ortodoxtewahedo | Unsorted

Telegram-канал ortodoxtewahedo - ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

64069

ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ። ‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3 https://youtu.be/csxxAMGtC4I ለመቀላቀል http://t.me/ortodoxtewahedo

Subscribe to a channel

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

"ቅዱስ ሚካኤል ኾይ"

እንደ ፀሐይ ሥነ ጸዳል የሚያንጸባርቁ በሰማይ ላይ ለሚንበለበሉ አክናፎችኽ ሰላም እላለኹ

የእግዚአብሔር ልዩ መልእክተኛ ሚካኤል ኾይ ከላይ ከሰማይ ተመልክተኽ በምትመጣበት ጊዜ ኹሉ በሲዖል የሚኖሩ ግዞተኞች ሚካኤል ኾይ መጣኽልን ደረስክልን እያሉ ደስታቸውን ይገልጻሉ።"

#መልክአ ቅዱስ ሚካኤል

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

"ቅዱስ ሚካኤል ኾይ"

እንደ ፀሐይ ሥነ ጸዳል የሚያንጸባርቁ በሰማይ ላይ ለሚንበለበሉ አክናፎችኽ ሰላም እላለኹ

የእግዚአብሔር ልዩ መልእክተኛ ሚካኤል ኾይ ከላይ ከሰማይ ተመልክተኽ በምትመጣበት ጊዜ ኹሉ በሲዖል የሚኖሩ ግዞተኞች ሚካኤል ኾይ መጣኽልን ደረስክልን እያሉ ደስታቸውን ይገልጻሉ።"

#መልክአ ቅዱስ ሚካኤል

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

እግዚአብሔር በሚያደርገው በጎ ነገር ሚካኤል ይታዘዛል✝
                         
Size 51.2MB
Length 55:18

  በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

♦አቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ ተመሰረተ !

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት
የሕግ አገልግሎት መምሪያው ከሕግ ባለሙያዎች ዐቢይ
ኮሚቴ ጋር በመሆን አቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ መሰረተ።

የቤተክርስቲያናችን ሕግ አገልግሎት መምሪያ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ባቀረበው ክስ የወንጀል ምርመራ ተደርጎ የምርመራ መዝገቡ መብቱ ለሚፈቅድለት የዐ/ሕግ ዘርፍ እንዲተላለፍለፍ ጠይቋል።

በወንጀል ተጠርጣሪ /ተከሳሽ - አቶ ትዝታው ሳሙኤል
ተጠርጣሪ /ተከሳሹ ነዋሪነቱን በውጪ ሃገር በማድረግ የቤተክርስቲያኒቱ የበላይ ውሳኔ ሰጪ አካልን ለማዋረድ፣
ለመስደብ እና የምዕመኑን ስሜት ለመንካት ብሎም በሀገሪቱ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እንዲነሳ በማሰብ በተለያዩ የመረጃ ማሰራጫ መንገዶች እና ከ5000 በላይ ተከታዮች ባሉት የራሱ የዪቲዩብ ቻናል በመጠቀም ከፍተኛ ቅስቀሳ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።

በማያያዝም ግለሰቡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዓን አባቶችን፣ በየገዳማቱ ውስጥ የሚገኙ ገዳማውያን መነኮሳትና አገልጋዮችን <<ግብረ ሰዶማውያን ናቸው>> በማለት፣እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን <<የመተት እና ጠንቋይ ቤት ናት >>በማለት፣ሲቀሰቅስ የቆየ መሆኑን የገለጸው መምሪያው ግለሰቡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የምትገለገልባቸውን ሃይማኖታዊ የፀሎት፣የታሪክ ፣የገድላትና ድርሳናት መጻሕፍትን <<ድውያን መጽሐፍት ናቸው መጥፋት አለባቸው>>ማለቱን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቅድስናየምታ
ከብራቸውንና የምትዘክራቸውን ቅዱሳን አባቶች እና እናቶችን << ጣኦታትና ጣኦት አምላኪ>> ናቸው በማለት ግለሰቡ የፈጸመውን የወንጀል አድራጎት በመጥቀስም ክስ መስርቶበታል።

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!

እንኳን ለቅድስት ሥላሴ በዓል እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

የአብርሐምን ቤት የባረኩ ሥላሴ እኛንም በህይወታችን በኑሮዋጭን በአገልግሎታችን በትዳርአችን በትምርታችን በሥራችን ይባርኩን ።

ሥሉስ ቅዱስ ለሚታምን ሁሉ እምነትን በረከትን ሀገራችን ኢትዮጽያን ሰላም ያድርጉልን አሜን ::

#መልካም እለተ ይሁንልን

🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈

ለመቀላቀል ➟ @weludebirhane

ለአስተያየት ➟ @weludebirhane_bot

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼.

