ewnetyasarfal | Unsorted

Telegram-канал ewnetyasarfal - እውነት ያሳርፋል You tube

-

የዚህ ቻናል ዋና አላማ ✞✞✞✞ 👉ልክ ባልሆነ መንገድ የተፈቱ ጥቅሶችን በማረም የተጻፈበትን አላማና መልእክቱን ማብራራት። 👉ሙስሊሞች በመጽሀፍ ቅዱስ ላይ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ምላሽ መስጠትና ቁርአንን መመርመር። ምንጮቼ ከተለያዩ መጽሐፍትና ድረ ገጾች። https://youtu.be/20oAilgqH-o @ewnetyasarfal_bot — 1ኛ ጴጥሮስ 3፥15 بطرس 3:15 (العربية)

Subscribe to a channel

እውነት ያሳርፋል You tube

ኢየሱስ አብ ከእኔ ይበልጣል ያለውን በመጥቀስ ኢየሱስ አምላክ አይደለም ብለው ለሚከራከሩ ሁሉ ይድረስ። SHARE አድርጉት። ቻናሉንም SUBSCRIBE አድርጉ። ሙስሊሞች ላይ ብቻ ትኩረት የሚያደርግና ጥያቄዎቻቸው የሚመለሱበት ቻናል ነው

https://youtu.be/sOS8lp9VM6U

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

Share ብታደርጉት ሌሎችንም ትጠቅማላችሁ። ክርስቲያን ይሁን ሙስሊም ሁሉም ጋር። በተለይ ግሩፖች ያላችሁ ግሩፖች ላይ። የምታደርጉት ተባረኩ!!😍

https://youtu.be/UNEJ-IxXqdw

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

የዮሐንስ ራእይ 3፥14 በመጥቀስ ኢየሱስ ተፈጣሪ ነው በማለት ለሚከራከሩ የተሰጠ ማብራሪያ ነው። እናንተም ስሙት ለሌሎችም በሌሎች ግሩፖች ላይ SHARE አድርጉት።
https://youtu.be/tR1-J__61Ao

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

https://youtu.be/WyuJNOC7Y5s

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

የሙስሊሞች የመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴን ወይም የክርክር ዘዴን ሙሉ ለሙሉ የሚገልጽ ቀልድ ነው። ከሙስሊሞች ጋር መወያየት የሚፈልግ ሰው የሚጠቅሱትን አንድ ጥቅስ ይዞ ምእራፉን ሙሉውን ወይም የተወሰነ ክፍል ወደላይና ወደታች ብለው እያነበቡ እንዲያስረዱ ማድረግ ነው። በዚህ መንገድ ስትወያዩ እነሱ ለማምለጥ ብዙ ጥቅሶችን ለመደርደራቸው የማይቀር ነው። እናንተ ግን እነሱ የትም እየኼዱ ርእስ ለማስቀየር ቢሞክሩ ያስጀመራችሁትን ክፍል ሳትጨርሱ ማለፍ የለባችሁም። እናውቃለን ብለው ጥቅስ እስከሰጧችሁ ድረስ የምዕራፉን አውድ ጠብቀው ያብራሩላችሁ። ያኔ ለሚጠይቋችሁ እናንተ ብቻ ሳትሆኑ ልባቸውም መልስ ይሰጣቸዋል። ከዛ እውነቱን የመምረጥና ያለመምረጥ የእነሱ ምርጫ ይሆናል ማለት ነው። ተባረኩ። ይህንን ለሌሎችም Share አድርጉት። ይህ ወንጌል የእግዚአብሔር ወንጌል ነው። ወንጌል ማባበል ሳይሆን እውነትን መግለጥ ነው።

