አባታችን ዜና ማርቆስ በኤልያስ ሠረገላ ሆነው እግዚአብሔርን ወደማያውቁት ወደ አዳል ሕዝቦች ሄደው ከጣ*ዖት አምላኪው ንጉሥ ከአብደልማል ፊት ወንጌልን ሲያስተምሩ ንጉሡ በጦር ወግቶ ገድሏቸዋል፣ ነገር ግን መልአኩ ሩፋኤል መጥቶ ከሞት አሥተስቷቸዋል፡፡ የንጉሡን ጣዖ*ትና አገልጋዮቹን መብረቅ ከሰማይ ወርዶ ሲያጠፋቸው ንጉሡ ሠራዊታቸው ደግሞ በመሬት ላይ ወድቀው ቀርተዋል፡፡ ከዓርብ እስከ ሰኞም ድረስ ጨለማ ሆኖ ከቆየ በኋላ ከአባታችን ከተወጋ ጎናቸው የፀሐይ ብርሃን ወጥቶ ለንጉሡ አብደልማል አብርቶለታል፡፡ እርሱም አምኖ ከነቤተሰቡ የተጠመቀ ሲሆን ሚስቱም በአረማውያን ዘንድ ለክርስቶስ ምስክር ሆና አንገቷን ተሰይፋ ሰማዕትነትን ተቀብላለች፡፡ በሀገሪቱም የተጠመቁት ሰዎች ቁጥር ከስምንት መቶ ሺህ በላይ ናቸው፡፡
ከዚህም በኋላ አቡነ ዜና ማርቆስ እንደ ሐዋርያትም ደመና በመጥቀስ ወደ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ሄደው ሁሉንም የተቀደሱ ቦታዎችን ተሳልሟዋል፡፡ ከጌታችን መቃብር ላይ አፈር ዘግነው ከዮርዳኖስም ወንዝ ውኃ ቀድተው ለንስር አሞራዎች አሸክመው ወደ ገዳማቸው በማምጣት በደብረ ብስራት ምድር ካለው አፈርና ውኃ ጋር ጨምረውታል፡፡ ጌታችም ‹‹ይህችን ምድርህን እንደ ኢየሩሳሌም አድርጌልሃለሁ›› የሚል ቃልኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ አባታችን ከደብረ ሊባኖስ አውራጃ ራሱን ያስመልክ የነበረን ሰይጣን ገዝተው ይዘው እስከ ደብረ ብስራት ድረስ የቤተክርስቲያን መሥሪያ እንጨት አሸክመውታል፡፡ በዚያም እንጨት በመሸከም ሲያገለግላቸው ኖሯል፡፡
አባታችን ዜና ማርቆስ ወደ ዋልድባ በመሄድ ከአባ ሳሙኤል ጋር ተገናኝተው እንዲሁም ከሌሎች በርካታ አባቶች በየቦታው እየሄዱ በረከት ተቀብለዋል፡፡ ወደ ትግራይም በመሄድ የተሰዓቱ ቅዱሳንን ገዳማት ተሳልመው ወደ ሰሜንም ሄደው ዜማውን ሲያዜም ያሳያቸው ዘንድ ወደ ቅዱስ ያሬድ መቃብር ሄደው ሰባት ቀን ሲማጸኑ ከቆዩ በኋላ ወደ አክሱም ጽዮን ሄደው በዚያ ከቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከቅዱስ ኤፍሬምና ከቅዱስ አባ ሕርያቆስ ጋር ሆኖ እነርሱ ድርሰታቸውን ሲያነቡ ያሬድ ደግሞ ድርሰታቸውን እያዜመው ተገልጠውላቸዋል፡፡ አባታችን ወደ ላሊበላም ሄደው ከቅዱስ ላሊበላ በረከትን ተቀብለዋል፡፡ ወደ ጣና ደሴትም ሄደው በዚያ ካሉ ቅዱሳን ተባርከዋል፡፡ ሐይቅ እስጢፋኖስም አባ ኢየሱስ ሞዐ ጋር በመሄድ እንዲሁ ተባርከዋል፡፡ በታናሽ ደመናም ወደ ብሔረ ሕያዋን ተነጥቀው ሞትን ካልቀመሱት ከሄኖክ፣ ከኤልያስና ከዕዝራ በረከትን ተቀብለዋል፡፡ ወደ እስላም ሀገርም በመሄድ ለአንድ ዓመት ቆይተው በዚያ ያሉ ሕዝቦችን በተአምራቸውና በትምህርታቸው አሳምነው አጥምቀዋቸዋል፡፡ ጌታችን በምድር ላይ ብዙ ቃልኪዳን ከሰጣቸው በኋላ ወደ ሰማይ አውጥቶ ገነትንና ሲኦልን ሁሉን አሳይቷቸዋል፡፡
አቡነ ዜና ማርቆስ 8 እንጀራን አበርክተው 8ሺህ ሰዎችን በመመገብ ጌታችንን መስለውታል፡፡ ቀድሰው ሕዝቡን ሁሉ ሲያቆርቡ ቢመሽባቸው ፀሐይን እንደ ኢያሱ ገዝተው አቁመዋታል፡፡ በታኅሣሥ ወር መባቻ አባታችን በገዳመ ደንስ በረሃ ያገኛት ተአምረኛዋ ሥዕለ ማርያም ወዳለችበት ቤተክርስቲያን ሄደና ለመቀደስ ሠራዒ ካህን ሆኖ ተሠየመና እንደሚገባ የቅዳሴውን ሥርዓት ጀመረ፡፡ ማዕጠንት ይዞ እየዞረ የቤተ ክርስቲያኑን በሮች በሚያጥንበት ጊዜ ሥጋ ወደሙን ለመቀበል እርስ በእርሳቸው ሲጨናነቁ የልጆቹ መነኮሳትን ብዛት ተመለከተ፡፡ ያን ጊዜም በልቡ አሰበ፣ እንዲህም አለ፡- ‹ይህን ያህል ያለውን ሰው ቅዱስ ቊርባን ማቀበል እንዴት ይቻላል? ይህ ሁሉ ሰው በተራ እስከሚቀበል ድረስ ፀሐይ ይገባል፣ መሽቶ ሌሊትም ይሆናል› አለ፡፡ ከዚህም በኋላ ዐይነ ልቡናውን ወደ ሰማይ አቅንቶ ‹አቤቱ ጠላቶቹን እስከደመሰሰና ለእስራኤል ልጆች ርስታቸውን እስካካፈለ ድረስ ለኢያሱ ፀሐይን በገባዖን ያቆምክ አንተ ነህ፤ ዛሬም ቅዱስ ሥጋህን ክቡር ደምህን ለእነዚህ ባሮችህ ቅዱሳን መነኮሳትና ለሕዝቦችህ እስከማቀብላቸው ድረስ እንዲሁ በቸርነትህ ብዛት ፀሐይን አቁማት› ብሎ በጸለየ ጊዜ ፀሐይዋ ወዲያውኑ ቆመች፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዳሴውን ጨርሶ ሕዝቡን ሁሉ አቆረባቸው፡፡››
ቅዱስ አባታችን በምሁር ኢየሱስ ገዳም ከሬብ በሚባል ዋሻ ውስጥ 40 ዓመት ዘግተው ተጋድለዋል፡፡ በዚህም ሳሉ መልአክ የዕረፍታቸውን ዕለት ታኅሣሥ ሦስት ቀን እንደሚሆን ስለነገራቸው ታኅሣሥ አንድ ቀን ወደ ገዳማቸው በመሄድ ቀድሰው ሕዝቡን ሁሉ ሲያቆርቡ ቢመሽባቸው ፀሐይን ለሁለተኛ ጊዜ እንደ ኢያሱ ገዝተው አቁመዋታል፡፡ አባታችን ዜና ማርቆስ የዕረፍታቸውን ዕለት ከመልአኩ ከተረዱ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱን እንዲህ አሏቸው፡- ‹‹ከዚህ ዓለም የምለይበት ጊዜ ደርሷልና ወደ ፈጣሩዬ እሄዳለሁ፣ እኔ ሽማግሌ አባታችሁ የምመክራችሁን ስሙ፣ ከበጎ ሥራ ሁሉ አስቀድማችሁ እርስ በእርሳችሁ ተዋደዱ፣ ፍቅር ሰማያዊ መንግሥትን ለማግኘት በባለሟልነት ወደ እግዚአብሔር ፊት ያደርሳልና›› ብለው መከሯቸው፡፡ ዳግመኛም ጾመኛ ነኝ አትበሉ አሏቸው፡፡ ‹‹ስለ ነፍሳችሁ ድኅነት፣ ከመከራና ከጥፋትም ሁሉ ለማምለጥ በምትጾሙ ጊዜ እንዲህ እየጾማችሁ ሳላችሁ ስለምትሹት ግብር ወደ ዓለም ሰዎች ብትደርሱና በጾም ቀን ሲበሉና ሲጠጡ ብታዩአቸው መብልና መጠጥን በሚወዱ ሰዎች ፊት በውጭ በአደባባይ ‹ዛሬ የጾም ቀን ስለሆነ እኛ እንጾማለን› አትበሉ፡፡ ስለ እናንተ መጾምና ስለ እነርሱም አለመጾም አንዳች አትናገሩ፣ ባለመጾማቸውም አትንቀፏቸው፡፡ ስለ ሌላ ሥራ ወደማይጾሙ ሰዎች ብትደርሱ ግን በጾም ዕለት ወንድሞቻችን ‹ኑ አብረን እንብላ› ቢሏችሁ እኛ እንጾማለን አትበሉ፣ እንዲህ በሉ እንጂ፡- ‹ወደ እናንተ ከመምጣታችን በፊት ከቤት በልተናል፣ ጠግበናል› ስትሏቸው እናንተ እንደምትጾሙ ያውቃሉ፡፡›››
ከዚህም በኋላ አቡነ ዜና ማርቆስ ታኅሣሥ ሁለት ቀን የደቀ መዛሙርቶቻቸውን እግር ሲያጥቡ ውለው አስቀድሞ መልአኩ እንደነገራቸው ታኅሣሥ ሦስት ቀን በ140 ዓመታቸው ነቢይም፣ ሐዋርያም፣ ካህንም፣ ባለራእይም፣ የሀገራችንም ብርሃን የሆኑት ጻዲቁ አባታችን በክብር ዐርፈዋል፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅድስት_ማርታ_ተሐራሚት
በዚህች ቀን በትኅርምትና በተጋድሎ የጸናች ቅድስት ማርታ አረፈች። ይቺም ቅድስት ከምስር ተወላጆች ውስጥ ነበረች ወላጆቿም እጅግ ባለጸጎች ነበሩ ከታናሽነቷም ጀምራ የረከሰ ዝሙትን የምትወድ ነበረች የከተማ ጐልማሶችና ታላላቆችም በሥውር ወደርሷ እየመጡ ያመነዝሩ ነበር። ከዚህ በኋላም ሥራዋ ተገለጠ የርኲሰት ሥራንም በግልጥ አብዝታ የምትሠራ ሆነች።
ክብር ምስጋና ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የከበረ ልደቱ በዓል በሆነ ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደች ልትገባም በፈለገች ጊዜ የቤተ ክርስቲያኑ ጠባቂ ከለከላት እንዲህም አላት አንቺ በምግባር የረከስሽ ስለሆነ ወደ ከበረች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መግባት አይገባሽም ይተዋትም ዘንድ አባበለችው እርሱ ግን ከለከላት በመካከላቸውም ታላቅ ጸብ ሆነ።
ኤጲስቆጶሱም ጩኸት ሰምቶ ተነሥቶ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ደጃፍ ደረሰ ማርታንም በአያት ጊዜ የእግዚአብሔር ቤቱ የከበረና የነጻ እንደ ሆነ አታውቂምን አንቺም የረከስሽ ስለሆንሽ ወደ እግዚአብሔር ቤት ትገቢ ዘንድ አይገባሽም አላት።
