው ብርሃን፣ ከሞት ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት፣ ከመዋቲነት ወደ ኢመዋቲነት ታድሶ ተሸጋገረ፡፡ ዓይነ ልቡና ባለማወቅ ጽልመት ከመታወር ድኖ በመስቀል የዕውቀት ብርሃን ተጥለቀለቀ፡፡ እዝነ ልቡና ካለማመን ድንቁርና ወጥቶ የእግዚአብሔርን ቃል ወደ መስማት ተመለሰ፤ ዕውራንም ብርሃናቸው ተመልሶላቸው የእግዚአብሔርን ክብር ማየት ተችሎአቸዋል፡፡ በቅዱስ መስቀሉ የተሰጡን ሀብታት እነዚህ ናቸው፡፡ በቅዱስ መስቀሉ ያልተሰጡን በረከቶችስ ምን አሉ?

እነሆ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእግዚአብሔር ማመንም ተመልሷል፤ የእውነት ወንጌልም ወደ ዓለም ሁሉ ደርሷል፡፡

ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ ሰማዕታትም ከመስቀል በኋላ ሞት ሞት መኾኑ እንደ ቀረና የሹመት የሽልማት ማሳ መኾኑን ዐውቀው አብረው ተገልጠዋል፤ በክርስቶስ ማመንም በሁሉም ዘንድ ተሰራጭቷል፡፡

ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእርሱም ሞት ራሱ ሞቷልና ትንሣኤ ሙታንም ተገልጧል፤ ሕይወትም ታይታለች፤ መንግሥተ እግዚአብሔርም እንደዚሁ እርግጥ ኾናለች፡፡

ቅዱስ መስቀሉ ለእነዚህ ኹሉ ነገሮች ምክንያት ኾኗል፡፡ በመስቀሉ እግዚአብሔርን ማመስገን ተማርን፡፡ እንግዲህ ከቅዱስ መስቀሉ ይልቅ ሌላ የተወደደ ምን አለ? እኮ ከቅዱስ መስቀሉ በላይ ለነፍሳችን የሚረባት ወይም የረባትና የጠቀማት ሌላ ምን አለ? ስለዚህ በሙሉ ልባችን ይህን እንመስክር እንጂ ስለ ቅዱስ መስቀሉ ለመናገር ቅንጣት ታህልስ እንኳን አንፈር፡

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

"የክርስቶስ መስቀል ታላቅ በረከትንና ድኅነትን እንድናገኝ ምክንያት እንደ ሆነ እናስተውላለን፡፡ የክርስቶስ መስቀል ስናስበው ሐዘንና ምሬት ነው ነገር ግን እውነታው ደስታና ሐሴትን የሚሞላ ነው፡፡ መስቀል ለቤተ-ክርስቲያን ድኅነት ነው መስቀል ተስፋ ለሚያደርጉት መመኪያ ነው መስቀል የእግዚአብሔር ጠላቶች የነበሩት የታረቁበትና ኃጢአን ወደ ክርስቶስ የቀረቡበት ነው፡፡ በመስቀል ከጠላትነት ወደ እግዚአብሔር ልጅነት ተሸጋግረናል በመስቀል ከዲያብሎስ ቀንበር ወጥተናል ከሞት ወደ ሕይወት መጥተናል፡፡ ስለ መስቀል የማንሰብክ ከሆነ አሁንም በሞትና በፍዳ እንደ ተያዝን ነው ማለት ነው፡፡
            ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
/channel/dnhayilemikael

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

"አቤቱ ጥበብንና ኃይልን ልብንና እና ልቡናን ዕውቀትንም ስጠን። እንግዲህ ከሚፈታተነን ከሰይጣን ሥራ ሁሉ እስከ ዘላለሙ እንርቅ እንሸሽም ዘንድ። አቤቱ ሁልጊዜ ፈቃድህን ውድህንም እንሠራ ዘንድ ስጠን።"
   ሥርዓተ ቅዳሴ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