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ በቤተ ክርስቲያን ደን ልማት ላደረጉት አስተዋጽኦ ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሽልማት ተበረከተላቸው።

Mk tv ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ የአመልድ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር በደን ልማት ላደረጉት አስተዋጽኦ ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሽልማት ተበረከተላቸው።

ሰኔ 4/2017 ዓ/ም በድርጅቱ ዋና መሥሪያ ቤት በተከናወነው የዕውቅናው መርሐ ግብር ላይ የምስጋና ወረቀትም ዶክተሩ የሚመሩት አመልድ ኢትዮጵያ ለአበረከተው አስተጽኦ ከቤተ-ክርስቲያን ደን ፕሮጀክት ተጠቃሚዎች ተበርክቶለታል።

ሽልማቱ የሰጡት በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በደራ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኙ የስድስት አብያተ ክርስቲያናት እና የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ተወካዮች ናቸው።

የአብያተ ክርስቲያናቱ ተወካዮች እንደገለጹት በዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ የሚመራው አመልድ ኢትዮጵያ በአካባቢያችን ለሚገኙ ጥንታዊ ገዳማት እና አድባራት ተፈጥሮአዊ ደኖቻቸው እና ይዞታቸወ እንዲጠበቅ፣ ኅብረተሰቡን በማስተባበር አጥራቸው እንዲታጠር እና በአካባቢው ለሚገኙ ድሃ ማኅበረሰቦች የኑሮ ማሻሻያ ድጎማ በማድረግ ያደረገውን ተግባራት አውስተው ተወካዮቹ ምሥጋና አቀርበዋል፡፡

የአመልድ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ዓለማየሁ ዋሴ (ፒ.ኤች.ዲ) እንደተናገሩት ለመጀመሪያ ጊዜ ከፕሮጀክት ተጠቃሚዎች መካከል ምስጋና ያቀረቡ መሆናቸውን አውስተው፣ በቀጣይ የቤተ-ክርስቲያን ደንን መሠረት ያደረገ የመልክዐ- ምድር መልሶ ማልማት ፕሮጀክት ሥራ በሌሎች ቦታዎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እና በአካባቢው የተሠራው ሥራ ዉጤታማ መሆኑን አድንቀዋል፡፡

ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ በቤተክርስቲያን የደንና ብዝኃ ሕይወት ዙሪያ የተለያዩ ጥናቶችን ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በማካሄድ ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ግንዛቤ መፍጠር የቻሉ ሲሆን እመጓ፣ መርበብት እና ዝጎራ በተባሉት መጽሐፎቻቸውም አንቱታን ያተረፉ መሆናቸው ይነገርላቸዋል።

©የዘገባው ምንጭ አመልድ ኢትዮጵያ ነው።

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

🙋‍♂አንድጥያቄ

✞በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው ሰውን መግደል የጀመረው በማን ነበር ⁉️✟

         

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

📖ቅጠል ረግፎ ቅጠል እንደሚተካው ሁሉ ሰው ወድቆ ሰውን ያኖራል።

📖እኛም ይሄው ነን ይህ ነው ታሪክና ሂደታችን ኑሮና ይህ ህይወታችንን እየወደቁ ያኖሩን እየሞቱ ያተረፉን ኗሪዎች ነን

📖ያንዳችን ሞት ላንዳችን ህይወት ነው በዚህ መንገድ ነው እየተተካካን የተጓዝነው

📖በዚህ ሂደት ነው ሰው ለመሆን የተንገዳገድነው እየሞቱ ያኖሩን እየወደቁ ያተረፉን የህይወት ቀብድ የተከፈለብን ኗሪዎች ነን

📖ያንዳችን ሞት የሌላችን ህይወት ነውና የተከፈለልንን ዋጋ ላለማባከን

📖 በእምነት በእውነትና በፅናት በመኖር ህሊናችንን እናሳርፈው።

📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

http://t.me/ortodoxtewahedo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰

🕹 #ጊዜ_አጠቃቀም

👍 #የጊዜ_አጠቃቀም_ጥቅሞች

🔸የጊዜ አጠቃቀም ጥቅሞች እንደየሰው ቁጥራቸው ሊጨምርና ሊያንስ ይችላል፡፡ እዚህም ጋር የሚከተሉት ሦስት ዋና ዋና ጥቅሞች ቀርበዋል፡፡

1⃣ በሌሎች ዘንድ የሚኖረን ተቀባይነት ከፍ ይላል


🔹አገልጋዮች ከፍተኛ የሆነ ማኅበራዊ ቁርኝት የሚጠበቅብን በመሆኑ የጊዜ አጠቃቀሙን መጀመርና መልመድ በምናደርገው ግንኙነት የሚጠበቅብንን በጊዜው እንድናከናውን ይረዳናል፡፡

🔸በዚህም በሰዎች ዘንድ የተግባር ሰው፣ ቃል አክባሪ፣ ትጉህ፣ ወዘተ የእኛ መገለጫዎች ይሆናሉ፡፡

🔹እነዚህ እሴቶች ደግሞ በመንፈሳዊውም ሆና ዓለማዊው እንቅስቃሴያችን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጉልናል፡፡

2⃣ የተመጣጠነ ሕይወት እንድንመራ ያስችለናል

🔸የጊዜ አጠቃቀምም በመንፈሳዊ፣ አእምሮአዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ጤናዊ አቋማችን የተመጣጠነ እንዲሆን ይረዳናል፡፡