በዚያን ጊዜም አለቀሰች ንስሓ እገባለሁ እንጂ ወደዚህ ሥራ እንግዲህ አልመለስም ብትቀበለኝም እመነኲሳለሁ አለችው። ኤጲስቆጶሱም ገንዘብሽንና ጥሪትሽን ሁሉ ወደዚህ አምጥተሽ በፊትሽ ካላቃጠልነው አላምንሽም አላት።
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን፡፡
ይህ የጽሁፍ መጠይቅ የተዘጋጀው በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ፣ በአዲስ አበባ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጥምረት እንዲሁም በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ ፍቁረ እግዚእ ሰንበት ት/ርት ቤት በአንድነት የተዘጋጀው የመጀመሪያ ዙር የሱባኤ ጉባኤ ትምህርት ክፍል የቡድን ሁለት (2) ተማሪዎች ነዉ።
ይህንን የጽሑፍ መጠይቅ ለመሙላት ፈቃደኛ ሰለሆኑልን እናመሰግናለን።
ይህን መጠይቅ በምትሞሉበት ጊዜ እኛም መጠይቁን ያዘጋጀነው ማን እንደሞላው የማናቅ መሆኑን በእግዚአብሔር ስም ልናስረግጥላችሁ እንወዳለን በመሆኑም ሳትሳቀቁ በነጻነት እንድትሞሉ በአክብሮት እንጠይቃለን
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSeQUJT7OmuDEvGpI9Q5h6HPgVL3KiPfjMcySMlW-gI47iDXYA/viewform?usp=sf_link
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ❤️ እንዲህ ያስተምረናል።
👉ኃጢአት ስትሠሩ እንጂ ንስሐ ስትገቡ አታፍሩ።
👉 የማይቆሰሉት የማይዋጉ ብቻ ናቸው።
👉 "ሰዎች ከኃጢአት እንዲርቁ የማሰብ ኃይል አላቸው."
👉 "በጥቃቅን ነገሮች ለመደሰት ለምን አትማርም - በጣም ብዙ ናቸው."
👉 "ያለ እርዳታ መምራት በቀላሉ የማይቻል ነው
የጸሎት፣ በጎ ሕይወት።
👉 "አእምሮን ከማሰልጠን እና የወጣቶችን ልማድ ከመፍጠር የበለጠ ምን ሥራ አለ?"
👉 "ትንኞች ከሰዎች ጋር ሲነጻጸሩ እንዲሁ ነው።
ፍጥረት ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር ሲወዳደር።
👉"የሥልጣን ፍቅርን ያህል ቤተ ክርስቲያንን የሚከፋፍላት የለም።"
👉 "ንብ ከሌሎች እንስሳት የበለጠ የተከበረች ስለምትደክም ሳይሆን ለሌሎች ስለምትደክም ነው።"
ግንቦት 29/2016 #ቅዱስ_በዐለ_ወልድ
#ፅንሰት_ልደት_ትንሣኤ
👉በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን በዚህ ቀን እመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም የከበረ መልአክ የቅዱስ ገብርኤልን የምሥራች የሠማችበት አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ የተወለደበት የከበረዉን #ትንሣኤውን የገለጠበት ወርሐዊ መታሰቢያ ነዉ
👉እንዲሁም በዚህች ቀን #አለም_የተፈጠረበት የጌታችንን ዳግመኛ #ምፅአቱን የምንጠባበቅበት እለትም ጭምር ነዉ
👉በዚህች ቀን ለእመቤታችን ለቅድስት #ድንግል_ማርያም የከበረ #መልአክ_ገብርኤል_የምሥራች የነገረበት ድኅነትን የተመላች ታላቅ በዓል ናት በዚህም የከበረ ወንጌል ምስክር ሁኗል እንዲህ ሲል
👉ኤልሳቤጥ በፀነሰች በስድተኛው ወር #መልአኩ_ገብርኤል የገሊላ ክፍል የሆነች ናዝሬት ወደምትባል አገር ከዳዊት ወገን ለሆነ ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደታጨች ወደ አንዲት ድንግል #ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ
👉የድንግሊቱም ስም #ማርያም ነው መልአኩም ወደርሷ ገብቶ ደስተኛ የሆንሽ ደስ ይበልሽ ፀጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነው አንቺ ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ አላት እርስዋም አይታ ከንግግሩ የተነሣ ደንግጣ እንዴት እንዲህ ያለ ሰላምታ ይቀበሏል ብላ አሰበች
👉መልአኩም እንዲህ አላት ማርያም ሆይ #በእግዚአብሔር ዘንድ ባለሟልነትን አግኝተሻልና አትፍሪ እነሆ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ ስሙንም #ኢየሱስ ትይዋለሽ እርሱ ታላቅ ነው የልዑል #እግዚአብሔር ልጅም ይባላል
👉 #እግዚአብሔር አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል ለያዕቆብ ወገንም ለዘላለም ነግሦ ይኖራል ለመንግስቱም ፍጻሜ የለውም አላት
👉ማርያምም መልአኩን ወንድ ሳላውቅ ይህ እንደምን ይሆናል አለችው መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት መንፈስ ቅዱስ መጥቶ ያድርብሻል የልዑል ኃይልም ያጸናሻል ከአንቺ የሚወለደው ከሶስቱ አካል አንዱ የልዑል #እግዚአብሔር ልጅ ይባላል
👉እነሆ ዘመድሽ ኤልሳቤጥም እርስዋ ደግሞ በእርጅናዋ ፀንሳለች ወንድ ልጅም አገኘች ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው #ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና #ማርያምም እነሆኝ የእግዚአብሔር አገልጋይ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ አለችው።
👉ያን ጊዜም ድንግል ስትሆን ረቂቅ ፅንስን ተቀበለች የእግዚአብሔር አካላዊ ቃል #ወልድ_ዋህድ ለኩነተ ሥጋ ወርዶአልና ይህም አንድ ባሕርይ አንድ ህልውና ሲሆን ከሦስቱ አካላት አንዱ ነው
👉ከዓለም መፈጠር አስቀድሞ የነበረ በማይመረመር ድንቅ በሆነ ተዋሕዶ እንዴትም እንደሆነ በማይታወቅ በቅድስት #ድንግል_ማርያም ማሕፀን አደረ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ተፀንሶ በህቱም ድንግልና #ታህሣሥ_ሀያ_ዘጠኝ ቀን ተወለደ
👉በዚያን ጊዜም የኋላ ኋላ መለየት ከቶ የሌለውን ፍጹም ሰውነት ነሥቶ ተዋሐደ መለኮቱ ከትስብእቱ ጋራ ያለ መለያየት አንድ ሆኖአልና ይቺም ዕለት የበዓላት ሁሉ በኩር ናት በእርሷም #የዓለም_ድኅነት ተጀምሮዋልና
👉ዳግመኛ በዚህችም ዕለት ደግሞ በመድኃኒታችን በከበረችና ልዩ በሆነች #ትንሣኤው የዓለም ድኅነት ሆነ በረቀቀ ጥበቡ ሠላሳ ሦስት ዓመት ያህል በምድር ላይ ሥራውን ሠርቶ በፈጸመ ጊዜ በፈቃዱ ሕማማተ መስቀልን ተቀብሎ ሙቶ ከተቀበረ በኋላ በሦስተኛው በዚች ቀን #በሃያ_ዘጠኝ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷልና
👉በዚች ቀን አስቀድሞ ደጅ ለሚጠኑት በዓለም ላሉ ሰዎች ሰው በመሆኑ ድኅነታቸውን አበሠራቸው እንዲሁም ደግሞ በዚች ዕለት ከሲኦል በመዳን #ሙታንና_ሕያዋን ደስ አላቸው
👉በዚህም በጌታችንና በመድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ በሥጋ መነሣት መነሣታቸውን አረጋገጡ የከበረ ጳውሎስ በመነሣቱ ክርስቶስ የሙታን በኵር ሆነ እንዳለ እርሱ ለሙታን በኵራቸዉ ነዉና
👉አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ከበአሉ በረከት ሁላችንንም ያሣትፈን ዳግም ሲመጣም ከቅዱሳኑ ጋር ይደምረን የምንሰማዉን የምናየዉን ክፉ ነገር ሁሉ ወደ በጎ ነገር ይቀይርልን
👉በዚህ እለት በመታሠቢያ በአላቸዉ የምናስባቸዉ ፃድቁ አባታችን #አቡነ_እጨጌ_ዮሐንስ በምልጃ ፀሎታቸዉ ይጠብቁን "አሜን" ✝️💒✝️
ግንቦት 28/2016 #ቅዱስ_አማኑኤል
#ርዕሰ_አበዉ_አብርሃም_ይስሐቅ_ያዕቆብ
