14074
ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=
عيد كم مبارك تقبل الله منا ومنكم صالح الامال
ዒዳችሁ የተባረከ ይሁን አሏህ ከናንተም ከኛም መልካ ስራችንን ይቀበለን ወድማችሁ sultan khedir
በዒድ ቀን የሚከሰቱ ስህተቶችንና የሸሪዓ ጥሳቶች (ሙኻለፋት) ዋና ዋና ነጥቦች፦
በዒድ ቀን የሚፈጸሙ ዋና ዋና ህፀፆች (ስህተቶች)
1. የዒድ ሶላትን መተው፦
አንዳንድ ሰዎች በበዓሉ ደስታ ተውጠው ወይም በእንቅልፍ ምክንያት የዒድ ሶላትን ይተዋሉ። ይህ ትልቅ ስህተት ነው፤ ምክንያቱም ትክክለኛው የዑለማዎች አቋም የዒድ ሶላት በሁሉም ላይ ግዴታ (ዋጅብ) መሆኑ ነው።
2. በሴቶች የሚታዩ ሸሪዓዊ ጥሳቶች፦
* መቆነጃጀትና ሽቶ መቀባት፦ ሴቶች ወደ መስገጃ ስፍራ (ሙሰላ) ሲወጡ ተኳኩለውና ሽቶ ተቀብተው መውጣታቸው የተከለከለ ነው። ነቢዩ (ﷺ) ሴቶች ወደ ሶላት ሲወጡ ሽቶ ሳይቀቡ እንዲወጡ አዝዘዋል።
* ከወንዶች ጋር መቀላቀል፦
በመንገድ ላይም ሆነ በመስገጃው ስፍራ መውጫና መግቢያ ላይ ከወንዶች ጋር መጋፋትና መቀላቀል መወገድ ያለበት ተግባር ነው።
ዒድ የአላህ ምስጋና የሚቀርብበት ቀን እንጂ ወደ ወንጀል መግቢያ መሆን የለበትም።
ተክቢር አል-ጀማዒይ)፦
ተክቢራው በጋራ በአንድ ድምፅ (እንደ ዘፈን) መደረጉ ስህተት (ቢድዓ)ነው።
አንዳንዶች ቀኑን ሙሉ በጨዋታና በፌሽታ አሳልፈው የፈርድ ሶላቶችን (እንደ ዙህርና ዐስር) ያሳልፋሉ።
የመቃብር ቦታዎችን መጎብኘት በራሱ የተፈቀደ ቢሆንም፣ ለዒድ ቀን ብቻ ብሎ ነጥሎ መዘይር ግን ከሱና መረጃ የሌለው ተግባር ነው።
ዒድ የአላህ ስጦታ ነው። ስጦታውን ደግሞ እርሱን በሚያስቆጣ ነገር ሳይሆን፣ እርሱን በሚያስደስት ተግባር ልናከብረው ይገባል። ነፍሳችንን በረመዳን ውስጥ ባገኘችው የነፍስ ፅዳት መልሳ እንዳታድፍ ከእንዲህ ያሉ ስህተቶች በመጠበቅ እውነተኛውን የዒድ ጣፋጭነት እናግኝ።
በደስታ ስም ሸሪዓዊ ጥሳቶች ውስጥ እንዳንወድቅ እንጠንቀቅ።
ጥበቅ ማለት አላህ የጠበቀው ነው።
አላህ እነዚህ ስህተቶች እና ጥሰቶች ላይ ከመውደቅ ይጠብቀን።
የየትኛውም ከተማ ውበትና ግርማ የፈለገ ቢገዝፍ፣ በመካ ካለው ታላቅነትና ክብር ጋር ሊወዳደር አይችልም።
ጌታችን ሆይ! የተከበረውን ቤትህን (ካዕባን) የምንጎበኝበትን መንገድ አቅልልን። ነፍሳችን የናፈቀችውን ያን የተቀደሰ ስፍራ ረግጠን፣ በራህመትህ ጥላ ስር የምንሰግድበትን ቀን አቅርብልን። አሚን።Читать полностью…
ሰልማን አል-ፋሪሲ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ብለዋል፦