+ ምቹ ቀን ሆነላት +
ማር 6:21
ብዙ ጊዜ ክፉ ሰዎች የሚጠሉትን ሰው ለማጥቃት ምቹ ጊዜ ይጠብቃሉ።መጽሐፍ ቅዱስ ይሁዳ ጌታውን አሳልፎ ለመስጠት ምቹ ጊዜ ይጠብቅ ነበር ይላል።"ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ አሳልፎ ሊሰጠው ምቹ ጊዜ ይሻ ነበር።"(ማቴ 26:16 ) ስለዚህ ወዳጄ በዙሪያህ ያሉ ሰዎች ሁሉ ስትስቅ የሚስቁት እንቅፋት ሲመታህ እኔን የሚሉ ሁሉ ይወዱሃል ማለት አይደለም አንተ የምትወድቅበትን ምቹ ቀን እየጠበቁ ነው።ጠላት ሁልጊዜም አንተን ለማጥቃት ወደ አንተ የሚቀርበው ደካማ ጎንህን አይቶ ነው።ይህን ያነሳሁበት ያለ ምክንያት አይደለም የጌታ መንገድ ጠራጊ ባሕታዊ መናኝ ካህን የሆነውን የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስን ራስ ያስቆረጠችው የሄሮዳዳ ልጅ የዚህን ቅዱስ ራስ ለማስቆረጥ መጽሐፍ እንደሚናገር ራሱን የምታስቆርጥበት ምቹ ቀን ትጠብቅ ነበር። ለንጉሡና ለእርሷ ምቹ ቀን ሆነላትና የቅዱሱን ራስ አስቆረጠችው።ሁልጊዜም አምነኸው የማይከዳህ ተደግፈኸው የማይጥልህ ለምነኸው ፊቱን የማያዞርብህ ቀን አይቶ ብቻህን የማይተውህ እግዚአብሔር ብቻ ነው።
አዲሱ ዓመት የሰላም የጤና ይሁንልን።
Dn Sintayehu Emagnu
መስከረም 01/01/2017 ዓ.ም

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

“ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንደሚሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋል” ዕብ 11፥6 እንዲል!
@ ጃንደረባው ሚዲያ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

"ለነፍስህ የምታደርግላት ታላቅ ነገር አለ ይኼውም ራስህን በሚገባ መርምረህ ማወቅ ነው።"
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#ፍኖተ #እንድርያስ
ብዙዎቻችን ለብዙ ደቂቃ ስላወራን የሰበክን ሊመስለን ይችላል። ለስብከት አርዓያ ብናደርጋቸው ብዬ የማስባቸው አራት ዓይናውን ሊቅ አቡነ እንድርያስን ነው። ብዙ ጊዜ ሲሰብኩ በቦታ ተገኝቼ ሰምቻለሁ። እኔ በተሳተፍኩባቸው ስብከቶች ረጅም ደቂቃ የሰበኩት 21 ደቂቃ ነው። ነገር ግን ከዐሥር ዓመት በፊት በአጭር ደቂቃ የሰበኩትን ስብከት እስካሁን አስታውሰዋለሁ።

በግሌ ስብከት ከ30 ደቂቃ ባይበልጥ ባይ ነኝ። በሠላሳው ደቂቃ ግን ቧልት፣ ፌዝ፣ ቀልድ ያልተቀላቀለበት ጉዳይ ተኮር፣ ሕይወት ተኮር ስብከት ቢሰበክ መልካም ነው። ስብከት እንዲህ ከሆነ ሥልጠና ግን ቀኑን ሙሉም ቢሰጥ ለውጥ ያመጣል ብየ አስባለሁ። ሥልጠና አንድን ጉዳይ አጥርቶ የማሳወቅ አቅሙ ከፍተኛ ነው።