Share ለሌሎች ሁሉም ይስማው።


https://youtu.be/tcz9p4WDbW4

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

በዚህ ክፍል ሙስሊሞችን ጨምሮ በአለም ላይ ያሉ ሰዎች፣ በስጋ የምድር ቆይታቸውን እስኪጨርሱ ድረስ በተሰጣቸው እድል እንዴት ተጠቅመው ይድናሉ የሚለውን የምናይ ይሆናል። በዚህ ውስጥ ቁርአን ስላሴ የሚለውንና ክርስቲያኖች ስላሴ የሚሉት ልዩነት በአጭሩ ታያላችሁ። ከሰማችሁተሰ በኋላ ክርስቲያን ነኝ የሚል ሁሉ Share ያድርገው።🙏

https://youtu.be/zzBcInZ30O8

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

አንድ የሙስሊም መምህር የዮሐንስ ወንጌል 7፥34 ኢየሱስ ሊሰቅሉት ቢፈልጉ እንኳን እንደማያገኙት ይናገራል ብሎ ላቀረበው የተሳሳተ ድምዳሜው የተሰጠ እርማት ነው። ስሙትና Share አድርጉት።

https://youtu.be/__1B6Hoa0FY

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

https://youtu.be/K2ulfif7Oy8

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

አስረኛ፡ ወደ መርከቡ ውስጥ የገቡት እንሰሶች ሁለት ጥንድ ወይንስ ሰባት ጥንድ?

ኖህ በዘፍጥረት 6፥19-20 መሰረት ከእያንዳንዱ ሕይወት ያለው እንሰሳ ሁለት፤ ሁለት ነበር ያመጣ የነበረው ወይንስ በዘፍጥረት 7፥2 መሰረት ንፁህ ከተባሉት እንሰሶች ሰባት ወንድና ሴት እንስሰሶችን ነበር? እንዲሁም ይህን በተመለከተ ዘፍጥረት 7፥8 እና 9 ተመልከቱ፡፡

በድምጽና በምስል ለመስማት መጨረሻ ላይ ያለውን ሊንክ ተጠቀሙ።

(እንዲህ ዓይነቱ ቅራኔ ክፍሉን በተሳሳተ መንገድ ከመጥቀስ የመጣ ችግር ነው፡፡)

ይህ በእርግጥ ለማንሳት በጣም ጥሩ ያልሆነ ጥያቄ ነው፡፡ ሻቢር አላይ በዘፍጥረት 6 ላይ ያለውን ክፍል አሳስቶ መጥቀሱ በጣም ግልፅ ነው፣ በዚያም ላይ ንፁህ የተባሉት እንስሳት በምንም መንገድ አልተጠቀሱም ነገር ግን በሰባተኛው ምዕራፍ ላይ በንፁህና ንፁህ ባልሆኑት እንሰሳዎች መካከል በተለየ ሁኔታ ልዩነት ተደርጓል፡፡ ዘፍጥረት 7፥2፤3፤ “ከንጹሕ እንስሳ ሁሉ ሰባት ሰባት ተባትና እንስት፥ ንጹሕ ካልሆነ እንስሳም ሁለት ሁለት ተባትና እንስት፥ ከሰማይ ወፍ ደግሞ ሰባት ሰባት ተባትና እንስት እያደረግህ በምድር ላይ ለዘር ይቀር ዘንድ ለአንተ ትወስዳለህ።” ይላል፡፡ ሻቢር ታዲያ ሁለት ጥንድ በሚለውና በሰባት ጥንድ መካከል ቅራኔ አለ ለማለት ሲነሳና ጥያቄውን ሲያቀርብ ስለ ምንድነው የክፍሉን ሁለተኛ ክፍል ማለትም ንፁህ ካልሆኑት ሁለት ጥንድ የሚለውን ያልጠቀሰው? በሁለቱ ዘገባዎች መካከል ምንም ቅራኔ የሌለ መሆኑ በጣም ግልጥ ነገር አይደለ? ችግሩ ያለው በጥያቄው በራሱ ላይ ነው፡፡

ሻቢር የራሱን ነጥብ ለማስረዳት የምዕራፍ ሰባትን ሁለት ቁጥሮች ማለትም ቁጥር 8 እና 9 ጠቅሶ ወደ መርከቡ ውስጥ የገቡት ሁለት ጥንዶች ብቻ ናቸው ይላል፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ጥቅሶች ሁለት ጥንድ ብቻ ወደ መርከቡ ገቡ በማለት የሚናገሩት ምንም ነገር የላቸውም፡፡ እነሱ በግልጥ የሚናገሩት ነገር ቢኖር ወደ መርከቡ ውስጥ የገቡት የንፁህ እንሰሶች ጥንዶችና ንፁህ ያልሆኑት እንሰሶች ጥንዶች ናቸው በማለት ብቻ ነው፡፡

