ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=
الشيخ عبد الودود مقبول حنيف
Читать полностью…أبو بكر الشاطري
نبرة مع الخشوع
"የመልክተኞቹ አለቃ የሆኑት ሰይዲ
ﷺ
ጥሪያቸው ከቁረይሽ፣ ከአይሁድ፣ ከክርስቲያኖች እና ከመናፍቃን "አዛ" (ጥቃት) አላመለጠም። ታዲያ ... የአሕሉ አስ–ሱናህ (የሰለፎች) ጥሪ ከጥቃት ነጻ እንዲሆን ትፈልጋላችሁን?!
በሱና (በነቢዩ ﷺ
መንገድ) ላይ ጸኑ፤ ትዕግስትም አድርጉ።"
— አሽ–ሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ ዑመር ባዝሞል
«ፈተናዎች(ችግሮች) የሚቆዩት ለተወሰነ ጊዜ ብቻ ነው፤ የሰው ልጆች ዕድሜ እንደሚጠናቀቅ ይጠናቀቃሉ።»
ስለዚህ በታጋሽነት ወደ አላህ ተጠጋ! 🌟
ኢብኑል ቀዪም /መዳሪጅ አስ–ሳሊኪን (374)
የተሰበሩ ቀልቦችን ጠግኑ፣ ለሰዎች ስሜት ግምት ይስጡ፣ ከመናገርዎ በፊት ቃላቶቻችሁን ጠንቅቀው ያዘጋጁ፣ በተግባራችሁ ርኅሩኅ ይሁኑ፣ የጋራ አኗኗራችሁን አስቡ፣ ማንንም አትጎዱ፣ ለሰዎች መልካም ቃል ተናገሩ፣ ንጹህና ገርነት ያለው ሕይወት ኑሩ፤ ይህ የነቢያት መንገድ፣ የታላለቆች አኽላቅ ነውና።" 🌸🌺
Читать полностью…أراد الله بعبده خيرًا يسّر لسانه للصلاة على محمد ﷺ.
ابن الجوزي
اللهم صلِّ وسلِّم وبارك على نبينا مُحمّد.🌿
ዒባዳዎች ከባድ አልነበሩም፤
በወንጀሎች የተነሳ ልቦቻችን ተበላሽተዉ እንጂ…
እስቲግፋር እናብዛ...🥀
ከሠለፎቹ መካከል አንዱ አንዲህ ብለዋል፦
«ሰዎች በነገስታት ደጅ ልቅናን ይፈልጋሉ ፥ ነገርግን አላህን በመታዘዝ ውስጥ እንጂ አያገኙትም።»
إغاثة اللهفان (1/٧٨)
«ሙስሊም ሆኜ ግደለኝ፡፡ በመልካቹም አስጠጋኝ።»
📚ዩሱፍ (101)
/channel/sultan_54
አል-ጁነይድ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለዋል፡-
«የመልእክተኛውን ﷺ ፈለግ ከተከተሉ፣ ሱናቸውን እና የሳቸውን ጎዳና አጥብቀው ከያዙ በቀር ሁሉም መንገዶች በፍጡራኑ ላይ የተዘጉ ናቸው።»
ኢብን ረጀብ ረሂመሁሏህ እንዲህ ይላሉ:**
"የሌሊትን ሰሏት መቆም ኃጢአቶችን የሚያስተሰርይ ሲሆን፣ በተጨማሪም የመልካም ምንዳዎች ደረጃዎችን ከፍ ያደርጋል። ቀደም ብለን ከዚህ በፊት እንደጠቀስነው፣ ይህን የ"ለይለ ሰላት" የሚያዘወትሩ ሰዎች ምንም ምርመራ ሳይደረግላቸው ወደ ጀነት ከመጀመሪያ ገቢዎች ተርታ የሚመደቡ ናቸው።"
ከረመዿን በኋላ ቁርኣንን የተዉ ሰዎች እና መፍትሄው
