ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ። ‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3 https://youtu.be/csxxAMGtC4I ለመቀላቀል http://t.me/ortodoxtewahedo
ለቅድስት ቤተክርስቲያን ላደረጉት መንፈሳዊ ተጋድሎ ለከፈሉት መስዋዕት ቅድስት ቤተክርስቲያን ሁሌም ስትዘክረው ትኖራለች
አባታችን አቡነ ጴጥሮስ ክብር ይገባቸዋል 🙏
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
ሻሸመኔ እና መሃል አዲስ አበባ ላይ እርሳቸው በለኮሱት እሳት ምክንያት በጥይት ለተቆሉ ምዕመናንን ጸጸት ወይም ሀዘኔታ አላሳዩም።
ላፈረሱት ቅኖና ፣ ለተዳፈሩት ክብር ፣ለፈጸሙት የስርዓት ህጸጽ ይቅርታ አልጠየቁም። ይልቁንስ ዛሬም ድረስ ትክክል እንደሆኑ ይሰማችዋል።
ከክርስቶስ ይልቅ ዘር እና ቋንቋቸውን አሳይተው በሥጋ ዋሻ የተጠለሉት የሌላ ቤተ እምነት ተከታይ የሆኑ ጭምር እንዲከተሏቸው ፊት ለፊት ቆመዋል።
ወጥቼበታለው ካሉት ዘር በእምነታቸው ብቻ ካህናት አባቶች እና ምዕመናንን እየተለቀሙ ሲገደሉ አንድ ቀንም -ስለልጆቼ- ብለው ቃል አላወጡም።
እርሳቸው ስርዓት ማፍረስ ትክክል እንደሆነ ፣ አመጸነት አዋጭ እንደሆነ በገለጡት ቤተክርስቲያን ውስጥ ቀጣይ 3 ዓመት ምን እንደሚከሰት እንግዲህ እናያለን።
እንግዲህ ምን እንላለን ? መንፈስቅዱስ የዘገዬ ቢመስልም በእውነት ይፈርዳል!!!
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
✝የእግዚአብሔር ፍቅር በልብህ ውስጥ ጠልቆ ከገባ ድካምህ ይጠፋል ።
ከእግዚአብሔርና ከትእዛዛቱ የበለጠ ኃጢአትን የምትወድ ከሆነ ደካማ ትሆናለህ ። ነገር ግን ፍቅሩ ወደ ልብህ ከገባ በውስጥህ ያለውን የኃጢአት ፍቅር አውጥቶ ይጥለዋል ። ስለሆነም ማንኛውንም ዓይነት ፈተና ለመቃወም ብርቱ ትሆናለህ ።
"ንስሓ ማለት ፍላጎትን በፍላጎት መቀየር ማለት ነው ።" ይህ ማለት የእግዚአብሔር ፍቅር የአለምን ፍቅር ይተካል ማለት ነው ። ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር የሚመሩህን ማንኛውም አይነት መንፈሳዊ መንገዶች ሁሉ ተከተል ። ከዚህ በተጨማሪ እግዚአብሔርን ከሚወዱት ጋር ተባበር ! እርሱን ስለ ወደዱት ሰዎች የተጻፈውንም አንብብ ! በመጨረሻም ምሳሌያቸውን ተከተል ።
አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
+ እናንተ የምድር ጨው ናችሁ . . . እናንተ የዓለም
ብርሃን ናችሁ:: በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትም:: መብራትንም አብርተው በዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያናሩታል:: በቤት ላሉት
ሁሉም ያበራል:: መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት
ይብራ::
+ (ማቴ.5:13-16)
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞
❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖
❖ ግንቦት 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
+°✝ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ✝°+
=>ለቤተ ክርስቲያን የብርሃን ምሰሶ ስለሆነላት ስለ ታላቁ
ሐዋርያዊ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ምን እላለሁ?
ምንስ
እናገራለሁ? እንደ እኔ ያለ ኃጥእ: ለባሴ ሥጋና ገባሬ ንስሃ
ስለሱ ሊናገር አይቻለውምና:: አባቶቻችን እንደ ነገሩን ስለ
አፈ ወርቅ ለመናገር አፈ ወርቅ መሆን ያስፈልጋል:: ግን
እስኪ በቅዱሱ አባት ምልጃ ጥቂት ልሞክር::
<< ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ማን ነው? >>
+ነገዱ ከሶርያ: የተወለደው በ347 ዓ/ም በእስክንድርያ
ሲሆን አባቱ አስፋኒዶስ እናቱ ደግሞ አትናስያ ይባላሉ::
እነርሱ
ደግ ቢሆኑ ይህንን እንቁ ልጅ እግዚአብሔር ሰጣቸው::
ዮሐንስ ለክርስቲያን እንደሚገባ በትምሕርትና በጥበብ
አደገ:: ገና
በሕጻንነቱ ወደ ግሪክ ሔዶ የዘመኑን ሳይንስ (ፍልስፍና)
ከአፉ እስከ ገደፉ ተምሮ ተመልሷል::
+ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን ለየት ከሚያደርጉት ነገሮችም
አንዱ ይሔው ነው:: በዘመናዊም ሆነ በመንፈሳዊ
ትምሕርት ይህ
ቀረህ የማይሉት ሊቅ የሆነው ገና በ15 ዓመቱ ነበር:: በ2
ወገን የተሳለ ሰይፍ በመሆኑ ስንኳን በሕይወተ ሥጋ እያለ
ዛሬም ለንፉቃን ትልቅ የራስ ምታት ነው::
+ቅዱሱ ገና በ16 ዓመቱ ሃብት: ንብረት: ውበት: ክብርና
