ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ። ‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3 https://youtu.be/csxxAMGtC4I ለመቀላቀል http://t.me/ortodoxtewahedo
#አልፋና ኦሜጋ
አልፋና ኦሜጋ ፈጣሪ የሆንክ
በካሃዲዎች እጅ ተይዘህ ቀረብክ
ተገፋህ ተደፋህ በጥፊ ተመታህ
እየደበደቡ ክርስቶስ ሆይ አሉሀ
ጽድቅን ስለ ሠራህ በወንጌል ከሰሱህ
ለአዳም ልጅ ብለህ ብዙ ተንገላታህ
………አዝ…………..
ቅዱሳን እጆችህ የፍጥኝ ታስረው
እንደ በግ ተጎተትክ ልትመራቸው
የትም ቦታ ያለህ ሁሉን የምታውቅ
ፊትህን ሸፈኑህ ለመመጻደቅ
………አዝ…………..
በዓውደ ምኲናን ከጲላጦስ ፊት
አሳልፈው ሰጡህ አጋልጠው ለፍርድ
ከሐና ቀያፋ ከመሳፍንቱ ደጅ
ከሄሮድስም ዘንድ አቀረቡህ በዋጅ
………አዝ…………..
ግርፋት ሕማሙ አልበቃ ብሎህ
በመስቀል ላይ ልትውል ተፈረደብህ
ሳዶርና አላዶር ዳናትና አዴራ
ተፈልገው መጡ ለችንካር በተራ
………አዝ…………..
የሰላም ባለቤት ደረትህ ተወጋ
ሊያያዝ በችንካር እጅህ ተዘረጋ
ግፈኞች አሁዶች በአንተ ላይ ቀለዱ
ምራቅን ተፉብህ እራስህን ሊጎዱ፤
👇👇. 👇👇👇
👉 /channel/ortodoxtewahedo👈
☝️☝️☝️☝️☝️☝️
#ጌታ ሆይ
#ሊቀ መ ዘምራን ኪነጥበብ
......
ጌታ ሆይ
አይሁድ አማፅያን ሰቀሉህ ሆይ
የአለም መድሐኒት የአለም ሲሳይ ሰቀሉህ ሆይ
የአለም መድሐኒት የአለም ሲሳይ ሰቀሉህ ሆይl
የአዳም በደል
አደረሰህ አንተን ለመገደል
የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት
የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት
......
ንፁህ ክርስቶስ
ሆንክ ወንጀለኛ ብለህ ስለኛ
መስቀል አሸክመው አስረው ገረፉህ እያዳፉህ
መስቀል አሸክመው አስረው ገረፉህ እያዳፉህ
ግብዞች
እንደራሳቸው መስሏቸው
ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጎዱ
ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጎዱ
......
እጅህና እግርህ
በችንካር ተመታ የአለም ጌታ
የሾህ አክሊል ደፋህ ጎንህን ተወጋህ አልፋ ኦሜጋ
የሾህ አክሊል ደፋህ ጎንህን ተወጋህ አልፋ ኦሜጋ
በመስቀል ላይ
ተጠማሁ ስትል ታላቅ በደል
ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው
ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው
......
ይቅር ባይ
ግልፅ በደላችን ሁሉን ሳታይ
አንተው ይቅር በለን በእኛው ሳትከፋ እንዳንጠፋ
አንተው ይቅር በለን በእኛው ሳትከፋ እንዳንጠፋ
👇👇👇👇👇
👉 /channel/ortodoxtewahedo 👈
☝️☝️☝️☝️☝️☝️
" የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።"
(የዮሐንስ ወንጌል 19:40)
http://t.me/ortodoxtewahedo
✞ ተፈጸመ✞
"ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ" (ዮሐ 19: 30)
ተፈፀመ የሚለው ቃል ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ነፍሱን ለወዳጆቹ ሲሰጥ ከመሞቱ በፊት የተናገረው የመጨረሻ ቃል ነው። " ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ" (ዮሐ 19: 30)። ተፈፀመ በግሪክ "ቴትለስታ'ይ" (τελείωσε /Tetelestai) ማለት ሲሆን ትርጉሙም ወደ ፍፃሜ ማምጣት፣ መጨረሻ መድረሱን፣ ማከናወንን ፣ ማለቅን የሚያሳይ ነው። በእርግጥ አማኑኤል TETELESTAI/ ተፈፀመ ሲል ምኑ ይሆን የተፈፀመው? ብሎ የሚጠይቅ ህሊና ያስፈልገናል።
አስቀድሞ ጌታችን ኢየሱስ አባቱ የሰጠውን ስራ ለመስራትና ለመፈፀም አምላክነቱን እንደመቀማት ሳይቆጥር በአባቱ በራሱና በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ወደ ዓለም እንደመጣ አስታውቆናል። ከመጣም በሇላ አባቱን የሚያከብር ስራን ሰርቷል "እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ" (ዮሐ 17: 4) እንዲል። ሊሰራ የመጣው የጠፋነውን የሰው ልጆች ሊፈልግና ሊያድን ዘንድ ነው ። በምድር ሲመላለስ የስራው ፍፃሜ የነበረውንም ነፍሱን ስለወዳጆቹ በመስጠት ፈፀመው ። ክርስቶስ ተፈፀመ ሲል የሽንፈት ቃል አይደለም የድልና የአሸናፊነት እንጂ ወደ ዓለም የመጣሁበትን ስራ በሞት ጨረስኩ፣ ህዝቦቼን በሞት አዳንኩ ፣ የኃጢአትን ኃይል ድል ነሳሁ ፣ በሞቴ ሞትን ገደልኩ ፣ በመከራዬ ለመንግስቴ ህዝብን ማረኩኝ ሲል ተፈፀመ አለ እንጂ!
የአንጾኪያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ዲዮናስዮስ ተፈፀመ ብሎ ስለሞቱ ሲናገር "በሞቱ ሞትን ያጠፋው እርሱ ነው፡፡ ሲኦልንም የበዘበዘው እርሱ ነው" አለ።
የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስና ሐዋርያው የነበረው ቅዱስ አትናቴዎስ ስለዚህ ድንቅ ነገር በድርሳኑ ‹‹ነፍሱን ከሥጋው በለየ ጊዜ ያን ጊዜ በሲኦል ፈጥኖ ብርሃን ታየ፡፡ ጌታችን በአካለ ሥጋ ያይደለ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ሔደ፡፡ ሲኦል ተነዋወጠች፤ መሠረቶቿም እፈርስ እፈርስ አሉ፡፡ ምድርን ያለ ጊዜዋ እንዳታልፍ ክብርት ደሙን በምድር ላይ አፈሰሰ፡፡ ከኅልፈት ጠበቃት በእርሷ ያለውንም ዂሉ ጠበቀ፡፡ ስለ ፍጥረት ዂሉ ሥጋውን በመስቀል እንደ ተሰቀለ ተወው፡፡ ነፍሱ ግን ወደ ሲኦል ወረደች ከዚያ ተግዘው የነበሩ ነፍሳትን አዳነች፤ ሲኦልንም በዘበዘች፡፡ ፍጥረትንም ዂሉ ገንዘብ አደረገች፡፡ ሥጋውም በመቃብር ያሉ ሙታንን አስነሣ፤ ነፍሱም በሲኦል ተግዘው የነበሩ ነፍሳትን ፈታች፤›› እያለ ያወሳል።
በአማን ኢየሱስ ክርስቶስ ተፈፀመ ሲል አስቀድሞ የገባው የአድናችኋለሁ ተስፋ አርብ ተፈጸመ ፣ የሴቲቱ ዘር የእባቡን ራስ እንደሚቀጠቅጥ የተነገረው ተስፋ ተፈጸመ ፣ የኩነኔና የእርግማን ዘመን በሞቱ ተፈጸመ (ገላ 4፥4) ፣ የእግዚአብሔፍ ፍቅር በመስቀል ሞት ፍጹም ሆኖ በመገለጥ ተፈጸመ/ ተከናወነ/ ፣ እኛ እንጸድቅ ዘንድ የኃጢአት ቅጣት በመስቀል ላይ ተፈጸመ ፣ ወደ ሰማይ እየወጣ በአምላካችን ፊት ይከሰን የነበረው የዲያቢሎስ የክስ መብት በክርስቶስ ሞት ተፈጸመ። ዛሬ ይከሰን ዘንድ ወደ ሰማይ ቢወጣ በጌታ በኢየሱስ እጆች ላይ የሚታዩ ችንካሮችና በልብሱ ላይ የሚታየው የደም ነጠብጣብ አፉን ይዘጋዋል። በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ገብቶ የነበረው ጥል በራሱ በጌታችን አስታራቂነት ለአንዴ ተፈጸመ። የሚሰሩትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ማለቱ ለእንዴና ለዘላለም የእግዚአብሔርን ምህረት የምናስታውስበት ድምጽ ሆነ ። የበረታ ጌታ ሁላችንንም በቸርነቱ አዳነን እርሱ ተፈፀመ ሲል የኛ ደስታ ፣ የኛ መዳን ፣ የኛ ተስፋ ፣ የኛ መቤዠት በእግዚአብሔር ወልድ በተፈፀመልን የዘላለም ኪዳን ደም መፍሰስ በእውነት ተፈጸመ!!!
ለታረደው በግ ለእርሱ መጀመሪያ ከሌለው አባቱ ጋርና ቅዱስ፣ መልካምና ህይወት ሰጪ ከሆነው መንፈስ ቅዱስ ጋር ክብር ሁሉ ይገባዋል። አሁንና ለዘላለም ለትውልደ ትውልድ አሜን!
/channel/ortodoxtewahedo
.#የሕማማት_ጥያቄዎችና_መልሶቻቸው
1. በሕማማት ለምን መስቀል አንሳለምም ወይም አናማትብም?
👉🏾የመስቀል ክብር እና ኃይል የታወቀው ጌታ በመስቀለ ከተሰቀለ በኋላ ነው
በሰሞነ ሕማማት ከሰኞ እስከ አርብ ያሉት ቀናት የዓመተ ፍዳ መታሰቢያ ናቸው።
በነዚህ ዘመናት ሰዎች የመስቀልን አገልገሎት እንዳልጀመሩ ለማሳየት
በሰሞነ
ሕማማት በቤተክርስተያን ስርዓት መሰረት መስቀል መሳለምም ሆነ የማማተብ ስርዓት የለም።
2. በሰሞነ ሕማማት ለምን አንሳሳምም?