3⃣ ውጤታማነታችን ያሳድጋል

🔹ውጤታማነት ሲለካ ሥራው መሠራቱ ብቻ ሳይሆን የሚታየው ሥራው የፈጀውም ጊዜ አንዱ መለኪያ በመሆኑ ግንዛቤ ውስጥ ይገባል፡፡

🔸ጊዜያችን በአግባቡ የምንጠቀም ከሆነ በሁሉም ረገድ በትንሽ ጊዜ ብዙ ሥራዎችን በማከናወን ውጤታማ መሆን እንችላለን፡፡

#ማጠቃለያ

❇️ጊዜ ሀብት ነው፤ እንዲሁም ጊዜ ለእያንዳንዳችን እኩል የተሰጠን ሀብት ነው፤ በመሆኑም እያንዳንዳችን አጠቃቀሙን ተረድተን ይህን ሀብታችንን ለውጤታማነት ልናውለው ይገባል፡፡

❇️ምንም እንኳ ጊዜ ሀብት ቢሆንም አጠቃቀሙን ካላወቅንበት፣ ሀብትነቱን ካልተረዳን ምንም ዋጋ አይኖረውም፡፡

👌ይህም ማለት ጊዜ ካወቅንበት እና ከሠራንበት የሚጠቅመን ሲሆን ካላወቅንበት ግን ምንም ጥቅም የለውም፡፡

❇️ጊዜ ለሁላችን እኩል የታደለ ሀብት ቢሆንም ጠቀሜታው ግን ለሁላችን እኩል አይደለም፡፡

👌ምክንያቱም የጊዜን ሀብትነት ተረድተው በአግባቡ የተጠቀሙበት ውጤት ሲያገኙበት ይህንን ያልተረዱ ግን ተጠቃሚ አይሆኑም፡፡

❇️ጊዜ ለእያንዳንዷ እንቅስቃሴአችን አስፈላጊ እና ጠቃሚ ሀብት በመሆኑ ትኩረትን ይሻል፡፡

ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን

📌ምንጭ
↪️ @Tewahedo12 Channel

⏰⏰⏰
⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰⏰

🙏 ሼር ማድረግ አይርሱ 🙏

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ይቆየን

📩Coment- @YeBiruk
- @Samiabush

@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo
@ortodoxtewahedo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የወርቅ መሠላል✝
  
           
Size:-132.4MB
Length:-2:23:00

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

📓#አንድጥያቄ
✟ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለአብርሃም ድንኳን ለኖህ መርከብ ለያዕቆብ መሰላል ለአዳም ምኑ ናት? ✟

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

"ጾመ ሀዋርያት(የሰኔ ጾም)"

ይህ ፆም ሐዋርያት ለማገልገል ከመሰማራታቸው በፊት አገልግሎታቸው የቀና እንዲሆን ለመንፈስ ቅዱስ ስራ መለየትን እግዚአብሔር እንዲሰጣቸው በመለመን የፆሙት ፆም ነው ::

ሐዋ 13:1-3

መሰረታችን ሐዋርያት ናቸውና የዋኖቻችንን ሥራ እኛም መፈጸም ስላለብን እንጾመዋለን፡፡
ሐዋርያትን እንዳፀናቸው በአገልግሎቱም እንዳበረታቸውና እንደለያቸው ሁሉ እኛም እንዲያፀናን እንዲያበረታን በመማፀን ለመልካሙ ሥራ እንተጋ ዘንድ በመለመን እፆመዋለን ከጵራቅሊጦስ ማግስት ጀምሮ ሐምሌ 5 በመፆም ይፈጸማል።

እንኳን አደረሳችሁ/አደረሰን የበረከት ጾም ይሁንልን

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

❖ ሰኔ ፲፪ ❖

✞ ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት [በነገዱ ውስጥ፥ በመላእክት ሁሉ ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት..፣ በእስክንድርያ ከተማ ቅዳሴ ቤቱ የከበረበት..፣ የሞት መልእክት የተጻፈባትን የቅዱስ ባሕራንን ደብዳቤ የለወጠበት..፣ ቅድስት አፎምያን ያዳነበት..፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ምሕረትን የሚለምንበት..በእለኚህ ምክንያት ነው በዓሉን የምናከብረው] ✞

"ሰላም ለሚካኤል መሐሪ ውእቱ፤ ወተአዛዚ ለሰብእ በዲበ ሠናይቱ፤ ለቀርነ ዝንቱ መልአክ በድምፀ ንፍሐቱ፤ በከመ ኮነ ቀዳሚ ውስተ ሰማያት ዕርገቱ፤ ለእግዚአብሔር ይከውን ዳግመ ምጽአቱ።"

@ortodoxtewahedo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ደጉ እና ሩሩህ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል አመታዊ በዓል እንኳን አደረሳቹ።

"ቅዱስ ሚካኤል ኾይ"

እንደ ፀሐይ ሥነ ጸዳል የሚያንጸባርቁ በሰማይ ላይ ለሚንበለበሉ አክናፎችኽ ሰላም እላለኹ

የእግዚአብሔር ልዩ መልእክተኛ ሚካኤል ኾይ ከላይ ከሰማይ ተመልክተኽ በምትመጣበት ጊዜ ኹሉ በሲዖል የሚኖሩ ግዞተኞች ሚካኤል ኾይ መጣኽልን ደረስክልን እያሉ ደስታቸውን ይገልጻሉ።"

#መልክአ ቅዱስ ሚካኤል

" የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።"

#መዝሙረ ዳዊት 34:7፤)

"በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤ ሕዝብም ከሆነ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል፤ በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል። "

