ortodoxtewahedo | Unsorted

Telegram-канал ortodoxtewahedo - ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

64069

ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ። ‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3 https://youtu.be/csxxAMGtC4I ለመቀላቀል http://t.me/ortodoxtewahedo

Subscribe to a channel

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

መ/ር ልደተቃል

ብርቱ አርቶዶክሳዊ ወጣት ቤተ ክርስትያን ብዙ ልደተዎች ያስፈልጓታል በርታልን ወንድማችን ።

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

🔴 መድኃኔአለም 🔴
✍️✍️✍️
መድኃኔአለም ማለት አለምን ያዳነ የአለም መድኃኒት ማለት ነው። ሰው በመበደሉ ምክንያት ከክብር ተዋርዶ ይኖር ነበር።ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የተዋረደውን ሰው እርሱ በመስቀል ተሰቅሎ ወደ ቀድሞ ክብሩ መለሰው። ምን አይነት ፍቅርነው?????
ወንድሜ /እህቴ አስባችሁታል ግን እኛን ለማዳን ብሎእኮ ነው

የተሰቀለው፡ራቁቱን በመስቀል ምን ያህል
አሳፋሪ እንደሆነ እናውቀዋለን
ጌታ ግን እኛን ለማዳን ብሎ መስቀሉን ናቀው።
በፈጠራቸው ፍጥረት ተተፋበት።
እኛን ትእግስት ሊያስተምረን እነርሱን ማጥፋት
እየቻለ እርሱ ግን

💖በፍቅር እያዩ የማያውቁትን አያውቁምና
አባት ሆይ ይቅር በላቸው ይል ነበር።
ክርስቶስ እኛን ለማዳን ሲሰድበት
አልተሳደበም ሲንቁት አልናቃቸውም
ሲታበዩበት ሁሉ እርስ ግን በትህትና ያያቸው ነበር።

💖ታዲያ እኛ ደግሞ እራሳችንን ለማዳን ሰዎች ሲንቁን ሲሰድቡን ሲታበዩን በፍቅር በዝምታ ማለፍ ይጠበቅብናል።
ይህን ካደረግን የክርስቶስ ደቀ መዝሙር እንባላለን።
በ 5 ችንካር ነበር የቸነከሩት።

በመስቀል የተገኙ ድንግል ማርያም ሐዋርያው ዮሐንስ ነበሩ። አንተም በመስቀሉ ስር
ለመገኘት ከፈለግህ ትእግስትን ፍቅርን ትሕትናን ገንዘብ አድርግ።

መድኃኔአለም በቸርነቱ ይቅር ይበለን።

#27 ❤️

"ወዳጄ ሆይ ሮማውያን ወታደሮች ጎንጉነው በጌታችን እራስ ላይ እሾህ እዳቀዳጁት ባሰብህ ጊዜ እጅግ ማዘንህ አይቀርም ። ሆኖም አንተም እሾህ የተባለውን አንድ ኃጢአት በሰራህ ቁጥር በጌታችን ላይ የተደፉትን እሾኾች ቁጥር እንደጨመርህ አስብ ።በፈጣሪ የማያምኑት ሮማውያን ወታደሮች ከጎነጎኑት እሾኽ በላይ የጌታችንን እራስ የበለጠ ዘልቆ የሚወጋው ደሙን አፍስሶ ያዳነን እኛ ክርስቲያኖች በኃጢአታችን የምንጎነጉነው የእሾኽ አክሊል ነው ።{ስለመተላለፋችን የቆሰለው አምላክ በመተላለፋችንም ይቆስላል ።!}

{በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን ከሚለው ርዕስ የተወሰደ )

[ ሕማማት]
{በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ}

መድኃኔዓለም ሆይ አባት ሆይ ይቅር በላቸው በማለት በታላቅ ቃል በመስቀል ላይ ፥ ለተናገረ ቃልህ ሰላም እላለሁ በመስቀል ላይም በሰቀሉህ ጊዜና ጎንህን በጦር በወጉ ጊዜ አንዳችም የተቃውሞ ትንፋሽ ላልተነፈሰ እስትንፋስህም ሰላም እላለሁ ።
መድኃኔዓለም ሆይ ጻድቃንን ያይደለ ኃጥአንን ለማዳን በራሱ ደም ራሱ ለተጥለቀለቀ ስነ መልክህ ሰላም እላለሁ !