እውቀት የሞላለት ቢሆንም ያለውን ሁሉ ለነዳያን ሰጥቶ
መጻሕፍትን ብቻ ሰብስቦ ከባልንጀራው ቅዱስ ባስልዮስ
ጋር በርሃ ገባ:: ሰውነቱን በጾምና በጸሎት እየቀጣ በበርሃ
ሲኖር
ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ
ዼጥሮስ ወደ እርሱ መጡ::
ሊቀ ሐዋርያት የመንግስተ ሰማያትን መክፈቻ ስልጣን
ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ ወንጌሉን ሰጥተው ተሰወሩት::
+ከዚህች እለት በኋላ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ባሕረ
ምስጢራት ሆነ:: ብሉይ ከሐዲስ: ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ
ራዕየ
ዮሐንስ ድረስ በአንድምታ ትርጉዋሜ ተነተናቸው:: በተለይ
ሐዲስ ኪዳንን እየመላለሰ አመሰጠረው:: ቅዱስ ሕሊናው
ሳይታክት:
ንጹሕ እጆቹ ሳይዝሉ የጻፋቸው ድርሳናት: መልዕክታትና
ትርጉዋሜያት ቢቆጠሩ አሥር ሺህ ሞሉ:: በእውነት ለዚህ
አንክሮ
ይገባል! የሚገርመው ይህን ሁሉ ሲሰራ እድሜው ገና
ለጋ: ማዕርጉም ዲቁና ነበር::
+ከዚህ በኋላ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ቅስና ተሹሞ
በስብከተ ወንጌል ብዙ ቦታዎችን አዳረሰ:: በቅድስናው
ወደውታልና
የቁስጥንጥንያ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት:: አፈ ወርቅ
ሲናገርም ሆነ ሲያስተምር እንኳን የሚያወራ ኮሽ የሚል
የለም::
ከጣዕመ ትምሕርቱ የተነሳ ሕዝቡ በተደሞ ይሰሙት ነበር::
+ሲያስተምር ምድራዊው ሰው ይቅርና ልዑላኑ መላእክት
ተሰብስበው ያደንቁት ነበር:: አንዴም እመቤታችን በሕዝብ
መካከል "
አፈ-ወርቅ" ብላ ጠርታዋለች:: ለዛም ነው አፈ-ወርቅ
የሚባለው:: ቅዱሱ በሥልጣነ ቃሉ መልዐከ ሞትን ገስፆ
10 ዓመት
አቁሞታል::
+ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለሰው ፊት አያደላም:: በርሱ
ዘንድ ንጉሥና ደሃ ነዳይ እኩል ነው:: ለሞት ያበቃውም
ይሔው
ነበር:: ምክንያቱም የወቅቱ ንግስት አውዶክስያ ያንዲት
ድሃ መበለትን መሬት ቀምታ አልመልስም በማለቷ መክሮ
አወገዛት::
እርሷ ግን ከኃጥአንና መናፍቃን ጋር መክራ 2 ጊዜ
አጋዘችው::
+በተሰደደበት ፍሬ አፍርቶ: አስተምሮና አሳምኖ በ407 ዓ/
ም አርፏል:: ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ሳይጠግቡት
እንደናፈቁት በ60 ዓመቱ አጡት:: በወቅቱ ታላቅ ሐዘንና
ለቅሶ ተደረገ::
+አንድ ቀን የዘመኑ ደግ ንጉሥ አርቃድዮስ ግብር አገባ
(ግብዣ አዘጋጀ):: በዚያች ሌሊት ደግሞ ቅዱሱ ሊቅ
ታጥቆ ሲጸልይ
ሳለ: አባ ማርዳሪ የሚባል ጻድቅ ደግሞ ከሰማይ 12ቱ
ሊቃነ መላእክት (እነ ቅዱስ ሚካኤል) በግርማ ሲወርዱ
ተመለከተ::
+ደንግጦ "ወዴት ናችሁ ጌቶቼ" ቢላቸው "ቁስጥንጥንያ:
ወደ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንሔዳለን:: እርሱ እመቤታችንን
እንደሚያመሰግናት ጌታ ነግሮናልና" አሉት:: "እባካችሁ
እኔም የአፈ ወርቅ ምስጋናው እንገለጥልኝ መርቁኝ"
አላቸው::
ሊቃነ መላእክቱም መርቀውት ጐዳናቸውን ቀጠሉ::
+በማግስቱ በቤተ መንግስት ውስጥ ሊቃውንቱ:
መሳፍንቱ: ዻዻሳቱ: ሕዝቡ ሁሉ ተሰብስበው ከድግሱ
በሉ:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ
ወርቅ ግን በመንበሩ ተቀምጦ ነበር እንጂ አልበላም::
ድግሱ ሲጠናቀቅ ንጉሡ አርቃድዮስ ሊቁን "ጥያቄ አለኝ"
ብሎ በጉባኤ
መካከል ጠየቀው::
+"ምነው ወንጌላዊ ማቴዎስ 'ኢያዕመራ ዮሴፍ እስከ አመ
ወለደት ወለደ ዘበኩራ-የበኩር ልጇን እስክትወልድ ድረስ
አላወቃትም'
ማለቱ (ማቴ. 1:25) ስለ ምን ነው?" ቢለው ቅዱሱ
ተነስቶ: በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ይተረጉምለት ጀመር::
+"ድንግል ማርያም ንጹሕ ብርሌን ትመስላለች:: ብርሌ
የተለያየ ቀለም ያለው ፈሳሽ ቢያስገቡበት ቀለሙ አብሮ
ይቀያየራል::
እመቤታችንም ጌታን ጸንሳለችና ሕብረ መለኮቱ ሲለዋወጥ
መልኳ አብሮ ሲለዋወጥ እያየ ዮሴፍ ይደነግጥ ነበር::
+'እርሷ ማን ናት? በማሕጸኗ ያለውስ ማን ነው' እያለ
ይጨነቅ ነበር:: ጌታን ከወለደች በኋላ ግን አንድ ሕብረ
መልክ
ሆናለችና:: አስቀድሞ ማን እንደ ነበረች አላወቀም::
+አሁን ግን እርሷም ወላዲተ አምላክ: ልጇም አምላክ
ዘበአማን መሆኗን አወቀ ማለት ነው" እያለ ሲተረጉም
ሰምተው ሁሉም
ሲያደንቁ: በዚያ የነበረች ስዕለ አድኅኖ "አፈ ወርቅ! ልሳነ
ወርቅ! አፈ በረከት!" ስትል ተናገረች::
+ያን ጊዜ አርቃድዮስ የወርቅ ልሳን በሊቁና በስዕሏ ላይ
አደረገ:: አፈ ወርቅ ግን ባጭር ታጥቆ "እሰግድ ለኪ!
