sultan_54 | Unsorted

Telegram-канал sultan_54 - የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

14074

ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=

Subscribe to a channel

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

📌ዙልሒጃ ቀን 09 (የዐረፋ ቀን)፦
> የዒድ ቀን ምንኛ ታላቅ ቀን ነው! ያ ቀን አላህን ወደማየት ቀን ያሻግረናል። አላህ መጋረጃውን ገልጦ፦ "ባሪያዎቼ ሆይ! ተመልከቱኝ" ይላል። አላህን ከመመልከት የበለጠ ያማረ ምንም ዓይነት ጸጋ የለም። አምላካችን ሆይ! እኛንም ከእነርሱ ወገን አድርገን! 🤲 رَبَّنَا تَقَبَّلْ مِنَّا #ዒድ_ሙባረክ #ዐረፋ

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

ዙልሒጃ 8(የውሙ ተርዊያህ)
ከሚና ጥሪው(ተልቢያው) ይጀምራል፣
በአረፋም እለት ዱዓዎች ወደ ላይ ይውጣሉ፣
በመቀጠል በሰከነ መንፈስ ወደ ሙዝደሊፋ፣
በጀመራትም የኢማን እርምጃዎች ይፈጸማሉ..
የሐጅ ትዕይንቶች በቅዱሳን ቦታዎች መካከል መዘዋወር ብቻ አይደሉም፤ ይልቁንም የልብ ወደ አላህ የመጓዝ ጉዞ እንጂ።
#ሐጅ
#ሐጅ_1447ዓ_ሂ

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

የአእምሮና የሃሳብ ጥንካሬ የሚገለጠው መርህን ግልጽ በማድረግና ማንነትን ጠብቆ በማስረዳት ላይ እንጂ፣ የሰሚዎችን ስሜት ለመከተልና የአስተሳሰብ ግጭትን ለመሸሽ ሲሉ በማንነት ውስጥ መለዘብ አይደለም።

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

📌ዙልሒጃ ቀን 08፦
> ከወንጀላቸውም ልክ እናታቸው እንደወለደቻቸው ቀን ሆነው ይነጻሉ! ሑጃጆቹ ሙሉ ስነ-ሥርዓቱን በደስታ ያጠናቅቃሉ፤ ፊታቸው በብርሃን ይፈካል፣ ልቦናቸው በደስታ ይሞላል። አላህ የሁሉንም ሐጅና ዱዓእ ተቀብሎ ከእሳት ነፃ ከሆኑት ያድርገን። 🕋 ሰፊ በረከቱ በሁላችንም ላይ ይውረድ። #ሐጅ #ዙልሒጃ

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

ዐላመቱ ኢብኑ ባዝ ረሂመሁላህ
### ጥያቄ (ከአድማጭ)፦
> "ጥያቄ አቅራቢው እንዲህ ይላል፦ 'እኔ መልካም ነገርን የምትወድ ነፍስ አለችኝ፤ ነገር ግን ደካማ ናት፣ ከወንጀልና ከጥፋት ፊት መቆም አትችልም። ወንጀልን ባየሁ ቁጥር ከፊቱ እደክማለሁ። ታዲያ ለዚህ የሚሆን፣ የሚመሩኝ መድኃኒት ወይም ፈውስ አለን?'"
>
### የሸይኽ ኢብን ባዝ ምላሽ፦
"አዎ! አላህ (ሱብሐነሁ ወተዓላ) *'ሰውም ደካማ ሆኖ ተፈጠረ'* ብሏል። ነገር ግን እንድትጠነክር አላህ መሣሪያዎችን ሰጥቶሃል።
ልብህ በእነርሱ እንዲጠነክር ያደረገልህን መሣሪያዎች ሰጥቶሃል፤ እነርሱም፦
* አላህን መታዘዝ፣ * ዚክርን (እርሱን ማውሳትን) ማብዛት፣ * በእርሱ ታላቅነት ላይ ማስተንተን እና በአንተ ላይ ስላለው መብት ማሰብ ናቸው።
አንተ ወደ እርሱ ተመላሽ መሆንህን፣ ተጠያቂ መሆንህንም አስብ፤ *'በጌታህ እምላለሁ! ከሚሠሩት ነገር በሙሉ በእርግጥ እንጠይቃቸዋለን'* ተብሏል።
አንተ በጥፋቶችህ ምክንያት ቅጣት የሚገባህ መሆንህን፣ በታዛዥነትህ ደግሞ ምንዳ (አጅር) የምታገኝ መሆንህን አስብ። ስለዚህ (ነፍስህን) አስታውሳት፤ ስሜትንም አትከተል፤ ከአላህ መንገድ ያሳስትሃልና። ነፍስ በአላህ እዝነት ካልተጠበቀች በስተቀር ሁልጊዜም ወደ መጥፎ ነገር አዛዥ መሆንዋን እወቅ። ስለዚህ ለስሜቷ አትታዘዝላት።
አላህ እንዲህ ብሏል፦
> *'ያ በጌታው ፊት መቆምን የፈራ፣ ነፍሱንም ከክፉ ስሜቷ የከለከለ፤ በእርግጥ ጀነት እርሷ መጠጊያው(መኖሪያወ) ናት።'*
>
ስለዚህ ነፍስህ ወደ ወንጀል ስትጠራህ፦ ነገሩ ከባድ መሆኑን፣ አላህ ከወንጀል መከልከሉን፣ በአላህ ቁጣና ቅጣት የተዛተበት መሆኑን አስታውሳት፤ (አላህ ካልማረው በስተቀር)። አንተ ደግሞ በዚያው ወንጀል ላይ እያለህ ልትሞት ትችል እንደሆነ፣ ይቅርታ ይደረግልህ ወይም ትቀጣ እንደሆነ አታውቅም።
ስለዚህ ታገላት፣ አስታውሳት፣ ነገሮችን አቅልሎ ከመመልከት (ቸልተኝነት) ተጠንቀቅ። በዚህ ላይ ከተሳካልህ አላህ ያግዝሃል፤ ከዚህችም ነፍስ ክፋት ትድናለህ።"

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

📌 ዙልሒጃ ቀን 07፦
> በዐረፋ ምሽት ላይ ከሰዎች ሁሉ የከፋው ሰው ማን እንደሆነ ያውቃሉ? ታላቁ ዓሊም ሱፍያን አስ-ሰውሪይ በጉልበታቸው ተንበርክከው ሲያለቅሱ "ከዚህ ስብስብ የከፋው ማነው?" ተብለወወ ሲጠየቅኘቁ፦ "አላህ አይምረኝም ብሎ የሚያስበው ሰው ነው" ሲል መለሱ። በአላህ ላይ መልካም ጥርጣሬ ይኑረን! 💫 #ዐረፋ #ተስፋ #የአላህ_እዝነት