👉🏾ይሁዳ ጌታውን በመሳም አሳልፎ ሰጥቶአል እኛም እንደ ይሁዳ ክፋት ካለው መሳሳም መለየታችንን ለማሰረዳት።
ከዚሀ በተጨማሪም ፍፁም ሰላም በዘመነ ፍዳ እንዳልነበረ ለማሳየት
በሰሞነ ሕማማት እሰከ መሳሳም የደረሰ ጥብቅ ሰላምታ የለም።
3. በሰሞነ ሕማማት የማይፈቀዱ ሌሎቸ ነገሮች ምን ምን ናቸው?
👉🏾ማንኛውም ለስጋ የሚያደሉ ተግባሮችን መቀነስ እና ቢቻለን አብዛኛውን ጊዜአችንን በቤተ እግዚአብሔር የጌታን መከራ ሕማም በማሰብ በፆም በስግደት
በጸሎት ማሳለፍ
በትዳር ያሉ በመኝታ ከመተዋወቅ መታቀብ
ቢቻል አመጋገባችንን ከወትሮው መቀነስ።
4. ስለ ሰሞነ ሕማማት በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈ አለን?
👉🏾ነብዩ ኢሳይያስ "በእውነት ደዌአችንን ተቀበለ ሕማማችንንም ተሸክሞአል "
ኢሳ.53፤4 ይላል።
ሕማማት የሚለው ቃለ በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ ተወሰደ ሲሆን የጌታን
መከራ የምናስብበት ሳምንት ነው።
የጌታችንን ሞቱን ሕማሙን ማሰብ መዘከር እንደሚገባ ቅዱስ ጳውሎስ እነዲህ ይላል፦
" ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና" 1ቆሮ.11፤26።
ይህ ሳምንት ለአይሁድና ለመሰሎቻቸው የደስታ ወቅት ቢሆንም
ለክረስትያኖች በጥልቅ ኅዘን ውስጥ የሚገቡበት ሳምንት ነው
እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ ''እናንተ ታለቅሳላችሁ ሙሾም ታወጣላችሁ
ዓለም ግን ደስ ይለዋል እናንተም ታዝናላችሁ ነገር ግን ኃዘናችሁ ወደ ደስታ
ይለወጣል'' ዮሐ16፤20
በእርግጥ ኃዘናችን ትንሳኤውን እሰክናይ ለጥቂት ጊዜ ቢሆንም ግን እናዝናለን
በትነሳኤው ደግሞ ደስታውን እንካፈላለን።
👉🏾ሰኞ አይሁድ እንዴት እንደሚይዙት ለመማከር ክፉ ጉባኤያቸውን ጀመሩ።
''በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የሕዝብም ሽማግሎች ቀያፋ በሚባለው
በሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ ጌታ ኢየሱስንም በተንኮል ሊያስይዙት ሊገሉትም ተማከሩ" ማቴ26፡3_4።
ይህንን ጉባዔ ቅዱሰ ዳዊት የከፉዎቸ ጉባዔ እያለ ይጠራዋል።
"ብዙ ውሾች ከበውኛልና የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ" መዝ21፤16 አይሁድ ሰኞ የጀመሩትን ዕረቡ ውሳኔአቸውን አጠናቀው በምሴተ ሐሙስ ከዕራትና ከቁርባን በኋላ ሰይፍ ጎመድ ይዘው መጡ።
በፈቃዱ ራሱን አሳልፎ ሰጣቸው ያዙትም እስከ አርብ ስድስት ሰአት
ሲያንገላቱት ቆይተው ከብዙ መከራ በኋላ ሰቀሉት ዘጠኝ ሰአት ላይ ቅድስት ነፍሱን በፈቃዱ ከቅዱስ ስጋው ለየ። ከአሰራ አንድ ሰአት በፊት ዮሴፍና ኒቆዲሞስ በምስጋና ገንዘው ቀበሩት።
ከሕማሙ ከመከራው በረከት ያሳትፈን ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን።
👉🏽ትምህርቱ ለሌሎችም ይጠቅማልና ሼር ያድርጉ!
"ጌታዬ እጠበኝ"
እግሮቼ የዛሉ ብዙ የተጓዝኩኝ
በቀኝ በግራ ስል መድረሻ ያጣሁኝ
ከጠባቧ መንገድ መርጬ ሰፊውን
በሰፊው ጎዳና ላይ እታች ስኳትን
ንጽሐ ሰውነቴን በበደል ያቆሸኩ
ንጽሐ ልቦናዬን በክፋት ያሳደፍኩ
በኃጥያት ቀንበር ሸክሜ ያጎበጠኝ
ውስጤ ክፋት ሞልቶት ጉልበቴ የከዳኝ
በነፍስ በስጋዬም እጅግ ደካማ ነኝ
ምህረትን የምሻ ተግባር የጎደለኝ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ልክ እንደ መጻጉ እንደ ምስኪኑ ሰው
ባህር ውስጥ ሚከተው ዘመድ እንደሌለው
መዳንን ትሻለክ ብለክ የጠየከው
በባህር ውስጥ ሚከት የለኝም መልካም ሰው
ብሎ እንደመለሰው
አይደለሁም እኔ አልጋ ላይ የቀረው
አካሌ የከዳኝ የቆምኩ የመሰለኝ
አልጋህን ተሸክመህ ሂድም እንዳትለኝ
በኃጢያት በሽታ መታመሜን ማላምን
መድኅኒት እንዳላገኝ ህመሜን ምሸሽግ በሽተኛ ሰው ነኝ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እንደ ባለሽቶዋ መግደላዊት ማርያም
አንተ ባረፍክበት ማንም ባይጠራትም
ከእግሮችህ ስር ወድቃ ሽቶዋን አፍስሳ
በእንባዋ አጥባ በፀጉራ አብሳ
ከኃጢያት እስራት ስትፈልግ መላቀቅ
በንሰሃ ልንቦናዋ ምህረትን ስጠይቅ
እንደ ሰዎች ሳይሆን ልቧን ተመልክተክ
ዳግም እንዳበድዪ ብለህ እንደማርካትክ
አይደለሁም እኔ ከእግር ስር የምወድቅ
ሽቶን የማላፈስ እንባዬም ነው ደረቅ
ለታይታ የምኖር ሰዎች ምን ይሉኛል ምል
በኃጥያት ቆሽሼ ንጹህ ሰው ስመስል
የምህረት ቀኔን በከንቱ ማሳልፍ
ልበ ደንዳና ነኝ ምግባሬም የሰንፍ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ቀድመህ እንደነገርከው ለሐዋርያው ጴጥሮስ
ሥስቴ እንደሚክድህ ፍርሃት በልቡ ሲነግስ
አላቀውም ብሎ ዶሮ እስኪጮህ ድረስ
የንሰሃው ዶሮ ለጸጸት ሲያነቃው
ፊትህን አዙረህ በትዝብት ስታየው
መበደሉን ገብቶት ህሊናውን ሊወቅስ
የንሰሀን እንባ ከአይኖቹ ቢያፈስ
ምህረትን ሲሻ መጸጸቱን አይተክ
በደሉን እረስተክ ንስሀውን ተቀበልክ
እኔ ግን ደካማው በጊዜዬ ያልነቃው
ኃጥያቴን እያወኩ ንስሃ ያልገባው
የንሰሃው ዶሮ ሰልሶ ቢጮህም
ፊትህም ወደኔ በምህረት ቢዞርም
ኅሊናዬ ገብቶት ልቤ አልደነገጠም
የንስሃም እንባም ከዐይኖቼ አሎጣም
።።።።።።።።።።።።።።።፡።፡።።።።።።።።
እናም ጌታዬ ሆይ እኔ ምለምንክ
በኃጥያት ላደፍኩኝ እንዲሆነኝ ምህረትክ
በበደል ዳክሬ ቆሽሻለውና
ሆሳዕና ጌታ ፈጥነህ ወደኔና
ደንዳናውን ልቤን እንድታለሰልሰው
የልቤን መዝጊያ በር በፍቅርህ ስበረው
በኃጥያት ሸክም የዛለ አካሌን
ጉልበቴ ሆነከኝ ልስበረው ቀንበሬን
እንደ መጻጉ አልጋን ባልሸከም
የኃጥያት እግሬ ነጽቶ በንጽሐ እድቆም
ከኃጥያት ልንፃ በፍቅርህ እጠበኝ
ከበረዶም ይልቅ በምህረትህ አንፃኝ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ገጣሚ፦ በላይ ኃ/ሚካኤል
@ortodoxtewahedo
#የሰሙነ_ሕማማት_ረቡዕ
#ምክረ_አይሁድ_ይባላል
ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር ያጠናቀቁበት ቀን ነውና፡፡ በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ቀን የተቃረበ በመሆኑ ብዙው ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለ ነበር ሁከት እንዳይፈጠር ነው፡፡ በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል፡፡ (ማቴ. 26÷1-14፣ ማር. 14÷1-2፣ ሉቃ. 22÷1-6) የሐዲስ ኪዳን ካህናትና ምእመናን በዚሁ ዕለት በቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው መላ ሰውነታቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው የሞት ፍርዱን በማሰብና በማልቀስ ሐዋርያት ከጌታችን መያዝ በኋላ በኀዘን በፍርሐት እንደነበሩ እያሰቡ መጻሕፍትን በማንበብ በጾም በጸሎትና በስግደት ተወስነው ይቆዩና ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡
#የመልካም_መዓዛ_ቀንም_ይባላል
ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት (ባለሽቱዋ ማርያም) "ከእንግዲህ ወዲህ በኃጢአት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ ኃጢአትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ" ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የተሞላ ሽቱ ይዛ በመሔድ በጠጉሩ (በራሱ) ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባችው ረቡዕ የመዓዛ ቀን ይባላል፡፡
#የእንባ_ቀንም_ይባላል
ማርያም እንተ እፍረት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና። (ማቴ. 26÷6-13፣ ማር. 14÷9፣ ዮሐ. 12÷8) ኃጢአትን በማሰብ ማልቀስና ራስን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ማቅረብን ከምታስተምረን ማርያም እንተ እፍረት እንባን ለንስሐ ሕይወት ልንጠቀምበት ይገባል፡፡
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ እግዚአብሔር ለብርሃነ ትንሣኤሁ በፍስሐ ወበሰላም።
http://t.me/ortodoxtewahedo
ከበሮ፣ጸናጽል፣መቋሚያና ከ፲ በላይ ቅዱሳት መጻሕፍትን የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን በቅጂና ተዛማች መብቶች ሥራ ተመዝግቦ ከሚያዚያ ፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ/ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አእምሯዊ ንብረት መሆኑ ተረጋግጧል።
ከዚህ ቀደምም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ በአእምሯዊ ንብረት ዐቢይ ኮሚቴ አማካኝነት በርካታ የቤተክርስቲያን ንብረቶች ተመዝግበው እውቅና ማግኘታቸውን የመምሪያው ኃላፊ መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ ገልጸዋል።
ምንጭ ፦ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
@ortodoxtewahedo
✝ጌታቸው ይፈልጋቸዋል✝
ሆሳዕና
Size:-111.4MB
Length:-2:00:19
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
ለመቀላቀል
👉 @ortodoxtewahedo
#ሰሙነ ሕማማት (ዘሰሉስ)
ማክሰኞ
#የጥያቄ ቀን በመባል ይታወቃል፡፡ ምክንያቱም ሹመትን ወይም ሥልጣንን ለሰው ልጅ የሰጠ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሰኞ ባደረገው አንጽሖተ ቤተ መቅደስ ምክንያት በዚህ ዕለት ስለ ሥልጣኑ በጻሕፍት ፈሪሳውያን ተጠይቋልና፡፡
ጥያቄውም ከምድራውያን ነገሥታት፣ ከሌዋውያን ካህናት ያይደለህ ትምህርት ማስተማር፣ ተአምራት ማድረግ፣ ገበያ መፍታት በማን ሥልጣን ታደርጋለህ? የሚል ነበር ይህንስ ሥልጣን እነዚህን እንዳደርግ እነግራችኋለሁ፡፡ የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረች? ከሰማይ ወይስ ከሰው? አላቸው፡፡ እነርሱም ከሰማይ ነው ብንል ለምን አልተቀበላችሁትም?
