የምትመራውን ከተማ እና የምትሰራውን ስራ በውጤታማነት የምትፈፅም ከንቲባ!!
@AdanechAbiebie
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ዓድዋ የኢትዮጵያዊነት ከፍታ፤ የአንድነት አርማ!
ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ የወል የሆነ ታሪኮች ያሏት ታላቅ ሀገር ነች፡፡ ከእነዚህም ታሪኮች መሀከል አብሮነት ፣ መከባበር ፣መደማመጥ ፣ የጋራ አላማ ከተያዘ የትኛውንም ምድራዊ ፈተናን ማለፍ እንደሚቻል ለዓለም ያሳየችበት የዓድዋ ድል በዓል አንዱ ነው ።
ሀገራት ዜጎቻቸውን ለተሻለ ድልና ስኬት ከሚያነሳሱባቸው ትርክቶች መሀከል የሆነው የእኛ የዓድዋ ድል ለጥቁር ህዝቦችም ጭምር ድል ነው።
ታላቅ የሆነች ለሁላችንም የምትሆን ሀገር በፅኑ መሰረት ላይ መገንባት የሚቻለውና በየወቅቱ ከሚገጥሙን ፈተናዎቻችን በዘላቂነት መላቀቅ የምንችለው በዚህ ልክ ተጨማሪ የወል የሆኑ አሰባሳቢ ታሪኮችን መስራት እና ያሉንን ደማቅ የሆኑ ታሪኮች መጠበቅ ሲቻል ነው።
የሀገር ዋልታና ማገር የሆነ ትውልድ ለመገንባትም የአንድነት አርማ የሆነው የዓድዋን ድል ከትውልድ ወደ ትውልድ ክብርና ሞገሱን ጠብቀን በጋራ ማስቀጠል ሲቻል ነው ።
"ዓድዋ መሪና ተመሪ - አስተዳዳሪና ተዳዳሪ ሲደማመጡ፣ ሲግባቡና ለአንዲት ሀገር ሲሰሩ የሚበግራቸው ነገር እንደማይኖር አስተምሮን ያለፈ ታሪክ ነው፡፡ የክብርህ መመኪያ ደስታና ህይወትህ የሆነችውን ውብ ሀገር ከወራሪ ትታደግ ዘንድ የምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜኑ እና የደቡቡ ሰው ፊትህን ወደ አድዋ አዙረህ ወረኢሉ ላይ ቆየኝ ያለውን የመሪውን ቀጠሮ አክብሮ ለነፍስ ቀጠሮ በነብስ የደረሰ ሳተና ህዝብ፣ የድል አክሊል የተቀናጀበት ታሪካዊ ቀን ነው"
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
በመሀል አዲስአበባ (ፒያሳ) የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ የምሽት ገፅታ 👆👆👆
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
በመሀል አዲስአበባ (ፒያሳ) የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ የምሽት ገፅታ 👇 👇 👇
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ እና የአዲስ አበባ ዝግጅት
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ከተማችን አዲስ አበባ ከየካቲት 3 እስከ 10 ቀን 2016 ዓ/ም ልዩ ልዩ ኩነቶችን ታስተናግዳለች። የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ኩነቶቹ በስኬት እንዲጠናቀቁ በፀጥታ ዕቅድ ላይ ተወያይቶ ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል። ባለድርሻ አካላት እና ህብረተሰቡ የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉም ተጠይቋል።
የካቲት 3 ቀን 2016 ዓ/ም ልዩ ልዩ እንግዶች እና የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የጋራ ትርክታችንን ይበልጥ የሚያጎላው የአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም በደማቅ ስነ-ስርአት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ይመረቃል።
የምረቃ ስነ-ስርአት በሰላም እንዲከናወኑ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ጥር 27 ቀን 2016 ዓ/ም በአዲስ አበባ ፖሊስ ሠላም አዳራሽ ውይይት አድርጓል።በዚህ ውይይት ላይ የሀገር መከላከያ ፣ የፌዴራል ፖሊስ ፣የብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት ፣የአዲስ አበባ ከተማ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ፣ የሸገር ከተማ ፖሊስ እና ሌሎች የፀጥታ አካላት ተሳትፈዋል።