( መልክአ - መድኃኔአለም )27❤

@ortodoxtewahedo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

☞ግንቦት 26 እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የልደት በዓላቸው
በሰላም አደረሳችሁ፡፡
☞አባታቸው ፍሬ ቡሩክ እናታቸው ዮስቴና የሚባሉ በሕገ እግዚአብሔር፡
በሃይማኖት በምግባር ጸንተው የሚኖሩ ደጋግ ክርስቲያኖች የገኙ አባት ናቸው፡፡
☞አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም ፅንሰታቸው ነሐሴ 26፤ ውልደታቸው ግንቦት
26፤ ዕረፍታቸው ኅዳር 26 ነው፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖት አቡነ ሀብተማርያምን አምስት መቅሰፍታት እንዲጠፋ
በደጄ በደብረ ሊባኖስ ተቀበርልኝ ብለው የለመኗቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ይህ
እንዴት ነው ቢሉ
☞አቡነ ተክለሃይማኖት እኔ ከተቀበርኩበት ቦታ እድትቀበር ቃልኪዳን ግባልኝ
ብለው ጠየቋቸው፡፡
☞አቡነ ሀብተማርያምም አባቴ ሆይ ይህንን አደርግ ዘንድ ሰለምን ትወዳለህ?
አላቸወ፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖትም በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስት መቅስፍቶች አሉና
ሰለዚህ ነው እነዚህም አንዱ መብረቅ ሁለተኛው ቸነፈር ነው ሦስተኛው ረሀብ
ነው፤ አራተኛው ወረርሽኝ ነው አምስተኛው የእሳት ቃጠሎ ነው፡፡ የአንተ አጽም
በውስጡ የተቀበረ እንደሆነ ከነዚህ መቅስፍታት ትድናለች አሏቸው፡፡
☞አቡነ ሀብተ ማርያም ንዑድ ክቡድ የምትሆን አባቴ ሆይ ልዩ ክብር በሚሆን
በአንተ አጽም መቀበር ያልዳነች በእኔ አጽም መቀበር ድኅነትን ታገኛለችን?
ብለው ተከራከሩ በዚህም ጊዜ አቡነ ተክለሃይማኖት መልሰው
☞አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሔር የተሰጠህ እኔ የማውቀው
ክብር አለህና ሰለዚህ ነው፡፡ ይልቅስ እንዳልኩህ በተቀበርኩበት ቦታ እንድቀበር
ቃልኪን ግባልኝ ብለው ማለዷቸው፡፡
☞ይህንንም ሲባባሉ እንዲህ የሚል ቃል መጣላቸው ከወዳጄ ከሀብተ ማርያም
እንደበት ይህ ቃል አይወጣም፤ ዳግመኛም ወዳጄ ተክለሃይማኖት ሆይ እርሱ
በወደደው የሚቀበር አይደለምንና እኔ ከተቀበሩኩበት እንድትቀበር ብለህ
የምታስገድደው ለምንድ ነው?
☞እኔ በወደድሁት ቦታ ይቀበራል እንጂ የሚል ቃል ተነገረ፡፡
☞አቡነ ተክለሃይማኖትንም እየለመኑና እየሰገዱከሥላሴ ዙፋን ተንበረከኩ፡፡
☞በሦስተኛውም ይሁን እንዳልከው ይቀበርልህ የሚል ቃል ተሰማ፡፡
☞ዳግመኛ በአንተም አጽም በሀብተ ማርያምም አጽም ቦታህ ከመቅሰፍት
ትድናለህ ልጆችህ ግን በቸነፈር ደዌ ቢሞቱ ከሰማዕትነት ተቆጥሮላቸው ወደ
መንግሥት ሰማያት እንዲገቡ በራሴ ምዬ ቃልኪን ገብቼለሃለሁ አላቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አቡነ ተክለሃይማኖት እጅግ ደስ ተሰኙ፡፡

(ገድለ አቡነ ሀብተማርያም)

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

" የአባቶቻችን ትምህርት እናስተምራለን ፤ ተስፋቸውንም ተስፋ እናደርጋለን ፤ የተማርናት ፤ ተስፋ የምናደርጋት ሃይማኖት ይህች ናት:: እንኖርባታለን ፤ እንሞትባታለን ፤ በእግዚአብሔር ፍቃድ እንነሣባታለን "

ሃይማኖተ አበው
እንቁ መምህራችን የሆኑት እዮብ ይመኑ ትምህርቶች ለማግኘት ከታች ናለድ ሊንክ ይግቡ❤️


የይቱብ ቻናላችን ሰብስክራይብ ያድርጉ
      👇👇👇
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9
https://youtu.be/yI-3Sl9NB5c?si=1fCKjnh4FjRC2OJ9

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

💍ከጋብቻ በፊት ሩካቤ (sex) መፈጸም ምን ችግር አለው⁉️

💁‍♂ከትዳር በፊት መሳም (ከንፈር ወዳጅ /kiss) ይቻላልን⁉️

👨‍🦱🧑‍🦳ፍቅረኛሞቹ እጅግ በጣም ስለሚውዋደዱ (ሩካቤ/sex) ቢፈጽሙ ምን ችግር አለው⁉️

⛪️በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ከተዋደዱ በኋላ ስሜታቸው ይገደባል⁉️

🤵‍♂የስሜት መግለጫዎች መፈጸም ይቻላል⁉️

በነዚህ ትምህርቶች ዙሪያ እየተማርን እንገኛለን
እርሶም እውቀቱ እዲኖርዎ ከፈለጉ ይህን ማስፈንጠሪያ Link ጠቅ ያድርጉት
                👇👇👇
     @EOTC_-OPEN_channel
     @EOTC_-OPEN_channel
     @EOTC_-OPEN_channel
     @EOTC_-OPEN_channel



        
                     🔔
          🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺‌‌
          ♦️በይቱብ♦️
                    👇🏽👇🏽
🧏መናፍቃን ከሚያነሷቸው ጥያቄዎች⁉️
የጌታችን እናት የአዳም የውርስ ኃጢአት/ጥንተ አብሶ/አለባት⁉️
የጌታችን እናት አልተነሳችም⁉️
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=K22Xvwmx3Xo89L8k
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=K22Xvwmx3Xo89L8k
         👆👆👆
👉ለነዚህ ጥያቄዎች እና ለመሳሰሉት በቂምልሽ ተሰቶበታ ይቱብላይ ታገኙታላቹ።

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

❖ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የዕርገት በዓል በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ።

#ዕርገት

ቤተክርስትያናችን ከምታከብራቸው በዓላት ውስጥ አንዱ የጌታችን የመድኃኒታችን የእየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ነው።ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ በ፵ኛው ቀን ማረጉን በማሰብ ቤተክርስትያናችን ዕርገትን ትንሳኤን በተከበረ በ፵ኛው ቀን ዕርገትን ታከብራለች።በዚህ ዓመትም ቤተክርስትያነችን ዕርገትን ግንቦት21 ታከብረዋለች።
ዕርገት ልክ እንደ ትንሳኤ ሁሉ ቀኑ ይለዋወጣል። ነገር ግን ምንጊዜም ዕርገት ሐሙስን አይለቅም።ልክ ትንሳኤ እሁድን ስቅለት አርብን እደማይለቅ ሁሉ እርገትም ሐሙስን አይለቅም።

ዐረገ በስብሐት

ዐረገ በስብሐት ዐረገ በእልልታ
በስብሐት በእልልታ ዐረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
ሞትን ደል አድርጎ የሰራዊት ጌታ
አረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
እየዘመሩለት መልአክት በደስታ
አረገ በስብሐት በእልልታ

