ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ። ‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3 https://youtu.be/csxxAMGtC4I ለመቀላቀል http://t.me/ortodoxtewahedo
🛒𝗜'𝗠 𝗕𝗨𝗬𝗜𝗡𝗚 𝗢𝗟𝗗 𝗧𝗘𝗟𝗘𝗚𝗥𝗔𝗠 𝗚𝗥𝗢𝗨𝗣𝗦🤩
❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️
1️⃣,old group ሲያመጡ history clear እንዳያረጉ በፍፁም
2️⃣. members ችግር የለውም
ዋናው groupፑ text ይኑረው
3️⃣. inbox ስትመጡ Hi አትበሉ
ቀጥታ ወደ ጉዳያቹ ግቡ
✔️𝟮𝟬𝟭𝟲 - 𝟮𝟬𝟮𝟮 ⬅️
✔️𝟮𝟬𝟮𝟯 𝗔𝗟𝗟 𝗠𝗢𝗡𝗧𝗛𝗦⬅️
✉️በውስጥ አውሩኝ👉 @Diroro12
💵 Payment method
🔠 all banks
🔠TELEBIRR
👎ከፍታችሁ የጠፋባችሁ group ካለም የምታገኙበት system አለን አውሩን
🤩 𝗛𝗶𝗴𝗵 𝗽𝗿𝗶𝗰𝗲 𝗳𝗼𝗿 𝗯𝘂𝗹𝗸 𝘀𝗲𝗹𝗹𝗲𝗿𝘀💵
🤩 𝗗𝗠 𝗠𝗘 𝗡𝗢𝗪 📩
🤩 @Diroro12 🤩
🛒𝗜'𝗠 𝗕𝗨𝗬𝗜𝗡𝗚 𝗢𝗟𝗗 𝗧𝗘𝗟𝗘𝗚𝗥𝗔𝗠 𝗚𝗥𝗢𝗨𝗣𝗦🤩
❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️
1️⃣,old group ሲያመጡ history clear እንዳያረጉ በፍፁም
2️⃣. members ችግር የለውም
ዋናው groupፑ text ይኑረው
3️⃣. inbox ስትመጡ Hi አትበሉ
ቀጥታ ወደ ጉዳያቹ ግቡ
✔️𝟮𝟬𝟭𝟲 - 𝟮𝟬𝟮𝟮 ⬅️
✔️𝟮𝟬𝟮𝟯 𝗔𝗟𝗟 𝗠𝗢𝗡𝗧𝗛𝗦⬅️
✉️በውስጥ አውሩኝ👉 @Diroro12
💵 Payment method
🔠 all banks
🔠TELEBIRR
👎ከፍታችሁ የጠፋባችሁ group ካለም የምታገኙበት system አለን አውሩን
🤩 𝗛𝗶𝗴𝗵 𝗽𝗿𝗶𝗰𝗲 𝗳𝗼𝗿 𝗯𝘂𝗹𝗸 𝘀𝗲𝗹𝗹𝗲𝗿𝘀💵
🤩 𝗗𝗠 𝗠𝗘 𝗡𝗢𝗪 📩
🤩 @Diroro12 🤩
ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ምስለ ኖኅ
ኪዳነ ዘአቀምከ፤ ለደቂቀ እስራኤል መና ዘአውረድከ፤
ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ ወሥነ
ገዳምኒ ምስለ ቅዱሳኒከ፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወከመ
ወሬዛ ኃየል መላትሒሁ ጉርዔሁ መዓርዒር አምሳሉ
ዘወይጠል፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ሰማየ ወምድረ ዘአንተ
ፈጠርከ፤ ፀሐየ ወወርኀ ዘአስተዋደድከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ በከዋክብት ሰማየ ዘከለልከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ ወመኑ መሐሪ
ዘከማከ፤ ቀደሳ ወአክበራ አዕበያ ለሰንበት፤ ወአልዓላ
እምኵሉ ዕለት፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፤ ወኵሉ ይሴፎ ኪያከ፤
#ትርጉም
ከኖኅ ጋር ቃል ኪዳን የገባህ እንዳንተ ይቅር ባይ ማነው
ለእስራኤል ልጆች መናን ያወረድክ፤ ምድርን በአበቦች
ያስጌጥክ፤ እንዳንተ ይቅር ባይ ማነው ? የምድረ በዳውን
አራዊት ከወዳጆችህ ጋር ያስማማህ እንዳንተ ያለ ይቅር ባይ
ማነው፤ ጉንጮቹ እንደ ዋልያ እንቦሳ ፈጣኖች ናቸው፤
አንደበቱ ጣፋጭ ነው፤ ተወዳጅነቱ እንደ ፌቆ ግልገል ነው፤
ሰማይና ምድርን የፈጠርክ፤ ፀሐይና ጨረቃን ያስማማህ፤
ሰማይን በከዋክብት የሸፈንክ፤ ምድርን በአበቦች ያሸበረቅህ፤
ሰንበትን ያከበርካት ከዕለታትም ለይተህ ከፍከፍያደረግኻት፤
አቤት!! እንዳንተ ይቅር ባይ ማንም የለምና ኹሉም አንተን
ተስፋ ያደርጋሉ።
#እንኳን_ለዓለም_ጌታ_ለፍጥረታት_አምላክ_ለነገስታት_ንጉስ_ልዑለ_ባህሪ_ለሆነው_ለአምላካችን_ለመድሐኒታችን_መድኃኒዓለም_ወርሀዊ_በዓል_አደረሰን !