👉በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ለአባቶቻችን አምላክ #ለቅዱስ_አማኑኤል አመታዊ መታሠቢያ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን
👉 #አማኑኤል ማለት #እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው ማለት ነው
👉 #የአብርሐም_የይስሐቅ_የያእቆብ አምላክ ቅዱስ #እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን በቸርነቱ ይጠብቀን
👉#አማኑኤል ማለት፣የአምላክ ሰላም፣#የእግዚአብሔር እርቅ የጌታ አንድነት ማለት ነው
👉 #አማኑኤል ማለት "አማኑ" እና "ኤል" ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው አማኑኤል ማለት #እግዚአብሔር ከኛ ጋር ማለት ነዉ
👉ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም #አማኑኤል ትለዋለች ትርጉሙም #እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው ( ኢሳ 7፥14)
👉ቸሩ #ቅዱስ_አማኑኤል ለእኛ ስትል በመስቀል ሞት የገለፅከዉን ፍቅርህን እያሰብን ከሐጢአት እና ከአመፅ እንድንርቅ ፍቅርህ በልቦናችን ይታተም #በትንሣኤህ የኛን ትንሣኤ የገለፅክልን ጌታችን እናመሰግንሃለን ክብር ኃይልና ምስጋና ለአምላካችን #ለቅዱስ_አማኑኤል ይሁን
👉በዚህ እለት በመታሰቢያ በአላቸዉ የምናስባቸው የአባቶቻችን #የአብርሃም_የይስሐቅ_የያዕቆብ ረድኤትና በረከት አይለየን የታላቁ ነብይ #የነብዩ_ኢሣያስ ምልጃ ፀሎቱ ይጠብቀን"አሜን" ✝️ 💒 ✝️
ግንቦት 28/2016 #ቅዱስ_አማኑኤል
#ርዕሰ_አበዉ_አብርሃም_ይስሐቅ_ያዕቆብ
👉በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ለአባቶቻችን አምላክ #ለቅዱስ_አማኑኤል አመታዊ መታሠቢያ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን
👉 #አማኑኤል ማለት #እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው ማለት ነው
👉 #የአብርሐም_የይስሐቅ_የያእቆብ አምላክ ቅዱስ #እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን በቸርነቱ ይጠብቀን
👉#አማኑኤል ማለት፣የአምላክ ሰላም፣#የእግዚአብሔር እርቅ የጌታ አንድነት ማለት ነው
👉 #አማኑኤል ማለት "አማኑ" እና "ኤል" ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው አማኑኤል ማለት #እግዚአብሔር ከኛ ጋር ማለት ነዉ
👉ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም #አማኑኤል ትለዋለች ትርጉሙም #እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው ( ኢሳ 7፥14)
👉ቸሩ #ቅዱስ_አማኑኤል ለእኛ ስትል በመስቀል ሞት የገለፅከዉን ፍቅርህን እያሰብን ከሐጢአት እና ከአመፅ እንድንርቅ ፍቅርህ በልቦናችን ይታተም #በትንሣኤህ የኛን ትንሣኤ የገለፅክልን ጌታችን እናመሰግንሃለን ክብር ኃይልና ምስጋና ለአምላካችን #ለቅዱስ_አማኑኤል ይሁን
👉በዚህ እለት በመታሰቢያ በአላቸዉ የምናስባቸው የአባቶቻችን #የአብርሃም_የይስሐቅ_የያዕቆብ ረድኤትና በረከት አይለየን የታላቁ ነብይ #የነብዩ_ኢሣያስ ምልጃ ፀሎቱ ይጠብቀን"አሜን" ✝️ 💒 ✝️
#ግንቦት_27
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ግንቦት ሃያ ሰባት በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሠላሳኛ የሆነ የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት #አባ_ዮሐንስ አረፈ፣ የማርያና የማርታ ወንድም #ጻድቅ_አልዓዛር አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ሊቀ_ጳጳሳት_አባ_ዮሐንስ
ግንቦት ሃያ ሰባት በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሠላሳኛ የሆነ የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሐንስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ደግ የተማረም ነበር። ከልጅነቱም ጀምሮ በገድል ተጠምዶ የሚኖር ነበር። ከዚህም በኋላ በዋሻ ውስጥ ራሱን እሥረኛ አደረገ። የትሩፋቱና የዕውቀቱም ዜና በተሰማ ጊዜ በእስክንድርያ አገር ላይ ይዘው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት። ብዙ ድርሳናትንም ደረሰ እግዚአብሔርም በዘመኑ የቤተ ክርስቲያንን ሥልጣን አጸና።
ይህ አባት በተሾመበት ወራት ደግ ምእመን አንስጣስዮስ የሚባል ንጉሥ ነበር። በአንጾኪያም የከበረ አባት አባ ሳዊሮስ ነበረ እርሱም ወደ አባ ዮሐንስ ስለ ቀናች ሃይማኖት እንዲህ ብሎ በመልእክቱ ውስጥ ጻፈ። ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተዋሕዶው በኋላ እንደ አባቶቻችን እንደ አባ ድሜጥሮስና እንደ አባ ዲዮስቆሮስ እምነት ያለ መቀላቀል ያለ መለወጥ ያለ መለያየትና ያለ መጨመር አንዲት ባሕርይ አለችው።
አባ ዮሐንስም መልእክቱን ተቀበለው ኤጲስቆጶሳቱም ሁሉ ተለያይተው የነበሩ ሕዋሳትም ተመልሰው አንድ ስለ ሆኑ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገኑት።
ከዚህም በኋላ ለመልእክቱ መልስ አባ ዮሐንስ ለአባ ሳዊሮስ እንዲህ ብሎ ጻፈለት። ይኸውም ስለ መለኮትና ትስብእት የአንድ ባሕርይ ህልውና ስለ ወልደ እግዚአብሔር ያለ መለያየት ያለ መቀላቀልና ያለ መለወጥ ሁለት ያይደለ የሰውን ባሕርይ ከመለኮቱ ባሕርይ ጋራ አንድ አድርጎ በመዋሐድ ሰው ስለ መሆኑ።
ጌታችንንም የሚከፋፍሉትን ወይም ተጨመረበት የሚሉትን ወይም ስለእኛ መከራ ተቀብሎ ተሰቅሎ የሞተው ዕሩቅ ብእሲ ነው የሚሉትን በመለኮቱ ባሕርይ መከራ ተቀበለ የሚሉትን አወ**ገዘ። የቀናች ሃይማኖትስ ይቺ ናት እግዚአብሔር ከእኛ በነሣው ሥጋ ስለ እኛ መከራ እንደ ተቀበለ እናውቃለን እኮን። ይቺም የሚጓዝባት የማይሳሳትባትና የማይደናቀፍባት የሕይወት መንገድ ናት አለ።
አባ ሳዊሮስም ይቺን የአባ ዮሐንስን መልእክት በአነበባት ጊዜ በመልካም አቀባበል ተቀበላት። በአንጾኪያ አገርም ሰበከባት ስለ ቀናች ሃይማኖትም በመካከላቸው ሰላም ፍቅርና ስምምነት ሆነ። ይህም አባት ሕዝቡን እያስተማረ ዐሥራ አንድ ዓመት ኑሮ ከዚህ በኋላ በሰላም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ጻድቅ_አልዓዛር
በዚችም ዕለት የማርያና የማርታ ወንድም ጻድቅ አልዓዛር አረፈ። ይህንንም ጻድቅ ሰው በአራተኛ ቀን ከመቃብር ከአስነሣው በኋላ በዚሁ ሳምንት ውስጥ መድኃኒታችን መከራ ተቀብሎ ተሰቅሎ ሞተ። ከትንሣኤውም በኋላ አልዓዛር ከሐዋርያት ጋራ አንድ ሆነ።
አጽናኝ መንፈስ ቅዱስም በወረደ ጊዜ ከሐዋርያት ጋራ ጸጋውን ተቀበለ። ሐዋርያትም በቆጵሮስ አገር ላይ በአንብሮተ እድ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት። መንጋውንም በመልካም አጠባበቅ ጠበቀ። በሹመቱም አርባ ዓመት ኑሮ በሰላም በፍቅር አረፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ግንቦት)
ከሞት መኃል ነጥቀሽ
ነፍስን ዘራሽብኝ
ሀጢአተኛ ሳለው
ሰው አርገሽ አቆምሽኝ
ሀዘን መከራየ
ታሪክ ሁኖ ቀረ
ኑሮየ በሙሉ
በድንግል አማረ
በማርያም አማረ
