ethiotube | Unsorted

Telegram-канал ethiotube - EthioTube

-

ኢትዪትዩብ፦ ኢትዮጵያዊ። ነፃ። ገለልተኛ። Follow us on other platforms: Facebook.com/EthioTube Twitter.com/EthioTube Youtube.com/EthioTube Instagram.com/EthioTube

Subscribe to a channel

EthioTube

የቦይንግ አውሮፕላን የሞተር ሽፋን በበረራ ላይ ተገንጥሎ መውደቁን ተገለጸ

የአሜሪካው የሳውዝዌስት አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን በበረራ ላይ እያለ የሞተሩ ሽፋን ተገንጥሎ መውደቁ ተነገረ።

135 መንገደኞችንና 6 የበረራ አባላት ያሳፈረው አውሮፕላን ዴንቨር ለማረፍ ከመደገጉ በፊት 10 ሺህ 300 ጨማ ከፍታ ላይ እየበረረ እንደነበረም ነው የተገለጸው።


ችግሩ ማጋጠሙን ተከትሎ የአሜሪካ የአየር መንግድ ተቆጣጣሪዎች አፋጣኝ ምርመራ እያደረጉ መሆኑም ተነግሯል።

የአሜሪካው የሳውዝዌስት አየር መንገድ በቦይንግ ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን ላይ ያጋጠመውን ችግር የአየር መንገዱ የጥገና ቡድን እንደሚመረምረው አስታውቀዋል።

አየር መንገዱ ለእንደዚህ አይነት ክፍሎች ጥገና ኃላፊነት እንዳለበት አረጋግጧል።

ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን የተመረተው በፈረንጆቹ በ2015 መሆኑን የፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (ኤፍኤኤ) መረጃ ያመለክታል።

ቦይንግ ኩባንያ የአሜሪካው የሳውዝዌስት አየር መንገድ በቦይንግ ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን ላይ ባጋጠመው ችግር ዙሪያ እስካሁን አስተያየት አልሰጠም።

የዓለማችን ግዙፍ የአቪየሽን ኩባንያ የሆነው ቦይንግ ካሳለፍነው ጥር ወር ጀምሮ በ737 ማክስ 9 አውሮፕላን መስኮቱ ተገንጥሎ መውደቁን ተከትሎ ትችቶችን እያስተናገደ ይገኛል።

ከዚህ ጊዜ በኋላ ተደጋጋሚ የምርት ጥራት ችግሮች የተከሰቱ ሲሆን የአሜሪካ አቪዬሽን አስተዳድር በኩባንያው ላይ የቴክኒክ ጥራት ምርመራዎችን አድርጓል።

ኩባንያው በቦይንግ 737 ማክስ 9 አውሮፕላን ምርቶች ላይ ካከናወናቸው 89 የጥራት ምርመራዎች ላይ በ33ቱ ጉድለት እንደተገኘበት መገለጹም ይታወሳል።

ይህ አውሮፕላን በተለይም የኤሮ ሲስተሙ ሲፈተሸ የጥራት ደረጃውን ያሟላው ከ13 ነጥቦች በስድስቱ ብቻ አልፏል ተብሏል።

የኩባንያው የቴክኒክ ባለሙያዎች ስለ 737 ማክስ 9 አውሮፕላን በቂ እውቀት እንዳላቸው በተደረገው ምርመራ የሚገባውን ያህል ያውቃሉ የሚለውን ኩባንያው ማስረዳት እንዳልቻለም ተገልጿል።

አል አይን

Facebook.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram.com/EthioTube
/channel/ethiotube

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያ፦ እለተ አርብ የኢት ዜና - መጋቢት 27 ፣ 2016 | #Ethiopia: Et News : አንኳር - Ethiopian Daily News Digest - April 5, 2024

👉አለም ባንክ የፈቀደችው አዲስ ብድር
👉የሶማሊና የኢትዮጵያ ጉዳይ እየከረረ መጥቷል
👉በባለቤቱ ላይ የመግደል ሙከራ የፈፀመው የፖሊስ አባል
ሌሎችንም መረጃዎች ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ 👇
https://youtu.be/6UrueGKPzvE

Читать полностью…

EthioTube

የሶማሊላንድ እና  ፑንትላንድ ባለሥልጣናት ሶማሊያ መንግስት የ ኢትዮጵያ ቆንስላ ለመዝጋት የሰጠውን ማስጠንቀቂያ ውድቅ አደረጉ

የሶማሊላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሮዳ ኤልሚ፤ የሶማሊላንድ የመረጃ፣ የባህልና ብሔራዊ መመሪያ ሚኒስትር አሊ ሀሰን ሞሃመድ እና የፑንትላንድ የመረጃ ሚኒስትር ማህሙድ አይዲድ ዲሪር የሶማሊያ መንግስት በሶማሊላንድ መዲና ሃርጌሳ እና በፑንትላንድ ጋሮዌ የሚገኙትን የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤቶች እንዲዘጉ የሰጠውን ማስጠንቀቂያ ውድቅ አድርገዋል።

በትላንትናው ዕለት የሶማሊያ መንግስት በ ሞቃዲሾ የሚገኙት የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ሞሃመድ ዋሬ  በ72 ሰዓት ውስጥ ሶማሊያን ለቀው እንዲወጡ ያዘዘ ሲሆን ሲሆን በተጨማሪም በኢትዮጵያ የሚገኙትን አምባሳደሩን ለምክክር በሚል መጥራቱን አስታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪም፤ የሶማሊያ መንግስት በሶማሊላንድ ዋና ከተማ ሀርጌሳ እና በፑንትላንድ ጋሮዌ ከተማ የሚገኙትን ቆንስላ ጽ/ቤቶች በሰባት ቀናት ውስጥ ይዘጋሉ ብሏል።

ይሁን እንጂ አምባሳደር ሮዳ ከቪኦኤ ሶማሊ ጋር ባደረጉት አጭር ቃለ መጠይቅ፤  (የሶማሊያ) ውሳኔው፤ "በህልም" ላይ የተመሰረተ እና "ጥቅም የሌለው" ነው ብለዋል።

የሶማሊላንድ የመረጃ፣ የባህልና ብሔራዊ መመሪያ ሚኒስትር አሊ ሀሰን ሞሃመድ በበኩላቸው በሰጡት መግለጫ፤ በሶማሊላንድ “የኢትዮጵያ ኢምባሲ በሶማሊ ላንድ ከመነሻው በሶማሊያ ፍቃድ አይደለም  የተከፈተው፤ ስለዚህ ሞቃዲሾ ባለመፈቀዷ አይዘጋም” ሲሉ ለሶማሊያ ምላሽ ሰጥተዋል።

በተመሳሳይ መልኩ፤  የፑንትላንዱ ማህሙድ አይዲድ የሶማሊያ መንግስት በጋሮዌ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ቆንስላ ለመዝጋት "የሚያስችል ስልጣን የለውም" ብለዋል።

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያና የዓለም ባንክ የ1 ነጥብ 72 ቢሊየን ዶላር የድጋፍና ብድር ስምምነት ተፈራረሙ