ይለናል፡፡
ከሰው ነው ብንል ሕዝቡ ሁሉ ዮሐንስን እንደ አባት ያከብሩታል፤ እንደ መምህርነቱም ይፈሩታልና ሕዝቡን እንፈራለን ተባብለው ወዴት እንደሆነ አናውቅም ብለው መለሱለት፡፡ እርሱም በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ እኔም አልነግራችሁም አላቸው፡፡
ይህንንም መጠየቃቸው እርሱ የሚያደርጋቸውን ሁሉ በራሱ ሥልጣን እንዲያደርግ አጥተውት አልነበረም፡፡
/channel/ortodoxtewahedo
#ሕማማት መስቀል " ተብለው የሚዘከሩት አሥራ ሦስት ሲሆኑ እነዚህም፦
1. በብረት ሐብለ መጋፊያና መጋፊያው እስኪጋጠም ድረስ የኋሊት መታሰሩ
2. ከአፍንጫው ደም እስኪውጣ ድረስ 25 ጊዜ በጡጫ መመታቱ
3. 65 ጊዜ ከግንድ ማጋጨታቸው
4. 120 ጊዜ በድንጋይ ፊቱን መመታቱ
5. 365 ጊዜ በሽመል መደብደቡ
6. 80 ጊዜ ጽህሙን መነጨቱ
7. 6666 ጊዜ መገረፉ
8. አክሊለ ሦክ በራሱ ላይ መደፋቱ
9. 136 ጊዜ በምድር ላይ መውደቁ
10. ሳዶር፡ አላዶር፡ ኤዴራ፡ ዳናትና ሮዳስ በሚባሉ 5ቱ ቅንዋተ መስቀልበችንካር መቸንከሩ
11. መራራ ሐሞትን መጠጣቱ
12. መስቀሉን ተሸክሞ መንገላታቱ
13. በመስቀል መሰቀሉ ናቸው።
/channel/ortodoxtewahedo
#በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
#እንኳን ለሰሙነ ሕማማት በሰላም አደረሰን/ አደረሳችሁ
እነዚህን የሰሙነ ሕማማት ቀናት ከሁሉ አሰቀድመን በፍርሃት ና በርአድ በመንቀጥቀጥ የክርስቶሰን ሕማሙን ፣ ግርፋቱን ፣ ስቃዩን ፣ በመስቀል ተቸንክሮ ራሱን ስለ ሁሉ ቤዛ አድርጎ የደረሰበትን መከራ ስቃይ እያሰብን የምናሳልፈው ሳምንት ነው፡፡
በተጨማሪ በሕማማት ሰሞን ውስጥ ወደ ግእዝም ሆነ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡና የምንጠቀምባቸዉ ፦
➊የዕብራይስጥ(hebrew)
➋የቅብጥ (ግብጽ) (coptic)
➌የግሪክ (ጽርዕ) (greek) ቃላት ይገኛሉ፡፡
የእነዚህ ቃላት ትርጉም በጥቂቱ እንደሚከተለዉ ነዉ፡፡
♦️ኪርያላይሶን ፦
ቃሉ የግሪክ(ጽርዕ) ሲሆን አጠራሩ "ኪርዬ ኤሌይሶን" ነዉ፡፡ "ኪርያ" ማለት "እግዝእትነ / እመቤታችን" ማለት ሲሆን "ኪርዬ" ማለት ደግሞ "እግዚኦ / ጌታ ሆይ / አቤቱ" ማለት ነዉ፡፡ "ኤሌይሶን" ማለት ደግሞ "ማረን / ይቅር በለን" ማለት ነዉ ፡፡ ሲጠራም "ኪርዬ ኤሌይሶን" መባል አለበት፡፡ ትርጉሙም "አቤቱ ማረን" ማለት ነዉ፡፡ "ኪራላይሶን" የምንለዉ በተለምዶ ነዉ፡፡ ይኸዉም "ኪርዬ" ከሚለዉ "ዬ" ኤሌይሶን" ከሚለዉ ደግሞ "ኤ" በመሳሳባቸዉ በአማርኛ "ያ"ን ፈጥረዉ ነዉ፡፡
♦️ናይናን ፦
የቅብጥ(ግብጽ) ቃል ሲሆን "መሐረነ / ማረን" ማለት ነዉ፡፡
♦️አብኖዲ ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን "አምላክ" ማለት ነዉ፡፡ "አብኖዲ ናይናን" ሲልም "አምላክ ሆይ ማረን" ማለት ነዉ ፡፡
♦️ታኦስ ፦
የግሪክ ቃል ሲሆን "ጌታ / አምላክ" ማለት ነዉ፡፡ "ታኦስ ናይናን" ሲልም "ጌታ ሆይ ማረን" ማለት ነዉ፡፡
♦️ማስያስ ፦
የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን "መሲሕ" ማለት ነዉ፡፡ "ማስያስ ናይናን" ሲልም "መሲሕ ሆይ ማረን" ማለት ነዉ፡፡
♦️ትስቡጣ ፦
"ዴስፓታ" ከሚለዉ የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን "ደግ ገዢ" ማለት ነዉ፡፡
♦️ሙዳሱጣ ፦
የግሪክ ቃል ሲሆን "ነበልባላዊ" ማለት ነዉ፡፡
♦️ መዓግያ ፦
የግሪክ ቃል ሲሆን "እሳታዊ" ማለት ነዉ፡፡
♦️አንቲፋሲልያሱ ፦
ቃሉ "በመንግስትከ / በመንግስትህ" ማለት ነዉ፡፡
♦️አምንስቲቲ ሙኪርያቱ አንቲፋሲልያሱ ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን "ተዘከረነ እግዚኦ በዉስጠ መንግስትከ / አቤቱ በመንግስትህ አስበኝ" ማለት ነዉ፡፡
♦️አምንስቲቲ መዓግያ አንቲ ፋሲልያሱ ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን "ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በዉስጠ መንግስትከ / ቅዱስ ሆይ በመንግስትህ አስበን" ማለት ነዉ፡፡
♦️አምንስቲቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋሲልያሱ ፦
የቅብጥ ቃል ሲሆን "ተዘከረነ እግዚአ ኲሉ መንግስትከ / የሁሉ የላይ የሆንክ ሆይ በመንግስትህ አስበን" ማለት ነዉ፡፡
♦️ኤልማስ ፦
የግሪክ ቃል ሲሆን "አምላኪየ / አምላኬ" ማለት ነዉ፡፡
♦️አህያ ሸራህያ ፦
የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን "ያለና የሚኖር" ማለት ነዉ፡፡
እነዚህ ከላይ ያሉና ሌሎች ቃላት ከሌሎች ቋንቋዎች በቀጥታ የተወሰዱ ናቸዉ፡፡
✿✿✿መልካም የሰሙነ ሕማማት ወቅት ይሁንልን ✿✿✿
ስብሐት ለከ፤
ሰጊድ ለአቡከ፤
ዕበይ ለመንፈስከ፤
ወምህረተ ፈኑ ለሕዝብከ፤
ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡፡
ሙሉዉን ያነበበ ብቻ አሜን ይበል፡፡
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽዐነ በፍሥሐ ወበሰላም
#ለመቀላቀል #ከታች #ሠማያዊውን #ይጫኑ
#JOIN #OUR #CHANNE
/channel/ortodoxtewahedo
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
አሜን
┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈
ሥርዓተ ጸሎት ሰሙነ ሕማማት ከሰኞ እስከ አርብ ካህናት እያዜሙ እየሰገዱ እኛም እየተቀበልን እያዜምን የምንሰግድበትን ሥርዓት ለማውቅ እና ለመፈፀም ከስር ያንብቡ
┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈
❖ ከሰኞ ጀምሮ እስከ ዓርብ ድረስ ባሉት ቀናት ውስጥ በመጀመሪያ ዲያቆኑ ቤተክርስቲያኑን ሦስት ጊዜ ዞሮ ደወል ካሰማ በኋላ መቶ አምሳው ዳዊት ይታደልና ይደገማል፡፡
❖ የሰባት ቀናት ውዳሴ ማርያምና አንቀጸ ብርሃን እስከ ይዌድስዋ ድረስ ታድሎ ይደገማል፡፡
❖ ከዚያም “እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ዓመ ከመ ዮም ያብጽሐኒ ያብጽሕክሙ አግዚአብሔር በፍሥሓ ወበሰላም” ተብሎ አቡነ ይደገምና በዐራቱም ወንጌላት መሠረት ለእያንዳቸው በእየዕለቱና ሰዓቱ የተመደበውን አቡነ ካህናቱ በቀኝና በግራ እየተፈራረቁ ይመራሉ፡፡
❖ ካህናቱና ሕዝቡም ይቀበላሉ፤ በመቀጠል
#ትእዛዝ
❖ ሕዝቡ በጸሎት በተሰበሰቡ ጊዜ ጠዋት ወይም በ3፣ በ6፣በ9፣ በ11ሰዓተ መዓልት መጀመሪያ ሕዝቡ እየሰገዱና እየተከተሉ እንዲህ ይበሉ)
❖ "ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም "
❖ "አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም"