✝✝✝ በስመ አብ : ወወልድ : ወመንፈስ ቅዱስ : አሐዱ አምላክ . . . አሜን :: ✝✝✝
+✝" አቡነ ሃብተ ማርያም ጻድቅ "✝+
=>እኒህ ጻድቅ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል::
+ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን አባታቸው ፍሬ ቡሩክ : እናታቸው ደግሞ ቅድስት ዮስቴና ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ : ምጽዋትን ወዳጅ : ቡርክት ሴት ነበረች:: እንዲያውም ከጻድቁ መወለድ በፊት መንና ጭው ካለ በርሃ ገብታ ነበር::
+ግን የበቃ ግኁስ አግኝቷት "ከማሕጸንሽ ደግ የሥላሴ ባርያ አለና ተመለሽ" ብሏት እንደ ገና ተመልሳለች:: ጻድቁን ወልዳ አሳድጋም እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ ዐርፋለች::
+ወደ ጻድቁ ዜና ሕይወት ስንመለስ አቡነ ሃብተ ማርያም ገና ሕጻን እያሉ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ሲባል ይሰማሉ:: ይሕችን ጸሎት በሕጻን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ "ማረን እባክህን?" እያሉ ይሰግዱ ነበር::
+የ5 ዓመት ሕጻን እንዲህ ሲያደርግ ማየቱ በእውነት ይደንቃል:: ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ:: ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:: የፈጣሪውን ስም ያቃለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል::
+ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው : መጻሕፍትንም አጥንተው መንነዋል:: በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኮሱ በሁዋላ የሠሩትን ትሩፋትና የነበራቸውን ተጋድሎ ግን የኔ ብጤ ደካማ ሰው ሊዘረዝረው አይችልም::
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ::
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ:: (መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ታላቅ ጸሎት ነው)
*በ40 ቀናት : ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ::
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው::
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ:: (ካህን ናቸውና)
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ : ክቡር ደሙን ይጠጣሉ::
*በፍጹም በልባቸው ውስጥ ቂምን : መከፋትን አላሳደሩም::
+በእነዚህና በሌሎች ትሩፋቶቻቸው ደስ የተሰኘ ጌታም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ኢየሩሳሌም ይሔዱ ነበር:: ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በሁዋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ አላቸው::
"1.ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ:
2.ስለ ምናኔሕ:
3.ስለ ተባረከ ምንኩስናህ:
4.ስለ ንጹሕ ድንግልናህ:
5.ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ:
6.ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ:
7.ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::"
+"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን : 500 የእንቁ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ : በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ! በርእስየ!' ብዬሃለሁ" አላቸው::
+ቅዱሳን መላእክትም "ሃብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: በዝማሬም ወሰዷት:: {ይህች ቀን (ግንቦት 26) ለጻድቁ ዕለተ ልደታቸው ናት::}
=>አምላከ አበው ወሰማዕት ጣዕመ ፍቅራቸውን: ክብራቸውን: ጸጋ በረከታቸውንም ይክፈለን::
=>+"+ እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና::
ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና::
ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል . . .
ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ::
በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ::
የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል::
የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው::
በእርምጃውም አይሰናከልም:: +"+ (መዝ. 36:28-31)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ❤️ እንዲህ ያስተምረናል።
👉ማር ያልቀመሰውን የማርን ጣፋጭነት በቃላት መግለጽ እንደማይቻል
👉 እኛም ራሳችን ወደ ጌታ ቸርነት በኛ ቸርነት ዘልቆ መግባት ካልቻልን
👉 የእግዚአብሄርን ቸርነት በማስተማር መንገድ በግልፅ መግለጽ አይቻልም። የራሱን ልምድ.
ቅዱስ ሰሎዋን ዘ አቶናዊ ❤️ ደግሞ እንዲህ ያስተምረናል።
👉ብዙ ባለጠጎች እና ኃያላን ሰዎች ጌታን ወይም እጅግ ንፁህ እናቱን ለማየት ብዙ ዋጋ ይከፍላሉ፣
👉 ነገር ግን እግዚአብሔር በሀብት አይገለጥም፣
👉ነገር ግን በትሑት ልብ... እያንዳንዱ ድሀ ሰው ትሑት መሆን እና እግዚአብሔርን ማወቅ ይችላል።
👉 እግዚአብሔርን ለማወቅ ገንዘብም ሆነ ስም አያስፈልገውም ነገር ግን ትህትና ብቻ ነው።
👉 የቱንም ያህል ብንማር እንደ ትእዛዙ እስካልኖርን ድረስ እግዚአብሔርን ማወቅ አይቻልም፤
👉 እግዚአብሔርን በመንፈስ ቅዱስ እንጂ በሳይንስ አያውቅም።
👉 ብዙ ፈላስፎች እና የተማሩ ሰዎች አምላክ መኖሩን ወደ ማመን መጡ, ነገር ግን እግዚአብሔርን አያውቁም ነበር.
👉እግዚአብሔር እንዳለ ማመን እና እሱን ማወቅ ሌላ ነገር ነው።
👉 አንድ ሰው እግዚአብሔርን በመንፈስ ቅዱስ ካወቀ፣ ነፍሱ ቀንና ሌሊት ለእግዚአብሔር ባለው ፍቅር ትቃጠላለች፣
👉ነፍሱም ከማንኛውም ምድራዊ ነገር ጋር ልትታሰር አትችልም።
ፈጣሪ እግዚአብሔር ❤️ከሁላችን ጋር ይሁን!!!
https://youtube.com/channel/UCAe0Vv9bIkCTTkeilxcUoYQ
እባካችሁን አሁን online ያላቹህ ይህንን መንፈሳዊ ቻናል ሰብስክራይብ አድርጉልን
#ሰኔ_3
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ሰኔ ሦስት በዚች ቀን #አባታችን_ዜና_ማርቆስ መታሰቢያቸው ነው፣ በትኅርምትና በተጋድሎ የጸናች #ቅድስት_ማርታ አረፈች፣ #ቅዱሰ_ኤላርዮስ የሚባል ኤጲስቆጶስ ሰማዕት ሆኖ አረፈ፣ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ #አቡነ_ተጠምቀ_መድኅን እረፍታቸው ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አቡነ_ዜና_ማርቆስ