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

📌 ዙልሒጃ ቀን 06፦
> በዐረፋ ቀን ከአላህ እዝነት ተስፋ እንዳትቆርጥ አደራ! በአንተ ላይ እንደ አሸዋ ቁጥር፣ እንደ ሰማይ ዝናብ ጠብታ ወይም እንደ ዱንያ ቀናት ብዛት ያህል ወንጀል ቢኖርብህ እንኳ አላህ ይምርሃል። አላህም መላእክቱን፦ "ምስክር ሁኑኝ፤ እኔ ወንጀላቸውን በሙሉ ምሬአቸዋለሁ" ይላቸዋል። 🌧️✨ #ምሕረት #የዐረፋ_ቀን

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

## የዒልም መብት ከዓሊም መብት ይቀድማል!
* **ከአላህ ዘንድ የወረደውን መከተልና ከእሱ ውጭ ያሉትን አለመከተል ግዴታ ነው።
** ማንኛውም ዓሊም  ለእኛ ተወዳጅ ቢሆንም፣ እውነት ግን ከእሱ የበለጠ ለእኛ የተወደደች መሆን አለባት።
*የአንድ ዓሊም ትልቅ ደረጃና ክብር እሱን ለማመካኛነትና ስህተቱን ለማረም የሚጠቅም እንጂ፣ የሰራውን ስህተት ትክክል ነው ለማለት ማስረጃ ሊሆን አይችልም።
  እውነት ከተናጋሪው ማንነት ሳይሆን ከራሱ ከንግግሩ ተነስተን የምንቀበለው ነው፤ ውሸትም (ባጢል) በተመሳሳይ መልኩ ተናጋሪው ማንም ይሁን ማን ውድቅ የሚደረግ ነው። እውነቱን የተናገረው ወይም ውሸቱን ያወራው ሰው ያለው ማዕረግ የእውነትን ወይም የውሸትን ምንነት አይቀይረውም።

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

📌ዙልሒጃ ቀን 05፦
> "እነዚህ ባሪያዎቼ አቧራ ለብሰው፣ ፀሐይ እየመታቸው ወደእኔ መጡ።" ጌታ ሆይ! ዛሬ ያንተን ውዴታ፣ ችሮታና እዝነት እንጂ ሌላ ምንም አልፈለጉም። ዛሬ በአንድ የውዴታ እይታ እንድትመለከታቸውና ዳግመኛ የማትቆጣበትን ውዴታ እንድትለግሳቸው ብቻ ነው የፈለጉት። 🤲❤️ #የዙልሒጃ_አስር_ቀናት #ዱዓእ

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

📌 ዙልሒጃ ቀን 04፦
> በነጭ አልባሳት ተጎናጽፈው፣ አቧራ ለብሰው የቆሙ የዐረፋ ሜዳ ላይ ያሉ ባሪያዎች! አላህ ይህንን አቧራ መልበሳቸውንና ወደእርሱ መተናነሳቸውን ይወደዋል። አላህ መላእክቶቹን፦ "መላእክቶቼ ሆይ! እነዚህን ባሪያዎቼን ተመልከቱ! እነዚህ እኮ የማንም ተገዢ አይደሉም፣ የእኔው ባሪያዎች ናቸው" ይላቸዋል። 🕋✨ #የሐጅ_መንፈስ #ዐረፋ

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

በቃዲ ዐብዱልጀባር አል-ሙዕተዚሊ እና በአቡ ኢስሃቅ አል-ኢስፈራዪኒ መካከል በቀደር ዙሪያ የተደረገ ክርክር
​የሙዕተዚላህ መሪዎች አንዱ የሆነው ቃዲ ዐብዱልጀባር አል-ሀመዳኒ፣ ሳሒብ ኢብኑ ዐባድ ዘንድ ገባ። እዚያም የአህሉ-ሱናህ መሪ ከሆኑትና "አል-ኡስታዝ" ተብለው ከሚጠሩት አቡ ኢስሃቅ አል-ኢስፈራዪኒ ጋር ተገናኙ። ቃዲ ዐብዱልጀባር ኡስታዝ አል-ኢስፈራዪኒን ባየው ጊዜ (የራሱን የሙዕተዚላህ እምነት ለማንጸባረቅ ፈልጎ) እንዲህ አለ፦

"ከመጥፎና ጸያፍ ነገር ሁሉ የጠራው (አላህ) ጥራት ይገባው።"

(ማለትም፦ አላህ መጥፎ ነገሮች እንዲከሰቱ ፈቃድ ከመስጠት የጠራ ነው፤ መጥፎ ነገር በአላህ ፍቃድና ውሳኔ አይከሰትም ማለቱ ነበር።)
​ኡስታዝ አል-ኢስፈራዪኒም ወዲያውኑ (የአህሉ-ሱናህን እምነት በማረጋገጥ) እንዲህ ሲል መለሰለት፦
"በግዛቱ ውስጥ እርሱ ከሻው (ከፈቀደው) ውጭ ምንም ነገር የማይከሰተው አምላክ ጥራት ይገባው።"

​ቃዲ ዐብዱልጀባርም ጠየቀ፦ "ለመሆኑ ጌታችን ሊያምጹት (ሊያምፁበት) ይሻልን?"
​ኡስታዝ አል-ኢስፈራዪኒም መለሰ፦ "ለመሆኑ ጌታችን በግዴታና በኃይል (ያለ እርሱ ፍቃድ) ይታመጻልን?" (ማለትም፦ በፈጠረው ዓለም ላይ በእርሱ ቁጥጥርና ፍቃድ ስር ያልሆነ ነገር በግዴታ ይከሰታልን?)
​ቃዲ ዐብዱልጀባርም (ሊሞግተው በመፈለግ) እንዲህ አለ፦ "እስኪ ንገረኝ! ቅኑን መንገድ (ሂዳያን) ቢከለክለኝ፣ በጥፋትና በክህደት ላይ ከወሰነብኝ፤ መልካም አደረገልኝ ወይስ በደለኝ?"
​አል-ኢስፈራዪኒም እንዲህ ሲል መለሰለት፦ "የከለከለህ ያንተ የሆነውን መብትህን ከሆነማ በድሎሃል። ነገር ግን የከለከለህ የእርሱ የሆነውን (ችሮታውን) ከሆነ፣ እርሱ እዝነቱን ለሻው ሰው ይመርጣል።"
​በዚህ ጊዜ ቃዲ አብዱልጀባር የሚመልሰው አጥቶ አፉ ተለጎመ (ተረታ)። ይሁን እንጂ እስከወዲያኛው በሙዕተዚላህ እምነቱ ላይ ጸንቶ ቀጠለ፣ መልስም መስጠት አልቻለም።