#ትንቢተ ዳንኤል 12:1

" የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሀያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤ እኔም ከፋርስ ነገሥታት ጋር በዚያ ተውሁት። "

#ትንቢተ ዳንኤል 10:13

" ነገር ግን በእውነት ጽሑፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም።
"
#ትንቢተ ዳንኤል 10:21፤)ዐ

"የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር። ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም።"

#የይሁዳ መልእክት 1:9፤

"ቅዱስ ሚካኤል ኾይ
እንደ ፀሐይ ሥነ ጸዳል የሚያንጸባርቁ በሰማይ ላይ ለሚንበለበሉ አክናፎችኽ ሰላም እላለኹ

የእግዚአብሔር ልዩ መልእክተኛ ሚካኤል ኾይ ከላይ ከሰማይ ተመልክተኽ በምትመጣበት ጊዜ ኹሉ በሲዖል የሚኖሩ ግዞተኞች ሚካኤል ኾይ መጣኽልን ደረስክልን እያሉ ደስታቸውን ይገልጻሉ።"

#መልክአ ቅዱስ ሚካኤል.

✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ያሉበትን ቤት ሁሉ ሞላው
         በዓለ መንፈስ ቅዱስ
Size:-28MB
Length:-1:20:27

በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#ሰንበተ ክርስትያን

እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች።

ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት
(ራዕይ 1፥10)

ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት።

መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን

#መልካም ቀን

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት መታሸጉን ተከትሎ አባላቱ ቅሬታቸውን ገለጹ !

ሰኔ 7 ቀን 2017 ዓ.ም [ተሚማ/ አዲስ አበባ]

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአርሲ ሀገረ ስብከት ካሉት ቀደምት እና አንጋፋ ሰንበት ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነው የአሰላ ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ትምህርት ቤት በደብሩ ሰበካ ጉባኤ አማካይነት መታሸጉን የሚዲያችን የመረጃ ምንጮች ለሚዲያ ክፍላችን መረጃውን አድርሰውናል። ይህንንም ተከትሎ የሰንበት ትምህርት ቤቱ አባላት ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

በሚያዝያ 08/2017 ዓ.ም በሰበካ ጉባኤ በቁጥር አካ/ደመ/መዓ/ቤክ/ሰጉ/0320/17 በተጻፈ ደብዳቤ የሰ/ት/ቤቱን ሊቀመንበርና የሕጻናት ክፍል መምህር ዲ/ን አበበ ይልማን ከሥራና ከሰ/ት/ቤቱ ሰብሳቢነት ማገዳቸውን በመግለጹ ሰንበት ት/ቤቱ በቀን ምልዓተ ጉባኤ አድርጎ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሊቀ መንበር የታገደበትን ውሳኔ ጠቅሶ ለሰበካ ጉባኤው በደብዳቤ ለወረዳው ቤተክህነት እና ለወረዳው ሰ/ት/ቤት አንድነት አስገብቶ አፋጣኝ ምላሽ ባለማግኘቱ በድጋሚ ለወረዳ ቤተ ክህነቱ በቀን 16/08/2017 ዓ.ም የቅሬታ ደብዳቤ አስገብቶ ፤ የወረዳው ቤተክህነት ጉዳዩን ተመልክቶ ሊቀ መንበሩ አለአግባብ መታገዱንና የሰ/ት/ቤቱን መብት የነካ ተግባር መሆኑን ጠቅሶ ለሰበካ ጉባኤው በቁጥር 97/2017 በቀን 17/08/2017 ዓ.ም እገዳው እንዲነሳ ደብዳቤ መጻፉን ለሚዲያችን አስረድተዋል።

ሆኖም ግን ሰበካ ጉባኤው ተፈጻሚ የወረዳ ቤተ ክህነቱን ትዕዛዝ ባለመቀበሉ በ25/09/2017 ለብፁዕ አቡነ ያሬድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ኃላፊና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባል ጠቅሰው ያስገቡት ደብዳቤ ምላሽ ሳይሰጣቸው ሰንበት ትምህርት ቤቱ በግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ታሽጎ አገልግሎት መስጠት ማቆሙን ሚዲያችን ለማወቅ የቻለ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከሀገረ ስብከቱ የተላኩ ልዑካን በተገኙበት የታሸገው የሰንበት ት/ቤት ሂሳብ ነክ እና አባላት ቁጥርን ከያዘው ሳጥን ባሻገር ሌላው የታሸጉት ተከፍተው ሰ/ት/ቤቱ ወደ አገልግሎት እንዲመለስ የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ደብዳቤ ጽፎ ቢልክም ሰበካ ጉባኤው የታሸገውን ለመክፈት ፈቃደኛ ሳይሆን መቅረቱን ለመረዳት ችለናል

ይህንን አስመልክቶ የሚዲያ ተቋማችን የካቴድራሉን አስተዳዳሪ አባ ፍቅረ ሥላሴን በተደጋጋሚ ደውሎ ለማነጋገር ቢሞክርም ሐሳባቸውን በስልክ ለማጋራት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሐሳባቸውን ማካተት ያልቻልን ሲሆን ፤ በተጨማሪም የወረዳው ሊቀ ካህናት እና የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ታምራት ወልዴን ለማግኘት ያደግረነው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል።