ውይይቱን የመሩትና የስራ መመሪያ የሰጡት የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ ሲሆኑ፤ በመድረኩ የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ተገኝተዋል፡፡
የካቲት 3 ቀን 2016 ዓ/ም የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ፣ የውጭ ሀገራት እንግዶች ፣ ዲፕሎማቶች ፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የኢትዮጵያ ብሔር ፤ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የትስስር አርማ የመላው ጥቁር ህዝቦች የነፃነታቸው ብስራት የሆነው የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በደማቅ ስነ-ስርአት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ይመረቃል። የምረቃ በዓሉን ተከትሎም በዕለቱ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑም የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ በዚህም መሰረት፡-
• ከአፍንጮ በር ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን
• ከሰሜን ሆቴል ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን
• ከዮሃንስ ቤተ ክርስቲያን ወደ አቡነ ጴጥሮስ
• ከአራት መንታ ወደ ጅንአድ
• ከይርጋ ሃይሌ የገበያ ማዕከል ወደ አቡነ ጴጥሮስ
• ከሃብተ ጊዮርጊስ ድልድይ ወደ ሱማሌ ተራ
• ከሱማሌ ተራ ወደ ኤሊያና ሆቴል(ባንኮዲሮማ) መስቀለኛ
• ከተክለ ሃይማኖት አደባባይ ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ
• ከአገር አስተዳደር መብራት( ኢሚግሬሽን) ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ
• ከንግድ ማተሚያ ቤት ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ
• ከአሮጌው ቄራ ወደ ባንኮ ዲሮማ መብራት
• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ደጎል አደባባይ
• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን
• ከመቅደላ ሆቴል ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን
• ከቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ወደ ቴሌ እና ወደ ቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ፊት ለፊት ወደሚገኘው አደባባይ የሚወስዱት መንገዶች የካቲት 3 ቀን 2016 ዓ/ም ከቀኑ 6 ሰዓት ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች ይህንን ተገንዝበው አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ እና የትራፊክ ፖሊሶች በሚጠቁሟቸውን አማራጭ አቅጣጫዎችን በመጠቀም አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
በዋዜማው የካቲት 2 ቀን 2016 ዓ/ም ከላይ በተጠቀሱት መንገዶች እና የምረቃ ስነ ስርዓቱ በሚከናወንበት በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ዙሪያ ተሽከርካሪ ማሳደርም ሆነ ለአጭርም ሆነ ለረጀም ሰዓት አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑንም አሳስቧል፡፡ ይለፍ ያላቸው አሽከርካሪዎች ቸርችር ጎዳና ጫፍ የቀድሞ ሜክሲኮ ታክሲ ተራ እና ከቴዎድሮስ አደባባይ እስከ ቸርችር ጎዳና ጫፍ መኪናዎቻቸውን መቆም እንደሚችሉ አዲስ አበባ ፖሊስ ገልፆ ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ እንደሚኖር የፕሮግሙ ታዳሚዎች ተገንዝበው የተለመደ ትብብር እንዲያደርጉ መለእክቱን አስተላልፏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ተጀምሮ እሰከሚጠናቀቅ ጥሪ ከተደረገላቸው እንግዶች ውጪ ወደ አድዋ መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስዱ መንገዶች ዝግጅቱ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለእግረኞችም ዝግ መሆናቸውን አዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