ከንፁሆቹ እንሰሳት ሰባት ጥንድ የተፈቀደበት ምክንያት በትክክል ግልፅ ነው፤ እነርሱ ውሃው ከጎደለ በኋላ ለአምልኮው መስዋዕት እንዲቀርቡ አገልግሎት ላይ የሚውሉ ነበሩ (በእርግጥም በዘፍጥረት 8፥20 ላይ በዚያ አገልግሎት ላይ ውለዋል)፡፡ በግልፅ እነዚህ ንፁህ እንሰሳት ከሁለት ጥንድ በላይ ባይኖሩ ኖሮ፣ እነርሱ በመሰዊያው ላይ በመሰዋታቸው ከምድር ላይ ጠፍተው ነበር ማለት ነው፡፡ ነገር ግን ንፁህ ባልሆኑት እንሰሳት ወፎች አንድ ጥንድ ብቻ በቂ ይሆን ነበር ምክንያቱም እነርሱ ለደም መስዋዕት አይፈለጉም ነበርና፡፡

የዩትዩብ ያናሌንም SUBSCRIBE በማድረግ እንዲሁም ይህ መልስ ለሌሎችም እንዲደርስ ግሩፖች ላይ እና ለጓደኞቻችሁ share በማድረግ አግዙኝ።
የዩትዩብ ሊንኬ ይህ ነው።


👇👇👇
https://youtu.be/g0HjsQHflXA

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

እናንተም SUBSCRIBE አድርጉ ሌሎችንም አስደርጉ። ወንጌልን ለሙስሊሞች😍
👇👇👇
https://youtube.com/c/EWNETYASARFAL

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

https://youtu.be/aSz16Nk3IJA

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

ሙስሊሞች ኢየሱስ ነቢይ ብቻ ነው። መጽሐፍ ቅዱስም ነቢይ እንደሆነ ይናገራል ይላሉ። አዎ ኢየሱስ ነቢይ መሆኑን እኛም እናምናለን። ግን ሙስሊሞች ይህንን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ለማንበብና ለመመስከር ለምን ከበዳቸው። አንድም ሙስሊም ይህንን ሲጠቅስ ሰምቼውም አንብቤም አላውቅም።

ኢየሱስ፣ ደቀመዛሙርቱ ከእነሱ ጋር በቆዩበት ጊዜዎች ምን እንደተረዱ ለማወቅ ሁለት ጥያቄ ጠየቃቸው።

1. እንደ እናንተ ቅርቤ ያልሆኑ ሰዎች ስለ እኔ ምን ይላሉ? የሚልና

2. አብራችሁኝ እየኖራችሁ ከእነሱ ይልቅ የምታውቁኝ እናንተ ደሞ እኔን ማን ትሉኛላችሁ? የሚል ሁለት ጥያቄ😱

ከባድ አይመስላችሁም!?😱 አዎ በጣም ከባድ ነው፤ ግን ለማን ከተባለ፣ ቀርበው ለማያውቁት ነው። ቀርበው የማያውቁት ስለሱ የሚገምቱትን ሲናገሩ አንዱ ያሉት ነገር፦ "ከነቢያት አንዱ እንደሆንክ ይናገራሉ (ነቢይ ነህ ይላሉ)" የሚል ነበረ። ታድያ እናንተ ቅርቤ የሆናችሁትስ ማን ትሉኛላችሁ ሲላቸው ጴጥሮስ ተነሳና "#አንተ_ክርስቶስ_የህያው_እግዚአብሔር_ልጅ ነህ" አለ።😱

ታድያ ያደነቀውና ይህንን የገለጠልህ የሰማይ አባቴ ነው በማለት የተናገረውም ለጴጥሮስ ንግግር እንጂ በሩቅ ያሉት ስለሚገምቱት አልነበረም።

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ለእነዚህ ነቢይ ነው ብለው ለሚያምኑት ሲነግራቸው ግን "እራሱን ከፍ አድርጎ አምላክ ነኝ እያለ አምላክን ይሳደባል" እያሉ ይሳደቡና በድንጋይ ወግረው ሊገሉት ይነሱ ነበር።