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

             
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

✣ ባለ ማኅተቦች ብቻ play  ይበሉ ✣
💒                                          💒
💒      #የተዋህዶ_ፍሬዎች        💒
💒◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈💒
💒       ከ፩ኛ ዓመት ጀምሮ         💒
💒 መንፈሳዊ ኮርሶችን መማር     💒
💒          ለምትፈልጉ፦              💒
💒       እሄን ጹህፍ ነክተው         💒
💒    ወደ እግዚአብሔር ቤት       💒
💒        መግባት ይችላሉ           💒
💒  💠መልካም ትምህርት💠    💒
💒◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈💒
💒                                          💒
💒💒💒💒💒💒💒💒💒💒💒
ባለ ማኅተቦች ብቻ play ይበሉ
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️
⬜️⬜️⬜️ play▶️ ⬜️⬜️⬜️
⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️⬜️

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

መ/ር አክሊል

ብርቱ አርቶዶክሳዊ ወጣት ቤተ ክርስትያን ብዙ አክሊልዎች ያስፈልጓታል በርታልን ወንድማችን ።

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

👉 ትዝታው ወደ ኢትዮጵያ መግባቱ እና ከቤተክርስቲያን ጋር ባለው ግንኙነት ዙሪያ የተነሱት ስጋቶች፣ በተለይም የሕግ ክፍል ሚና ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ነው።

የቤተክርስቲያን የሕግ ክፍል ሚና እና ተጠያቂነት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሕግ ክፍል፣ ልክ እንደማንኛውም ተቋም የሕግ ክፍል፣ የቤተክርስቲያኗን ሕጋዊ መብቶችና ጥቅሞች የማስጠበቅ ኃላፊነት አለበት። ይህ የሚያጠቃልለው፡-
የቤተክርስቲያኗን ስም መጠበቅ: ማንኛውም የቤተክርስቲያኗን መልካም ስም የሚጎዳ፣ የሚያጠለሽ ወይም ውሸት የሚያሰራጭ አካል ላይ ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ።
ንብረት ጥበቃ: የቤተክርስቲያኗን ንብረቶች (ሕንፃዎች፣ መሬቶች፣ ቅርሶች፣ ገንዘብ ወዘተ) ከሕገ-ወጥ ወረራ፣ ብዝበዛ ወይም ጉዳት መጠበቅ።
የአስተምህሮ ጥበቃ: የቤተክርስቲያኗን አስተምህሮ የሚጻረሩ ወይም ምእመናንን የሚያደናግሩ ድርጊቶችን ሕጋዊ በሆነ መንገድ መከላከል (ይህ ግን የሃይማኖት ነጻነትን የማያደናቅፍ መሆን አለበት)።
ውሎች እና ስምምነቶች: ቤተክርስቲያን የምትገባባቸውን ማንኛውንም ውሎች እና ስምምነቶች ሕጋዊ ገጽታ ማረጋገጥ።
የውስጥ ክርክሮች: በቤተክርስቲያኗ አባላት ወይም አካላት መካከል የሚፈጠሩ የሕግ ጉዳዮችን መፍታት።
"ቤተክህነቱ የሕግ ክፍል ነፍስ አለው?" የሚለው ጥያቄ
ይህ ጥያቄ ቤተክርስቲያን እንደ ተቋም ለሚያጋጥሟት ችግሮች ምላሽ የመስጠት ፍጥነት እና ብቃት ላይ ያነጣጠረ ነው። "ነፍስ አለው?" ሲባል፣ የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍል ንቁ፣ ብቁ እና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አቅም አለው ወይ? የሚል ጥያቄን ይዞ ይመጣል።
ተቋማዊ ሕይወት: ማንኛውም ተቋም (እንደ ቤተክርስቲያን) የራሱ ሕግና ሥርዓት ያለው አካል ሲሆን፣ የሕግ ክፍሉም ይህንን ሥርዓት በሕይወት ለማቆየትና ለማንቀሳቀስ ቁልፍ ሚና አለው። ስለዚህ በንድፈ ሀሳብ ደረጃ "ነፍስ" ወይም "ሕይወት" አለው ሊባል ይችላል።
ተግባራዊ ችግሮች: ሆኖም በተግባር ግን እንደ ማንኛውም ትልቅ ድርጅት፣ የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍልም ቢሮክራሲ፣ የሀብት እጥረት፣ የሰው ኃይል ውስንነት ወይም የውሳኔ አሰጣጥ መዘግየቶች ሊያጋጥሙት ይችላሉ። እነዚህ ችግሮች "ነፍስ የለሽ ሬሳ" አስመስለው ሊያቀርቡት ይችላሉ።
ትዝታው እና የቤተክርስቲያን መልካም ስም ጉዳይ
ትዝታው በኢትዮጵያ ውስጥ በቤተክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ሲያቀርባቸው የነበሩ አስተያየቶች በብዙዎች ዘንድ አነጋጋሪ እንደሆኑ ይታወቃል። የቤተክርስቲያኗን መልካም ስም አጠፋተዋል የሚል ቅሬታ ካለ፣ የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍል ይህንን ቅሬታ መርምሮ በሕግ አግባብ ክስ መመስረት የሚችልበትን ሁኔታ ማየት አለበት።
ማስረጃ ማሰባሰብ: "ብዙ ማስረጃ አለ" ተብሎ እንደተጠቀሰው፣ የሕግ ክፍሉ መጀመሪያ እነዚህን ማስረጃዎች በጥንቃቄ ማሰባሰብ፣ ማደራጀት እና ሕጋዊ ክብደት እንዳላቸው ማረጋገጥ አለበት።
የክሱ ዓይነት: ክሱ የስም ማጥፋት (defamation)፣ የሐሰት ወሬ ማሰራጨት ወይም ቤተክርስቲያኗን የሚያጎድፍ ሌላ ሕገ-ወጥ ድርጊት ሊሆን ይችላል።
የፍጻሜ አደራረስ: "ሬሳ የሕግ ክፍል ክስ ቢከስም ለፍጻሜ አያደርስም!" የሚለው አስተያየት የሕግ ክፍሉን አቅም መፈተሽ ነው። ክሱ ለፍጻሜ ለመድረስ ጠንካራ የሕግ መሠረት፣ በቂ ማስረጃ፣ ብቁ የሕግ ባለሙያዎች እና የቤተክርስቲያኗ ከፍተኛ አመራሮች የፖለቲካ ፍቃደኝነትና ድጋፍ ያስፈልገዋል። ያለዚህ ድጋፍ፣ ሕጋዊ ሂደቶች ቀርፋፋ ሊሆኑ ወይም ሙሉ በሙሉ ሊዳክሙ ይችላሉ።