እሰግድ
ለኪ! ወእዌድሰኪ . . ." ብሎ ዛሬ በተአምረ ማርያም
የምናውቀውን ምስጋና ሰተት አድርጐ አደረሰላት:: ይህንን
ምስጋናም
ሊቃነ መላእክቱ ሰምተው እያደነቁ ወደ ሰማይ
ወጥተዋል::
+ሊቁ ባረፈ በ35 ዓመቱ: በትንሹ ቴዎዶስዮስ ዘመን:
ሥጋው ፈልሷል:: ወደ ቁስጥንጥንያ ሲደርስም ከናፍቆት
የተነሳ ታላቅ
ዝማሬና እንባ ተደርጓል:: አፈ ወርቅም ቀና ብሎ ሕዝቡን
ባርኳል::
✔ቅዱሱ ሲጠራ እንዲሕ ነው:-
*ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
*አፈ በረከት
*አፈ መዐር (ማር)
*አፈ ሶከር (ስኳር)
*አፈ አፈው (ሽቱ)
*ልሳነ ወርቅ
*የዓለም ሁሉ መምሕር
*ርዕሰ ሊቃውንት
*ዓምደ ብርሃን (የብርሃን ምሰሶ)
*ሐዲስ ዳንኤል
*ሊቀ ዻዻሳት ዘበርትዕ (እውነተኛው)
*መምሕር ወመገስጽ ዘኢያደሉ ለገጽ
*ጥዑመ ቃል - - -
+እግዚአብሔር ከቅዱሱ በረከት አብዝቶ: አብዝቶ: አብዝቶ
ይክፈለን::
+ዳግመኛ በዚህ ቀን ታላቁ ጻድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት
ሥጋቸው ፈልሷል:: ይሕ የተደረገው ጻድቁ ከረፉ ከ56
ዓመታት
በኋላ ነው:: በዕለቱም ድንቅ ድንቅ ተአምራት
ተፈጽመዋል::
+እናታችን ርሕርሕቷ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ደግሞ
በዚሕ ቀን ስሟን ለጠራና መታሠቢያዋን ላደረገ የምሕረት
ቃል ኪዳን
ተቀብላለች::
❖ቸር አምላካቸው ከሁለቱም ብሩሃን ቅዱሳኑ ክብር
ያድለን::
❖ግንቦት 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ (የዓለም ሁሉ መምሕር)
2አቡነ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ጻድቅ (ፍልሠታቸው)
3.ቅድስት እናታችን ክርስቶስ ሠምራ (ቃል ኪዳን
የተቀበለችበት)
4.አባ አብርሃም ዘደብረ ሊባኖስ
5.ቅዱስ ዕንባቆም ነቢይ
6.እስክንድር ንጉሠ ኢትዮዽያ
7.ቅዱስ መስቀል (የተአምር በዓሉ)
8.አባታችን ያሬድ (የማቱሳላ አባት)
9.ቅዱስ ሚናስ ዲያቆን
❖ወርኃዊ በዓላት
1፡ ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት
🇪🇹 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ የትኞቹን መዝሙራት ማግኝት ይፈልጋሉ❓
Читать полностью…ሰሞኑን ለምታገቡ፣ ከዚህ በፊት ላገባችሁና ወደፊት ለማግባት ላቀዳችሁ ድንቅ ትምህርት ነው
✝ያለወንድ ሴት የለም ያለሴትም ወንድ የለም✝
Size:-6.5MB
Length:-28:11
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
የእስር ዜና!!!
ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ታሰረ‼️
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በስብከት አገልግሎቱ፣በተለያዩ ስልጠናዎች ላይ ስልጠና በመስጠት፣በተለይም ተሃድሶውያንን በመዋጋት የምናውቀው ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ዛሬ በፀጥታ ኃይሎች መወሰዱ ተሰማ።
እንደሚታወቀው የቅዱስ ሶኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሚካሄድበት ወቅት በተለይም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በሚመረጥበት ግዜ ሁሉ ለቤተክርስቲያን ይታገላሉ የሚባሉ ወንድሞች እና እህቶች ይታሰራሉ። ዛሬም ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ታስሯል።
የቅዱስ ሲኖዶስን ጸሐፊ እና የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅን መምረጥ የመንፈስ ቅዱስ እና የብፁዓን አባቶች ድርሻ ነው። በዚህ ወቅት የሚታሰር አንዳችም ሰው መኖር የለበትም ።ወንድማችንን እንድትፈቱት እንጠይቃለን ።
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
ዜኖኩ ጽድቅከ ወነገርኩ አድህኖትከ ከሰትኩ ቃላቲከ ለህዝበ ኢትዮጲያ(፪)
# ግንቦት_11
በምድር ሁኖ በሰማያዊ ቋንቋ የሚናገረው አልቦ እምቅድሜከ ወአልቦ እምድህሬከ ከአንተም በፊት ከአንተ በኋላ አንተን የሚመስል የለም የተባለለት ብቸኛው የኪሩብም ደቀ መዝሙር ቅዱስ ያሬድ የመሰወር በዓሉ ነው በረከቱ ይደርብን
ዜኖኩ ጽድቅከ ወነገርኩ አድህኖትከ ከሰትኩ ቃላቲከ ለህዝብከ ኢትዮጲያ(፪)
በጸጋሑ ለመንፈስ ቅዱስ ወመሀርክዎሙ አነ ይቤ ያሬድ ካህን(፪)
+++ጽድቅህን ነገርኩ አዳኝነትህን አስተማርኩ ቃላትህን ለኢትዮጲያ ሕዝብ ነገርኩ(፪)
