ethiotube | Unsorted

Telegram-канал ethiotube - EthioTube

-

ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ። Follow us on other platforms: Facebook.com/EthioTube Twitter.com/EthioTube Youtube.com/EthioTube Instagram.com/EthioTube

Subscribe to a channel

EthioTube

የሱዳን የሲቪሎች ጥምረት የበላይ እና የፈጥኖ ደራሹ ኃይል አለቃ በአዲስ አበባ ይገናኛሉ።

አገሪቱ በጦርነት መናጥ ከጀመረች በኋላ መላ ለማፈላለግ ከተወሰዱት እርምጃዎች አንዱ የሆነው የሲቪሎች ጥምረት በቀድሞው የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ ይመራል። በሐምዶክ እና ከሁለቱ ተፋላሚ ኃይሎች አንደኛው የሆነው የፈጥኖ ደራሹን ኃይል በሚመሩት ጄነራል ዳጋሎ መካከል የሚደረገው ስብሰባ መቀመጫ እንድትሆን አዲስ አበባ ተመርጣለች።

በጄኔራሉ እና በተፎካካሪዎች የሱዳን ጦር መሪ ጄኔራል አል ቡርሃን መካከል ከሰሞኑ በጅቡቲ ውይይት ይደረጋል ተብሎ የነበረ ሲሆን የጅቡቲ ባለስልጣናት የሁለቱ መሪዎች ግንኙነት መራዘሙን ባለፈው ሳምንት ይፋ አድርገዋል። ይሄንን ተከትሎም ሃሜቲ በሚል ቅፅል ስማቸውም የሚጠሩት ጄኔራል ዳጋል በምስራቅ አፍሪካ ባሉ የተለያዩ አገራት እየተዘዋወሩ የአካባቢውን ፖለቲከኞች ማግኘት ላይ አተኩረዋል።

ወደካምፓላ አቅንተው የአገሪቱን መሪ ዩዌሪ ሙሴቪኒን ካገኙ በኋላ ወደኢትዮጵያ በመምጣት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ተገናኝተዋል። ከዚያም ወደጅቡቲ አምርተው ኢስማዔል ኦማር ጌሌ ጋር መክረዋል። አሁን ደግሞ ወደአዲስ አበባ ተመልሰው ከስልጣናቸው ከፈነቀሏቸው ሃምዶክ ጋር የሚወያዩ ይሆናል። ሃምዶክ የሱዳን ሕዝባዊ ተቃውሞ የአገሪቱ የረጅም ዘመን መሪ ኦማር አልበሽርን ከስልጣን ከገረሰሰ በኋላ የተቋቋመው የሲቪል መንግስት ጠቅላይ ሚኒስትር ነበሩ። ይሁንና አሁን በጠላትነት ጦር የተማዘዙት ጀኔራሎች ተባብረው ከስልጣን ካባረሯቸው በኋላ አገሪቷን ለሁለት ማስተዳደር ጀምረው ነበር። ባለፈው ዓመት አጋማሽ ገደማ ግን ጄኔራሎች አገሪቷ መከተል አለባት ብለው በሚያስቡት አቅጣጫ የተነሳ አልስማማ ብለው አገራቸውን ወደጦርነት እሳት ከትተዋል። ጄኔራል አል ቡርሃን የሱዳን የነፃነት ቀን ምክንያት በማድረግ ባስተላለፉት መልዕክት ተቀናቃኛቸውን ጄኔራል ዳጋሎን እያስተናገዱ ያሉ የምስራቅ አፍሪካ አገራትን በአገራችን ጉዳይ ጣልቃ እየገቡ ነው ሲሉ ወርፈዋቸዋል።

ለወትሮውም ከአል ቡርሃን ጋር ጥሩ ግንኙነት የላትም የምትባለው ኢትዮጵያ ታዲያ ዳጋሎን ከሳምንት ባልበለጠ ጊዜ ለሁለተኛ ጊዜ አስተናግዳቸዋለች። በሃምዶክ እና በሃሜቲ መካከል የሚደረገው ውይይት ሰላማዊ ዜጎችን ከጥቃት በመጠበቅ፥ የሰብዐዊ እርዳታ በአግባቡ እንዲሰራጭ በማስቻል እንዲሁም ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ የሚፈታበትን መንገድ በማፈላለግ ላይ እንደሚያተኩር የሲቪል ጥምረቱ ገልጿል። በሱዳን ጦርነት በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ከሰባት ሚሊዮን የሚበልጡት ደግሞ ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። ይሄንንም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት “የዓለማችን ትልቄ የመፈናቀል ቀውስ” ሲል ጠርቶታል።

Читать полностью…

EthioTube

በቤንሻንጉል-ጉሙዝ ታጣቂዎች ሰው ገድለው ሁለት ባንኮችን ዘረፉ።

ዘረፋው የተፈፀመባቸው የአዋሽ እና የንግድ ባንኮች ሲሆኑ ፖሊስ ጣብያም መቃጠሉ ነው የተዘገበው ፡፡ ጥቃት አድራሾቹ በክልሉ ምዥጋ ወረዳ ሰርገው በመግባት ጥቃት የሰነዘሩ ሲሆን ሶጌ በምትባል በወረዳው በምትገኝ ከተማ በደረሰው ጥቃት ቢያንስ የሦስት ሰዎች ህይወት ማለፉን የአካባቢው አስተዳደር ገልጿል።

የጀርመን ድምፅ ሬዲዮ የወረዳው ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ ለጥቃቱ መንግስት ሸኔ ሲል የሚጠራውን በአብዛኛው በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀስ ታጣቂ ቡድን ተጠያቂ አድርገዋል ብሏል። ራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት የሚለው ይሄው ቡድን ግን በጉዳይ ላይ እስካሁን ያለው ነገር ስለመኖሩ አልተዘገበም። በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኛነት የተፈረጀው ይሄው ቡድን ከመንግስት ጋር በሁለት ዙሮች ያደርገው ድርድር ሳይሳካ መበተኑ ይታወሳል። ይሄንን ተከትሎም በተለይ በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ግጭቶች ተፋፍመዋል፤ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችም ዳግም አንሰራርተዋል።

ጥቃት ባስተናገደችው የቤንሻንጉል-ጉምዝ ከተማ አካባቢ ይገኙ የነበሩ የፀጥታ ኃይሎች ለግዳጅ ወደሌላ ስፍራ መንቀሳቀሳቸውን ተክተሎ ታጣቂዎቹ ለመግባት ብዙም አልከበዳቸውን የተባለ ሲሆን ለሰዐታትም በከተማዋ ሲንቀሳቀሱ ነበር ተብሏል። ከባንክ ዝርፊያ በተጨማሪም የፖሊስ ጣብያ እና በርካታ ተሽከርካሪዎች መቃጠላቸውም አብሮ ተዘግቧል።

ታጣቂዎቹ ወደከተማዋ አርብ ዕለት ከገቡ በኋላ ብዙ ተኩስ በመኖሩ ሰላማዊ ነዋሪዎች ለሽሽት ተዳርገው የነበረ ሲሆን በማግስቱ ግን መረጋጋት መመለሱንና ይሄንንም ተከትሎ ነዋሪዎች መመለሳቸውን ዘገባው አመላክቷል።

መንግስት በተዳጋጋሚ በቤንሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጋር የሰላም ስምምነት አድርጌ አንፃራዊ መረጋጋት ተመልሷል ሲል ይደመጣል፤ ይሁንና መሰል ጥቃቶች አልፎ አልፎ መሰማታቸው አልቀረም።

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያ፦ የእለተ አርብ ኢትዮትዩብ አንኳር አጫጭር ዜናዎች - ታህሳስ 19 ፣ 2016 | #Ethiopia: EthioTube Ankuar : አንኳር - Ethiopian Daily News Digest - December 29 , 2023

👉 የመብቶች ተሟጋቹ ኢሰመጉ በታጣቂዎች ለሚደርሱ ጥቃቶች መንግስት ተገቢ ትኩረት እየሰጠ አይደለም ሲል ከሰሰ።

👉 የሽግግር ፍትሕ ሂደት የጥቃት ሰለባዎችን ያማከለ መሆን አለበት ተባለ።

ሌሎችንም መረጃዎች ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ 👇

https://youtu.be/7DRPCvX1imI

Читать полностью…

EthioTube

የመብቶች ተሟጋቹ ኢሰመጉ በታጣቂዎች ለሚደርሱ ጥቃቶች መንግስት ተገቢ ትኩረት እየሰጠ አይደለም ሲል ከሰሰ።

በኦሮሚያ ክልል አርሲ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች ተከስተዋል የተባሉ ጥቃቶችን አስመልክቶ መግለጫ ያወጣው የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ጥቃቶች ከግድያ እና ከአካል ጉዳት በተጨማሪ የንብረት ውድመትን፣ መፈናቀልን እንዲሁም ሌሎች “መጠነ ሰፊ የሆኑ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን” እያስከተሉ ነው ሲል ገልጿል።

ከተቋቋመበት 1984 ዓ.ም አንስቶ ኢሰመጉ ለ154ኛ ጊዜ ባወጣው በዚሁ መገለጫ በተለይ ማንነት ላይ ያነጠጠሩ ጥቃቶች ከሚደርሱባቸው ክልሎች አንዱ ኦሮሚያ ነው ብሏል። ለሚደርሱ ጥቃቶችም ዘላቂ መፍትሔ መሰጠት አልሰተቻለም፤ እንዲሁም መንግስት የዜጎችን ደህንነት በተገቢው ሁኔታ ማስጠበቅ ብሎም ሰብዓዊ መብቶቻቸውን ማስከበር አልቻለም ሲል ኢሰመጉ ይወነጅላል።

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን ሽርካ ወረዳ በተለይም ጢጆ ለቡ፥ ሔላ ጢጆ ሴሮ እና በሮቤ እንደቶ ወደተባሉ ቀበሌዎች ባለሞያዎቼን አሰማርቼ ነበር የሚለው ኢሰመጉ በዚህም በወርሃ ሕዳር ሁለተኛ አጋማሽ የተከሰቱ የመብት ጥሰቶችን መርምሬያለሁ ብሏል በመገለጫው።

ይሁን እንጅ በቄለም ወለጋ ዞን ጊዳሜ ወረዳ ማልኢኩ መንደር በሕዳር አጋማሽ የተከሰተ በወንጌላዊት ቤተ ክርስትያን ላይ ደርሷል የተባለን ጥቃት ለመመርመር ፈልጌ በፀጥታ ችግር ምክንያት ወደስፍራው ማቅናት ሳልችል ቀርቻለሁ ብሏል።