እስከ 5ሺ ሰዎች የሚሳተፉበት #አድዋ_ሩጫ ሊካሄድ ነው።
“አድዋ ሩጫ” የተሰኘ የጎዳና ላይ ሩጫ ሊካሄድ እንደሆነ የሩጫው አዘጋጅ የአድዋ ሩጫ ኢቨንት ኦርጋናይዘር ሥራ አስኪያጅ ሄኖክ ፀጋዬ፣ በዛሬው ዕለት በኢዮሜር ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል።
የአድዋ ድል መታሰቢያ ክብረ በአል ከሚከበርበት የካቲት 23 ቀደም ብሎ ባለው እሁድ በየአመቱ በአገር ውስጥና ከተወሰኑ አመታት በኋላም በተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት የሚካሄድ የ10 ኪ.ሜትር የአደባባይ ሩጫ እንዲሁም ከ10 አመት በኋላም በአለም አቀፍ ደረጃ የሚከናወን «አድዋ ማራቶን» ለማዘጋጀትና ከ3 አመት በኋላም የአድዋን ሩጫ ጊነስ ወርልድ ቡክ ላይ ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል።
በዚህ የ10 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ 5ሺ ሰዎች ይሳተፉበታል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ በዚህ ሩጫ መሳተፍ የሚፈልግ ሰው የምዝገባ ሂደቱ የሚከናወነው በቴሌ ብር ሲሆን የቲ-ሸርቱ ዋጋ 2ሺ ብር ነው ተብሏል።
ከጎዳና ሩጫ የሚገኘው ገቢ ከወጪ ቀሪ በድርቅና በረሃብ ለተጎዱ ወገኖች እንደሚውልም ተጠቁሟል፡፡
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የነበሩትን ስራዎች እና መሻሻሎች በጥልቀት መገምገም ጀምረዋል።
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ከየካቲት 9 እስከ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ የሚካሄደውን 9ኛው ሀገር አቀፍ የከተሞች ፎረም ለማስተናገድ ዝግጅት ማድረጉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አስታወቀ፡፡
እንግዶችን ለማስተናገድ ኮሚቴ ተቋቁሞ በርካታ ሥራዎች መከናወናቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ሰናይት ሰለሞን ተናግረዋል፡፡
ለአብነትም የእንግዶች ማረፊያ እንዲሁም የፎረሙ ተሳታፊ ከተሞች የሚተዋወቁበት የዐውደ-ርዕይ ቦታ መዘጋጀቱን ጠቅሰዋል፡፡
የክልሉ ሕዝብ በኢትዮጵያዊነት ባህል እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት አድርጓል ማለታቸውን የወላይታ ዞን ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
በፎረሙ ከ200 የሚልቁ ከተሞችና የተለያዩ ተቋማት ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ተመላክቷል፡፡
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
በተጨባጭ ለውጥ ፣በላቀ ሀሳብ ከተማዋን እየመራች ያለች ድንቅ ከንቲባ!!
@AdanechAbiebie
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
የተወሰደውን ሕይወታችሁን አስመልሱ!
ሕይወታችንን ማስመለስ ማለት በአጭሩ ሲተረጎም በአንድ ሰው፣ ሁኔታ ወይም ልምምድ ምክንያት ከደረሰብን ቀውስ የተነሳ በትክክል ማሰብ፣ መስራት፣ መተኛትም ሆነ መኖር እስከማንችል ድረስ የደረሰውን ሁኔታችንን እንደገና ወደቀድሞው ጤናማ ሁኔታ ማስመለስ ማለት ነው፡፡
• የጎዳችሁና እስክትበቀሉት ድረስ ውስጣችሁን የሚያናድደው ሰው የወሰደባችሁን ሕይወታችሁን አስመልሱ!
• ሰዎችን አምናችሁ በተወሰደባችሁ ቁሳቁስ ወይም ገንዘብ ምክንያት ዘወትር ከመቆጨታችና ከመቆዘማችሁ የተነሳ የተወሰደውን ሕይወታችሁን አስመልሱ!