❖ መልካም በዓል #ምሽት/ቀን ይሁንልን።


#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

እመቤታችን በደብረ ምጥማቅ በምትባል ቦታ ወርቅ ወንበር ላይ ተቀምጣ ለአምስት ቀን የታየችበት ነው።

ይህም በዓል ከ33ቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ሲሆን በዚህ ቀን ግብጽ ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቦታ በተሰራች ቤተክርስቲያን እመቤታችን ጻድቃንን መልአክትን አስከትላ ትገለጽላቸው ነበር።

እስላምም ክርስቲያንም በግልጽ ይመለከቷት ነበር። ከየአገሩ ያሉ ሰዎች ይሰበሰባሉ ድንኳን ተክለው ሰቀላ ሰርተው አጎበር ጥለው ይከትማሉ ፤ድንግልም ከግንቦት 21 ቀን ጀምሮ ለአምስት ተ...ከታታይ ቀናት ሳታቋርጥ ትገለጽላቸው ነበር።

ህዝቡ የተለያየ ጥያቄ ይጠይቃታል አዳም አባታችንን አሳይን ይሏታል ግማሹ ነብዩ ዳዊትን ግማሹ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሳይን ይሏታል አንዳንዱም ከዚህ ቀደም የሞተ ዘመዱን እንድታሳየው ይጠይቃታል፤እርሷም ለሁሉም ፍቃዳቸውን ትፈጽምላቸው ነበር።

አዳምን ስትጠራው ከሔዋን ጋር ዳዊትን ስትጠራው ከበገናው ጋር ቅዱስ ጊዮርጊስን ስትጠራው ከጸአዳ ፈረሱ ጋር ነው።የእመቤታችን ረድአት እና በርከቱ በሁላችን ላይ ይድርብን አሜን 🙏

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ትዳር✝
  
           
Size:-61.2MB
Length:-1:06:04

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

2. ለሰዋስው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የትርጓሜ መጻሕፍትና የሴሚናሪ ደቀ መዛሙርት የሚሰጠው የምስክር ወረቀት ዲግሪ እንዲሆን በተወሰነው መሠረት በመማር ላይ ያሉትና በቀድሞው ሥርዓተ ትምህርት ተምረው በመመረቅ ቤተ ክርስቲያናችንን በማገልገል ላይ የሚገኙት ምሩቃን ተጓዳኝ ትምህርቱን ተምረው ዲግሪያቸውን ማግኘት እንዲችሉ የቀረበው ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ እንዲደረግ፣በኮሌጁ የተጀመረው ሁለገብ ሕንፃም በተያዘለት የጊዜ ሠሌዳ መሠረት እንዲጠናቀቅ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
3. በገዳማት አስተዳደር መምሪያ አስፈጻሚነት የተደረገው የአንድነት ገዳማት ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ በየዓመቱ እንዲካሄድና የአቋም መግለጫው ላይ የቀረቡት ሐሳቦች በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት በኩል እየታዩ በቅደም ተከተል እንዲፈጸሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አስልፏል፡፡
4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሀገራችን እድገትና ሥልጣኔ ፈር ቀዳጅ በመሆን ያበረከተችው አስተዋጽኦ በታሪክ ምዕራፍ ውስጥ ጉልህነት ያለው ሲሆን፣ አሁንም እየተሠራ ባለው የኮሪደር ልማት መርሐ ግብር ላይ ኃላፊነቷን እየተወጣች ትገኛለች፡፡
ይኽን ቋሚ ታሪክ ያልዘነጋው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ የቤተ ክርስቲያንን ይዞታ ለግንባታ በሚያመች ሁኔታ አሰባስቦ በመስጠት ለፈረሱ ቤቶች ካሣ በመክፈል፣ በጽርሐ ምኒልክ ሕንጻ ምትክ በነባሩ ቦታ ላይ B+G+4+ቴራስ በመንግሥት በጀት መልሶ እንዲገነባ በማድረጋቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡

በይዞታዎቻችንም ላይ ደረጃውን የጠበቀ ግንባታ ለማካሄድ የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ተሰይሞ ገቢ የማሰባሰብ ሥራው በሕጋዊ መንገድ እንዲከናወን ቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያ ሰጥቷል፡፡
በመሆኑም በፈረሱት ቤቶች ምትክ የተረከብናቸውን ክፍት ቦታዎች በአጭር ጊዜ ማልማት ግዴታ ስለሆነ በዓለም ዙሪያ ያላችሁ ኦርቶዶክሳውያን የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን እንደ አባቶቻችሁ የታሪክ ባለቤቶች ትሆኑ ዘንድ ልማቱን በገንዘብና በእውቀት እንድታግዙ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
5. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የተፈጠረውን የአስተዳደር ችግር አስመልክቶ በብፁዓን አባቶች የሚመራው አጣሪ ልዑክ ባቀረበው ሪፖርት መሠረት ውይይት በማድረግና የሥራ ኃላፊዎቹን በማንሣት ቅዱስ ሲኖዶስ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡
ወደፊትም በየደረጃው ያለውን ችግር ማስተካከል ይቻል ዘንድ ችግሩን እያጠና የሚያቀርብ ኮሚቴ እንዲቋቋም ምልአተ ጉባኤው ወስኗል፡፡

6. ዝክረ ኒቅያ በሚል መሪ ቃል ከመላው ሀገራችን በተወከሉ የምስክር ጉባኤ ቤቶች መምህራን በተካሄደው ጉባኤና የጥናት ውይይት የቀረበው ምክረ ሐሳብ እጅግ የሚጠቅም የሊቃውንት ድምጽ በመሆኑ፣በነገረ ማርያም፣ በነገረ ክርስቶስና በሌሎችም አስተምህሮዎች ዙሪያ የተሰጡት ሐሳቦች የቅዱሳት መጻሕፍት ትርጓሜን መሠረት በማድረግ ተብራርቶና ተስተካክሎ፣ የጎደለው ሞልቶ፣ የጠመመው ተቃንቶ በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በመጽሐፍ መልክ እንዲታተም፣በሚዲያ ሊተላለፍ የሚገባው አስተምህሮ ደግሞ በሊቃውንት ጉባኤ ብቻ እንዲተላለፍ፣
የሊቃውንት ጉባኤውም በተሟላ የሰው ኃይልና በጀት ተጠናክሮ እንዲደራጅ፣ሀገር አቀፍ ጉባኤው በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲደረግና የጉባኤው መዋቅር በየአህጉረ ስብከቱ እንዲጠናከር ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