> «ሶላት ልክ እንደ መለኪያ (ሚዛን) ናት፤ (መስፈርቱን) አሟልቶ የሰራ ሰው፣ እርሱም (ምንዳው) ሙሉ ይሆንለታል። በመለኪያው ላይ ያጎደለ (የቀነሰ) ሰው ደግሞ፣ አላህ መለኪያ በሚያጎድሉ ሰዎች (ሙጠፊፊን) ላይ ምን እንዳለ ታውቃላችሁ።»
> — (አዝ-ዙህድ ለኢብን አል-ሙባረክ፣ 1192)
>
የመልዕክቱ ፅንሰ–ሀሳብ፦
ይህ ንግግር ሶላታችንን ስንሰግድ ግዴታ የሆኑትን የሶላት ክፍሎች፣ ሩኩዕን፣ ሱጁድን እና ኹሹዕን (ትኩረትን) ጠብቀን እንድንሰግድ ያሳስበናል።
በንግድ ስራ ላይ መለኪያ ማጉደል ወንጀል እንደሆነ ሁሉ፣ በሶላት ውስጥም ስነ-ስርዓቱን አለማሟላት አደጋ እንዳለው ያስገነዝባል።መረጃዎችን ለመከታተል፦
🔴 ሰበር ዜና፦ የዒድ አል-ፈጥር ጨረቃ አልታየችም
በሳዑዲ ዓረቢያ በዛሬው ዕለት የሸዋል (የዒድ) ጨረቃ ባለመታየቷ፣ ነገ ሐሙስ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. የረመዳን 30ኛው ቀን ሆኖ ይጾማል።
በዚህም መሰረት የዘንድሮው የ1447ኛው የሂጅራ ዘመን ዒድ አል-ፈጥር በመጪው አርብ መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ.ም. (April 20, 2026) እንደሚከበር የሳዑዲ ዓረቢያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በይፋ አረጋግጧል።
እንኳን ለዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
መረጃዎችን ለመከታተል፦
👇👇
/channel/sultan_54
🔴 ሰበር መረጃ፦
እስከ አሁን ባለው መረጃ መሰረት፣ በአብዛኞቹ የሳውዲ አረቢያ ግዛቶች የነበረው የአየር ሁኔታ የሸዋልን ጨረቃ ለማየት አስቸጋሪ አድርጎታል።
ለመከታተል፦
👇👇
/channel/sultan_54
ይህ ማለት የረመዳን ወር ነገ 30 ተሞልቶ ከነገ በስቲያ ዒድ ሊሆን የሚችልበት እድል ሰፊ መሆኑን ይጠቁማል። ይሁንና በጉዳዩ ላይ የሚወጣውን ኦፊሴላዊ መግለጫ መከታተል ያስፈልጋል።
🌙 የዕለቱ ወሳኝ መልክት!
ታላቁ ዓሊም ኢብኑ ረጀብ (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፡-
"አንድ አማኝ ረመዳንን ሲሰናበት እንዴት እንባው አይፈስም? እርሱ እኮ በሕይወት ዘመኑ ዳግመኛ ወደዚህ ወር ለመመለስ ዕድል ይኖረው እንደሆነ አያውቅም!"Читать полностью…
— [ለጧኢፉል መዓሪፍ (217)]
29 | رمضان
*"اللهم لا تجعل حظنا من صيامنا الجوع والعطش، ولا من قيامنا السهر والتعب، واجعلنا ممن صام رمضان وقام إيماناً واحتساباً فغفرت له ما تقدم من ذنبه، وما تأخر*🤲🏻🤎🤎🍂
"በታሪክ - ረመዳን 29 ምን ተከሰተ?"