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
#በከንቱ_አምተናታል
ዮሴፍ በጽኑ መረበሽ የተያዘበት ወቅት ነበር። የእመቤታችን መፀነስ ከሚያወቀው ተፈጥሯዊ አካሔድ ውጪ ስለሆነበት ልቡ ክፉኛ ተሸብሮ ነበር። በእርግጥ ዮሴፍ በእመቤታችን መፀነስ መደናገጡ ብዙም ላያስደንቅ ይችላል። መካን ሆነው ሳለ በልመናቸው ብርታት የወለዱ አሉ÷ እንደነ ሣራ በስተርጅናቸው የፀነሱም አሉ። የእርሷ ግን የተለየ ነው በድንግልና የወለደ ከእርሷ በፊትም ይሁን ከእርሷም በኋላ አልተገኘም።
መጻሕፍት እንደሚነግሩን ዮሴፍ ግን ከመደነቅ ይልቅ ከንግድ ሲመለስ ያገኘው ፈላስፋው ዮሐንስ "ይህቺ ሴት ካንተ ነው የፀነሰችው" ብሎ የተናገረው ቃል ከድንጋጤ አድርሶታል። በዚህም ምክንያት ነበር "መኑ ቀረጸ አክናፈ ድንግልናኪ" ብሎ የመፀነሷን ነገር የጠየቃት። ንጽሕት የሆነች እርሷ ግን "መልአኩ አክብሮ ከነገረኝ ውጪ ሌላ ምንም የማውቀው የለም አለችው" የእመቤታችን ትሕትና መግለጽ የሚቻለው አንደበት የለም ቃሏና ምላሿ ሁሉ በትሕትና የታሹ ናቸው።
ዮሴፍ አሁንም ቢሆን ከጥርጣሬው መዳን አልቻልም አንድ አንድ ጊዜ ፍርሐት እና የሰዎችን ወቀሳ ማስታወስ ወደ ጥርጣሬ አሮንቃ ውስጥ ይከተናል አረጋዊው ዮሴፍም የሆነው እንዲሁ ነው። ይህንን ጥርጣሬውን ልታስወግድለት የወደደች እመቤታችን ግን አአዕዋፍ እንዲራቡ የሚያደርግ አአዕዋም እንዲያፈሩ የሚያደርግ ማን ምስሎሃል? ብላ ከግሰጸችው በኋላ ከደጃቸው የቆመ ደረቅ ግንድ ነበር እርሱን አለምልማ አሳየችው። መልአኩ ትፀንሺያለሽ ብሎ ባበሠራት ወቅት ይህ እንዴት ይሆንልኛል ብትለው "ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም" ብሎ የመለሰላትና እርሷ በተግባር አሳየችው። በተረቱበት መርታት ልማድ ነው።
እመቤታን ያለውንድ ዘር በድንግልና የመጸነሷ ነገር ምትሐት ሳይሆን የእግዚአብሔር ሥራ መሆኑን ብትገልጥለትም። ለቆጠራ ወቅት ግን ይዟት ይወጣ ዘንድ ፈራ። ከእግዚአብሔር ሥራ ይልቅ ፍርሐታችንን እናምነዋለን በዚህም በተሳሳተ እምነታችን የእግዚአብሔር ዓላማ አደናቃፊዎች ሆነን እንገኛለን። ዮሴፍም ያለ ወንድ ዘር እንድትጸንስ ያደረገውን የእግዚአብሔርን ሐይል ሳያስተውል ይዟት ሲወጣ ግን አይሁዶች ሊፈጥሩት የሚችሉት ትንኮሳ አስፈራው።
ይዟት ቢወጣ ሕጋቸውን ቢያስቀራት ደግሞ ያደረገውን ዓውቆ ጥሏት ወጣ እንዳይሉ ወሪያቸውን ፈርቶ ሳለ መልአኩ ከያዘው ፍርሐት አርቆ ይዟት ይወጣ ዘንድ አዘዘው። ዮሴፍ በመልአኩ ትዕዛዝ ይዟት ቢወጣም የዲያቢሎስ የግብር ልጆች የሚሆኑ በትጠጣው ለሞት የሚያደርሳትን ማየ ዘለፋን ትጠጣልን አሉ። የአምላክ እናት እርሷ ግን ማየ ዘለፋን ከጠጣችው በኋላ እነርሱ እንዳሰቡት ሳይሆን ከወትሮው አበራች ጽድልት ሆና ታየች ከፀሐይ ይልቅ አብርታ ተገኘች በጊዜ የተቀሩት አይሁድም ይህን ቢመለከቱ "ይህችን ብላቴና በከንቱ አምተናታል" አሉ።
የእመቤታችንን ክብር ከመናገር እርቀው በከንቱ የሚያሙ ሰዎች የበቀሉት ገና በማኅጸን ሳለች ነው። መወለዷን የጠሉ ዳግመኛ የመውለዷን ነገር አለወደድዱምና በጊዜው ነውር እንደተገኘባቸው ሴቶች እርሷን በከንቱ አሟት። እውነት ደቆ ሐስት ረቆ ባየለበት በእኛ ዘመንም ዓይነ ልቦናቸው የታወረባቸው በከንቱ ያማሉ። የእግዚአብሔርን ሳይሆን የግብር አባታቸውን የዲያቢሎስን ድምፅ እየሰሙ በቅዱሳኑ ላይ በከንቱ ይናገራሉ። ከሁሉ ልቆ የታየው ግን የአይሁድ ከንቱ የሆነው ሐሜታቸው ሳይሆን ስለ ክፉ ፈንታ ክፉ ያለመለሰች የእመቤታችን ትሕትና ነበር።
ዲ/ን ሞገስ አብርሃም
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
Old Group አላችሁ እንዴ?