7. የመናገሻ አምባ ማርያምና የጋራው ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም አንድነት ገዳም ጥንታዊ የሆነ ሰፊ ታሪክ ያለው በመሆኑ ሁለቱ ገዳማት በአንድ አበምኔት በአንድነት ገዳም ሥርዓት በጋራ እንዲመሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤

8. በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት መነኰሳትን ከመላክ ጀምሮ፣በአስተዳደራዊና ቀኖናዊ አሠራር ክፍተት ምክንያት የተከሰቱ ችግሮችን በማረምና ሊቀ ጳጳሱን በማዛወር ማእከላዊ መዋቅር እንዲጠበቅ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነ ሲሆን፣ነባሩ መተዳደሪያ ደንብ ተሻሽሎ እንዲቀርብ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ ኮሚቴ ሰይሟል፤

9. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሕገ ልቡና፣በሕገ ኦሪትና በሕገ ወንጌል ያገኘቻቸው ዶግማዊ፣ ቀኖናዊና ትውፊታዊ ሀብቶቿ የሕግ ጥበቃና ከለላ አግኝተው ሃይማኖታዊ፣ታሪካዊና ሁለንተናዊ ይዘታቸውን ሳይለቁ ተከብረውና ተጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
10.  የ2018 ዓ.ም የመደበኛ እና የካፒታል ዓመታዊ በጀት ብር 5,407,415,607.25/አምስት ቢሊየን አራት መቶ ሰባት ሚሊዮን አራት መቶ ዐሥራ አምስት ሺህ ስድስት መቶ ሰባት ብር ከሃያ አምስት ሣንቲም/እንዲሆንና የበጀት አርዕስቱ ተጠብቆ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

11. በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ በመገንባት ላይ የሚገኘውን ሕንጻ በተመለከተ የተፈጠረው የአሠራር ግድፈት እንዲታረም፣ዩኒቨርስቲው ከባንክ ጋር የገባው የብድር ውል እንዲቋረጥና የተጀመረውን ሕንፃ በራሱ አቅም እንዲገነባ ሆኖ፤ የቤተ ክርስቲያናችንን አንጡራ ሀብት ማለትም ሕንጻዎችን፣መሬቶችንና ሌሎች ቋሚ ንብረቶችን በማስያዝ የሚደረጉ ብድሮች ተፈጻሚ እንዳይሆኑ የሚያደርግ መመሪያ ለሁሉም አህጉረ ስብከት እንዲተላለፍ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
12. የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደር ልማት ድርጅትን አስመልክቶ በቀረበው ሪፖርት መሠረት የሥራ ክፍተቱን በማረም በየደረጃው ያሉ ኃላፊዎች እንደየጥፋታቸው እንዲጠየቁና እንዲታረሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
13. የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ምርጫን አስመልክቶ በሥራ ላይ የነበሩት ብፁዓን አባቶች የሥራ ዘመናቸውን ያጠናቀቁ በመሆኑ ለቀጣይ ሦስት ዓመታት የሚሠሩ ብፁዓን አባቶችን ለመምረጥ ዕጩዎችን የሚያቀርቡ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን በመሰየም ምልዓተ ጉባኤው ተገቢውን ምርጫ አከናውኗል፡፡
በዚሁም መሠረት ፡-
*. ለቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊነት ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ፣ በደቡባዊ ዞን ማይጨው፣ የደቡባዊ ምሥራቅ ትግራይና የራያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን መርጦ ሰይሟል

*. ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪጅነት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ፣የሸገር ከተማ እና የምስካዬ ኀዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ሊቀጳጳስን መርጦ ሰይሟል፡፡
* ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀድያና ስልጤ አህጉረ ሰብከትን እንደያዙ  የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
* ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲሠሩ ቅዱስ ሲኖዶስ መርጦ ሰይሟል፡፡
* ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ
* ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የሜኖሶታና የኮሎራዶ አህጉረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲሠሩ ቅዱስ ሲኖዶስ መድቧል፡፡

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ምን አይነት መዝሙሮችን ይፈልጋሉ?👇👇👇

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ዲ/ን ፈለገ አትናቴዎስ

ብርቱ አርቶዶክሳዊ ወጣት ቤተ ክርስትያን ብዙ ፈለገዎች ያስፈልጓታል በርታልን ወንድማችን ።

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

🌎አንዴ ብቻ ይንኩት አለማትን የፈጠረውን ጌታ በሕይወት ያመስግኑ ፣ ስትነኩት የሚወስዳችሁ ቦታ በጣም ይጠቅማቹሀል !
                 👇👇👇

.            ✦              ‍ ‍ ‍ ‍                  ,    

.             .   ゚     .         🌑            .           .            

 ˚                     ゚     .               .      🌎 ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ‍ ,                * .                    .           ✦           ˚              *                      .  

.             .   ゚     .             .

      ,       .                               ☀️                                *         .           .             .                                                               ✦      ,         *   🚀        ,    ‍ ‍ ‍ ‍               .            .                                   ˚          ,                              .                 

         

             *          ✦                                .                  .        .        .     🌑            .           .            

 ˚                     ゚     .               .