• አፍቅራችሁ ትንሽ ከተጓዛችሁ በኋላ ያ ሰው ለእናንተ ምንም ፍላጎት እንደሌለው ብትደርሱበትም ካላችሁ የስሜት ትስስር የተነሳ ልትረሱት ባልቻላችሁት ሰው የተወሰደውን ሕይወታችሁን አስመልሱ!
• ማንኛውንም ሰውም ሆነ ሁኔታ ከመፍራታችሁ የተነሳ ወደፊት መራመድ እስከማትችሉ ድረስ በመሆናችሁ ምክንያት የተወሰደውን ሕይወታችሁን አስመልሱ!
ወደራሳችሁ ተመለሱ! ወደቀደመው ሰላማችሁ ተመለሱ! ወደእውነተኛው ማንነታችሁ ተመለሱ! ከምንም ሁኔታና ከማንም ሰው ጫና ውጪ ወደነበራችሁበት ሚዛናዊ ሕይወት ተመለሱ!
ንቁ! ወስኑ! ምክርና እገዛን ፈልጉ! የድሮውን ጤናማ ማንነታችሁን እንደገና የራሳች አድርጉ እንጂ የሰውና የሁኔታዎች ሰለባና መጫወቻ አትሁኑ!
መልካም ቀን!
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው እለት የተለያዩ ሹመቶችን ሰጥተዋል። በዚህም መሰረት 👇
1. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን - የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር
2. ትዕግስት ሃሚድ - የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር በመሆን ተሹመዋል፡፡
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን በ15ኛ መደበኛ ስብሰባ 👇
👉 አቶ ተመስገን ጥሩነህ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር
👉 አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
👉 ዶ/ር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስትር አድርጎ ሾሟል።
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
አድዋ ነጠላ ትርክትን የናደ፣ የኢትዮጵያዊያንን ህብረት ያነፀና የብሔራዊ አርበኝነትን በማይነቀነቅ ዓለት ላይ ያስቀመጠ የወል እውነታችን ማጽኛ ነው!
ኢትዮጵያውያን ብዝሃነታቸው የጥንካሬያቸው መሰረት መሆኑን በተግባር የተገለፀበት ኢትዮጵያዊነት ብሎም አፍሪካዊነት ከፍ እንዲል ፈር የቀደደ የታሪካችን አሻራ ነው ዓድዋ! ዓድዋ ኢትዮጵያዊያን በህብረት ከጫፍ ጫፍ ተምመው በአብሮነት ደምና አጥንታቸውን የገበሩበት የሕብረ ብሔራዊ አንድነት ዓርማ ነው።
ዓድዋ ኢትዮጵያዊያን በብሔራዊ ገዥ ሀሳብ ሲሰባሰቡ ጠንካራ የማስተባበር፤ የመምራት፤ የመደማመጥና ፈተናዎችን በአብሮነት የመሻገር ችሎታ እንዳላቸዉ ያስመሰከሩበት ታላቅ ታሪክ ነው።
የዓድዋ ድል ለኢትዮጵያዉያን ሁሉ የአርበኝነት አምድ የሆነ በእሳት ተፈትኖ የነጠረ በወጀብ የማይናወጥ ህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት የታነፀበት የብሔራዊ አርበኝነት ምሰሶ ነው።
ዓድዋ የኢትዮጵያዊያን አይበገሬነት፤ ጀግንነት፣ ሕብረትና አንድነት በተግባር የተመሰከረበት የብሔራዊነት ምልክት፣ የወል ታሪካችን አርማ ነዉ። ዓድዋ የብሔራዊነት ምሰሶ ነው ስንል ኢትዮጵያዊያን ከጫፍ ጫፍ በወል ተምመዉ ያስመዘገቡት ድል የጋራ ትናንትን ከነገ ጋር ማስተሳሰሪያ ገመዳችን መሆኑን የሚገልጽ ሀቅ ስለሆነ ነው፡፡
ብሔራዊ ገዥ ትርክት ልክ እንደ ዓድዋ ድል ሁሉም ኢትዮጵያዊያን በሀገራቸው ጉዳይ እኩል ተሳትፎና ተጠቃሚነት እንዲኖራቸው የሚያስችል ሲሆን ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ በተሰናሰለ የብሔር-ብሔረሰቦች ላብ እና ደም ድምር ውጤት የተገነባችና በወል ጥረቶቻቸው የምትበለጽግ ሀገር ናት።
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 15ኛ መደበኛ ስብሰባ የአስፈጻሚ አካላት ሹመት ያፀድቃል፡፡
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
የም/ቤቱን 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ እና 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ ጉባኤዎች መርምሮ በማፅደቅ የዕለቱን መደበኛ ስብሰባ የሚጀምር ይሆናል፡፡
ምክር ቤቱ በነገው ዕለት ከ1ኛ ልዩ ስብሰባ የተሸጋገሩ የተለያዩ አጀንዳዎችንም መርምሮ የሚያፀድቅ ይሆናል፡፡