በአርሲ ዞን በደረሱት ጥቃቶች 53 ሰዎች ተገድለው የነበረ ሲሆን ሁለት ደግሞ ቆስለዋል ሲል ኢሰመጉ በምርመራው ደርሼበታለሁ ያለውን አስፍሯል። በጥቃት ህይወታቸውን ያለፈውን ሰዎች ስም እና ዕድሜ ዘርዝሮ አቅርቧል። ሪፖርቱን በፎቶዎችም ደግፏል። ከሟቾች እና ከቁስለኞች በተጨማሪ በርካታ ቤቶች ተቃጥለዋል ሲል አክሏል። ጥቃቶቹን በተመለከተ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብት ኮሚሽን፥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን እንዲሁም ልዩ ልዩ የብዙሃን መገናኛዎች መዘገባቸው ይታወሳል።

በወቅቱ መንግስት ራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት በሚል የሚጠራውን ታጣቂ ቡድን ወንጅሎ ነበር። መንግስት ሸኔ በሚል ስም የሚጠራው ታጣቂ ቡድን በአገሪቱ ፓርላማ ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀ ሲሆን ውንጀላውን አጣጥሎ ነበር።
ኢሰመጉ በቄለም ወለጋ ቤተ ክርስትያን ላይ በደረሰው ጥቃት ህይወታቸው አልፏል ያላቸውን ዘጠኝ ስም ዘርዝሮ አቅርቧል።
የመብት ተሟጋቹ ከዚህም በዘለለ በኦሮሚያ ክልል አውራ ጎዳናዎች ላይ እና በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች እገታ እየተለመደ የመጣ የመብት ጥሰት ነው ያለ ሲሆን ይህንን አስመልክቶ በተደጋጋሚ ማሳሰቢያ ባሰማም መንግስት ለእዚህ ድርጊት ተገቢው ትኩረት እና ህጋዊ ዘላቂ መፍትሄ አልሰጠም፤ ይሄንን ተከትሎም ድርጊቱ በተጠናከረ መልኩ እየቀጠለ መገኘቱ የሚያሳስበው መሆኑን መግለጽ ይወዳል።

የኢሰመጉ መግለጫ ለክልሉ እና ለፌዴራል መንግስት ደህንነት ማስጠበቅ መብት እንዲያሰክብሩ፥ ጥቃት ያደረሱ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል። የመብት ጥሰት የተፈፀመባቸው አካላት ከፍትህም ባሻገር ካሳም ይሻሉ ሲል ጨምሮ ተናግሯል።

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያ፦ የእለተ ሀሙስ ኢትዮትዩብ አንኳር አጫጭር ዜናዎች - ታህሳስ 18 ፣ 2016 | #Ethiopia: EthioTube Ankuar : አንኳር - Ethiopian Daily News Digest - December 28 , 2023

👉 የምዕራብ አገራት ኤምባሲዎች በዲፕሎማቶች ላይ የደረሰው ጥቃት አሳስቦናል አሉ።

👉 በሰሜን ኢትዮጵያ የቀደሙ ዘመናትን የሚያስታውስ ረሃብ ሊከሰት ይችላል ተባለ።

ሌሎችንም መረጃዎች ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ 👇

https://youtu.be/PLoluTYYFi0

Читать полностью…

EthioTube

ኤርትራዊያን ስደተኞች በዘፈቀደ እየታሰሩ ነው ተባለ።

የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች በፀጥታ ኃይሎች ያለአግባብ እየተያዙ ሲሆን ባለፉት ሦስት ዓመታት በአዲስ አበባ የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች ምዝገባ ያለመካሄዱ ለችግሩ አስተዋፅዖ አድርጓል ብለዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ ዘገባ የሠሩት የዓለም አቀፍ የብዙሃን መገናኛዎች ያነጋገሯቸው በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ኤርትራዊ ስደተኞች በፀጥታ ኃይሎች በዘፈቀደ የመያዝ ስጋት እንዳለባቸውና አንዳንድ ጊዜም በፖሊሶች ታስረው ከአጭር ጊዜ በኋላ እንደሚለቀቁ ተናግረዋል።

ኢሰመኮ የስደተኞች ምዝገባ በአስቸኳይ እንዲጀመር ማሳሳቢያ ያቀረበ ሲሆን የስደተኞች ጥበቃ አደጋ ውስጥ ገብተዋል ሲል ተናግሯል።

ኢትዮጵያ ለዓመታት ያህል በግዛቷ ለውጭ አገር ስደተኞች እና ጥገኝነት ፈላጊዎች አስተማማኝ ከለላ መስጠቷ የኩራት ምንጭ ሆኖላት ቆይቷል። ከጎረቤቶቿ በተለይም ከኤርትራ፥ ከሶማሊያ እና ከደቡብ ሱዳን የሚመጡ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ስደተኞችን በልዩ ልዩ ካምፖች የምታስተናግድ ሲሆን ከስደተኞች መካከል የተወሰኑት ከካምፕ ውጭ ሆነው ከማኅበረሰብ ጋር በመቀላቀል እንዲኖሩ የሚያስችል አሰራር አላት። ከዚህ አሠራር ጋርም በተያያዘ ከፍ ያለ ቁጥር ያላቸው ኤርትራዊያን በልዩ በልዩ ከተሞቸ በተለይም በአዲስ አበባ እንደሚገኙ ይነገራል።

ይሁንና በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት የስደተኞች ደህንነት ላይ ስጋትን ጥሎ ቆይቷል። በትግራይ ክልል ውስጥ የነበሩ የኤርትራ ስደተኞች መቆያ ጣብያዎች ወደጎረቤት አማራ ለመዛወር የተገደዱባቸው አጋጣሚዎች ሲኖሩ ስደተኞች ለተወሰነ ጊዜ እርዳታ ተቋርጦባቸውም ቆይቷል።

ከዚህም ባለፈ የአስመራን መንግስት ወይንም አስገዳጅ የብሔራዊ ውትድርናን ሸሽተው ኢትዮጵያ ከሚገኙ ስደተኞች መካከል የተወሰኑትን ተይዘው ወደኤርትራ መመለሳቸውም ተዘግቧል።

መቀመጫውን በፈርንሳይ መዲና ፓሪስ ያደረገው እና በኤርትራ መንግስት ላይ የቅዋሜ ድምፅ የሚያሰማው ሬዲዮ ኤረና በአዲስ አበባ የፀጥታ ኃይሎች በህጋዊ መልኩ ወደአገሪቱ የገቡ ኤርትራዊያንን ጭምር እያሰሩ ነው ሲል ይወነጅላል። በጉዳዩ ላይ ከመንግስት ወገን የተሰማ አስተያየት ግን እስከ አሁን የለም።

Читать полностью…

EthioTube

በሰሜን ኢትዮጵያ የቀደሙ ዘመናትን የሚያስታውስ ረሃብ ሊከሰት ይችላል ተባለ።

መንግስት በበኩሉ ድርቅ ቢከሰትም ረሃብ የለም ይላል፤ ረሃብ እንዳለ የሚናገሩት ሌላ ዓላማ ያላቸው ወገኖች ነው ሲልም ይከሳል።

በጦርነት ደቅቃ ድርቅ የተደረበባት ትግራይ ክልል በመጓዝ ዘርዘር ያለ ዘገባ የሠራው የካናዳው ስመ ጥር ግሎብ ኤንድ ሜይል ጋዜጣ የረድዔት ድርጅት ሠራተኞችን በመጥቀስ ኢትዮጵያን መጥፎ ስም ያሰጧትን ከአስርት ዓመታት በፊት የተከሰቱትን የሚገዳደር ረሃብ አንዣብቧል ሲል አስጠንቅቋል።

አውዳሚው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በሰላም ስምምነት ተቋጭቶ ቢያንስ በትግራይ ክልል የተኩስ ድምፅ መሰማት ያበቃ በመሰለባቸው አስራ አራት ወራት በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በምግብ እጥረት ህይወታቸው አልፏል ጋዜጣው እንደሚለው።

የጭላ በምትባለው ብዙ እርዳታ ጠባቂዎች በተሰባሰቡባት ትንሽ ከተማ በየዕለቱ ምንዱባን የተራድዖ እህል ማከማቻ መጋዘን አጠገብ ይሰባሰባሉ ሲል ያየውን የዘገበው ጋዜጣው አንዳንዶች ደግሞ ከአካባቢው መስተዳደር ፅህፈት ቤት በር ውጭ ይከማቻሉ፤ አንዳንዶቹ እንዲያውም አንዳች ነገር ጠብ ቢል በሚል እዚያው ያድራሉ ሲል አስነብቧል።

በ1977 ገደማ በኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረው ረሃብ ክፉኛ ጡጫውን ካሳረፈባቸው የአገሪቷ አካባቢዎች መካከል አንደኛዋ ትግራይ እንደነበረች ያስታወሰው ዘገባው አሁን ያንዣበበው መዐት ከዚያም ሊከፋ ይችላል ብሏል። በጦርነት ምክንያት የክልሉ ሰብል ማምረቻዎች፥ የጤና ማዕከላት እና የመንግስት ፅህፈት ቤቶች ወድመዋል ወይንም ተዘርፈዋል ያለው ጋዜጣው መልሶ የመገንባት ጥረት ብዙም አይስተዋል ብሏል። ረሃብን በማስመልከት ቅድመ ማስጠንቀቂያ የሚሰጠው ዘ ፋሚን ኧርሊ ዋርኒንግ ሲስተምስ ኔትዎርክ የተባለው የምርምር ተቋም ከጥቂት ቀናት በኋላ በሚጀመረው የፈረንጆች 2024 የመጀመሪያ ወራት ረሃብ በትግራይ በሰፊው ሊሰራጭ ይችላል ይላል። የክልሉ ባለስልጣናት 3.5 ሚሊዮን ገደማ ሰዎች አስቸኳይ እርዳታ ያሻቸዋል የሚሉ ሲሆን ከመካለላቸውም የሚበዙቱ አርሶ አደሮች ናቸው።