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

📌 ዙልሒጃ ቀን 03፦
> "ጌታዬ ሆይ! አረጀሁ እኮ፤ ስለዚህ ከእሳት ነፃ አውጣኝ!" — አቡ ዑበይዳህ አል-ኸዋስ በዐረፋ ቀን ላይ ዕድሜያቸው ገፍቶ ፂማቸው በፈካ ጊዜ ፂማቸውን ይዘው አላህ ፊት ይንበረከኩ ነበር። ባሪያዎች ሲያረጁ ጌቶቻቸው(አሳዳሪዎቻቸው) በነፃ እንደሚለቋቸው ሁሉ፣ አላህም በእርጅናቸው ከእሳት እንዲጠብቃቸው ይማጸኑ ነበር። 🕊️ #የአላህ_እዝነት #ዙልሒጃ
>

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

📌ዙልሒጃ ቀን 02፦
> የአላህ ቅን ባሪያዎች አላህ ፊት ያላቸው መተናነስ ድንቅ ነው። ታላቁ ዓሊም ሙጠሪፍ ኢብኑ ዐብዲላህ በዐረፋ መድረክ ላይ ቆመው፦ "አምላኬ ሆይ! በእኔ ወንጀል ምክንያት የዚህን ሁሉ ሁጃጅ ዱዓእ እንዳትመልስባቸው!" እያሉ ያለቅሱ ነበር። ራሳችንን ዝቅ አድርገን ምሕረትን የምንለምንበት ወቅት ይሁንልን። 🌙 #ዙልሒጃ #ኢስላማዊ_ማስታወሻ

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

### በጊዜ ያልተገደበ (ሙጥለቅ) እና በጊዜ የተገደበ (ሙቀየድ) ተክቢራ
1  አት-ተክቢር አል-ሙጥለቅ (በጊዜ ያልተገደበ)፦ በማንኛውም ሰዓትና ጊዜ የሚባል፣ በአንድ የተወሰነ ወቅት ወይም ከፈርድ ሶላት ማግስት ብቻ የማይገደብ ተክቢራ ነው።
* አት-ተክቢር አል-ሙቀየድ (በጊዜ የተገደበ)፦ ከአምስቱ ግዴታ (ፈርድ) ሶላቶች  (ከማሰላመት በኋላ) ብቻ ተያይዞ የሚባል ተክቢራ ነው።
2. የሚጀምሩበትና የሚያበቁበት ጊዜ፦
* በጊዜ ያልተገደበው (ሙጥለቅ) ተክቢራ፦ በሁለቱ የዒድ ሌሊቶች (የረመዳን እና የሐጅ ዒድ ዋዜማ ላይ) ይባላል። እንዲሁም የዙልሒጃህ አስር ቀናት ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ የመጨረሻው የተሽሪቅ ቀን ፀሐይ እስከምትጠልቅበት ጊዜ ድረስ በማንኛውም ሰዓት ይባላል።
* በጊዜ የተገደባው (ሙቀየድ) ተክቢራ፦ * ሐጅ ላላደረገ ሰው ከአረፋ ቀን የፈጅር (ሱብሒ) ሶላት ጀምሮ እስከ መጨረሻው የተሽሪቅ ቀን የአስር ሶላት ማግስት ድረስ ይባላል።
   * ሐጅ ለሚያደርግ ሰው (ሑጃጅ)፦ በዒድ ቀን (የእርድ ቀን) ከዙህር ሶላት ጀምሮ እስከ መጨረሻው የተሽሪቅ ቀን የአስር ሶላት ማግስት ድረስ ይባላል።
3. ሁለቱ ተክቢራዎች የሚገናኙባቸው ቀናት፦
ሐጅ ላላደረገ ሰው ሁለቱ የተክቢራ ዓይነቶች (ሙጥለቅ እና ሙቀየድ) ከአረፋ ቀን ሱብሒ ሶላት ጀምሮ እስከ መጨረሻው የተሽሪቅ ቀን(ዙልሂጃ 13)  ፀሐይ መጥለቅ ድረስ ባሉት 5 ቀናት ውስጥ ይገናኛሉ (በአንድ ላይ ይከሰታሉ)። ለሑጃጅ (ሐጅ ለሚያደርግ ሰው) ደግሞ ከእርድ ቀን (የዒድ ቀን) ዙህር ሶላት ጀምሮ እስከ መጨረሻው የተሽሪቅ ቀን ፀሐይ መግቢያ ድረስ ይገናኛሉ።
4. የተክቢራው አባባል (ዘይቤ፦
የተክቢራው አገላለጽ፦
> *«አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር፣ ላ ኢላሀ ኢለላህ፣ አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር፣ ወሊላሂል ሐምድ»*
>
የፈለገ ሰው ተክቢራውን ሶስት ጊዜ በማድረግ (በመደጋገም) እንዲህ ሊል ይችላል፦
> *«አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር፣ ላ ኢላሀ ኢለላህ፣ አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር፣ ወሊላሂል ሐምድ»*
>
5. የተክቢራ ታላቅነትና የማስታወሻ ጥሪ፦
በጊዜ ያልተገደበው ተክቢራ የዙልሒጃህ አስር ቀናት ሲገቡ የሚጀምር ሲሆን፣ ሰዎች በሚሰበሰቡባቸው ቦታዎች ላይ ድምፅን ከፍ አድርጎ ማለቱ ይበልጥ የተወደደ ነው። ይህንን ሸሪዓዊ ሥነ-ሥርዓት (ሸዒራህ) ግልጽ ለማድረግ ከሚመቹ ወቅቶች መካከል በነዚህ አስር ቀናት ውስጥ በአዛንና በኢቃማ መካከል ያለው ጊዜ አንዱ ነው።
አረቦች «አላሁ አክበር» የሚለው ቃል አላህን ለማላቅና ለማክበር ከተነገሩ ንግግሮች ሁሉ እጅግ ጥልቅና ላቅ ያለ መግለጫ እንደሆነ ይናገራሉ። ትርጉሙም «አላህ ከማንኛውም ነገር በላይ ታላቅ ነው፤ አላህ በልቦና ውስጥ ከሚመላለስና ከሚታሰብ ነገር ሁሉ በላይ ታላቅ ነው» ማለት ነው።
በመጨረሻም፣ እያንዳንዱ ሙስሊም ይህንን ታላቅ ሱና ሕያው ማድርግና ይህንን ሸሪዓዊ መለያ (ሸዓኢር አድ–ዲን)በየቦታው ይፋ ማድረግ ተገቢ ነው።
(ከሸይኽ ሰዐድ ኸሥላን ትምህርት የተወሰደ)

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

ተክቢራ
በቃሪእ ሰዕድ አልጋሚዲይ ድምፅ
‏ احيوا سنة التكبيــــــــــر

      وذكــــــــــروا بها

الله اكبر ، الله أكبر ، الله أكبر
      🍃 لاإله إلا الله 🍃

الله أكبـــــــر ، الله أكبـــــــر
      🍃 ولله الحمد 🍃
🌸🍃
/channel/sultan_54

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

ያለፈውን እና የመጪውን አመት ሀጢአት ያስምራል!