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ከዐራቱ ወንጌላውያን በስዕሉ ላይ አንበሳ ከጎኑ ሆኖ የሚሳለው ማን ነው❓

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የብልጽግናው ዋና ሴራ አስኪያጅ ባለሙሉ ሥልጣን ሆኖ ቤተ ክርስቲያን ላይ ተቀምጧል፡፡ በመጨረሻም ሰዎቹ እንደፎከሩት፣ እንደቀሰቀሱት ቤተ ክርስቲያንን ከነሁለንተናዋ ተረክበዋል፡፡ ያ ሁሉ ግርግር፣ ያሁሉ እስር፣ ያ ሁሉ ቅስቀሳ ለዚህ ነበር፡፡

የኢትዮ ፎረሙ ዘገባ ወገባቸውን የመታው፣ ሴራቸውን ቀድሞ ያጋለጠባቸው ለዚህ ነበር፡፡ ያንን ሲያጣጥሉ የነበሩ የቤተ ክርስቲያን ሰዎች አሁን እርማቸውን ያውጡ፡፡ ሁኔታዎችን ባለመረዳት ጭምር ቤተ ክርስቲያናቸውን አዘናግተዋታልና፡፡ አሳዛኞች፡፡

ቤተ ክርስቲያንን ለመክፈል ቀንደኛ የነበረውን ሰው፣ 'መክፈል ምን ይሠራልሃል፣ ገብተህ ሙሉውን ተረከብ እንጂ' በሚለው የብልጽግና ፈሊጥ ምክንያት ይኸው በቦታው ላይ አስቀምጠውታል፡፡ አሁን ከልካይም፣ ተቆጭም ገልማጭም፣ አምቢ ባይም የላቸውም፡፡ የፈለጉትን የሚሹትን የሚያደርጉበትን ሥልጣን ይዘዋል፡፡ ምክትላቸው ቄስ በላይ ገንዘብ ሠርቆ ታሠረባቸው እንጂ ያኔ ጀምረው ያቀዱት ይኸንን ሙሉ ወረራ ነበር፡፡

ቦታውን የፈለጉት ለቤተ ክርስቲያን ሥራ ሊሠሩላት ሳይሆን ሊሠሩባት፣ ቤተ ክርስቲያንን ሊያዋርዷት፣ ሊዘርፏት፣ ሊቀሟት ነው፡፡ ለብልጽግናም ሰጥ ለጥ ብላ እንድትገዛ ለማድረገ ነበር፡፡ አሁን ቤተ ክርስቲያ በገጣባ አህያ ተወራለች፡፡ ጫካ ሄዶ ሲኖዶስን ከከፈለ ሰው በላይ በክርስትናው ገጣባ አህያ ከየትም አይገኝም፡፡ ገጣ አህያ ደግሞ ጠባዩን ባለፈው አስረድቻለሁ፡፡ ክህደቱ፣ ሸፍጡ፣ ዘረኝነቱ ያመረቅዝበታል እንጂ የሚድንበት አንዳች እድል የለውም፡፡ በድለዳል፣ በጨርቅ ወዘተ ብታለባብሰው የሚሆን አይደለም፡፡

አሁን ያ ጸጉሩ መሸበቱን ለማየት ቆራጩን ሲያጣድፈው ለነበረው ሰው 'ሲወድቅ ልታየው ምን ያስቸኩልሃል እንዳለው' ቤተ ክርስቲያንም ጸጉሯን ተላጭታ፣ ሸበቶውን በግላጭ ፊታችን ወድቆ አየነው፡፡ መልኳ ተቀየረ፣ ያለ ተቆርቋሪ ቀረች፣ አሳልፋ ተሰጠች፣ ሲሞናዊነት ዐይኑን ጨፍኖ መላዋን ወረራት ማለት ነው፡፡

አሁን ቤተ ክርስቲያን የሚጠበቃትን የተጠናከረ ስደት፣ ሊሆንባት የታቀደውን፣ ማንንም መጠየቅ አያስፈልገንም፣ ራሳችን ፊት ለፊታችን መከራዋን ሲገለጥ አየነው፡፡ ሳዊሮስ መከራ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ሳዊሮስ አሳልፎ ሻጭ ነው፡፡ የምናውቅለት ታሪኩ ይኸ ነው፡፡

አሁን ያኔ 'ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር እርስዎ እኮ ቤቱን ትተውታል፣ እስከዛሬ እኮ እንዲህ አልነበረም' ያለውን ቃል ለመፈጸም፣ ቤተ ክርስቲያንን ለብልጽግና አሳልፎ የሚሰጥበትን ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡

በኦሮሚያ የሚደረግ የቤተ ክርስቲያን ስደት፣ በዐዲስ አበባ የሚደረግ የቤተ ክርስቲያን ወረራ ያለማንም ተቆጭና ገልማጭ ያስፈጽሙታል፡፡ የቤተ ክርስቲያንን መዋቅር ከላይ እስከ ታች፣ ከታጠቀ ኃይል እስከ ስለላ መረብ ተብትበው ተቆጣጥረውታል፡፡ 'ምንም አታመጡም እንዳሉት' አድርገውታል፡፡

አሁን ሁሉም በእጃቸው ነው፣ ዛሬ ደግሞ በጻዕር ላይ የነበረውን ጠቅላይ ቤተ ክህነትንም ፈጽመው ገድለውታል፡፡ ያንን ያደረጉት ደግሞ 'በመንፈስ ቅዱስ ይመራሉ' የተባሉት አባቶች ሲሆኑ በመንፈስ ቅዱስ መመራታቸውን ትተው እነ ከድር በጠቆሟቸው መሠረት የእነ ከድርን አባት የቤተ ክርስቲያኒቱ ሥራ (ሴራ) አስኪያጅ አድርገው መርጠዋል፡፡

በእኔ በኩል ቤተ ክርስቲያኔን የተቀማሁት ዛሬ ነው፣ ዛሬ የግመሉን ወገብ የሰበረው የመጨረሻው በትር ቤተ ክርስቲያን ላይ አርፎል አይቸዋለሁ፡፡ ምእመናን ሰሚ እንደሌላቸው፣ ጠላት ደግሞ የፈለገውን ነገር የማድረግ አቅሙን ያሳዩበት ነው፡፡ ሰማያዊቷን ቤተ ክርስቲያን ሊቀሙን ባይችሉም፣ የሰማያዊቷን ቤተ ክርስቲያን ማሳለጫ የሆነችውን የምድራዊቷን ቤተ ክርስቲያንን መዋቅር ያላቸውን ኃይል ተጠቅመው ከምእመናን መቀማት የቻሉበት ቀን ተደረጎ ይወሰዳል፡፡