❖ " ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም "
❖ " ኃይልየ ወጸወንየ ውእቱ እግዚእየ፤ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኰቴት"
#ትእዛዝ
❖ በዚህ ጊዜ ካህኑ እየተከተሉ አቡነዘበሰማያት ይድገሙ ።
❖ ይህን የላይኛውን ጸሎት እያመላለሱ ከአቡነ ዘበሰማያት ጋር 12 ጊዜ ይበሉ
❖ " ለአምላክ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"
❖ "ለሥሉስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"
❖ "ለማሕየዊ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"
❖ "ለዕበዩ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"
❖ "ለእዘዙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"
❖ "ለመንግሥቱ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"
❖ "ስለልጣኑ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"
❖ "ለኢየሱስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"
❖ "ለክርስቶስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"
❖ "ለሕማሙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"
❖ "ለመስቀሉ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም"
#ትእዛዝ
❖ ይህ ሦስት ጊዜ እየተመላለሰ ይባላል፡፡
❖ በመጨረሻም የሚከተለውን ሦስት ጊዜ እያመላለሱ ይበሉ፡፡
❖ "ለከ ይደሉ ኃይል፣ ወለከ ይደሉ ስብሐት ወለከ ይደሉ አኰቴት ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም"
❖ ካህኑ ‹ጸልዩ በእንተ ጽንዓ ዛቲ . . .› ብሎ በሚያነብ ጊዜ በየምዕራፉ "እግዚኦ ተሳሃለነ" እየተባለ ይሰገዳል፡፡
#ትእዛዝ
❖ ከዚህ ሁሉ በኋላ ሕዝቡ የሚከተሉትን ጸሎት በግራና በቀኝ ይበሉ፤
"ክርስቶስ አምላክነ፤ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ በሕማማቲሁ ቤዝወነ፤ ንሰብሖ ወናልዕል ስሞ ኅቡረ፤ እስመ ውእቱ ገብረ መድኃኒተ በዕበየ ሣህሉ" (በዐርብ) ዘሐመ ወሞተ በእንቲአነ ይባላል፡፡
#ትእዛዝ
❖ ቀጥሎም ሕዝቡ በሁለት ክፍል ሆነው የሚከተለውን ጸሎት ሁለት ጊዜ በመከታተል አንድጊዜ በማስተዛዘል ይበሉት፡፡
ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤
አብኖዲ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን
ናይን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን ፤
ታዖስ ናይን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤
ማስያስ ናይን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤
ኢየሱስ ናይን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤
ክርስቶስ ናይን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤
አማኑኤል ናይን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤
ትስቡጣ ናይን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን፤ ኪርያላይሶን
#ትእዛዝ
❖ ከዚህ በኋላ ኪርያላይሶን አርባ አንድ ጊዜ ይባላል፡፡
❖ ይኸውም በአንድ ወገን 20 ጊዜ በሌላው ወገን 21 ጊዜ በጠቅላላው 41 ጊዜ ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን ኪርያላይሶን እየተባለ ይሰገዳል፡፡
#በመጨረሻ ጊዜ
❖ ስብሐት ለእግዚአብሔር ኪያነ ዘፈጠረ ከመ ናምልኮ (እናመልከው ዘንድ ለፈጠረን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባል)
❖ ስብሐት ለማርያም እመ አምላክ እግእዝትነ ወመድኃኒትነ (እመቤታችንና መድኃኒታችን ለሆነች ለአምላክ እናት ለማርያም ምስጋና ይገባል)
❖ ስብሐት ለመስቀለ ክርስቶስ ዕፀ መድኃኒት ኃይልነ ወፀወንነ(ኃይላችን መጠጊያችን ለሆነ ድኅነት ለተገኘበት ለክርስቶስ ምስጋና ይገባል)፤፤ ጸሎተ ሃይማኖትን ሐመ እስከ ሚለው ድረስ መድገም ነው፡፡ /ከሰኞ እስከ ረቡዕ ይባላል/
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን
http://t.me/ortodoxtewahedo
ኦ አርምሞ ዘመጠነ ዝ አርምሞ ?
ኦ ትዕግስት ዘመጠነ ዝ ትዕግስት?
ኦ ሂሩት ዘመጠነ ዝ ሂሩት ?
ኦ ፍቅር ዘመጠነ ፍቅረ ሠብ ?
( ይህን ያህል ትዕግሥት እንደምን ያለ ትዕግሥት ነው ? ይህን ያህል ዝመታ እንደምን ያለ ዝመታ ነው ? ይህን ያህል ሰውን ማፍቀር እንደምን ያለ ፍቅር ነው ?
ለመቀላቀል
👉 @ortodoxtewahedo
#እውነት_ስለሆነ
#ሊቀ መ ዘምራን ይልማ ሀይሉ
እውነት ስለሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ
ዋለ ባደባባይ ሲሰደብ ሲከሰስ
የሀሰት ዳኝነት አምላክን ወቀሰው
ህይወት ሰጠን እንጂ ጥፋቱ ምንድነው/2/
ከቃሉ እብለትን ባያገኙበትም
ዝምታውን አይተው አላዘኑለትም
ባላወቁት መጠን ጠሉት ካለበደል
ጥፋቱ ምን ይሆን የሚያደርስ ከመስቀል/2/
የልቡን ትህትና ፍቅሩን ሳያስተውሉ
ቸሩ ጌታችንን አቻኩለው ሰቀሉ
እሩህሩሁን ጌታ ቸንክረው ሰቀሉት
ሞትን አስውግዶ ቢሰጣቸው ህይወት/2/
ስለ ቸርነቱ ስድብን ከፈሉት
ስለ ርህራሄው የሾህ አክሊል ሰጡት
ሀሞትና ከርቤ ሆምጣጤ ደባልቀው
መራራ አስጎነጩት ጨክኖልባቸው/2/
ፈውስን ለሰጣቸው ልባቸውን ሞልተው
አሉት ወንበዴ ነው ስቀለው ስቀለው
ከጁ በረከትን የተሻሙ ሁሉ
ይጮሁ ነበረ ይገደል እያሉ/2/
💚 /channel/ortodoxtewahedo 💚
💛 /channel/ortodoxtewahedo 💛
❤️ /channel/ortodoxtewahedo ❤️
#ሕማሙን ልናገር
#ሊቀ መዘምራን ይልማ ሀይሉ
ሕማሙን ልናገር *አንደበት ቢያጥሩኝም*/2/
መቼም ምንም ቋንቋ *ለዚህ አይገኝም*/2/
ከረጂሙ በጭር *ከሰፊው በጠባብ*/2/
ስለከፈለልኝ *ስለጌታ ላስብ*/2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
በጌቴሴማኒ *በአታክልቱ ቦታ*/2/
ምድሪቷ ተሞልታ *በታላቅ ጸጥታ*/2/
የአዳምን ልጅ ስቃይ *በደሉን ሊሸከም*/2/
ጌታችን አዘነ *ተጨለቀ በጣም*/2/
ሐዋርያት ደክመው *ተኝተው ነበረ*/2/
ይሁዳ ከአይሁድ *እንደተማከረ*/2/
ጭፍሮች እየመራ *ጌታውን ሊያስገድል*/2/
የተሠራለትን *ቸርነት ሳይቆጥር*/2/
ፋና እያበሩ *ጭፍሮቹ ሲመጡ*/2/
ጌታን ሊያንገላቱት *እንደዚያ ሲቆጡ*/2/
የአምላኩን ጠላቶች *መንገድ እመራ* /2/