እኔም በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አስተማርኳቸው አለ ያሬድ ካህን(፪)
በመጨረሻም እግዚአብሔር ለቅዱስ ያሬድ ቃልኪዳን ገብቶለታል
ዝክረ ቅዱስ ያሬድ
'ብፁዕ ውእቱ ዘገብረ ተዝካረከ...አነ እሁቦ ሕይወተ ዘለዓለም ወአወርሶ መንበረ ክብር' ይቤሎ እግዚአብሔር ለያሬድ ካህን
እግዚአብሔር ለካህን ያሬድ እንዲህ ብሎታል 'ተዝካርህን ያደረገ ንዑድ ነው ክቡር ነው... የዘለዓለም ሕይወትን እሰጠዋለሁ መንግሥተ ሰማያትንም አወርሰዋለሁ' በምልጃው ያስበን
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
#11 የቅዱስ ያሬድ በዓል]
#በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አባቱ አብዩድ (ይሥሐቅ) እናቱ ክርስቲና (ታውክልያ) ሲባሉ የተወለደውም በ፭፻፭ ዓ.ም. ነው፡፡ ሰባት ዓመት ሲመላው አባቱ ስላረፈ፤ እናቱ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እንዲያስተምረው ለአባ ጌዴዎን ሰጠችው፡፡ ነገር ግን ማጥናት ስላልቻለ አባ ጌዴዎን ይቈጣው ነበርና ሸሽቶ ከዱር ውስጥ ገባ፤ ከዐዘኑም ብዛት የተነሣ በዛፍ ሥር ተጠልሎ ሳለ አንዲት ታናሽ ትል ከዛፍ እኩሌታ ደርሶ ሲወድቅ ሲነሣ በመጨረሻም በጭንቅ ከዛፉ ላይ ሲወጣ በማየቱ እግዚአብሔር በዚኽች ታናሽ ፍጥረት እንዳስተማረው በመረዳት ይቅርታ ጠይቆ ወደ መምህሩ ተመልሷል፡፡
“ወእምዝ ሶበ ሰአለ ኀበ እግዚአብሔር በብካይ ብዙኅ ተርኅወ ልቡናሁ ወተምህረ በሐጺር ዕለት መጻሕፍተ ብሉይ ወሐዲስ” ይላል ከዚኽ በኋላ ቅዱስ ያሬድ ወደ እግዚአብሔር በለመነ ጊዜ ልቡናው ብሩህ ኾኖለት በዐጭር ጊዜ ውስጥ የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን ተምሮ በመጨረስ ዲቁናን ተሾመ፤ እስከ ርሱ ዘመን በማነብነብ እንጂ በከፍተኛ ድምፅ የመዝሙር ማሕሌት አልነበረም፤ እግዚአብሔርም ለዚኽ አባት የመላእክትን ዝማሬ ሊያሳየው ስለወደደ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እስከ ሦስተኛው ሰማይ እንደተነጠቀ ኹሉ ሊቁም ተነጥቆ የኻያ አራቱ ካህናተ ሰማይን የምስጋና ዝማሬ ሰምቶ ተመለሰ፡፡
ቅዱስ ያሬድ ከአርያም ወርዶ ወደ ምድር እንደ ደረሰ ወደ አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ገብቶ፡- “ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይገብር ግብራ ለደብተራ” (ለአብ ምስጋና ይገባል፣ ለወልድም ምስጋና ይገባል፣ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፡፡ ከጽዮን አስቀድሞ ሰማይን ፈጠረ ዳግመኛም ለሙሴ የድንኳኑን ሥራ እንዴት እንደሚሠራ አሳየው) ሲል ዘምሮ ይቺኑ መዝሙር ከሰማይ መላእክት አገኘኹት፣ በማለት አርያም በሚል ሥያሜ ጠርቷታል፡፡
ይኽነኑ ድርሳነ ዜማ የጻድቁ ካሌብ ልጅ ንጉሥ ገብረ መስቀል በሰማ ጊዜ ጫማውን ሳይጫማ ንግሥቲቱም ደንገጡሮቿን አጃቢዎቿን ሳታስከትል መኳንንቱ፣ ካህናቱና መምህራኑ እነሱን ተከትለው እየተጣደፉ ወደ ዐደባባዩ በመኼድ በተመስጦ ሲሰሙት ውለዋል፡፡
ቅዱስ ያሬድ ዐምስት የዜማ መጻሕፍትን የደረሰ ሲኾን እነርሱም
፩ኛ) ድጓ ፪ኛ) ጾመ ድጓ
፫ኛ) ምዕራፍ ፬ኛ) ዝማሬ ፭ኛ)መዋሥዕት ናቸው፡፡
እነዚኽንም ታላላቅ ድርሰቶቹን በሦስት የዜማ ስልቶች ማለት በግእዝ፣ በዕዝል፣ በአራራይ አዘጋጅቷቸዋል፡፡ “ወአሐተ ዕለተ እንዘ ይዜምር ያሬድ ቀዊሞ ታሕተ እገሪሁ ለንጉሥ ገብረ መስቀል ወእንዘ ያጸምዕ ንጉሥ ቃሎ ለያሬድ ተከለ በትረ ኀጺን ውስተ መከየደ እግሩ ለያሬድ” ይላል፤ ከዕለታት ባንዳቸው ቅዱስ ያሬድ በተመስጦ ልዑል እግዚብሔርን በዝማሬ ሲያመሰግን ንጉሥ ገብረ መስቀል ሳያውቁት ልባቸው በጣዕመ ዜማው በመመሰጡ የብረት ዘንጉን በቅዱስ ያሬድ እግር ላይ ተክለውታል፤ ከእግሩም ብዙ ደም ቢፈስስም ቅዱስ ያሬድ ግን ማሕሌቱን እስከሚፈጽም ድረስ ምንም አልሰማውም ነበር፡፡
ንጉሡም የደሙን መፍሰስ አይቶ ደንግጦ ቅዱስ ያሬድን “የደምኽ ዋጋ የፈለግኸውን ንገረኝ” አለው፤ ቅዱስ ያሬድም ተምኔቱ ወደ ገዳም መኼድ እንደኾነ ነገረው፤ ያን ጊዜ ንጉሡ እያዘነ አሰናብቶታል፡፡