የክልሉ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር ከ77ቱም የሚከሰት ረሃብ እየመጣ ነው ሲሉ ለጋዜጣው ነግረውታል፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርዳታ ማስተባበሪያ ፅሕፈት ቤትም የቀድሞ ኃላፊም መረጃዎች በሙሉ የሚጠቁሙት ከአርባ ዓመታት ገደማ በፊት የተከሰተውን መዐት የሚገዳደር ቸነፈር እየመጣ መሆኑን ነው ይላሉ።

አንዲት ሴት ለጋዜጣው ዘጋቢ በአዝጋሚ ሞት ውስጥ ነው ያለነው ሲሉ ነግረውታል። ድርቁ እና የምግብ እጥረት በአጎራባች የአማራ ክልል ዞኖች እንደተከሰተም ይዘገባል።

የመንግስት የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር ሽፈራው ተክለማርያም ግን በቅርቡ ስለጉዳዩ ሲናገሩ ድርቅ ተከስቶ በርካቶችን ለምግብ እጥረት ቢዳርግም ረሃብ የለም ማለታቸው ይታወሳል። መንግስት ለችግር ለተጋለጡ ዜጎች እርዳታ ለማድረስ ከፍተና ገንዘብ መድቦ እየተንቀሳቀሰ ነው ሲሉም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል። በአንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ችግር እርዳታ ለማድረስ የሚደረግ ጥረትን ማደናቀፉንም ጨምረው ገልፀው ነበር።

ኤርትራዊያን ስደተኞች በዘፈቀደ እየታሰሩ ነው ተባለ። የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች በፀጥታ ኃይሎች ያለአግባብ እየተያዙ ሲሆን ባለፉት ሦስት ዓመታት በአዲስ አበባ የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች ምዝገባ ያለመካሄዱ ለችግሩ አስተዋፅዖ አድርጓል።

በጉዳዩ ላይ ዘገበ የሠሩ የዓለም አቀፍ የብዙሃን መገናኛዎች ያነጋገሯቸው በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ኤርትራዊ ስደተኞች በፀጥታ ኃይሎች በዘፈቀደ የመያዝ ስጋት እንዳለባቸውና አንዳንድ ጊዜም በፖሊሶች ታስረው ከአጭር ጊዜ በኋላ እንደሚለቀቁ ተናግረዋል።

ኢሰመኮ የስደተኞች ምዝገባ በአስቸኳይ እንዲጀመር ማሳሳቢያ ያቀረበ ሲሆን የስደተኞች ጥበቃ አደጋ ውስጥ ገልጿል ሲል ተናግሯል።

ኢትዮጵያ ለዓመታት ያህል በግዛቷ ለውጭ አገር ስደተኞች እና ጥገኝነት ፈላጊዎች አስተማማኝ ከለላ መስጠቷ የኩራት ምንጭ ሆኖላት ቆይቷል። ከጎረቤቶቿ በተለይም ከኤርትራ፥ ከሶማሊያ እና ከደቡብ ሱዳን የሚመጡ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ስደተኞችን በልዩ ልዩ ካምፖች የምታስተናግድ ሲሆን ከስደተኞች መካከል የተወሰኑት ከካምፕ ውጭ ሆነው ከማኅበረሰብ ጋር በመቀላቀል እንዲኖሩ የሚያስችል አሰራር አላት። ከዚህ አሠራር ጋርም በተያያዘ ከፍ ያለ ቁጥር ያላቸው ኤርትራዊያን በልዩ በልዩ ከተሞቸ በተለይም በአዲስ አበባ እንደሚገኙ ይነገራል።

ይሁንና በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት የስደተኞች ደህንነት ላይ ስጋትን ጥሎ ቆይቷል። በትግራይ ክልል ውስጥ የነበሩ የኤርትራ ስደተኞች መቆያ ጣብያዎች ወደጎረቤት አማራ ለመዛወር የተገደዱባቸው አጋጣሚዎች ሲኖሩ ስደተኞች ለተወሰነ ጊዜ እርዳታ ተቋርጦባቸውም ቆይቷል።

ከዚህም ባለፈ የአስመራን መንግስት ወይንም አስገዳጅ የብሔራዊ ውትድርናን ሸሽተው ኢትዮጵያ ከሚገኙ ስደተኞች መካከል የተወሰኑትን ተይዘው ወደኤርትራ መመለሳቸውም ተዘግቧል።

መቀመጫውን በፈርንሳይ መዲና ፓሪስ ያደረገው እና በኤርትራ መንግስት ላይ የቅዋሜ ድምፅ የሚያሰማው ሬዲዮ ኤረና በአዲስ አበባ የፀጥታ ኃይሎች በህጋዊ መልኩ ወደአገሪቱ የገቡ ኤርትራዊያንን ጭምር እያሰሩ ነው ሲል ይወነጅላል። በጉዳዩ ላይ ከመንግስት ወገን የተሰማ አስተያየት የለም።

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያ፦ የእለተ ረቡዕ ኢትዮትዩብ አንኳር አጫጭር ዜናዎች - ታህሳስ 17 ፣ 2016 | #Ethiopia: EthioTube Ankuar : አንኳር - Ethiopian Daily News Digest - December 27 , 2023

👉 ተቃዋሚው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) የመንግስት ኃይሎች እህል በመሰብሰብ ላይ የነበሩ ሰላማዊያንን ገድለዋል አለ።

👉 የዚምባበዌ ፖሊስ አስራ ሦስት ህገ ወጥ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ተደብቀው ባሉበት ቤት ይዣለሁ አለ።

ሌሎችንም መረጃዎች ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ 👇

https://youtu.be/Wnefuvb9t1k

Читать полностью…

EthioTube

የዚምባበዌ ፖሊስ አስራ ሦስት ህገ ወጥ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ተደብቀው ባሉበት ቤት ይዣለሁ አለ።

ኢትዮጵያዊያኑ በህገ ወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች አማካይነት ወደአገሪቷ ያለፈቃድ ሳይገቡ አልቀረም ተብሎ እንደተጠረጠረ የአገሪቱ የብዙሃን መገናኛዎች ዘግበዋል። ወደዚምባቡዌ የገቡትም በዛምቢያ አቋርጠው ነው ተብሏል።

በአንድ መሸሸጊያ ቤት ተጠልለው የነበሩትን ኢትዮጵያውያን የተመለከተ ጥቆማ ከማኅበረሰብ አባላት ደርሶት ፖሊስ እንደተንቀሳቀሰና በስፍራው የፖሊስ አባላት በስፍራው ሲደርሱም ያለጉዞ ሰነድ የተደበቁ ሰዎችን ማግኘታቸውን ዘገባዎች አመላክተዋል።

አስራ ሦስቱም ኢትዮጵያውያን ወንዶች ሲሆኑ በሃያ እና በአርባ የዕድሜ ክልል ውስጥ እንደሚገኙም አብሮ ተጥቅሷል። ሰዎቹ በተያዙባት በአገረቷ ምዕራባዊ ክፍል በምትገኘው ቪክቶሪያ ፎልስ የተባለች ከተማ ህገወጥ ስደተኞችን በማሸጋገር የሚታወቁ አጓጓዦች አሉ ተብሏል። እንደዘገባዎቹ ከሆነ እነዚህ አጓጓዦች መዳረሻቸውን ደቡብ አፍሪካ ያደረጉ ህገ ወጥ ስደተኞችን ማሸጋገር ሥራቸው ነው። ኢትዮጵያውያኑ ፍርድ ቤት ቀርበው ያለፈቃድ ወደአገር ውስጥ በመግባት ወንጀል ክስ እንደሚመሰረትባቸው ይጠበቃል።

በርካታ ኢትዮጵያውያን አያሌ የአፍሪካ አገራትን በማቆራረጥ ደቡብ አፍሪካ ለመድረስ ጥረት እንደሚያደርጉ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህም ጋር በተያያዘ በልዩ ልዩ አገራት የፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር የመዋላቸው ዜና እንግዳ አይደለም።

Читать полностью…

EthioTube

አዲስ በተቋቋመው የማዕክላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ሠራተኞች ደምወዝ በአግባቡ ያለመከፈል ዜጎችን ከችግርም አልፎ ለእስር እያጋለጠ ነው ተባለ።

በዚሁ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአካባቢያዊ ገቢዎችን ማነስ እና ከፌዴራል ተልኮ የሚመጣ በጀት ለማደበሪያ ግዥ መዋሉን የአጥቢያ ሹማምንት በምክንያትነት ያነሳሉ። የደምወዝ ክፍያ ችግር ለጤና እና ትምህርት ተቋማት አገልግሎት መስተጓጎል ምክንያትም ሆኗል ተብሏል።


የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በቅርቡ ባወጣው መግለጫ በተለይ አዲስ በሚዋቀሩ ክልሎች ደምወዝ ያለመከፈል ወይንም ዘለግ ላለ ጊዜ የመዘግየት አጋጣሚዎች አሉ ሲል መግለፁ ይታወሳል።

ኮሚሽኑ ይህ መሰሉ አጋጣሚ ከተስተዋለባቸው ክልሎች መካከል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች ነቅሶ ጠቅሷል። አሁን ደግሞ በተለይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያዋ የሆሳዕና አካባቢ የመንግስት ሠራተኞች ተገቢ ክፍያን ከማግኘትም ባለፈ ለእስር እየተዳረጉ ነው ሲሉ ልዩ ልዩ የብዙሃን መገናኛዎች ዘግበዋል።

በዚሁ አካባቢ የህክምና ባለሞያዎች ከደምወዝ ክፍያ ጋር በተገናኘ የስራ ማቆም አድማዎችን ስለማድረጋቸው መዘገቡ ይታወሳል። በዚሁ የሀድያ ዞን ከፖሊስ፥ ከፍርድ ቤት እንዲሁም ከፍትሕ ተቋማት ሰራተኞች በስተቀር አብዛኞቹ የመንግስት ሠራተኞች ካለፈው ዓመት ነሐሴ አንስቶ ለወራት እንዳልተከፈላቸው በስፍራው ተገኝቼ አረጋግጫለሁ ያለው የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ይሄም ለዘርፈ ብዙ የምጣኔ ኃብታዊ፥ ማኅበራዊ እና ስነ ልቦናዊ ቀውስ ዳርጓቸዋል ብሏል።

ከደምወዝ ክፍያ ጋር በተገናኘ የትምህርት እና የጤና ተቋማት ስራ እያቋረጡ ወይንም ሙሉ በሙሉ ግልጋሎት እያልሰጡ እንደሆነ የተናገረው ኮሚሽኑ ይሄንን ተከትሎም የአካባቢው ማኅበረሰብ መሠረታዊ ግልጋሎት ፍለጋ ወደአካባቢው ለመሄድ ተገድድዋል ሲል አክሏል።