ዓውደ ምሕረቶች ነገረ ክርስቶስ፣ ነገረ ቅዱሳን፣ ነገረ ማርያም፣ ነገረ ሃይማኖት፣ የሥርዓትና የሥነ ምግባር ትምህርቶች ቢሰጥባቸው አትራፊ እንሆናለን። የሙገሣ የጭብጨባ የግርግር ሰዓት ባይሆኑ ይመረጣል። ብፁዕ አባታችን አቡነ እንድርያስ በስብከት መካከል ጭብጨባንና እልልታን አጥብቀው ይቃወማሉ። እንኳንስ መንፈሳዊ ማዕድ ሥጋዊ ማዕድ ቀርቦ ምግቡ ቢጣፍጠን እንኳ ጣፈጠን ብለን መካከል ላይ እልል አንልም አናጨበጭብም። ምግቡን እያጣጣምን በሥርዓት እንመገባለን። በስብከት ሰዓት ጭብጨባና እልልታ ተገቢ አይደለም።

የጭብጨባና የእልልታ ሰዓት ማኅሌት ነው እንጂ ስብከት አይደለም። ፍኖተ እንድርያስን እንከተል ስል

፩ኛ ስብከታችን አንድን ጉዳይ ዓለማዊ ፍልስፍና ሳንቀላቅልበት እንደእርሳቸው መንፈሳዊውን ጉዳይ አሥርፀን ማጠቃለል ብንችል።

፪ኛ ሰዓት ማርዘም ሳይሆን ማስተማር የፈለግነውን ጉዳይ ግልጽ በሆነ አቀራረብ እስከ ሠላሳ ደቂቃ ባለው መጨረስ ብንችል። ከሠላሳ ደቂቃ በኋላኮ አብዛኛው የመስማት አቅሙ ይቀንሳል።

፫ኛ በስብከታችን መካከል ቧልት፣ ፌዝ፣ ቀልድ ባንቀላቅል።

ማለቴ ነው። የክርስትና ሕይወትና ትምህርት የሚሰለች አይደለም። በሕይወት እየተረጎምነው ስንሄድ ሁልጊዜ አዲስ (እንደገና አዲስ)፣ እያደር አዲስ ነው። የምናውቀውን ታሪክ መምህሩ ሲደግመው ብንሰማ እንኳ በዚህ ታሪክ ምን ያህል እንደተለወጥን ራሳችንን መመርመር ይገባናል።