ከተሸጋገሩት አጀንዳዎች ውስጥ የፌዴራል የመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን በተመለከተ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል፡፡
በተጨማሪም የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የሰራተኞች አስተዳደር ረቂቅ ደንብን በተመለከተ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ደንቡን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በመጨረሻም የኢትዮጵያ የሜዳይ፣ ኒሻን እና ሽልማት እንዲሁም የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የሚቀርብ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ ይመራል።
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
Adwa Victory Memorial 🇪🇹
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
በኦሮሚያ ክልል 20 ከተሞች የሚካሄደውን ሕዝባዊ የውይይት መድረክ የሚመሩ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ወደ ክልሉ ገብተዋል።
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ፀሐይ አውሮፕላን ዛሬ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስትደርስ ደማቅ አቀባበል ተደረገላት።
እ.አ.አ በ1935 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ ተገጣጥማ በረራ ያደረገችው ፀሐይ አውሮፕላን ከበርካታ ዓመታት በኋላ ዛሬ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስትደርስ በደመቀ ሁኔታ አቀባበል እንደተደረገላት የኢትዮጵያ አየር መንገድ መረጃ ያመላክታል።
በጀርመናዊው ኢንጅነር ሄር ሉድዊግ ዌበር እና የኢትዮጵያ ባለሞያዎች ትብብር የተሰራችው "ፀሐይ" አውሮፕላን በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲፕሎማሲ ጥረት ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ መብቃቷ ይታወቃል።
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
Congratulations አቶ ኢሳያስ ጅራ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ የካፍ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሆነው ተመረጡ።
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ባደረገው ስብሰባ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራን የካፍ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ (executive committee) አባል አድርጎ መምረጡን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አቶ ኢሳያስ ጅራ የካፍ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሆነው በመመረጣቸው የተሰማውን ደስታ የገለፀ ሲሆን ስኬታማ የሥራ ጊዜንም ተመኝቷል።
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተጠናከረ መልኩ፣ ችግር ፈቺ በሆነ መንገድ እየተሰጠ ውሏል።
የባለጉዳይ ቀንን በማስመልከት እየተሰጠ ያለው የአንድ ማእከል አገልግሎት የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወልዴ ወገሴ፣ የክፍለ ከተማው ምክትል ስራ አስፈጻሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰሎሞን ታደሰ እና የክፍለ ከተማው ሴክተር ጽ/ቤት ኃላፊዎች በተገኙበት ተገልጋዮችን እያስተናዱ የነበረው፡፡
ዛሬም እንደወትሮው በአስተዳደሩ የግልጽነትና ተጠያቂነት አሠራርን በመፍጠር የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻልና የተገልጋዩን አንግልት ለመቀነስ የሚያስችል የአንድ ማእከል አገልግሎት በተጠናከረ መልኩ እየተሰጠ ውሏል።