አሁን ውሉ ወደማይታወቅ፣ እጅግ በሚያሳስብ ጨለማ ተወርውረናል፣ መዋቅሩም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ወድቋል፡፡

ዳሩ ግን ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያን ትንሣኤ ይኖራት ይሆን? ለዚህስ የሚረባረቡ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ይኖሩ ይሆን? ምእመናን ሰፊ ትግል ይጠይቀናል፡፡ ይኸንን ችላ ብለን የተውን እንደሆነ፣ በመዋቅሯ ሽባነት ስደት፣ ፈተና፣ የመንጋ ነጠቃ መከራ ስትቀበል የቆየችው የነበረችው ቤተ ክርስቲያን፣ አሁን ደግሞ በቅሰጣ ባልሆነ ነገር ግን በሁለንተናዊ ነጠቃ ሙሉ በሙሉ ልናጣት የምንችልበት አጋጣሚ ተፈጥሯል፡፡

አሁን ድርሻው የምእመናን ነው፡፡ እለ ከድር በመረጡላቸው፣ ፖለቲከኞች እንደፎከሩት ባስቀመጡላቸው ሰው ሴራ አስኪያጅነት እየተመሩ ቀጣዩን ሦስት ዓመታት ቤተ ክርስቲያናቸውን በማፍረስ ይተባበራሉ? ሰውየውም ቃል እንደገቡት ቤተ ክርስቲያኗን ከነሁለንተናዋ ለብልጽግና ሲያስረክብ ዝም ብለው ያዩ ይሆን? የሚሉት ጥያቄዎች በቀጣይ የሚታዩ ይሆናሉ፡፡

ሰፊ ትግል፣ ሰፊ ርብርብ የሚጠይቅበት ወቅት ላይ ወድቀናል፡፡ አሁን መተኛት እንኳን የሚቻለው በአንድ ዐይን ብቻ ይሆናል፡፡ አሁ ይሉኝታ ሊኖር አይገባም፣ አሁን የውጭና የውስጥ የሚባል ጠላት ቀርቷል፣ አሁን ያለው የውስጥ ጠላት ሆኗል፡፡ የውጩም ከነመሣሪያው ውስጥ ገብቶ ተጠቃሏል፡፡

ትግሉም ዋጋ የሚያስከፍል ዋጋም የሚያሰጥ ነው የሚሆነው፡፡

አንቺ ቤተ ክርስቲያን መጽናኛ ይስጥሽ!

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

🛑እነሆ አዲስ ቻናል ይዘንሎት መጣን🛑
በማርያም ይህን ቻናል ሳይቀላቀሉ እንዳያልፉ ይደሰቱበታል መርጠን ለናንተ አቀረብንሎ
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

         ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
         █   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲      █          
         ◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ሰንበተ ክርስትያን

እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች።

ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት
(ራዕይ 1፥10)

ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት።

መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን

#መልካም ቀን

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

❤️“ ንዑ ንትመሀር ልሳነ ግእዝ ”
🔅ኑ የግእዝ ቋንቋ እንማር🔅

📜 የሀገራችን የኢትዮጵያ ቀዳማዊና ጥንታዊ ስለሆነው የግእዝ ቋንቋ መሠረታዊ ትምህርት እንሰጣለን። እርስዎም አባቶቻችን ያቆዩልንን ቋንቋ በመማርና ለትውልድ በማስተላለፍ ኃላፊነትዎን ይወጡ!
📜