የከተማ እና የወረዳ አስተዳደሮች የችግሩን መኖር አምነውልኛል ይላል የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን። ለዚህም በምክንያነት ከሚያነሱት አንዱ የአካባቢያዊ ገቢዎችን ማነስ ነው። ከፌዴራል መንግስት ተምድቦ የሚመጣ በጀት ለሌላ ስራ የሚውልባቸው ጊዜያትም አለ ተብሏል። ከእነዚህም መካከል የማዳበሪያ ግዥ አንዱ ነው።

የመንግስት ሠራተኞች አንዳንድ ጊዜ ከደምወዟቸው ተቀንሶ እንደሚሰጣቸውም ኮሚሽኑ በሪፖርቱ የጠቀሰ ሲሆን ለቅጥረኛ ሠራተኞች በአግባቡ እና ሙሉ ሙሉ የደምወዝ ክፍያን ያለመፈፀም የመብት ጥሰት ነው ሲል አክሏል። ደምወዝን በመደበኛነት ያለመክፈል የዓለም አቀፉ የሥራ ድርጅት ስምምነት የሚጥስ ከመሆኑም ባሻገር የፌደራል የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ የሚፃረርም ነው ብሏል ኢሰመኮ።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ የመስክ ምልከታ ባደረግኩባቸው ከተሞችና የወረዳ አስተዳደሮች ሁሉ የጤና ጣብያዎች እና የጤና ኬላዎች ሙሉ በሙሉ አገልግለት እየሰጡ ያለመሆኑን አይቻለሁም ብሏል ኢሰመኮ። አንደአብነትም ምስራቅ ባድዋቾ በሚባል ወረዳ አራት ጤና ጣብያዎች እና 22 የጤና ኬላዎች አገልግሎት እየሰጡ አይደለም ሲል ያውን ገልጿል የሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን።

Читать полностью…

EthioTube

Comeback at Old Trafford!

ማንችስተር ዩናይትድ በሜዳው በአስቶን ቪላ በመጀመሪያው አጋማሽ 0 ለ 2 ሲመራ ቆይቶ፥ በሁለተኛው አጋማሸ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር 3 ለ 2 ያሸነፈበት አስገራሚ ጨዋታ በምስሎች።

#ManchesterUnited #AstonVilla #EPL #PremierLeague

Читать полностью…

EthioTube

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በየትኛዉም መልክ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን አትፈቅድም።

ከሰሞኑ የሮማዉ ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ቤተክርስቲያኗ ለተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች ቡራኬ እንዲሰጡ ፈቃድ መስጠታቸዉን የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል። ይህንኑ ተከትሎም የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽ/ቤት በጉዳዩ ላይ መግለጫ አዉጥቷል።

ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ከካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ስርዓተ አምልኮ ጋር የሚጻረር ወይንም ዉዥንብርን ሊፈጥር የሚችል ስርዓተ አምልኮን ያወግዛል ብሏል። ሆኖም የጳጳሱ መልዕክት በተቃራኒው ተወስዷል የሚል ሃሳብ ያለዉን መግለጫ ያወጣ ሲሆን ለተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች ጋብቻን ግን ጳጳሱ ፈቃድ አልሰጡም ብሏል።

አክሎም የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅስን በማስቀመጥ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በየትኛዉም መልክ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን አትፈቅድም ፤ አታጸድቅምም ማለቱን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ከመግለጫው ተመልክቷል።

ቤተክርስቲያኒቱ ሀጢያትን አትባርክም ታወግዛለች እንጂ ያለዉ መግለጫዉ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ የኢትዮጵያ ባህል እና እሴትን የሚጥስ በመሆኑ ተቀባይነት እንደማይኖረዉም በመግለጫው አስታዉቋል።

Читать полностью…

EthioTube

ሚኒስትር ድዔታው አገር ጥለው መኮብለላቸው ተነገረ።

አንደኛው ሚኒስትር ድዔታው ከኃላፊነት የተነሱበት እና ወዲያውም ለእስር የተዳረጉበት ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ አሁን ደግሞ ሌላኛው ድዔታው ጥለውት ከአገር መውጣታቸው ተዘግቧል።

ባለፈው ሳምንት በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሚኒስትር ድዔታ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ታየ ደንደዓ ከስልጣናቸው መነሳታቸውን ገልፀው ሲያገለግሉት የነበረውን መንግስት እንዲሁም የፓርቲያቸውን መሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጠንከር ባሉ ትችቶች ነቅፈው ነበር።

ብዙም ሳይቆይ ግን የፀጥታ ኃይሎች በወንጀል እንደጠሯቸውና ገልፀው በቁጥጥር ስር አውላቸዋል። ታየ ከፀጥታ አደፍራሽ ታጣቂ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አላቸው፥ ከሰዎች መታገት ጋርም ይያያዛሉ ተብለው ነው በፀጥታ ኃይሎች የተጠረጠሩት።

አሁን ደግሞ ሌላኛው የሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ድዔታ ዶክተር ስዩም መስፍን አገር ጥለው መኮብለላቸው ተዘግቧል።

ስዩምም እንደታየ ሁሉ በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻቸው ጠንከር ያለ ትችትን አባል ሆነው ሲያገለግሉት በቆዩት ገዥው ፓርቲ ላይ አዝንበዋል። ፓርቲውን “መንግስታዊ ባህርይን ያልተላበሰ” ነው ያሉት ሲሆን አባላቱን በሴራ ፖለቲካ ተጠምደው የሚራኮቱ ናቸው ብለዋቸዋል። ገዥውን ፓርቲ ከዚህም በዛ ያለውን የአገሪቱን ክፍል በቅጡ እያስተዳደረ አይደለም ያሉት ሲሆን የራሱ አባላት እንኳ እምነት የማይጥሉበት ነው ብለውታል። በግሌ በህዝብ ላይ ያደርስኩት በደል ባይኖርም፥ የመንግስት አካል ሳለሁ በሕዝብ ላይ ለደረሰው በደል ይቅርታ እጠይቃለሁ ብለዋል።

ከስዩም አስተያየት በኋላ ገዥው ፓርቲ በጉዳዩ ላይ ያለው ነገር ስለመኖሩ አልተሰማም።

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያ እዳዋን የመክፈያ ተጨማሪ ቀናቶቿን ሳትከፍል አጠናቀቀች

ኢትዮጵያ የ33 ሚሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ ብድር ወለድ ትናንት በቀነ ገደቡ ሳትከፍል መቅረቷን ብሉምበርግ ዘግቧል።

የወለዱ መክፈያ ዋናው ቀነ ገደብ ያለፈው ከሁለት ሳምንት በፊት ሲሆን፣ ቀነ ገደቡ የ14 ተጨማሪ የእፎይታ ቀናት ነበረው።

መንግሥት የ1 ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ብድር ወለዱን ከሁለት ሳምንት በፊት ያልከፈለው፣ ሁሉንም አበዳሪዎች በእኩል ለማስተናገድ እንደሆነ መግለጡ ይታወሳል።

የወለድ መክፈያው የእፎይታ ጊዜ ትናንት ማብቃቱን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያ የውጭ ዕዳዋን መክፈል ያልቻለች አገር ሆናለች።

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያ፦ የእለተ ሰኞ ኢትዮትዩብ አንኳር አጫጭር ዜናዎች - ታህሳስ 15 ፣ 2016 | #Ethiopia: EthioTube Ankuar : አንኳር - Ethiopian Daily News Digest - December 25 , 2023

👉 የአፍሪካ ልማት ባንክ የውጭ አገር ሰራተኞቹን ጠቅልሎ ከኢትዮጵያ እንዲያስወጣ ካስገደደው ጥቃት ጀርባ ዘርዘር ያሉ መረጃዎች ተሰምተዋል

👉 ተፈናቃዮች ሳንፈልግ ሸሽተነው ወደመጣነው ቦታ ተመለሱ እየተባልን ነው አሉ

👉 ግብፅ በኢትዮጵያ ላይ ዛቻ መሰንዘሯን ቀጥላለች።

ሌሎችንም መረጃዎች ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ 👇

https://youtu.be/lGtNQiDy5SY

Читать полностью…

EthioTube

የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ምዘገባ አላቋረጥኩም ሲል የሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን በኤርትራ ስደተኞች ዙርያ ያወጣውን ሪፖርት ተችቷል።

ከስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች ጋር የሚከወኑ ሥራዎችን የመፈፀም እና የመቆጣጠር ኃላፊነት የተሰጠው አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ትናንትና በተጠናቀቀው የፈረንጆች 2023 በድምሩ ከ140 ሺህ በላይ ስደተኞችን መዝግቤያለሁ ብሏል። ባለቀው የፈረንጆች ዓመት ከ26,500 በላይ አዲስ የተወለዱ የስደተኛ ልጆችም ተመዝግበዋል ሲል አክሏል። ይሄንን ያለው ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በተለይ በአዲስ አበባ የኤርትራ ስደተኞች ምዝገባ መቋረጡ ለተለያዩ የመብት ጥሰቶች አስተዋፅዖ እያደረገ ነው በሚል ላወጣው መግለጫ በሰጠው ምላሽ ነው።

ኢሰመኮ ኤርትራዊያን ስደተኞች በቅርብ ጊዜያት ለዘፈቀደ እስር እና እንግልት እየተጋለጡ ነው ሲልም አክሎ ተናግሮ ነበር። የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት ታዲያ ከጎረቤት አገራት ለሚገቡ ስደተኞች ምዝገባ የሚከናወንላቸው በድንበር አካባቢዎች እንጅ በአዲስ አበባ አይደለም ያለ ሲሆን ምዝገባው በመዲናይቱ እንደተቋረጠ ተደርጎ መገለፁ ተገቢ አይደለም ብሏል። በአዲስ አበባ ለሚገኙ ስደተኞች መታወቂያ እና የልደት የምስክር ወረቀት መስጠቴን ቀጥያለሁም ሲል ተናግሯል።

Читать полностью…

EthioTube

ከወራት በፊት ብሪክስ በሚል ስያሜ ወደሚጠራው በማደግ ላይ ያሉ አገራት ስብስብ የተጋበዘችው ኢትዮጵያ ይፋዊ አባልነቷን ዛሬ ትጀምራለች።

