ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=
ዘካተል ፊጥር በገንዘብ ሳይሆን
በእህል የሆነበት ጥበብ ምንድ ነው?
ሸይኽ ዐብዱሰላም በሚገርም ሁኔታ ይገልፁታል!
🔴 የዛሬው የጁምዓ ኹጥባ
🎙 خطبة الجمعة
ماذا بعد رمضان؟!
❗️ከረመዳን በኋላስ!
🕌 ቃሊቲ ቸራሊያ ሀምዛ ቁ/1 መስጂድ
🗓 ረመዷን 28/1446 አ/ሂ
http://t.me/sultan_54
በረመዳን መሰናበቻ ላይ…
።
አላህ ሥራውን የተቀበለው ማን እንደሆነ ባውቅ ብዬ ተመኘሁ፤ እንኳን ደስ ያለህ ብዬ ደስታዬን ልገልፅለት። ከእኛም መካከል እደለ–ቢስ የሆነውን እንድናፅናናው?!
እናንተ አላህ ሰራችሁን የተቀበላችሁ፣ እንኳን ደስ አላችሁ። እናንተ አላህ ስራችሁን የገፈተረባችሁ፣ አላህ በመከራችሁ ላይ ፅናቱን ይስጣችሁ
الوالد أوسط أبواب الجنة
አባት የጀነት ምርጡ እና በላጩ በር ነው።
ረሱል ﷺ
اللهم إنك عفو تحب العفو فاعف عنا
Читать полностью…👆👇👇ዓረብኛ ማንበብ የምንችል ይህን ዱዓ በዛሬው ለሊት ለምናደርገው ዱዓ ያግዘናል በተለይ ሱጁድ ላይ።
በትላልቅ ፎንተ የተዘጋጀ ከነቢዩ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም የተገኘ ዱዓ
“ለይለተል ቀድርን በመጨረሻ አስር የረመዳን ቀናቶች ውስጥ ፈልጓት።”
ረሱል
صلى الله عليه وسلم
"…ወራችሁ(ረመዳን) መጎደሉን ተያይዞታል።
እናንተ ደግሞ መልካም ስራችሁን ጨመርመር አድርጉ።"
(ኢብኑ ረጀብ/ለጣኢፉ አልመዓሪፍ /262)
ጾም ለፅናት ትልቁ ከሆኑ ሰበቦች አንዱ ነው። ጾም የሚያስደንቅ ተጽዕኖ አለው፤ ውጫዊ አካላትን (ሰውነት) እና የውስጥ ኃይሎችን (ነፍስ) በመጠበቅ ላይ። ጾም ልብን እና አካልን ጤናማ አድርጎ ይጠብቃል፤ ለመጥፎ ፍላጎቶችም (ለስሜት) እጅ የሰጠውን ሁሉ ያስመልሳል። ስለዚህ፣ ጾም በአላህ ፍራቻ ላይ ትልቁ የረዳት መንገዶች አንዱ ነው።
—ኢብን ቀዪም
"إذا وافقت ليلة الجمعة إحدى ليالي الوتر من العشر الأواخر فهي أحرى أن تكون ليلة القدر".
❤️ - نقله ابن رجب عن ابن هبيرة، في لطائف المعارف لابن رجب.
መስሩቅ (ረሂመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦
"አንድ ሰው በዕወቀቱ መደነቁ ለጅህልናው በቂው ነው፣
አላህን መፍራቱ ከዕውቀት በቂው ነው።"
【ሙሰነፍ ኢብኑ አቢ ሸይባ፤13/405】
የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
«የሰው ልጅ (በህይወት ሳለ) አንዲትም ሰዓት አላህን ባለማውሳት(ያለ ዚክር) በማለፏ የተነሳ የቂያማ ቀን ይጸጸታል።»
"ሰላት ተራዊሕ ወይም ተሀጁድ ላይ ለወላጆችህ ዱዓ ማድረግህ ፤ አሥር ግመሎችን አርደህ ሰደቃ ከማውጣት ይበልጣል።"
#ሸይኽ_ኡሰይሚን
ሱለይማን ኢብኑ ዐብዱል መሊክ አቡ ሓዚምን እንዲህ ሲሉ ጠየቋቸው፦
👉"ለምንድን ነው እኛ ሞትን የምንጠላው?”