“ወእምዝ ቦአ ያሬድ ውስተ ቤተ ክርስቲያን ወቆመ ቅድመ ታቦተ ጽዮን” ይላል ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ በታቦተ ጽዮን ፊት በመቆም የአንቀጸ ብርሃንን ምስጋና ከመዠመሪያው እስከ መጨረሻው በተናገረ ጊዜ በእግዚአብሔር ኀይል ክንድ ያኽል ከምድር ከፍ ከፍ አለ፤ ከዚኽ በኋላ ወደ ሰሜን ተራራዎች ወደ ገዳም ሲኼድ የአኲስም ጽዮን ካህናት እስከ ተከዜ ወንዝ ድረስ ሸኙት ርሱም እጅግ ባማረ ጣዕመ ዜማ ድምፁን ከፍ አድርጎ “ሰላም እግዚአብሔር ኲሉ ባቲ ተሃሉ ወትረ ምስለ ኲልክሙ” (በኹሉ ላይ ጸንታ የምትኖር የእግዚአብሔር ሰላም ዘወትር ከኹላችኊ ጋር ትኑር) ብሎ የስንብት መዝሙርን ዘመረ፤ ካህናቱም ይኽነን ቃል ሰምተው መሪር እንባን አለቀሱና ተሰነባበቱ፡፡
በትርጓሜ ቅዳሴ ማርያም መቅድም ላይ እንደምናነብበው ቅዱስ ያሬድ ማይ ኪራህ በተባለው ቦታ ተሰውሮ ጸዋትወ ዜማን ሲያስተምር እመቤታችን ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬምን የብህንሳውን አባ ሕርያቆስን በአካለ ነፍስ እንዲመጡ አድርጋ ኤፍሬም ውዳሴዬን፤ ሕርያቆስ ቅዳሴዬን ነግራችኹት ቅዱስ ያሬድ በዜማ ይድረስልኝ ብላ ነግረውት በዜማ ደርሶታል፤ ይኽም ሊታወቅ ሥረይ በቅዳሴ ማርያም ይበዛል፡፡
ርሱም ጸዋትወ ዜማን ለደቀ መዛሙርቱ እያስተማረ መላእክት ዘወትር እየጐበኙት በጾም በጸሎት ተወስኖ በተጋድሎ ለኻያ ኹለት ዓመት ጸንቶ ኖረ፤ በመጨረሻም ጌታችንም ለቅዱስ ያሬድ ተገልጾለት “ኦ ፍቁርየ ቀዳሚኒ በከመ ሰመርኩ ትርአይ ሥርዐተ ስብሐተ መላእክት ዘበሰማያት ወአስተኀለፍከ ዘንተ ማሕሌተ ዲበ ምድር... ” (ወዳጄ ሆይ ቀድሞ በሰማይ ያለ የመላእክትን ሥርዐተ ማሕሌት እንድታይና ወደ ምድርም አስተላልፈኽ ይኽነኑ ዜማ እንድትመሠርት እንደ ወደድኊ ኹሉ እኔ ዳግም ተመልሼ በምመጣበት ጊዜ ከካህናተ ሰማይና ሄሮድስ ደማቸውን ካፈሰሰው ሕፃናት ጋር በደብረ ጽዮን ትዘምር ዘንድ ሰማያዊ የክብር አክሊልና የብርሃን ልብስ ተዘጋጅቶልኻል” ብሎት ቃል ኪዳንን ሰጥቶት በክብር ዐረገ፡፡ የቅዱስ ያሬድ መታሰቢያውም ግንቦት ዐሥራ አንድ ነው፡፡
ሊቁ አርከ ሥሉስም የቅዱስ ያሬድን ነገር በአርኬው ላይ፦
“ሰላም ለያሬድ ስብሐተ መላእክት ለሕዋጼ እንተ አዕረገ በልቡ ኅሊና መንፈስ ረዋጼ ለትምህርተ መጽሐፍ ገብአ እምኀበ ኮነ ነፋጼ በብዙኅ ጻማ ዘአልቦ ሑጻጼ*መልዕልተ ጒንደ ዖም ነጺሮ እንዘ የዐርግ ዕጼ”
(የመላእክትን ምስጋና ለመጐብኘት ከመንፈስ ቅዱስ የሚሰጥ ፈጣን ዐሳብን ወደ ልቡናው ያሳረገ ለኾነ፤ ጒድለት በሌለበት በብዙ ድካምም ወደ ዛፍ ግንድ ጫፍ ላይ ትል ሲወጣ ተመልክቶ፤ ኰብልሎ ከኼደበት መጻሕፍትን ለመማር የተመለሰ ለኾነ ለያሬድ ሰላምታ ይገባል) በማለት ሊቁ ማሕሌታይን አመስግኖታል፡፡
ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ ማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን ሊቁ ቅዱስ ያሬድን ሲያወድስ፡-
“ሰላም ለያሬድ ቀሲስ ዘጽጉብ እክለ መንፈስ ቅዱስ፤
ዘአስተጋብአ ምድራሳተ እምኲሎሙ መጻሕፍት
ወአሰርገዋ በሐዋዝ ስብሐት ወበጥዑም ማሕሌት
ለብሔረ ኢትዮጵያ በስብሐት ሃሌ ሉያ
ዘከዐወ ቃለ መለኮት ዲቤሃ
ከመ አስራበ ወርቅ ንጹሐ”፡፡
(የመንፈስ ቅዱስን ምግብን የጠገበ፤ ከመጻሕፍት ኹሉ ትርጓሜያተ ድርሰትን ያሰባሰበ፤ ሃሌ ሉያ በሚል ምስጋና የኢትዮጵያ ሀገርን በጥዑም ማሕሌትና በሚያምር ምስጋና ያስጌጠ፤ የመለኮት ቃልን በላይዋ ላይ እንደ ንጹሕ የወርቅ ሻሻቴ ያፈሰሰ ለኾነ ለካህኑ ያሬድ ሰላምታ ይገባል) ይለዋል፡፡
[የጽሑፉ ምንጭ፡- አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የደረሰው ተአምኆ ቅዱሳን ንባቡና ትርጓሜው በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ የተጻፈ፤ ከገጽ 232-235]፡፡
የቅዱስ ያሬድ በረከት ይደርብን፤ እናንተም ይኽነን ሊቅ አወድሱት።
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
ዜኖኩ ጽድቀከ ወነገርኩ አድኅኖተከ
ከሠትኩ ቃላቲከ ለሕዝብከ ኢትዮጵያ(፪)
በጸጋሁ ለመንፈስ ቅዱስ ወመሀርክዎሙ
አነ ይቤ ያሬድ ካህን(፪)
ጽድቅህን ነገርኩ አዳኝነትህን አስተማርኩ(፪)
ቃላትህን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ገለጥኩ
እኔም በመንፈስ ቅዱስ ፀጋ አስተማርኩአቸው አለ ያሬድ ካህን(፪)
#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ ከፍ አድርጋቸው/2/
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ግሩኙን ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedoo
#ለሃሳብ አስተያየት
@Orthodox_tewahedo_Bot
ተመሰጌን
የበፊቱ ፓስተር የአሁኑ ባለማዕተብ ተሙ!