2018
2019
2020
2021
2022
2023 የተከፈቱ ካላቹ እገዛለሁ Member 0 ብሆንም ችግር የለውም ግን History clear ያልተደረገ።
ድሮ ድንገት እንኳን ከፍታችሁ ከረሳችሁ የሚያሳይ Bot እኔጋ ስላሌ አሳውቁኝ እልክላችኋለሁ
ለመሸጥ👉 @Diroro12
የዋጋ ጭማሪ 🔥🔥🔥🔥
2023 group ያላችሁ በአሪፍ ዋጋ አየገዛን ነው ያላቹን group እኛ ጋር ይዛቹ ኑ።✨✨
Dm fast ዋጋው ስለሚቀንስ ይፍጠኑ ።
#ከስንክሳር_ገጾች አንድ ቅዱስ - ሰኔ 26
ቅዱስ ኢያሱ ነብይ ወመስፍን
በዚችም ቀን የታላቁ ነቢይና መስፍን የነቢያት አለቃ የሙሴ ደቀ መዝሙር የነዌ ልጅ የኢያሱ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። ይህም ከታናሽነቱ ጀምሮ ለሙሴ አንገቱን ዝቅ አድርጎ የሚታዘዝ ፍጹም ትሑት ሆነ ስለዚህም በሙሴ ላይ ያደረ መንፈስ ቅዱስ አደረበት። ነቢዩ ሙሴም ከአረፈ በኋላ በእግዚአብሔር ትእዛዝ የእስራኤልን ሕዝብ ተረከባችው።
እግዚአብሔርም ኢያሱን እንዲህ አለው ከሙሴ ጋራ እንደኖርሁ ከአንተም ጋራ እኖራለሁ ጽና በርታ ለባለሟሌ ሙሴ ያዘዝሁትን ሕጌን ጠብቅ ከእርሱም ፈቀቅ አትበል ሕጉንም ትጠብቀውና በሱም ትጸና ዘንድ በውስጡም የተጻፈውን ታደርገው ዘንድ በቀንም በሌሊትም አንደበትህ ማንበብን አያቋርጥ።
ኢያሱም በእግዚአብሔር ሕግ ሔደ። ዕድሜውም መቶ ሃያ በሆነው ጊዜ የእስራኤልን ልጆች ሰበሰባቸው የኦሪትን ሕግ እንዲጠብቁ በአምልኮተ እግዚአብሔርም እንዲጸኑ ትእዛዞቹንም እንዳይተላለፉ አዘዛቸው። እንዲህም አላቸው እርሱ ፈጣሪያችን ቀናተኛ ነውና ጣዖት ብታመልኩ ያጠፋችኋል ሕጉን ብትጠብቁ ግን የበረከት ልጆች ትሆናላችሁ።
ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ ያዕቆብ ከኤሞር ልጆች በመቶ በጎች በገዛው ናብሎስ በሚባል ቦታም ተቀበረ ሠላሳ ቀኖችም ያህል ታላቅ ልቅሶ አለቀሱለት።
ሰኔ 26 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
ወርኃዊ በዓላት
🔻ሰላም Old Group ማለትም የቆየ የቴሌግራም ግሩፕ ያላችሁ በከፍተኝ ዋጋ እየገዛን ነው በነዚ አመተምህረት የተከፈተ ካላችሁ አናግሩን⬇️
✅2️⃣0️⃣1️⃣7️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣1️⃣8️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣1️⃣9️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣2️⃣0️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣2️⃣1️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣2️⃣2️⃣💵💵💵
📥📥ማሳሰቢያ ❌‼️
⏬ የግሩፑ Member ብዛት ''0'' ሆነ ''1000'' ሆነ '10,000'' ዋጋው እኩል ነው
እኛ የምንፈልገው የተከፈተበትን አመተ ምህረት ብቻ መሆኑን ይገንዘቡ😘😍
😑 clear history ያልተደረገ ግሩፕ ነው የምንፈልገው
⏺ Dm
Old Group አላችሁ እንዴ?