ስብስቤ በፈረንጆቹ 2000ዎቹ ነበር በአንድ ተጀምሎ መጠራት የጀመረው። በቅድሚየም የኢንቨስትመንት ፈንድ ለማቋቋም የፈለጉ ባንከኞች ነበሩ የአራት አገራትን የመጀመሪያ ሆሄያት በመውሰድ ብሪክ የሚል ስያሜ በኢመደበኛነት የፈጠሩት። ብራዚል፥ ሩሲያ፥ ህንድ እና ቻይና ቀዳሚዎቹ አባላትም ነበሩ። ከጥቂት ዓመታት በኋላ ደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያዋ አፍሪካዊት አገር ሆና ቡድኑን ስትቀላቀል ብሪክ የነበረው መጠሪያ ወደብሪክስነት እደገ።

የቡድኑ አባላት ዓመታዊ ስብሰባን የሚያደርጉ ሲሆን ፕሬዚዳንትነትንም እየተቀያየሩ ይወስዳሉ። የዓለም ባንክን የመሳሰሉ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት በምዕራብ አገራት ተፅዕኖ ስር ናቸው እያሉ የሚያማርሩት የብሪክስ አባላት የአዳጊ አገራት ተሳትፎ ከፍ እንዲል ይወተውታሉ።

ከወራት በፊት በደቡብ አፍሪካ በተደረገ ስብሰባው ተጨማሪ ማስፋፊያ ማድፈግን የወጠነው ብሪክስ ኢትዯጵያን ጨምሮ ለስድስት አባላት አገራት የተቀላቀሉን ግብዣ አቅርቦ ነበር። ግብፅ፥ ኢራን፥ ሳዑዲ አረቢያ፥ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እና አርጀንቲና ሌሎቹ ጥሪው የደረሳቸው አገራት ነበሩ። አገራቱ በጥሪው ደስታቸውን ገልፀው የነበሩ ቢሆንም ከዚያ በኋላ በተደረገ ምርጫ ያሸነፉት አዲስ የአርጀንቲና ፕሬዚዳንት ሃቭየር ሜሊየ አገራቸው ጥሪውን እንደማትቀበል አሳውቀዋል።

አዳዲሶቹ ዕጩዎች ማኅበሩን አዲስ የምዕራባውያን ዓመት በተጀመረበት በዛሬው ቀን እንደሚቀላቀሉ ተነግሮ ነበር።

በግጭቶች እና በዓለም አቀፉ የኮቪድ ወረርሽኝ ምክንያት ምጣኔ ኃብቷ ክፉኛ የደቀቀው ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባልነት ምን ያህል ጥቅም ልታገኝ ትችላለች የሚለው ገና ወደፊት የሚታይ ቢሆንም ባለስልጥኖቿ ማኅበሩን መቀላቀልን እንደትልቅ ዲፕሎማሲያዊ ድል አድርገው ማቅረባቸው አልቀረም።

አዳዲሶቹ አባላት በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ በተደረገ የቅድመ ዝግጅት አድራጊ የባለሟሎች ስብሰባ ላይ የተሳተፉ ሲሆን ቀጥሎ በሩሲያዋ መዲና ሞስኮ በሚደረገው አጠቃላይ ጉባዔ ላይ አገራቱ ሙሉ ተሳትፎ ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Читать полностью…

EthioTube

ከእንቅልፉ በድንገት የነቃው የእስራኤል ወታደር ጓደኞቹን ተኩሶ መምታቱ ተገለጸ

ለፍልስጤም ነጻነት እታገላለሁ የሚለው ሐማስ ከ83 ቀናት በፊት በእስራኤል ላይ ያልተጠበቀ ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ ጦርነት መቀስቀሱ ይታወሳል።

እስራኤል በወሰደችው የአጸፋ እርምጃ ከ21 ሺህ በላይ ፍልስጥኤማውያን ሲገደሉ ከ1ሺህ 200 በላይ እስራኤላውያንም ተገድለዋል።

ወደ ጋዛ እግረኛ ወታደሮቿን ያሰማራችው እስራኤል ከሀማስ ታጣቂዎች ጋር ከባድ ውጊያ በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡

በእርፍት ላይ የነበረ የእስራኤል ወታደርም ከእንቅልፉ ድንገት በመንቃት አብረውት እረፍት ላይ የነበሩ ወታደሮቹ ላይ መተኮሱን ጀረሰላም ፖስት ዘግቧል፡፡

እንደዘገባው ከሆነ ወታደሩ ከአስፈሪ ቅዠት በመንቃት አጋሮቹ ላይ ተኩሷል የተባለ ሲሆን እስካሁን ቁጥራቸው በይፋ ያልተገለጹ ወታደሮችን አቁስሏል፡፡

ወታደሩ ለቀናት በጋዛ ውስጥ በነበረው ከባድ ውጊያ ውስጥ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን ከእንቅልፉ ድንገት በመንቃት ሊተኩስ የቻለው ከነበረበት ከባድ ጊዜ በሚገባ ባለማገገሙ ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል፡፡

ይህ ወታደር ወደ አዕምሮ ህክምና ድጋፍ ማድረጊያ ማዕከል ገብቷል የተባለ ሲሆን ምርመራ እና ህክምና ከተደረገለት በኋላ በህግ ይጠየቅ አይጠየቅ የሚባለው ይወሰናልም ተብሏል፡፡

እስራኤል በጋዛ የጀመረችውን ጦርነት እንድታቆም የተለያዩ ጫናዎች በመደረግ ላይ ሲሆኑ ኢራን እና የየመን አማጺዎች ደግሞ ጦርነቱ ካልቆመ ወደ ጎረቤት ሀገራት ሊስፋፋ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ላይ ናቸው፡፡

Читать полностью…

EthioTube

የሽግግር ፍትሕ ሂደት የጥቃት ሰለባዎችን ያማከለ መሆን አለበት ተባለ።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዐዊ መብቶች ፅህፈት ቤት እና የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን በጋራ ባወጡት የዘጠና ገፅ መግለጫ ነው ይሄንን ያሉት። መንግስት የሽግግት ፍትሕ ፖሊሲውን በዓለም አቀፍ የሰብዐዊ መብት ህግጋት ጋር እንዲያጣጥም፥ ለጥቃት ሰላባዎች እና ለቤተሰቦቻቸው ፍትሕን ማስገኘትን ዓላማ እንዲያደርግ ሁለቱ ተቋማት በመግለጫቸው ጠይቀዋል።

ከሐምሌ 2014 እስካለፈው መጋቢት ድረስ ባለው ጊዜ የተደረጉ አስራ አምስት የማኅበረሰብ ምክክሮች ላይ ተመስርቶ ነው ሪፖርቱ የተጠናቀረው። ምክክሮቹም በትግራይ፥ በአማራ፥ በአፋር፥ በአሮሚያ፥ በሶማሊ፥ በሐረሪ ክልሎች እና በድሬዳዋ አስተዳደር ነው የተካሄዱት ተብሏል። ከስምንት መቶ የሚልቁ ግለሰቦችም ተሳትፈዋል።

በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች የሞቱበት የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በሰላም ስምምነት ከተቋጨ እና ቢያንስ በትግራይ የጥይት ድምፅ ከቆመ በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አለኝ ሲል ቆይቷል።

የመንግስታቱ ድርጅት የሰብዐዊ መብት ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ ከሰላም ስምምነቱ ጋር የሚስማማ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲን ለማርቀቅ ተጨባጭ እርምጃ መውሰዷን በመልካምነት አነስተዋል። ነገር ግን ፖሊሲው ከዓለም አቀፍ የሰብዕዊ መብት ህግጋት ጋርም የሚጣጣም መሆን አለበት፤ የጥቃት ሰለባ የሆኑ ማኅበረሰባትን በተለይም ደግሞ ሴቶችን እና ታዳጊ ሕፃናትን ማዕከል ያደረገ ሊሆን ይገባዋል ሲሉ ኮሚሽነሩ ገልፀዋል።

ሪፖርቱ አሁንም ኢትዮጵያ ውስጥ የሚስተዋሉ ግጭቶች ሰላማዊ መፍትሔ መስጠት እንዲሁም የተፈናቀሉ ዜጎችን ሰብዐዊ ክብራቸው በተጠበቀ መልኩ ወደቀያቸው መመለስ ትኩረት መስጠት ይገባል ሲል አክሏል።

Читать полностью…

EthioTube

የኢንተርኔት መዘጋት ከፍተኛ ኪሳራ ያደረሰባቸውን አገራት ዝርዝር ኢትዮጵያ ትመራለች ተባለ።

በመጠናቀቀ ላይ ባለው የፈረንጆቹ 2023 የመጀመሪያ አጋማሽ በኢንተርኔት መዘጋት ምክንያት ኢትዮጵያ በመቶ ሚሊዮን ዶላሮች የሚቆጠር ገንዘብ አጥታለችም ተብሏል።

ይሄንን ያለው በዲሞክራሲ እና በመብቶች ጥበቃ ላይ የሚሰራው ሴንተር ፎር አድቫንስመትን ኦፍ ራይትስ ኤንድ ዲሞክራሲ ወይንም በምህፃረ ቃል ካርድ እየተባለ የሚጠራው ተቋም ነው። ተቋሙ ለመረጃው በምንጭነት ቴክ ኔክስት የሚሰኝ በቴክኖሎጂ ዙርያ የሚሰራ ኅትመትን ጠቅሷል።

በዚሁ የጊዜ ክልል በዓለም ዙርያ በአስራ ሦስት አገራት ስድሳ አምስት ኢንተርኔትን የመጠርቀም እርምጃዎች ተወስደዋል ይላል ይህ ተቋም። ከዚህም የተነሳ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር የሚልቅ ኪሳራ አጋጥሟል።

ከፍተኛውን እጦት ያስመዘገበችው ኢትዮጵያ ስትሆን ህንድ እና ፓኪስታን ይከተላታል ተብሏል።

ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በርካታ አጋጣሚዎች የኢንተርኔት አገልግሎትን ያቋረጠች ሲሆን ይህም በመረጃ ነፃነት ተሟጋች ተቋማት ጥርስ ውስጥ እንድትገባ አድርጓታል። ካለፈው ክረምት አንስቶ ግጭት ውስጥ በሚገኘው እና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በታወጀበት የአማራ ክልል የኢንተርኔት አገልግሎት ከተቋረጠ ወራት ተቆጥረዋል።