ለ34 ዓመት በፕሮቴስታንት ውስጥ ቆይቷል
ለአንድ አመት በጥሞና ቆይቷል። ለ interview ሲጠየቅ እራሱ መጀመሪያ ክርስትናን ልኑረው ነው መልሱ።
ተሙ ሁለት ቸርች ከነምዕመኑ ያስጠመቀ ጀግና ነው።
ክርስቶስ ስለበራልኝ ነው ወደ ኦርቶዶክስ የመጣሁት በማለት መስክሯል። እንዲህ በማለት.......
"ፕሮቴስታንት ጋር አብዛኛው ጊዜ ቸርች የግለሰብ ነው ነገር ግን እውነተኛ ቸርች የግለሰብ ሳይሆን የክርስቶስ ነው ።
እሮብ እኮ ፓስተር እከሌ ይመጣል ተብሎ ይኬዳል ስለዚህ ህዝቡ የሚሄደው ነቢይ ደመቀን ወይም ኢዩ ጩፋን ለመቀበል እንጂ ኢየሱስን ለመቀበል አይደለም።
አሁንም መምጣት የሚፈልጉ አሉ ነገር ግን እንደሚታወቁ ደሞዝ ይከፈላቸዋልና ስንወጣ ምን እንሆናለን ነው የሚይአሳስባቸው።
በዚህ አጋጣሚ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በጀት መድባ ትልቅ ሥራ ብትሰራ ደስ ይለኛል። ምክንያቱም ከመጡ ቸርቻቸውን ዘግተው ነው የሚመጡት ሌላ ስራ የላቸውም።
የፕሮቴስታንት ቸርች ጭስ አልባ ኢንዱስትሪ ነው።
ብዙኦች ገና ይመጣሉ ትዝታው እራሱ ይመጣል አይታችሁት እንደሆነ የእሱ ትችት የክርስቶስ ትምህረት ላይ ሳይሆን በግለሰብ ነው። ኦርቶዶክስ ደግሞ በግለሰብ አትለካም እኛ ሰዎች ደካማ ነን አንድ ጳጳስ ፣ አንድ ቄስ ሳተ አንድ ዲያቆን ተሳሳተ ማለት ኦርቶዶክስ ተሳሳተች ማለት አይደለም።
በዚህ አጋጣሚ የኦርቶዶክስ ወጣቶች ጀግና ናቸው፣ ዘመዴ፣ ወገኔ የምላቸው የበፊት ጓደኞቼ ሁሉ የእግዚአብሔር ሰላምታ እራሱ ሲነፍጉኝ ኦርቶዶክሳዊያን ግን በፍቅር ወደ እውነተኛው የክርስቶስ ህብረት እንድጨመር ምክንያት ሆኖዉኛል"
በማለት ገልጿል። በርታ! 💪
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
👑 ስለ ንጉስ ቴዎድሮስ 🤴
🩸 ትንቢት የተነገረለትን ንጉስ የቴዎድሮስ የሚነሳበት አስደናቂና ምስጢራዊ ስፍራ
🩸 እውነት ትንቢት የተነገረለት ንጉስ ቴዎድሮስ ይመጣል ?
🩸 በፍካሬ ኢየሱስና በገድለ ፊቅጦር ስለ ትንቢታዊው ንጉስ ቴዎድሮስና ተጽፎ ይገኛል
🩸 የየረር ተራራ አስገራሚ ምስጢሮች
ለእነዚህ ጥያቂዎች መልስ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
እዚህ ጋር ይጫኑ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN ➢ JOIN ➢ JOIN ➢JOIN
🙏ከሹመቱ ምርጫ በፊት የህንፃው ምረቃ ጥድፊያ
👉በቀድሞው የደቡብ ምዕራብ ሸዋ በአሁኑ በሸገር ሀገረስብከት ስር የሚገኘው የገላን ጉዳ ክፍለ ከተማ የነበረ ህንፃ ግንቦት 10 , 2017 ዓ.ም እንደሚመረቅ የመረጃ ምንጮቻችን አድርሰውናል ፦
👉በዚህ ምርቃት ላይ አቡነ ሳዊሮስ ፣ ለጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጁ ሹመት ድጋፍ ለማግኘት ሆን ብለው ይህንን ቀን የመረጡ መሆኑን የመረጃ ምንጮቻችን በመረጃውን በማድረስ ፣
👉በዚህ ምርቃት ላይ በርካታ ጳጳሳት እንደተጠሩ ፣ብሎም በዚህ ምርቃት ላይ ለሚገኙ አባቶች ስጦታ የብር መስቀል እጅ መነሻ እና በቂ መስተንግዶም እንደተዘጋጀ እንዲሁም የዚህ ዝግጅት ዋና እስፖንሰር ፣ የፍኖተ ጽድቅ ባለቤት አቶ ጸጋዬ መሆናቸውን የመረጃ ምንጮቻችን ለኢትዮ ቤተሰብ አድርሰውናል ፣
👉እንዲህ ዓይነቱ ድርጊት ከዚህ ቀደምም በአባ ሳዊሮስ ጋባዥነት የተከናወነ ሲሆን ፣ ይህ መርሀግብር ጳጳሱ እና ግብራበሮቻቸው ላሰቡት የቡድን የምርጫ ቅስቀሳ ይረዳቸው ይሆን? ዝርዝሩን በመደበኛ መርሀግብራችን ይጠብቁን ፦
ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ የሁሉም ለሁሉም ድምፅ
ምንጭ 👉 ኢትዮ ቤተሰብ
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
አልተገለገላችሁም አገለገላችሁን እንጂ !