የቤተክርስቲያኗ የሕግ ክፍል በሕግ ፊት ስልጣን ያለው አካል ሲሆን፣ የቤተክርስቲያኗን መብቶች ማስጠበቅ የሕግ ግዴታው ነው። ትዝታው በቤተክርስቲያኗ ላይ ጉዳት አድርሷል ተብሎ ከታመነ፣ የሕግ ክፍሉ ያሉትን ማስረጃዎች ተመልክቶ ሕጋዊ እርምጃ የመውሰድ ሥልጣን አለው። ሆኖም የሕግ ሂደቶች ውስብስብ እና ጊዜ የሚጠይቁ በመሆናቸው፣ ውጤታማ ለመሆን ጠንካራ የሕግ አቅም እና ተቋማዊ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ቤተክርስቲያኗ ምን አይነት እርምጃ ትወስዳለች ብለው ያስባሉ?
  
           
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

#ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማታረጅ #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትታደስ #ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትጠፋ
#ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትለወጥ
#ኦርቶዶክስ_ተዋህዶ የማትሻሻል


📖በክርስቶስ ደም የተመሰረተች እውነተኛ ዘላለማዊ ሕይወት ናት ከድንግል ማርያም ፍቅር ከተዋህዶ ማዕድ አይለየን

📖አሜን ተዋህዶ ለዘላለም ትኑር
በዚህ ወቡ በሆነች ሐይማኖት እስከዘላለም ያፅናን።

#አሜን
#አሜን
#አሜን

#share #share #share

📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖📖

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ያሉበትን ቤት ሁሉ ሞላው
         በዓለ መንፈስ ቅዱስ
Size:-28MB
Length:-1:20:27

በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
  
           
#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

“ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።”

  — 1ኛ ቆሮንቶስ 10፥13


#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

🤔 ስለ ምን ማወቅ ይፈልጋሉ ❓

👳‍♂ሰለ ንስሐ
ንስሐ እንዴት እንግባ ⁉️፡
ንስሐ በጾም መግባት ይቻላል⁉️
ሁለት የንስሐ አባት መያዝ የቻላል⁉️
ስለ ስርአተ ቤተክርስቲያን:ስለ ምስጢረ ቁርባን፡ መንፈሰዊ ምክር፡ታሪክ የየእለቱ ስንክሳር ፡
❤️🧡💛💚💙💙💜💚💜💙💚💛ቆየት ያሉ ዝማሬዎች፡አዳዲስ ዝማሬዎች የመዝሙር ግጥሞች
መንፈሳዊ የዜማ መሳርያዎች  የበገና ፡የክራር ፡የመሰንቆ  ትምህርት የሚሰጥበት ተከታታይ የሐዲስ ኪዳን ትምህርት የፈለጉት መጽሐፍ የሚያገኙበት የግዕዝ ትምህርት የሚሰጥበት የፈለጉት የሚጠይቁበትና ምላሽ  የሚያገኙበት ቻናል ነው። ለመቀላቀል ከስር Join የሚለውን ንኩት።
                 👇👇👇
         ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
         █   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲      █          
         ◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢




🖥ትምህርቱን በይቱብ መከታተል ለምትፈልጉ⁉️
𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 በማድረግ ይከታተሉ።
         👇🏽👇🏽

https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=pMjUosQePGmp8VuO
https://youtu.be/8tUjf9miCtQ?si=pMjUosQePGmp8VuO

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

ብዙ ስለበደልኩ በእግዚአብሔር ፊት መቅረብ የሚቻለኝ አይደለሁም አትበል፡፡ ተስፋ አትቁረጥ፡፡ ተስፋ በመቁረጥ ምክንያት ኃጢአትህን አትጨምር፡፡

መሓሪ በሆነው _ አምላክ ርዳታ ወደ ቀደመ ማንነትህ መመለስ ይቻልሃል፡፡ እርሱ እንዲህ ብሏልና፡- ወደእኔ የመጣውን ወደውጪ _ አላወጣውም፡፡/ዮሐ 6፡37/