1. የሙሳ ቢን ኑሰይር ወደ አንደሉስ (ስፔን) መግባት (92 ሂጅራ)
በታላቁ ኡመያዊ ኸሊፋ ወሊድ ቢን አብዱልመሊክ ዘመን፣ ታዋቂው አዛዥ ሙሳ ቢን ኑሰይር በረመዳን 29 ከሰሜን አፍሪካ ተነስቶ ወደ አንደሉስ ተሻገረ። ይህ ጉዞ ጣሪቅ ቢን ዚያድ የጀመረውን የድል ጉዞ ለማጠናከር የተደረገ ሲሆን፣ ለ800 ዓመታት የዘለቀውንና ለአለም ስልጣኔ ብርሃን የሆነውን የእስልምና ስርወ-መንግስት በስፔን ለመመስረት መሰረት ጥሏል።
መስጂደል አቅሳን ከወራሪዎች ነፃ ለማውጣት መንገድ የከፈተ አጋጣሚ ነበር።
💡 የመንፈስ ስንቅ
ረመዳን 29 አብዛኛውን ጊዜ የረመዳን የመጨረሻ ቀን ወይም "የጥርጣሬ ሌሊት" (የሸዋል ጨረቃ የምትጠበቅበት) ነው። በታሪክ ሙስሊሞች ይህንን ቀን ረመዳን በማለፉ በማዘንና የዒድ ደስታ በመምጣቱ በመደሰት መካከል ሆነው፣ በዱዓና በኢባዳ ተጠምደው ያሳልፉት ነበር።
🌙 በዒዱ ዋዜማ የተሰጠ ምክር…
የሰዎች ልብስ አሮጌም ይሁን ርካሽ፣ ከውድ ሱቅ የተገዛ ይሁን ከተራ ... አንተን የሚመለከትህ ጉዳይ አይደለም።የሰዎች አለባበስ ለፌዝ ወይም ለትችት የሚቀርብ አይደለም፤ የኢኮኖሚ ሁኔታቸውና የኑሮ ደረጃቸው ደግሞ ፈጽሞ ልትሳለቅበት የሚገባ ነገር አይደለም።
የበዓል ደስታ የሚገኘው በአዲስ ልብስ ብቻ ሳይሆን፣ የተሰበረን ልብ በመጠገን እና የሌሎችን ስሜት ባለመጉዳት ጭምር ነው። Читать полностью…
🏔️ "ነፍስህን አሸንፈህ ተራራውን ውጣ!"
ወደ አላህ አዝ–ዘወጀለ የሚደረገው ጉዞ አልጋ በአልጋ አይደለም። ኢማም ኢብኑል ቀይም እንዳሉት፦ "ነፍስህ ወደ ጌታህ በሚወስደው መንገድ ላይ የተጋረጠች ታላቅና አድካሚ ተራራ ነች።"
ይህንን ተራራ ሳትወጣና ሳትሻገር እውነተኛውን የዒባዳ ለዛና የልብ እርካታ ማግኘት አይቻልም።
ለምን ተራራ ተባለች?
ስለምታደክም፦ ልክ ተራራ መውጣት ትንፋሽ እንደሚቆርጥ፣ ነፍስያን መታገልም ትዕግስትና ጽናት ይጠይቃል።
ወደ ኋላ ስለምትጎትት፦ ስንፍና፣ የዱንያ ምኞትና ጫጫታ ልክ እንደ ቁልቁለት ወደ ታች ይጎትቱሃል።
መድረሻው ግን ከላይ ነው፦ ተራራውን የወጣ ሰው የሚያገኘው ንጹህ አየርና ሰፊ እይታ ወደር የለውም። ነፍሱን ለአላህ ትዕዛዝ ያስገዛ ሰውም በልቡ ውስጥ የሚሰማው ሰላም (ኢጥሚናን) እንዲህ ነው።
ዛሬውኑ ቆርጠህ ተነስ!
ከተራራው ግርጌ በዱንያ ወሬና በግርግር አትታለል። "ነገ እሰግዳለሁ፣ ነገ ቁርዓን እቀራለሁ" የሚለው የነፍስያህ ሰበብ ከተራራው ግርጌ ሊያስቀርህ ነው።
ያስታውሱ፦ ተራራውን በወጣህ ቁጥር መንገዱ እየጠበበና ፈተናው እየበዛ ሊሄድ ይችላል፤ ነገር ግን ወደ ጫፉ (ወደ አላህ ውዴታ) በተቃረብክ ቁጥር የድልህ ቃና ይጣፍጣል።
"ጌታዬ ሆይ! ተራራውን አልፈን ካንተ ዘንድ ከሚረኩት ባሮችህ አድርገን።"
🕊️ ዱዓህ ለምን ተቀባይነት አጣ? (ልብ ሊባል የሚገባው ሚስጥር!)