ሰኔ ሦስት በዚች ቀን አባታችን ዜና ማርቆስ መታሰቢያቸው ነው፡፡ ሀገራቸው ጽላልሽ አውራጃ ምድረ ዞረሬ ስትሆን ትውልዳቸው ከነገደ ሌዊና ከእስራኤል ነገሥት ወገን ነው፡፡ ወላጆቻቸው ልጅ በማጣት ሲያዝኑ አንድ ዕለት ሐዋርያውና ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወደ እናታቸው ማርያም ዘመዳ ሌሊት መጥቶ ገድሉና ትሩፋቱ በዓለም ሁሉ የመላ ጻዲቅ ልጅ እንደምትወልድ ነገራት፡፡ ለአባቱ ለቀሲስ ዮሐንስም እንዲሁ ተገልጦለት ‹‹ሚስትህ ማርያም ዘመዳ የካቲት 24 ፀንሳ ኅዳር 24 ቀን ይኸውም በካህናተ ሰማይ በዓል ቀን ትወልዳለች፣ ስሙም ዜና ማርቆስ ይባላል›› በማለት ብስራቱን ነግሮታል፡፡
በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ብሥራት መሠረት አባታችን በተወለዱም ዕለት ቅዱስ ዑራኤልና ቅዱስ ሩፋኤል የብርሃን ልብስ አልብሰው በክንፋቸው ሲጋርዱአቸው ለሰዎችም ሁሉ ታይቷል፡፡ በወቅቱም የአባ ሳሙኤል ዘወገግ አባት እንድርያስና የአቡነ ተክለሃይማኖት አባት ቅዱስ ጸጋ ዘአብ እስኪደነቁ ድረስ ይህን በዓይናቸው ተመልክተዋል፡፡ ሁለቱ መላእክትም ከእናታቸው ዕቅፍ ወስደው ወደ ሐዋርያው ማርቆስ መቃብር ወስደው ለማርቆስና ለቅዱሳን ጳጳሳት አስባርከዋቸው መልሰው ለእናቱ ሰጧቸው፣ እናቱ ግን ይህን አታውቅም ነበር፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስም በተወለዱ በሦስተኛው ቀን በእግራቸው ቆመው ‹‹አንድ አምላክ ለሆኑ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ እሰግዳለሁ›› ብለው ሦስት ጊዜ አምላካቸውን አመስግነው ሰግደዋል፡፡ በ40 ቀኑ ሲጠመቅ የሚያጠምቀው ካህን የአባቱ ወንድም እንድርያስ ውኃው ሲፈላ አይቶ ሸሽቷል፡፡ መልአኩም እንዳይፈራ ነግሮት ለእርሱም ተአምር እንደሚደረግለት አስረዳው፡፡ እንድርያስም ዕድሜው 72 ነበርና ራሰ በራ ስለነበር በውኃውም ራሱን ቢታጠብበት ጸጉር አብቅሏል፡፡ ሕዝቡም ሁሉ ይህን አይቶ አደነቀ፡፡ ያችም ውኃ ሌሎች በጣም ብዙ ተአምራትን አደረገች፡፡
አንድ ዓመት በሆነውም ጊዜ ቤተክርስቲያን ውስጥ እየዳኸ ሲሄድ መልአክ በክንፎቹ አቅፎ ወስዶ ጌታችንና እመቤታችን ጋር አቅርቦት አስባርኮታል፡፡ እንዲሁም የ15ቱን ነቢያት፣ የ12ቱን ሐዋርያት የ72ቱን አርድእት፣ ሃይማኖታቸው የቀና የ318ቱን ሊቃውንት፣ የጻድቃንን፣ የሰማዕታትን የእነዚህን ሁሉ በረከት እንዲቀበል ካደረገው በኋላ ወደዚያች ቤተክርስቲያን መለሰው፡፡ ከጳጳሱ ከአቡነ ጌርሎስ ድቁናን ተቀብሎ ከአባቱ ጋር ወደ ሀገሩ ሲመለስ ዘራፊዎች ደብድበው በትራቸውንም ሳያስቀሩ ዘረፏቸው፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስም ወደ ፈጣሪው በጸለየ ጊዜ በትራቸው እባብ ሆና ነድፋ ገደለቻቸው፡፡ በኋላም ወደ አምላካቸው ጸልየው ከሞት እንዲነሱ በማድረግ በአካባቢውም ያሉ ሰዎች ሁሉ በእርሱ አምላክ እንዲያምኑ አድርጓቸዋል፡፡
ከዚህም በኋላ ብሉያትንና ሐዲሳትን ጠንቅቆ ከተማረና ካደገ በኋላ ሚስት አጭተው አጋቡት፡፡ እርሱ ግን በዚያው በሠርጉ ዕለት ማታ ጌታ ‹‹እናትና አባቱን ሚስቱን ቤቱን ንብረቱን ያልተወ ሊያገለግለኝ አይችልም›› ያለውን ቃል አስቦ ሚስቱን እንዲህ አላት፡- ‹‹እኅት ሆይ! የዚህ ዓለም ኑሮ ምን ይጠቅመናል፣ ዓለሙም ፍላጎቱም ያልፋል፡፡ ስለዚህ የነፍሴን ድኅነት ለመሻት እሄድ ዘንድ አሰናብችኝ›› ሲላት እርሷም ‹‹አንተ የተውከው ዓለም ለእኔስ ምን ይጠቅመኛል?›› በማለት ሁለቱም ሰው ሳያያቸው ከጫጉላ ቤታቸው በሌሊት ወጥተው ሄዱ፡፡ ቅዱስ ዑራኤልና ቅዱስ ሩፋኤልም እየመራቸው ዜና ማርቆስን ምሁር ገዳመ ኢየሱስ እርሷን ደግሞ ወደ ቤተ ደናግል ማማስ ደብር አደረሷቸው፡፡ እርሷም ሙትን እስከማስነሣት ድረስ ታላላቅ ተአምራትን እያደረገች ቆይታ ተጋድሎዋን ፈጽማ በጥር 21 ቀን በክብር ዐርፋለች፡፡ ዐርፋ የተቀበችውም በደመና ተነጥቃ ኢየሩሳሌም ከሄደች በኋላ እመቤታችን በተቀበረችበት በጌቴሴማኒ ሲሆን ሁለት አንበሶች ጉድጓድ ቆፍረው ቀብረዋታል፡፡
አባታችንም በምሁር ሀገር ይመለክ የነበረውን ማኮስ የተባለውን ጣ*ዖት በመሬት ውስጥ ቀበረውታል፡፡ ገዥውም ተቆጥቶ በአባታችን ላይ ክፉ ሲያደርግ ‹‹ካላመንክ አንተም እንደ አምላክህ እንደ ማኮስ መሬት ተከፍታ ትውጥሃለች›› ብሎ በተናገረበት ቅጽበት ገዥውን ከነሠራዊቱ መሬት ተከፍታ ዋጠቻቸው፡፡ ከዚያም ፈጥነውና በደመና ተነጥቀው ወደ ግብፅ በመሄድ ከአባ ብንያሚን ቅስና ተቀብለው መጡና መሬት ተከፍታ የዋጠችውን የገዥውን ቤተሰቦች ጨምሮ ብዙ ሺህ የምሁር ሕዝቦችን አስተምረው አጠመቋቸው፡፡ ያንን ገዥም ስለ ተጠመቁ ልጆቹና ሚስቱ ብለው ከ5 ዓመት በኋላ በጸሎታቸው ኃይል ከሞት አስነስተውታል፡፡ በዚሁ ሀገር ከአባ ዜና ማርቆስ ጋር ሳሉ የኢትዮጵያው ጳጳስ አባ ጌርሎስ በድንገት ዐርፈው ሳለ ጻዲቁ ዜና ማርቆስ ጸሎት አድርገው ከሞት አስነሥተዋቸዋል፡፡ ሌላም እንዲሁ በጉራጌ ሀገር ገርዳን የሚባለውን ጣዖት ሰባብረው በውስጡ የነበረውን ሰይጣንን እንደ ትቢያ በኖ እስኪጠፋ ድረስ አስጨንቀውታል፡፡ ሕፃናቱን ጨምሮ ከ124 ሺህ በላይ የሚሆኑትን ሕዝቦችም አስተምረው አጥምቀዋቸዋል፡፡ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤልም ሁልጊዜ እንደ ጓደኛ እያናገራቸው ይረዳቸው ነበር፡፡
አባታችን ዜና ማርቆስ የሚያደርጓቸው እጅግ ድንቅ የሆኑ ተአምራት በሕዝብ ዘንድ ውዳሴን እያመጣ እንዳያስቸግራቸው ብለው ይህን ተአምር የማድረግ ሥራ እግዚአብሔር እንዲያርቅላቸው ይለምኑት ነበር፡፡ ወግዳ በምትባል ሀገር ሄደው በዋሻ ውስጥ ሳሉ አቡነ ተክለሃይማኖት ወደ እርሳቸው መጥተው አብረው በዋሻው ብዙ ተአምራትን እያደረጉ ቆይተዋል፡፡ ለአባ ዜና ማርቆስና ለሌሎች ለብዙ አባቶች የምንኩስና አባት የሆኑት አቡነ ተክለሃይማኖት ትሕትናቸውን ያሳዩ ዘንድ አቡነ ዜና ማርቆስን ያገለግሏቸው ነበር፡፡ ወደ ሞረት ሀገር እንዲሄዱ መልአክ ነግሯቸው ሁለቱም ሄደው በዚያም አብረው ተቀምጠዋል፡፡ ጣዖት አምላኪውን የሞረቱ ገዥ ሊገድላቸው ፊልጎ ከነሠራዊቱ ወዳሉበት ዋሻ ሄደ፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስም ተራራዋን በሥላሴ ስም ባርከው ቢያዟት የገዥውን ጭፍሮች አፏን ከፍታ ዋጠቻቸው፡፡ ገዥውን ድል አሰግድንም በተአምራቸው አሳምነውት አስተምረው አጠመቁት፡፡
ከዚህም በኋላ ቅዱስ ገብርኤል ለአቡነ ተክለሃይማኖት ተገልጦላቸው ወደ ግራርያ ሀገር እንዲሄዱ ስለነገራቸው አቡነ ተክለሃይማኖት የመላእክትን አስኬማ ለአቡነ ዜና ማርቆስ አልብሰዋቸው ዜና ማርቆስንም በደብረ ብስራት እንዲጸኑ ነግረዋቸው ወደ ግራርያ ሄዱ፡፡ ሲሄዱም የደብረ ብስራት ዛፎቹ እንጨቶቹና ደንጊያዮቹ ሁሉ አቡነ ተክለሃይማኖትን እንደ ንጉሥ ሠራዊት ከፊት ከኋላ ሆነው ሸኝተዋቸዋል፡፡ አባታችንም ‹‹የወንድሜን የዜና ማርቆስን ቦታ ትታችሁ ከዚህች ምድር ትሄዱ ዘንድ አልፈቅድምና ሁላችሁ በየቦታችሁ ቁሙ›› ብለዋቸዋል፡፡ ‹‹ሰውም እንኳ ቢሆን ለምንኩስና ወደ እኔ ዘንድ ወደ ግራርያ ከመምጣቱ በፊት ይህን ምድር ሳይሳለም ወደ እኔ አይምጣ›› በማለት ቃልኪዳናቸውን ከደብረ ብስራት ጋር አድርገዋል፡፡
ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን❤️ እንዲህ ያስተምሩናል
👉ሙስሊሞች ሰልጥነው ሙተው እንዲህ ይላሉ።
👉የመጀመሪያው ሀይማኖት ሙስሊም ነው
👉እናንተ እኮ ክርስቲያን የምትሆኑት ከ40 ቀን በኋላ ነው ይላሉ።
ነገር ግን አይደለም
መልስ
👉እስከ 40 ቀን ድረስ ክርስትና የማንነሳው ሙስሊሞች ስለሆን አይደለም ።
እንዴት?