እርሱ ንጽሐ ባሕርይ ስለሆነ ወደ እርሱ የሚቀርቡ ወገኖችን እንደሚያነጻቸው እንደሚቀድሳቸውም እውነተኛ የሆነ ንስሐን እመን፡፡

እንዲህ ተብሎ እንደተጻፈ፡-

« ከክፋት ተመልሰህ መልካም ነገርን አድርግ፡፡/1ኛ ጴጥ 3፡11/

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…

ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ

#በዓለ ጰራቅሊጦስ

የቤ/ክ የልደት ቀን

‹‹ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም›› /ዮሐ. 14፥18/

ጰራቅሊጦስ፡- ቃሉ ግሪክ ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት መጽንኢ በእምነት የሚያጸና፣ መንጽሒ ከኃጢአት የሚያነጻ፣ ናዛዚ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፣ መስተፍስሒ፣ የተጨነቁትን የሚያስደስት፣ ከሣቲ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው፡፡

ጰራቅሊጦስ፡- መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የጰራቅሊጦስ በዓል ታሪክ እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡

ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም የሚሠራውን ሥራ ከጨረሰ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያትን ወደ አባቴ እሄዳለሁ (አርጋለሁ) ሲላቸው ደነገጡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም መደንገጣቸውን አይቶ ‹‹ኢይደንግድክሙ ልብክሙ እመኑ በእግዚአብሔር ወእመኑ ብየ እስመ ውስተ ቤተ አቡየ ብዙኅ ማኅደር ወምዕራፍ ቦቱ›› (ልባችሁ አይደንግጥባችሁ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም እመኑ በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ ማለት ባባቴ ቤት በመንግሥተ ሰማያት ብዙ ማዕርገ ሀብታት አለ) /ዮሐ. 14፥1)

እንዲሁም /በዚሁ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 14፥18/ ላይ እንደተጻፈው ‹‹ኢየጎድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ›› (ወላጆች እንደሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም) ሲል መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን አጽናንቷቸዋል፡፡

/በሉቃስ ወንጌል 24 ቁጥር 49/ ላይ እንደተጻፈው የሰላም አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊያርግ ሲል ቅዱሳን ሐዋርያትን ‹‹አንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም እስከ ትለብሱ ኃይለ እምአርያም›› (እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ) አላቸውና ዐረገ፡፡ እነርሱም ይህን አምላካዊ ቃል መሠረት በማድረግ በኢየሩሳሌም በጽርሐ ጽዮን በማርቆስ እናት በማርያም ቤት ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው ተሰብስበው ሳሉ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአረገ በአሥረኛው ቀን በተነሣ በሃምሳኛው ቀን የጰራቅሊጦስ እለት ጧት በሦስት ሰዓት ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ በእሳት አምሳል ወረደላቸው ከዚህ በኋላ ፍርሃት ከውስጣቸው ወጣ መንፈሳዊ ድፍረት አገኙ፡፡

አንድ የዕብራይስጥ ቋንቋ ብቻ ነበር የሚያውቁት ሰባ አንድ ዓይነት ቋንቋ (የአገሩ ሁሉ ቋንቋ) ተገለጸላቸው፡፡ ከእነርሱ ጋር በሰባ ሁለት ዓይነት ቋንቋ ተናገሩ፡፡ የአገሩ ሁሉ ቋንቋ የተገለጸላቸውም ሁሉንም በአገሩ ቋንቋ እንዲያስተምሩ ነው፡፡ ከተለያየ ክፍለ ዓለም የመጡ ነበሩ፡፡ እነዚህ የገሊላ ሰዎች አይደሉምን? እንዴት የእኛን አገር ቋንቋ ሊናገሩ ቻሉ? በማለት ተገረሙና አመንትተው እርስ በርሳቸው እንጃ ይህ ምን ይሆን? አሉ፡፡ ሌሎች ግን ጉሽ የወይን ጠጅ ጠጥተው ሰክረው ነው አሉ ነገር ግን ቅዱስ ጴጥሮስ ከአሥራ አንዱ ጋር ቆመ ድምፁንም ከፍ አድርጎ እንዲህ ብሎ ተናገራቸው፡- የይሁዳ ሰዎች በኢየሩሳሌምም የምትኖሩ ሁላችሁ፡- ይህ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን ቃሎቼንም አድምጡ፡፡ ለእናንተ እንደመሰላችሁ እነዚህ የሰከሩ አይደሉም ከቀኑ ገና ሦስተኛ ሰዓት ነውና ነገር ግን ይህ በነቢዩ ኢዩኤል የተነገረው ይፈጸም ዘንድ ነው፡- ይህም ‹‹እግዚአብሔር ይላል በኋለኛይቱ ቀን እንዲህ ይሆናል ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች አገልጋዮች ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ፡፡ ድንቆችንም በላይ በሰማይ ምልክቶችንም በታች በምድር ደምም፣ እሳትም የጢስ ጭጋግም ይሆናል የታወቀችዋም ታላቅዋ የእግዚአብሔር ቀን ሳትመጣ ፀሐይ ወደ ጨለማ ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣል የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል›› /ኢዩ. 2፥28-32/ ይህን መሠረት በማድረግ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ልብን የሚነካ ትምህርት ሰጠ፡፡