ከአንድ ዓመት ገደማ በፊት መቀመጫውን በእንግሊዟ ለንደን ባደረገ ቶፕቴን ቪፒኤን የተባለ ተቋም ይፋ የሆነ ሪፖርት በጦርነት ምክንያት ኢንተርኔት ተቋርጦበት በነበረው ትግራይ ክልል የሚገኙ የንግድ ተቋማት ከ145 ሚሊዮን ዶላር የሚልቅ ገንዘብ በዚሁ ምክንያት ብቻ በአንድ ዓመት ማጣታቸውን ዘግቦ እንደነበር መገልፁ ይታወሳል።

Читать полностью…

EthioTube

16ዓመት ተፈርዶበታል

በሐዋሳዋ የዳሸን ባንኳ ሰራተኛ ፀጋ በላቸው ላይ የጠለፋ እና አስገድዶ መድፈር ወንጀል በመፈፀሙ የዋስትና መብቱ ተነፍጎ ከሐዋሳ ማረሚያ ሆኖ ችሎቱን ሲከታተል የነበረው እና የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የግል ጠባቂ የሆነው ኮንስታብል የኋላመብራት ወልደ ማሪያም በሀዋሳ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በዋለው የወንጀል ችሎት በተከሰሰባቸው ሁለቱም ወንጀሎች ጥፋተኛ ነው ተብሎ በቀን 04/04/2016 መወሰኑ የሚታወስ ሲሆን በቀን 11/04/2016 የዋለው ችሎት ደግሞ የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት ከተቀበለ በኋላ በዛሬው ዕለት ማለትም በ18/04/2016 ዓ.ም ተከሳሹን እጁ ከተያዘበት ጀምሮ በሚቆጠር በ16ዓመት ጽኑ እስራት የቀጣ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

Читать полностью…

EthioTube

የምዕራብ አገራት ኤምባሲዎች በዲፕሎማቶች ላይ የደረሰው ጥቃት አሳስቦናል አሉ።

የአፍሪካ የልማት ባንክ ከፍተኛ ሹሞች የሆኑ ሁለት የውጭ አገር ዜጎች በፀጥታ ኃይሎች ታስረው መደብደባቸው ከተዘገበ እና ባንኩም ዓለምአቀፍ ሠራተኞችን ከኢትዮጵያ ለማስወጣት ወስኛለሁ ካለ በኋላ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ሦስት የምዕራብ አገር ኤምባሲዎች በጉዳዩ ላይ ኃሳባቸውን ገልፀዋል። የዩኤስ አሜሪካ፥ የካናዳ እና የብሪታንያ ኤምባሲዎች አከታትለው ባወጧቸው መግለጫዎች ከጥቃቱ ጋር ተጠያቂነት እንዲሰፍን ጠይቀዋል።

ሁለቱ የአፍሪካ ልማት ባንክ ሠራተኞች ለጥቃት የተጋለጡት ከስምንት ሳምንታት በፊት መሆኑ የተዘገበ ሲሆን የባንኩ ላዕላይ ኃላፊዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ተገናኝተው እንዳስፈቷቸው በሰፈው መዘገቡ ይታወሳል። ሠራተኞቹም ወዲያውኑ አገር ለቅቀው ሄደዋል። ይሄንን ተከትሎ ባንኩ ከመንግስት በጉዳዩ ላይ ምርመራ እንደሚደረግና ጥቃቱን ያደረሱ አካላትም ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ቃል የተገባልኝ ቢሆንም ምርመራው ምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ የማውቀው ነገር የለም ብሏል። ከዚህም ባሻገር ለሠራተኞቼ ደህንነት ምንም ያህል ዋስትና የለኝም በማለት የውጭ አገር ዜግነት ያላቸው ሠራተኞቹ በሙሉ ኢትዮጵያን ለቅቀው እንዲወጡ ወስኗል።

ውሳኔው ባንኩ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ቀጣይ ግንኙነት እንዲሁም በአገሪቷ ውስጥ ለጀመራቸው እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነውም ተብሏል።

በጉዳዩ ላይ ኃሳቡን ያሰፈረው የአሜሪካ ኤምባሲ በዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች ዙርያ በዓለም ዙርያ የሚተገበረውን እና የቪየና ቃል ኪዳን ተብሎ የሚጠራውን ስምምነት ማክበር እንደሚያስፈልግ አፅንፆት ሰጥቶ ተናግሯል። ጥቃቱ አሳስቦናል፤ ጥፋተኞችም ተጠያቂ ሊሆኑ ይገባቸዋል ሲልም አቋሙን ገልጿል።

የአፍሪካ ልማት ባንክን በገንዘብ ከሚደጉሙት አገራት መካከል እንገኝበታለን ያለችው ብሪታንያ በበኩሏ በዓለም ዙርያ ያሉ ዲፕሎማቶች ተልዕኳቸውን እንዲወጡ የሚያስችለው የቪየና ቃል ኪዳን ሊከበር እና ሊጠበቅ ይገባዋል ብላለች። በጥቃቱ ዙርያ ጠለቅ እና ዘርዘር ያለ ምርመራ ያስፈልጋል ስትልም ጨምራ አሳስባለች።

የካናዳ መግለጫ ደግሞ ጥቃቱ እስካሁንም እንዳሳሰበን ነው ይላል። ጥቃት አድራሾቹ እስካሁን ተጠያቂ ያለመሆናቸው እጅጉን የሚያስቆጭ ነገር ነው ስትል አክላለች። ባንኩ የውጭ አገር ሰራተኞችን ማስወጣቱ አስደንግጦናል ስትልም ተናግራለች። ዓለም አቀፍ የጥበቃ ቃልኪዳን የሚጣስ ከሆነ ዲፕሎማቶች በአግባቡ መከወን አይችሉምም ብላለች።መግለጫዎቹ እንደሚያሳዩት ጥቃቱ የኢትዮጵያ ገፅታ ላይ ጥላሸት ያሳረፉ ይመስላል። ጥቃቱ ደብዛው ከጠፋቨ አምስት ሚሊዮን ዶላር ጋር የሚገናኝ እንደሆነ የጠቆሙ ዘገባዎች በቅርቡ መውጣታቸው ይታወሳል።

በሰሜን ኢትዮጵያ የቀደሙ ዘመናትን የሚያስታውስ ረሃብ ሊከሰት ይችላል ተባለ። መንግስት በበኩሉ ድርቅ ቢከሰትም ረሃብ የለም ይላል፤ ረሃብ እንዳለ የሚናገሩት ሌላ ዓላማ ያላቸው ወገኖች ነው ሲልም ይከሳል።

በጦርነት ደቅቃ ድርቅ የተደረበባት ትግራይ ክልል በመጓዝ ዘርዘር ያለ ዘገባ የሠራው የካናዳው ስመ ጥር ግሎብ ኤንድ ሜይል ጋዜጣ የረድዔት ድርጅት ሠራተኞችን በመጥቀስ ኢትዮጵያን መጥፎ ስም ያሰጧትን ከአስርት ዓመታት በፊት የተከሰቱትን የሚገዳደር ረሃብ አንዣብቧል ሲል አስጠንቅቋል።

አውዳሚው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በሰላም ስምምነት ተቋጭቶ ቢያንስ በትግራይ ክልል የተኩስ ድምፅ መሰማት ያበቃ በመሰለባቸው አስራ አራት ወራት በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በምግብ እጥረት ህይወታቸው አልፏል ጋዜጣው እንደሚለው።

የጭላ በምትባለው ብዙ እርዳታ ጠባቂዎች በተሰባሰቡባት ትንሽ ከተማ በየዕለቱ ምንዱባን የተራድዖ እህል ማከማቻ መጋዘን አጠገብ ይሰባሰባሉ ሲል ያየውን የዘገበው ጋዜጣው አንዳንዶች ደግሞ ከአካባቢው መስተዳደር ፅህፈት ቤት በር ውጭ ይከማቻሉ፤ አንዳንዶቹ እንዲያውም አንዳች ነገር ጠብ ቢል በሚል እዚያው ያድራሉ ሲል አስነብቧል።

በ1977 ገደማ በኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረው ረሃብ ክፉኛ ጡጫውን ካሳረፈባቸው የአገሪቷ አካባቢዎች መካከል አንደኛዋ ትግራይ እንደነበረች ያስታወሰው ዘገባው አሁን ያንዣበበው መዐት ከዚያም ሊከፋ ይችላል ብሏል። በጦርነት ምክንያት የክልሉ ሰብል ማምረቻዎች፥ የጤና ማዕከላት እና የመንግስት ፅህፈት ቤቶች ወድመዋል ወይንም ተዘርፈዋል ያለው ጋዜጣው መልሶ የመገንባት ጥረት ብዙም አይስተዋል ብሏል።

ረሃብን በማስመልከት ቅድመ ማስጠንቀቂያ የሚሰጠው ዘ ፋሚን ኧርሊ ዋርኒንግ ሲስተምስ ኔትዎርክ የተባለው የምርምር ተቋም ከጥቂት ቀናት በኋላ በሚጀመረው የፈረንጆች 2024 የመጀመሪያ ወራት ረሃብ በትግራይ በሰፊው ሊሰራጭ ይችላል ይላል። የክልሉ ባለስልጣናት 3.5 ሚሊዮን ገደማ ሰዎች አስቸኳይ እርዳታ ያሻቸዋል የሚሉ ሲሆን ከመካለላቸውም የሚበዙቱ አርሶ አደሮች ናቸው።

የክልሉ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር ከ77ቱም የሚከሰት ረሃብ እየመጣ ነው ሲሉ ለጋዜጣው ነግረውታል፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርዳታ ማስተባበሪያ ፅሕፈት ቤትም የቀድሞ ኃላፊም መረጃዎች በሙሉ የሚጠቁሙት ከአርባ ዓመታት ገደማ በፊት የተከሰተውን መዐት የሚገዳደር ቸነፈር እየመጣ መሆኑን ነው ይላሉ።

አንዲት ሴት ለጋዜጣው ዘጋቢ በአዝጋሚ ሞት ውስጥ ነው ያለነው ሲሉ ነግረውታል። ድርቁ እና የምግብ እጥረት በአጎራባች የአማራ ክልል ዞኖች እንደተከሰተም ይዘገባል።