👉አንዲት ሴት ከፈሳሽ የምትነፃው ወንድ ልጅ ከወለደች በ33 ኛውቀን ነው
👉ሙሴ ኦሪት ዘሌዋውያን 12፡1 ላይ የመንፃት ህግ ብሎ 7ት ቀን ሰርቷል
👉33 + 7 = 40 ይሆናል።
ስለዚህ
👉በቤተክርስቲያን ውስጥ የፍጡር ፈሳሽ እንዳይፈስ
👉የሴቲቱ ደም ሳይቆም ቤተክርስቲያን እንዳትገባ
👉ስለ ቤተክርስቲያን ክብር ነው እንጂ ሙስሊሞች ስለሆን አይደለም።
👉ሌላ አዳም በ40 ቀን ገነት እንደገባ የገነት አምሳል ቤ/ን አለች
👉ቤተክርስቲያን ትትሜሰል በጽርሐ አርያም ዘላዕሉ እንዲል
👉ቅድስት ቤተክርስቲያን በላይኛይቱ ሰማይ በጽርሐ አርያም ትመሰላለች
👉ስለዚህ አዳም ገነት እንደገባ
እኛ ደግሞ
- አማናዊት ገነት ከተባለችው
-የሰላም ከተማ ከሆነችው
-የብርሃን ምሰሶ ካላት
- ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፡መላእክት፡ ሐዋርያት ፡
- ነብያት ፡ ፃድቃን : ሰማዕታት ፡ደናግላን ፡ መነኰሳት ፡
-ካህናት ፡ ዲያቆናት : አናጉንስጢስ ፡ መዘምራን ፡ አበው ፡ እመው ካሉባት
👉በገነት አምሳል የግድ 40 ቀን መጠበቅ ስላለብን በዚህ ምክንያት እኛ በ 40 ቀን እንጠመቃለን።
🎤ሴቶች ለምንድን ነው በ 80 ቀን የሚጠመቁት ሲባል
👉1ኛ ሔዋን በ80 ቀን ገነት ስለገባች
👉2ኛ ሴት ከወለደች ከፈሳሽ ነጻ መሆኛ ቀን በ66 ኛ ቀን
የሙሴ ሕግ ከፈሳሽ ነፃ መኾኛ ቀን 14 ኛ ቀን
ድምር 66 + 14 = 80 ቀን
🎤እንዲት ሴት መንታ ብትወልድ መቼ ወደ ቤተክርስቲያን ትሄዳለች
ማለት አንድ ወንድ አንዲት ሴት ብትወልድ
👉ወንድ ከወለደች ወንዱ በ ሞግዚት ይጠመቃል
👉ሞግዚት ማለት በእህት በአክስት በጎረቤት በሌላ ሴት ታዝሎ ሂዶ ይጠመቃል
ለምን?
👉እሷ ስለሴቲቱ ምክንያት 80 ቀን መጠበቅ ስላለባት
👉ስለዚህ እሷ በ 80 ቀን ሴት ልጇን ይዛ ታሰጠምቃለች
👉ወንዱ ግን በሞግዚት ይጠመቃል ማለት ነው
👉ኢየሱስ ክርስቶስ❣️ በእውነት ኃጢአታችንን አጠበልን
👉ክርስትያኖች ደስ ሊለን ይገባል
👉በልቡናችን ንጹህ መንፈስ ተስሎብናል
👉እግዚአብሔርን የመምሰል ኃይል ተሰጥቶናል
👉ዛሬ አንዳንድ ወጣት ሴቶች ፈረንጅን ለመምሰል
👉በተሌቭዥን መስኮት የሚያዩያቸውን ሴቶችን ለመምሰል
👉ልብሳቸውን አሳጥረው ከመታጠቂያቸው አድርሰው ቆንጠል ቆንጠልእያሉ ነው
👉እግዚአብሔርን መምሰል ለእናንተ በቂ ነው
👉ፈረንጅ መምሰል እንስሳትን መምሰል አያስፈልግም
👉እግዚአብሔርን መምሰል በቂ ሀብት ነው ።
ይሄን ሃብት የተሰጠነው መቼ ነው ካላችሁ ?
በ 40 በ 80 ቀን ስንጠመቅ ።
🌼🌼🌼 እነሆ🌼🌼🌼
▶እነሆም ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ ዳን ፲:፳፩◀
▶ሚካኤል◀
አዲስ ዝማሬ በዘማሪ ዲ/ን መርሃ ጽድቅ // መሳይ ቢቂላ
የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ሰኔ 11 ከምሽቱ 3:00 በዘማህደር ቲዮብ // በዘማህደር የቴሌግራም ቻናል //በዘማህደር የፌስቡእ አካወንት ይለቀቃል ሁላችሁም ሼር በማረግ ለሌሎች አጋሩ።zemahidertube?si=EAEAplYRmsxnJWwC" rel="nofollow">https://youtube.com/@zemahidertube?si=EAEAplYRmsxnJWwC 👈 Follow
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ❤️ እንዲህ ያስተምረናል።
👉ቃልህ ምንም ያህል ቢሆን በንዴት ስትናገር ሁሉንም ነገር ታበላሻለህ።"
👉 "ብል ልብስን እንደሚያላግጥ ሰውንም ቅናት ይበላል።"
👉 "እግዚአብሔር የሚጠይቀው ጥቂት ነው, ግን ብዙ ይሰጣል."
👉 "እያንዳንዱ ሰው የህይወቱ ሠዓሊና ቀራፂ ነው።"
👉 "ጸሎት" ሥር፣ ምንጭ፣ የሺህ በረከት እናት ናት።"
👉 "የሥጋ ጾም የነፍስ መብል ነው።"
👉 "ሀብታም ብዙ ያለው ሳይሆን ብዙ የሚሰጥ ነው።"
👉 "ክብር ለነገሩ ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን!"
👉 በትንንሽ ነገር ታማኝ መሆን ትልቅ ነገር ነው።
👉 "በህፃናት ትምህርት ውስጥ ዋናው ግብ ማስተማርእና የመልካም ህይወት ምሳሌን መስጠት ነው."
✞ “እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።
” አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከኛ ጋር ሆነ ማለት ነው።
የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ ይሆን ዘንድ ሰው ሆነ፤ ስሙምአማኑኤል ተባለ፤ ትርጉሙም “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር” ማለት ነውና ማቴ. ፩፡ ፳፫፡፡
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
1TON= 600 BIRR 🤑😱
ለማስጀመር:
1,ይህን ሊንክ ተጠቅመው START ይበሉት 👉/channel/preton_drop_bot?start=ee4312b0-beea-4927-bd9c-49273af3d41e
2,@preton_eng የሚለውን ንኩት እና JOIN ይበሉት።
3, JOIN ካሉ በኋላ CHECK THE SUBSCRIPTION የሚለውን ይንኩ።
ከዛ በፊት የሚመጣሎትን 1 የመደመር ጥያቄ መመለስ እና ቋንቋ ENGLISH ማድረግ አይርሱ!
ለወዳጅ ዘመዶ ሊኩን በመላክ ይጋብዙ!
መልካም እድል!