Читать полностью…የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«የጁምዓ ሰላት ገላውን ታጥቦ በጊዜ ወደ ጁምዓ የሄደ፤ ከዚያ በኃላ በሰዎች መካከል ሳይለያይ አላህ የወሰነለትን የሰገደ፤ በዕለቱና በሚቀጥለው ጁምዓ መካከል የሚፈፅመው ኃጢዓቶች ይሰረዝለታል።»
(ቡኻሪ ዘግበዉታል)
የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
"አላህ በዚህ ቁርኣን ሰዎችን ከፍ ያደርጋል። ሌሎችን ደግሞ በርሱ ያዋርዳል።”
/channel/sultan_54
ከታዋቂ የአገር ሽማግሌዎችና ምሁራን አንዱ የነበሩት ሀጂ ደርባቸው መሐመድ ዛሬ ከጁምዓ ሰላት በፊት ወደ አኼራ ሄደዋል።
አላህ ይዘንላቸው፤ ስራቸውን ይቀበላቸው ወንጀላቸውንም ይማራቸው። የቀብር ስነስርዓቱ በአላህ ፈቃድ ዛሬ አስር ላይ በኮልፌ መካነ መቃብር የሚፈፀም ይሆናል።
አል ዓፊያ አ/ማ የቦርድ ሰብሳቢ ለሆኑት ልጃቸው ሸይኽ አዩብ ደርባቸው፣ ለመላው ቤተሰባቸውና ወዳጆቻቸው ሁሉ መፅናናትን ይመኛል።
ረሒመሁላሁ ረህመተን ዋሲዓህ
وفاة الحاج درباتشو محمد والد استاذ أيوب رحمه الله اليوم قبل الجمعة والدفن وقت العصر إن شاء الله.
رحمه الله رحمة واسعة
إنا لله وإنا اليه راجعون
ቃዲ ሹረይህ እንዲህ ይላሉ፦፡-
«ፊትናዎች በመጡ ጊዜ አትጠይቁ፣ አታውሩም!»
ምንጭ፦ _ሲያር አዕላም ነብላእ
ማለትም ስለእርሷ መረጃ አትጠይቁ፤ ስለ ፊትናው መረጃ ካላችሁም ለማንም አትንገሩ፣ ፊትናውን በማራገብ ወይም በማስፋፋትም አትሳተፉ።
በዚህ ዘመን ይህ ምክር ምንኛ አስፈላጊ ነው!?
አሏህ ሆይ ከይፋም ሆነ ከተደበቀውም! ከክፉ ፊትናዎች ጠብቀን።
በማህበራዊ ሚዲያ ዘመን ይህ ምክር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው። ያልተረጋገጠ መረጃ ማራመድ ህብረተሰቡን ሊያደናግር ብሎም ግዜውን ያላግባብ ሊያባክን ስለሚችል፣ ይህን የሰለፎችን ንግግር ከግምት ማስገባት አስፈላጊ ነው።
ኢስላማዊ የልጆች አስተዳደግ ዋና ዋና መርሆች**
ኢስላም ለልጆች አስተዳደግ ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥ ሃይማኖት ነው። በቁርአን እና በሐዲስ መሠረት፣ ልጆችን በአላህ ፍራቻ፣ በአኽላቅ፣ እና በጥበብ ማዳበር ይገባል። ከኢስላማዊ ተርቢያ ዋናዎቹ መርሆች መካከል፦
### 1.ስለ ተውሒድ (አላህን ብቻ መገዛት) ማስተማር
- በመጀመሪያ ልጆችን ስለ አላህ ብቸኛ ተመላኪነት (ተውሒድ) አስተምሩ።
- "ልጅህ አፍ መፍታት ሲጀምር ለእሱ 'ላ ኢላሀ ኢላ አላህ' (ከአላህ በቀር ሌላ አምላክ የለም) የሚለውን ቃል ደጋግመህ አሰተምር።"