አቡ ሓዚምም፦
“ምክንያቱም ዱንያችሁን ገንብታችሁ አኼራችሁን ስላበላሻችሁ፤ ከገነባችኃት ዱኒያ ወደ አፈራረሳችሁት ቦታ መሸጋገር ስለምትጠሉ ነው።"በማለት መለሱላቸው።
📚 【ታሪኽ አዲመሽቂይ ሊብኑ ዐሳኪር 20/22】
"…ወራችሁ(ረመዳን) መጎደሉን ተያይዞታል።
እናንተ ደግሞ መልካም ስራችሁን ጨመርመር አድርጉ።"
(ኢብኑ ረጀብ/ለጣኢፉ አልመዓሪፍ /262)
Te»/channel/sultan_54
اللهم ارزقنا الاخلاص في القول والعمل!
Читать полностью…📌የዒባዳ ትጥቅህን እንዳትፈታ…
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
“ለይለተል ቀድርን በመጨረሻ የረመዳን ሌሊት ላይ ፈልጓት።”
ረመዷን ጥሎን እየሄደ ነው ልናለቅስ ይገባል**
✍️ አል-ሓፊዝ ኢብን ረጀብ (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፡
«የጥንቁቆች(ሙተቂዎች) ልቦች ይህ ወር (ረመዷን) ሲሰናበታቸው ሀዘናቸው ይጎልበታሉ፤ ከርሱ መለያየት ህመም የተነሳ ያለቅሳሉ።»
📘 [«ላጣኢፍ አል-መዓሪፍ» ገጽ (304)
✍️ እንዲሁም ብለዋል፡
«አማኙ በረመዳን መሄድ የተነሳ የሀዘን እንባ እንዴት አያፈስም? ዳግም ረመዷንን ለማግኘት ዕድሜው ምን ያህል እንደቀረው ስለማያውቅ!»
📘 [«ለጣኢፍ አል-መዓሪፍ» ገጽ(217)
ኢብኑል አልቀዪም እንዲህ ይላል፡-
«አላህ የሸይኽ ኢብኑ ተይሚያን ሩሕ ይቀድሰውና እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ፦
‹‹ሥራህ በልብህ ውስጥ ደስታ እና እርካታ የማያስከትል ከሆነ፣ በእርሱ ተጠራጠር። አላህ አመስጋኝ(ሸኩር) ነውና፤ (ማለትም) ለሠሪው በዚህ ዓለም በቀልቡ ውስጥ ደስታ፣ የልብ እረፍት እና የአይን እርካታ ሊሰጠው ይገባል። ይህን ያላገኘ ከሆነ፣ ሥራው ላይ የኢኽላስ ክፍተት እንዳለ ይወቅ! የተበላሸ (እምብዛም ተቀባይነት የሌለው) ነውና።›
يقول ابن القيم: وسمعت شيخ الإسلام ابن تيمية قدس الله روحه يقول:إذا لم تجد للعمل حلاوة في قلبك وانشراحا فاتهمه، فإن الرب تعالى شكور، يعني أنه لا بد أن يثيب العامل على عمله في الدنيا من حلاوة يجدها في قلبه وقوة انشراح وقرة عين، فحيث لم يجد ذلك فعمله مدخول .
ማሳሰቢያ⚠️⚠️**
⛔️ዛሬ ሌሊት 27ኛው ሌሊት ነው፤ እሷም ለይለቱ አልቀድር ፍተኛ ተስፋ የሚጣልባት ሌሊት ናት። ይህች ሌሊት፤
- ከመጨረሻዎቹ አስረት ቀናት ውስጥ ናት፣
- ከቀሩት ሰባት ጎደሎ ያልሆኑ (ተጨማሪ) ሌሊቶች ናት፣
- ዊትር ጎዶሎ ( ኢተጋማሽ) ሌሊት ናት፣
- ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም በዚህ ሌሊት ከፍተኛ ጥረት ያደርጉባት ነበር፣
- ቤተሰቦቻቸውን ሰብስበው ለይል ሰላት (ቂያም) በጀመዓ አሰግደደዋቸዋል፣
- ሰሓቦቻቸውን በጀመዓ አሰግደዋቸዋል፣ ያ
- ቂያማቸውን ከዒሻ ጀምሮ እስከ ፈጅር አቅራቢያ ያራዝሙት ነበር፣
- ከሰሓቦች እና ከሰለፎቹ ውስጥ በነዚህ ሌሊት ለይለተ አል ቀድር መሆኗን እንደማያጠራጥሩ ተገልጿል፣
- ከቀደምት ሊቃውንትም የተወሰኑት ይህች ለሊት በትክክል ለይለተ ቀድር እንደሆነች ገልጸዋል፣
- ሌሎቹ ደግሞ ዊትር ሌሊቶች (21፣23፣25፣27፣29) መካከል የምትገኝ ስትሆን በብዛት ለይለተ አል ቀድር በየዓመቱ እንደምትለዋወጥ ተናግረዋል፣ ነገር ግን በብዛት በ27ኛው ሌሊት እንደምትከሰት ጠቅሰዋል፣
- ማስረጃዎቹም ሲሰባሰቡ ይህን አቋም ይደግፋሉ።
እደለ–ቢስ ሰውማ እሷን (ለይለተል ቀድር) ያጣ ነው!