የመንግስት የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር ሽፈራው ተክለማርያም ግን በቅርቡ ስለጉዳዩ ሲናገሩ ድርቅ ተከስቶ በርካቶችን ለምግብ እጥረት ቢዳርግም ረሃብ የለም ማለታቸው ይታወሳል። መንግስት ለችግር ለተጋለጡ ዜጎች እርዳታ ለማድረስ ከፍተና ገንዘብ መድቦ እየተንቀሳቀሰ ነው ሲሉም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል። በአንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ችግር እርዳታ ለማድረስ የሚደረግ ጥረትን ማደናቀፉንም ጨምረው ገልፀው ነበር።

Читать полностью…

EthioTube

የአማራ ክልል ያለመረጋጋት ለጣና ሐይቅም ስጋት ፈጥሮበታል ተባለ።

የክልሉ የኮምኒዩኬሽን ፅሕፈት ቤት የሐይቁ ህልውና ላይ አደጋን ፈጥሮ የነበረውን የእምቦጭ አረምን ለመከላከል ይደረጉ የነበሩ ጥረቶች በፀጥታ ስጋት ምክንያት መታወኩን ገልጿል።

የአገሪቷ ትልቁ ሐይቅ ጣና በወራሪው እምቦጭ አረም ምክንያት በተደጋጋሚ ስጋት የሚፈጥረበት ሲሆን የአካበቢ እና የፖለቲካ ሹማምንት የተለያዩ የማኅበረብ ክፍሎችን በማስተባበር አረሙን ለማጥፋት ሲጥሩ ነበር። ይሁንና እና ከክረምት ወር አንስቶ የተፈጠረው ያለመረጋጋት ይሄንን ማድረግን አዳጋች አድርጎታል።

ክልሉ ለስድስት ወራት በታወጀ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በተለይ በትንንሽ ከተሞች እና በገጠር ቀበሌዎች እስካሁንም በሚዘገቡ ግጭቶች ምክንያት ቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ፈታኝ ሆኗል።

የክልሉ መንግስት አሁን እንደሚለው ባለፉት ጥቂት ወራት የመከላከል እርምጃ በበቂ ሁኔታ ባለመወሰዱ የእምቦጭ አረም ክፉኛ ተስፋፍቶ ይገኛል።

ሁኔታው አሳሰቢ ነው ያለው የክልሉ የኮምኒዩኬሽን ቢሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ አለባቸው ብሏል።

መነሻው ከወደ ደቡብ አሜሪካ ሳይሆን አይቀርም ተብሎ የሚጠረጠረው አምቦጭ በኢትዮጵያ የውሃ አካላትን ከሚወርሩ ከሰላሳ የሚልቁ አረሞች መካከል አንዱ ነው። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በጣና ሐይቅ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም የውሃ አካላት ላይ ተስተውሎ እንደነበር ሲዘገብ ቆይቷል።

Читать полностью…

EthioTube

በቦረና ያቤሎ አጠቃላይ ሆስፒታል መንታ ልጆች ተጣብቀው መወለዳቸው ተገለፀ።

ቦረና በሚገኘው ያቤሎ አጠቃላይ ሆስፒታል ሁለቱም ወንድ የሆኑ መንትያ ልጆች ተጣብቀው መወለዳቸው ሲገለፅ የልጆቹ እናት በምስራቅ ቦረና የዋጪሌ ወረዳ ነዋሪ ናት ተብሏል።

ያቤሎ አጠቃላይ ሆስፒታል የጽንስና ማህፀን ህክምና ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር ዋርዮን ፥ የተወለዱት ህፃናት በልባቸው አካባቢ ተጣብቀው መወለዳቸውን የገለፁ ሲሆን የህፃናቱ የትኛው ክፍል መተሳሰሩን ለማጣራት ምርመራ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።

ዶ/ር ዋርዮን የህፃናቱ ጉዳይ ከሆስፒታሉ አቅም በላይ የሚሆን ከሆነ በሀገሪቱ በሚገኙ ትልልቅ የህክምና ሆስፒታሎች ሊታዩ እንደሚችሉ አስረድተዋል።

Читать полностью…

EthioTube

ተቃዋሚው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) የመንግስት ኃይሎች እህል በመሰብሰብ ላይ የነበሩ ሰላማዊያንን ገድለዋል አለ።

በውንጀላው ዙርያ ከመንግስት በኩል የተሰማ ነገር የለም። ኦነግ ግድያው ተፈፅሟል ያለው በምዕራብ ኦሮሚያ በሚገኘው በሆሮ ጉድሩ አካባቢ ሲሆን አካባቢው በአየር ጥቃት እና በከባድ መሳርያ ተደብድቧል ሲልም አክሏል። በሦስት ዙር ተከናውኗል ባለው ጥቃት ከንፁሃን ዜጎች በተጨማሪ እንስሳትም ተገድለዋል ፓርቲው እንዳወጣው መግለጫ። በጥቃቱ ህይወታቸው ያለፈ ስምንት ሰዎችን ለይተናል ያለው ኦነግ ተገድለዋል ያላቸውን እነዚሁ ሰዎች በስም አስቀምጧል። ከዚህም በተጨማሪ በጥቃት ቁስለኛ ሆነዋል ያላቸውን ሁለት ሰዎች ስምም ጨምሮ በመገለጫው አካትቷል።

ኦነግ የመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ኃላፊነት የጎደለው እርምጃ እየወሰዱ ነው ያለ ሲሆን ይህንንም በፅኑው አውግዛለሁ ብሏል። በሁሉም የኦሮሚያ አካባቢዎች በሰው ደም እየተጫወተ ነው ሲልም በመግለጫው የሰላ ትችትን ሰንዝሯል። በገዥው ብልፅግና ፓርቲ የሚመራው መንግስት የንፁሃን ሰዎችን መብት መጣስን የቀን ተቀን ሥራው አድርጎታል ያለው ኦነግ በዚህም ምክንያት የንብረት ዝርፊያ፥ የጅምላ እስር፥ ግድያ እንዲሁም የቤቶች መቃጠል የሰርክ ተግባር ሆኗል ብሏል። የኦሮሞ ሕዝብ እና ሌሎችም ብሔር ብሔረሰቦች ጭቆናን መታገል አለባቸው የሚል ጥሪም አሰምቷል።

መንግስት ባልታጠቁ ሰዎች ላይ እርምጃ አዘውትሮ መውሰዱ የቀቢፀ ተስፋ ምልክት ነው ሲልም ገልጿል። በሆሮ ጉደሮ የድሮን ጥቃት ሳይደርስ እንዳልቀረ እና የአንድ ፕሮቴስታንት ቤተ ክርስትያን አባላት የሆኑ ዜጎች የቤተ ክርስትያኗን እህል በመሰብሰብ ላይ እያሉ የጥቃት ሰለባ ስለመሆናቸው የዘገቡ የብዙሃን መገናኛዎች ነበሩ።

መንግስት ከዚህ የኦነግ መግለጫ ጋር በተያያዘ እስካሁን የሰጠው ምላሽ ባይኖርም ከዚህ ቀደም ሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥቃት ያደርሳል በሚል የቀረቡበትን ውንጀላዎች እንዳጣጠለ አይዘነጋም። በኦሮሚያ ክልል ሸኔ እያለ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን ላይ ግን እርምጃ እየወሰደ እንደሆነ ይገልፃል።

ራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት እያለ የሚጠራው እና ከኦነግ ተሰንጥቆ የወጣ እንደሆነ የሚነገርለት ይህ ታጣቂ ቡድን በአገሪቱ ህግ በሽብርተኛነት የተፈረጀ ነው። ከቡድኑ ጋር መንግስት በታንዛኒያ በሁለት ዙር ድርድር ሲያደርገው የነበረው ድርድር ያለውጤት ከተበተነ በኋላ በኦሮሚያ ልዩ ልዩ አካባቢዎች ግጭቶች መጠናከራቸው ይዘገባል። ቡድኑ ራሱ ካለፈው መስከረም አንስቶ ከመንግስት ጋር አድርጌያቸዋለሁ ያላቸውን ፍልሚያዎች የዘረዘረ ሲሆን በሕዳር እና በታህሳስ ወሮችም ግጭቶች እንደነበሩ ተናግሯል።

የአገር መከላከያ ሠራዊት በቅርቡ በሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥቃት ለማድረስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የሸኔ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ወስጃለሁ ማለቱ አይዘነጋም። በእነዚህ እርምጃዎችም ቁጥራቸውን በግልፅ ያልጠቀሳቸውን የቡድኑን አባላት መግደሉን እና መማረኩን ተናግሯል። የግጭቶች መቀጠል በመኃል የሰላማዊ ዜጎችን ቁምስቅል ያበዛል የሚል ስጋት አይሎ አለ።

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያ፦ የእለተ ማክሰኞ ኢትዮትዩብ አንኳር አጫጭር ዜናዎች - ታህሳስ 16 ፣ 2016 | #Ethiopia: EthioTube Ankuar : አንኳር - Ethiopian Daily News Digest - December 26 , 2023

👉 ሚኒስትር ድዔታው አገር ጥለው መኮብለላቸው መነጋገሪያ ሆኗል

👉 ኢትዮጵያ እዳዋን የመክፈያ ተጨማሪ ቀናቶቿን ሳትከፍል አጠናቃለች ቀጣይ እጣፈንታዋ ምን ይሆን

ሌሎችንም መረጃዎች ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ 👇

https://youtu.be/fEo-sGeSiB8

Читать полностью…

EthioTube

የመከላከያ ሠራዊት በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች በታጣቂዎች ላይ እየወሰድኩት ባለው እርምጃ ድል እየቀናኝ ነው አለ።

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን መንግስት ሸኔ እያለ በሚጠራው እና ራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት እያለ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን ላይ በተወሰደ እርምጃ “ጥቂት የማይባል” የቡድኑ አባላት ተመትተዋል ያለው የአገር መከላከያ ሠራዊት በተመሳሳይ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን በሚንቀሳቀሱ እና ፅንፈኛ ባላቸው ኃይሎች ላይም ከስድሳ በላይ ታጣቂዎች “ከጥቅም ውጭ” አድርጌያለሁ ብሏል።

በሁለቱ ክልሎች የሚገኙ አንዳንድ ዞኖች ግጭቶችን ማስተናገዳቸውን የቀጠሉ ሲሆን ግጭቶቹ አንዳንድ ጊዜ በከባድ መሣርያ እንዲሁም በድሮኖች የታጀቡ እንደሆኑ ዘገባዎች ያትታሉ። ይህም ከሰሜኑ ጦርነት ጦስ ገና ጨርሳ ላልወጣቸው አገር ምጣኔ ኃብት ድቀት ከሚኖረው ጫና በተጨማሪ የሰላማዊ ዜጎችን ደህንነት አደጋ ላይ ይጥላል የሚል ስጋትን ፈጥሯል።