2018
2019
2020
2021
2022
2023
የተከፈቱ ካላቹ እገዛለሁ Member 0 ብሆንም ችግር የለውም ግን History clear ያልተደረገ።
ለመሸጥ👉 @Diroro12
🔻ሰላም Old Group ማለትም የቆየ የቴሌግራም ግሩፕ ያላችሁ በከፍተኝ ዋጋ እየገዛን ነው በነዚ አመተምህረት የተከፈተ ካላችሁ አናግሩን⬇️
✅2️⃣0️⃣1️⃣7️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣1️⃣8️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣1️⃣9️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣2️⃣0️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣2️⃣1️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣2️⃣2️⃣💵💵💵
📥📥ማሳሰቢያ ❌‼️
⏬ የግሩፑ Member ብዛት ''0'' ሆነ ''1000'' ሆነ '10,000'' ዋጋው እኩል ነው
እኛ የምንፈልገው የተከፈተበትን አመተ ምህረት ብቻ መሆኑን ይገንዘቡ😘😍
😑 clear history ያልተደረገ ግሩፕ ነው የምንፈልገው
⏺ Dm
🇮🇱 የእስራኤላውያን ቋንቋ ( ዕብራይስጥ ) መማር የምትፈልጉ ብቻ
@Hebrewethio
@Hebrewethio
🙏🏻 አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናትሽን ይማርልሽ በክርስቶስ እኅታችን 🙏🏻
Exactly ሙሉ ለሙሉ እውነት ይሁን አላረጋገጥኩም ፥ ግን አሁን በዚህ ኹኔታ ላይ ኾና ኅሊናዬ እሺ አይለኝም "ገና እናረጋግጥ" ለማለት። እባካችሁን በክርስቶስ ለእኅታችን እንድረስላት።
"ማርያምን ክርስቲያን ወንድሞቼ የሰው ፊት አያሳያቹ ግን ወድጄው አይደለሞ አባቴ ሞቶብኛል እናቴ ታማ ብዙ መድሀኒት ታዞላት ነበር ግን መድሀኒቱ ወደ 45000ብር ይደርሳል እኔ የዩንቨርሲቲ ተማሪ ነኝ እናቴ ገጠር ናት በዚህ ከቀጠለች መሞቷ ነው እግዛብሄርን እንቅልፍ በአይኔ አልዞረም ሚያግዘኝ ምንም ሰው የለም በአላህ አቅም ያላቹ ተባበሩኝ የሌላቹ በጸሎት አግዙኝ"
@Maraki_lo
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ሃቢብ ጊዮርጊስ ግን ቤተ ክርስቲያንን አልከሰሰም፤ ሸክሟን ተሸከመ እንጂ።
፩. የዘመኑ ታሪካዊ ቀውስና የቤተ ክርስቲያን ፈተና
በዐሥራ ዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃና በሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን መባቻ ላይ፣ የግብጽ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ እጅግ ውስብስብ ከሆኑት ፈተናዎች እያስተናገደች ነበር። ቀውሱ የውጭ ጫና ብቻ ሳይሆን፣ ከውስጥ የመነጨና የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕልውና የሚፈታተን ነበር። ይህ ድክመት በአስተዳደር መላሸቅ፣ በመልካም አስተዳደር እጦት፣ በሙስናና በአንዳንድ አገልጋዮች የሥነ ምግባር ውድቀት ተገልጧል። ከዚህም በላይ፣ የትምህርተ ሃይማኖት ዕውቀት በእጅጉ ተዳክሞ፣ የመንፈሳዊ አገልግሎት ጥራትና ስፋት በእጅጉ ቀንሶ ነበር።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ፣ የዚያን ዘመን አሳሳቢ ገጽታ ሲመሰክሩ እንዲህ በማለት ሁኔታውን ያጠቃልሉታል፡-
“በሃያኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ፣ ስብከቶች ደረቅና ሕይወት አልባ ነበሩ፤ መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች ከሞላ ጎደል አልነበሩም፤ ድንቁርና በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ፣ እንዲያውም በቀሳውስቱ መካከል እንኳ ሰፍኖ ነበር።”
ይህ ምስክርነት እንደሚያሳየው፣ ችግሩ የገጸ-ድካም ጉዳይ አልነበረም። ይልቁንም፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሐዋርያዊ ተልዕኮና የአደረጃጀት መሠረት ያናጋ፣ ብዙዎችን ተስፋ ሊያስቆርጥና ለዓመፅ ወይም ለመለያየት ሊዳርግ የሚችል ጥልቅ መንፈሳዊና መዋቅራዊ ቀውስ ነበር። እንዲህ ባለ ከባድ ወቅት፣ የአንድ አማኝ ቤተ ክርስቲያናዊ ንቃተ ህሊና (ecclesiological consciousness) እና ታማኝነት በእጅጉ ይፈተናል።
፪. የዲያቆን ሃቢብ ጊዮርጊስ መነሣትና የመስዋዕትነት መንገድ
በዚህ መንፈሳዊ ጨለማ ውስጥ ነበር ሃቢብ ጊዮርጊስ የተባለው የብርሃን ሰው የተነሳው። እርሱ በቤተ ክርስቲያን ያደገና ዲያቆን እንደመሆኑ፣ የችግሮቹን ስፋትና ጥልቀት ከውስጥ ሆኖ ተመልክቷል። የቤተ ክርስቲያኒቱን የአስተዳደር ድክመት፣ የአገልጋዮቿን የዕውቀት ማነስና የሕዝቡን መንፈሳዊ ጥማት ተገንዝቧል። ነገር ግን፣ እንደ ብዙዎቹ፣ ጣቱን ለመቀሰር፣ ለማሳጣትና ለማጣጣል፣ የውግዘት ድምፅን ለማሰማት ወይንም በራሱ አካሄድ የቤተክርስቲያኒቷን አካሄድ ልከልስ ማለትን አልመረጠም። ይልቁንም፣ በታማኝ አገልግሎትና ሸክምን በመሸከም ለችግሩ ተግባራዊ ምላሽ ሰጠ። መንገዱ የክስ ሳይሆን የመስዋዕትነት ነበር፤ ይህም በገላትያ 6፡2 ላይ ያለውን “የአንዱን ሸክም አንዱ ይሸከም፣ እንዲሁም የክርስቶስን ሕግ ፈጽሙ” የሚለውን ሐዋርያዊ ትዕዛዝ ሕያው ምስክርነት ነው።
ገና ከወጣትነቱ ጀምሮ ለትምህርት በነበረው ጥልቅ ፍቅር፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀጣይ ትውልድ የማነጽ ኃላፊነት በራሱ ላይ ጫነ። የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ንቅናቄ በመላ ሀገሪቱ በማደራጀት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕፃናትና ወጣቶች የኦርቶዶክሳዊት እምነታቸውን እንዲያውቁና እንዲኖሩባት መሠረት ጣለ። በካይሮ ሥነ-መለኮታዊ ኮሌጅ ውስጥ በአካዳሚክ ዲንነትና በመምህርነት ሲያገለግል፣ ዕውቀትና መንፈሳዊነት የተዋሐደላቸውን አገልጋዮች አፈራ። ድርጊቱ ሁሉ ይመነጭ የነበረው፣ ቤተ ክርስቲያንን በአስተዳደራዊ ድክመቶቿ ውስጥ እያየ እንኳ፣ የማይነቀንቅ የክርስቶስ አካልና የድኅነት ታቦት መሆኗን ካመነበት ጥልቅ ሥነ-መለኮታዊ እምነት ነበር።
ለዚህም ነው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ፣ የአንድን ሰው ታማኝ አገልግሎት ፍሬያማነት ሲመሰክሩ፣ እንዲህ ያሉት፡-
“የሰንበት ትምህርት ቤት ንቅናቄ ከሃቢብ ጊዮርጊስ በቀር ሌላ ፍሬ ባያፈራ ኖሮ እንኳ፣ እርሱ ብቻ በቂ ነበር።”
፫. የመዋቅር ድክመትን ከሃይማኖት ስህተት መለየት
የሃቢብ ጊዮርጊስ ጥበብና ሥነ-መለኮታዊ ልሕቀት ከሁሉ በላይ የሚገለጠው፣ በዘመኑ የነበረውን የመዋቅር ድክመት ከቤተ ክርስቲያን ንጽሕተ ሃይማኖት ጋር ባለማደባለቁ ነው። ቤተ ክርስቲያን በትምህርተ መለኮቷ ኑፋቄን ታስተምራለች ብሎ አንድም ቀን አልከሰሰም። ሥርዓቷን አላጣጣለም፤ ቀኖናዎቿንና ይትባሕሎቿን "ካልከለስኩ" አላለም። ችግሩ ያለው በሐዋርያት በኩል በተሰጠችው የቀናች እምነት ላይ ሳይሆን፣ ያችን እምነት በሚያገለግሉና በሚያስተዳድሩ ሰዎች ላይ በሚታየው ድካም እንደሆነ በሚገባ ተረድቶ ነበር።
ይህ መረዳት፣ ቤተ ክርስቲያን መለኮታዊ-ሰብዓዊ (Theanthropic) ተቋም መሆኗን ከመቀበል ይመነጫል።
እርሷ፣ እንደ ክርስቶስ አካል፣ በመለኮታዊ ተፈጥሮዋ ቅድስት፣ ፍጽምትና ከስህተት የጸዳች ናት፤ ነገር ግን በውስጧ የሚያገለግሉት ሰዎች የሰብዓዊ ድካም ተገዢዎች ናቸው። ቅዱሳን አባቶች ይህንን ልዩነት በሚገባ አስተምረዋል። ለምሳሌ፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የክህነትን ቅድስናና የአገልጋዩን ግላዊ ድካም ሲለይ፣ የክህነቱ ኃይል የሚመነጨው ከሰውየው ማንነት ሳይሆን ከክርስቶስ ሹመት መሆኑን ያስረዳል። ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያም ንስጥሮስን የታገለው፣ የአንጾኪያን ቤተ ክርስቲያን መዋቅር ለመናድ ሳይሆን የተሳሳተውን የሃይማኖት ትምህርት ለማረም ነበር።
ስለሆነም፣ የሃቢብ ጊዮርጊስ መፍትሔ ከቤተ ክርስቲያን ውጭ አዲስ ሥርዓት መመሥረት ሳይሆን፣ በውስጧ በመሆን፣ በትሕትናና በመታዘዝ፣ ያንን ሰብዓዊ ድካም መፈወስና ማነጽ ነበር። ሥራው ሁሉ የሚያሳየው ይህንን ነው፡- በገዛ አረዳዱ "የተበላሸውን" ብሎ የገመተውን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ለማረም አልሞከረም፤ ይልቁንም ያንን ያልተበረዘ ትምህርት ለተራበው ሕዝብ ለማድረስ ራሱን አሳልፎ ሰጠ።
፬. ትምህርቱ ለዛሬው ትውልድ፡- የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ተዛምዶ
ይህ የታሪክ ትምህርት በዘመናችን ላለችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥልቅና አስቸኳይ መልእክት አለው። ዛሬ በርካታ ምእመናን በአስተዳደራዊ ብልሽቶች፣ በመንፈሳዊ አመራር ድክመትና በአንዳንድ አገልጋዮች ሥነ ምግባር ጉድለት የተነሣ በብስጭትና በቅሬታ ተሞልተዋል። ይህ ስሜት መነሻው ቅን ሊሆን ይችላል።
ችግሩ ያለው ለዚህ ስሜት በሚሰጠው ምላሽ ላይ ነው። ብዙዎች፣ ልክ በሃቢብ ጊዮርጊስ ዘመን እንደነበሩት ተቺዎች፣ መላዋን ቤተ ክርስቲያንን ይወቅሳሉ፤ ሐዋርያዊ ትውፊቷን ይጠራጠራሉ፤ አልፎ ተርፎም በግል አስተያየታቸውና ፍልስፍናቸው ያንን ትውፊት ለመተካት ይዳዳሉ። ከዚህም የከፋው፣ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ትይዩ መዋቅሮችንና ርዕዮተ ዓለሞችን ለመገንባት መሞከር ነው፤ ይህም አንድነቷንና ሐዋርያዊ ሥርዓቷን በእጅጉ ይጎዳል። ይህ አካሄድ፣ የቅዱስ ኢግናጥዮስ ዘአንጾኪያ "ከኤጲስ ቆጶሱ ውጭ ምንም ነገር አታድርጉ" የሚለውን ሐዋርያዊ መመሪያ የሚጻረር ነው።
፭. ኦርቶዶክሳዊው የማነጽ መንገድ፡-
ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ ቤተ ክርስቲያንን የምትረዳበትና የማነጽ አካሄዷ ግልጽ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌሶን 4፡11–13 ላይ፣ ክርስቶስ ራሱ ለቤተ ክርስቲያኑ "ሐዋርያትንና ነቢያትን፣ ወንጌላውያንንም፣ እረኞችንና አስተማሪዎችንም" የሰጠው፣ "ቅዱሳን … ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ፣ ለክርስቶስም አካል ሕንጻ" እንደሆነ ያስረዳል። መዋቅርና ሥርዓት የተሰጠው ለማነጽ እንጂ ለመበታተን አይደለም።
የማረምና የማነጽ ሥራ እንዴት መከናወን እንዳለበትም መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስቀምጣል። በይሁዳ መልእክት 1፡22 ላይ "አንዳንዶችንም በምትለዩበት ጊዜ፣ ምሕረት አድርጉላቸው፤ ሌሎችን ግን ከእሳት እየነጠቃችሁ በፍርሃት አድኗቸው" ይላል። ይህ ቃል፣ ችግሮችን የምንቀርብበት መንገድ በጥበብና በልዩነት መሆን እንዳለበት ያስተምራል እንጂ ሁሉን በአንድ ላይ የመውቀስ አካሄድን አይደግፍም።
ስለዚህ የተለያዩ ቻናሎች ሄደህ አንብብ ስማ፥
@nooralmassih
@enibakom_apologetics
ለምሳሌ ሞክራቸው ፥ ሌሎችንም ቻናሎች ተመልከታቸው።
#ከስንክሳር_ገጾች አንድ ቅዱስ - ሰኔ 28
አባ ቴዎዶስዮስ
ጻድቁ ሊቀ ጳጳሳት ተወልዶ ያደገው በምድረ ግብጽ በ6ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው። ከልጅነቱ መጻሕፍትን ተምሮ በመንኖ ጥሪት የሚኖር ደግ ሰው ነበር። ያ ዘመን መለካውያንና ልዮናውያን (ክርስቶስን 2 ባሕርይ የሚሉ) የሰለጠኑበት ዘመን ነበር። በአንጻሩ ደግሞ ተዋሕዶን የሚያምኑ ሊቃውንትና ምዕመናን ቁጥራቸው የተመናመነ ነበር።
ችግሩ ግን ይህ ብቻ አልነበረም። በጊዜው ተዋሕዶን አምኖ መገኘት እስከ ሞት የሚደርስ ዋጋንም ያስከፍል ነበር። ለዚህም ነው ሮማውያን ሃይማኖትን በግድ ለማስለወጥ ከነገሥታቱ ጋር የተቆራኙት። ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ጋግራ ደሴት ውስጥ ከተገደለ በኋላ በግብፅ የተሾሙ ሊቃነ ጳጳሳት አብዛኞቹ መከራና ስደትን ቀምሰዋል። ትልቁን ቦታ ግን አባ ቴዎዶስዮስ ይወስዳል።
አባ ቴዎዶስዮስ ለእስክንድርያ (ግብፅ) 33ኛ ፓትርያርክ ነው። ገና እንደ ተሾመ የቀረበለት ጥያቄ አንድ ነበር። "ተዋሕዶን ትተህ መለካዊ ትሆናለህ ወይስ የሚከተልብህን ፍርድ ትቀበላለህ?" አሉት። ይህንን ያሉት ከንጉሡ ዮስጢያኖስ የመጡ መልእክተኞች ነበሩ። መልሱ ፈጣን ሆነባቸው። "እኔንም ሆነ ሕዝቤን ከቀናችው እምነታችን በምንም ልትለዩን አትችሉም" አላቸው።
በዚህ ምክንያት በቀጥታ ግዞት (ስደት) ተፈረደበት። ወደ በርሐ ሲያግዙት ካህናት፥ መምህራንንና ምዕመናንን አደራ ብሏቸው ነው የሔደው። መናፍቃኑ እሱን ካሰደዱ በኋላ ሕዝቡን ለመቀየር ብዙ ደክመዋል። ግን ሊሳካላቸው አልቻለም። ምክንያቱም አደርነትን የማይረሱ ደጋግ መምሕራን ነበሩና ነው። በዚያ ላይ አባ ቴዎዶስዮስ ጦማር (መልእክት) በየጊዜው ይጽፍላቸው ነበር። እጅግ ብዙ ከሆኑት መልእክቶቹ የተወሰኑት ዛሬም ድረስ ሃይማኖተ አበው መጽሐፍ ውስጥ ይገኛሉ።
በዚህ አስቸጋሪ ዘመን መልካም ነገሮችም ነበሩ። ቀዳሚው ማኅቶተ ተዋሕዶ ቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዳይ ሲሆን 2ኛው ደግሞ የንጉሡ ሚስት የተባረከችው ታኦድራ ናት። አባ ቴዎዶስዮስ በግዞትና በስደት ሳለ ንግሥቲቱ ትራዳው፥ ምዕመናንንም ትንከባከብ ነበር። ቅዱስ ያዕቆብ ከሊቀ ዻዻሱ ዘንድ ክህነትን ተቀብሎ ከሶርያ እስከ ምድረ ግብጽ ስለ ተዋሕዶ ሕልውና ተጋድሏል። ምናልባትም ከሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሁዋላ በፈሊጥ ክርስትናን በማስፋፋት ቀዳሚ አባት ነው (በነገራችን ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ማዕተብ ማሰርን ያስተማረ አባትም ነው።)
2ቱ (አባ ቴዎዶስዮስና ቅዱስ ያዕቆብ) ስለ ቀናች ሃይማኖት ብዙ ስለ ደከሙ የዘመኑ ምዕመናን በስማቸው ያዕቆባውያን እና ቴዎዶስዮሳውያን ተብለው ተጠርተዋል። አባ ቴዎዶስዮስ ግን ሲታሠር ሲፈታ፥ ሲሰደድ ሲመለስ ብዙ ተሰቃየ። ሕዝቡን ግን በመልካም እረኝነት ጠብቆ፥ ከተኩላ አፍ ታደገ። በዚህች ቀንም ዐርፎ ተቀብሯል። በፓትርያርክነት ያገለገለባቸው ዘመናት 32 ዓመታት ሲሆኑ ከእነዚህ ዓመታት 28ቱ ያለቁት በስደትና በመከራ ነው። እግዚአብሔር የአባቶቻችን ስደት አስቦ ከነፍስ ስደት ይሰውረን። ከበረከታቸውም ያድለን።
ሰኔ 28 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
ወርኃዊ በዓላት
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
💠 በዘባነ ኪሩብ 💠
በዘባነ ኪሩብ ለሚቀመጠው
በእሳት ድንጋዮች ቅጥሩን ለአጠረው
ዘምሩ ለእግዚአብሔር ለጌታ ዘምሩ
የተከበረ ነው በሰማይ በምድሩ።
ኢሳይያስ ሲያየው እጅግ አፈረ
የተፈራ ነው የተከበረ
የሰማይ ደጆች ተንቀጠቀጡ
ለቅዱስ ስሙ ክብርን ሲሠጡ።
ያልተቀደሰ ለምጽ ያነደደው
እንዴት ይችላል ሊያመሰግነው
በል ፍቀድልኝ ፍቅር ነህና
ልግባ መቅደስህ ላቅርብ ምስጋና።
ዙፋንህ ታየኝ ትምክህቴ ሆይ
ስትመሰገን በሰማይ ላይ
ሲያመሰግንህ ያልተደሰተ
ባይተዋር አልሁን አልውጣ ከአንተ።
ቅኔ የሞላበት ያንን ሰገነት
ልቀላቀለው ተመኘው በእውነት
ልዘምርልህ ባይገባኝም
ዝም የሚል ልሳን አልሰጠኽኝም።
በሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
💚 @mary21God 💚
💛 @mary21God 💛
❤️ @mary21God ❤️
መልካም ዜና ለኢትዮጵያውያን በሙሉ
#በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሎም በአፍሪካ ደረጃ የመጀመሪያዉ ኢንዱስትሪ ከተመሠረተ በጥቂት አመት ዉስጥ ለበርካታ ኢትዮጲያውያን ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረ ህይወታቸዉን ዜና ለኢትዮጵያውያን በሙሉ
#በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሎም በአፍሪካ ደረጃ የመጀመሪያዉ ኢንዱስትሪ ከተመሠረተ በጥቂት አመት ዉስጥ ለበርካታ ኢትዮጲያውያን ዜጎች የስራ እድል እየፈጠረ ህይወታቸዉን እየቀየረ ይገኛል።
©እርሰዎ ምን ይፈልጋሉ ? ስራ ወይስ ተጨማሪ ገንዘብ? እድሉ እንዳያመልጥዎ ፈጥነዉ ይመዝገቡ
© የትምህርት ደረጃ አይጠይቅም።
©ስራዉ በየትኛዉም ቦታ በማነኛዉም ሰአት ሊሰራ የሚችል ቀላልና ግልፅ የሆነ ።
©ግማሽ ቀን (part time) ወይም ሙሉቀን(full time) ሊሰራ የሚችል።
©የምዝገባ ግዜ ከ 28/10/2017ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10(አስር) ተከታታይ ቀናት
ለበለጠ መረጃ :-0996342232
የዳታ ወጪ ያማረራችሁ ነፃ Interenet መጠቀም ፈልጋችሁ ግን channel ያጣችሁ ባዮ ላይ አለላችሁ😎ማርያምን ካርድ ወጭ የለም ከዚህ በኋላ 💪ሚስጥር ነው እያዘጉብን ስለሆነ 🤫🤫 ጀማሪ YouTubers ትፈለጋላችሁ
Читать полностью…✨ሰላም ተወዳጆች እንዴት ናችሁ...የጌታ ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁንና ላለፉት ጥቂት ጊዜያት በአንዳንድ ምክንያቶች ትንሽ ተጠፋፍተን ነበር።
✨ከዚህ በኋላ ግን ጌታ ቢፈቅድ እና ብንኖር የተለያዩ መንፈሳዊ ሀሳቦችን እና ጽሑፎችን በጌታ ፍቅድ ለመልቀቅ እሞክራለሁ።