https://moneyeasilytbq.buzz/80376071153407
Ere guys yehe neger yelele migerm new be website new miseraw be task becha ena invite bemaderg ke 200usd jemero mawetat yechalal demo be commercial bank mawetat yechalal tolo jemerut 100%ewenet new
ዐሥራ ሦስቱን ሕማማተ መስቀል ተቀብሎ ከፍዳ ከኩነኔ ያዳነን መድኃኔዓለም (የዓለም መድኃኒት) ኢየሱስ ክርስቶስ ክብር፥ምስጋና፥ስግደት ለእርሱ ይገባል።
***ዐሥራ ሦስቱ ሕማማተ (መከራ) መስቀል፤
፩ኛ/ተኮርዖተ ርዕስ:-ራሱን በዘንግ መመታቱ፤፪ኛ/አክ ሊለ ሦክ:-የሾህ አክሊል ጎንጉነው ደፍተውበታል። ማር:፲፭፥፲፰።፫ኛ/ተአስሮ ድኅሪት:-እጆቹን ወደ ኋላ ጠፍረው አስረውታል።፬ኛ/ስትየ ሐሞት:-ተጠማሁ ባለ ጊዜ ሐሞት፥ከርቤና ወይን ቀላቅለው አቅርበውለ ታል።መዝ:፷፰፥፳፩፣ማቴ:፳፯፥፴፬፣ማር:፲፭፥፳፫፣ሉቃ:፳፫፥፴፮።ቀምሶ ተወው።፭ኛ/ወሪቀ ምራቅ:-ሐክታቸ ውን ከፊቱ ላይ ተፍተውበታል።ኢሳ:፶፥፮፣ማቴ:፳፯፥፳፱ ።፮ኛ/ተቀስፎ ዘባን:-ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪቆ ጠር ድረስ አምስት ሺ አምስት መቶ ጅራፍ ገርፈው ታል።ኢሳ:፶፥፮።፯ኛ/ጸዊረ መስቀል:-ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ ከባድ መስቀል ተሸክሟል።ዮሐ:፲፱፥፲፯።፰ኛ/ ተጸፍዖ መልታህት:-ፊቱን በጥፊ መትተውታል። ማቴ:፳፮፥፷፰።ከ፱ - ፲፫ ያሉት ሳዶር፥አላዶር፥ዳናት፥ አዴራ፥ሮዳስ የተባሉት አምስቱ ቅንዋተ መሰቀል ናቸው።(አምስቱ ችንካሮች)።መዝ:፳፩፥፵፮።
***ሰባቱ አጽርሐ መስቀል፤(በመስቀል ላይ የተናገራ ቸው)።
፩ኛ/“ኤሎሄ፥ኤሎሄ ላማ ሰብቅታኒ፤አምላኬ፥አምላኬ ለምን ተውከኝ?”ብሏል።ማቴ:፳፯፥፵፮።እርሱ በተዋ ህዶ የከበረ የባህርይ አምላክ ሲሆን ስለ አዳም ተናግ ሮታል።አዳም በሲኦል የጸለየው ጸሎት ነው።
፪ኛ/“አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ፤” ብሏል።ከዚያ በፊት ነፍስ የምትሰጠው ለሲኦል ነበር፥ እርሱ ቀረላችሁ ሲል ነው።ሉቃ:፳፫፥፵፮።እርሱ ራሱ ዕሩይ ምስለ አብ ስለሆነ ነፍስን ይቀበላል።የሐዋ:፯፥ ፶፱።
፫ኛ/“እነሆ ልጅሽ፥እነኋት እናትህ፤”በማለት ድንግል ማርያምን የአደራ እናት አድርጎ ለቅዱስ ዮሐንሰ (በእ ርሱም በኩል ለቤተ ክርስቲያን)፥እርሱንም የአደራ ልጅ አድርጎ ለእርሷ አረካክቧል።እመቤታችን በሕይወ ታችን ተጠብቃ የምትኖር አምላካዊ አደራ ናት።ዮሐ: ፲፱፥፳፯።
፬ኛ/የሕይወት ውኃ እርሱ ”ተጠማሁ፤”ብሏል።ዮሐ:፲፱ ፥፳፰፣፬፥፲፬፣፮፥፴፭፤፩ኛ:ቆሮ:፲፩፥፬።
፭ኛ/ባለቀ ሰዓት ንስሐ የገባውን፥በቀኙ የተሰቀለውን ወንበዴ:-“ከአዳም ቀድመህ ገነት ትገባለህ፤”ብሎታል ።ሉቃ:፳፫፥፵፫።
፮ኛ/መከራ አጽንተው የሰቀሉትን ሁሉ ይቅር ብሎ “አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላ ቸው፤”በሏል።አብ ይቅር አለ ማለት ከእርሱ ጋር በአን ድነት የሚመሰገኑ ወልድ መንፈስ ቅዱስም ይቅር ብለዋል ማልት ነው፥በመለኮት አንድ ናቸውና።ሉቃ: ፳፫፥፴፬።
፯ኛ/በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ማኅ ፀን የዕለት ፅንስ ሆኖ የጀመረውን የማዳን ሥራ በመ ስቀል ላይ በመፈጸሙ “ተፈጸመ፤”በሏል።ዮሐ:፲፱፥፴።
ቢያንስ ለ10 ሰዎች በመላክ ሰብስክራይብ እና ላይክ በማስደረግ አገልግሎቱን ያጠናክሩ።
https://kassdire.psee.ly/5zyxnm
✝✝✝ በስመ አብ : ወወልድ : ወመንፈስ ቅዱስ : አሐዱ አምላክ . . . አሜን :: ✝✝✝
"✝" ግንቦት 26 "✝"
+*" አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ "*+
=>እግዚአብሔር በ13ኛው መቶ ክ/ዘ እነ አቡነ ኢየሱስ ሞዐን ባያስነሳ ኑሮ ምናልባትም ዛሬ የኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያንን በምናያት መንገድ ላናገኛት እንችል ነበር:: እውነተኛ አባቶቻችን ፈጽሞ ከሚቆረቁራቸው ነገር አንዱ የጻድቅና ሐዋርያዊ አባት አቡነ ኢየሱስ ሞዐ መዘንጋት ነው::
+እርሳቸው ፍሬ ሃይማኖት ሆነው ከጽድቅ ፍሬአቸው አዕላፍ ቅዱሳንን ወልደው ሃገራችን በወንጌል ትምሕርትና በገዳማዊ ሕይወት እንድታሸበርቅ አድርገዋል:: እስኪ በዕለተ ዕረፍታቸው ስለ ጻድቁ ጥቂት ነገሮችን እናንሳ::
+አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ የተወለዱት ጐንደር : የድሮው ስማዳ (ዳኅና) አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ዘክርስቶስና እግዚእ ክብራ ይባላሉ:: የተወለዱት በ1210 ዓ/ም ነው:: ነገር ግን አንዳንድ ምንጮች በ1196 ዓ/ም ያደርጉታል::
+ጻድቁ ከክርስቲያን ወላጆቻቸው ጋር እንደሚገባ አድገዋል:: በልጅነታቸው በብዛት ወላጆቻቸውን ያግዙ ነበር:: በትርፍ ጊዜአቸው ደግሞ ትምሕርተ ሃይማኖትንና ሥርዓቱን ያጠኑ ነበር:: በ1240 ዓ/ም ግን (ማለትም 30 ዓመት ሲሞላቸው) ይሕቺን ዓለም ይተዋት ዘንድ አሰቡ::
+አስበውም አልቀሩ ፈጣሪን እየለመኑ ደብረ ዳሕሞ ገቡ:: በወቅቱ ዳሞ የትምሕርት : የምናኔ ማዕከል ከመሆኑ ባሻገር የአቡነ አረጋዊ 5ኛ የቆብ ልጅ ካልዕ ዮሐኒ ነበሩና የእርሳቸው ደቀ መዝሙር ሆኑ::
+አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በደብረ ዳሞ በነበራቸው ቆይታ ቀን ቀን ሲታዘዙ : ሲፈጩ : ውሃ ሲቀዱ ውለው ሌሊት እኩሉን በጸሎት በስግደትና የቀረውን ሰዓት ደግሞ ቅዱሳት መጻሕፍትን በመገልበጥ አሳለፉ::
+በመጨረሻም ልብሰ ምንኩስናን ለበሱ:: ይህን ጊዜ 37 ዓመታቸው ሲሆን ዘመኑም 1247 ዓ/ም ነው:: ወዲያውም በዳሞ ሳሉ መልአከ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ተገልጦ "ወደ ወሎ ሐይቅ ሒድ : ብዙ የምትሠራው አለና" አላቸው::
+በአንዴም ከዳሞ (ትግራይ) ነጥቆ ሐይቅ እስጢፋኖስ (ወሎ) አደረሳቸው:: በዚያም ለ7 ዓመታት በዼጥሮስ ወዻውሎስ ቤተ መቅደስ በተጋድሎ : በስብከተ ወንጌል : በማዕጠንትና ሐይቁ ውስጥ ሰጥሞ በመጸለይ ኖሩ::
+ቅድስናቸውን የተመለከቱ አበውም በግድ አበ ምኔት አድርገው ሾሟቸው:: ይህ ነው እንግዲህ በኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን ላይ ትልቁ መሠረት የተጣለበት አጋጣሚ:: ነገሩ እንዲህ ነው:-
+ስም አጠራሯ የከፋ ዮዲት ጉዲት ለ40 ዓመታት ሃገሪቱን እንዳልነበረች ብታደርጋት ክርስትና ተዳከመ:: ባዕድ አምልኮም ነገሠ:: አቡነ ኢየሱስ ሞዐ (ትርጉሙ ኢየሱስ ክርስቶስ አሸነፈ ማለት ነው) ደግሞ ሃይማኖታቸው የቀና ከ800 በላይ ክርስቲያኖችን ሰበሰቡ::
+በሃገሪቱ ትልቅና የመጀመሪያው ሊባል የሚችል ቤተ መጻሕፍት አደራጁ:: እነዚያን አርድእት በቅድስናና በትምሕርት አብስለው አመነኮሱና "ሒዱ! ሃገሪቱን ታበሩ ዘንድ ተጋደሉ" ብለው አሰናበቷቸው::
+ክእነዚህ መካከልም ታላላቁን አቡነ ተክለ ሃይማኖትን: አቡነ በጸሎተ ሚካኤልን እና የሁዋላውን ፍሬ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫን መጥቀስ እንችላለን:: በዚህም ምክንያት ጻድቁ "ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን - አእላፍ ቅዱሳንን የወለደ" ሲባሉ ይኖራሉ::
+ጻድቁ ከዚህ በተጨማሪ የወቅቱን ንጉሥ አፄ ይኩኖ አምላክን በማስተማር ለሃገርና ለቤተ ክርስቲያን ጠቃሚ ሰው አድርገዋል:: በግላቸው ሐይቅ ውስጥ ገብተው ሲጸልዩ የብርሃን ምሰሶ ይወርድላቸው ነበር:: ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳምንም ከጠፋ ከ300 ዓመታት በሁዋላ አቅንተዋል::
+እንዲህ ለቤተ ክርስቲያን ሲተጉ : በተለይ በአበ ምኔትነት በቆዩባቸው 45 ዓመታት ለዓይናቸው እንቅልፍን አላስመኙትም:: ጐድናቸውም ከምኝታ ጋር ተገናኝቶ አያውቅም::