- በተፈጥሮ ውስጥ የአላህን ምህረት፣ እና በፍጥረታት ውስጥ የአላህን መነሩን የሚጠቁሙ ምልክቶችን ያሳዩኣቸው።
### 2. የነቢዩ (ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም) ምሳሌ መከተል
- ነቢዩ ሙሐመድ (ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም) ለልጆች የሚያሳዩትን ፍቅር፣ ርኅሩኅነት እና ትምህርት ይከተሉ።
### 3. የስነ ምግባር እሴቶችን ማስተማር
- እውነትን መናገር፣ አክብሮት፣ ምሕረት፣ እና ፍትሕ እንዲያውቁ ያድርጉ።
- "እውነትን ተናገሩ፣ ምንም እንኳን ከራስዎ ጋር ቢሆንም።" (ቡኻሪ ሀዲስ)
- ሀራም ነገሮችን እና ድንጋጌዎችን (ሀላል እና ሀራም) አስረዱኣቸው።
---
### 4. የሰላት እና የቁርአን ትምህርት
- ልጆችን ከህፃንነታቸው ጀምሮ ሰላት፣ ዚክር፣ እና ቁርአን አስተምሩኣቸው።
- "ልጆቻችሁን ሰላትን በሰባት ዓመት ያስተምሩ።" (ሀዲስ)
- ቁርአንን በማንበብ እና ትርጉሙን በማወቅ እንዲያድጉ ያግዙኣቸው።
### 5. ፍቅር እና ቅጣት መለያየት
- ፍቅርን አሳዩ፣ ነገር ግን ስህተት ሲፈፅሙ በጥበብ የሚማሩባቸው ቅጣት ይስጡ።
---
### 6. የቤተሰብ ግንኙነትን ማጠናከር
- ከልጆች ጋር ጊዜ ያሳልፉ፣ የታላለቅ ስብእናዎችን ታሪኮችን ይንገሯቸው፣ በቤተሰብ ውስጥ የሰላም አካባቢ ይፍጠሩ።
- "እናንተ አማኞች ሆይ! ነፍሶቻችሁን እና ቤተሰቦቻችሁን ከእሳት አድኑ።" (አትሕሪም:6)
### 7. ኢስላማዊ ትምህርት በጥበብ ማዳበር።
- ልጆችን በሥነ-ምግባራዊ ትምህርት ያንፁ።
- "ዕውቀትን መፈለግ በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው።" (ሀዲስ)
### 8. የልጅን መብት ማክበር
- ልጆች የሚገባቸውን **ፍትሕ፣ አክብሮት፣ይስጡ።
“አላህ ለባሪያው መልካምን በሻ ጊዜ ፣ አንደበቱን በነቢዩ አለይሂ ሰሏት ወሰላም በማውረድ ላይ ያገረዋል።”
(ኢብኑል ጀውዚ)
ሰለዋት እናብዛ ጁምዓም አይደል?!
خشوع وبكاء شديد للشيخ الشربم
Читать полностью…«ዱዓእን ያዘወተረ፣ የንጉሱን በር ማንኳኳትን ሙጥኝ ያለ... ለእርሱ ይከፈትለታል!»
አቡደርዳእ/ሲየሩ አዕላሚ ኑበላእ
➪ስራህን በአግባቡ ሳትሰራ ቀርተህ አለቃህ ለብቻህ እፈልግሃለሁ ሲልህ ምን ያህል ያስፈራል፣ያስደነግጣል! አይደል?!
☞︎︎︎የአለቃዎች አለቃ ረቡል ዓለሚን ዘንድ የቂያማ ዕለት ለብቻህ ሲያናግርህስ…
𝐓𝐞:http://t.me/sultan_54
وكُلُّهُمْ آتِيهِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ فَرْدًا
"ሁሉም፤ በትንሣኤ ቀን ለየብቻ ኾነዉ ወደርሱ መጪዎች ናቸዉ"
【መርየም፤95】
ጌታችን ሆይ!
