እንኳን ደህና መጡ። በቴሌግራም ውስጥ የታዋቂ ሰዎች ማለትም 💥አርስቶትል 💥አብርሀም ሊንከን 💥አልበርት አንስታይን 💥ማህተመ ጋንዲ... እንዲሁም የሌሎችም አባባል የሚያገኙበት ቻናል🎯 ሲሆን አላማችንም ሰዎች በሚያነብቡት ጥቅስ የአስተሳሰባቸውን አድማስ ማስፋት ነው። ስለመረጡን እናመሰግናለን 🙏 Contact፦ @onajonah
ይችላል
"እውነት ነው።
ብዙ ነገር ተስፋ ያስቆርጣል።
ስራ አታገኝም!
ብታገኝም ብሩ አይበቃህም!
ዙሪያው ሁሉ ጨልሞ
ተስፋ የሌለህ መስሎሃል።
እና በቃ አልችልም ብለሃል።
ግን ከዚህ ሁሉ በላይ ፈጣሪ አለ!
ፈጣሪ አይችልም ትላለህ?
አትልም።
ይችላል!
ያመንከው ላይ ተስፋ አትቁረጥ።"
ፈጣሪን ተማምነህ ወደህልምህ መጓዝን ቀጥል
መልካም ቀን
share @ethio_tksa_tks
ቀይሩ
👉 ክፉን በጥሩ
👉መጥፎ ሐሳቦችን የንጽህና ነገሮችን በማሰብ
👉ኃጢአትን በንስሐ
👉አድልኦን ሁሉንም በመውደድ
👉ኩራትን በትህትና
ሰናይ ቀን
@ethio_tksa_tks
ፈጣሪህን እንዲህ በለው
ፈጣሪዬ ኾይ
በማይታወቀው ነገ ውስጥ
"መልካሙን"
በክፉ ዘመን
" ተስፋ ማድረግን"
በደስታ ጊዜ
"መረጋጋትን"
ላለፈው ትናንት
"ይቅር ባይነትን"
ስጠኝ!!!
አሜን።
@ethio_tksa_tks
ሞኝ ሰው በሩቅ ደስታን ይፈልጋል; ጠቢብ ከእግሩ በታች ያበቅላል.
አንድ ዛፍ ጫካን ማስጀመር ይችላል
አንድ ፈገግታ ወዳጅነትን ይችላል
አንድ እጅ አንዲት ነፍስን ሊያነሳ ይችላል
አንድ ሻማ ሙሉ ጨለማን ሊገፍፍ ይችላል
ዛሬ ያንን አንድ ሰው ሁን
@ethio_tksa_tks
#ለፈገግታ
ከእናቱ ጋር ፊልም ሲያይ የቆየው ልጅ ወደ እናቱ ዞር ብሎ ''እናቴ አኔ ሳድግ እንደ አክተሩ 7 ሚስት ነው ማገባው" አላት እተተኮላተፈ። እናት ፈገግ ብላ "ምን ያረጉልሀል ሰባት ምታገባው አንድ አይበቃህም?" አለችው።
"አይ እናቴ ሰባት ነው ማገባው። የመጀመሪያዋ ምግብ ታበስልልኛለች፣ ሁለተኛዋ ልብሴን ታጥብልኛለች ......... እያለ ሲዘረዝር እናት ግራ ተጋብታ "ታድያ የትኛዋ ናት አብራህ የምትተኛው?' አለችው። ልጁም ወዲያው ያለምንም ማንገራገር "የምተኛውማ ካንቺ ጋር ነው ከእናቴ ጋ" አላት .
እናት ደስ አላት የኔ ልጅ እያለች እቅፍ አርጋ ሳመችውና "ታዲያ ሚስቶች ከማን ጋር ሊተኙ ነው?'' አለችው በስስት እያየችው።
"እነሱማ ከአባቴ ጋር ይተኛሉዋ : አላት
እናት
ስራ ይዞ ወሬውን ሲከታተል የተበረው አባት ደሞ ብድግ ብሎ ልጁን አቀፈውና "ተባረክ ልጄ ብሩክ ሁን ያሰብከው ይሳካልህ'😂
Share @ethio_tksa_tks
ምላሽ የመስጠት ጥበብ
🙂
አንድ አህያ ከመስጂድ ፊት ለፊት ሞቶ ተገኘ። ይህን የተመለከቱት ኢማም ከንቲባውን ጠርተው እንዲህ አሉት፡-“ክቡር ፕሬዝዳንት አንድ አህያ ከመስጂድ ፊት ለፊት ሞታለች”
ከንቲባው፡-“ሼኽ ሆይ ከኔ ምን ፈልገው ነው ታድያ?”