በዚህ ዘመን ያለውም እውነታ ይሄ ነው። በሩቅ ላሉት ሙስሊሞችና የእነሱን መሳይ እምነት ላላቸው፣ ኢየሱስ ነቢይ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው። ምክንያቱም ቀርበው አያውቁትም ለመቅረብም ዝግጁ አይደሉም። እነዚህ ሰዎች በኃጢአታቸው ይሞታሉ። ልባቸው ቅን የሆኑት ግን ይህንን ጌታና አዳኝ ይተዋወቁትና ያርፋሉ። ምክንያቱም እውነትን የምታውቅ ነፍስ ታርፋለች። እውነት ደሞ ኢየሱስ ነው። ለእኔ ግን ኢየሱስ ነቢይ ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር ልጅ ነው። እስኪ አንብቡትና ለሌሎች ደሞ እናንተ Share አድርጉት። ለእናንተ ኢየሱስ ማን ነው?

የበለጠ ለሙስሊሞች ጥያቄ መልስ ለማግኘትና ለመማር ይህንን ሊንክ ተጭናችሁ ቻናሉን subscribe አድርጉና የደውል ምልክቱን አብሩት።

https://youtu.be/Xb8OlsNIhSg

ማቴዎስ 16
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፦ ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ።
¹⁴ እነርሱም፦ አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም #ከነቢያት_አንዱ ነው ይላሉ አሉት።
¹⁵ እርሱም፦ እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።
¹⁶ ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፦ #አንተ_ክርስቶስ_የሕያው_እግዚአብሔር_ልጅ ነህ አለ።
¹⁷ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ።

ይህንንም ጨምራችሁ አንብቡት።

ዮሐንስ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁴ አይሁድም እርሱን ከበው፦ እስከ መቼ ድረስ በጥርጣሪ ታቆየናለህ? አንተ ክርስቶስ እንደ ሆንህ #ገልጠህ_ንገረን አሉት።
²⁵ ኢየሱስም መለሰላቸው፥ እንዲህ ሲል፦ #ነገርኋችሁ_አታምኑምም እኔ በአባቴ ስም የማደርገው ሥራ ይህ ስለ እኔ ይመሰክራል፤


²⁹ የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ ከአባቴም እጅ ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም።
³⁰ እኔና አብ አንድ ነን።
³¹ አይሁድ ሊወግሩት ደግመው ድንጋይ አነሡ።
³² ኢየሱስ፦ ከአባቴ ብዙ መልካም ሥራ አሳየኋችሁ፤ ከእነርሱ ስለ ማናቸው ሥራ ትወግሩኛላችሁ? ብሎ መለሰላቸው።
³³ አይሁድም፦ ስለ መልካም ሥራ አንወግርህም፤ ስለ ስድብ፤ አንተም ሰው ስትሆን ራስህን አምላክ ስለ ማድረግህ ነው እንጂ ብለው መለሱለት።


³⁶ #የእግዚአብሔር_ልጅ_ነኝ ስላልሁ እናንተ አብ የቀደሰውን ወደ ዓለምም የላከውን፦ ትሳደባለህ ትሉታላችሁን?
³⁷ እኔ የአባቴን ሥራ ባላደርግ አትመኑኝ፤
³⁸ ባደርገው ግን፥ እኔን ስንኳ ባታምኑ አብ በእኔ እንደ ሆነ እኔም በአብ እንደ ሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ሥራውን እመኑ።
³⁹ እንግዲህ ደግመው ሊይዙት ፈለጉ፤ ከእጃቸውም ወጣ።

እንደተጠቀማችሁ ተስፋ አደርጋለው። SHARE ማድረግ እንዳይረሳ😍👍
ተባረኩ!!