ብዙዎቻችን አላህን እንለምናለን፣ ነገር ግን የምንለምንበት መንገድ ስህተት ሊሆን ይችላል። የዱዓ ሚስጥሩ በቃላት ብዛት ሳይሆን፣ በምንለምንበት ወቅት በልባችን ውስጥ ባለው የእርገጠኝነት (የቂን) ደረጃ ላይ ነው።
ሊታወቁ የሚገቡ ወርቃማ ህጎች፦
እርግጠኝነትና ጥርጣሬ አብረው አይሄዱም
ዱዓ ስታደርግ አላህ መልሱን እንደሰጠህ፣ የፈለግኸው ነገር በእጅህ ላይ እንዳለ አድርገህ እሰብ።
አላህ ዱዓ እንድታደርግ የልብ መነሳሳትን (ኢልሃም) የሰጠህ፣ ሊሰጥህ ስለፈለገ ብቻ ነው። እርሱ የማይሰጠህን ነገር እንድትለምነው አይገፋፋህም።
>
عَنْ مَعْقِلِ بْنِ يَسَارٍ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: "الْعِبَادَةُ فِي الْهَرْجِ كَهِجْرَةٍ إِلَيَّ"
በግርግር (በሁከትና በፈተና) ወቅት አምልኮ (ዒባዳ) ማድረግ፣ ወደ እኔ እንደ መሰደድ (ሂጅራ) እንደማድረግ ይቆጠራል።"
*اللهم آتِ نفوسنا تقواها، وزكِّها أنت خير من زكّاها، أنت وليُّها ومولاها* 🤲🏼
ይህ እጅግ ጥልቅ የሆነና የነፍስን ንጽህና የሚለምን ውብ ዱዓ ነው።
ትርጉሙም፦
"ጌታ ሆይ! ለነፍሶቻችን ጥንቃቄን (ተቅዋን) ስጣት፤ አንተ ከሁሉም በላይ አጥሪ ነህና አንጻት (እጠባት)፤ አንተ ረዳቷም ጌታዋም ነህና።" 🤲🏼
عن البراء بن عازب -رضي الله عنهما- قال: قام رجل فقال: يا رسول الله: إن حمدي زين وإن ذمي شين، فقال النبي ﷺ: "ذاك الله عز وجل".
رواه الترمذي وصححه الألباني والوادعي.
عيد كم مبارك تقبل الله منا ومنكم صالح الاعمال
ዒዳችሁ የተባረከ ይሁን አሏህ ከናንተም ከኛም መልካም ስራችንን ይቀበለን።
ወድማችሁ sultan khedir
የዒድ ዋዜማና የዒድ ቀን ሱናዎችና አዳቦች፦
አንድ ሙስሊም ሊያከናውናቸው የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦች፦
1. ተክቢራ ማድረግ፦
ይህ ከታላላቅ የዒድ ሱናዎች አንዱ ነው። አላህ በቁርአኑ፦ "...ቁጥሩንም እንድትሞሉ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ልታልቁት (ተክቢራ ልትሉ) (ታመሰግኑት) ዘንድ (ደነገገላችሁ)" (አል-በቀራህ፡ 185) ብሏል።
* ወቅቱ፦ ከዒድ ዋዜማ ጀምሮ ኢማሙ ለሶላት እስከሚወጣ ድረስ ባለው ጊዜ ወንዶችም ሴቶችም ድምፃቸውን ከፍ አድርገው (ሴቶች ለብቻቸው ሲሆኑ) ተክቢራ ማድረጋቸው የተወደደ ነው።
2. መታጠብ (ጉስል)፦
ለዒድ ሶላት ከመውጣታቸው በፊት መታጠብ የሰለፎች ተግባር ነው። ዐብዱላህ ኢብኑ ዑመር (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ወደ ዒድ ሶላት ከመውጣታቸው በፊት ይታጠቡ እንደነበር ተዘግቧል።