አቡ–ቀታዳ ረዲየላሁ ዓንሁ እንዳስተላለፉት:‐ «የአላህ መልእክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ስለ እለተ ዓረፋ ጾም ተጠየቁ፤ እሳቸውም "ያለፈውን እና የመጪውን አመት ሀጢአት ያስምራል" አሉ።» (ሙስሊም ዘግበውታል)

ያስታውሱ ዛሬ ከዙል–ሒጃ ወር ስምንተኛው ቀን (የውሙ አት–ተርዊያ) ሑጃጆች የሐጅ ስራቸውን የሚጀምሩበት እለት ነው።

የነገው ዘጠነኛው ቀን የውሙ ዓረፋ ነው። ሑጃጆች በዓረፋ ምድር የሚቆሙበት ለነሱም ይሁን ለሌላው ሙስሊም ማህበረ–ሰብ እጅግ ልዩ የዒባዳ ቀን ነው።

በጾም፣ በዚክር በተለይ ተክቢራ እና ዱዓእ እንድንጠቀምበት ልንተዋወስ እና አንዳችን ሌለኛውን ሊያበረታታ ይገባል።
የነገውን ቀን ጾም በተመለከተ ከላይ በጠቀስነው ሀዲስ ላይ መልእክተኛው ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ያለፈውን እና የመጪውን አመት ወንጀል ያሰምራል ማለታቸው ይህን እለት በጉጉት እንድነጠብቀው ያደርጋል።

ከጾም ውጪ በዚህ ቀን ልዩ በሆነ መልኩ ልናደርጋቸው የሚወደዱ ነገሮችን በተመለከተ በተከታይ ጽሁፎች ኢንሻ አላህ ለመጠቆም እሞክራለሁ።

ወደ መልካም አመላካች እንደ ሰሪው ምንዳ አለው!!

ለሌሎችም መልእክቱን እናስተላልፍ

✍️ ጣሀ አህመድ

🌐
/channel/tahaahmed9

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

##"የዓረፋ ቀን በዓል (ዒድ) መሆኑን ያውቃሉን? አዎ!
እሱማ አላህ ዲኑን የሞላበት፣ ጸጋውንም ያጠናቀቀበት ቀን አይደለምን? ይህ የሆነው ደግሞ ከብዙ የተውሂድ አንቀጾች፣ ከታሪኮች፣ ከሕግጋቶችና ከነቢያዊ ሐዲሶች ረጅም ሰንሰለት በኋላ ነው።
ይህ በዓል ለሙስሊሞች ዘንድ እጅግ ታላቅ መሆኑን ማስታወስና ማስተንተን ይገባል። እንዲያውም አንድ አይሁዳዊ (ለዑመር ኢብኑል ኸጣብ) እንዲህ ብሏቸው ነበር፦ *‘እኛ የይሁዳ ማኅበረሰቦች ላይ እንዲህ ዓይነት አንቀጽ (አያህ) ወርዶ ቢሆን ኖሮ፣ ያንን ቀን የበዓል ቀን (ዒድ) አድርገን እንይዘው ነበር።’* ዑመርም (ረዲየሏሁ.ዐንሁ) እንዲህ ሲል መለሱለት፦ *‘እኔ ይህች አንቀጽ( ማለትም፦"...ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለእናንተ ሞላሁላችሁ፤ ጸጋዬንም በእናንተ ላይ ፈጸምኩ፤ ለእርናንተም እስልምናን ከሃይማኖት በኩል ወደድኩ..." (አል-ማኢዳህ: 3)
በየትኛው ቀን በነቢዩ (ﷺ) ላይ እንደወረደች ጠንቅቄ አውቃለሁ፤ እሷም የወረደችው በዓረፋ ቀን ነበር።’*"
#ዒድ_ዐረፋ#ዙልሒጃ

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

ቃላት ፍርድ አላቸው
በሸሪዓ ሚዛን "ሙስሊም አይደለሁም" የሚሉ ግልጽ ቃላት እንደ ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ወይም እንደ ምሳሌያዊ አነጋገር አይታዩም። ይልቁንም ቀጥተኛ የእምነት ክህደት መግለጫ ናቸው። አንድ ሙስሊም ከእውነተኛ ማስገደድ ውጭ ይህንን ለማድረግ መብት የለውም።