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

የዚህ ቻናል አላማ ጥሩ ነው ብላችሁ ያመናችሁ ሁሉ SUBSCRIBE በማድረግና Like በማድረግ አግዙኝ። ተባረኩ!!😍🙏

ይህንን ሊንክ በመጠቀም ወደ ቻናሉ በቀጥታ መገሰባት ትችላላችሁ።
👇👇👇
https://youtu.be/8n4E7ioABDI

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

ኢየሱስ ራሱን ማዳን እየቻለ፣ በመስቀል ላይ እጆቹና እግሮቹ ተቸንክረው ሲዘባበቱበት ታገሰ።

ማቴዎስ 27
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴⁰ ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራው፥ ራስህን አድን፤ የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ ከመስቀል ውረድ አሉት።
⁴¹ እንዲሁም ደግሞ የካህናት አለቆች ከጻፎችና ከሽማግሎች ጋር እየዘበቱበት እንዲህ አሉ።
⁴² ሌሎችን አዳነ፥ ራሱን ሊያድን አይችልም፤ የእስራኤል ንጉሥ ከሆነ፥ አሁን ከመስቀል ይውረድ እኛም እናምንበታለን።
⁴³ በእግዚአብሔር ታምኖአል፤ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎአልና ከወደደውስ አሁን ያድነው።
⁴⁴ ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዶች ደግሞ ያንኑ እያሉ ይነቅፉት ነበር።

ግን ለምን ታገሰ?

የታገሰበት ምክንያትማ በዮሐንስ ወንጌል 12፥24 “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የስንዴ ቅንጣት በምድር ወድቃ ካልሞተች ብቻዋን ትቀራለች፤ ብትሞት ግን ብዙ ፍሬ ታፈራለች።” ብሎ አስቀድሞ በተናገረው መሰረት እሱ ሞቶ ብዙ ፍሬን ለማየት ነው።

ነቢዩ ኢሳይያስ ይህንን እንዲህ ሲል አስቀድሞ መስክሯል፦

ኢሳይያስ 53
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈቀደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።
¹¹ ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሸከማል።
¹² ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።

መልካም ቀን!
ይህንን መዝሙር ተጋብዛችኋል። በዛውም ወንጌልን ለሙስሊሞች ለማድረስ የተቋቋመ ቻናል ስለሆነ SUBSCRIBE በማድረግና የደውል ምልክቱን all የሚለው ላይ በማድረግ ተማሩበት ለሌሎችም Share አድርጉት።

👇👇👇
https://youtu.be/nxeKagS1_Lo

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

ለሙስሊሞች ጥያቄ መልስ የሚሰጥበት ቻናል ነው። አዲስ ከሆናችሁ SUBSCRIBE አድርጉ።
https://yt6.pics.ee/42r5jw

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

ይህንን ምስክርነት Share አድርጉት። ተባረኩ!!
https://youtu.be/5j7UIBUrT-A

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

የምትችሉ ግሩፖች ላይ Share በማድረግ አግዙኝ😍 ተባረኩ!!🙏

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

ሙሉ ትምህርቱን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ተጠቀሙ። ይህንን ቀንጭቤ ያመጣሁት ከሙስሊሞች ጋር በምንወያይበት ጊዜ ሙስሊሞች ለመረዳት የሚከብዳቸው የአማርኛ (የቆንቋ) አጠቃቀም ችግር ነው። ይህንን ደሞ ሆን ብለው ለማጣመም ያድርጉ፣ ሳይገባቸው ቀርቶ ይሁን ግራ የሚያጋባ ነው። ምክንያቱም ችግሩ የሚጀምረው ሙስሊሙ ማህበረሰብ ሊቆቻችን ብሎ ከሚቆጥራቸው ነው። ችግሩ የእስልምና አስተምህሮ ብቻ ሳይሆን አማርኛን በአግባቡ ያለመማር ችግርም በጣም ይመስላል። ነገር ግን ነፍሱን ማዳን የሚፈልግ እውነትን ይፈልጋል፣ ይህ ለዛ አይነት ሰው በጣም ጠቃሚ እንደሚሆን አምናለው።

Share ማድረግ አይረሳም😍

https://youtu.be/23_2GNnCcG8

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

https://youtu.be/s9R0f4ecdeQ

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

ይህ የአንድ ሙስሊም ሼኪ ምስክርነት ነው። ኢየሱስ/ዒሳ ነቢይ ብቻ ሳይሆን ፈጣሪም መሆኑን ይመሰክራሉ። እናንተም ስሙት ለሌሎችም SHARE አድርጉት። ለቻናሉ አዲስ የሆናችሁ ደሞ SUBSCRIBE በማድረግ ፕሮግራሙን ደግፉ። የምለቃቸው ቶሎ እንዲደርሷችሁ ደሞ የደውል ምልክቱን ALL የሚለው ላይ አድርጉት። ስለ ትብብራችሁ ተባረኩ!!