ሕዝቡም ቅዱስ ጴጥሮስ በሰጠው ትምህርት ልባቸው ተነካ ቅዱስ ጴጥሮስንና ሌሎቹንም ሐዋርያት ወንድሞች ሆይ ምን እናድርግ? አሉአቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ንስሐ ግቡ ኃጢአታችሁም ይሠረይ ዘንድ ተጠመቁ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ፡፡ የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ አምላካችንም ወደ እርሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉ ሁሉ ነው
ስለዚህ ራሳችሁን ከዚህ ክፉ ዓለም አድኑ ብሎ መከራቸው፡፡ በዚህ ቀን ሦስት ሺህ ሰዎች አምነው ተጠመቁ፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው የሞቱና የትንሣኤው ምስክሮች ሆኑ፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በነሱ ላይ ሲያድር ለቤተክርስቲያን ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ተከፈተ፡፡

ይህ የጰራቅሊጦስ በዓል በግሪኮች ቋንቋ ጰንጠቆስጤ ይባላል፡፡ ጰንጠቆስጤ ማለት ሃምሳኛ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ከተነሣ በኋላ ሃምሳኛው ቀን ነው፡፡ ይህም ዕለት በዓለ ሃምሳ፣ በዓለ ጰራቅሊጦስ ነው፡፡

እንዲሁም ታላቁ ሊቅ ቅ/ዮሐንስ አፈወርቅ ይህን በዓል በሚገባ አነጋገር ‹‹የቤተክርስቲያን የልደት ቀን›› ብሎታል፡፡ ይህ በዓል በብሉይ ኪዳን የእሸት በዓል (በዓለ ሰዊት) ይባላል፡፡ እስራኤል የነጻነት በዓላቸውን ከሚያከብሩበት ከበዓለ ፋሲካ ጀምረው ሃምሳውን ቀን በዓል አድርገው ይሰነብታሉ፡፡ በሃምሳኛው ቀን በዓለ ሰዊትን (የእሸት በዓላቸውን) ያከብራሉ፡፡ በሀገራቸው ከመጋቢት እስከ ግንቦት ያለው ወቅት በሀገራችን ከመስከረም እስከ ኅዳር እንዳለው የእሸት ወራት (የጸደይ ወራት) ነውና የእሸት በዓላቸውን የሚያከብሩት በኦሪት ዘሌዋውያን /ምዕራፍ 23፥10-17/ በታዘዘው መሠረት ማንኛውም እሥራኤላዊ ገበሬ ከዘራው ሁሉ በያይነቱ እሸቱን ቆርጦ ተሸክሞ ወደ ምኩራቡ ይመጣል፡፡ በቤተ መቅደስ የሚያገለግለው ካህን ተቀብሎ ባርኮ ጸልዮ የሚጠበሰው እየተጠበሰ የሚታሸው እየታሸ በማኅበር አንድነት ይበላል፡፡ ይህም ‹‹ቀዳምያት›› ይባላል፡፡ የመጀመሪያው ማለት ነው፡፡ ከማንኛውም በረከት የመጀመሪያው እግዚአብሔር ፊት መቅረብ፣ ለእግዚአብሔር መሰጠት እንዳለበት ታዟልና፡፡

በዚህ መሠረት ከበዓለ ጰራቅሊጦስ የምንማረው፡-ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን ‹‹እናንተ ግን ከላይ ኃይልን እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ተቀመጡ›› ባላቸው መሠረት በኢየሩሳሌም ተቀምጠው ተስፋውን ሲጠባበቁ መንፈስ ቅዱስ ወርዶላቸዋል፡፡ ዛሬ መንፈስ ቅዱስ የሚወርድባት ኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን ናት ‹‹ ሚ መጠን ግርምት ዛቲ ዕለት ወዕፅብት ዛቲ ሰዓት እንተ ባቲ ይወርድ መንፈስ ቅዱስ እመልዕልተ ሰማያት›› (ይህች ቀን ምን ያህል የምታስፈራ ናት? ይህች ሰዓት ምን ያህል የምታስጨንቅ ናት? መንፈስ ቅዱስ ከሰማየ ሰማያት የሚወርድባት) /ሥርዓተ ቅዳሴ/ ለቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ እንደ ወረደላቸው ለእኛም እንዲወርድልን ሁልጊዜ ቤተ ክርስቲያን መሄድ ይገባል፡፡ ከቤተክርስቲያን ተለይቶ ጽድቅ የለም።

ቤተ ክርስቲያን፡- የመንግሥተ ሰማያት በር ናት ‹‹ዛቲ ይእቲ ኆኅታ ለሰማይ›› (ይህች የሰማይ ደጅ ናት) /ዘፍ 28፥17/
በዚህ መሠረት ለእኛም በ40 ቀንና በሰማንያ ቀን የተሰጠን ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እንዳይለየን ሕጉን ትእዛዙን መጠበቅና ጧት ማታ ወደ ቤተ ክርስቲያን መገስገስ ይገባል፡፡
ለዚህም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንዲሁም ቅዱሳን በአማላጅነታቸው ይርዱን፡፡ አሜን

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፡፡
***

#ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo

#ለሃሳብ አስተያየት

@ortodoxtewahedoo

#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር

Читать полностью…
Subscribe to a channel