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

## 🌟 የዓረፋ ቀን እና የዕርድ ቀን (የዒድ ዕለት) ታላቅነት!
ምስጋና ለአላህ ይሁን። የዓረፋ ቀን በአላህ (ዓዘ ወጀል) ዘንድ እጅግ ታላቅ ቀን ነው። ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰልም) በትክክለኛ ሐዲሳቸው እንዲህ ብለዋል፦
> *“አላህ በዓረፋ ቀን ከእሳት ነፃ የሚያወጣቸውን ያህል ባሮችን (ከእሳት) ነፃ የሚያወጣበት ሌላ ምንም ቀን የለም።”*
>
የአንዳንዶቹ የዓሊሞች አባባል እንደሚያመለክተው፣ አላህ በቁርአኑ “በመስካሪውና በተመሰከረበትም እምላለሁ” (وشاهد ومشهود) ሲል የፈለገበት ‘የተመሰከረበትን ዕለት’ ማለትም የዓረፋን ቀን ነው። እሱ ፀሐይ ከወጣችባቸው ቀናት ሁሉ በላጩ ቀን ነው። በዚህ ዕለት ከሚደረግ ዱዓእ የበለጠ በአላህ ዘንድ ታላቅ የሆነ የለም። የአላህ መልዕክተኛም ((ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰልም))፦ *“ከዱዓእ ሁሉ በላጩ የዓረፋ ቀን ዱዓእ ነው”* ብለዋል።
የዓረፋ ቀን ትሩፋትና የአላህን ችሮታ ማግኘት ሑጃጁንም (ሐጅ ላይ ያለውን) ሆነ ሀገር ላይ ያለውን (ሐጅ ያላደረገውን) እኩል ያጠቃልላል። ሑጃጆች በዓረፋ ሜዳ ላይ በመቆም ታላቁን የሐጅ (ሩክን) ማዕዘን ይፈጽማሉ፤ ነቢዩ ((ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰልም)) *“ሐጅ ማለት ዓረፋ ነው”* እንዳሉት። ሐጅ ያላደረጉት ደግሞ የዓረፋን ቀን በመጾም ወደ አላህ መቃረቢያን ይሻሉ። ይህንንም ጾም የአላህ መልዕክተኛ ((ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰልም)) እንደተናገሩት፦ ያለፈውን አንድ ዓመትና የሚመጣውን አንድ ዓመት (በድምሩ የሁለት ዓመት) ወንጀል ያስተሰርያል ብለው ከአላህ ዘንድ ተስፋ ያደርጋሉ።
ስለሆነም እሱ በረከቱ አጠቃላይ፣ ትሩፋቱ ታላቅ፣ ምሕረቱና እዝነቱ የሰፋ፣ ከእሳት ነፃ የመውጫ ቀን ነው። ይህ ቀን ከዱንያ ቀናት ሁሉ በአላህ ሚዛን ዘንድ እጅግ ከባድ ቀን ነው። ወደ ዓረፋ ቀን ከተመለከትክና “በነዚህ አስሩ የዙልሒጃ ቀናት ውስጥ ከዓረፋ ቀን በስተቀር ሌላ ቀን ባይኖር እንኳ፣ የአስሩን ቀናት በላጭነት ከሌላው የዓመቱ ቀናት ሁሉ በላይ ለማስበለጥ በቂ በሆነ ነበር” ብትል እውነት ነው። ታዲያ ከላይ የተጠቀሱት ታላላቅ ትሩፋቶች ሁሉ ተደምረውበትማ እንዴት አይበልጥ?! እነኚህ ቀናት አላህ ሐጅን ያዘዘበትና ሑጃጆች የአምልኮ ሥርዓታቸውን የሚፈጽሙባቸው የታወቁት ቀናት ማጠቃለያ ናቸው። ይህም አላህን ለማውሳትና በነዚህ ቀናት ውስጥ ያሉትን ጥቅሞች ለመታደም የተደነገገ ነው።
በመቀጠልም የአስሩ ቀናት ማሳረጊያ (አሥረኛው ቀን) የሆነው የዕርድ ቀን (يوم النحر) ይመጣል። እሱም በምሥራቅም ሆነ በምዕራብ ያሉ የሙስሊሞች ኡማህ በደስታ የሚሞሉበት ታላቅና የተባረከ የዒድ ቀን ነው። ይህ ቀን በአላህ ዘንድ እጅግ ታላቅ ከሆኑ ቀናት ውስጥ አንዱ ነው። ነቢዩ ((ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም)) እንዲህ ብለዋል፦
> *“በአላህ ዘንድ ከቀናት ሁሉ ታላቁ ቀን የዕርድ ቀን (የዒድ ዕለት) ነው።”*
>
ይህ የአላህ መልዕክተኛ ((ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም)) የተናገሩት ፍፁም የሆነ ማበላለጥ (تفضيل مطلق) ነው። ይህ ፍፁም ማበላለጥ የዒድ ቀንን በናፍቆት የምትጠብቀው ታላቅ ቀን አድርገህ እንድትይዘው ያደርግሃል። ይህ በታላቁ ጌታህ ዘንድ ከሁሉ የበላይ የሆነ ታላቅ ቀን ከሆነ፣ በአላህ ይሁንብህ! አንተ በዚህ ቀን ምን ልትሠራ ተዘጋጅተሃል?! በአላህ ዘንድ ከቀናት ሁሉ በላጭ በሆነው ቀን ምን ታደርጋለህ?
አላህ በዚህ ቀን ተክቢራን ደንግጎልሃል፣ የዒድ ሰላትን ደንግጎልሃል፣ የምታርደውን ኡድሒያ (ዕርድ) ደንግጎልሃል። ለሙስሊሙ ኡማህ በሙሉ፤ ሑጃጁንም ሆነ ሌላውን፣ አላህን በማክበር ድምፃቸውን ከፍ አድርገው አላህን እንዲያወድሱ፣ ተክቢራ፣ ተህሊልና ተሕሚድ እንዲያደርጉ ደንግጓል።
የሙስሊሙ ኡማህ ሑጃጁም ሆነ በሀገሩ ያለው ሁሉ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ በአንድ ድምፅ ይሰበሰባል። ምድር በሙሉ ለታላቁ ጌታችን በምናደርገው ተክቢራ፣ ተህሊልና ተሕሚድ ትናወጣለች፣ በድምፅም ትሞላለች። በእርግጥም የሙስሊሙ ኡማህ የዚህን ቀን ታላቅነት በአምልኮ ሥርዓቱ፣ በሸሪዓው፣ በዓቂዳውና በባህሉ ላይ ያንጸባርቃል። በዚህም የሙስሊሙ ኡማህ አረብም ሆነ አረብ ያልሆነው፣ ታናሹም ታላቁም፣ ወንዱም ሴቱም ሁሉ በአንድ ሰው ልብ ላይ ሆነው በአንድ ድምፅ እንዲህ ይላሉ፦
> الله أكبر الله أكبر الله أكبر لا إله إلا الله
> الله أكبر الله أكبر ولله الحمد
> *(አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር፣ ላ ኢላሀ ኢልለላህ፣ አላሁ አክበር አላሁ አክበር ወሊላሂል ሐምድ)*
>
🚩 @ /channel/sultan_54

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

የታላቁ ዓሊም የኢማም ኢብኑል ቀይም (ረሒመሁላህ) ዕንቁ ምክር፦

ኢማን በልብ ውስጥ የሚገኝ ደስታ፣ ጥፍጥና እና እርካታ አለው።
አንድ ሰው የአምልኮ ተግባራትን በሚፈጽምበት ጊዜ ያንን ጣፋጭና መንፈሳዊ የደስታ ቃና ካላገኘ፣ ኢማኑን አጥቷል ወይም ጎድሏል ማለት ነው!»


​📔 አር-ሪሳላህ አት-ተቡኪይያህ (7)*

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

በኢስላም ታሪክ ውስጥ ካሉ ትልልቅ **"የፈላስፎች እና የከላም ምሁራን የቁጭት እምነት ምስክርነቶች"
(اعترافات أهل الكلام والفلسفة)


የታላቁ የከላም (የነገረ-መለኮት) ምሁር እና ተፍሲር አዋቂ የፋኽሩዲን አር-ራዚ (እ.ኤ.አ በ1210 የሞቱት)
እንዲህ ይላሉ፦
> "የከላም (የአመክንዮ) መንገዶችን እና የፍልስፍና ስልቶችን በሙሉ በጥልቀት መረመርኩ፤ ነገር ግን የታመመን ልብ ሲፈውሱም ሆነ የተጠማውን ቀልብ ሲያረኩ አላየኋቸውም። ከሁሉም ይበልጥ ወደ እውነት ቀራቢው መንገድ የቁርአን መንገድ ሆኖ አገኘሁት!"
>
### የዚህ ምስክርነት (اعتراف) ትርጉም እና በጀርባው ያለው ታሪክ
ፋኽሩዲን አር-ራዚ እድሜያቸውን በሙሉ በፍልስፍና፣ በአመክንያታዊ ክርክር (ከላም) እና በግሪክ አመክንዮ ውስጥ ካሳለፉ በኋላ፣ በህይወታቸው ፍፃሜ ላይ የደረሱበትን ፍሬ ነገር ነው የተናገሩት። ይህ ንግግራቸው "አቅሳሙ አል– ለዛት" (أقسام اللذات) በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ የሰፈረ ሲሆን፣ ተከታዩንም ግጥም አካተውበታል፦