ኢትዮጵያ እና የዓለም ባንክ የ1 ነጥብ 72 ቢሊየን ዶላር የድጋፍ እና የብድር ስምምነት ተፈራረሙ፡፡የብድር እና የድጋፍ ስምምነቱ በኢትዮጵያ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የሚውሉ ስድስት ፕሮጀክቶችን ለመተገበር እንደሚውል ተገልጿል፡፡የድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ እና በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ኦስማን ዲዮን ተፈራርመውታል፡፡

ከተደረገው ድጋፍ ውስጥ 300 ሚሊየን ዶላር የሚሆነው በገጠር አካባቢዎች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ማሳለጥ ለሚያስችል የመንገድ መሰረት ልማት ግንባታ እንደሚውል ተገልጿል፡፡200 ሚሊየን ዶላሩ ደግሞ በኢትዮጵያ እየተተገበረ የሚገኘውን የሴፍቲ ኔት ፕሮግራም ለማጠናከር እና ለማስፋፋት እንደሚውል የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

በተመሳሳይ ከተሰጠው ብድር ውስጥ 340 ሚሊየን የሚሆነው በኢትዮጵያ ቆላማ አካባቢዎች የሚኖሩ አርብቶ አደር እና ከፊል አርብቶ አደር የማህበረሰብ ክፍሎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል እንደሚውል ተጠቅሷል፡፡

522 ነጥብ 6 ሚሊየን ዶላር በላይ የሚሆነው ደግሞ በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሃይል ተደራሽነትን ለማስፋት እና ታዳሽ ሃይል ማመንጨት የሚቻልበትን ሁኔታ ለመደገፍ እንደሚውል ተጠቁሟል፡፡275 ሚሊየን ዶላር የሚሆነው ደግሞ በኢትዮጵያ ከተሞች የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን እና ተደረሽነትን ለማስፋት እንዲሚውል ተገልጿል፡፡

Читать полностью…

EthioTube

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ 70ሺህ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ሁኔታዎችን የሚያመቻች የመንግሥት ልዑክ በቀጣይ ቀናት ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ እንደሚያቀና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብዩ ተድላ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ፤ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ የሚመራው ከተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ተወካዮች የተካተቱበት የልዑካን ቡድኑ የሚያቀናው ከሳዑዲ አቻው ፣ በሪያድ እና ጂዳ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች ጋር በመተባበር
መሆኑን ተናግረዋል።

ቃል አቀባዩ ልዑኩ በሳዑዲ በሚኖረው ቆይታ አስፈላጊውን ዝግጅት ካጠናቀቀ በኋላ በፍጥነት ዜጎችን የመመለስ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር ገልጸዋል።

መንግሥት ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተለያዩ አገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ከ50 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ማድረጉንም አቶ ነብዩ አስታውሰዋል።

መንግሥት በአሁኑ ወቅት ዜጎችን ከመመለስ ባሻገር ሕጋዊ የሥራ ሥምሪት ለማመቻቸት እየሠራ መሆኑን ተቅሰው፤ እስካሁን ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች፣ከሳዑዲ ዓረቢያ፣ከሊባኖስ እና ዮርዳኖስ ጋር ሕጋዊ የሥራ ሥምሪት መፈራረሙን አብራርተዋል።

ከኩዌት ፣ከባሕሬን እና ኦማን ጋርም ሕጋዊ የሥራ ሥምሪት ስምምነት ለመፈራረም በሂደት ላይ መሆኑን ቃል አቀባዩ ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የፍልሰተኞች መነሻ ብቻ ሳትሆን ከ1 ሚሊዮን በላይ ከተለያዩ ሀገር የመጡ የውጭ ሀገር ፍልሰተኞችን አስተናጋጅ ሀገር መሆኗን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በፍልሰተኞች አያያዝ እያደረገችው ላለው ሥራ ዓለም አቀፉ ማኀበረሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል መጠየቃቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

(EBC)

Читать полностью…

EthioTube

ሶማሊያ የኢትዮጵያን አምባሳደር ከሀገሯ ማባረሯን ገለጸች።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሄ አብዲ ከአራት ወራት በፊት በአዲስ አበባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ይታወሳል።

ይህ ስምምነት ሶማሊላንድን የራሷ ሉአላዊ ግዛት አድርጋ በምታያት ሶማሊያ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣንና እና ተቃውሞን ማስከተሉም አይዘነጋም።

ይህንን ተከትሎም ሶማሊያ የተለያዩ ዲፕሎማያው እርምጃዎችን ስትወስድ የቆየች ሲሆን፤ ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያን አምባሳደር ከሀገሯ ማባረሯን ሮይተርስ ዘግቧል።

እንደ ዘገባው ከሆነ ሶማሊያ በሞቃዲሾ የኢትዮጵያን አምባሳደር ያባረረች ሲሆን ለውሳኔው መነሻ የሆነው ደግሞ ከሶማሊላንድ ጋር ባሳለፍነው ጥር ወር ላይ ባደረገችው የወደብ ስምምነት ምክንያት ነው።

ከዚህ በተጨማሪም ኢትዮጵያ በፑንትላንድ እና ሶማሊላንድ ያሉ የኢትዮጵያን ቆንስላ ጽህፈት ቤቶችንም ዘግቻለሁ ብላለች።

አል ዐይን አማርኛ በጉዳዩ ላይ ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ነቢዩ ተድላ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም።

በተያያዘ ዜና የፑንትላንድ ገንዘብ ሚንስትር መሀመድ ፋራህ የመሩት ልዑክ በኢትዮጵያ ጉብኝት ማድረጉ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብዩ ተድላ ፑንትላንድ በገንዘብ ሚንስትሯ መሀመድ ፋራህ የተመራ ልዑክ በኢትዮጵያ ጉብኝት ማድረጉን ተናግረው ይህ የአዲስ አበባ ጉብኝት ከሰሞኑ ወቅታዊ ጉዳይ ጋር የማይገናኝ እንደሆነ እና የጉብኝት ፕሮግራሙም የቆየ ቀጠሮ ነው ሲሉ በዛሬው ሳምንታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች መግለጫቸው ላይ ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ ባሳለፍነው ጥር ወር ላይ ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ባደረጉት የወደብ መግባቢያ ስምምነት ምክንያት የኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ግንኙነት እንዲሻክር ምክንያት ሆኗል።

ስምምነቱን ተከትሎም የሶማሊያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ መንግስት በኢትዮጵያ የሚገኙትን የሀገሪቱን አምባሳደር አብዱላሂ መሀመድ ወርፋን ለምክክር ወደ ሞቃዲሾ መጥራቱን ይታወሳል።

Читать полностью…

EthioTube

43 አገራት በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የቀጠሉ ግጭቶችና የመብት ጥሰቶች አሳስቦናል አሉ

43 አገራት በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች የቀጠሉ ግጭቶችና የመብት ጥሰቶች በጣም እንዳሳሰቧቸው ትናንት ለተካሄደው 55ኛው የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ስብሰባ ባስገቡት መግለጫ ላይ ገልጸዋል።

አገራቱ፣ ሁሉም የግጭቶች ተሳታፊ ወገኖች በንግግር ሰላምን እንዲሽቱና በአገራዊ የውይይት ሂደቱ እንዲሳተፉ ጠይቀዋል። አገራቱ፣ በኢትዮጵያ ሰላምና እርቅ ለማስፈን ተዓማኒነት ያለው የሽግግር ፍትህ ፖሊሲና ተጠያቂነት አስፈላጊ መኾኑንም አውስተዋል።

የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ማዕቀፉ፣ እውነተኛ ተጠያቂነትን፣ እውነት አፈላላጊነትን፣ ካሳ እና ጥሰቶች ድጋሚ ላለመፈጸማቸው ማረጋገጫ መስጠትን ማካተት እንዳለበትም አገራቱ አሳስበዋል።

Facebook.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram.com/EthioTube
/channel/ethiotube

Читать полностью…

EthioTube

ትዝታ ስራ አገኘች

ትዝታ ገረመው አዲሱን ስራዋን በኢትዬጲያን ቢዝነስ ሪቪዊ Ethiopian Busines Review የመረጃ ጥንቅር እና ምርምር ኦፊሰር (Data Researcher) ሆና ሚያዝያ 1 ሥራ ለመጀመር የቅጥር ደብዳቤ ዛሬ ተቀብላለች።

ቢሮ ተገኝታ ከቅርብ አለቃዋ የEthiopian Business Review ዋና አዘጋጅ ወይዘሪት ኤደን ተሾመ፣ እንደዚሁም የአስተዳደር እና ፋይናንስ ኃላፋዋ ወይዘሪት ሃና ፈቃዱ ጋር ስለ አዲሱ ስራዋ እና የድርጅቱ የሥራ መመሪያ በዝርዝር ገለፃ ተደርጎላታል። ከተቀሩት የድርጅታችን ሰራተኞች ጋርም ትውውቅ አድርጋለች።

ቅዳሜ ዕለት ያቀረብነውን የትብብር ጥያቄ ተቀብላችሁ አድራሻዋን በመስጠት እንድንገናኝ ላገዛችሁ ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን።

ምንጭ፡ አማን ይሁን በፌስቡክ

Читать полностью…

EthioTube

በመሬት አገልግሎት ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ ተነሳ

ላለፉት ሦስት ወራት እግድ ተጥሎበት የነበረው የመሬት አገልግሎት ካለፈው ሰኞ መጋቢት 23 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ መነሳቱ ተገለጸ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በተጠናው የመዋቅር ጥናት መሠረት የሰራተኞች ድልድል ተካሂዶ ምደባ እስከሚካሄድ ድረስ ከጥር  21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት ሦስት ወራት ታግዶ የቆየው የመሬት አገልግሎት፣ የዜጎችን መብት የጣሰ እንደነበር በመናገር  ተገልጋዮች ሲያማርሩ ቆይተዋል።

አስተዳደሩ እንደገለጸው አጠቃላይ የሰራተኛ ድልድሉ በመጠናቀቁ ከቀን ከመጋቢት 23 ቀን2016 ዓ.ም ጀምሮ የመሬት አገልግሎት የተጀመረ መሆኑን አስታውቋል።

Читать полностью…

EthioTube

ከ8ሺህ በላይ የሆኑ የብልፅግና ፓርቲ አባላት  ተባረዋል ተባለ፡፡

በዘንድሮው የበጀት ዓመት በስድስት ወር የስራ አፈፃፀም ላይ  በተደረገ ግምገማ ከ8 ሺህ በላይ የብልፅግና ፓርቲ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)  ይህን የገለፁት በትላንትናው  ዕለት ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤ከፓርቲዎች በብልሹ አሰራር ዙሪያ ለተነሳላቸው ጥያቄ  ምላሽ በሰጡበት ወቅት ነው፡፡

ከ8 ሺህ በላይ የሚሆኑት የብልፅግና ፓርቲ አባላት  እንደ ስራቸው አስተዳደራዊ እርምጃ ከመውሰድ በተጨማሪ እስከ ማባረር የደሰረ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡መጋቢት 2015 ዓ.ም ፓርቲው ባካሄደው ጉባዔ ላይ የፓርቲው ፕሬዝዳንት ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ፤ ፓርቲው በኢትዮጵያ ታሪክ ከዚህ በፊት ከነበሩ ፓርቲዎችና ድርጅቶች በቁጥርም፥ በአደረጃጀትም፥ በሀሳብም የተለየ ፓርቲ መሆኑንም መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡

በወቅቱ  ፓርቲው በመላው ሀገሪቱ ከ11 ሚሊየን በላይ አባላት እንዳው በመግለፅ፤ ሁሉም ብሄሮች በሚገባቸው ልክ የተወከሉበት ፓርቲ መሆኑንም አስታውቀዋል።ገዢው ፓርቲ ብልፅግና ባለስልጣናት  መካከል የክህሎት፣ የመቀራረብና  የአስተሳሰብ አንድነት ያመጣል የተባለ ስልጠናና ውይይት በሁሉም ክልሎች ማካሄዱ የሚታወስ ነው፡፡

Facebook.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram.com/EthioTube
/channel/ethiotube

Читать полностью…

EthioTube

ዛሬ የመጨረሻ ቀን ነው ‼

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያላግባብ ከ121 ሺህ እስከ 95 ሺህ ብር ወስደው ያልመለሱ ደንበኞቹን ማንነት የሚገልጡ የፎቶግራፍና ሌሎች መረጃዎችን ትናንት ምሽት ለሕዝብ ይፋ አድርጓል።

ባንኩ እስከ ትናንት ድረስ ያላግባብ ገንዘቡን የመለሱ ደንበኞቹ ብዛት ከ10 ሺህ በላይ መድረሱን አስታውቋል።ባንኩ ለደንበኞቹ የሰጠው የገንዘብ መመለሻ ተጨማሪ ቀነ ገደብ ዛሬ ያበቃል።

Facebook.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram.com/EthioTube
/channel/ethiotube

Читать полностью…

EthioTube

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) እና ብልፅግና ፓርቲ በፕሪቶሪያ ውል መሰረት ፓለቲካዊ ውይይት ለመጀመር ተስማሙ

ህወሓት በይፋዊ የማህበራዊ የትስስር ገፁ  ባሰራጨው መረጃ ፥ በብልፅግና ምክትል ፕረዚደንት አቶ አደም ፋራህ የሚመራ ቡድን  ዛሬ መጋቢት 24/2017 ዓ.ም በመቐለ  ከህወሓት ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጋር ተወያይቷል።

የሁለቱም ፓለቲካዊ ፓርቲዎች የፓለቲካ ውይይት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ቀደም ብሎ መጀመር እንደነበረበት በመተማመን በአጭር ጊዜ ውስጥ ውይይት እንዲጀምሩ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ህወሓት ገልጿል።

Читать полностью…

EthioTube

የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገ/መስቀል፣ የሩሲያ ባሕር ኃይል ምክትል ዋና አዛዥ አድሚራል ቭላድሚር ካሳቶኖቭ የመሩት ከፍተኛ ልዑካን ቡድን ትናንት ምጽዋ መግባቱን የኤርትራ መንግሥት አስታውቀዋል።

የማነ፣ ልዑካን ቡድኑን የኤርትራ ጦር ኃይሎች ኤታማዦር ሹም ጀኔራል ፊሊጶስ ወልደማርያም እንደተቀበሉት ገልጸዋል። የሩሲያ ባሕር ኃይል አንዲት ወታደራዊ መርከብ ከኤርትራ ባሕር ኃይል ጋር ለዘጠኝ ቀናት የሚቆይ ልምምድ በቀይ ባሕር ላይ ለማድረግ ባለፈው ሳምንት ዓርብ ምጽዋ መድረሷ ይታወሳል።