https://youtu.be/xlwXX5I1Tzk

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

ሰላም እንዴት ናችሁ!! ሙስሊሞች 303 ጥያቄዎች ብለው ለሚያከፋፍሉት pdf (አህመዲን ጀበል ላዘጋጃቸው ጥያቄዎች) መልስ የሚሰጥ ሊንክ ይዤላችሁ መጥቻለው። ከታች ያለውን ሊንክ ተጠቀሙ። በዛውም ሙስሊሞች ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች መልስ የሚሰጥበትን የዩትዩብ ቻናል SUBSCRIBE በማድረግ ቻናሉን አሳድጉ። ስለምታደርጉት ተሳትፎ እግዚአብሔር ይባርካችሁ። ሙስሊሞች ከመቼውም ጊዜ በላይ የቃሉ እውቀት የሌላቸውን ክርስቲያኖች ለማወዛገብ ታጥቀው የተነሱበት ጊዜ በመሆኑ የእናንተ ንቁ ተሳትፎ በጣም አስፈላጊ ነው። ለሌሎቸ ክርስቲያኖችም ግሩፖች ላይ Share ብታደርጉት መልካም ነው።

የዩትዩብ ቻናሌን ለማግኘት ይህንን ተጠቀሙ👇


https://youtube.com/c/EWNETYASARFAL

ለአህመዲን ጀበል 303 ጥያቄዎች መልስ ለማግኘት ይህንን ተጠቀሙ👇
http://www.ewnetlehulu.org/am/our-answers/jebel/ch1_p1/

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

ወንጌል ለሙስሊሞች

ይህንን ቢያንስ ለ10 ሰው share በማድረግ አግዙኝ። እናንተም SUBSCRIBE በማድረግና የደውል ምልክቱን በማብራት ተከታተሉ። ወንጌልን ለሙስሊሞች ለማድረስና ክርስቲያኖችንም በሙስሊሞች ከሚመጡ ማደናገሪያዎች ለመጠበቅ የተቋቋመ ቻናል ነው። ታዛዦች እንደምትሆኑ ተስፋ አደርጋለው።

ይህንን ሊንክ ስትነኩት ወደ ዩትዩቡ ይወስዳችኋል። ተባረኩ!!😍
👇👇👇
https://youtube.com/c/EWNETYASARFAL

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

https://youtu.be/PIbHbjR3_6k

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

https://gofund.me/7917949f

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

ዘጠነኛ፡ የቃል ኪዳኑ ታቦት ወደ ኢየሩሳሌም የተወሰደው መቼ ነበር?

በ2 ሳሙኤል 5 እና 6 መሰረት ዳዊት የቃል ኪዳኑን ታቦት ወደ ኢየሩሳሌም የወሰደው ፍልስጥኤማውያንን ድል ካደረገ በኋላ ነው ወይንስ በ1ዜና ምዕራፍ 13 እና 14 መሰረት ከጦርነቱ በፊት ነበር?

እንዲህ ዓይነቱ ቅራኔ እንዳለ ተደርጎ የሚቀርበው አጠቃላይ ክፍሉን ካለማንበብና አውዱንም ካለመረዳት የተነሳ ነው፡፡

ይህም ለክስትያኖች በእውነት ችግር አይደለም፡፡ ይህንን እንደ ችግር ያነሳው ሻቢር የሚባል ሰው 1ኛ ዜና ምእራፍ 13 እና 14ን ብቻ አንብቦ ከሚያቆም ምዕራፍ 15 ድረስ ቀጥሎ ማንበብ ነበረበት፣ እንደዛ ቢያደርግ ኖሮ ዳዊት የቃል ኪዳኑን ታቦት ፍልስጥኤማውያንን ካሸነፈ በኋላ ሲያመጣ ይመለከተው ነበር፡፡ ለዚህም ምክንያቱ እስራኤላውያን የቃል ኪዳኑን ታቦት ሁለት ጊዜ ማንቀሳቀሳቸው ነበር፡፡ በመጀመሪያም ፍልስጥኤማውያንን ከማሸነፋቸው በፊት ከበዓል ስፍራ አንቀሳቅሰውት ነበር በ2ሳሙኤል ምእራፍ 5 እና 6 ላይ እንደምናየው እንዲሁም በ1ኛ ዜና 15 ላይ፡፡ አንድ ጊዜ ነቢዩ ሳሙኤል ዳዊት በፍልስጥኤማውያን ላይ ያገኘውን ድል ከዘገበ በኋላ የቃል ኪዳኑ ታቦት ሁለት ጊዜ እንደተንቀሳቀሰ ደግሞ ይነግረናል፡፡ ይሁን እንጂ በ1ኛ ዜና ላይ ያለው ቅደም ተከተል እንደሚከተለው ነው፦ የቃል ኪዳኑ ታቦት በቅድሚያ ወደ በዓል ተንቀሳቀሰ፣ ከዚያም ዳዊት ፍልስጥኤማውያንን ድል አደረገ እናም በመጨረሻ ላይ የቃል ኪዳኑ ታቦት ከዖቤድ-ዶም ቤት ተንቀሳቀሰ፡፡