ኢማሙም መለሱ፡-“የማዘጋጃ ቤቱ ሃላፊዎችን ጥራቸው። ሰራተኞቹ መጥተው አህያውን ከመስጂዱ ያንሱልን።”
ከንቲባው በኢማሙ ላይ እየተሳለቀ፡-“ያ ሼይኹ እኔ በሃይማኖታችን እንደተማርኩት ከሆነ እናንተ ናችሁ ሟችን አጥባችሁ የመቅበር ግዴታ ያለባችሁ”
ኢማሙም በተረጋጋ መንፈስ መለሱ፡-“ልጄ የተናገርከው ሁሉ እውነት ሆኖ ሳለ አህያዋ መሞቷን ግን ለአንተ መናገር ነበረብኝ ምክንያቱም እኛ አጥበን የመቅበር ግዴታ እንዳለብን ሁሉ፤ የሟች ቤተሰብ የቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ ለመጨረሻ ግዜ ሬሳውን እንዲሰናበት የማሳወቅ ግዴታም አለብን”
አርምሞ
@ethio_tksa_tks
ለፈገግታ
ፍልስፍና ሲማር የነበረው ልጅ ትምህርቱን አጠናቆ ቤተሰቡ ለመዘየር ወደ ቀየው ይሄዳል። አባትም ደስተኛ ሁነው ዶሮ አርደውና አዘጋጅተው ይጠብቁታል። ቃለ ምልልሳቸው ከብዙ በጥቂቱ ይህ ነው።
አባት፦ እና አሁን በቃ ዶክተር ሁነሀልና የታመሙ ሰዎችን ማከም ጀመርክ እንዴ?
ልጅ፦ አይደለም አባቴ እኔ ዶክትሬቴን የያዝኩት በፍልስፍና ነው፤ ከህክምና ጋር አይያያዝም።
አባት፦ ደግሞ የሱ ጥቅም ምንድን ነው?
ልጅ፦ ላስረዳህ አሁን እዚህ ጋ የምታየው ዶሮ አንድ ዶሮ ብቻ ነው አይደል?
አባት፦ አዎ
ልጅ፡- በፍልስፍና እውቀቴ መሠረት ግን እዚህ ላይ ያለው ዶሮ አንድ ብቻ ሳይሆን ሁለት ናቸው ብየ ላሳምንህ እችላለሁ።
አባት፦ "ማሻአላህ ልጄ ቀድመህ ካሁኑ አሳመንከኝ እኮ"
ልጅ፦ እንዴት?
አባት :- ጠረንጴዛው ላይ ያለውን አንድ ዶሮ እያነሱ "እኔ ይህኛውን ዶሮ እበላለሁ አንተ ካገኘኸው ሁለተኛውን ዶሮ መብላት ትችላለህ 😂።
@ethio_tksa_tks
ፈጣሪ
👉በሀዘን ውስጥ
ፈገግ የምትልበት
👉ተከድተህ
የምታምንበት
👉በቀውስ ውስጥ
ሰላም የምታገኝበት
👉በድክመት
የምትበረታበት
👉ፈርተህም
ወደ ፊት የምትጓዝበት
ምክንያት ይሁንልህ!!!
አሜን
@ethio_tksa_tks
ሁሌም ከቀን ላይ ቀን ሲጨመርልህ ይህንን የፈጣሪ መልእክት አሰላስለው
💬 ሁልጊዜ ካንተ ጋር ነኝ
💬 ሕልምህን የሰጠሁህ በምክንያት ነው
💬ከእኔ ጋር ሁሉም ይቻላል
💬 አትጨነቅ፤ በእኔ ተማመን
💬 መቼም አልተውህም
💬 ጊዜው ሲደርስ፤ ያኔ አደርግልሃለሁ
💬 ናፍቀኸኛል፤ አዋራኝ
💬 ጭንቀትህን ለእኔ ስጠኝና ተኛ
መልካም ቀን🙏
@ethio_tksa_tks
> አንድ ሰው በበረሃ እየተጓዘ እያለ የያዘው ውሃ አልቆበት በውሃ ጥም ይያዛል ቀስ በቀስ ውሃ ጥሙ ሰውዬውን እያደከመው ይመጣል በስተመጨረሻ ከአንድ የውሃ ጉርጓድ ጋር ይደርሳል ጉርጓዱ በጣም ጥልቅ ነበረ ውሃ ይኑረው አይኑረው አይታይም፡፡
ከዚያም ከጉርጓዱ ጎን አንድ አሮጌ የውሃ መሳቢያ ሞተር አለ ሞተሩ ላይ እንዲህ የሚል ፅሁፍ ሰፍሯል፡፡ <<ይህ የውሃ መሳቢያ ሞተር የሚሰራው በውሃ ነው›› ይላል፡፡