ብጹአን አባቶች ብጹዕ አቡነ አብርሃም እና ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ
በረከታችሁ ይደርብኝ ። ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ለከፈላችሁት ተጋድሎ ውለታን የማርሳ የታመናችሁለት ኢየሱስ ክርስቶስ አሁንም ባላችሁ ኃላፊነት ብርታቱን ይስጣችሁ ።
በተለይ ብጹዕ አቡነ አብርሃም ለአስራ አንድ ዓመታት ደብራችንን በአስተዳዳሪነት ባገለገሉበት ወቅት የነበርዎትን መንፈሳዊነት እና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዕድገት ያሳዩትን ትጋት እንኳን እኛ ምዕመናን ማንም የሚመሰክረው ሃቅ ነው ።
አንዳንድ ያልታደሉ ሰዎች ሹመትን ይገለገሉበታል የታደሉት ደግሞ በዓላማ እና በጽናት በቆራጥ መንፈሳዊነት ጭምር መንጋውን ያገለግሉበታል ። ለዚህ ምሳሌ ስለሆናችሁን እንደ ልጅነቴ ዝቅ ብዬ ባላመሰግናችሁ ያጸናችሁ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ይቅር አይለኝም ።
በምትካችሁ ለተሾማችሁት ት ብጹዐን አባቶች መልካም የኃላፊነት ጊዜ ይሆንላችሁ ዘንድ ምኞታችንም ጸሎታችንም ነው ።
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል ፦
1. ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤
2. ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
3. ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስን የሐዲያ ሀ/ስብከትን እንደያዙ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
4. ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ዘኮሎራዶን የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ገዳማት ሊቀ ጳጳስ፤
5. ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን ሚኒሶታን እንደያዙ የኮሎራዶ ሀ/ስብከትን እንዲመሩ፤
6. ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የደቡብ አፍሪካ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳ ጳስ፤
7. ብፁዕ አቡነ ዕንባቆምን የገዳማት መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ፤
8. ብፁዕ አቡነ ሙሴ አውስትራልያን እንደያዙ የግቢ ቅዱስ ገብርኤልና የበዐታ ለማርያም ገዳም ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ ወስኗል።
መረጃው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተገኘ ነው።
@Ortodoxtewahedo
✞✞ ክርስቲያናዊ አስተሳሰብ ✞✞
ክርስቲያናዊ አስተሳሰብ ከፈጣሪ ጋር እንዴት በመንፈሳዊ ሕብረት መኖር እንደምንችል ጥልቅ የሊቃውንት የአስተምሕሮ ፁሑፎች ሚቀርቡበት ቻናል
📗📜📚📗📜📚📗📚📜❗❗❗
@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channel
@EOTC_-OPEN_channe
READE.....MORE
#ያንተን ስራ ያንተን ክብር ፣
ማን ይመራመር ።
እግዚአብሔር ምን ይበል እኛ ቅጥ ብናጣ ፣
በስምንተ ሺ በቀጠሮ መጣ።
ለመቀላቀል
👇👇👇👇👇👇👇
@Ortodoxtewahedo
2፡ ቅዱስ ድሜጥሮስ
3፡ ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
4፡ ቅዱስ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ
5፡ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ
6፡ ቅዱስ ላሊበላ
7፡ ቅድስት መስቀል ክብራ
++"+ እናንተ የምድር ጨው ናችሁ . . . እናንተ የዓለም
ብርሃን ናችሁ:: በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር
አይቻላትም:: መብራትንም አብርተው በዕንቅብ በታች
አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያናሩታል:: በቤት ላሉት
ሁሉም ያበራል::
መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን
አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት
ይብራ:: +"+ (ማቴ.
5:13-16)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
#ሼር_ይደረጋ
እኛ ኦርቶዶክስቂያን ከአባታችን ብሔር ሳይሆን ቤተክርስቲያን ማቅ ከለበሱት የፓትራሪክነት ጥማታቸው ነው ጉዳያችን::
ይህን ጥማታቸውን ለማስከት የሄዱበት መንግድ እደግ በጣም የብዙ ኦርቶዳክያያን ልብ የሰበር ነበር ከቤተክርስቲያን ፈተና ጀርባ ሁሉ እሳቸው አሉበት ይህ ደግሞ አባታችን በፊት ባለቸው አቋም ቀጥለው ወሳኝ በሆኑ ቦታዎች ላይ ከተቃመጡ ቀጠይ የቤተክርስቲያንን ፈተና ጊዜውን ከማራዘም የዘለለ ጥቅም የለውሞ እሳቸው እንዲሾም ቤቴክርስቲያኒቱን ማንቋሽሽ ተገቢ አይደለም ለአንድ አገልጋይ እሳቸው ከደርነት ደርጊት / ጥፋታ/ ይልቅ የሳቸውን የሃስት ፕሮፖጋንዳ ማዛመት እሳቸው ከዚህ በፊት የፈጽሙትን ቤተክርስቲያንን የመክፍፍል ስራ መደገፍ መሆኑንን እወቁት::
ይህ የፖሎቲካ ቅስቀሳ አይደለም የመንፍስ ቅዱስ አሰራር እንጂ ለሁሉም የቀድሞ አባቶቻችን እውነተኛ አባልግሎት በጉበኤው ይስፍን :: አሜን
#Share_goodha
Nuti Ortodoksoonnii dhimmi keenyii saba abbaa keenyaar miti dhimmii keenyii dheebuu angoo paatirarikkummaa barbaacha abbaa kan huccuu gurachaa mana Kiristaanaa uffiisuun onnee Ortodoksoota hedduu cabseera irrattidha male. Qormaata Mana Kiristaanaa hunda duuba isaan jiru. Abbaan keenyas ejjennoo duraan qaban itti fufee iddoowwan murteessoo mana kiristaana ta’an yoo qabatan faayyidaan isaa qormaata Mana Kiristaanaa dheeressuu qofa. Muudamaaf Mana Kiristaanaa Ortodoksii arrabsuun sirrii miti. Tajaajilaan tokko rakkoo isaan mana kiristaana hiruuf hojjeeten caalaa, olola hojii sobaa isaaani babal’isuun, hojii Mana Kiristaanaa addaan qoodu isa kanaan dura hojjete deeggaruun sirrii miti.