የሠራዊቱ የማኅበራዊ መገናኛ የትስስር ገፅ በምዕራብ እዝ የአንድ ክፍለ ጦር አዛዥ የሆኑትን ኮሎኔል መሃመድ ሙሳን ጠቅሶ እንደዘገበው በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ እንዲሁም በኢቨንቱ ሀሮ ሊሙ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የሸኔ ታጣቂ ቡድን አባላት ላይ ነው እርምጃ ወስዷል።

የታጣቂ ቡድኑ አባላት በአካባቢው ዝርፊያ እና ግድያዎች ሊፈፅሙአ እየተዘጋጁ ነበር ሲልም ዘገባው አክሏል። ሠራዊቱ በታጣቂዎቹ ላይ እርምጃ የወሰደው ከኅብረተሰቡ ጥቆማ ደርሶት ነው ያለው ዘገባው “ጥቂት የማይበሉ” የቡድኑ አባላት ተገድለዋል፤ ሌሎች ደግሞ ተማርከዋል ሲል ገልጿል። የተገደሉትን ታጣቂዎች ቁጥር ግን በግልፅ አላስቀመጠም። ሰላማዊ አማራጭን ትቶ በጉልበቱ እየዘረፈ መኖርን ምርጫው አድርጓል በሚል በዘገባው በተጠቀሱ አንድ መኮንን የተወነጀለው ታጣቂ ቡድን ላይ እርምጃ መወሰዱ ይቀጥላልም ተብሏል።

በኢትዮጵያ ህግ በሽብርተኛነት የተፈረጀው የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት በጉዳዩ ላይ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ያለው ነገር የለም።

በኢትዮጵያ መንግስት እና በታጣቂ ቡድኑ መካከል በሁለት ዙሮች በታንዛኒያ የተደረጉ ድርድሮች ያለውጤት መበተናቸው አይዘነጋም። ይሄንን ተከትሎም በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ግጭቶች እና ጥቃቶች መዘገባቸውን ቀጥለዋል።

በሌላ በኩል በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ደጀን ወረዳ አካባቢ ግዳጅ ላይ በነበረ አንድ አሃድ ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከሩ ታጣቂዎች ሙከራ ከሽፏል ሲል የሠራዊቱ የማኅበራዊ ትስስር ገፅ በሌላ ዘገባ አትቷል። ጥቃቱን የፈፀሙት የህዝብን እና የመንግስትን ንብረት የመዝረፍ አባዜ የተጠናወተው ፅንፈኛ ቡድን ነው ብሏል።

የታጣቂው ቡድን አባላት “ክፉኛ” ተመትተዋል ያለው ዘገባው በቁጥር ስድሳ የሚሆኑ ታጣቂዎች “ከጥቅም ውጭ ሆነዋል” ያለ ሲሆን ይህንን ሲል ምን ማለቱ እንደሆነ አላብራራም። ይሁን እንጅ ታጣቂው ቡድን “ቁስለኛውን እያንጠባጠበ” ከአካባቢው ሸሽቷል ሲል አክሏል። ይህንን በተመለከተ ከሌላ ወገን የተገኘ ማረጋገጫ የለም።

አማራ ክልል ካለፈው ክረምት አንስቶ የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከትሎ በታወጀ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር የሚገኝ ሲሆን የመንግስት ባለስልጣናት አንፃራዊ መረጋጋት ተመልሷል ይላሉ። ይሁን እንጅ አሁንም ግጭቶች መሰማታቸው አልቀረም።

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያ መሳብ የቻለችው የውጭ ኢንቨስትመንት ከፍተኛ ማሽቆልቆል ታይቶበታል ተባለ።

ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንቷ ባለፉት ዓመታት ከነበረው ጋርም ሆነው በአቅራቢያዋ ካሉ የምስራቅ አፍሪካ አገራት ጋር ሲተያይ የቁልቁል ተጉዟል ተብሏል። ይሄን ያለው በዓለም ላይ ከፍተኛ ከሚባሉት አራት የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (አካውንቲንግ) ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ኧርነስት ኤንድ ያንግ ወይንም ኢዋይ ነው።

በአንድ ወቅት ለቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት ተመራጭ የነበረችው ኢትዮጵያ ባለፉት ሦስት ዓመትት መሳብ የቻለችው መጠን ከሦስት ቢሊዮን ዶላር ወደስድስት መቶ ሚሊዮን ዶላር ክፉኛ ዝቅ ብሏል። በፈረንጆች አቆጣጠር በ2019 በአገሪቷ ውስጥ ሰላሳ አራት ያህል የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ፕሮጄክቶች የነበሩ ሲሆን ይህ ቁጥር በ2022 ወደስድስት ዝቅ ብሏል።

ይህን ካመጡት ምክንያቶች መካከልም የሩሲያና የዩክሬን ጦርነት፥ የኮቪድ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ እና የኢትዮጵያ የአገር ውስጥ ግጭቶች እና ጦርነት ይገኙበታል ሲል የአካውንቲንግ ኩባንያው ገልጿል።
ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ልዩ የቀረጥ ተጠቃሚነት (አጎዋ) መቀነሷ እንዲሁም የውጭ ምንዛሬን የተመለከቱ የደንብ ማነቆዎች ሌሎች ምክንያቶች ናቸውም ተብሏል።

በምስራቅ አፍሪካ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ከጨመረላቸው አገራት መካከል ኡጋንዳ እና ኬንያ ይገኙበታል። ኡጋንዳ በፈረንጆች 2022 አስር ቢሊዮን ዶላር ገደማ የውጭ ምንዛሬ አግኝታለች ተብሏል። በዚህም ከ6300 የሚለቁ ዜጎቿ ስራ አግኝተዋል።

Читать полностью…

EthioTube

ውይይት በቴሌግራም ከዘጠኝ ሞት ደራሲ እና አዘጋጅ ዳዊት ተስፋይ ጋር 👇🏾

/channel/Cinemagallery11?videochat

Читать полностью…

EthioTube

ግብፅ በኢትዮጵያ ላይ ዛቻ መሰንዘሯን ቀጥላለች።

በያዝነው ዓመት ብቻ በአራት ዙሮች የተካሄደው የህዳሴው ግድብ ድርድር ያለውጤት መበተኑን ተከትሎ የግብፅ ባለስልጣናት ዛቻ የቀላቀሉ ንግገሮችን ማሰማታቸውን ቀጥለዋል። በቅርቡ አስተያየታቸውን የሰጡት የአገሪቱ የመስኖ እና የውሃ ኃብት ሚኒስትር የአገራቸው የውሃ ደህንነት አደጋ የሚጋረጥበት ከሆነ “ተመጣጣኝ የሆነ እርምጃ” እንወስዳለን ሲሉ ተሰምተዋል። ይህ እርምጃ ምን እንደሆነ ግን ዘርዝረው አልገለፁም።

አራተኛው ዙር ድርድር ያለውጤት ባለፈው ሳምንት እንደተቋጨ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢትዮጵያን በአቋሟ ግንችር ብላ ስምምነት ላይ እንዳይደረስ አስቸግርላች የሚል ክስ ሰንዝሮባት ነበር። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም በበኩሉ ይህ የግብፅ መግለጫ ዓለም አቀፍ መርኆዎችን የጣሰ ነው ሲል አጣጥሎታል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አክሎም ግብፅ የቅን ግዛት ዘመን አስተሳሰብ ላይ ቆማ ቀርታለች ሲል ወርፏታል።

የካይሮው የመስኖ እና ውሃ ኃብት ሚኒስትር ሃኒ ሰዋሊም በሳምንቱ የእረፍት ቀናት ወቅት አል-አራቢያ በተባለ የቴሌቭዥን ጣብያ ቀርበው ስለታላቁ የህዳሴ ግድብ በተጠየቁበት ወቅት ኢትዮጵያ በግድቡ ያላት ፍላጎት የኤልክትሪክ ኃይል ከማመንጨትም አልፎ ፖለቲካዊ የበላይነት የመያዝ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያዊያኑ በግድቡ የገነቡት የውሃ ቋት እናመነጨዋለን ለሚሉት የኤሌክትሪክ ኃይል ከሚያስፈልገው እጅግ የበለጠ ነው ሲሉ የተሰሙት ሚኒስትሩ እንደዚህ የተጋነነ ሐይቅ ለመገንባት የፈለገችው ኢትዮጵያ ሌላ ድብቅ ፍላጎት ስላላት ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በግድቡ ሐይቅ ግንባታ ላይ ብቻም ሳይሆን ለድርድሩ ይዛው በምትቀርበው አቋም እንዲሁም የግድቡ ባላት አስተያየት ከኤሌክትሪክ ኃይል የሚሻገር ዓላማ እንዳላት ግልፅ ነው ሲሉም አክለዋል።

“የህዳሴው ግድብ የፖለቲካ ጥቅም ይኖረዋል፤ ኢትዮጵያ የናይል ውሃን እንድትቆጣጠር እና የበላይነት እንዲኖራት ግብፅ አትፈቅድም” ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ግብፅ በግድቡ ዙርያ ዛቻ የተቀላቀለበት ንግግር ስታደርግ ይህ የመጀመሪያው ጊዜ አይደለም። ተደጋጋሚ ድርድሮችም ባለፉት ዓመታት ተከናውነዋል። ይሁንና ውጤት ሲያስገኙ አላስተዋለም። ኢትዮጵያም የግብፅን ማስፈራሪዎች ችላ ብላ ከታሰበበት ጊዜ እጅጉን ዘግይቶም ቢሆን ግድቡን ለማጠናቀቅ ተቃርባለች።

በግጭቶች ክፉኛ በደደቀችው ኢትዮጵያና ከዓለም ትልልቅ የጦር ኃይሎች የአንዱ ባለቤት በሆነችው መካከል ቀጥተኛ ጦርነት ይጫራል ተብሎ ባይታሰብም ዲፕሎማሲያዊ ቁርሿቸው ሌሎች የፀጥታ እና የምጣኔ ኃብት መዘዞችን ሊያስከትሉ ግን ይችላሉ።

Читать полностью…
Subscribe to a channel