አገልግሎት ፈላጊዎችም የሚመለከታቸው አመራሮች በአንድ ላይ ሆነው ጉዳያቸውን በየተራ በመግባት በማቅረብ የሚሰጣቸው ምላሽም ተገቢና ጥሩ ሆኖ እንዳገኙት ተናግረዋል።
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ6 ወራት ውስጥ 15 አዋጆችን ማፅደቁን ገለፀ።
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2016 በጀት ዓመት የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለምክር ቤቱ የአማካሪ እና አስተባባሪ ኮሚቴዎች አቅርቦ ውይይት እየተካሄደበት ይገኛል።
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ታገሰ ጫፎ የውይይት መድረኩን በንግግር ከፍተዋል።
የምክር ቤቱን የስድስት ወራት ሪፖርት የምክር ቤቱ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር ምስራቅ መኮንን ያቀረቡ ሲሆን ምክር ቤቱ ባለፉት ስድስት ወራት ከቀረቡለት 23 ረቂቅ አዋጆች ውስጥ አንድ ደንብን ጨምሮ 15 አዋጆችን እንዳጸደቀ አስረድተዋል።
ረቂቅ አዋጆቹ የጸደቁት ለህዝብ የሚሰጡት ጥቅም በትኩረት ታይቶ እና ተመርምሮ ሰፊ ውይይት ከተካሄደባቸው በኋላ እንደሆነ ዶክተር ምስራቅ በሪፖርታቸው አብራርተዋል።
የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም እንዲሁም የግል ዳታ ጥበቃ ረቂቅ አዋጆችን ጨምሮ ሌሎች አዋጆች በቀጣይ ስድስት ወራት ምክር ቤቱ መክሮባቸው የሚጸድቁ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።
ምክር ቤቱ በዚህ ስድስት ወራት ውስጥ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ጨምሮ ሰባት ውሳኔዎችን ማስተላለፉንም ዶ/ር ምስራቅ በሪፖርታቸው ገልጸዋል።
ምክር ቤቱ ባለፉት ስድስት ወራት ከ474 የምርጫ ክልሎች ውስጥ በ305 ምርጫ ክልሎች ተመራጮች ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ውይይት መደረጉን ክምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በተደረገው የመራጭ ተመራጭ ውይይት 1ሺህ 733 የሚሆኑ ጥያቄዎች ከህዝቡ የተሰበሰቡ ሲሆን፤ ለ48 ተቋማት ጥያቄዎቹ ተልከው 47ቱ ተቋማት ምላሽ መስጠታቸውንም ዶ/ር ምስራቅ በሪፖርታቸው አብራርተዋል።
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ስራዎችን መገምገም ጀመሩ።
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
CONGRATULATIONS ክቡር ሚኒስትር
አቶ መላኩ አለበል ”የአፍሪካ ምርጡ የኢንዱስትሪ መሪ” በሚል ተሸለሙ። አቶ መላኩ አለበል የአፍሪካ ምርጡ የኢንዱስትሪ መሪ ኾነው መሸለማቸው ተሰምቷል፡፡
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል፣ በቢዝነስ ኤክስኪዩቲቭ አዘጋጅነት፣ ሞሪሽየስ በተካሄደው የአፍሪካ የመሪዎች የሽልማት ጉባኤ ላይ የአፍሪካ ምርጡ የኢንዱስትሪ መሪ ተብለው መሸለማቸውን ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የነበሩትን ስራዎች እና መሻሻሎች በጥልቀት መገምገም ጀምረዋል። ይህ በፌደራል እና የክልል ኃላፊነት ባላቸው የስራ ተዋንያን የሚደረገው ጠቃሚ ግምገማ በድኅረ ግጭት መልሶ ግንባታ እና በሰላም ስምምነት አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ነው።
Prime Minister Abiy Ahmed has embarked on an in-depth review of the initiatives and progress in the Tigray Region since the inception of the Interim Regional Administration. This significant evaluation of Federal and Regional actors focuses on the critical areas of post-conflict reconstruction and the implementation of the peace agreement.