3. በልቶ ወደ መስገጃው ስፍራ መውጣት (በዒድ አል-ፊጥር)፦
ወደ ሶላት ከመውጣት በፊት ጥቂት ተምሮችን (በቁጥር ጎዶሎ ቢሆኑ ይመረጣል) መብላት ሱና ነው።
ነቢዩ (ﷺ) ተምሮችን ሳይበሉ ለዒድ ሶላት አይወጡም ነበር። (ቡ
ነቢዩ (ﷺ) በሁለቱ ዒዶችና በጁምዓ ቀን የሚለብሱት የሚያምር ካባ ነበራቸው።
ሴቶች ግን ከቤት ሲወጡ ሽቶ መቀባትና ወንዶችንም ሆነ ሴቶችን ትኩረት የሞሰብ እጅግ የተዋባ ልብስ መልበስ የለባቸውም።
የዒድ ሶላት በሁሉም ላይ ዋጅብ (ግዴታ) መሆኑ ነው።
ነቢዩ (ﷺ) በዒድ ቀን መንገድ ይቀይሩ ነበር።
ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም" (አላህ ከእኛም ከእናንተም መልካም ሰራችን ይቀበል) በማለት እንኳን አደረሳችሁ መባባል መልካም አዳብ ነው። ይህ በሶሐባዎች ዘንድ ይዘወተር ነበር።ማጠቃለያ
የዒድ እና የጁምዓ ሶላት በአንድ ቀን ሲገጥሙ የሚመለከት ፈትዋ፦
የዒድ አል-ፊጥር ወይም የዒድ አል-አድሐ በጁምዓ ቀን ቢውሉና ሁለቱ በዓላት (የዒድ እና የሳምንቱ በዓል የሆነው የጁምዓ ቀን) ቢገጥሙ፤ በዒድ ሶላት ላይ የተገኘ ሰው ጁምዓን የመስገድ ግዴታ አለበት ወይንስ በዒድ ሶላት ይበቃዋል? በጁምዓ ፋንታ ዙህር ይሰግዳል ወይንስ አይሰግድም? በየመስጂዱስ ለዙህር ሶላት አዛን ይደረጋል? ለነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ይሆን ዘንድ የሳዑዱ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ የሚከተለውን ውሳኔ አውጥቷል፦
* የዒድ ሶላትን የሰገደ ሰው፦
በጁምዓ ሶላት ላይ ላለመገኘት ፈቃድ (ሩኽሷ) አለው፤ በዚህም በጁምዓ ፋንታ በዙህር ወቅት የዙህርን ሶላት ይሰግዳል።
የዒድ ሶላትን ያልሰገደ ሰው፦ ይህ ፈቃድ (ሩኽሷ) እሱን አይመለከተውም። ስለዚህም የጁምዓ ሶላት ግዴታነቱ ከላዩ ላይ አይነሳለትም።
ወደ መስጂድ ሄዶ ጁምዓን መስገድ ይኖርበታል፤
🌙 የረመዷን የመጨረሻው ዕድል፦ ትጥቅህን አትፍታ!
አላህ (ሱብሃነሁ ወተዓላ) አንድ ተጨማሪ ቀን በጸጋው ለገሰን!
ይህች የመጨረሻዋ የረመዷን ቀን የድል ቀን ናት። ብዙዎች በዝግጅትና በገበያ ስራ በሚጠመዱበት በዚህ ሰዓት፣ አንተ ግን ትኩረትህን ወደ አላህ አድርግ።
ይህች ቀን የረመዷን ማጠቃለያ እንደመሆኗ መጠን፣ ያለፉትን ቀናት ጉድለት የምንሞላባትና በኢስቲግፋር (ምህረት በመጠየቅ) የምናሸብርቃት ልዩ ዕድል ናት።ዋና ዋና መልዕክቶች፦
ኢስቲግፋር አብዛ፦ ስራዎቻችን ተቀባይነት እንዲያገኙና ጉድለቶቻችን እንዲታረሙ "አስቲግፊሩላህ" ማለትም አታቋርጥ።* ዱዓ አድርግ፦
አላህ ጾማችንን እንዲቀበለንና ከእሳት ነፃ ከሚወጡት ባሮቹ እንዲያደርገን በልመና በርታ።
🔴#አዲስ_መረጃ