📚የሸይኽ ሱለይማን አር-ሩሀይሊ (አላህ ይጠብቃቸውና)
ከትዊትር ገፃቸው ከለቀቁት ወደ አማርኛ የተተረጎመ ።
አልኢማም ኢብኑልቀይም ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡-
“ለይለተልቀድር በአመት ውስጥ የምትገኝ አንዲት ቀን ብትሆን
እሷን ለማገኘት ስል አመቱን ሁሉ እቆም ነበር፡፡ በ(ረመዳን) አስር
ለሊቶች ውስጥ ከሆነችማ ምን ነካህ? (እንዴት እዘናጋለሁ?!)” [በዳኢዑልፈዋኢድ፡ 1/55
🔴 የዛሬው የጁምዓ ኹጥባ
🎙 خطبة الجمعة
فضل العشر الأواخر وليلة القدر
❗️ አስርቱ የመጨረሻ ቀናት
እና ለይለቱል ቀድር
🕌 ቃሊቲ ቸራሊያ ሀምዛ ቁ/1 መስጂድ
🗓 ረመዷን 21/1446 አ/ሂ
http://t.me/sultan_54
ሑዘይፋ ኢብኑል‐የማን [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንዲህ ይላሉ: ‐
«ወደፊት እንደሰጠመ ሰው ዱዓ ከሚያደርግ ሰው በስተቀር ማንም የማይድንበት ዘመን በሰዎች ይመጣል!»
🔴 የዛሬዋ ለሊት ለይለተል ቀድር በጣም የሚከጀልባት ለሊት ናት!
"ጁምዓ ሌሊት ከረመዳን የመጨረሻው አስርት ቀናት ጎዶሎ ቁጥር ያላቸው ሌሊቶች (21፣ 23፣ 25፣ 27፣ 29) ጋር ብትገጥም፣ እርሷ ለይለቱል ቀድር ለመሆን ይበልጠ የቀረበች ናት።"**" ❤️
— ኢብን ሩጀብ ኢብን ሁበይራን ጠቅሰው "ለጣኢፍ አልማዓሪፍ" በተሰኘው ኪታባቸው ውስጥ ጠቅሰውታል።
ዐሽር አል ኣዋከኺር መች ነው የሚጀምረው?
ረመዳን ሀያኛው ቀን ፀሐይ ከጠለቀችበት ሰአት (ከመግሪብ) አንስቶ ዐሽር አል ኣዋኺር ይጀምራል።
✍ ሸይኽ ዑሠይሚን
📚 (መጅሙዕ አልፈታዋ (20/170
/channel/sultan_54
የምዕመናን እናት ዓኢሻ (ረዲየላዑ ዓንሀ) እንዲህ ትላለች፦
‹‹የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ከረመዳን የመጨረሻዎቹ አስርት ከሌላ ጊዜ በተለየ መልኩ (በዒባዳ) ላይ ይተጉ ነበር››
📚ሙስሊም ዘግበውታል
"ፈረሶች በውድድር ላይ ሳሉ መጨረሻ ሲቀራርቡ ድልን ለማስመዝገብ ከፍተኛ ጥረት ያደርጋሉ። ስለዚህ፣ ፈረሶች ከአንተ የበለጠ ብልህ አይሁኑ! ሥራዎች በመጨረሻዎቻቸው ነው የሚገመገሙት።"
- ኢብን አልጃውዚ
🔸ተራዊሕ ላይ ስንት እና ስንት ወጣቶች ሲልፈሰፈሱ በእድሜያቸው የገፉ አባቶች ጥንካሬና ብርታት ስታይ....
ጉዳዩ የቀልብ እንጂ የቁዋ(ጉልበት) አለመሆኑ ትገነዘባለህ!!
Te»http://t.me/sultan_54
القارئ الشيخ أبو بكر الشاطري
Читать полностью…ያረብ ከፆሙት እንጂ ከተራቡት አታደርገን🤲
Читать полностью…