ከሞተሩ ጎን አንድ ጆግ ሙሉ ውሃ ተቀምጧል ጆጉ ላይ እንዲሁ አንድ ፅሁፍ ሰፍሯል ‹‹ወዳጄ ሆይይህንን ጆግ ውሃ ሞተሩ ውስጥ ጨምረው ሞተሩ ብዙ ውሃ ያወጣልሃል ታዲያ አደራ አንተም እንዳንተ ላለ ሌላ መንገደኛ ይጠቅማልና ውሃው ከጉርጓዱ ሲወጣልህ ጆጉን ሞልተህ ማስቀመጥን አትርሳ›› ይላል፡፡
በጆግ ያለውን ውሃ ሞተሩ ውስጥ ይጨምረው ወይስ ይጠጣው? እዚጋር ሰውዬው በሁለት ሃሳብ ተወጠረ ‹‹አንደኛ ይህ ሞተር አርጅቷል ጨምሬው ባይሰራ ይህንንም ውሃ አጣሁ ማለት ነው ሞትኩ ማለት ነው ስለዚህ ልጠጣውና ህይወቴን ላድን ፡ ደሞ ማሳሰቢያውስ ውሃው ያለሞተር አይሰራም እንደኔ ውሃ የተጠማ ሰው ቢመጣ ይህንን ማንቀሳቀሻ ከጠጣሁት ይሞታሉ›› ብሎ ለራሱም ለሌሎቹም አሰበና በሃሳብ ተወጠረ በስተመጨረሻ በብዙ ጭንቀት ተወጥሮ ትልቅ ውሳኔ ወሰነ እንዲህ አለ <<ውሃውን ወደሞተሩ ብጨምረው ይሻላል ከሰራ ጥሩ ካልሰራ ግን እሞታለሁ እንጂ በፍፁም ይህንን ጆግ ውሃ ጠጥቼ ሄጄ ዛላለሜን ስለዚህ ጉርጓድና ይህንን ውሃ አተው ስለሚሞቱ ሰዎች እያብኩ መኖር አልፈልግም›› አለ፡፡
ከዚያም የጆጉን ውሃ ወደ አሮጌው ሞተር ውስጥ ጨመረውና የሞተሩን ማስነሻ ተጫነው፡፡ ሞተሩም ድምፅ እያሰማ ውሃ የማውጣት ስራውን ጀመረ፡፡ ሰውዬው ተደነቀ የሚፈልገውን ያህል ጠጣ አካባቢው በሙሉ በውሃ እራሰ ከጠበቀው በላይአካባቢው ሁሉ ውሃ በውሃ ሆነ ከዚያም በተባለው መሰረት እሱም ጆጉን በውሃ ከሞላው ቦሃላ ጆጉ ላይ ፅሁፍ ጨመረበት <<እመኑኝ በትክክል ይሰራል›› አለ፡፡
እና ምን ለማለት ፈልጌ ነው ለራስ ማሰብ በህይወት መኖር ነው ለሌላው ማሰብ ግን ሰው መሆን ነው፡፡ ያለህን በሙሉ ሳትሰስት ከሰጠህ በእጥፍ ድርቡ ፈጣሪ ይሰጥሃል። ሰውዬው ጆግ ውሃ ሰቶ አካባቢን የሚያርስ ውሃ እንደተቸረው አንተም የምትሰጣት ጠብታ ከልብህ ከሆነ በእጥፉ ይሰጥሃል፡፡ በምትሰፍረው መስፈሪያ ይሰፈርልሃል በሰጠኸው ልክ ይሰጥሃል ስለዚህ <<አመድ አፋሽ ሆንኩ›› ከማለትህ በፊት አመድ ሰተህ ከሆነስ፡፡ መስጠትን ብቻ ሳይሆን አሰጣጥህ ወሳኝነት አለው፡፡
@ethio_tksa_tks
ለራስህ ካላሰብክ ማንም ላንተ አይጨነቅም!
ካልሰራህ ደሃ እንደሆንክ ትቀራታለህ እንጂ ማንም አንተን ሃብታም አያረግም😊
ካላጠናህ ትወድቃለህ እንጂ ማንም አያስጠናህም
ገንዘብ ካልሰራህ ትቸገራለህ እንጂ ማንም እሱ ገንዘብ የለውም ቆይ በደንብ ልስራና ልስጠው አይልም
ለምንድነው እነዚህን ነገሮች ማስታውስህ እንዳትረሳው ነው።
እነዚህን መርሳት ስትጀምር ሰነፍ መሆን ትጀምራለህ
#አስታውስ እኔ ካልሰራው ማንም መጥቶ ከድህነት አያወጣኝም በል ፣ እኔ ካልሞከርኩ ማን ይጨነቃል ስለኔ ትዝም አልላቸው በል።
ደግሞም ውሸት አይደለም ትዝም አትለንም🤨
እንትና አለልኝ አትበል እሱም የራሱ ህይወት አለው።
ገንዘብ ቸግሮሃል?