ይሁዳ ብቅ አለ *ከቀያፋ ጋራ* /2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
ላቡ ከግንባሩ *እንደ ውኃ ሲወርድ*/2/
በታላቅ ይቅርታ *ጌታችን ሲራመድ*/2/
ምስኪኖችን ሊያጠግብ *ድሆችን ሊታደግ*/2/
ኢየሱስ ቀረበ *እንደሚታረድ በግ*/2/
ይሁዳ ጉንጮቹን *ሳመው በክህደት*/2/
የተማከረውን *የማያውቅ መስሎት*/2/
የአይሁድም ጭፍሮችም *ያዙት ተናጠቁት*/2/
በታላቅ ጭካኔ *በሰንሰለት መቱት*/2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
በጲላጦስ ችሎት *አቁመው ከሰሱት*/2/
ንጹሑ እየሱስ *ይሙት በቃ አሉት*/2/
እጆቹን ቸንክረው *በጠንካራ ብረት*/2/
በእፀመስቀሉ *ቀራንዮ ዋለ*/2/
ወልደ እጓለዕመኅያው *ተጠማሁ እያለ*/2/
ሐሞት እና ከርቤ *ቀላቅለው አጠጡት*/2/
እረ እንዴት ጨከኑ *በምሬት ላይ ምሬት*/2/
------------------------------------------
ሕማሙን ልናገር አንደበት ቢያጥሩኝም
መቼም ምንም ቋንቋ ለዚህ አይገኝም
ከረጂሙ በጭር ከሰፊው በጠባብ
ስለከፈለልኝ ስለጌታ ላስብ
አዝ . . . . . . . . . . . //
ፍጥረታት ተጨንቀው በአይሁድ ክፋት
በየተፈጠሯቸው እርቃሉን ሸፈኑት
ጨረቃ ደም ሆነች ፀሐይም ጨለመች
አልፋና ኦሜጋ ተሰቅሎ ስላየች
ከዋክብት እረግፈው ምድር ተናወጠች
መባርቅትም ታዩ ተቆጣ ባሕሩ
መለሳቸው እንጂ ስለፈጹም ፍቅሩ/2/
ከወንበዴ ጋራ ከመሀል አድርገው
ጌታን አንገላቱት በመስቀል ላይ ሰቅለው
በቀኝ የነበረ ወንበዴው ለመነው
በመንግሥትህ ጌታ አስበኝ እያለው
አዝ . . . . . . . . . . . //
ከመስቀሉ በታች ዮሐንስን አየው
እስከመስቀል ድረስ ስለተከተለው
ታላቋን ስጦታ እናቱንም ሰጠው
ተፈፀመ አለ ጌታ ህይወቱን ሰጠ
ሞትንም ከሕዝቡ በፍጹም ቆረጠ/2/
አዝ . . . . . . . . . . . //
እንደተለመደው ዲያቢሎስ ቀረበ
ነፍሳትን ለመብላት እርሱ እንደተራበ
ፍጡር መስሎት ነበር በመስቀል ላይ ያለው
በአራቱም ማዕዝን በንፋስ ወጠረው
በሲኦል ወረደ በኃይሉ ብርሃን
ማረከ ጌታችን የአዳም ልጆችን
በሦስተኛውም ቀን ጌታችን ተነሳ
ሞትን ድል ያረገው የይሁዳ አንበሳ
በቃ ተወገደ የሰው ልጅ አበሳ /2/
#ሼር_share በማድረግ ለወዳጅ ዘመድዎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓት የጠበቁ ፅውፎች ለማንበብ ሆነ ለመማር፡፡
ለመቀላቀል
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
💠 http://t.me/ortodoxtewahedo 💠
💠 http://t.me/ortodoxtewahedo 💠
💠 http://t.me/ortodoxtewahedo 💠
እግዚአብሔር ሃገራችንን እና ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን የእመቤታችን ምልጃና ጸሎት አይለየን ።
#ጌታችን በመስቀሉ ከ6-10 ሰዓት በመስቀልላይ ሳለ የተፈጸሙ 7ቱ
ተአምራቶች፤
1ኛ. ፀሐይ ጨለመች
2ኛ. ጨረቃ ደም ሆነች
3ኛ. ከዋክብት ብርሃናቸውን ነሱ
4ኛ. የቤተመቅደስ መጋረጃ ለሁለት ተከፈለ
5ኛ. ዐለቶች ተሰነጣጠቁ
6ኛ. መቃብራት ተከፈቱ
7ኛ. የሞቱት ተነሡ፤ ማቴ.27፤45-46
ጌታችን ከ6-9 ሰዓት በመስቀል ላይ ሳለ የተናገራቸው 7ቱ የፍቅር
ቃላት
1ኛ.ኤሎሄኤሎሄ ኤልማስላማሰበቅታኒ ማቴ.27፤46
2ኛ. እውነት እውነት እልሃለሁ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትኖራለህ፡፡
ሉቃ.23፤43
3ኛ.አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራእሰጣለሁ፡፡ ሉቃ.23፤46
4ኛ.አባት ሆይየሚያደርጉትን አየውቁምናይቅር በላቸው፤ሉቃ.2334
5ኛ. እናትህ እነኋት፤ እነሆ ልጅሽ፤ዮሐ.19፤26-27
6ኛ. ተጠማሁ፤ ዮሐ.19፤30
7ኛ. ተፈጸመ፤ ዮሐ.19፤30
13ቱ ሕማማተ መስቀል
1ኛ. ተአስሮ ድኅሪት (ወደኋላ መታሰር)
2ኛ. ተስሕቦ በሐብል (በገመድ መሳብ)
3ኛ. ወዲቅ ውስተ ምድር (በምድር ላይመውደቅ)
4ኛ. ተከይዶ በእግረ አይሁድ (በእግረ አይሁድመረገጥ)
5ኛ. ተገፍዖ ማዕከለ ዓምድ (ከምሶሶ ጋርመላተም)
6ኛ. ተጽፍዖ መልታሕት (በጥፊ መመታት)
7ኛ. ተቀሰፎ ዘባን (ጀርባን በጅራፍ መገረፍ)
8ኛ. ተኰርዖተ ርእስ (ራስን በዱላ መመታት)
9ኛ. አክሊለ ሦክ (የሾህ አክሊል መድፋት)
10ኛ. ፀዊረ መስቀል (መስቀል መሸከም)
11ኛ. ተቀንዎ በቅንዎት (በችንካር መቸንከር)
12ኛ. ተሰቅሎ በዕፅ (በመስቀል ላይመሰቀል)
13ኛ. ሰሪበ ሐሞት (መራራ ሐሞትንመጠጣት)
ስብሐትለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱድንግል
ወለመስቀሉክቡር
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
/channel/ortodoxtewahedo
👆👆👆👆👆👆👆👇👇👇
#ዕለተ_ዓርብ፤ #ዕለተ_መድኃኒ
#በዲ/ን_በረከት_አዝመራ
"#ለመስቀልከ ንሰግድ ኦ ሊቅነ፤ ጌታችን (መምህራችን) ሆይ! ለመስቀልህ እንሰግዳለን፡፡"
***
"ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም፤ ኃይል ክብር ምስጋና እና ብርታት ለአንተ ይገባል"
በሰሙነ ሕማማት #በስግደት ወቅት ደጋግመን የምንለው #ምስጋና ነው:: ጌታችን ለሰው ልጆች #ድኅነት መከራ ተቀብላሏል: በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ስለእኛ ሞትን በፈቃዱ ቀምሷል:: ይህ ድካም የመሳላቸው ብዙዎች ናቸው:: (አጋንንት፣ ብዙኃኑ አይሁድ፣ መናፍቃን)
ቤተ ክርስቲያን መከራውና ሞቱ የድካም ሳይሆን የካሳ መሆኑን እና ብርቱ የሰው ልጆች ጠላቶች (ኃጢአት፣ ሞት፣ ዲያብሎስ) የተሸነፉበት መሆኑን በማወቅ 'ኃይል ክብር ምስጋና እና ብርታት የአንተ ነው' በማለት ታመሠግነዋለች:: ይህን ምሥጋና ቀድሞ መላእክት #በመስቀሉ ሥር #እየሠገዱ ተናግረውታል::ኪርያላይሶን (ጌታ ሆይ ማረን)
ክርስቶስን ለመከራ ያደረሰው የሰው ኃጢአት ነው:: መከራና ሞቱም #የምሕረት ምንጭ ነው:: በዚህም ምክንያት ኃጢአታችንን እያሰብን እና በመስቀል የተገለጠውን #ምሕረት እና #ፍቅር እያመንን 'ኪርያላይሶን ጌታ ሆይ ማረን' እያልን እንሰግዳለን:: 'እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ' በማለትም ደጋግመን
#እንማጸናለን::
ምስባካት እና ምንባባት
ዲያቆናት ከዳዊት መዝሙር ስለ መከራው እና ሞቱ የተነገሩ ትንቢቶችን በሚያሳዝን ዜማ ይሰብካሉ፤ ሕዝቡም በስግደት ይቀበላል:: ካህናትም በየሰዓታቱ የተደረጉ ድርጊቶችን የሚገልጹ #የወንጌል ምንባባትን ያነባሉ:: ሁሉም በስግደት ይታጀባሉ፤ በየመካከሉ ካህናት የእጣን ማእጠንት እየወዘወዙ ያጥናሉ:: ይህም #ክርስቶስ መልካም መዓዛ ያለው ንጹሕ #መሥዋዕት ሆኖ መቅረቡን ያዘክራል:: የሕዝበ ክርስቲያኑ #ጸሎትና ተዘክሮም ከዕጣኑ ጋር አብሮ ያርጋል::
"አምነስቲቲ ሙኪርያ አንቲ ፋሲልያሱ..."