Kun duula siyaasaa osoo hin taane, hojii hafuura qulqulluuti malee, haafurri abbootii keenya dhugaa warraa ganamaa yaa'iicha haa hoogannu. Ameen
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
" የአባቶቻችን ትምህርት እናስተምራለን ፤ ተስፋቸውንም ተስፋ እናደርጋለን ፤ የተማርናት ፤ ተስፋ የምናደርጋት ሃይማኖት ይህች ናት:: እንኖርባታለን ፤ እንሞትባታለን ፤ በእግዚአብሔር ፍቃድ እንነሣባታለን "
ሃይማኖተ አበው
እንቁ መምህራችን የሆኑት እዮብ ይመኑ ትምህርቶች ለማግኘት ከታች ናለድ ሊንክ ይግቡ❤️
የይቱብ ቻናላችን ሰብስክራይብ ያድርጉ
👇👇👇
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
✝ርክበ ካህናት✝
Size:-29.2MB
Length:-31:32
በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
መዝሙር 78
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁴ ይበሉም ዘንድ መናን አዘነበላቸው፥ የሰማይንም እንጀራ ሰጣቸው።
²⁵ የመላእክትንም እንጀራ ሰው በላ፤ ስንቅንም እስኪተርፋቸው ላከላቸው።
...
በሰማይ መላእክት አንጻር "እስመ አኮቴቶሙ እረፍቶሙ፥ ወእረፍቶሙ አኮቴቶሙ" እንዲል ቅዱስ ያሬድ የመላእክት እረፍታቸው ምስጋናቸው ፤ ምስጋናቸው እረፍታቸው ነው፤ የመላእክት ምግብና መጠጣቸውም ምስጋናቸው ነው፤
ስለዚህ የመላእክት እንጀራን የሰው ልጅ በላ ማለት ፤ አመሰገነ ማለት ነው፤
ይህንን አጥንትን የሚያለመልም የመላእክት እንጀራ ምግብ የሆነ ምስጋና ወደኛ ላመጣልን በመላእክት ምስጋናም ምስጉን እግዚአብሔርን እንድናመሰግን ላደረገን ለቅዱስ ያሬድ ለተሰወረበት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤
የቅዱሱ በረከት ይደርብን😊
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
#የቅዱስ_ያሬድ_ሌሎች_መጠሪያ_ስሞች
፠ ጥዑመ ልሳን፤
፠ የሱራፌል አምሳያ፤
፠ የቤተ ክርስቲያን እንዚራ፤
፠ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን፤
፠ መዓርዒረ ዜማ፤
፠ ካህን (ካህነ ስብሐት)
፠ ማኅሌታይ፤
፠ መዘምር ዘበድርሳን፤
፠ ሊቅ (ርእሰ ሊቃውንት)
፠ ዓርከ ሊቃውንት፤
፠ ደራሲ፤
፠ የመጽሐፍ መምህር፤ (ብሉያትንና ሐዲሳትን የሊቃውንትንም መጻሕፍት አስማምቶ የተረጐመ)
፠ ባለቅኔ (የቅኔ ጀማሪ)፤
፠ የቤተክርስቲያን ጌጧና መሠረቷ ሕይወቷና እስትንፋሷ
፠ ልዑለ ስብከት፤
፠ ሰማዕት፤
፠ ባሕታዊ፤
፠ መናኝ
፠ የዜማ አባት፤
፠ የኢትዮጵያ ብርሃን፡፡
፠ አንደበቱ ጣፋጭ (ጥዑም) የኾነ::
፠ እግሮቹ በመልካም መንገድ የሚጓዙና ወደ መልካም መንገድ የሚያስጕዙ
፠ ልቡናው የቅድስና ማኅደር የኾነ::
፠ ሕሊናው የምሥጢራት ሠረገላ የኾነ::
፠ አእምሮው የመጠቀ፤
፠ ድርሰቱ የተራቀቀ፤
፠ እስከ አርያም ተነጥቆ ዕፁብ ድንቅ ምሥጢራትን የተመገበ ማን እንደርሱ:: …...
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
መላእክት ምስጋናቸው እረፍታቸው ፣እረፍታቸው ምስጋናቸው ሆኖ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ እግዚአብሔርን ያለማቋረጥ ያመሰግናሉ፡፡
ቤተክርስቲያንም አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ናትና ይህን አብነት በማድረግ ልዑል እግዚአብሔር ሃያ አራት ሰዓት የሚመሰገንበትን የምስጋና ሥርዓት ዘርግታለች፡፡
ሕያው እግዚአብሔር የአዳም ልጆች በመላእክት ምስጋና
እንዲያመሰግኑት በመውደዱ ሰማያዊውን ምስጋና ይማር
ዘንድ ቅዱስ ያሬድን መረጠ፡፡
ማህሌታዊው ቅዱስ ያሬድ የመላእክት የምስጋናውን እንጀራ
ያበላን የቤተ ክርስቲያን ባለውለታ እንቁ ነው።
በረከቱ ይደርብን!
< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >
#መልካም ቀን
#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ
ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
📌 የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ?
📌 ሊቀ መዝሙራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
📌 ሊቀ መዝሙራን ይልማ ኃይሉ
📌 ዘማሪ አርቲስት ይገረም ደጀኔ
📌 ዘማሪ ገ/ዮሐንስን ገ/ፃዲቅ
📌 ቀሲስ ምንዴዬ ብርሀኑ
📌 ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ
📌 ዘማሪ ምርትነሽ ጥላሁን
📌 ዘማሪት አቦነሽ አድነው
እና የሌሎችንም ...........
የዘማሪዎችው መዝሙሮችን ለማግኘት ከስር Join የሚለውን ንኩት 🔻🔻🔻
👇👇👇
/channel/+2ua4-eAbNTI1MTRk
/channel/+2ua4-eAbNTI1MTRk
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
አይደረግም ‼️
የቤተ ክርስቲያን የሴራ ፖለቲካ አስፈፃሚ እንድትሆን መከራዋ እንዲበዛ ካልተፈለገ በስተቀር አባ ሳዊሮስን በየትኛው መልካም ስራው ይመረጣል ኸረ እረፉ ነገ የምትቆጩበትን ስራ ዛሬ አትስሩ እባካችሁ አባቶች የምእመናን እንባ አይገዳችሁም ወይ ?
#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo