ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ። ‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ›› ት.ኢሳ 58÷3 https://youtu.be/csxxAMGtC4I ለመቀላቀል http://t.me/ortodoxtewahedo
ኦ አርምሞ ዘመጠነ ዝ አርምሞ ?
ኦ ትዕግስት ዘመጠነ ዝ ትዕግስት?
ኦ ሂሩት ዘመጠነ ዝ ሂሩት ?
ኦ ፍቅር ዘመጠነ ፍቅረ ሠብ ?
( ይህን ያህል ትዕግሥት እንደምን ያለ ትዕግሥት ነው ? ይህን ያህል ዝመታ እንደምን ያለ ዝመታ ነው ? ይህን ያህል ሰውን ማፍቀር እንደምን ያለ ፍቅር ነው ?
ለመቀላቀል
👉 @ortodoxtewahedo
እንኳን ጥንተ ስቅለቱ ለሚታሰብበት ለመጋቢት 27 በዓለ መድኃኔዓለም ክርስቶስ በሰላም በጤና ጠብቆ አደረሳችሁ
ለአገልጋዮች ሁሉ መልካም አግልግሎት ይሁንላችሁ ዘንድ ተመኘን 🙏🥰
እንኳን አደረሳችሁ
@mery21God
" ትጉሃን በሰማያት የሚያመሰግኑት እርሱ የእሾህ ዘውድ ደፋ ከወንበዴዎች ጋር በዕፀ መስቀል ላይ ተሰቀለ ልዑላኑ እየፈሩ በፊታቸው እራሳቸውን የሚያዋርዱለት እርሱ አሚሰቅሉት ፊት ለህማም ራሱን አዋረደ፡፡ ሰማይና ምድር የተሸከመውን በዕፀ መስቀል ላይ ደካማ እንጨት ተሸከመው ሰማይ እና ምድር የሚንቀጠቀጡለትን ጠባብ መቃብር ወሰነው፡፡ "
#አኮቴተ ቁርባን ዘቅዱስ ቄርሎስ
ለመቀላቀል
👉 @ortodoxtewahedo
††† እንኳን ለጌታችንና አምላካችን መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††
††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††
††† መድኃኔ ዓለም †††
††† ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ለእኛ ሲል በፈጸመው የማዳን ሥራ በዚሕ ዕለት ክፉዎች አይሁድ ከምሽቱ 3:00 ጌቴሴማኒ ውስጥ ያዙት::
ሙሉውን ሌሊት ከቀያፋ ወደ ሐና: ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት: አስረው ሲደበድቡት አድረዋል::
*ዝም ቢላቸው ዓይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት:: ምራቃቸውን ተፉበት:: ዘበቱበት:: ራሱንም በዘንግ መቱት:: እርሱ ግን ሁሉን ታገሰ::
*በጧት ከገዢው ዘንድ ሞት እንዲፈረድበት አቀረቡት:: በሠለስት (ሦስት ሰዓት ላይ) አካሉ እስኪያልቅ እየተዘባበቱ 6,666 ገረፉት:: ሊቶስጥሮስ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት::
*ስድስት ሰዓት ላይ በረዣዥም ብረቶች አምስት ቦታ ላይ ቸንክረው ሰቀሉት:: ሰባት ታላላቅ ተአምራት በምድርና በሰማይ ታዩ::
ዓለም በጨለማ ሳለች ጌታ በመስቀል ላይ ሰባት ቃላትን ተናገረ::
*ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በባሕርይ ሥልጣኑ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ:: በዚያች ሰዓትም ወደ ሲዖል ወርዶ የታሠሩትን ሁሉ ፈታ:: አሥራ አንድ ሰዓት ላይ ደጋጉ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር ቀበሩት::
*በዚያች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተቃጠለ:: ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ:: ቅዱሳት አንስት በዋይታ ዋሉ:: (ማቴ. 27:1, ማር. 15:1, ሉቃ. 23:1, ዮሐ. 19:1)
††† ለእኛ ለኀጥአን ፍጡሮቹ ሲል ይህንን ሁሉ መከራ የታገሰ አምላክ ስለ አሥራ ሦስቱ ኅማማቱ: አምስቱ ቅንዋቱ: ስለ ቅዱስ መስቀሉ: ስለ ድንግል እናቱ ለቅሶና ስለ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስ ብሎ ይማረን::
††† ከቅዱሳኑ በዚሕች ዕለት:-
††† ከ80 ዓመታት በላይ በገዳም የኖረ: የገዳማውያን ሞገሳቸው: የመነኮሳትም ሁሉ አለቃ ታላቁ ቅዱስ መቃርስ አርፏል::
††† ዳግመኛ በዚህ ቀን ንግሥናን ከሊቅነት: ጽድቅን ከሰማዕትነት ጋር የደረበው ሰማዕቱ ቅዱስ ገላውዴዎስ አንገቱን ተከልሏል:: ቅዱስ ገላውዴዎስ የጻድቁ ዐፄ ልብነ ድንግል ልጅ ነው::
††† መድኃኔ ዓለም ከወዳጆቹ ጸጋ ክብርን ያድለን::
††† መጋቢት 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ (ፍቁረ እግዚእ)
2.ቅዱሳት አንስት (ከእግረ መስቀሉ ያልተለዩ)
3.ቅዱሳን ባልንጀሮች (በጌታ ስቅለት ጊዜ ከሞት የተነሱ)
4.ቅዱሳን ዮሴፍና ኒቆዲሞስ
5.ታላቁ ቅዱስ መቃርስ (የመነኮሳት አለቃ)
6.ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት (የኢትዮዽያ ንጉሥ)
7.ቅዱስ ዕፀ መስቀል
††† ወርኀዊ በዓላት
1.አቡነ መብዐ ፅዮን ጻድቅ
2.ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት
3.ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
4.ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት
††† "የተጠራችሁለት ለዚህ ነው:: ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሏልና:: እርሱም ኃጢአት አላደረገም:: ተንኮልም በአፉ አልተገኘበትም:: ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም:: መከራንም ሲቀበል አልዛተም . . . እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ::" †††
(፩ጴጥ. ፪፥፳፩-፳፭)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
ለመቀላቀል
👉 @ortodoxtewahedo
በጌታችን የዕለተ አርብ የመከራ ጊዜ ላይ የነበሩ በወንጌል በልዩነት የተጠቀሱ ሰዎችን ማንነት ለዩ...
@ortodoxtewahedo
Gin beregitegninet seweriwa maryam lemedi new ayideli??
Читать полностью…በድንግል ማርያም ስዉሯ ማርያም ገዳም ጉዞ ለመሄድ 500 ብር የኢትዮጵያ ብር ጎሎኝ ነዉ ተባበሩኝ ማርያምን እዉነቴን ነዉ በእመአምላክ 🥺🙏
Читать полностью…🇮🇱 የእስራኤላውያን ቋንቋ የሆነውን ዕብራይስጥ ቋንቋ መማር ትፈልጋላችሁ ?
👇
@Hebrewethio
@Hebrewethio
ዋነኛው ችግር እንደምጽፈው የምናገር አለመኾኔ ነው ፥ አይደለም ውይይቶችንና ክርክሮችን እንዲሁ ንግግሮችን እንኳን ማድረግ እቸገራለሁኝ። አምላኬ ፈቅዶ ያንን ብለምድና የንግግር ክርክሮችን ብለምድ ፥ I wish to debate your best።
ለአሁን ያለኹት እስኪ መጻፍ ላይ ነው። ሌሎቹ ችግሮች ግን የምኾንባቸው ቦታዎች ምናምን ናቸው።
ደግሞ እንደዚያ አይደለም እንዲሄድ የምፈልገው፥ አንድ እሰጥሃለሁኝ እርሱ ላይ ብቻ እንመላለሳለን። 115 ቦታ መርገጥ አያስፈልገንም።
በላይቭ አልገባም ፥ አይመቸኝም። ለኹሉም ሰው ነው እንደዚያ የምለው ፥ የክርስቲያኖች ላይቭ እንኳን አልገባም። እርሷን እና ሌሎች ሰዎችን እንኳን ጠይቃቸው ፥ በድምፅ አይመቸኝም።
በቃ በድምፅ ብቻ ከኾነ ተውሒድ ላይ ያሉኝን ጥያቄዎች ውሰድና ጠይቀው ፥ ጥቂት ቆይቼ ልላክልህና ገብተህ ጠይቀው። ከዚያ መልሶቹን አምጣልኝና እስኪ እውነት መልስ እንደኾነ እንመልከት።
ንቅረብ ለመድኃኒተ ሕይወት
✍ ኪዳን ዘኢየሱስ እንደ ጻፈው
ኢየሱስ የሕይወት እንጀራ ነው፤ ኢየሱስ የሕይወት መጠጥ ነው። ለሥጋችን ምግብና ውኃ ሳንሰጥ አንድ ቀን እንኳን መቆየት የሚከብደን ኾነን ሳለ ነፍሳችንን ለምን እናስርባለን? ለምንስ እናስጠማለን? የክርስቶስ ሥጋና ደም ለሥጋችን፥ ለነፍሳችን፥ ለመንፈሳችን ቅድስና እና ሕይወት የተሰጠ ዘለዓለማዊ ምግብ ነው። ምነው እኛ ግን መራባችንን ያላወቅን ረሃብተኞች ኾንን? ለምንስ የሕይወት መድኃኒት ከኾነው ጌታ ራቅን?
ዳዊት በመዝሙር ቃል “ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ ነፍሴም ወደ አንተ ትናፍቃለች” እያለ የነፍሱን ጥም ሊያረካለት ወደ ሚችለው ጌታ ያማትራል፤ ለነፍስ ሕይወት የሚኾነውን ውኃ ሊሰጥ የሚችለው ጌታ ብቻ መኾኑን ያውቃልና። እኛ ግን ነፍሳችን ሕይወትን ናፍቃ ተጠምታ ሳለ ወደ ሕይወት መድኃኒት ላለመቅረብ ምክንያት እንደረድራለን፤ ‛መጀመሪያ ሕይወት ይኑረኝ፥ ኃጢአትን ላቁም’ እንላለን። የሕይወትን መድኃኒት ሳንቀበል በራሳችን ሕይወት የለንም፤ ለኃጢአት ሥርየት የተሰጠውን፥ ኃጢአትን የሚያስተወውን #መድኃኒት ሳንቀበል ከኃጢአት ልንላቀቅ ከቶ አንችልም!
ክርስቲያኖች ሆይ፥ በነፍሳችን አንቀልድ። የያዝነው ሕይወት ነው። በነፍሳችን ላይ ቁማር አንጫወት ነፍሳችን ከእኛ ሳትወሰድ በፊት “ወደ ሕይወት መድኃኒት እንቅረብ፤ ጸጋ ኾኖ የተሰጠንን ቅድሳት (ሥጋውና ደሙን) በእግዚአብሔር ጥበብ እንቀበል።” (ቅዳሴ እግዚእ)
#ከስንክሳር_ገጾች አንድ ቅዱስ - መጋቢት 27
ታላቁ ቅዱስ መቃርስ
ቅዱስ መቃርስ የ5ኛው መቶ ክ/ዘመን ሰው ሲሆን የቅዱስ ቄርሎስና የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ተከታይ ነው። ከሕይወቱ ማማርና ከቅድስናው መሥመር የተነሳ አበው አመስግነውት አይጠግቡም። ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት “ጻድቅ እንደ ዘንባባ ያፈራል” እንዳለው። (መዝ. 91) ዳግመኛ "ወይከውን ከመ ዕጽ እንተ ትክልት ኀበ ሙሐዘ ማይ" (መዝ. 1፥3) እንዳለው ቅዱስ መቃርስ እጅግ ብዙ ትሩፋቶችን አፍርቷል። ከሁሉ አስቀድሞ በበረሐ ኗሪ ከሆነበት ቀን ጀምሮ ስለ ጌታ ፍቅር እንባው እንደ ዥረት እየፈሰሰ። ራሱን በብረት ዘንግ ይመታ ነበር።
ቃው በምትባል ሃገር ዻዻስ ሆኖ በተሾመ ጊዜም ተጋድሎውን አልቀነሰም። ዻዻስ ቢሆንም የሚለብሰው የበርሃዋን ደበሎ ነው። ከብቅዓቱ የተነሳ የሕዝቡ ኃጢአት በግንባራቸው ላይ ተጽፎ እየታየው ስለ ወገኖቹ ያለቅስ ነበረ። በቤተ መቅደስ ውስጥ ቆሞ አንጀቱ ቅጥል እስኪል ድረስም ያለቅስ ነበር።
ሁልጊዜ ሲቀድስ ጌታችንን ከመላእክቱ ጋር ያየው ነበር። አንድ ቀንም ጌታ ቅዱስ መቃርስን “ዻዻሱ ሆይ ሕዝቡን ገስጻቸው። ብትገስጻቸውና ባይሰሙህ እዳው በእነርሱ ላይ ነው” አለው። ቅዱስ መቃርስም ሕዝቡ ከኃጢአታቸው ይመለሱ ዘንድ ይመክራቸው፥ ይለምንላቸውም ነበር።
ከዚህ ሁሉ በኋላ በጉባኤ ኬልቄዶን (ጉባኤ አብዳን) 636 ዻዻሳት ንጉሡን ፈርተው ሃይማኖታቸውን ሲክዱ ቅዱሳኑ ዲዮስቆሮስና መቃርስ “ተዋሐዶን አንክድም” በማለታቸው ዘበቱባቸው። ብዙ አሰቃይተውም ወደ ጋግራ ደሴት አሳደዷቸው። ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ጋግራ ውስጥ ሲሞት ቅዱስ መቃርስ ወደ እስክንድርያ ተመልሶ ሕዝቡን ሲመክር ያዙት። ከመሬት ላይ ጥለውም እየደጋገሙ ኩላሊቱን ረገጡት። ከመከራው ብዛትም በዚህች ቀን ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ። ቅዱሱ ሙታንን ማስነሳትን ጨምሮ ብዙ ተአምራትን ሠርቷል። መድኃኔ ዓለም ከወዳጆቹ ጸጋ ክብርን ያድለን።
መጋቢት 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
ወርኃዊ በዓላት
ትርፍ ሰዓቶን ብቻ ተጠቅመው ውጤታማ መሆን ይፈልጋሉ?
እንግዲያውስ የእጅ ስልኮትን እና internet በመጠቀም ብቻ
ምንም አይነት ገንዘብ ከኪሶ ሳያወጡ ይለወጡ
ከሰሩ በቀን በonline ብቻ ከ3ሺ ወይም ከ4000 ብር በላይ ያገኛሉ
መስራት ከኛጋ መለወጥ ከፈለጉ በውስጥ አናግሩን📩
ሳዶር: ቅኝ እጁን የተቸነከረበት
አላዶር: ግራ እጁን የተቸነከረበት
አዴራ: ደረቱን የተቸነከረበት
ሮዳስ: ከወገቡ አጣብቆ እንዲይዝ የተቸነከረበት
ዳናት: እግሮቹን የተቸነበረበት
#የቤት_ለቤት_አስጠኚ_ይፈልጋሉ?
👉 አስጠኚዎቻችን ለልጅዎ ውጤታማነት የሚተጉ፤ ለተማሪዎች በትምህርት ቤት ከመምህራኖቻቸዉ ሊያገኙ የማይችሉትን ግላዊ ትኩረትና ክትትል የሚሰጡ፤ እንዲሁም ተማሪው ያለበትን የትምህርት፣ የባህሪና ሌሎችም ክፍተቶችን በመሙላት ብቁ የሚያደርጉ ናቸው።
አገልግሎቱ የትኛውን የክፍል ደረጃ ያካትታል?
ጥናቱ በማን ይሰጣል?
#ከስንክሳር_ገጾች አንድ ቅዱስ - መጋቢት 26
ቅድስት ኢዮጰራቅስያ
በዚህ ዕለት እናታችን ቅድስት ኢዮጰራቅስያ ድንግል አርፋለች። ቅድስቲቱ በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበረች እናት ስትሆን ገና በ9 ዓመቷ ምድራዊ ሀብትን ንቃ መንናለች። ምክንያቱም ዘመዶቿ የሮም ነገሥታት እነ አኖሬዎስ ነበሩና። ድንግል ኢዮጰራቅስያ በገዳም፥ በጾምና በጸሎት፥ በፍፁም ትኅትናና ታዛዥነት፥ እንዲሁም በፍቅር ኑራ በዚህች ቀን አርፋለች። አምላካችን ከቅድስት እናታችን በረከት አይለየን።
መጋቢት 26 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
ወርኃዊ በዓላት
“ስለ ስሜም ቤቶችን ወይም ወንድሞችን ወይም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም እርሻን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል፤ የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል።” (ማቴ. 19፥29)Читать полностью…
✅ አሁን online ላላችሁ ብቻ ጥያቄና መልስ ውድድር ልንጀምር ነው❗️
1️⃣ ለወጣ 100 ብር ካርድ
2️⃣ ለወጣ 50 ብር ካርድ
3️⃣ ለወጣ 25 ብር ካርድ
➡️ ዝግጁ ከሆናችሁ ጀምር የሚለውን ይጫኑ።👇
ሰላም ጤና ይስጥልኝ እስከዓለም እባላለው የምሰራው የግል ስብና personal development ነው በስልጠናዎች ከሚሰጡት የኢትዮጵያ ድርጅትጋር ነው በአሁኑ ሰዓት ብዙ ሰዎች ህልሞቻቸውን ራዕያቸውን እንዲያውቁ በስልጠና እየደገፈ ያለ ሲሆን በተጨማሪ የራሳቸውን ስራ በሙሉ ሰዓት እየሰሩ በትርፍ ጊዜ የሚሰሩት የስራ እድል እየሰጠ ይገኛል ምን አልባት አንተ(ቺ) እንደዚ አይነት እድል ብታገኝ እድሉን መጠቀም የምትችል(ችይ)?? ይመስልሃል (ሻል)??
Telegram
👇👇👇👇
@eskel123
@edkel123
@eskel123
🖕🖕🖕🖕🖕
Tell me inbox
Sorry Lenege alagegnim gin Le kidame limokirilik
Читать полностью…500 birr rasu beki new eza lemehed eko may be yebajaji birr kagodele new enji beguzo mekinami hone begili 700 birr beki new 200 birr lebajaji begili kehedachu
Читать полностью…#ከስንክሳር_ገጾች አንድ ቅዱስ - መጋቢት 25
ቅዱስ አንሲፎሮስ
ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ የከበረና የተመሰገነ ሐዋርያ አንሲፎሮስ ዐረፈ። ይህም ከእስራኤል ልጆች ከቢንያም ነገድ ነው ወላጆቹም የኦሪትን ሕግ የሚጠብቁ ናቸው እርሱም ሥራዎቹን በአየ ጊዜ ትምህርቶቹንም በሰማ ጊዜ ጌታችንን ተከተለው። ድንቅ የሆኑ ተአምራቶችን እየተመለከተ ጥቂት ቀን ተቀመጠ ጌታችንም በሀገረ ናይን የመበለቲቱን ልጅ በአስነሣው ጊዜ ከዚያ ነበረ። ይህን አይቶ ወዲያውኑ አመነ።
ሌላ ምልክት አልፈለገም፤ ብልጭ ብልጭ ሲል የነበረ የአይሁድ የሕግ ፋና ትቶ ወደ እውነተኛ ፀሐይ ወደ ጌታ ኢየሱስ ቀርቦ ደቀ መዝሙሩ ሆነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከዐረገ በኋላ በጽዮን አዳራሽ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከሐዋርያት ጋራ የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ተቀብሎ ሐዋርያትንም በመከተል በብዙ አገሮች ውስጥ አስተማረ።
ሐዋርያትም በሀገረ አቴና ኤጲስቆጶስ አድርገው ሾሙት። በውስጧም ወንጌልን በመስበክ ብዙዎችን አሳመነ፤ የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው። በትምህርቱና በምክሩ ዕውቀት እንዲያድርባቸው አደረጋቸው በትምህርቱም ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ ፈወሳቸው።
ተጋድሎውንም በፈጸመ ጊዜ በሰላም አረፈ። በድል አድራጊነትም የክብር አክሊል ተቀበለ። መላ ዘመኑ ሰባ ዓመት ነው፤ በአይሁድ ሕግ ሃያ ዘጠኝ ዓመት በክርስትና ሕግ አርባ አንድ ዓመት ኖረ። የከበረ ሐዋርያ ጳውሎስም በመልእክቶቹ አስታውሶታል፤ ሰላምታም አቅርቦለታል። በጸሎቱ የምትገኝ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።
መጋቢት 25 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
ወርኃዊ በዓላት
Egziabher ymesgen endet nesh ehtachn
Читать полностью…ምክንያትህስ መናገር አትችልም ወይ እናንተ ጠይቁ ምትለው ጭራሽ ማይሆን ነው ምክንያቱም የጠየከኝን አንድ ጥያቄ መልሱን እዤልህ ብመጣ በዛ መልስ እንደገና ሌላ ጥያቄ ይኖርሃል እንደዛ እያለ ይቀጥላል ከዝህ ሁላ አፍህ መናገር ሚችል ከሆነ ማለትም ተፈጥሮኣዊ ችግር ካሌለብህ ላንተም ለሁሉም ሚበጀውም ውጤት ምያመጣውም እሱ ነው
Читать полностью…በላይቭ ገብታችሁ በድምፅ ታወራላችሁ አንተ ካልፈለከ ርከርድ አይደረግም አብሽር ደግሞ በነፃነት ነው ምታወራው በግልም ሆነ በውስጥ ምታወራው ከሱ ብቻ እስከሆነ ድረስ ያው ነው ደግሞ መናገር ምትችል ከሆነ ምትፂፈውን ራሱ ነው ምታወራው የእጅ ፅሁፍ ልምድህን ለማበልፀግ ከፈለከ በስልክህ አንዳንድ ኖቶችን አየያዝከ ተለማመድ ከዝህ ወጪ በፅሁፍ ይሁን የሚለው መስፈርት የመገናኘት ፍላጎት አለመኖርን እንጂ ሌላ ያምያመላክት አይመስለኝም ደግሞ ልጁ ሲበዛ ጨዋ ነው እያዝናናክ ነው ምያወያይህ
Читать полностью…