ድብርት ውስጥ ነህ?..
ማን የራሱን ችግር ትቶ ያንተ ያሳስበዋል? ማንም!
ሁሉም ላይፉን ይኖራል እንጂ ያንተን ላይፍ አያስተካክልም።
"ለራስህ ያለኸው ራስህ ነህ!"
በርትተህ ቀጥል ወይም ተስፉ ቆርጠህ ተቀመጥ! 2ኛው ግን የሰነፎች ምርጫ ነው!
እንደውም ሰው ስላንተ ማሰብ ሚጀምረው ደሃ እያለህ ፣ ጭንቀታም እያለህ ፣ ሰነፍ እያለህ አይደለም ስኬታማ ስትሆን ፣ ደስተኛ ስትሆን ነው ሰው ስላንተ ሚያስበው። ደስታው ግን ከየት መጣ ይላሉ ምንሆኖ ነው ያላሉህ ስትጨነቅ ፣ ደሃ ሆነህ ያልጠየቁህ ገንዘብ ስትይዝ ከ10 አመት በፊት እንደምትተዋወቁ ትዝ ይላቸዋል🤔
አለም እንዲ ናት! ሁሉም የራሱን የሚያሳድድባት!
በርትተህ ቀጥል🔥
ፈተናን ተጋፈጥ ⚡️
ጠንካራ ሁን 💪
ጀግና ሁን👏
ወደፊት ገስግስ ⏩
በጽናት ቀጥል እስኪሳካ ድረስ!👍
መልካም ምሽት
share @ethio_tksa_tks
በቻናላችን የምትገኙ ሙስሊም ቤተሰቦቻችን እንኳን ለ1446ኛ የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! 🌙
መልካም በዓል ፤ መልካም ቀን ❤️
@ethio_tksa_tks
መሞት ትፈልጋለህ❓
ራስህን ወንዝ ውስጥ ክተትና እንዴት ራስህን ለማዳን እንደምትፍጨረጨር ታየዋለህ
ራስህን ከማጥፋት ይልቅ ውስጥህ ያለውን ነገር ለማጥፋት ሞክር።
Share @ethio_tksa_tks
ህይወት አጭር ናት
አንዲት አሮጊት ሴት አውቶብስ ላይ ወጥተው ተቀመጡ። በቀጣዩ ማቆሚያ ላይ አንዲት ወጣት ሴት ብዙ ቦርሳዎችን ይዛ እየተጣደፈች ገባች። ከአሮጊቷ ሴት አጠገብ ተቀምጣ በቦርሳዎቿ ገጨቻቸው።
አሮጊቷ ዝም አሉ፣ ነገር ግን ወጣቷ አስተውላ "በቦርሳዎቼ ስገጭዎት ለምን ምንም አላሉም?" ብላ ጠየቀች።
አሮጊቷ ፈገግ ብለው "እንዲህ ላለው ትንሽ ነገር መጨቃጨቅ አያስፈልግም። ከአንቺ ጋር ያለኝ ጉዞ አጭር ነው - በቀጣዩ ማቆሚያ እወርዳለሁ።" አሉ።
ይህ መልስ ሊታወስ የሚገባው ነው፡
"አብረን የምንቆየው ጊዜ በጣም አጭር ስለሆነ በትናንሽ ነገሮች መጨቃጨቅ አያስፈልግም።"
ህይወት በንዴት፣ በቅናት፣ ቂም በመያዝ ወይም አላስፈላጊ በሆኑ ክርክሮች ጊዜን ለማባከን በጣም አጭር ናት።
አንድ ሰው ስሜታችሁን ጎዳው/ጎዳሽ? ተረጋጉ። ህይወት በጣም አጭር ናት።
አንድ ሰው ከዳችሁ፣ዋሻችሁ ወይም አሳፈራችሁ በጥልቀት ተንፍሱ።ተዉት ህይወት በጣም አጭር ናት።
አንድ ሰው ያለ ምክንያት ሰደባችሁ ጉልበታችሁን አታባክኑ። ችላ በሉት። ህይወት በጣም አጭር ናት።
ጎረቤት መጥፎ ነገር ተናገሩ? ይዛችሁ አትቀመጡ ይቅር በሉ ቀጥሉ። ህይወት በጣም አጭር ናት።
በዚህ ዓለም ላይ የማንም ሰው ጉዞ ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ ማንም አያውቅም። የማቆሚያው ጊዜ መቼ እንደሚመጣ ማንም አያውቅም። ለዚህ ነው በዙሪያችን ያሉትን ሰዎች ማድነቅ፣ ደግ መሆን እና በቀላሉ ይቅር ማለት ያለብን።
ፍቅርን፣ ትዕግስትን እና ደስታን እንምረጥ - ምክንያቱም አብረን የምናደርገው ጉዞ በጣም አጭር ነው።
ፈገግታችሁን አካፍሉ… ምክንያቱም ህይወት አጭር ናት። ❤️
መልካም ምሽት
@ethio_tksa_tks
ይቺ ፍቅር የሆነች ሚጢጢ ህጻን የጋዛ ነዋሪ ናት። እና አይደለም ምግብ የፖሊዮ ክትባት እንኳን እንዳይገባ በከለከለው የእስራኤል ማእቀብ ምክንያት፣ የምግብ እጥረት ተከስቶ ርቧት ነበር ።
.....