✨ ካሰብኩት ውስጥ ደግሞ መንፈሳዊ Book Review(የመጽሐፍ ዳሰሳ) አንዱ ነው። እናም መንፈሳዊ መጽሐፎችን እየመረጥን አንብበን በየምዕራፉ ወይን በየክፍሉ ዋና ጭብጥ ሀሳቡን ለመልቀቅ እሞክራለሁ። ጌታ ይርዳኝ እና ከዚህ በታች በማስቀምጥላቹ poll እስከ ማታ ድረስ ደስ ያላችሁን መጽሐፍ ምረጡ እና እንገልጠዋለን😊
የዋጋ ጭማሪ 🔥🔥🔥🔥
2023 group ያላችሁ በአሪፍ ዋጋ አየገዛን ነው ያላቹን group እኛ ጋር ይዛቹ ኑ።✨✨
Dm fast ዋጋው ስለሚቀንስ ይፍጠኑ ።
$5 $5 $5
🔻ሰላም Old Group ማለትም የቆየ የቴሌግራም ግሩፕ ያላችሁ በከፍተኝ ዋጋ እየገዛን ነው በነዚ አመተምህረት የተከፈተ ካላችሁ አናግሩን⬇️
✅2️⃣0️⃣1️⃣7️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣1️⃣8️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣1️⃣9️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣2️⃣0️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣2️⃣1️⃣💵💵💵
✅2️⃣0️⃣2️⃣2️⃣💵💵💵
📥📥ማሳሰቢያ ❌‼️
⏬ የግሩፑ Member ብዛት ''0'' ሆነ ''1000'' ሆነ '10,000'' ዋጋው እኩል ነው
እኛ የምንፈልገው የተከፈተበትን አመተ ምህረት ብቻ መሆኑን ይገንዘቡ😘😍
😑 clear history ያልተደረገ ግሩፕ ነው የምንፈልገው
⏺ Dm
Tik tok account migaza Dm Ba views Dollar yamisara Ba uk yatakafata 12k followers
Читать полностью…Tik tok account migaza Dm Ba views Dollar yamisara Ba uk yatakafata 12k followers
Читать полностью…#ወንድማችንን ፍቱት
ሊቀ ትጉኅን ደረጀ ነጋሽ (ዘወይንዬ) ዛሬ ከግል ቢሮአቸዉ ወጥተዉ ወደ ተሽከርካሪያቸዉ ሲያመሩ ለጥያቄ እንፈልግዎታለን ተብለዉ ደህንነት ነን ባሉ አካላት መወሰዳቸዉን ከቤተሰቦቻቸዉና ከሥራ ባልደረቦቻቸው ከሰማን ቀናት አለፊ ።
ይሁን እንጂ መምህር ደረጀ ነጋሽ እስከ አሁን ያሉበትን ፖሊስ ጣቢያ ለማወቅ አልታቻለም።
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ዋናው መሠረታዊ እውነት ይህ ነው፡- እውነተኛ ለውጥና ትንሳኤ የሚመጣው ቤተክርስቲያንን በመክስና በግላዊ የክለሳ አካሄድ ሳይሆን፣ በታማኝ አገልግሎትና የጋራ ሸክምን በመሸከም ነው።
፮. ሸክሙን መሸከም ወይስ ጣትን መቀሰር?
ቤተ ክርስቲያን ዛሬ የምትፈልገው ተጨማሪ ከሳሾችንና በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚተቹትን አይደለም፤ የምትፈልገው የሃቢብ ጊዮርጊስን ዓይነት መንፈስ የተላበሱ ልጆችን ነው። ችግሩን ከማራገብ ይልቅ የመፍትሔው አካል የሚሆኑትን፤ የቤተ ክርስቲያንን ሸክም በትከሻቸው ተሸክመው የክርስቶስን ሕግ የሚፈጽሙትን።
ስለዚህ፣ እያንዳንዱ የበሰለ ኦርቶዶክሳዊ አማኝ ራሱን ሊጠይቅ ይገባል፡- እኔ የቤተ ክርስቲያንን ሸክም አግዤ እየተሸከምኩ ነው? ወይስ በቁስሏ ላይ ጣቴን እየቀሰርኩ፣ የውግዘት ድንጋይ እየወረወርኩ ነው?
የዛሬው ጥሪ፣ ልክ እንደ ሃቢብ ጊዮርጊስ፣ ኃላፊነትን መውሰድ ነው። ይህ ደግሞ በፍቅር፣ በዲሲፕሊን፣ በትሕትናና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስና እርሱ አካሉ በሆነችው ቤተ ክርስቲያኑ ላይ ባለ ጽኑ እምነት የሚከናወን የተቀደሰ ተግባር ነው።
©አቦርሃም ሲሳይ
#ለመቀላቀል
@ortodoxtewahedo
#ለሃሳብ አስተያየት
@ortodoxtewahedoo
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር
ብቻህን መሆንን ተለማመድ። ብቻን መሆን የሕይወት ጉዞ አንዱ አካል መሆኑን አስታውስ። ያጀበ ሲበተን ደህና ትሆናለህ።
Cheek my bio🙏🙏🙏
ማርያምን ክርስቲያን ወንድሞቼ የሰው ፊት አያሳያቹ ግን ወድጄው አይደለሞ አባቴ ሞቶብኛል እናቴ ታማ ብዙ መድሀኒት ታዞላት ነበር ግን መድሀኒቱ ወደ 45000ብር ይደርሳል እኔ የዩንቨርሲቲ ተማሪ ነኝ እናቴ ገጠር ናት በዚህ ከቀጠለች መሞቷ ነው እግዛብሄርን እንቅልፍ በአይኔ አልዞረም ሚያግዘኝ ምንም ሰው የለም በአላህ አቅም ያላቹ ተባበሩኝ የሌላቹ በጸሎት አግዙኝ
Читать полностью…