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
በስደት የሚኖሩ ሀበሾች ሩም ሜት ሆነው በአንድ ቤት ውስጥ እንደሚኖሩ ይታወቃል። እዚህ አዲስ አበባ ግን ሁሉም ላጤ የቤት ኪራይ አናቱ ላይ ቢወጣበትም በብዛት ብቻውን እንጂ ደባል ሆኖ አይኖርም።
ለምን ይሆን ?
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
The Great Adwa Victory Memorial
የታላቁ ዓድዋ ድል መታሰቢያ!
@AdanechAbiebie
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ሁለቱ የቡዳ መድኃኒቶች
@AbiyAhmedAli
@TirunehDinku
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ሰላማችንን በመጠበቅና ጽንፈኝነትን በጋራ በመታገል የሀገራችንን ብልጽግና እውን እናድርግ!
ሰላምን እውን የማድረግም ሆነ ሰላምን የማጣት ወሳኙ እኛው ራሳችን ነን። ዛሬ በእጃችን ያለው ሰላም ነገም በአስተማማኝ ደረጃ ሊቀጥል የሚችለው ሁሉም ለሰላም ተግቶ ሲሰራና ሰላምን የሚያፈርሱ ነገሮችን ያለ ምህረት ሲታገል ብቻ ነው፡፡
ሰላምን ከሚያደፈርሱ ነገሮች አንዱ ደግም ጽንፈኝነት ነው። ጽንፈኝነት ከመደመር ሳንካዎች ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ሲሆን የራስን ፍላጎት በሌሎች ላይ የመጫን ወይም የማስገደድ አባዜ የተጠናወተው ጫፍ የሚይዝ የኋላቀርነት መገለጫ ነው፡፡
መነሻው በተናጠል ፍላጎቷቶች ላይ የሚመሰረትና የሌሎችን መስተጋብሮች ለመቀበል የሚቸገር ነው። ኢትዮጵያ ደግም ብዝሃ ሀሳብ፣ ብዝሃ ባህል፣ ብዝሃ ቋንቋና ብዝሃ ሃይማኖት ባለቤት ናት።
በመሆኑም የአዲሱ የብልፅግና እሳቤ መሰረት የሚያደርገው የመደመር ትውልድ አስተሳሰብ ትርክቱ የትስስር ትርክት፣ የአብሮነት ትስስር ነው፤ በማናቸውም የፖለቲካ፣ ማህበራዊ፣ የሀገር ደህንነትና ውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎች እኔም፣ እኛም፣ ባጠቃላይ ሁላችንም በጋራ መጠቀም አለብን ማለት መቻል አለብን።
በመሆኑም ከጽንፈኝነት በመራቅ፣ ሰላማችንን መጠበቅ እና መንከባከብ አማራጭ የሌለው የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ነው።
እኛ ኢትዮጵያዊያን ሀገራችን ሰላም ከሆነች የምንናፍቀውን ብልጽግና በአጭር ጊዜ እውን ከማድረግ የሚከለክለን ምድራዊ ሀይል አይኖርም። ሰላማችንን በመጠበቅና ጽንፈኝነትን በጋራ በመከላከል የሀገራችንን ብልጽግና እውን እናድርግ!
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ከአማራ ክልል ጋር በተያያዘ 👆👆👆
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የቪዛ ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሪያን ማኪነርኒ ዛሬ ረፋዱ ላይ አግኝተው ድርጅቱ በኢትዮጵያ ባለው ሥራ ላይ ተወያይተዋል።
Prime Minister Abiy Ahmed met with VISA’s CEO, Ryan McInerney earlier this morning for a discussion on the work VISA is undertaking in #Ethiopia.
#PMOEthiopia
estifopp" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@estifopp