እርቧት ስታለቅስ ቆይታ ይህን ምግብ ከማግኘቷ አንድ አለም አቀፍ ጋዜጠኛ የዚህች ምስኪን ህጻን ነገር አሳዝኗት ልታቅፋት ተጠጋቻት ።
........
ጋዜጠኛዋ አይን ላይ እንባ ነበር ። እና ይህን ያየችው ህጻን ልክ እንደ እሷ፡ ርቧት የምታለቅስ ለመሰለቻት፣ ጋዜጠኛ ምግብ ለመስጠት እጇን ዘረጋች ❤️
Share @ethio_tksa_tks
ሰውየው ከስሩ እባብ እንዳለ አያውቅም።
ሴትየዋ ሰውየውን የሚጨፈልቅ ድንጋይ እንዳለ አታውቅም።
ሴትየዋ እንዲህ ታስባለች፦ “ልወድቅ ነው! እባቡ ሊነድፈኝ ስለሆነ መውጣት አልችልም! ሰውየው ትንሽ ተጨማሪ ጉልበት ተጠቅሞ ለምን ወደ ላይ አይጎትተኝም!”
ሰውየው እንዲህ ያስባል፦ “በጣም እየተሰቃየሁ ነው! ግን አሁንም በምችለው መጠን እየጎተትኩሽ ነው! አንቺስ ትንሽ አጥብቀሽ ለመውጣት ለምን አትሞክሪም!?”
ሞራሉ ወይም ትምህርቱ—ሌላው ሰው ምን ዓይነት ጫና ውስጥ እንዳለ ማየት አትችልም፣ ሌላው ሰው ደግሞ አንተ ውስጥ ያለውን ህመም ማየት አይችልም።
ይህ ህይወት ነው፣ በስራ፣ በቤተሰብ፣ በስሜት ወይም በጓደኞች መካከል ቢሆን፣ እርስ በርስ ለመረዳዳት መሞከር አለብን። በተለየ መንገድ፣ ምናልባትም በግልጽ እና በተሻለ ሁኔታ ማሰብን ተማሩ። ትንሽ ማሰብ እና ትዕግስት ትልቅ ለውጥ ያመጣል።
@ethio_tksa_tks
አምልጥ፦
👉 ወደ ጥል ከሚያመራ ወሬ
👉 አቅደው ከሚያሳንሱህ ሰዎች
👉 ዋጋህ ከማይገባቸው ወዳጆች
ተው፦
👉 ሁሉንም ላስደስት ማለትህን
👉 መስዬ ልኑር ባይነትን
👉 አልችልም ማሰብን
ቻልበት፦
👉 ፈጣሪ ፈርቶ መኖርን
👉 ራስን ተቀብሎ
ለራስና የሚወዱት መኖርን
@ethio_tksa_tks
#ስብሃት ጫት ሲቅም የደረሰ አንድ ወጣት ነው አሉ “ይመክረዋል። ጋሽ ስብሃት አይቃሙ።መቃም ሱስ ያሲዛል።
#እኔ አልቅምም!
ስብሃት ዝም ይልና ሲጋራ ይለኩሳል።ወጣቱ ምክሩን
ይቀጥላል። 'ጋሽ ስብሃት አያጭሱ። ማጨስ ሡስ ያሲዛል።
እኔ አላጨስም!
ስብሃት ዝም ይልና ቡና ያዝዛል። "ትጠጣለህ?"
ወጣቱን ሊጋብዝ፡
"ቡና አልጠጣም ሱስ ያሲዛል!