በአብዛኞቹ የሳዑዲ ዓረቢያ የጨረቃ መመልከቻ ጣቢያዎች ደመናማ የአየር ሁኔታ መቀጠሉ እተገለጸ ይገኛል፣ በአሁኑ ሰዓት ዝናብም እየጣለ በመሆኑ ጨረቃን ለማየት እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታ መፈጠሩን ያመለክታል።
በዚህም ምክንያት የሳዑዲ ዓረቢያ የጠቅላይ ፍርድ ቤት (Supreme Court) የሚሰጠውን ይፋዊ መግለጫ መጠበቅ ይኖርብናል።
/channel/sultan_54
በረመዳን ፍፃሜ እነዚህ ስራዎች ላይ ትኩረት ያሻሉ፦
"ተዋደየዕ" የትህትና አስፈላጊነት፦ ረመዳን ሲጠናቀቅ በሰራናቸው መልካም ስራዎች እና ኢባዳዎች (አምልኮዎች) ልባችን በትዕቢት እንዳይሞላ እስቲግፋር ማድረግ ይገባል። በሰራው ስራ የሚኩራራና ራሱን የሚያደንቅ ሰው ለጥፋት የተጋለጠ ነው።
የስራዎቻችን ጉድለት ማስተዋል፦ በእውነተኛ ልብ ምህረትን የሚጠይቅ ሰው ስራው የቱንም ያህል የበዛ ቢሆን በውስጡ ጉድለት እንዳለበት ያውቃል። በአላህ ፊት በመተናነስ የቀረበ ጥቂት ስራ፣ በትዕቢት ከተሞላ ብዙ ስራ ይበልጣል።
የምንዳ (አጅር) መብዛት፦
አላህ ለአንዳንዶች መልካም ስራቸውን እስከ 700 እጥፍ ያባዛላቸዋል፤ ለሌሎች ግን ላይባዛ ይችላል። ይህ የሚወሰነው በልባችን ውስጥ ባለው ቅንነትና ትህትና ነው።
🌙 የዒድ አል-ፊጥር ጨረቃ ፍለጋ - ወቅታዊ መረጃ!
🔴 የዒድ አል-ፊጥርን ጨረቃ የመመልከት ሂደት ውጤትን ዛሬ ምሽት በቴሌግራም ቻናላችን እንከታተላለን።
🔴 የሸዋል (የዒድ) ጨረቃ ዛሬ ረቡዕ ምሽት በነዚህ አገራት ይፈለጋል፦ ፍልስጤም፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ የመን፣ ኩዌት፣ ባህሬን፣ ኳታር፣ ሊባኖስ፣ ሱዳን፣ ኢራቅ እና ሶማሊያ።
🔴 የተቀሩት የአረብ አገራት ግን የረመዳን መጀመሪያ ቀናቸው የተለየ በመሆኑ፣ ጨረቃውን ነገ ሐሙስ ምሽት የሚፈልጉ ይሆናል።
🔴 አዳዲስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማድረስ የቴሌግራም ቻናላችንን ይከተሉ፦
🔗 /channel/sultan_54
⏳ በአዛንና በኢቃማ መካከል ያለው "የምላሽ ሰዓት!
ብዙዎቻችን አዛን ተደምጦ ኢቃም እስኪባል ድረስ ያለውን ጥቂት ደቂቃዎች በወሬ ወይም በዝምታ እናሳልፋለን። ነገር ግን ይህች አጭር ጊዜ የሰማይ ደጃፎች የሚከፈቱባትና የባሮች ልመና ተቀባይነት የሚያገኝበት ልዩ ቅጽበት ናት።
ለምን በዚህ ሰዓት ዱዓ እናደርጋለን?
የአላህ ቃል ኪዳን፦
ነቢዩ (ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም) በዚህ ሰዓት የሚደረግ ዱዓ እንደማይመለስ በግልጽ ነግረውናል።
የመረጋጋት ሰዓት፦ ነፍስያችን ከዱንያ ግርግር ወጥታ ለሶላት የምትዘጋጅበትና ወደ ጌታዋ የምትቃረብበት ወቅት ስለሆነ ዱዓው ከልብ የመነጨ ይሆናል።
የመላእክት ዱዓ፦ አንድ ሰው ሶላትን እየጠበቀ ባለበት ሰዓት መላእክት "ጌታ ሆይ ማረው፣ ጌታ ሆይ እዘንለት" እያሉ ዱዓ ያደርጉለታል።
ምን ብለን ዱዓ እናድርግ?