እዘንልን፣ወንጀላችንን ደብቅልን፣ይቅርታም አድርግልን።
ዩሱፍም ወንድሞቹ( እርሱ ቢሰርቅም ከዚህ በፊት ወንድሙም ሰርቆ ነበር) ባሉ ጊዜ በውስጡ ዋጥ አድርጎ ያዘ ቅጥፈታቸውን ይፋ አላደረገም(አልተጋፈጣቸውም)**
(ዩሱፍ :77)
በእርግጥም! አንዳንዴ መወቃቀሰ ልቦችን ያጠራል፣ ቁስሎችን ያፅዳል፣ ቁስል ከመሰፋትዎ በፊት ፍቱን ፈውስ ነው።
ግን ሁሉም ሁኔታዎች ለመወቃቀስ የማይመቹ ሊሆኑ ይችላሉ።
አንዳንዴ ሁሉን ነገር ብትረዳም እንዳልተረዳህ በመምሰል ማሳለፍ አለብህ!
ሁሉን ነገር ባየህም ጊዜ እንዳላየህ ሆነህ ማለፍ አለብህ!
አፍታዊ ሽንፈት ቢመስለህም እንኳ!
አንዳንዴ አውቆ እንዳላወቀ ማለፍን ተለማምድ።
የታላላቅ ስብእና ባለቤት፤ አጋጣሚውን ሁሉ ተጠቅሞ ሰዎችን ልክልካቸውን ከመናገር ይልቅ ሰዎችን ማግባባት የተሻለ መሆኑን ይገነዘባሉ።
ዩሱፍ ዐለይሂ ሰላም በውስጣቸው ያለውን ቅሬታ አምቀው ይዘው፤ ልክልካቸውን በመናገር እውነታውን አላፍረጠረጡትም፣ ምክንያቱም አውቆ ማለፍ ከትላልቅ ስብእናዎች አንዱ ስለሆነ ነው!
ኢማም አህመድ እንዲህ ይሉ ነበር፡
"ከሰዎች ጋር ጤናማ መስተጋብር ለመመስረት ዘጠኝ አስርተኛ በመተላለፍ ውስጥ ነው።"
ኢማም ሻፊዒ ደግሞ፡ "ብልሃተኛው ጠቢብ ምንም እንኳ የተረዳ ቢመስልም የሚተላለፍ ነው።" ይላሉ።
አክሠም ኢብን ሰይፊ እንዲህ ይላሉ፦"አንድ ሰው ከሰዎች ጋር ባለው አኗኗር ጠበቅበቅ ያለ፣ ከሰዎች በፍጥነት ይለያያል፣ ፈታ ያለ ሰው ግን ከሰዎች ጋር ይቀራረባል፣ ደስታም በመተላለፍ ውስጥ ነው።"
ኢብኑ አል ቀዪም እንዲህ ይላሉ፡ "ከኩሩ(ከላቁ) ባህሪያት አንዱ የሰዎችን ጥፋቶች መተላለፍ ነው!"
📕- አድሃም ሸርቃዊ || ረሳኢሉን ሚነል ቁርኣን 🤍🤍
🔖"…ሸዋል ስምንተኛው ቀን የአብራሮችም(የጥሩዎች) ሆነ የፋጂሮች(የጠማማዎች) በዓል አይደለም።ይህንኑ ቀን በዓል ነው ብሎ ማንም ሊያስበው አይገባም። ከዲን መገለጫዎች አንዱንም ቢሆን በዚሁ ቀን መተግበር አይገባም።"
📚【ኢኽቲያራት አልፊቂሂያ ሊኢብኑ ተይሚያ ገፅ :199】
/channel/sultan_54
«ሱን'ና ብቸኛው መዳኛ‼» (السنة سفينة النوح) በሚል ርዕስ ኡስታዝ ሱልጧን ኸድር ትናንት በአዳማ ከተማ ዑመር መስጅድ ያደረገው መሳጭ ሙሐደራ!