ስብሃት ዝም ይለዋል። በመጨረሻ ሁሉም አልቆ መጠጣት ሲጀመር ወጣቱ "መጠጥ ሱስ ያሲዛል አይጠጡ። እኔ ሱስ እንዳዪዘኝ አልጠጣም' ሲለው
ስብሃት ገረፍ አድርጎ አይቶት "ከሱስ አላመለጥክም፤ሱስ የመፍራት ሱስ አለብህ” አለው፡፡
እኛም ምናልባት ሱስ የለብንም ብለን ሳናውቀው ሱስ የሆነብን ነገር አለ
share @ethio_tksa_tks
የሆስፒታል አልጋ ላይ አይደለህም!
እስር ቤት ውስጥ አይደለህም!
ከመሬት በታች አይደለህም!
እስኪ ለ1 ደቂቃ ፈጣሪህን አመስግን!!
@ethio_tksa_tks
አይገርምም የሆነ ግዜ እንቅልፋችንን ሰውተን ስናወራቸው የነበሩ ሰዎች አሁን ግን እነሱን ላለማየት በግዜ መተኛታችን ምክንያት ናቸው የሆነ ጊዜ በጣም ሰው የማመናችን ምክንያቶች አሁን እራሳችንን መውደዳችን ምክንያቶች ናቸው በጣም ልናያቸው የምንፈልጋቸው ሰዎች አሁን እነሱን አያሳየን ብለን የምንፀልይላቸው ሰው ሆነዋል💔
@ethio_tksa_tks
"አስራ አምስት ብር አለህ "??
አለኝ የሰፈራችን ቀፋይ ከ2ቀናት በፊት
"ለምንህ ነው"?አልኩት የሁልጊዜ ሰበቡ ስለሚያስቀኝ
"ባክህ እራሴን ላጠፋ ፈልጌ አሪፍ ገመድ መግዛት ፈልጌ ነው "አለኝ እየሳቀ
ከኪሴ ድፍን 50ብር አውጥቸ እየሰጠሁት"ከሚል ሱቅ አሪፍ ሲባጎ አለልህ 2ሜትሩን በ10ብር ይሸጥልሀል "አልኩት
"ታድያ ለምን 50ብር ለምን ትሰጠኛለህ"?አለኝ ግራ በመጋባት
"በ 20ሲጋራ ግዛበት በ10መናዘዣ ወረቀትና እስክርቢቶ .."ብየው ላልፍ ስል
"የቀረውን 10ብር ምን ላርጋት"?ሲለኝ
"ባክህ ወንድ ልጅ ባዶ ኪሱን አይሞትም።"አልኩት ኮስተር ብየ።
ከስአት ቡሀላ ቀፋየ እራሱን ማጥፋቱን ሰማሁ ።ዛሬ በሰልስቱ ድንኳን ውስጥ ካርታ እየተጫወትኩ ሳስበው የገረመኝ ነገር በኑዛዜው ማብቂያ አካባቢ ሞቱን ስፖንሰር ስላደረግኩ ማመስገኑ ነበር።
ስቀልድ ነው ከምትለዋ ቃል ጀርባ እውነት አለ
የስንቱ ህመም በፈገግታ ሽፋን ስር ሰዶ ይሆን?
እኛስ የስንቱ ሞት ስፖንሰር ሁነን ይሆን?
የስንቱ ቤት ሳናስተውል በወረወርነው ጠጠር ንደን ይሆን ?
ስንቱን ቀለድን ብለን በወረወርናቸው ቃላት ልቡን ሰብረን ይሆን??
አንዳንዴ አጠገባችን ያሉ ስወች ስለሳቁ ብቻ ደስተኛ ናቸው ብለን እናስባለን ህመማቸውን እየነገሩን እንኳን እየቀለዱ ነው ሚመስለን አንዴ እንኳን ቆም ብለን ደህንነታቸውን ብንጠይቅኮ ብዙ የተደበቀ ህመም ያልታየ ስብራት ይኖራል።
ጓደኝነታችን አብሮ ከመዝናናት ያለፈ ነው ??
ምን ያህል ትተዋወቃላችሁ ??
ከሳቁ ከጨዋታው ትንሽ አረፍ ብላችሁ እስኪ የልብ የልባችሁን አውሩ የሰው መድሀኒቱ ሰው አይደል..
ሰናይ ቀን🙏
ቢያንስ አንድ ሰው ያስተምራል ካላችሁ Share @ethio_tksa_tks
እንዲህ ማን ነው ሚያስደነግጠኝ!!