نِهَايَةُ أَقْدَامِ العُقُولِ عِقَالُ ... وَأَكْثَرُ سَعْيِ العَالَمِينَ ضَلَالُ


وَلَمْ نَسْتَفِدْ مِنْ بَحْثِنَا طُولَ عُمْرِنَا ... سِوَى أَنْ جَمَعْنَا فِيهِ: قِيلَ وَقَالُوا

> *የአእምሮዎች መጨረሻ መረባበሽ (መሸበር) ነው፣*
> *የአለም ምሁራንም ጥረት መጨረሻው ጥፋት ነው።*
> *በአካላቶቻችን ውስጥ ከመንፈሳዊ ስቃይ በቀር አልተጠቀምንም፣*
> *ከዘመናት ፍለጋ ያገኘነውም ቢኖር፡ 'እንዲህ ተባለ' እና 'አሉ' የሚሉ ወሬዎችን መሰብሰብ ብቻ ነው።*
>
ይህ ዓይነቱ የእምነት ኑዛዜ ወይም ምስክርነት በአር-ራዚ ብቻ የተገደበ አይደለም፤ ሌሎችም ታላላቅ የፍልስፍና እና የከላም መሪዎች በህይወታቸው መጨረሻ ላይ ተመሳሳይ የቁጭት ምስክርነት ሰጥተዋል፦
* ኢማም አል-ጁወይኒ (ኢማሙ እል-ሐረመይን)፦
"يَا أَصْحَابَنَا لَا تَشْتَغِلُوا بِالكَلَامِ، لَوْ عَرَفْتُ أَنَّ الكَلَامَ يَبْلُغُ بِي إِلَى مَا بَلَغَ مَا اشْتَغَلْتُ بِهِ، لَقَدْ طُفْتُ المَعَاهِدَ الكِبَارَ، وَخُضْتُ البِحَارَ، وَتَرَكْتُ أَهْلَ الإِسْلَامِ وَعُلُومَهُم، وَدَخَلْتُ فِي الَّذِي نَهَوْنِي عَنْهُ، وَالْآنَ فَإِنْ لَمْ يَتَدَارَكْنِي اللهُ بِرَحْمَتِهِ فَالْوَيْلُ لِابْنِ الجُوَيْنِي، وَهَا أَنَا ذَا أَمُوتُ عَلَى عَقِيدَةِ أُمِّي" (وفي رواية: "عَلَى عَقِيدَةِ عَجَائِزِ نَيْسَابُورَ").

"​"እናንተ ወዳጆቻችን ሆይ! በከላም (በአመክንዮ/በፍልስፍና) እውቀት ላይ አትጠመዱ። ይህ የከላም እውቀት አሁን ካደረሰኝ (የጥርጣሬና የመዋለል) ደረጃ ላይ እንደሚያደርሰኝ አስቀድሜ ባውቅ ኖሮ ኖሮ ፈጽሞ በእሱ ላይ ባልተጠመድኩ ነበር። ትልልቅ የትምህርት ተቋማትን በሙሉ አዳረስኩ፣ (የፍልስፍናን) ባህሮች ዋኘሁ፣ የኢስላም ሰዎችንና እውቀቶቻቸውን ንቄ እነሱ ከተከለከሉት ነገር ውስጥ ገባሁ። አሁን ግን አላህ በራህመቱ (በእዝነቱ) ፈጥኖ ካልደረሰልኝ ለጁወይኒ ልጅ ወዮለት! እነሆ እኔ አሁን (ሁሉንም ፍልስፍና ትቼ) በእናቴ እምነት ላይ ሆኜ እሞታለሁ።"
(በሌላ ዘገባ ደግሞ፦ "በነይሳቡር የዋህ አረጋውያን ሴቶች እምነት ላይ ሆኜ እሞታለሁ" ብለዋል)

* አቡ ሓሚድ አል-ገዛሊ፦ ህይወታቸውን በሙሉ በፍልስፍና እና በከላም ካሳለፉ በኋላ፣ በመጨረሻው ዘመናቸው ወደ ሐዲስ ትምህርት በመመለስ የኢማም አል-ቡኻሪን የሐዲስ መጽሐፍ ደረታቸው ላይ አቅፈው እንደሞቱ ይነገራል።
እነዚህ ሁሉ ምስክርነቶች (اعترافات) የሚያረጋግጡት አንድ እውነትን ነው፡- የሰው ልጅ አእምሮአዊ ፍልስፍና ለጊዜው የሚያደናግር እንጂ፣ ልብን በፍጹም እርጋታና እውነተኛ እምነት (የቂን) ሊሞላ የሚችለው ቀጥተኛውና ግልጹ የቁርአን እና የሱና መለኮታዊ ብርሃን ብቻ መሆኑን ነው።

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

## የኢማም አል-ሙዘኒ እና የኢማም አሽ-ሻፊዒ ውይይት
ኢማም አል-ሙዘኒ (አላህ ይዘንላቸውና) ሸይኻቸው የሆኑትን ኢማም አሽ-ሻፊዒን የጠየቁት ጥያቄ ኢማም አዝ-ዘሃቢ "ሲየር አዕላም አን-ኑበላእ" በተሰኘው መጽሐፋቸው ውስጥ ዘግበውታል።
ታሪኩም እንደሚከተለው ነው፦ በኢማም አል-ሙዘኒ ልብ ውስጥ ከተውሒድ (አስማኡ ወሲፋት) ጉዳዮች መካከል በአንዱ ላይ ጥርጣሬ ወይም አሻሚ ነገር ተፈጠረባቸው።
ዋናው ፍሬ ነገር ግን፤ አል-ሙዘኒ ወደ ኢማም አሽ-ሻፊዒ መጥተው ስለዚህ ጉዳይ ጠየቋቸው። ኢማም አሽ-ሻፊዒም (አላህ ይዘንላቸውና) ካሏቸው ነገሮች መካከል የሚከተለው ይገኝበታል፦
> ኢማም አሽ-ሻፊዒ፦ "በሰማይ ላይ ስንት ከዋክብት እንዳሉ ታውቃለህ?"
> አል-ሙዘኒ፦ "አላውቅም" (አል-ሙዘኒ ታሪኩን ሲያወራ እንዲህ ነው ያለው)።
> ኢማም አሽ-ሻፊዒይ፦ "መልካም! ከእነሱ ውስጥ ስለ አንዱ ኮከብ፤ የወጣበትን አቅጣጫ፣ የሚጠልቅበትን ቦታ እና ከምን እንደተፈጠረ ታውቃለህ?"
> አል-ሙዘኒ፦ "አላውቅም" አልኳቸው። ይላሉ