ካህናቱ እየመሩ ሕዝቡ እየተከተሉ 'አምንስቲቲ ' እያሉ በሚያሳዝን ዜማ ይጸልያሉ:: 'አቤቱ በመንግስትህ አስበን' ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቁጭ ተብሎ ራስ በነጠላ ውስጥ ይሸፈናል:: ጸሐይ ስትጨልም እና የክርስቶስ #ዘላለማዊ ንጉሥነት ሲገለጥ በቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ (ፈያታዊ ዘየማን) #የጸለየው ጸሎት ነው:: ከሁሉ ቀድሞ #ገነት ያስገባውን ጸሎቱን ጸሎታችን አድርገን እንጸልያለን::
የድል ቀን
ቤተ ክርስቲያን ሕማሙን ትካፈላለች እንጂ ጌታ በግድ የተሰቀለ ይመስል የሽንፈት #ኃዘን አታዝንም:: ይልቁንም በድካም: በሞት የተገለጠ ፍቅሩን እያሰብን ትእዛዙን እየጠበቅን ከእርሱ ጋር ለመኖር ቃል ኪዳናችን እናድሳለን:: የሚታዘነው ፍቅሩ ሊታየው ላልቻለ እና አሁንም ወደ #መድኃኒት ክርስቶስ መቅረብ ላልቻለ ነው::
በዕለቱ የሚነበቡ የነቢያት መጻሕፍት የድል ቀን መሆኑን ነው የሚነግሩን:: ዓርብ በስድስት ሰዓት የሚነበበው የኢሳይያስ ትንቢት "በዚያም ቀን፡— አቤቱ፥ ተቈጥተኸኛልና፥ ቍጣህንም ከእኔ መልሰሃልና፥ አጽናንተኸኛልምና አመሰግንሃለሁ። እነሆ፥ አምላክ መድኃኒቴ ነው፤ ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌና ዝማሬዬ ነውና፥ መድኃኒቴም ሆኗልና በእርሱ ታምኜ አልፈራም ትላለህ። ውኃውንም ከመድኃኒት ምንጮች በደስታ ትቀዳላችሁ። በዚያም ቀን እንዲህ ትላላችሁ፡— እግዚአብሔርን አመስግኑ፥ ስሙንም ጥሩ፤ በአሕዛብ መካከል ሥራውን አስታውቁ፤ ስሙ ከፍ ያለ እንደ ሆነ ተናገሩ። ታላቅ ሥራ ሠርቷልና ለእግዚአብሔር ተቀኙ፤ ይህንም በምድር ሁሉ ላይ አስታውቁ። አንቺ በጽዮን የምትኖሪ ሆይ፥ የእስራኤል ቅዱስ በመካከልሽ ከፍ ከፍ ብሏልና ደስ ይበልሽ ፤እልልም በዪ" ይላል:: (ኢሳ. 12:1-6)
በዐሥራ አንድ ሰዓትም "ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ: የተመሰገነ እግዚአብሔርን እናመስግነው" የሚለው የእሥራኤላውያንን መዝሙር እንዘምራለን:: እሥራኤል ይህን #ምሥጋና ያመሰገኑት ባህር ከፍሎ እና ፈርኦንን አስጥሞ ወደ #ተስፋዋ ምድር ስላሻገራቸው ነው:: ቤተ ክርስቲያን የምትዘምረው ሞትን አጥፍቶ፣ ዲያብሎስን አሸንፎ፣ ሲኦልን በርብሮ ወደ #ገነት መንግሥተ ሰማያት ስላሻገረን ነው::
/channel/ortodoxtewahedo
💁♂ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ ግዴታዬ ነው የሚል የማንኛውም ኦርቶዶክስ ሊቀላቀለው የሚገባ ቻናል። ጥያቄ ይጠየቃል ምዕመኑም ይሳተፋል
ቻናሉን ለመቀላቀል ከስር ክፍት የሚለውን
መጫን በቂ ነው።
ክፈት ክፈት
ክፈት ክፈት
ክፈት ክፈት ክፈት ክፈት
ክፈት ክፈት ክፈት ክፈት
ክፈት ክፈት
ክፈት ክፈት
#ፀሎተ ሀሙስ
#ሀሙስ ምሽት ጌታችን ያደረገልን ትህትና ዮሐንስ 13
እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ
እንዲህም አላቸው፦ ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?
እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ እንዲሁ ነኝና መልካም
ትላላችሁ።
እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ
እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ
ይገባችኋል።
እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ
ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና።
እውነት እውነት እላችኋለሁ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም።
መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም። 17 ይህን ብታውቁ
ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ።
ስለ ሁላችሁ አልናገርም እኔ የመረጥኋቸውን አውቃለሁ
ነገር ግን መጽሐፍ፦ እንጀራዬን የሚበላ በእኔ ላይ ተረከዙን
አነሣብኝ ያለው ይፈጸም ዘንድ ነው።
በሆነ ጊዜ እኔ እንደ ሆንሁ ታምኑ ዘንድ ከአሁን ጀምሬ
አስቀድሞ ሳይሆን እነግራችኋለሁ።
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለዘላለም ትኑር በመጀመሪያነት ያጋሩት፦
በሰሞነ ህማማት የሚገኙ እለታትና ስያሚያቸው ........እለተ ሀሙስ -በዚህ እለት ጌታችን አምላካችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ መሆኑን ለመግለፅና ለአርያነት ፀሀፍት ፈሪሳውያን የአይሁድ ካህናት መጥተው እስኪይዙት ድረስ ሲፀልይ በማደሩ ምክንያት ፀሎተ ሀሙስ በመባል ይታወቃል ፡፡
ትህትና ፍቅር መታዘዝ እንድሁም የአገልግሎትም ትርጉም
ለማስረዳትና ለማስገንዘብ እርሱ ጌታ አምላክ ሆኖ ሳለ ዝቅ ብሎ የደቀመዛሙርቱን እግር በማጠቡ ህፅበተ እግር በመባልም እንደሚጠራም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይናገራሉ ፡፡
ሀዋርያው ቅዱስ ዮሀንስም እግራቸውን አጥቦ ልብሱንም አንስቶ ዳግመኛ ተቀመጠ እንድህም አላቸው ያደረኩላችሁን
ታስተውላላችሁን እንግድህ ጌታ መምህር ስሆን እግራችሁን
ካጠብሁ እናንተ ደግሞ ለታናናሾቻችሁ እንድሁ ታደርጉ ዘንድ ይገባችኀል ሲል ተናግራል፡፡ ይኸውም ዮሀንስ ወንጌል 13 ፣12
- 20 በዝርዝር ይገኛል ፡፡
ይህ ለእናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ስጋየ ነው እንካችሁ
ብሉ ይህ ፅዋ ለእናንተ የሚፈሰው የሀዲስ ኪዳን ደሜ ነው ከእርሱ ጠጡ በማለት ሚስጥረ ቁርባንን የመሰረተበት ወይንም
እራሱ ጌታችን አምላካችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ሚስጥረ ቁርባንን የጀመረበት እለት በመሆኑ የሚስጥር ቀን በመባል ይጠራል ፡፡
ይኸውም የሰው ልጆች ስጋውንና ደሙን ተቀብለው ከእርሱ ጋራ
አንድነትንና ህብረትን እንድኖረን ጥንተ ጠላት ዳቢሎስን ድል
ነስተን ሰማያዊዩን እርስት እንድንወርስ ሊያደርግ ነው፡፡ ይህም በማቴወስ 26 ፣ 26 - 29 በዝርዝር ይገኛል ፡፡
አይሁድ ጌታችንን ለመያዝ በእነርሱ ጥበብና ፍላጎት ቀስ ብለው
መጥተው የያዙበት ስለሆነ በዚህ እለት በለ ሆሳስ ወይም ብዙ
የጩኸት ድምፅ ሳይሰማ የቅዳሴ ስርአት ይፈፀማል ፡፡
ስለሆነም መላው ህዝበ ክርስቲያን በዚህ የህፅበተ ሚስጥር የፀሎት እለት በሆነው በዚህ እለት በንስሀ ታጥበው የጌታን ስጋና ደሙን እንድቀበሉ ቤተ ክርስቲያን በአፅኖት ታስተምራለች ፡፡
እኛም በንስሀ ታጥበን ወደ አምላካችን ቀርበን ስጋወ ደሙን
ልንቀበል ይገባናል የጌታችን ቸርነት ፍቅሩ የእመ አምላክ
የንፅሒተ ንፁሀን የድንግል ማርያም ምልጃ የመላክት ጥበቃ
የሠማአታት ፀጋ በረከታቸው በሁላችን ላይ ይደርብን አሜን
አሜን አሜን !!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
http://t.me/ortodoxtewahedo
✝ሕማማት✝
"በሕማማት የሚደረጉና የማይደረጉ ነገሮች"
Size:- 26MB
Length:-1:14:43
በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@ortodoxtewahedo
ሰሙነ ሕማማት
👉 ረቡዕ
ምክረ አይሁድ ይባላል፦ ረቡዕ እለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የመከሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክረ አይሁድ ይባላል። ወቅቱ የፋሲካን በዓል የሚያከብሩበት ቀን በመሆኑ እና ብዙ ህዝብም ጌታን ይከተለው ስለነበር ሁከት እንዳይነሳ ስጋት ነበራቸው። ነገር ግን ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ስለነገራቸው /ሉቃ ፳፪፥፩-፮/ጭንቀታቸው ተወግዶ በጌታ መያዝ ተስማምተዋል።
የመልካም መዓዛ ቀንም ይባላል፡- ጌታችን በዚህ ዕለት በለምጻሙ በሰምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት/ባለሽቶዋ ማርያም/ ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ የአልባጥሮስ ሽቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ማቴ ፳፮፥፮-፯ የመዓዛ ቀን ይባላል።
የእንባ ቀን ይባላል፡- ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ እፍረት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እየለመነች በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አርሳለችና ማር ፲፬፥፱ የእንባ ቀን ይባላል።
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻም ወድካም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም።
👉 @ortodoxtewahedo
እንበለ ደዌ ወሕማም
እንበለ ፃማ ወድካም
አመ ከመ ዮም
ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሣኤሁ
እግዚአብሔር በፍስሓ ወበሰላም!
"ያለ ደዌና ያለ ሕማም፥ ያለ ፃማና ያለ ድካም እግዚአብሔር ለትንሣኤው ብርሃን እንደ ዛሬ ቀን በደስታና በፍቅር በአንድነት ያድርሰን ያድርሳችሁ!"
አሜን!