ኒውዚላንድ ውስጥ ነው ። ኤፕሪል አንድ ቀን ፡ በሀገሪቱ ተነባቢ የሆነ አንድ ጋዜጣ እንዲህ የሚል ማስታወቂያ ይዞ ወጣ ።
መኪናዎት ምን አይነት ነው ? አሮጌ መኪና እየነዱ ለመቀየር ግን አቅሞት ስለማይፈቅድ አዝነዋል ? እንግዲያውስ አሮጌ መኪናዎን ይዘው በመምጣት ምንም ያልተነዳ አዲስ ሞዴል BMW መኪና በነጻ ይውሰዱ ። የሚል ማስታወቂያ ነበር ።
እናም ያንን April -1 ( የኤፕሪል ዘ ፉል ቀን) በጋዜጣ የወጣ ማስታወቂያ ሺዎች አነበቡት ። እና ሺዎቹም ፡ ሞኝህን ፈልግ ፡ ማንን መሳቂያ ለማድረግ ነው ብለው ፡ ካምፓኒው ያወጣውን ማስታወቂያ ስቀው አለፉት ።
እና ግን ከብዙ ሺህ ሰወች መሀል አንድ ሴት ፡ በተለየ አይነት መልኩ አሰበች ። ይሄ ነገር እውነት ቢሆንስ ፡ ለምንድነው ሄጄ የማልሞክረው በማለት ማስታወቂያው የወጣበትን ጋዜጣ ይዛ ፡ BMW ካምፓኒ ወደሚገኝበት ቦታ ሄደች ።
ከትልቁ ካምፓኒ እንደደረሰችም ለተቀበለቻት ፀሀፊ ሚስተር ቶምን ፈልጌ ነው አለቻት ፡ ሰውየው መጣ ፡ ሰላምታ ካቀረበላት በኋላም ምን ልርዳሽ አላት .....
" በነጻ መኪና ይሰጣል የሚል ማስታወቂያ አይቼ ነው "
ሰውየው ልክ ይህን ሲሰማ ፡ ልብ በሚያሞቅ መልኩ ፈገግ እያለ Ok መኪናሽ ምን አይነት ነው ሲል ጠየቃት
" አሮጌ ሞዴል ኒሳን " ስትል መለሰች
በጣም ጥሩ በይ የአሮጌ መኪናሽን ቁልፍ ስጭን ፡ አንቺ ደግሞ ይህን የአዲስ ሞዴል BMW ቁልፍ ተረከቢ ብሎ ፡ ከፊት ለፊት ሸራ ለብሳ የተሸፈነችውን BMW መኪና ቁልፍ ሰጣት ።
ሺዎች ባሰቡበት መንገድ ሳይሆን ፡ በተለየ መንገድ አሰበች ። የተለየ ሽልማት ጠበቃት ።
በተለየ መንገድ አስብ !
«ድንጋይ ከሆንክ ተገንባ »
«ዛፍ ከሆንክ ፍሬ ስጥ »
ሰው ከሆንክ አስብ !
©ደራሲ እና ሐያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ
በአንድ ወቅት አንድ ቀልጣፋ እንጨት ቆራጭ በአንድ የስራ መስክ በጥሩ ደሞዝ ተቀጠረ።ስለዚህም እንጨት ቆራጩ የሚችለውን ሁሉ ለማድረግ እና ጥሩ ስራ ለመስራት ይወስናል።
በመጀመሪያው ቀን ሃላፊው መፍለጫ ሰጠውና የሚሰራበትን ቦታ አሳየው። መቁረጥ የሚችላቸው ዛፎች እነዚህ እንደሆኑ አስረድቶት ሄደ።በርግጥም እንጨት ቆራጩ በመጀመሪያው ቀን 15 ዛፎችን ቆርጦ ማስተካከል ቻለ።
በሁለተኛው ቀን የበለጠ ለመስራት ወስኖ ቢሞክርም ከ10ዛፍ በላይ መቁረጥ አልቻለም ነበር።
በሶስተኛው ቀን ከሁለቱ ቀናት የበለጠ ቢተጋም ከ7 ዛፍ በላይ መቁረጥ አልቻለም።
ቀናቶች ባለፋ ቁርጥ የሚቆርጣቸው ዛፎች መጠን እያነስ እያነስ መሄድ ጀመረ። በስተመጨረሻም አንዲትን ዛፍ መቁረጥ ከበደው። ሞከረ ሞከረ ሊሳካለት አልቻለም።
ይሄኔ ሃይሉን እንዳጣ ተሰማው። ጉልበቴም ከዳኝ ብሎ በማሰብ ላይ ሳለ የሆነ ሌላ ሰው ሲያልፍ ይህንን ሰው አንዲትን ዛፍ ያለጥቅም ሲደበድብ ይመለከተዋል።
"ሰውየው ወደ እንጨት ቆራጩ ጠጋ አለና አንድ ምክር ልምከርህ ትፈቅድልኛለህ?" አለው።
እንጨት ቆራጩም "አሁን ስራ ላይ ስለሆንኩ ምንም መስማት አልፈልግም" ይለዋል።
ሰውየውም እንዲህ አለው" እየፈለጥክበት ያለከው ፋስ(መፍለጫ) ስለት የለውም ዶምድሟል። ከጥቅም ውጭም ሆኗል። ይህን አውቀህ እረፍት በማድረግ የምትሰራበትን #ፋስ ልታስለው ይገባል" አለው።
ይሄኔ ይህ እንጨት ቆራጭ ቆም ብሎ አሰበ። እንዲህም አለ"እውነትም ፋሴን አሞረድኩትም። ዛፎችን በመቁረጥ ቢዚ ስለነበርኩ" ብሎ ፋሱን በእርጋታ ሞረደና ከድሮ በተሻለ መልኩ ስራውን በአግባቡ ማከናወን ቀጠለ።
በህይወትህ ውስጥ መለወጥ ያለብህን ነገር ለመለወጥ ግዜ አትስጥ። ሁሉንም ነገር በጊዜ ለማከናወን ሞክር።
@ethio_tksa_tks
እናትህን እያት!