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ስርዓተ ኦሪት ስርዓተ ሀዲስ ከተፈጸሙባቸው 5 መቅደሶች መሐከል እንዷ የሆነችው የደቡቧ ኮከብ ብርብር ማርያም ነገ የእናታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ መገለጧን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች።
~~~~~~~

የደቡብ ክልል የክርስትና መነሻ እና የጥንታዊ ህገ እግዚአብሔር አምልኮ ማዕከል የሆነችው በጋሞ ጎፋ ሀገረስብከት የምትገኘው ብርብር ማርያም ነገ የእናታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ መገለጧን በደምቀት ታከብራለች።

በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መሰዋተ ኦሪት ከተፈጸመባቸው 5ቱ መቅደሶች መሀከል አንዷ የሆነችው ብርብር ማርያም ገዳም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓላትን እንደ ብሔራዊ በዓላት ልክ የአከባቢው ምዕመናንን እንደሚያከብሩ ይታወቃል።

የቴሌግራም ቻናላችን ከታች ያለውን ሊንክን በመስፈንጠር ቤተሰብ ይሁኑን፤

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

† እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የመገለጥ በዓል (ደብረ ምጥማቅ) በሰላም አደረሳችሁ †

†ደብረ ምጥማቅ †

=>የአርያም ንግሥት: የሰማይና የምድር እመቤት: የሰውነታችንም መመኪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በዚሕች ዕለት በምድረ ግብፅ ለተከታታይ ቀናት ተገልጻለች::

+ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:

+ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድረ ግብፅና ኢትዮዽያ በተሰደደ ጊዜ ከድንግል እናቱ: ከዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ዛሬ ደብረ ምጥማቅ በሚባለው ቦታ ላይ አርፎ ነበር:: ቦታውን ባርኮ ለዘለዓለም ያንቺ መገለጫ ይሁን ብሎም ቃል ኪዳን ገብቶላት ነበር::

+ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት ቤት ሆነ:: እመቤታችንም በልጇ ፈቃድ ግንቦት 21 ቀን አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላት መጣች::

+በዚያ ሕዝበ ክርስቲያንም: አሕዛብም ተሰብስበው ለ5 ቀናት ከእመ ብርሃን ጋር ይሰነብታሉ:: እንግዲህ ልብ በሉት:-
እንኩዋን የአርያም ንግስት: የአምላክ እናቱ እመቤታችንን ይቅርና በዚሕ ዓለም ሰይጣን ቤቱ ያደረጋቸውን: የመዝናኛው ኢንዳስትሪ ዝነኛ ሰዎችን ለማየት የዘመናችን ሰው እንዴት እንደሚቸኩል::

+እመቤታችንን በአካል መመልከት አይደለም ስሟን መጥራት ነፍስን ከሥጋ መለየት የሚችል ጣዕምና ደስታ አለው:: ባይሆን ይሔ ለሚገባውና ላደለው ብቻ ነው::

+የደብረ ምጥማቅና የአካባቢዋ ሰዎች ከእመቤታችን ጋር የሚቆዩባቸው ቀናት የዘለዓለም የሕይወት ስንቅ የሚይዙባቸው ናቸው:: ፈልገው የሚያጡት: ጠይቀው የማይፈጸምላቸው ምንም ነገር አልነበረም:: ነቢያት: ሐዋርያት: ጻድቃን: ሰማዕታት: ደናግል: መነኮሳት: መላዕክትና ሊቃነ መላእክት ለድንግል ማርያም ሲሰግዱ ይታዩ ነበርና:: እመ ብርሃንም እየመላለሰች ትባርካቸው ነበር::

+እነዚያ እርሷን ያዩ ዐይኖች: በፊቷ የቆሙ እግሮች ክብር ይገባቸዋል:: 5ቱ ዕለታት ሲፈጸሙ ሕዝቡ እመቤታችንን በዕንባ ይሰናበቷታል:: እመ ብርሃንም በብርሃን መስቀል ባርካቸው ከቅዱሳኑ ጋር ታርጋለች::

እናቶቻችን የተገለጠች እመቤታችን ለእኛም በረድኤት ትገለጽልን:: ጣዕመ ስሟ በአንደበታችን: ጣዕመ ፍቅሯ በልባችን ይደርብን:: †††

"+ የምድር ባለጠጐች አሕዛብ በፊትሽ ይማለላሉ::
ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ሁሉ ክብሯ ነው::
ልብሷ የወርቅ መጐናጸፊያ ነው::
በሁዋላዋ ደናግሉን ለንጉሥ ይወስዳሉ . . .
በአባቶችሽ ፈንታ ልጆች ተወለዱልሽ::
በምድርም ሁሉ ላይ ገዥዎች አድርገሽ ትሾሚያቸዋለሽ::
ለልጅ ልጅ ሁሉ ስምሽን ያሳስባሉ::

+"+ (መዝ. 44:12-17)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር >

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

+ ደብረ ምጥማቅ +

ከሠላሳ ሶስት የእመቤታችን በዓላት አንዱ ነው ግንቦት_21 ቀን የሚከበረው ይህ የእመቤታችን በዓል ደብረ ምጥማቅ በምትባል ቦታ የወርቅ ወንበር ላይ ተቀምጣ ለአምስት ቀን የታየችበት ሲሆን በዚህ ቀን በግብጽ ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቦታ በተሰራች ቤተክርስቲያን እመቤታችን ጻድቃንን መልአክትን አስከትላ ተገለጽላቸው ነበር ።

እመቤታችን በስደት ሳለች ጌታ በዚህ ቦታ በስምሽ ቤተ ክርስቲያን ይታነጻል ስሙንም ደብረ ምጥማቅ ይሉታል ብሎ ነግሯት ነበር ይኸውም አልቀረም በዚሁ ቦታ በእመቤታችን ስም ቤተ ክርስቲያን ታንጾ ስሙ ደብረ ምጥማቅ ተብሏል ።

በዚህ ዕለት እመቤታችን ከፀሐይ ሰባት እጅ አብርታ ከጉልላቱ ላይ በመንበር ብርሃን ተቀምጣ መላእክት ሊቃነ መላእክት ከበው ሲያመሰግኗት ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃን ሰማዕታት እጅ ሲነሣት ታይታለች

እስከ አምስት ቀንም ምእመናኑን አረማውያኑን አንድ ወገን አድርጋ ስትባርክ ሰንብታለች ከዚህም በኋላ ምእመናንም አረማውያንም በየዓመቱ እነዚህን ከግንቦት 21 እስከ ግንቦት 25 ለአምስት ዕለታት በደብረ ምጥማቅ ተሰብስበው የሚያከብሩ ሆነዋል ።

እኛም ለልጆቿ በሕይወታችን እየተገለጠች በረድኤት በበረከት ትባርከን !!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

14. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ሰብከት ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች አህጉረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካልፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሚዲያ ያስተላለፏቸው ትምህርቶች ስሕተትና ነቀፋ ያለባቸው  መሆናቸውን አምነው ቅዱስ ሲኖዶስንና መላውን ሕዝበ ክርስቲያን ይቅርታ በመጠየቅ ሊቃውንት ጉባኤ ከቅዱሳት መጻሕፍት በማጣቅስ ያቀረበውን አስተምህሮ የተማሩት የሚያምኑትና የሚያስተምሩት መሆኑን በመግለጻቸው ቅዱስ ሲኖዶስ የሦስቱን አባቶች ይቅርታ ተቀብሎ ወደፊት እንዲህ ዐይነት የስሕተት  ትምህርት ውስጥ እንዳይገኙና ነቀፋ ያለበትን ትምህርታቸውን በማረምና በማስተካከል  ርቱዕ የሆነውን የቤተ ክርስቲያናችንን አስተምህሮ መሠረት በማድረግ በኢትዮጵያ ኦርቶዶስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  መገናኛ ብዙኀን ሥርጭት ድርጅት በመቅረብ ትምህርት እንዲሰጡ በማለት ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡
15. በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚኖሩ በግልና በቡድን ተደራጅተው ማኅበራዊ ሚዲያዎችን በመክፈት ከሃይማኖት ሥነ ምግባር በወጣ መልኩ የቤተ ክርስቲያናችንን ልዕልና የቅዱስ ሲኖዶስን ክብር የሚጋፋ ፣የአባቶችንና የአገልጋዮችን ተልእኮ የሚያደናቀፍ ያልተገባና መሠረት የሌለው መግለጫ የሚያሰራጩ አካላት እንዲታረሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በጥብቅ ያሳስባል፡፡

በመጨረሻም በሀገራችን በአንዳንድ ቦታዎች የሚታየው ግጭትና መፈናቀል ተወግዶ፣የሰው ልጅ የመኖርና የመዘዋወር መብት ተከብሮ፣ ሰብዓዊ ክብሩ ተጠብቆ ሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በሰላምና በፍቅር ተከባብሮ በጋራ እንዲኖር፤ አለመግባባቶች በውይይት እንዲፈቱ ቤተ ክርስቲያን የሰላም ጥሪዋን ታስተላልፋለች፡፡

ግጭት፣ ጥላቻና ደም መፋሰስ፣ አካል ከማጉደልና ንብረት ከማጥፋት በቀር የሚያመጡት ክብርና ዘላቂ ሰላም ስለሌለ ልጆቻችን ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ እንድትፈቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ደጋግሞ ጥሪውን በማቅረብ በመላው ዓለም ጦርነት ባለባቸው ሀገራት ሁሉ ሰላምና ዕርቅ እንዲሰፍን በመጸለይ ቅዱስ ሲኖዶስ ግንቦት 20 ቀን 2017 ዓ.ም ዓመታዊ ጉባኤውን በጸሎት አጠናቋል፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ

                  አባ ማትያስ ቀዳማዊ
      ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ግንቦት ፳ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የቅዱስ ሲኖዶስ  መግለጫ

ግንቦት ፳/፳፻፲፯ ዓ.ም

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት የርክበ ካህናት መደበኛ ስብሰባውን ከግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ አካሂዷል፡፡
የመንበረ ሐዋርያት ወራሽ የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነትና እድገት፣ ለሀገር ሰላምና መረጋጋት፣ ለሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋትና ለመንፈሳዊ ልዕልና ልዩ ትኩረት በመስጠት አስፈላጊ ውሳኔዎችን አሳልፎአል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
1. ለሰላምና ለአንድነት ቅድሚያ መስጠት፣ምትክ ለሌለው የሰው ልጅ ሕይወት ባለአደራ የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ሰላም ያለማቋረጥ መጸለይ፣ ጸሎተ ምሕላ ማወጅ፣ የሰላምና የአንድነት ጥሪ ማስተላለፉ እንደተጠበቀ ሆኖ ለሰላምና ለአንድነት ልዩ ትኩረት ሰጥተው ሁሉን አቀፍ ሥራ የሚሠሩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን “የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ” በማድረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡
ኮሚቴውም ዘላቂ ሰላምንና አንድነትን ለማስፈን፣ የዜጎችን ሕይወት እየነጠቀ ያለው ግጭት እንዲቆም ጥረት እንዲያደርግ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትን ባካተተ መልኩ በየደረጃው የምክክርና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና፣ ውይይቶችንና የጥናት መድረኮችን እንዲያዘጋጅ፤ አፈጻጸሙንም በየሦስት ወሩ ለቋሚ ሲኖዶስ ሪፖርት እንዲያደርግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

እኔና ልጄ ሰግደን እንመለሳለን✝
  
           
Size:-54.4MB
Length:-58:44

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ


#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የብርሃን እናት ነሽና /፪/
ለምኝልን ድንግል /፪

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ዲ/ን ዶር ቴዎድሮስ በለጠ ከአንድ ዓመት የጽሙና ጊዜ በኋላ ቀሪ ጊዜያቸውን በምንኩስና ሕይወት ለመኖር ጉዞውን ጀምረዋል። አባ ክፍለ ሥላሴም እንደ ተባሉ ምንጮች ገልጠዋል። የአበውን ጸጋ ሰጥቶ ያጽናልን
“ያላገባው ጌታን እንዴት ደስ እንዲያሰኘው የጌታን ነገር ያስባል፤” 1ኛ ቆሮ 7፥32

ምንጭ፦ማ/ሚድያ

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#like#share
ወደደንም ጠላንም እኝህ አባት የብዙ ኦሮቶዶክሳዊያን ስማእታት ደም በእጃቸው አለ ። ammatanis Amanuu baataniAbbaan keenyi kun Dhigga wareggamtoottaa Harka isaani irra jira.

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የቆያችኋባቸው መናብርት ከእናንተ በፊት በተራ የሚዳረሱና ማንም ጉዳይ የማይላቸው "የዙር ወንበሮች" ነበሩ። ከእናንተ በኋላ ያ ተቀይሯል። በገሐድም፣ በኅቡዕም፣ በመልከ ብዙ ግንባር (alliance) ከያዛችሁት ርቱዕ መንገድ እንድትናጠቡ የሚደረገውን ያልታዘብን አይደለንም። ያልተደረብንላችሁ እውነት ተደራቢ ስለማትሻ ነው። ባሰባችሁበትና ባሰብነው ልክ ተቋሙን ለመለወጥ እንዳልቻላችሁ እናውቃለን። ያንን የኃላፊነት ቀንበር ግን ብቻችሁን አትሸከሙትም። እንጋራችኋለን። በሦስት ዓመት የሠላሳ ዓመት ሰቆቃ የሚመዝን ድካም ውስጥ እንደ ነበራችሁ እንረዳለን። በዚህም "አባቶቻችን" ስንል አናፍርባችሁም። እናመሰግናለን። ቤተ ክርስቲያን ታመሰግናችኋለች።

ለቅድስት ቤተክርስቲያን ላደረጉት መንፈሳዊ ተጋድሎ ለከፈሉት መስዋዕት ቅድስት ቤተክርስቲያን ሁሌም ስትዘክረው ትኖራለች


#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…
Subscribe to a channel