Читать полностью…

EthioTube

12 ማዳበሪያ አደገኛ ዕፅ በማዘዋወር ጥፋተኛ የተባለ የመንገዶች ባለስልጣን የመኪና ሹፌር በጽኑ እስራት ተቀጣ

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የመኪና ሹፌር  የሆነው ታምሩ ፍቅሩ የተባለ ተከሳሽ በታርጋ ቁጥር ኮድ 4 ኢት 15731 መኪና 12 ማዳበሪያ  አደገኛ ዕፅ ሲያዘዋውር ተይዞ ጥፋተኛ መባሉን የፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።

ተከሳሹ በሸገር ከተማ ልዩ ቦታው በተለምዶ ዓለምገና ተብሎ በሚጠራው የመኖሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ 12 ማዳበሪያ 280 ሺህ 50 ግራም የሚመዝን ካናቢስ የተባለ አደገኛ ዕፅ በተሸከርካሪ ውስጥ ይዞ መገኘቱ ተጠቁሟል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የድንበር ተሻጋሪ ወንጀል ችሎት አደገኛ ዕጾችን በማዘዋወር ወንጀል ተከሳሹን ያርማል በማለት በ12 ዓመት ጽኑ እስራት እና በ40 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ወስኗል።

Читать полностью…

EthioTube

ከጠ/ሚኒስትሩ ጋር በዉይይቱ ያልተሳተፍነዉ “የለበጣ እና ከፎቶ ባለፈ ምንም ቁም ነገር እንደማያመጣ ሰለተረዳን ነዉ” ሲሉ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ተናገሩ

የአስራ አንድ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጥምረት (ሲኦፒ) ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጋር ለመወያየት የቀረበለትን ጥሪ ውድቅ ያደረገው መንግሥት በአገሪቱ አሳሳቢ ጉዳዮች ላይ የመነጋገር ፍላጎት ስለሌለው መሆኑን ዳጉ ጆርናል መዘገቡ አይዘነጋም።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት ከተፎካካሪ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ሰኞ መጋቢት 23/2016 ዓ.ም. ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ የጥምረቱ አባላት ግን ሳይሳተፉም ቀርተዋል።

የጥምረቱ አባላት በውይይቱ ላለመገኘት የወሰኑት “መንግሥት አሳሳቢ በሆኑ አገራዊ ጉዳዮች ላይ መነጋገር ስለማይፈልግ” መሆኑን የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ፕሮፌሰር መረራ እንዳሉት ውይይቱ “ዝም ብሎ የለበጣ እና ከፎቶ ባለፈ ምንም ቁም ነገር እንደማያመጣ ሰለተረዳን እና ተቃዋሚዎችን አናገርኩ የሚል የይምሰል በመሆኑ” ላለመሳተፋቸው ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ባለፉት ስድስት ዓመታት በአገር ውስጥ እንዲሁም ኔዘርላንድ እና ደቡብ አፍሪካን ጨምሮ በውጭ አገራት ከእሳቸውም እንዲሁም ከተወካዮቻቸው ጋር ድርድር ቢደረግም ፍሬ አላፈራም ብለዋል ፕሮፌሰሩ።

ከገዢው ፓርቲ ጋር በተደረጉ በርካታ ንግግሮችም የተረዱት መንግሥት “መሠረታዊ እና አሳሳቢ በሆኑ ጉዳዮች ላይ መደራደርም ሆነ መነጋገር አይፈልግም” ሲሉም ፕሮፌሰር መረራ አጽንኦት ይሰጣሉ።

እሳቸው መሠረታዊ ብለው ከሚያነሷቸው ጉዳዮች አንዱ ኦሮሚያ እና አማራ ክልሎችን ጨምሮ በአገሪቱ ለበርካታ ሰዎች እልቂት የእየሆኑ ያሉትን ግጭቶች እና ጦርነቶችን ነው። እነዚህ ጦርነቶች በሰላማዊ መንገድ እንዴት ይቋጭ? በሚለው ጉዳይ ላይ “መንግሥት መነጋገርም ሆነ ወደ መደራደር አይሄድም” ይላሉ።

በአገሪቱ ውስጥ የሰፈነው “የመገደደል ፖለቲካን ማቆም” ዋነኛ እና መሠረታዊ ጉዳይም እንደሆነም ነው የሚገልጹት።

ሌላኛው ፖለቲከኛው የሚጠቅሱት ጉዳይ አገሪቱ ወደ ዲሞክራሲ የምታደርገው ሽግግር መክሸፉን በመጥቀስ፤ ይህንን የአገሪቱ የዲሞክራሲ የመቀልበስ ሂደት ላይም ገዢው ፓርቲ መወያየት አይፈልግም ይላሉ።

“መነጋገር ደግሞ ውል እና ማሰሪያ ያለው ነገር ይዞ መሠረታዊ ነገሮችን አንስተን ሰጥቶ በመቀበል ፖለቲካ ችግሮችን መፍታት ካልቻልን ንግግሩ ብዙም ትርፍ ስለሌለው ሕዝቡንም ላለማሳሳት ያደረግነው ነው” ብለዋል።

አገሪቷን እየናጧት ያሉ ግጭቶችንም ሆነ ሌሎች መሠረታዊ ያሏቸውን ጉዳዮች ፊት ለፊት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በማንሳት መነጋገር አይቻልም ነበር ወይ? በሚል ቢቢሲ ፕሮፌሰር መረራን ጠይቋቸዋል።

እሳቸውም ከዚህ በፊት የተደረጉ በርካታ ንግግሮች ፋይዳ እንዳልነበራቸው እና ወደየትም ያልተራመዱ መሆናቸውን በመጥቀስ ምላሽ ሰጥተዋል።

“ጦርነቱን ማስቆም አልተቻለም። መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ ካልተወያየን ከፎቶ ባለፈ ምንም ቁም ነገር ስለማያመጣ መሳተፍን አልመረጥንም እንጂ መነጋገርንም ሆነ መደራደርን ጠልተን አይደለም” ሲሉም መልሰዋል።

አክለውም “በእነዚህ ንግግሮች የመጣ ለውጥ፣ የምናስተካክለው ነገር ወይም የምንፈይደው ነገር ስለሌለ ነው። ሕዝቡን በማይሆን መንገድ እየተነጋገርን ነው፤ በውይይይ እየተፈታ ነው የሚል አጉል ተስፋ ላለመስጠት እኛ የመሰለንንን እርምጃ ወስደናል” ብለዋል።

ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የነበረውን ውይይት ግብዣ ላለመቀበል የመወሰናቸው እርምጃ ዋጋ የሚያስከፍላችሁ አይመስላችሁም ወይ በሚልም ቢቢሲ የጠየቃቸው መረራ “ከዚህ በላይ ዋጋ ከፍለናል” ብለዋል።

ኢትዮጵያ ባለፈው ባደረገችው ምርጫ የእሳቸው ፓርቲ እና ኦነግ “ተገፍተው” ከምርጫው እንደወጡ በመጥቀስ የከፈሉት ዋጋ መሆኑን አንስተዋል።

ኦፌኮ ብቻ ሳይሆን በምርጫው ተሳታፊ የነበረው አብን አንዳንድ አመራሮች ለእስር መዳረጋቸውንም ያነሱት ፕሮፌሰር መረራ “ሌሎቹም አልተጠቀሙም” ይላሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ያደረጉት የአንድ ቀን ውይይት ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ተግባራት ላይ አስተያየቶችን እና ትችቶችን ለማሰባሰብ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

መንግሥት እያከናወናቸው ያሉ ልማቶችን በተመለከተ ለተቃዋሚ ፓርቲዎቹ ገለጻ መደረጉም ተጠቅሷል።

መረራ በበኩላቸው በእነዚህ ልማቶች ላይ ጥያቄ በማንሳትም “የሚለማው ሕዝብ ነው መሬት አይደለም። ይሄንን ገዢው ፓርቲ እንዲረዳ ካልፈለገ? ምን ማድረግ ይቻላል?” ሲሉም ይጠይቃሉ።

ሁለቱ ሰፊ የኢትዮጵያ ክልሎች የድሮኖችን ጥቃት ጨምሮ ሰፊ እልቂት እና ጦርነት እያስተናገዱ እንደሆነም የሚያነሱት መረራ፤ እነዚህን እልቂቶች “ወደ ጎን ትቶ ይሄ ህንጻ ተሠራ፣ መንገድ ተሠራ በማለት ያለውን የሕዝብ ትግል ዝቅ ማድረግ ተገቢ አይደለም” ብለዋል።

አክለውም “በግልጽ ለመንግሥት፣ ለገዢው ፓርቲም ሆነ ለሕዝቡ እያልን ያለው እየተካሄደ ያለው ጨዋታ የትም አያደርስም። ኳሱ ያለው በገዢው ፓርቲ ነው እኛ ጋር አይደለም” ብለዋል።

በዚህ ውይይት ላይ ለፖሊሲ ግብዓት አስፈላጊ የሆኑ እርማቶች እና ማስተካከያዎች ተለይተው ወደፊት ለመቀጠል በሚያስፈልጉ የትብብር ዓይነቶች ላይ ምክክር መካሄዱንም የጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።

ከሁለት ዓመታት ገደማ በፊት የተመሠረተው የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥምረት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ፣ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር፣ የኦጋዴን የነጻነት ግንባር፣ ህብር ኢትዮጵያ፣ አረና ትግራይ ፓርቲ፣ የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ የአፋር ሕዝቦች ፓርቲን የያዘ ሲሆን ከዚህ ቀደምም አንዳንድ የመንግሥት ውሳኔዎችን በመቃወም ይታወቃል።

በአማራ ክልል እንዲሁም በሌላው የኢትዮጵያ አካባቢዎች እንደ አስፈላጊነቱ ተግባራዊ ይሆናል የተባለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መራዘም ተቃውሞም መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።

Facebook.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram.com/EthioTube
/channel/ethiotube

Читать полностью…

EthioTube

ማንችስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን ነጥብ ማስጣሉን ተከትሎ አርሰናል መሪነቱን ተረክቧል። የዋንጫው ትንቅንቅ በማን አሸናፊነት የሚጠናቀቅ ይመስላችኋል?

#PremierLeague #ManUnited #Liverpool

Читать полностью…

EthioTube

31 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በማላዊ ታግተው ለማስለቀቂያ ከቤተሰቦቻቸው 1ሺ ዶላር መጠየቃቸው ተጠቆመ

የማላዊ ባለስልጣናት በህገወጥ መንገድ ወደ  ሀገሪቱ የገቡ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በህገወጥ አዘዋዋሪዎች ታግተው ለማስለቀቂያ በነፍስ ወከፍ 1ሺ ዶላር እየተጠየቀባቸው እንደነበር አረጋግጫለሁ ማለቱን ኒያሳ ታይምስ የተሰኘው የሀገሪቱ የዜና ምንጭ ዘግቧል።

የሀገሪቱ የደህንነት ባለስልጣን ኬን ዚክሃሌ ንጎማ በሊሎንግዌ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አህመድ ሙሀመድ እና ዲሞራህ የተባሉ ኢትዮጵያውያን ጥንዶች 31 ኢትዮጵያውያን አግተው ኢትዮጵያ ካሉ ቤተሰቦቻቸው ለማስለቀቂያ 1ሺ ዶላር እየጠየቁ እንደነበር መረጋገጡን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች ወደ ማላዊ ለመግባት 200 ዶላር እንደሚከፍሉ ባለስልጣኑ የገለፁ ሲሆን ህገወጥ የሰው አዘዋዋሪዎቹ ጥንዶች ለረዥም ጊዜ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ንግድ ተሰማርተው እንደቆዩ አብራርተዋል። ይህ ድርጊታቸው ከታወቀ በኋላ ከሀገሪቱ እንዲባረሩ ሲደረግ ኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች ስላሉበት ሁኔታ የተጠቀሰ ነገር የለም።

Читать полностью…

EthioTube

በአሶሳ ከተማ በትዳር አጋሩ ላይ ከባድ የመግደል ሙከራ የፈጸመው የፖሊስ አባል በእስራት ተቀጣ ተቀጣ

በአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ በትዳር አጋሩ ላይ በድምፅ አልባ መሳሪያ ከባድ የመግደል ሙከራ ወንጀል የፈጸመው የፖሊስ አባል በፅኑ እስራት መቀጣቱ ተነግሯል ።

ተከሳሽ ዋና ሳጅን ማስረሻ ፈንታዬ  በከተማ አስተዳደሩ ወረዳ አንድ  በተለምዶ ጤና ቢሮ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ነዋሪ ሲሆን ጥር 6 ቀን 2016 ዓ.ም ሆን ብሎ በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ ከባለቤቱ ጋር በነበረው አለመግባባት በመነሳሳት እና ቂም በመያዝ ወንጀሉን መፈፀሙ ተገልጿል ።

በዚህም ተከሳሽ በያዘው ድምፅ አልባ መሳሪያ ጩቤ ጭካኔ እና ነውረኝነት በተሞላበት ሁኔታ የግል ተበዳይን በጀርባዋ ላይ ስድስት ጊዜ ፣ ግንባሯ ላይ አንድ ጊዜ በመውጋት እንዲሁም በሳንባዋ ላይ በስለት ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተጠቁሟል ።

ሆኖም መረጃው የደረሰው የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ተከሳሹን በቁጥጥር ስር አውሎ  የወንጀል ምርመራ በማጣራት መዝገቡን ለዓቃቤ ህግ መላኩን በከተማ አስተዳደሩ የወረዳ አንድ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ሃላፊ የሆኑት ምክትል ኮማንደር በላቸው ፈረደ ከብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል ።

የምርመራ መዝገቡ የደረሰው የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ዓቃቤ ህግ በሰውና በህክምና ማስረጃ አስደግፎ ተከሳሽ በፈጸመው ከባድ የሰው መግደል ሙከራ ወንጀል ክስ መስርቶበታል። በዚህ መሠረት የክስ መዝገቡን ሲመለከት የቆየው የወረዳው ፍርድ ቤት ተከሳሽን ጥፋተኛ ሲል ብይን ሰጥቷል ።

ፍርድ ቤቱ መጋቢት 23 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት በ10 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ዉሳኔ ማሳለፉን ምክትል ኮማንደር በላቸው ፈረደ ጨምረዉ ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል ።
     

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያ፦ እለተ ሀሙስ የኢት ዜና - መጋቢት 26 ፣ 2016 | #Ethiopia: Et News : አንኳር - Ethiopian Daily News Digest - April 4, 2024
👉ሶማሊያ የኢትዮጵያን አንባሳደር አባረረች
👉ዲጂታል መታወቂያ የሌለው ነጋዴ አዲስ ህግ
👉በአማራ ክልል እና በኦሮሚያ ክልል ያልረገው ጦርነት

ሌሎችንም መረጃዎች ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ 👇
https://youtu.be/weYzrMg3_6k

Читать полностью…

EthioTube

የአሳማ ኩላሊት የተለገሰው ግለሰብ ከሆስፒታል አገግሞ መውጣቱ ተሰማ

ለመጀመሪያ ጊዜ የአሳማ ኩላሊት ንቅለ ተከላ የተደረገለት ግለሰብ ከሆስፒታል አገግሞ መውጣቱ ተሰምቷል፡፡

የኩላሊት ህመም በዓለም አቀፍ ደረጃ የብዙዎችን ሕልም ያጨለመና በርካቶችን ለህልፈት የዳረገ እና እየዳረገ የሚገኝ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

ኩላሊት ሥራውን በአግባቡ ለመከወን ሲሰንፍ የኩላሊት ህመም ተከስቷል ይባላል፤ ህመሙ በጊዜ ከተደረሰበት በንቅለ ተከላ የሚታከም ቢሆንም ኩላሊት ማግኘት ግን ፈታኝ ጉዳይ ነው፡፡

አሁን ላይ በአሜሪካ ማሳቹሴትስ አጠቃላይ ሆስፒታል የተሰማው አዲስ ሕክምና የብዙዎችን ጭንቀት ወደ እፎይታ የቀየረና ተስፋ ሰጪ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

በሆስፒታሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓሳማን ኩላሊት ለሰው ልጅ በንቅለ ተካላ በመተካት ውጤታማ ሕክምና ማድረግ መቻሉ ተሰምቷል፡፡
የ62 ዓመቱ የዕድሜ ባለጸጋ ሪቻርድ ስሌይማን የኩላሊት ህመም እንዳለባቸውና በአፋጣኝ የኩላሊት ንቅለተከላ ማድረግ እንዳለባቸው ተነግሯቸው ዲያሊሲስ ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡

ሆኖም ግለሰቡ የዓሳማ አካል ከአካላቸው ተስማምቶ ወደጤናቸው እንደሚመለሱ እርግጠኛ መሆን አልቻሉም ነበር ፤ይሁን እንጂ ሕክምናው በባለሙያዎች ታግዝ እውን ሆኗል፡፡
ከአሁን በፊት ተሞክሮ ያልተሳካው የዓሳማ ኩላሊት ንቅለ-ተከላ ጊዜው ደርሶ በዘርፉ ሊቆች ታግዞ የግለሰቡን ሕይዎት ማትረፉም በብዙዎች ዘንድ አግራሞትን ጭሯል፡፡

የንቅለ-ተከላ ሂደቱ አራት ሰዓታት እንደፈጀ የተናገሩት ሃኪሞች ፥ በአሁኑ ወቅት የዓሳማው ኩላሊት ከግለሰቡ ተዋህዶ በአግባቡ እየሰራ መሆኑን በማረጋገጥ ከሆስፒታል እንዲወጣ መደረጉን ገልጸዋል፡፡

ስሌይማን በበኩላቸው ፥ ህክምናው ተሳክቶ ወደቤቴ መሄዴ የሕይወቴ ትልቁ ደስታ ነው ማለታቸውን የዘገበው ቢቢሲ ነው፡፡
ታካሚውከአሁን በፊት ያደረጉት ንቅለተከላ ከሰው በተለገሳቸው ኩላሊት እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ፥ ሆኖም ትንሽ ቆይቶ መስራት ማቆሙ ተነግሯል፡፡

ይሁን እንጂ ሕክምናው ሃኪሞች ባነሱት የዓሳማ ኩላሊት ንቅለ ተከላ ሙከራ መሳካቱ ነው የተነገረው፡፡

የዓሳማ ኩላሊት ንቅለ ተከላ ሕክምነው “እኔን ለመርዳት ብቻ ሳይሆን በሕይወት ለመትረፍ ንቅለ ተከላ ለሚያስፈልጋቸው በሺዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች ተስፋ የሚሰጥ መንገድ ሆኖ አይቸዋለሁ” ሲሉም ገልጸዋል።

ምንጭ፦ FBC

Читать полностью…

EthioTube

በቀጣይ ዓመት ብሔራዊ መታወቂያ የሌላቸው ነጋዴዎች የንግድ ፈቃድና ምዝገባ አገልግሎት አያገኙም ተባለ

በሚቀጥለው ዓመት የንግድ ፈቃድና ምዝገባ አገልግሎት ለማግኘት ብሔራዊ መታወቂያ ያስፈልጋል በማለት በቀጣይ ዓመት ብሔራዊ መታወቂያ የሌላቸው ነጋዴዎች አገልግሎት ማግኘት እንደማይችሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

የንግድ ፈቃድና ምዝገባ አገልግሎት ማግኘት የሚፈልጉ ደንበኞች በአካል መገኘት ሳይጠበቅባቸው በኦንላይን አገልግሎት እያገኙ ነው ሲባል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚሰጣቸው አገልግሎቶች ከሌሎች ተቋማት ጋር የሚያገናኘው በመሆኑ ከተቋማቱ ጋር ሲስተም የማናበብ ስራ በፋይዳ መለያ የሚሰራ መሆኑ ተጠቁሟል።

ስለዚህ የንግዱ ማህበረሰብ ከ2017 በፊት ብሔራዊ መታወቂያ በማውጣት ራሱን ለነገሮች ዝግጁ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉ በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የላይሰንሲንግ እና ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጅራታ ነመራ ተናግረዋል።

Facebook.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram.com/EthioTube
/channel/ethiotube

Читать полностью…

EthioTube

በመዲናዋ በመፍረስ ላይ ያሉ ቤቶች "በቅርስነት ለመመዝገብ የሚያስችል መስፈርት ያላሟሉ" ናቸው - የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ከአዲስ አበባ ኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጉዳዮችን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ በመዲናዋ በኮሪደር ልማት ስራ ምክንያት የሚፈርሱ ቤቶች "በቅርስነት ለመመዝገብ የሚያስችል መስፈርት የሚያሟሉ ባለመሆናቸው" ነው ብለዋል።

ከዚህ ቀደም በመዲናዋ የቅርስ መስፈርቶችን ያላሟሉ ሁሉ የተመዘገቡ መኖራቸውን አስታውሰው፤ በተዘጋጀው መስፈርት መሰረት በአዲስ መልክ የቅርስ ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚሁ መሰረት ከዚህ በፊት የተመዘገቡ በቅርስነት የሚቀጥሉ ሲኖሩ በመመሪያው መሰረት መስፈርቱን የማያሟሉ ደግሞ የማይቀጥሉ መሆናቸውን ገልፀዋል። ከቀናት በፊት ባለስልጣኑ በአዲስ አበባ የመልሶ ግንባታና ኮሪደር ልማት የቅርስ መስፈርት የማያሟሉ ቤቶችንና አካባቢዎችን በመልሶ ማልማት የቀደመ ስያሜና አገልግሎታቸው እንዲቀጥል እንደሚደረግ ማስታወቁን ፕሬስ ድርጅት መዘገቡ ይታወሳል።

ቤቶቹን በቅርስነት ለመመዝገብ ያላቸው ታሪክ፣ አሁን ያሉበት ውጫዊ እና ውስጣዊ ገፅታ፣ እድሜያቸው፣ አርክቴክቸርን ጨምሮ በርካታ መስፈርቶች መቀመጣቸውን ገልጸዋል። በተቀመጡት መመዘኛዎች መሰረት ከ50 በመቶ በላይ ውጤት ያመጣ በቅርስነት እንደሚመዘገብ እና በአንጻሩ ከ50 በታች የሆነ ቤት ቅርስ ተብሎ ሊመዘገብ እንደማይችል ጠቁመዋል።

ለየሀገር ከፍተኛ ትርጉም ያላቸውን ቅርሶችን መጠበቅና መንከባከብ ላይ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን የባለሙያዎች ቡድን በማዋቀር በኮሪደር ልማቱ የሚፈርሱ ቤቶች ላይ የክትትልና የቁጥጥር ስራ እየሰራ ይገኛል ማለታቸውን ተገልጿል።

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያ፦ እለተ ረቡዕ የኢት ዜና - መጋቢት 25 ፣ 2016 | #Ethiopia: Et News : አንኳር - Ethiopian Daily News Digest - April 3, 2024

👉ሕወሓት ዕውቅናው እንዲመለስለት ያቀረበውን ጥያቄ👉በመሬት አገልግሎት ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ ተነሳ
👉ከ8ሺህ በላይ የሆኑ የብልፅግና ፓርቲ አባላት ተባረዋል

ሌሎችንም መረጃዎች ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ 👇
https://youtu.be/ZkqKQfdsqx8

Читать полностью…

EthioTube

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የሞተር ሳይክል እና የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን የሚወስን አዲስ መመሪያ መዘጋጀቱ ተነገረ።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ በከተማዋ የሞተር ሳይክል ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ አካላትን በአሰራርና በተደራጀ ሁኔታ ለመምራት የሞተር ሳይክል እና የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን ለመወሰን አዲስ መመሪያ ተግባራዊ ማድረጉን ተናግሯል፡፡

በመመሪያውም ከአሽከርካሪው ውጪ ሌላ ሰው መጫን እንደማይቻልና ለእቃ ማመላለሻ ብቻ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ፣ ከኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል ውጪ አዲስ የአገልግሎት ፍቃድ እንደማይሰጥ፣ ከ250 አባላት ጀምሮ በማህበር በመደራጀት ፍቃድ እንደሚሰጥ ተጠቅሷል፡፡

አሁን በስራ ላይ የሚገኙ የሞተር ሳይክሎች ቢሮው በሚያስቀምጠው የጊዜ ገደብ መነሻነት ወደ ኤሌክትሪክ የሞተር ሳይክል መለወጥ እንደሚገባ ቢሮው አሳስቧል፡፡

ቢሮው ባወጣው መመሪያ መሰረት አገልግሎቱን የማይሰጡ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች በመመሪያው መሰረት እንደ ጥፋቱ እርከን ቅጣት እንደሚጣልባቸውም አሳስቧል፡፡

አዲሱ መመሪያ ወደ ተግባር እንዲገባ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች እንዲሁም የሚመለከታችው ሁሉ አስፈላጊውን ትብብር እንድታደርጉ ሲል የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ጠይቋል፡፡

Читать полностью…

EthioTube

ደራርቱ ቱሉ ከጃፓን መንግስት የኒሻን ሽልማት ተረከበች

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ከጃፓን መንግስት የተበረከተላትን የወርቅ ጨረር ያለው የኒሻን ሽልማት ተረከበች።

ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ በስፖርት ዲፕሎማሲ ላበረከተችው አስተዋፅኦ ቀደም ሲል ከጃፓን መንግስት የክብር ኒሻን ሽልማት እንደተበረከተላት ይታወሳል።

በጃፓን እና በኢትዮጵያ መካከል ካበረከተችው የስፖርት ዲፕሎማሲ በተጨማሪ ለአትሌቲክስ ዕድገት እና ለሀገር ሰላም ላበረከተችው አስተዋፅኦም ነው ሽልማቱ የተበረከተላት።

ሽልማቱን ከኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ ሂሮኖሪ መረከቧን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል።

Facebook.com/EthioTube
Twitter.com/EthioTube
Youtube.com/EthioTube
Instagram.com/EthioTube
/channel/ethiotube

Читать полностью…

EthioTube

ኢትዮጵያ፦ እለተ ማክሰኞ የኢት ዜና - መጋቢት 24 ፣ 2016 | #Ethiopia: Et News : አንኳር - Ethiopian Daily News Digest - April 2, 2024

👉መራራ ጉዲና ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን ተቹ

👉የመንገዶች ባለስልጣን ሾፌር አደገኛ እጽ በማዘዋወር ተቀጣ

👉የ 12 አመቷን ህፃን ያገባት የ 63 ዓመቱ ጋናዊ

ሌሎችንም መረጃዎች ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ 👇

https://youtu.be/acJX8nL_pXQ?si=B0RSpELK-sgIU9uR

Читать полностью…

EthioTube

የሐማስ መሪ እስማኤል ሃኒዬ እህት በእስራኤል በቁጥጥር ስር ዋለች

የእስራኤል ፖሊስ በደቡብ እስራኤል ባደረገው ዘመቻ የ57 አመቷን የሃማስ መሪ እስማኤል ሃኒዬህ እህት መያዙን አስታዉቋል።የእስራኤል ዜጋ የሆነችው ሳባህ አብደል ሳላም ሃኒዬህ በቴልሼቫ ከተማ በቁጥጥር ስር የዋለች ሲሆን የእስራኤል የደህንነት ኤጀንሲ ሺን ቤትን ያካተተ የምርመራ ዘመቻን መደረጉን ተከትሎ ነዉ።የሃኒዬ እህት መሆኗን ያረጋገጡት የፖሊስ ቃል አቀባይ "ከሃማስ ኦፕሬተሮች ጋር ግንኙነት በመፍጠር እና ከድርጅቱ ጋር በመገናኘት በእስራኤል ውስጥ የሽብርተኝነት ድርጊቶችን በማነሳሳት እና በመደገፍ ተጠርጥራለች" ብለዋል፡፡

በቤቷ ውስጥ "በእስራኤል መንግስት ላይ ከባድ የደህንነት ጥፋቶችን የሚያሳዩ ሰነዶች፣ ሚዲያዎች፣ ስልኮች፣ ሌሎች ግኝቶች እና ማስረጃዎች"መያዙን ፖሊስ አስታዉቋል፡፡በሌላ በኩል በፈረንሣይኛ ስያሜው ኤም ኤስ ኤፍ የሚታወቀው ድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን፣ በአል አቅሳ ሆስፒታል የሚሠራው ስራ እሁድ ዕለት በእስራኤል የአየር ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ ሥራ ማቆሙን እና ሽፋን እየፈለገ መሆኑን አስታዉቋል፡፡

"ቡድናችን በአቅራቢያው ከፍተኛ ፍንዳታ ሲሰማ ጥቃቱ ማለቁ እስኪረጋገጥ ድረስ በሆስፒታሉ ውስጥ የነበረንን ስራ አቁመናል" ሲሉ አስተባባሪዎቹ  ተናግረዋል።ኤም ኤስ ኤፍ “አፋጣኝ እና ቀጣይነት ያለው” የተኩስ አቁም ጥሪውን በድጋሚ አቅርቧል።በጥቃቱ ቢያንስ አራት ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች 17 ሰዎች ቆስለዋል።

የጋዛ ጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው እስራኤል ወታደሮቿን እና ታንኮችን ከጋዛ አል-ሺፋ የህክምና ኮምፕሌክስ ዉስጥ አውጥታለች ብሏል።ሚኒስቴሩ በደርዘን የሚቆጠሩ አስከሬኖች ከፍርስራሽ ዉስጥ ተገኝተዋል ብሏል፡፡የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ናስር ካናኒ ከአል-ሺፋ ሆስፒታል የተገኙት ምስሎች “አስፈሪ እና አስደንጋጭ ናቸው” ብለዋል።‹‹ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና ተቋማት ኃላፊነታቸውን ይወጡ ይሆን? የታወቁ የሰብአዊ መብት ተከራካሪዎች የዚህን ግልጽ የጦር ወንጀል ስፋት በተመለከተ አለም አቀፍ ምርመራን ይደግፋሉ ወይንስ መራጭ እና አድሎአዊ ባህሪው ይቀጥላል? በማለት የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ በኤክስ ገጻቸዉ ላይ አስፍረዋል፡፡

የእስራኤል ጦር በበኩሉ ከጥቅምት 7 ጥቃት ወዲህ የተገደሉበት ወታደሮች ቁጥር 600 መድረሱን አስታዉቋል፡፡

ዳጉ ጆርናል

Читать полностью…

EthioTube

የተፈጠረው የነዳጅ እጥርት እስከ ነገ ጠዋት ድረስ ይቀረፋል ፦የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት

ከሰሞኑ በአዲስ አበባ ከተማ ረጃጅም የነዳጅ ሰልፎች ማስተዋል የተለመደ ሆኗል።

ይሄንንም ተከትሎ የረጃጅም የነዳጅ ሰልፎች ምክንያት ምን እንደሆነ ለማወቅ ኢቢሲ ሳይበር የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅትን አነጋግሯል፡፡

የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ይስማ አለም ምህረቱ የነዳጅ እጥረት የተፈጠረው ጅቡቲ ላይ የዘነበውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ ድልድይ በመሰበሩ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም ነዳጅ የጫነ አንድ የነዳጅ ቦቴ ተገልብጦ መንገድ መዘጋጋት በማስከተሉ የነዳጅ እጥረት መከሰቱን አስረድተዋል፡፡

Читать полностью…

EthioTube

የ63 ዓመቱ ጋናዊ ቄስ የ12 ዓመት ታዳጊ ማግባታቸው ቁጣ ቀሰቀሰ

ኑሞ ቦርኬቴ ላዌህ ትሱሩ 33ኛ ቅዳሜ ዕለት በተካሄደ የሠርግ ሥነ-ሥርዓት ነው ታዳጊዋን ያገቡት። ምንም እንኳ በርካታ ትችት እየዘነበ ቢሆንም የማሕበረሰብ መሪዎች፤ ሰዎች በባሕል እና ወጋችን አያገባቸውም የሚል ምላሽ እየሰጡ ነው።

በጋና ከ18 ዓመት በታች ጋብቻ መፈፀም ሕጋዊ አይደለም። ምንም እንኳ በሀገሪቱ ያለዕድሜ ጋብቻ እየቀነሰ ቢመጣም አሁንም በአንዳንድ ሥፍራዎች ይህ ሲከናወን ይታያል።

ቅዳሜ ዕለት የነበረውን ፕሮግራም የሚያሳዩ ቪድዮዎች እና ፎቶዎች እንደሚጠቁሙት በርካታ የማሕበረሰብ መሪዎች ታድመዋል።

ቪድዮዎች እና ፎቶዎች ማሕበራዊ ሚድያዎች ላይ በስፋት መሰራጨታቸውን ተከትሎ ጋናዊያን ቁጣቸውን እያሰሙ ነው።

በሥነ-ሥርዓቱ ወቅት አንዲት ጋ በተሰኘው ቋንቋ ንግግር ያሰሙ ሴት፤ ታዳጊዋ ባሏን በሚማርክ መልኩ እንድትለብስ ሲመክሩ ይደመጣሉ።

አክለው የሚስት ተግባራትን ለመከወን እንድትዘጋጅ እና በስጦታ የተሰጣትን ሽቶ ተቀብታ ለባሏ ወሲብ ቀስቃሽ ሆና እንድትገኝ ሲናገሩ ይደመጣሉ።

ይህ ንግግር በጋናዊያን ዘንድ ያለውን ቁጣ እጅግ ያጋለው ሲሆን ጋብቻው እንዲሁ ለወግ ብቻ የተዘጋጀ አይደለም ማለት ነው የሚል ሐሳብ ጭሯል።

ብዙዎች መንግሥት ጋብቻውን እንዲያፈርስ እና ትሱሩን የተባሉትን ቄስ እንዲመረምር ጥያቄ እያቀረቡ ነው።

ታዳጊዋ እና ቄሱ አባል የሆኑበት ኑንጋ የተባለው ጥንታዊ ብሔረሰብ መሪዎች ከተቀረው የጋና ክፍል የቀረበባቸውን ትችት አስተባብለው ትችቱ “ካለማወቅ የመነጨ ነው” ብለዋል። ኒ ቦርቴ ኮፊ ፍራንክዋ 2ተኛ የተባሉ አንድ የማሕበረሰብ መሪ እሑድ ዕለት ታዳጊዋ የቄሱ ሚስት ሆና የምትጫወተው ሚና “ባሕላዊ እና ወጋዊ ብቻ ነው” ብለዋል።

Читать полностью…

EthioTube

ለሀገር ውስጥ የውሃ ትራንስፖርት እንዲያገለግሉ የተገዙት ሁለት ዘመናዊ ጀልባዎች ጅቡቲ ወደብ ደርሰዋል ተባለ

በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ጣና ሐይቅ ላይ ለሀገር ውስጥ የውሃ ትራንስፖርት እንዲያገለግሉ የተገዙት ሁለት ዘመናዊ ጀልባዎች ትላንት ጅቡቲ ወደብ መድረሳቸው ተነግሯል።

ጅቡቲ የደረሱት "ጣና ነሽ ፪" የተሰኘችው የሰው ማጓጓዣና የመዝናኛ መርከብ እንዲሁም ሌላኛዋ መለስተኛ ፈጣን ቃኝ ጀልባ ናቸው። ጣናነሽ ዘመናዊ የሰው ማጓጓዣ እና የመዝናኛ መርከብ ስትሆን 38ሜ እርዝመት እንዳላት እና በአንድ ግዜ 188 ሰዎችን የመጫን አቅም እንዳላት ተጠቁሟል።

Читать полностью…
Subscribe to a channel