ስለዚህም ሁለቱ ዘገባዎች እርስ በእርሳቸው በፍፁም የሚቃረኑ አይደሉም፡፡ እዚህ ላይ ያለን ነገር በቀላሉ ነቢዩ የቃል ኪዳኑን ታቦት በተመለከተ በአንድ ጊዜ አጠቃላዩን ታሪክ ሲሰጠን ነው (ይህም በኋላ ስለ እርሱ ከመጥቀስ ይልቅ ነው) እንዲሁም ሌላው ደግሞ ታሪኩን በተለየ መንገድ ሲያቀርበው ነው፡፡ በሁለቱም መንገድ የክስተቶቹ ጊዜዎች ተመሳሳይ ናቸው፡፡

ይህንን በተመለከተ ስለ ቁርአንም ተመሳሳይ ቅራኔ ነገር አለ ሊባል ይቻላል፡፡ (እዚህ ነጥብ ላይ ሁሉንም መጥቀስ ባይቻልም) በቁርአን ምዕራፍ 2 ላይ እኛ የተነገረን ነገር ስለ አዳም ውድቀት ነው፣ ከዚያ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ምህረት ሲያደርግ ይታያል፤ ይህም የፈርዖንን በባህር መስጠም ተከትሎ ነው፣ እንዲሁም የሙሴ ነገር ሲቀጥልና የወርቁ ጥጃ ታሪክ፡፡ ከዚያ ቀጥሎ ደግሞ እስራኤላውያን ስለ ምግብና ስለ ውሃ ሲያጉረምርሙ ይታያሉ፤ ከዚያ በኋላ ስለ ወርቁ ጥጃ ዘገባ እንደገና እናገኛለን፡፡ ከዚህም ቀጥሎ ስለ ሙሴና ስለ ኢየሱስ እናነባለን ከዚያም ስለ ሙሴና ስለወርቁ ጥጃ እንደገና እናነባለን፣ ከዚያም ደግሞ ስለ ሰሎሞንና ስለ አብርሃም፡፡

አንድ ሰው ስለ ቅደም ተከተል መናገር ከፈለገ ሙሴ ከኢየሱስ ጋር ምን የሚያገናኘው ነገር አለ ወይንም ሰሎሞን ከአብርሃም ጋር ምን ያገናኘዋል? ቅድም ተከተልን በተመለከተ የቁርአኑ ምዕራፍ ሁለት ማቅረብ የነበረበት ነገር ቢኖር ከአዳም ውድቀት በኋላ፤ የቃየንን፤ ከዚያም የአቤልን፤ የሄኖክን፤ የአብርሃምን፤ የሎጥን፤ የይስሐቅን፤ ቀጥሎም የያቆብንና የኤሳውን ከዚያም የዬሴፍን ቀጥሎም የእስራኤል ልጆችንና ሙሴን በዚያ ቅደም ተከተል ማቅረብ ነበረበት፡፡ እንዲህ ዓይነት ዝብርቅርቁ የወጣ የቅደም ተከተል ድብልቅ በዚያ አንድ የቁርአን ምዕራፍ ከተገኘ፤ ሻቢር አላይ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስህተት ወይንም ቅራኔ የሚመስሉ ነገሮችን እያነሳ ለማስረዳት ከመነሳት በፊት፤ በቁርአኑ ውስጥ ያሉትን እነዚህን ድብልቅልቆች ለማስረዳትና ሰዎች እንዲቀበሏቸው ለማድረግ ጥሩ ስራ መስራት ነበረበት ፡፡

ይህንን ቻናል በማሳደግ ወንጌልን ለሙስሊሞች እናድርስ። አዲስ ከሆኑ SUBSCRIBE ያድርጉ። ይህንንም ወደሚችሉት ቦታ ሁሉ SHARE ያድርጉት። ተባረኩ!!
@ewnetyasarfal
👇👇👇
እውነት ያሳርፋል You Tube
https://youtu.be/gBkTP8uT8jc

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

ስምንተኛ፡ ኃያሉ ሰው የገደለው ሦስት መቶ ሰው ወይንስ ስምንት መቶ ሰው?