© በትረ ማርያም አበባው

Читать полностью…

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

ደብረ ታቦር  


❖በዓለ  ደብረ  ታቦር  የሚውለው  በነሐሴ  13  ቀን  በመሆኑ ለጾመ ፍልሰታ ሱባዔ ልዩ ምዕራፍ ሆኖ በታላቅ መንፈሳዊ ተመስጦና  ማኀሌት  ይከበራል።  ከዘጠኙ  ዐበይት የጌታችን  በዓላት  አንዱ  ነው።  ምን  አድርጎበታል  ቢሉ ብርሃነ  መለኮቱን  ለሐዋርያት  በደብረ  ታቦር    ገልጾበታል። ደብር  ተራራ  ታቦር  የተራራ  ስም  ነው።  ጌታ  በመዋዕለ ስብከቱ  ብዙውን  ጊዜ  የሚያስተምረው  ተአምራት የሚያደርገው  በተራራ  ላይ  ነበር።  በዚህም  ዕለት ዘጠኙን  ከእግሩ  ደብር  ትቶ  ሶስቱ  ጴጥሮስን  ዮሐንሰንና ያዕቆብን  አስከትሎ  ከርእሰ ደብር ወጣ። ወተወለጠ ራዕዩ በቅድሜሆሙ  ወአብርሀ  ገጹ  ከመ  ፀሐይ  ወአልባሲሁኒ ኮነ  ጸዓዳ  ከመ  በረድ  ይላል  መልኩ  ተለውጦ  ፊቱ  እንደ ጸሐይ  አብርቶ  ልብሱ  እንደ  በረድ  ነጽቶ  ሙሴና  ኤልያስ በቀኝ  ሆነው  ታዩአቸው።  ሙሴንና  ኤልያስን  መምረጡ  ስለምንድነው  ቢሉ  ሙሴ  570    ጊዜ  ቃል በቃል  ተነጋግሮ    ባይህ  እወዳለሁ  አለው  ፊቴን  አይቶ  አንድ  ሰዓት  እንኳ  መቆም  መቆየት  የሚቻለው የለም  አለው  ።  ይህማ  ካልሆነማ  ባለሟል  መባሌ  ምኑ  ላይ  ነው።  ቢለው  ኃላ  ሰው  ሆኜ  ስመጣ እታይሃለው  ብሎት  ነበርና  ዘጸ  33:18-23  ነው።  ያን  ለመፈጸም  ኤልያስም  እንዲሁ  ተስፋ  ነበረውና አንድም  ጌታ  ዕውር  ቢያበራ  ሙት  ቢያነሳ  ሙሴ  ነው  ኤልያስ  ነው  ብለውት  ነበርና  የኛን  ጌታ  ማን ሙሴ   ማን ኤልያስ ይልሀል የሙሴ የኤልያስ ጌታ ይበሉህ እንጂ ብለው እንዲመሰክሩ አምጥቷቸዋል። ፍጻሜው  ግን  ደብረ  ታቦር  የመንሥተ  ሰማያት  ምሳሌ  ናት።  ሕጋውያንም  ደናግልም  እንዲወርሷት ለማጠየቅ ከሕጋውያን ሙሴን ከደናግል ኤልያስን አመጣ። ጴጥሮስ እመሰ ትፈቅድ ንንበር ዝየ ወንግበር ሠለስተ ማኅደረ አሐደ ለከ አሐደ ለሙሴ ወአሐደ ለኤልያስ ብትወድስ  አንዱን  ላንተ  አንዱን  ለሙሴ  አንዱን  ለኤልያስ  ሶስት  ጎጆ  ሠርተን  በዚህ  እንኑር  አለው። መጽአ  ደመና  ብሩህ  ወጸለሎሙ  ይላል  ።  ይህን  ሲናገር  ብሩህ  ደመና  መጥቶ  ጋረዳቸው  ወዲያውም ዝንቱ  ውእቱ  ዘአፈቅር  ወሎቱ  ስምዕዎ  ቢሉ  ደስ  የሚለኝ  ልጄ  ይህ  ነው።  እሱን  ስሙት  የሚል  ድምፅ ከወደ  ላይ  ተሰምቷል  ።እነ  ጴጥሮስ  ደንግጠው  ወደቁ  ተንሥኡ  ወኢትፍርሁ  ብሎ  አንስቷቸዋል  ። ከርእሰ  ደብር  ሲወርዱም  ያዩትን  የሰሙትን  እስከ  ትንሳኤው  ለማንም  እንዳይናገሩ  አዟቸዋል ።ማቴ  17  :3-9  ዘጠኙን  በእግረ  ደብር  ትቶ  ሶስቱን  አስከትሎ  መውጣቱ  ስለምንድነው  ቢሉ ከዘጠኙ  ብርሃነ  መለኮት  ሊያይ  የማይገባው  ይሁዳ  ነበርና  ትቶትም  ቢሄድ  ለየኝ  ባለ  ነበርና  አንድም ጴጥሮስ  እሞታለሁ  እነሣለሁ  ቢለው    ካንተ  ይራቅ  ብሎት  ነበርና  እሱን  ስሙት  የሚለውን  እንዲሰማ አምጥቶታል። ዮሐንስና ያዕቆብንም በመንግሥቱ በመጣ ጊዜ በቀኝ በግራ መቀመጥን ሽተው ነበርና ነው።  ያስ  ቢሆን  ከተራሮች  ሁሉ  ታቦርን  ስለምን  መረጠ  ቢሎ ዳዊት ታቦር  ወአርሞንኤም በስመ ዚአከ ይትፌስሑ መዝ 87:12ብሎ ያን ለመፈጸም ነው።

Читать полностью…
Subscribe to a channel