> ኢማም አሽ-ሻፊዒ፦ "እንግዲህ በአይንህ የምታየውንና ከፍጡራን ወገን የሆነን ነገር እንኳን ምንነቱንና እንዴትነቱን የማታውቅ ከሆነ፤ እንዴት ብለህ ነው ስለ ፈጣሪህ እውቀት (ስለ ባህሪያቱ እንዴትነት) ልትናገር የምትደፍረው?!"
> ሲየር አዕላም አንኑበላእ
### ዋናው መልእክት💡
በአይንህ የምታየውን፣ ፈጽሞ የማትስተውንና የምታውቀውን ፍጡር እንኳን እንዴትነቱን(ከይፊያውን) የማታውቅ ሆነህ ሳለ፤ ታዲያ አንድ ሰው ከዚህ በኋላ እንዴት ደፍሮ ስለ ፈጣሪው (የላቀና የከበረው አላህ) ማንነትና ባህሪያት 'እንዴትነት' (ከይፊያህ) ሊናገር ይችላል?!
🔴 ይህ ዓይነቱ አካሄድ (ስለ አላህ ባህሪያት እንዴትነት በጥልቀት መመርመር) ፍጹም አስተማማኝና ሰላማዊ ያልሆነ መንገድ እንደሆነ ጥርጥር የለውም።

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

قال ابن الجوزي رحمه الله :
الليالي والأيام الفاضلة لا يصلح أن يغفل عنها، لأنه إذا غفل التاجر عن موسم الربح فمتى يربح؟!"
(منهاج القاصدين ١/٣٤٣)

ኢብኑል ጀውዚ (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፦
​" ታላቅ ደረጃ ያላቸው (ቅዱሳን) ሌሊቶችና ቀናትን በቸልተኝነት ማሳለፍ በፍጹም አይገባም። ምክንያቱም አንድ ነጋዴ የትርፍ ወቅቱን በቸልተኝነት ካሳለፈ፣ ታዲያ መቼ ሊያተርፍ ነው?!"
(ሚንሃጁል ቃሲዲን፣ 1/343)

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

​🔹 የዘመኑን የክህደት (ኢልሃድ) ፈተና መጋፈጥ
​ይህ የአላህ መኖር እውነት እጅግ ግልፅ ቢሆንም፣ በዘመናችን የወጣቱን ትውልድ እምነት (አቂዳ) እና ስነ-ምግባር ለመበከል የሚንቀሳቀሱ ጥቂት ጠማማዎች አሉ።
​ይህንን የሃሳብ ወረራና የኢልሃድ ፈተና መጋፈጥ፣ የወጣቶችን እምነት መጠበቅ በአላህ መንገድ ላይ ከሚደረጉ ትላልቅ ጂሃዶች (ትግሎች) አንዱ ነው፤ ምክንያቱም ይህ ትግል ዲናችንንም ሆነ ዱንያችንን ከጥፋት የመከላከል ስራ ነው።
​🔗 ኪታቡን ሊንክ ለመጫን፦
كتاب الإلحاد وسائله و خطره و سبل مواجهته
/channel/amaliketeladab/8319

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

"እናንተ ሰዎች ሆይ! በቁርአን በወረደበትና በዓረብኛ ቋንቋ የታወቀውን ትርጉም—ይኸውም 'ላይ መሆን እና ከፍ ማለት' የሚለውን ትተው—አላህ ከዙፋኑ (ከዓርሹ) በላይ ሆኗል (*ኢስተዋ*) ማለትን ለምን ትቃወማላችሁ?
እነሱም፦ *'ምክንያቱም ከፍ ማለት (ኢስቲዋእ) የፍጡራን ባህሪ ነው፤ ከፍ የሚልን ማንኛውንም አካል ፍጡር መሆኑን እንጂ ሌላ አናውቅም'* አሉ።
እሺ ችግር የለውም፤ ታዲያ ፦
الرَّحْمَنُ عَلَى الْعَرْشِ اسْتَوَى [طه:5]
የሚለውን የቁርአን አንቀጽ ምን ልናደርገው ነው?
'በቁጥጥር ስር ማዋል ወይም መቆጣጠር (*ኢስቲላእ*) በሚለው ትርጉም እንፈታዋለን (እንተረጉመዋለን)' አሉ።
እኛም እንላቸዋለን፦ በእናንተ ህግና መርህ መሰረት፣ እኮ ማንኛውንም የሚቆጣጠርና በቁጥጥር ስር የሚያውልን አካል ፍጡር መሆኑን እንጂ ሌላ አናውቅም።
ታዲያ እናንተ አላህን ከፍጡር ጋር ማመሳሰል (*ተሽቢህ*) ውስጥ አልገባችሁምን? በዚያ በተቀጠፈው የቅኔ ስንኝ ውስጥ ገጣሚው ያላችሁን አታወሱም?
قَدِ اسْتَوَى بِشْرٌ عَلَى العِرَاقِ ... مِنْ غَيْرِ سَيْفٍ وَدَمٍ مُهْرَاقِ
*'ቢሽር (የተባለው ሰው) ያለምንም ሰይፍና ደም መፋሰስ በኢራቅ ላይ የበላይነቱን አረጋገጠ (ተቆጣጠረ)'* የሚለውን። በእነሱ ዘንድ እዚህ ጋ 'ኢስተዋ' ማለት 'ኢስተውላ' (በስልጣኑ ተቆጣጠረ) ማለት ነው።
እንግዲህ 'ቢሽር' የተባለው ፍጡር ተቆጣጠረ ከተባለ፣ እናንተም አላህን 'ተቆጣጠረ' ስትሉ ፍጡርን አላህ ጋር አመሳሰላችሁ ማለት ነው። ስለዚህ እናንተ ራሳችሁ አላህን ከፍጡር ጋር ወደ ማመሳሰል ተግባር ውስጥ ወድቃችኋል።
እነሱም፦ *'አይ ወንድሜ ሆይ! አንተ በስህተት ነው የተረዳኸን፤ እኛ ማለቱ የፈለግነው ከአላህ ታላቅነት ጋር የሚመጥን ቁጥጥር (ኢስቲላእ) ነው እንጂ እንደ ፍጡር ቁጥጥር አይደለም'* ካሉ፤
እኛም፦ 'ለአላህ ጥራት ይገባውና!)' እንላለን።
እኛስ የምንለው ምንድን ነው? ከአላህ ታላቅነትና ልቅና ጋር የሚመጥን ከፍ ማለት (*ኢስቲዋእ*) ነው እንላለን። በእኛ አባባል ላይ የምትሰጡትን ማንኛውንም ምላሽ፣ እኛም በእናንተ ቃል ላይ መልሰን እንመጣባችኋለን።"
ሸይኽ ሷሊሕ አስ–ሲንዲይ