በ2 ሳሙኤል 23፥8 ላይ “የዳዊት ኃያላን ስም ይህ ነው። የአለቆች አለቃ የሆነ ከነዓናዊው ኢያቡስቴ ነበረ፤ እርሱም ጦሩን አንሥቶ ስምንት መቶ ያህል በአንድ ጊዜ ገደለ" ይላል።

በ1ኛ ዜና 11፥11 ላይ ደግሞ “የዳዊትም ኃያላን ቍጥር ይህ ነበረ፤ የሠላሳው አለቃ የአክሞናዊው ልጅ ያሾብአም ነበረ፤ እርሱ ጦሩን አንሥቶ ሦስት መቶ ሰው በአንድ ጊዜ ገደለ።" የሚለውን ጽሑፍ እናነባለን፡፡

ጥያቄው ስሙ የተጠቀሰው ኃያል ሰው ስንት ሰዎችን ነው በአንድ ጊዜ የገደለው የሚለው ነው፡፡ ለዚህ መልሱ በዚህ ቦታ ላይ ሁለቱም ጸሐፊዎች የተለያዩ ክስተቶችን እየገለፁ ሊሆን የሚችል ነገር ነው፡፡ ይህም ምንም እንኳን ነገሩ የተደረገው በአንድ ሰው ቢሆንም ጭምር ማለት ነው፡፡ ወይንም ደግሞ አንድ ጸሐፊ በአንድ ሰው የተደረገውን ነገር በከፊል ሲያቀርብ ሌላው በሙሉም አቅርቦትም ሊሆን ይችላል፡፡

የሆነው ሆኖ ይህ አይነቱ በቁጥር መዛባት ላይ ያለው ችግር የታሪክን አውድ ወይንም የጸሐፊውን ዓላማ ካለመረዳት የሚመጣ ችግር ነው፡፡ (ከዚህም በፊት እንደተጠቆመው ሁሉ እንዲህ ዓይነት ችግሮች  አጠቃላይ የትምህርት መዛባት ወይንም መሰረታዊ ትምህርት ላይ ወይንም ደግሞ ትርጉም ላይ የሚያመጡት ችግር የለም፡፡

የዩትዩብ ቻናሌን SUBSCRIBE በማድረግ ፕሮግራሙን ደግፉ፣ እናንተም ይበልጥ ተማሩበት። ለሌሎች Share ማድረግም thank you የምትሉበት አንዱ መንገድ ይሁን። ተባረኩ!!
👇👇👇
https://youtu.be/7htEV-10--I

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

https://youtu.be/OOS_cuC4EFQ

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

https://youtu.be/Xb8OlsNIhSg

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

#እውቀት_ከንቱ_ነው?

“ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ።”
— ሆሴዕ 4፥6

እግዚአብሔር ቃሉን እንድናውቅ ይፈልጋል ማለት ነው። የቃሉ መሃይም መሆን ያጠፋል ማለት ነው።🤔 ስለዚ እግዚአብሔር እውቀትን ይወዳል ማለት ነው። ታድያ እኛ እንዳንጠፋ ምን ያህል ቃሉን ለመረዳት እያጠናን ነው?🤷‍♂️

ቃሉን ባለማወቅ ከሚጠፉት እንሆን?🤷‍♂️

ለሙስሊሞች ጥያቄ መልስ የሚሰጥበት ቻናል ነው። አዲስ ከሆናችሁ SUBSCRIBE አድርጉ።
https://yt6.pics.ee/42r5jw

ለሌሎች Share አድርጉት😍🙏

Читать полностью…

እውነት ያሳርፋል You tube

https://youtu.be/PfQOnsydDf4

Читать полностью…
Subscribe to a channel