ብታዳምጡትና ለሌሎችም ብታሰራጩት መልካም ነው። በጣም ደስ የሚል ሙሐደራ ነበር።
ነሲሓ የዒልም ቅፍለት: ቁጥር ④
||
t.me/MuradTadesse
🔴 የዛሬው የጁምዓ ኹጥባ
🎙 خطبة الجمعة
الحفاظ على الحسنات
❗️መልካም ስራችን እንዳይበላሽ
🕌 ጎተራ ሼል ዲፖ (54) ፈትሕ መስጂድ
🗓 ሸዋል 6/1446 አ/ሂ
http://t.me/sultan_54
{አላህ ከዚያ በኋላ(ከፍቺ በኋላ) አዲስና የማይታወቅ ነገር ሊከስት ይችላል…}😍❤️
( ሱረቱ አጥ_ጠላቅ:1)
ሰው በእጅጉ በተጨነቀ ጊዜ ከእርሱ መውጫ የለም ብሎ ያስባል። ነገር ግን አላህ ከሱ ምህረቱን( ፈረጃውን) ያመጣል። እንደ "ሃጀር" በሠፏ እና መርዋ መካከል ጥቂት ውሃን ለማግኘት ብላ እዚህም እዚያም ተጨንቃ በሀይል የምትሮጥ ሴት ልጅዋ ኢስማዒል እግር ሥር የዘምዘም ውሃ እንደሚፈነዳ ማን ያስብ ነበር? ይህ ውሃ ለእርሷና ለልጇ ብቻ ሳይሆን እስከ ቂያማ እለት ድረስ የሚመጡ ሕዝቦች የሚጠጡት።
እንደዚሁ አላህ ሁኔታዎች በአንድ የዓይን ብሌን ብልጭታ ነገሮችን ሊቀያይር ይችላል። ችግር ረጅም ጊዜ አይቆይም።
ኢብኑ ቀዪም እንደተናገሩት፡ “ሁላችንም ከባድ የመከራ ጊዜዎችን አሳልፈናል። እነሱም ዛሬ ላይ ተረስተው ትውስታ ብቻ ሆነው ቀርተዋል።”
ስለዚህም ተስፋ አትቁረጥ፤ በጌታህ ላይ ተማመን። ችግር ያልፋል ብሎ በትአግስት መጠበቅ ላቅ ካሉ ዒባዳዎች አንዱ ነውና።
📕- አድሃም ሸርቃዊ || ረሳኢሉን ሚነል ቁርኣን 🤍🤍
ጥያቄ፦
አልሀምዱሊላህ ረመዳንን በጥሩ ነበር ያላለፍኩት በተለይ የመጨረሻ 10 ቀኖችን አሁን ግን ከኢድ ቡሆላ በጣም ደካማ ሆንኩኝ፣ እንቅልፍ ብቻ ሆኑኩ፣ ከረመዳን ቡሗላ ረመዳን የነበረውን ተነሳሽነት ያላስቀጠለ፣ ከዒባዳው ዝንጉ የሆነ ረመዳኑ ተቀባይነት እንዳላገኘ ያሳያል፣የሚባል ነገር ሰምቼ ነበር ምን ማድረግ አለብኝ?