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
#ቤተ_ክርስቲያን_መሄድ_ለማትችሉ_ሰሙነ_ሕማማትን_በስደት_በሥራ_ለምታሳልፉ_በየቤታችሁ_ሁናችሁ_ለምትሰግዱ_እንዲህ_እያላችሁ_ስገዱ 🙏
👉በመጀመሪያ በስመአብ ብለን የዘወትር ጸሎትን አድርሰን ውዳሴ ማርያምን ቆመን እንደግማለን
በመቀጠል
👉 ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም
👉 አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከለዓለመ ዓለም
👉 ኦእግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከለዓለመ ዓለም
👉 ኃይልየ ወጸወንየ ውእቱ እግዚእየ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኮቴት
🙏 አቡነ ዘበሰማያት / አባታችን ሆይ/
ከቻልን እየመላለስን 12 ግዜ እያልን መስገድ 12 ጊዜ ካልቻልን የቻልነውን ያህል
👇 ይህን ስንጨርስ በዛው ቀጥለን
🙏 ለአምላክ ይደሉ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም
🙏 ለስሉስ ይደሉ ክብር
🙏 ለማኅየዊ ይደሉ ክብር
🙏 ለእዘዙ ይደሉ ክብር
🙏 ለመንግሥቱ ይደሉ ክብር
🙏 ለሥልጣኑ ይደሉ ክብር
🙏 ለምኩናኑ ይደሉ ክብር
🙏 ለኢየሱስ ይደሉ ክብር
🙏 ለክርስቶስ ይደሉ ክብር
🙏 ለሕማሙ ይደሉ ክብር
👉 እስከ አርብ ድረስ እስከዚህ ሲሆን አርብ ለመስቀሉ ይደሉ ይጨምራል
እንዲህ እያልን ከሰገድን በኋላ መዝሙረ ዳዊትን መጽሐፍ ቅዱስ ከኦሪት ከነቢያት ከወንጌል የቻልነውን እናነባለን
ከዛም 👇
👉 ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን ኪርያ ላይሶን
👉 ክርያላይሶን ኪርያላይሶን ዕብኖዲ ናይን ኪርያላስይሶን
🙌 ታኦስ
🙌 ማስያስ
🙌 ኢየሱስ
🙌 ክርስቶስ
🙌 አማኑኤል
🙌 ትስቡጣ
👇 እንዲህ እያልን ከሰገድን በኋላ
✋ 41 ጊዜ የቻለ ከዛም በላይ ኪርያላይሶን እያሉ መስገድ ነው።
✍ የቃላት ትርጉም
👉 ኪርያላይሶን ማለት ቃሉ ግሪከኛ ሲሆን አቤቱ ማረን ማለት ነው
👉 ዕብኖዲ ማለት የግጽ ቅብጥኛ ሲሆን አምላክ ማለት ነው
👉 ናይን /ናይናን/ ማለት እኛን ማረን / ቅብጥኛ/
👉 ታኦስ / ግሪከኛ / አምላክ
👉 ማስያስ ።/ እብርይስጥኛ / መሲሕ
👉 ኢየሱስ መድኃኒት
👉 ክርስቶስ ንጉሥ ቅቡዕ የባሕርይ አምላክ
👉 ትስቡጣ /ግሪክኛ / ደግ ገዥ
🤝 የቃሉን ትርጉም እንዲህ እያሰብንና እየተረዳን መስገድ ይገባናል ።ላስተማሩን አባቶቻችን ቃለ ህይወት ያሰማልን።
/channel/ortodoxtewahedo
#ይህ ሳምንት ከሰርከ ሆሳዕና እስከ ትንሣኤ ያሉትን ቀናት
ያካትታል::
#የጌታን መከራ እንግልት መሰቀል መሞት መቀበር የምናስብበት ነው:: ለእኛ ሲል የተቀበላቸውን 13ቱ ሕማማተ መስቀል በማሰብ በልቅሶ በስግደት በጸሎት ልናሳልፈው
ይገባል:: በዚህ ሳምንት ሊሰሩ ያልተፈቀዱ በርካታ ናቸው::
በመስቀል መባረክ ማማተብ መሳቅ መሳሳም ከሴት ጋር
መገናኘት ኑዛዜ መፈጸም ፈጽሞ የተከለከለ ሲሆን የ5500ው
የጨለማ ዘመን መታሰቢያ በመሆኑ መንበሩ በጥቁር ልብስ
ይሸፈናል ካሕናትም ጥቁር ይለብሳሉ:: በዚህ ሳምንት ለሞተ
ጸሎተ ፍትሐት አይጸለይለትም ክርስትናም እንዲሁ አይፈጸምም::
እግዚአብሔር ይፍታህ አይባልም ሳምንቱ የሚታሰበው ሕማሙን
ሞቱን በማሰብና በስግደት ነው:: የግዝት በዓላት እንኳ
ይሰገድባቸዋል:: የዚህ ሳምንት ጾም የቻለ ሁለት ሁለት ቀን
ያልቻለ እስከ ጀንበር ግባት ድረስ ነው:: ምግቡም ቆሎ ዳቦ
የላመ የጣመ ያልሆነ ደረቁን በበርበሬ ነው መጠጡም ንጹህ
ውኃ ነው:: ጠጅ ያንቆረቆረ ጮማ የቆረጠ እድል ፈንታው ጽዋእ
ተርታው በጌታ ሞት ከተደሰቱት ከአይሁድ ጋር ነው:: ጸሎቱ
ውዳሴማ ርያም አንቀጸ ብርሃን መልክአ ሕማማት መዝሙረ
ዳዊት ነው:: የቅዱሳን መልክአ መልክእ አይጸለይም:: የጾሙ
ሥርዓት ምን ይመስላል ካሉ፡
ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15
ቁጥር 578፡ በሊህ በስድስቱ ቀኖች (በሰሙነ ሕማማት) ከቂጣ
ከጨው ከውኃ ብቻ በቀር አይብሉባቸው፡፡ በሊህ ቀኖች ከወይን
ከሥጋ ተለዩ የኀዘን ቀኖች ናቸውና የደስታ ቀኖች አይደሉም፡፡
ዓርብንና ቅዳሜን ግን ሁለቱንም በአንድነት ጹሟቸው፡፡ የሚችል
እስከ ሌሊቱ ዶሮ ጩኸት ጊዜ ድረስ ምንም ምን አይቅመስባቸው
ሰውየውም ሁለቱን ቀኖች በአንድነት መጾም ባይቻለው ግን
የቅዳሜን ጾም ይጹም፡፡
ቁጥር 590፡ ካህን ሰሙነ ሕማማትን ቀንና ሌሊቱን ሳያስተካክል
አስቀድሞ ቢያውል ይሻር፡፡ ከሕማማት ቀጥላ ከምትሆን ከቅዳሜ
ስዑር በቀር እሑድንና ቅዳሜን የጾመ ካህን ቢኖር ይሻር፡፡
ቁጥር፡ 593፡ ከካህናት ወገን ማንም ቢሆን በአርባ ጾም
በዓርብና በረቡዕም ጾም ወይን መጠጣት አይገባውም ወደ
መዋት (ውሽባ ቤት) አይግባ፡፡ በዐቢይ ጾም ወራት ሰው ከሚስቱ
ጋር አይተኛ፡፡
ቁጥር 597፡ ሴቶችም ጌጣቸውን ይተው፡፡ ሁሉም ለእያንዳንዱ
በአርባ ጾምና በሰሙነ ሕማማት መጠበቅ ይገባዋል ድኅነታችንና
የኃጢአታችን ሥርየት በእነርሱ ነውና፡፡ ይኸውም ሥራ አንዱስ
እንኳ በአርባ ጾም ወራት በምንጣፍ ፈጽሞ እንዳይገናኝ ከጋብቻ
ሕግ የወጣ ነው፡፡ ክብርት በምትሆን በሕማማት ወራት ይህችን
ኃጢአት የሚሠራት ሰው ወዮለት፡፡ በአርባ ጾም በተድላ በደስታ
ፈቃዳችንን ካደረግን ትንሣኤውን ባየን ጊዜ ተድላ ደስታችን
ወዴት አለ?
ቁጥር 599፡ በተባሕትዎ በትሕትና አርባ ቀን ጾምን ይጹሙ፡፡
ከጥሉላት መከልከል ይገባል፡፡ አያግቡም፡፡
ቁጥር 600፡ በሰሙነ ሕማማት ክርስትና ማንሣት ክህነት
መስጠት ለሞቱ ሰዎች መጸለይ አይገባም፡፡ በእነዚህም ቀኖች
በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ፈጽሞ ማገልገል ይገባል እንጅ፡፡
በሰሙነ ሕማማት ስለሚሞቱት ሰዎች የሙታን ግንዘትና
የሐዋርያት ሥራ ወንጌላት የሙታን ፍትሐት በሆሣዕና በዓል ቀን
ይነበብ እንጅ፡፡
ቁጥር 601፡ በጸሎተ ሐሙስ ጸሎተ ተአምኆ እግዚአ ሕያዋን
የቡራኬ ጸሎት አይባልም (አይጸለይም)፡፡ ቅዳሜ ግን እግዚአ
ሕያዋን ይባላል ፍትሐት ይፈታል፡፡ ከመሳለም በቀር ጸሎተ
ዕጣንም ይጸለያል፡፡ በዕለተ እሑድ ግንዘት ማድረግ በፋሲካ
ቀንም ማልቀስ አይገባም፡፡ ዳግመኛም በውስጧ በአርባ ጾም
ከተድላ ከደስታ ወገን ምንም ማድረግ አይገባም፡፡ መጋባት
ክህነት መስጠት ክርስትና ማንሣት ከሹመትም ወገን
ስለሚሞቱት ከመጸለይ በቀር ምንም ማድረግ አይገባም፡፡
ይሞታል ተብሎ ለሚያስፈራው ግን ጥምቀተ ክርስትና
ይደረግለታል፡፡
የተከለከሉ ነገሮች ምን ምን ናቸው ካሉ፡
1. እጅ ተጨባብጦ ሰላምታ መባባል መሳሳም
2. ሩካቤ ሥጋ ማድረግ
3. መስቀል ማሳለም እና መሳለም
4. ክርስትና ማስነሣት
5. ለሙታን ፍትሐት ማድረግ
6. ክህነት መስጠት
7. የላመ የጣመ ምግብ መመገብ
8. መሳቅ መጫዎት መጨፈር
9. አብዝቶ ጠግቦ መመገብ
10. መስከር ወዘተ ናቸው፡፡
/channel/ortodoxtewahedo
#እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 5ቱ ሀዘናት
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ፣ በወወልድ፣ በወመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን።
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፭ቱ ታላላቅ ኀዘናት ማን ማን ናቸው ቢሉ?
ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በእኔ ምክንያት ካገኙሽ ኅዘናት የትኛው ይበልጣል ብሎ በጠየቃት ጊዜእመቤታችንም ልጄ ወዳጄ ሆይ ባንተ ምክንያት ካገኙኝ ኅዘናት እነዚህን አምስቱ ይበልጣሉ ብላ እመቤታችን የጠቀሰቻቸው ታላላቅ ኅዘናት የሚከተሉት ሲሆኑ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እነዚህን ያንችን ኅዘናት እያሰበ የጸለየ ኃጢአቱን ይቅር እለዋለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል።
#፩ኛ - ስምዖን በቤተ መቅደስ ትንቢት በተናገረ ጊዜ።
===>ስምዖን የተባለው፦ አረጋዊው ስምኦን ነው የእመቤታችን ሐዘን የሚጀምረው ገና አንድዬ ልጇን ከመውለዷ በስምተኛው ቀን ነው ቤተመቅደስ ይዛው በሄደች ጊዜ አረጋዊው ስምዖን “በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል (ልጅሽ በቀራንዮ ይሞታል)” ሉቃስ 2፥34-35 ብሎ በነገራት ጊዜ ድንግል ማርያም አምርራ አዘነች አለቀሰች።
እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥ በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት። ሉቃ (2፡34-35)
#፪ኛ - ከቤተ መቅደስ ፈልጌህ ባጣሁህ ጊዜ።
ወላጆቹም በያመቱ በፋሲካ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ይወጡ ነበር። የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ በሆነ ጊዜ፥ እንደ በዓሉ ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ፤ቀኖቹንም ከፈጸሙ በኋላ፥ ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፥ ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር።
ከመንገደኞች ጋር የነበረ ስለመሰላቸው የአንድ ቀን
መንገድ ሄዱ፥ ከዘመዶቻቸውም ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፈለጉት፤ ባጡትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ።
ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም በመቅደስ አገኙት፤ የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ተገረሙ። ባዩትም ጊዜ ተገረሙ፥ እናቱም። ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን አለችው። ሉቃ (2፡41-48)
#፫ኛ - በጲላጦስ አደባባይ በገረፉህ ጊዜ::
በዚያን ጊዜም ጲላጦስ ኢየሱስን ይዞ ገረፈው። ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ አኖሩ ቀይ ልብስም አለበሱት፤ እየቀረቡም።
የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን ይሉት ነበር፤ በጥፊም ይመቱት ነበር። ጲላጦስም ደግሞ ወደ ውጭ ወጥቶ። እነሆ፥ አንዲት በደል ስንኳ እንዳላገኘሁበት ታውቁ ዘንድ እርሱን ወደ ውጭ አወጣላችኋለሁ አላቸው። ኢየሱስም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀይ ልብስም ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ። ዮሐ (19፡1-5)
#፬ኛ - በዕለተ ዓርብ በሰቀሉህ ጊዜ።
ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ። በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ።
ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው፤ ጽሕፈቱም። የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ የሚል ነበረ።ኢየሱስም የተሰቀለበት ስፍራ ለከተማ ቅርብ ነበረና ከአይሁድ ብዙዎች ይህን ጽሕፈት አነበቡት፤ በዕብራይስጥና በሮማይስጥ በግሪክም ተጽፎ ነበር።ስለዚህ የአይሁድ ካህናት አለቆች ጲላጦስን። እርሱ። የአይሁድ ንጉስ ነኝ እንዳለ እንጂ የአይሁድ ንጉሥ ብለህ አትጻፍ አሉት። ጲላጦስም። የጻፍሁትን ጽፌአለሁ ብሎ መለሰ። ዮሐ. (19፡17-2
#፭ኛ- ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ገንዘው ወደ አዲስ መቃብር ባወረዱህ ጊዜ።
ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ።
ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ። የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት።
በተሰቀለበትም ስፍራ አትክልት ነበረ፥ በአትክልቱም ማንም ገና ያልተቀበረበት አዲስ መቃብር ነበረ።ስለዚህ መቃብሩ ቅርብ ነበረና ስለ አይሁድ ማዘጋጀት ቀን ኢየሱስን በዚያ አኖሩት። ዮሐ (19፡38-42) እንዚህን አምስቱን የእመቤታችን ሐዘናት እያሰበ ያዘነ ዝክሯን የዘከረ በአማላጅነቷ የታመነ ዋጋው ከቶ አይጠፋበትም፡፡
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
።።።አሜን አሜን።።።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
/channel/ortodoxtewahedo
#ሰሙነ_ሕማማት
ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ሰሙነ ሕማማት የጾመ ሁዳዴ የመጨረሻው ሳምንት፤ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማም የሚታሰብበት፤ ካህናትና ምእመናን በአጸደ ቤተክርስቲያን ተሰብስበው የሕማሙን ነገር የሚያወሳውን ዜማ የሚያዜሙበት፤ ግብረ ሕማም በመባል የሚታወቀውን መጽፍ የሚያነቡበትና የሚሰሙበት፤ በነግህ፣ በሠልስት፣ በስድስት፣ በተሰዓት /ዘጠኝ /ሰዓት፣ በሰርክ /በዐስራ አንድ/ ሰዓት እየመላለሱ የሚሰግዱበትና የሚጸለዩበት ልዩ ሳምንት ነው ከሆሳዕና ማግስት እስከ ትንሳኤ።
በዚህ ሳምንት በተለይ ካህናት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ ምክንያቱም ጌታችን የደረሰበትን መከራና ስቃይ እንዲሁም የሰው ልጅ ፭ ሺ ፭ መቶ ዘመን በጨለማ ግዞት ይኖር እንደነበር ለማዘከርም ጭምር ነው። የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራና ሕማም በጽኑ እንድናስበው ያስተማሩን ሐዋርያት ናቸው። ለእነርሱም የነገራቸው ደግሞ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ሰሙነ ሕማማት የጌታችንን ሕማማት ከማሰብ ጋር በየዕለቱ በርካታ ድርጊቶች መፈጸማቸውን የምናስታውስበት ሳምንት ነው፦
#ሰኞ
#መርገመ_በለስ_የተፈጸመበት_ሰኞ_ይባላል፦
በዚህ ዕለት ጌታችን ከቢታኒያ ሲወጣ ተራበ ቅጠል ያለባትን በለስ ተመልክቶ ወደ በለሲቱ ቢቀርብ ከቅጠል በቀር ምንም ነገር ባለማግኘቱ “ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም ምንም ካንቺ ፍሬ አይበላ” ማር ፲፩፥፲፬ በማለት ስለረገማት መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ ይባላል።
#አንጽሖተ_ቤተ_መቅደስ_ይባላል፡-
ጌታ ወደ ቤተመቅደስ ሄዶ በቤተመቅደሱ የሚሸጡትን እና የሚለውጡትን “ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች” ማቴ ፳፩፥፲፫ በማለት ከቤተመቅደስ ገርፎ አስወጥቷቸዋልና።
#ማክሰኞ
#የጥያቄ_ቀን_ይባላል፦
ሰኞ ዕለት በቤተመቅደስ ሲሸጡ እና ሲለውጡ የነበሩትን ሁሉ እየገረፈ በማባረሩ ምክንያት ለሰው ልጅ ሹመትንና ስልጣንን የሰጠ ጌታ “በምን ስልጣን ይህንን ታደርጋለህ?” ማቴ ፳፩፥ ፳፫ ተብሎ በፈሪሳውያን ተጠይቋልና የጥያቄ ቀን ይባላል።
#የትምህርት_ቀን_ይባላል፡-
በዚህ ዕለት በቤተመቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረም የትምህርት ቀን ይባላል። ሉቃ ፳፩ ፥፳፰ ፣ ማር ፲፪፥፪።
#ረቡዕ
#ምክረ_አይሁድ_ይባላል፦
ረቡዕ እለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የመከሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክረ አይሁድ ይባላል። ወቅቱ የፋሲካን በዓል የሚያከብሩበት ቀን በመሆኑ እና ብዙ ህዝብም ጌታን ይከተለው ስለነበር ሁከት እንዳይነሳ ስጋት ነበራቸው ። ነገር ግን ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ስለነገራቸው ሉቃ ፳፪፥፩-፮ ጭንቀታቸው ተወግዶ በጌታ መያዝ ተስማምተዋል።
#የመልካም_መዓዛ_ቀንም_ይባላል፡-
ጌታችን በዚህ ዕለት በለምጻሙ በሰምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት/ባለሽቶዋ ማርያም/ ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ የአልባጥሮስ ሽቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ማቴ ፳፮፥፮-፯ የመዓዛ ቀን ይባላል።
#የእንባ_ቀን_ይባላል፡-
ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ እፍረት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እየለመነች በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አርሳለችና ማር ፲፬፥፱ የእንባ ቀን ይባላል።
#ሐሙስ
#ጸሎተ_ሐሙስ_ይባላል፦
ጌታችን ለአይሁድ ተላልፎ ከመሰጠቱ በፊት በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ ሲጸልይ በማደሩ ማቴ ፳፮፥፴፮ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል።
#የምስጢር_ቀን_ይባላል፡-
ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምስጢር ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱ በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምስጢር ቀን ይባላል።
#የሐዲስ_ኪዳን_ሐሙስ_ይባላል፡-
መሥዋዕተ ኦሪት /በእንስሳት ደም የሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም ድኅነት ራሱን ያቀረበበት ቀን በመሆኑ ሉቃ ፳፪፥፳ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል።
#የነጻነት_ሐሙስ_ይባላል፡-
ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነም ዮሐ ፲፭፥ ፲፭ የነጻነት ሐሙስ ይባላል።
#ዓርብ
#የስቅለት_ዓርብ_ይባላል፦
ጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ነውና ማቴ ፳፯፥፴፭ የስቅለት ዓርብ ይባላል።
#መልካሙ_ዓርብ_ይባላል፡-
ከጌታ ስቅለት በፊት በተለይም በሮማውያን ህግ የወንጀለኛ መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል ጌታችን በደሙ ቀድሶ የምህረት፣ የሕይወት አርማ፣ የዲያቢሎስ ድል መንሻ ስላደረገው፤ በሞቱ መልካሙን ሕይወት ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ይባላል።
#ቅዳሜ
#ቀዳም_ስዑር_ትባላለች ፦
ይህች እለት ከድሮ በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረች ቅዳሜ ይባላል።
#ለምለም_ቅዳሜ_ይባላል፡-
ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት በመሆኑም ለምለም ቅዳሜ ይባላል። ምዕመናንም ይህንን ለምለም ቀጤማ እስከ ትንሣኤ ለሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል።
#ቅዱስ_ቅዳሜ_ይባላል፡-
ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ያረፈበት ቀን ሲሆን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ስራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ በነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዶ ሲኦልን በርብሮ ባዶዋን ሲያስቀራት በዚያ የነበሩትን ነፍሳት የዘላለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል።
(ስምዐ ጽድቅ መጋቢት ፳፻፪ ዓ.ም)
http://t.me/ortodoxtewahedo