ፊቷ ላይ ያለ እያንዳንዱ ጥቁረት ላንተ የተከፈለ ነው!
የመሸነፍ መብት የለህም!
የማቋረጥ መብት የለህም!
አኩራት!
አንድ ቀን " ይህን ሁሉ ያደረግኩት ላንቺ ነው!"
ትላታለህ!
ድካሟን በከንቱ አታስቀረው!
ተነስ! ተፋለም! አሸንፍ!
በቅንነት Share በማድረግ ይተባበሩን
@ethio_tksa_tks
አንድ ድሀ ሰውዬ እድሜ ልኩን ለፍቶ ያጠራቀመውን ሁሉ አፍስሶ ለብዙ አመታት ቤት ሲሰራ ይቆይና ያጠናቅቀዋል።
ሆኖም ግን በቀጣዩ ቀን ቤተሰቦቹን ይዞ ሊገባው ሲዘጋጅ ቤቱ ተደርምሶ ወድሞ ያድራል።
በነጋታው ጠዋት የአካባቢው ሰዎች በቦታው ተሰባስበው የሰውየውን የብዙ አመት ልፋትና በቤቱ ውስጥ ለመኖር የነበረውን ጉጉት ስለሚያውቁ እያዘኑ አንዳንዶች ሲያየው እጅግ በጣም ያዝናል! ሌሎች ደግሞ አይ ራሱን ያጠፋል! ሲባባሉ ድሀው ሰውዬ ደረሰ።
ሰውዬው ከፍርስራሹ ፊት በርከክ አለና ድምፁን ከፍ አድርጎ "ጌታ ሆይ ዛሬ እንዲወድም ስላደረግከው አመሰግንሀለሁ! በእጅጉ እንደምትወደኝም አረጋግጫለሁ!" እያለ በደስታ ማመስገን ጀመረ።
ያዝናል ወይም ራሱን ያጠፋል ብለው ሲጨነቁ በደስታ ተሞልቶ ሲያመሰግን ያዩት የአካባቢው ሰዎችም "ለምንድን ነው በደስታ ተሞልተህ የምታመሰግነው? የወደመው እኮ ከልጅነት እስከሽምግልና ያጠራቀምከውን ገንዘብ፣ ብዙ ጉልበትና ጊዜ አፍስሰህ የሰራኸው ቤትህ ነው?" ብለው ጠየቁት።
ሰውዬውም በደስታ እንደተሞላ እንዲህ አላቸው፦
"አያችሁ ወገኖቸ! አስባችሁታል ይህ ውድመት ነገ ማታ ከገባንበት በኃላ ቢከሰት ኖሮ ምን እንደሚፈጠር?
እኔም፣ ልጆቸም፣ ባለቤቴም፣ የቤት ዕቃየም፣ የቤት እንስሳቶቸም ይህኔ አንኖርም ነበር እኮ!" አላቸው። ያኔ የደስታው ምክንያት ሲገለጥላቸው እነሱም በሰውየው አስተዋይነት ተደንቀው አብረው ፈጣሪን አመሰገኑ ይባላል።
ባጣነው ነገር ከማልቀስ ይልቅ በአተረፍነው ነገር መደሰት ይሻላል። በጎውን ነገር ስለማናስተለው ነው እንጅ ሁሉም ነገር የሚሆነው ለበጎ ነው! አስተዋይ አእምሮ ይስጠን 🙏።
SHARE @ethio_tksa_tks