መልስ፦
ማንኛውም ሰው በዒባዳው ከጥረት እና ከተነሳሽነት በኋላ ድክመት እና መዘናጋት ቢያጋጥመው ተፈጥሮኣዊ ነው።
ልክ መልክተኛው ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዳሉት፣ *"ከማንኛውም የዒባዳ ጥረት እና ተነሳሽነት ጋር የሚገናኝ ዝንጉነት እና ድክመት አለ፤ ከማንኛውም ከፍተኛ ተነሳሽነት በኋላ ድክመት (ፊትራ) ይከተላል። የትኛውም ሰው ጥንካሬው ወደ ሱናዬ ከሆነ፣ እርሱ ፀንቷል(ድኗል)፤ የትኛውም ሰው ግን ከፍተኛ ተነሳሽነቱ ወደ ሌላ ከሆነ፣ እርሱ ጠፍቷል(ለጥፋት ተዳርጓል)"* (ኢማሙ አሕመድ ዘግበውታል)። ግን አንድ ሰው በጣም መጠንቀቅ ያለበት ድክመቱ ወደ ግዴታዎች መተው እና ቸልተኛ፣ ነፍሱን በኃጢኣት በማርከስ፣ መጥፎ ነገሮችን ማድረግ አይገባውም።
ኢብኑ አልቀዪም ረሂመሁሏህ እንዲህ ብለዋል፦ *"በዒባዳ ለሚተጉ ሰዎች (አስ_ሳሊኪን) ከዒባዳ በኃላ የድክመት ጊዜያት የማይቀር ነው። የትኛውም ሰው ድክመቱ ወደ አላህ ቅርብ ለመሆን(ሚዛናዊነት) እና ሥራውን ለማስተካከል ከተመራ፣ ከግዴታ (ፈርድ) አስካልወጣ፣ ወደ እርም (ሐራም) አስካልገባ፣ ከቀድሞው ሁኔታው የተሻለ ሆኖ መመለሱ የሚጠበቅ ነው።"*
ዐሊይ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንዲህ ብለዋል፦ *"ነፍስ መንፈሳዊ ጥንካሬ ላይ ሆና ወደ አላህ መቃረብ (ዒባዳ የሚገራላት) ጊዜ አላት፣ በአንፃሩም ከከፍተኛ ተነሳሽነት በኃላ ወደኃላ መጎተት ( መሳነፍ) ጊዜ አላት። በተነሳሽነቷ(በነሻጧዋ) ጊዜ፣ በቆራጥነት በተጨማሪ ዒባዳ ያዛት፤ በመዳከሟ ጊዜም፣ በግዴታዎች (ፈርዶች) እና በዋጅባት ሥራዎች ላይ ብቻ ገድባት።"*
አንድ ሙስሊም በነፍሱ ውስጥ መዳከም (ፉቱር) ወይም መሳነፍ ሲሰማው፣ ለነፍሲያው በመታዘዝ ዒባዳውን ሊያቋርጥ አይገባም። ይልቁንም በጥበብ እንዲሁ ራሱን ሊያከም ይገባዋል፤ ሐላል የሆኑ መዝናኛ ጨዋታዎች በመጠቀም ነፍሱን ሊያድስ ይገባል፤ ነገር ግን ዒባዳውን ሙሉ በሙሉ እንዳያቋርጥ ጥንቃቄ ያሻል። በተጨማሪም ሚዛን (ሚዛናዊነት) መጠበቅ አለበት፤ ይህም ሆኖ፣
1. አንድ ሙስሊም ነፍሱን በግድ በትእዛዝ ላይ በመጫን ዒባዳ እንድትጠላ እንዳያደርጋት።
2. የነፍሱንም ልጓም ፈቶ ሲያበቃ፣ በመዝናኛ እና በኃጢአት ባሕር ውስጥ ያለ ምንም ቁጥጥር እንዳትዋኝ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት።
ያም ሆነ ይህ እምነታዊ ጉዞ ላይ ያለ ሰው በድክመት ወቅቱ በፅናት ከነፍሱ ጋር ሊታገል ይገባል፣ በጥበብ እና በሚዛን መርህ መንገዱን እንዲቀጥል የሚያስችል እርምጃ መውሰድ አለበት ። በአንፃሩም፣ ከግዴታዎች መዘንጋት ወይም ወደ ኃጢአት ውስጥ መዋኘት እንዳይከሰት ትኩረት መስጠት አስፈላጊ ነው።
በማንኛውም ነገር ላይ በሚዛናዊነት ላይ አደራ!ካሰቡበት ግብ መድረስዎ አይቀርም።
/channel/sultan_54