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

> "የአእምሮን ጥንካሬ (ማሰብን) መጀመሪያ የሚያዳክመው ነገር... እነዚህ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የምታዩዋቸው አጫጭር ቪዲዮዎች (Shorts/Reels) ናቸው። እነዚህ በፍጥነት የሚቀያየሩት አጫጭር ቪዲዮዎች አእምሮን ይበታትኑታል። አእምሮ ከ5 ደቂቃ በላይ ዘልቆ በጥልቀት እንዳያስብ ያደርጉታል። በአንድ ነገር ላይ መቆየትና ማተኮር አይችልም።
> ንቃትና ማስተዋል መሰልቸት(ትዕግስት ማጣት)፣ ከአእምሮ መዳከም እና ከትዕግስት ማነስ ጋር አብረው ሊሄዱ አይችሉም፤ በፍጹም አይቻልም!
> ንቁና አስተዋይ ለመሆን ከነዚህ ነገሮች መራቅ አለብህ። ከነሱ የምትወስደው ለአስፈላጊ ጉዳይ ያህል ብቻ መሆን አለበት። ነገር ግን በእነሱ ሱሰኛ መሆን ንቃትንና ማስተዋልን ያርቃል።
> (በዚህ ሱስ ከተጠመድክ) ዝም ብለህ የምትቀበል( ተመልካች)፣ ጥልቀት የሌለው፣ በስሜት ብቻ የምትነዳ፣ የማታስተውልና የማታሰላስል ሰው ትሆናለህ።"
> — አሽ–ሸይኽ ዶ/ር ሷሊህ ኣሊ ሸይኽ
>

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

«ولا نُزِيلُ صِفَةً مِنْ صِفَاتِهِ لِشَنَاعَةٍ شُنِّعَتْ»
> "ተቺዎች ስላሸማቀቁበት ወይም ስላስፈራሩበት ብቻ ከአላህ ባህሪያት መካከል አንዳቸውንም ባህሪ ውድቅ አናደርግም (አንሰርዝም)።"
(ኢማሙ አሕመድ)
>
ኢማም አሕመድ ይህንን የተናገሩት የአላህን ስሞችና ባህሪያት (አስማእ ወስ-ሲፋት) በሚመለከት የጥመት አንጃዎች (እንደ ጃሕሚያህና ሙዕተዚላህ ያሉ) የሱና ሰዎችን ለማጥቃትና ለማሸማቀቅ ይጠቀሙበት የነበረውን ስልት ለመመከት ነው።
* የተቺዎች ስልት (ሽናዓህ)፦ እነዚህ ቡድኖች አህሉስ ሱናዎች በቁርኣንና በሐዲስ የመጡትን የአላህ ባህሪያት (ለምሳሌ፦ ማየቱን፣ መስማቱን፣ ከዐርሽ በላይ መሆኑን፣ መውረዱን፣ ፊቱን...) እንዳለ ሲያጸድቁ፣ እነርሱ «ይህ እኮ አላህን ከፍጡር ጋር ማመሳሰል (ተሽቢህ) "ተጅሲም" ነው» እያሉ በተራው ሕዝብ ዘንድ  ያስፈራሩበት ነበር።
* የኢማም አሕመድ ጽናት፦ ኢማሙ ምን አሉ። አላህ ለራሱ ያጸደቀውን ወይም መልእክተኛው (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ያጸደቁለትን ባህሪ፣ ሰዎች ስም ስላወጡለት ወይም ስላስፈራሩን ብቻ «ሰዎች እንዳይገምቱን» ብለን አንክድም፣ አንደብቅም፣ አንሰርዝምም።
ባጭሩ፦ በዲንና በአቂዳ ጉዳይ ላይ የሰዎች ትችትና ማጠልሸት ሳይሆን መከተል ያለብን በቁርኣንና በሐዲስ የመጣውን ቀጥተኛውን መረጃ ብቻ ነው።

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

በአላህ እምላለሁ! እንደነዚህ ያሉ (የዙልሒጃህ አስር) ቀናት በፍጹም አይገኙም። ከበጎ ሥራዎች ማከናወን የምትችሉትን ሁሉ አድርጉ! ከበጎ ሥራዎች ማከናወን የምትችሉትን ሁሉ ፈጽሙ!
​ዚክሮችን፣ ዱዓዎችን፣ ቁርኣን መቅራትን፣ ማስተንተንን፣ ማሰላሰልን፣ ወላጆችን መንከባከብን (ቢሪል ዋሊደይን)፣ ዝምድናን መቀጠልን፣ ለጎረቤት መልካም መዋልን፣ እንዲሁም የተለያዩ የሰደቃ ዓይነቶችን ሁሉ አዘውትሩ።
​ማከናወን የምትችሉትን ማንኛውንም በጎ ነገር ሁሉ አድርጉ፤ ለዲንና ለዕውቀት የሚሆኑ መልዕክቶችን መጻፍና ማሰራጨት፣ ሰዎችን ወደ በጎ ነገር ማነቃቃትን ጨምሮ። የአላህ ባሪያ ሆይ! ከበጎ ሥራዎች አንዳች ነገር እንኳ እንዳታስቀር! ይልቁንም ያለህን አቅምና ጉልበት ሁሉ አስተባብረህ ተጠቀምበት።
​የሌሊት ሶላትን (ቂያሙል ለይል)፣ የዱሐ ሶላትን፣ የተለያዩ የነዋፊል (የትርፍ) ሶላቶችን ስገድ። ወደ መስጂዶች ቀድሞ መግባትን፣ ከአንድ ሶላት በኋላ ሌላኛውን ሶላት በጉጉት መጠባበቅን አዘውትሩ። በነዚህ አስር ቀናት ውስጥ ቁርኣንን አክትመሃልን? ዘጠኙን ቀናት ወይም ከፊሉን ጾመሃልን?
​ማከናወን የምትችለውን መልካም ነገር ሁሉ አድርግ! በአላህ እምላለሁ፣ እንደነዚህ ያሉ የተከበሩ ቀናት በፍጹም አይገኙም! በአላህ እምላለሁ፣ እንደነዚህ ያሉ ቀናት በፍጹም አይገኙም!"


ሸይኽ ሷሊሕ አል ሙነጂድ

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

አሕዩ ወንሽሩ ሱነተ-ትተክቢር**
> *"የተክቢራን ሱና ሕያው አድርጉ፤ አሰራጩም!"*
> *"እኛ አሁን እንግዲህ በዱንያ ላይ ካሉት ታላላቅና አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ ከሆኑት ቀናት ውስጥ ነው ያለነው።"*
>
አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር፣ ላ ኢላሀ ኢለላህ፣ አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር፣ ወሊላሂል ሐምድ

>

Читать полностью…

የኡስታዝ ሱልጣን ኸድር የትምህርት መድረክ (official)

ይህ ምስል የዙልሒጃ አስር ቀናትን በመጠቀም ቁርኣንን ሙሉ ለሙሉ ቀርቶ ለማኽተም የሚረዳ የቲላዋህ ፕሮግራም (جدول) ነው።

Читать полностью…
Subscribe to a channel