"እንዘ የኀሊ ዘበሰማያት ዐስቦ::
መጠነ ዓመታት ሃምሳ ኢሰከበ በገቦ::" እንዲል::
+ከዚህ በሁዋላ የሚያርፉበት ዕለት ቢደርስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወርዶ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል:: በተወለዱ በ82 ዓመታቸው (በ86 ዓመታቸው የሚልም አለ) በ1282 ዓ/ም በዕለተ ሰንበት ዐርፈው ተቀብረዋል:: {ይህች ቀን (ግንቦት 26) ለጻድቁ ዕለተ ልደታቸው ናት::}
<< ጻድቁ ስም አጠራራቸው እጅግ የከበረ ነው !! >>
=>+"+ ለመንጋው ምሳሌ ሁኑ እንጂ ማሕበሮቻችሁን በኃይል አትግዙ:: የእረኞችም አለቃ በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብርን አክሊል ትቀበላላችሁ:: እንዲሁም ጐበዞች ሆይ! ለሽማግሌዎች ተገዙ:: ሁላችሁም እርስ በርሳችሁ እየተዋረዳችሁ ትሕትናን እንደ ልብስ ታጠቁ:: እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማልና:: ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል:: +"+ (1ዼጥ. 5:3)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
🕊መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስኅ ግቡ🕊
(ማቴ ፫:፫)
✨በአማን ተንሥአ መድኃኒነ!✨
🌿ብፁዕ አባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘኤለ ገዳማተ እምኀበ እግዚኡ ይነሣእ እሴተ ቦአ ሀገረ ደብረ ሊባኖስ በፍሥሐ ወበሰላም።
⚜ሰአል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ ሐረድዎ ወገመድዎ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኀበ ሰብአ ነገሥት ረገጸ ምድረ አንሥአ ሙታነ አባ ጊዮርጊስ በሰላም ዐደወ መንግሥተ ክብር ወረሰ።
🌿ወልደ እግዚአብሔር አምላክነ ወመድኃኒነ ዕቀብ ሕይወተነ እም ገሀነመ እሳት ወእምኵሉ መንሱት በእንተ ቅዱስ ስምከ ወበእንተ ማርያም እምከ ወበእንተ ቅዱስ መስቀል ወበእንተ ዮሐንስ ወንጌላዊ ወበእንተ ዮሐንስ መጥምቅከ ወበእንተ ኵሎሙ ቅዱሳን ወሀባ ሰላመ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተክርስቲያን።
⚜ሰላም ለክሙ ጻድቃን ወሰማዕት እለ አዕረፍክሙ በዛቲ ዕለት መዋዕያነ ዓለም አንትሙ በብዙኅ ትዕግሥት። ሰአሉ ቅድመ ፈጣሪ በኩሉ ሰዓት እንበለ ንስሐ ኪያነ ኢይንሣእ ሞት።
🌿አንቅሐኒ በጽባሕ ክሥተኒ ዕዝንየ በዘአጸምእ አምላኪየ አምላኪየ እገይሥ ኀቤከ ዘይሰማዕ ግበር ሊተ ምሕረተከ በጽባሕ"
⚜ነቢያት ወሐዋርያት፥ ጻድቃን ወሰማዕት፤ ደናግል ወመነኮሳት፥ አዕሩግ ወሕጻናት፤ ገዳማውያን ወሊቃውንት፤ ሰአሉ ለነ ኲልክሙ፥ ቅድመ መንበሩ ለጸባኦት።
🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።
✝ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር
🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)
🔗/channel/zikirekdusn
▶️ZikereKedusan" rel="nofollow">https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
👉እያንዳንዱ ክርስቲያን ቅድስናን ለራሱ አስፈላጊ እና ማበረታቻ ማግኘት አለበት።
👉ያለ ተጋድሎና ቅድስናን ተስፋ ሳታደርጉ የምትኖሩ ከሆነ በስም ብቻ እንጂ በመሠረታዊነት ክርስቲያን ናችሁ።
👉ነገር ግን ያለ ቅድስና ማንም ጌታን አያየውም ማለትም ዘላለማዊ በረከትን አያገኙም።
👉 ኢየሱስ ክርስቶስ ኃጢአተኞችን ሊያድን ወደ ዓለም መጣ የሚለው የታመነ ቃል ነው (1ጢሞ. 1፡15)።
👉እኛ ግን ኃጢአተኞች ሆነን ድነናል ብለን ካሰብን ራሳችንን እናስታለን።
👉ክርስቶስ እነዚያን ኃጢአተኞች ቅዱሳን የሚሆኑበትን መንገድ በመስጠት አዳናቸው።
ከቅዱሳን አንዱ እንዳስተማረው
ሰይጣን ሰበበኛ አድርጎናል!
👉አንዳንዶቻችን ለኃጢአታችን ተጠያቂ መሆናችንን ሳይቀር እስከመካድ በሚያደርስ ደረጃ "ሰይጣን አታለለኝ" በምትል ጥቅስ ራሳችንን ከጥፋተኝነት ነፃ ለማድረግ እንሞክራለን።
👉 በእውነቱ አሁን ላይ ሰው በኃጢአቱ እግዚአብሔርን ከማሳዘኑ በላይ የሚያስጨንቀው በሰዎች ዘንድ ምን ዓይነት ስም ይሰጠኝ ይሆን ብሎ ነው! በዚህም ለኃጢአቱ ሰይጣንን ተጠያቂ ያደርግና ራሱን ገሸሽ ያደርጋል።
👉ሰይጣን አስገድዶ የኃጢአትን ሸክም በአንተ ላይ አይጭንብህም!
👉 ኃጢአትን በልብህ ፀንሰህ በተግባር እንድትወልዳት ግን ውብ እና ማራኪ አስመስሎ ያቀርብልሃል!
👉ይህን የክፋት ግብዣ መቀበል ያለመቀበል ያንተ ድርሻ ነው!
👉 ግብዣውን ተቀብለህ ጋባዡን ብቻ ለስህተትህ ማጋፈጥ ፍትሐዊ አይደለም!
+++ ግንቦት 24 +++
††† እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የስደት
በዓል በሰላም አደረሳችሁ †††
=>የአርያም ንግሥት: የፍጥረታት ሁሉ እመቤት ድንግል ማርያም የባሕርይ
አምላክ ልጇን አዝላ በዚህች ቀን ወደ ምድረ ግብፅ ወርዳለች::
+በወንጌል ላይ (ማቴ. 2:1-18) እንደተጻፈው ጌታችን በተወለደ በ2 ዓመቱ
የጥበብ ሰዎች (ሰብአ ሰገል) ወደ ቤተ ልሔም መጥተው ሰግደውለት: ወርቅ
እጣን ከርቤውን ገበሩ: አገቡለት::
+ንጉሥ ተወልዷል መባሉን የሰማ ሔሮድስ 14,000 ሕጻናትን ሲፈጅ በቅዱስ
ገብርኤል ትዕዛዝ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 1 አምላክ ልጇን
አዝላ: በአንዲት አህያ ጥቂት ስንቅ ቁዋጥራ: ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ስደት
ወጣች::
+ከገሊላ ተነስታ በጭንቅ በመከራ: በረሃብና በጥም: በሐዘንና በድካም:
በላበትና በእንባ ተጉዛ በዚሕች ቀን ምድረ ግብፅ ገብታለች::
+የአምላክ እናቱ
*እሳትን አዝላ በብርድ ተንገላታለች::
*ለእኛ የሕይወት እንጀራን ተሸክማ እርሷ ተራበች::
*የሕይወትን ውሃ ተሸክማ ተጠማች::
*የሕይወት ልብስን ተሸክማ ተራቆተች::
*የሕይወት ፍስሐን ተሸክማ አዘነች::
*እመ አምላክ ተራበች: ተጠማች: ታረዘች: ደከመች: አዘነች: አለቀሰች:
እግሯ ደማ: ተንገላታች::
+ለሚገባው ይሕ ሁሉ የተደረገው ለእኛ ድኅነት ነው:: በእውነት ይህንን
እያወቀ ለድንግል ማርያም ክብር የማይሰጥ ሰይጣን ብቻ ነው:: አራዊት:
ዕፀዋትና ድንጋዮች እንኩዋ ለአመላክ እናት ክብር ይሰጣሉ::
+አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ሰሎሜ ደግሞ የክብር ክብር ይገባቸዋል::
ከአምላክ እናት ከድንግል ማርያምና ከቸር ልጇ ጋር መከራ መቀበልን
መርጠዋልና::
=>መድኃኔ ዓለም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ተሰደደ?
ለምንስ ስደቱን ወደ ግብፅና ኢትዮዽያ አደረገ?
1.ትንቢቱን ይፈጽም ዘንድ:: በፈጣን ደመና ወደ ግብፅ እንደሚወርድ
ተነግሯልና (ኢሳ. 19:1, ዕን. 3:7)
2.ምሳሌውን ለመፈጸም:: የሥጋ አባቶቹ እነ አብርሃም: ያዕቆብ (እሥራኤል):
ኤርምያስ ወደዚያው ተሰደዋልና::
3.ከግብፅ ጣዖት አምልኮን ያጠፋ ዘንድ:: (ኢሳ. 19:1)
4.የግብፅና የኢትዮዽያ ገዳማትን ይቀድስ ዘንድ::
5.ሰው መሆኑ በአማን እንጂ ምትሐት እንዳልሆነ ለማጠየቅ:: ሰው ባይሆን
ኑሮ አይሰደድም ነበርና:: ሔሮድስ ቢያገኘው ደግሞ ሊገድለው አይችልም::
ያለ ፈቃዱና ያለ ዕለተ ዐርብ ደሙ አይፈስምና::
6.ስደትን ለሰማዕታት ባርኮ ለመስጠት:: እና
7.የአዳምን ስደት በስደቱ ለመካስ ነው::
=>ቸሩ መድኃኔ ዓለም የድንግል እናቱን ስደት አስቦ ከመንግስተ ሰማያት ስደት
ይሠውረን:: ከስደቱ በረከትም ያድለን::
ከቴሌግራም ከዝክረ ቅዱሳን ገጽ
©gigar negusse