የዱንያና የአኺራን መልካም ነገር ሁሉ መለመን ይቻላል።
በተለይ ደግሞ "አላሁመ ኢኒ አስአሉከ አል-ዓፍወ ወል-ዓፊያህ" የሚለውን ዱዓ ማብዛት ይመከራል።
መልእክቱ፦ "አዛን ተደምጦ ሶላት እስኪቆም ድረስ ባሉት ጥቂት ደቂቃዎች የልብህን መዝገብ ለጌታህ ክፈት። ያንተ 'ያ ረብ' እና የእርሱ 'ለበይክ' የሚገናኙበት ሰዓት አሁን ነው!"
اللَّهُمَّ يا سامِعَ الصَّوتِ، ويا كاسيَ العِظامِ لَحمًا بعدَ الموتِ، أسألكَ أن تجعلَنا من أهلِ الجنَّةِ الذينَ لَا خَوۡفٌ عَلَيۡهِمۡ وَلَا هُمۡ يَحۡزَنُونَ🤲🤲🤲
Читать полностью…
💎 *دعاء الثبات والبركة* 💎
عن *النبي ﷺ* أنه كان يدعو ويقول:
اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ الثَّبَاتَ فِي الْأَمْرِ، وَالْعَزِيمَةَ عَلَى الرُّشْدِ، وَأَسْأَلُكَ مُوجِبَاتِ رَحْمَتِكَ، وَعَزَائِمَ مَغْفِرَتِكَ، وَأَسْأَلُكَ شُكْرَ نِعْمَتِكَ، وَحُسْنَ عِبَادَتِكَ، وَأَسْأَلُكَ قَلْبًا سَلِيمًا، وَلِسَانًا صَادِقًا.
🌙 የረመዳን የመጨረሻዎቹ ሁለቱ ቀናት እና "የኡሁድ ተራራ" ወጥመድ!
በኡሁድ ዘመቻ ወቅት፣ ቀስተኞች ጦርነቱ ያለቀ መስሏቸው ከተራራው ላይ ወርደው ምርኮ በመሰብሰብ ተጠመዱ። ያኔ ነበር ያልታሰበ ሽንፈት የደረሰው።
የመጨረሻዎቹን ሰዓታት ክብር ለጥቂት የዱንያ ጥቅሞች አሳልፋችሁ አትስጡ። እስከ መጨረሻው (በዒባዳችሁ)ተራራ ላይ ጽኑ!Читать полностью…
(
وعجلت إليك ربي لترضى)
በዱንያ ላይ ምድራዊ ጀነት አለች፤ እሷንም ሳይገቡ የነገዋን የኣኺራ ጀነት መግባት አይቻልም።" እሷም አላህን በማወቅና በማምለክ ውስጥ የምትገኝ የልብ እርካታ ነች።”በጠባብ እስር ቤት ውስጥ ሆነው እንኳ፦
ጠላቶቼ ምን ሊያደርጉኝ ይችላሉ? ጀነቴና የምቦርቀበት የአትክልት ስፍራዬ በልቤ ውስጥ ናቸው"
የዱንያ ሰዎች እጅግ ጣፋጭ የሆነውን ነገር ሳይቀምሱ ከዱንያ ወጡ።"
እኛ ያለንበትን የደስታና የእርካታ ጥግ ነገሥታትና የነገሥታት ልጆች ቢያውቁት ኖሮ፣ በሰይፋቸው ተዋግተው ይነጥቁን ነበር።">
"እንዴ ነጋ እንዴ?"
"የወንጀሎችን (የኃጢአትን) እውነታና መጥፎ ውጤታቸውን ማወቅ ከፈለግክ 'አድ-ዳእ ወደ-ደዋእ' (በሽታና መድኃኒቱ) የተሰኘውን መጽሐፍ አንብብ። ስለ ወንጀል ያለህን አመለካከት 180 ዲግሪ ይቀይረዋል፤ እኛ አቅልለን የምናያቸው ወንጀሎች ምን ያህል ከባድ እንደሆኑም ትረዳለህ። አላህ ይቅር ይበለን። እንዲሁም የአላህን ፍትሃዊነትና ቅጣቱን ታውቅበታለህ።"
سهري لتنقيح العلوم ألذ لي *** من وصل غانية وطيب عناق
وتمايلي طربا لحل عويصة *** أشهى وأحلى من مدامة ساقይህ ግጥም፦
የኢማም አሽ-ሻፊዒ (ወይም እንደ አንዳንዶች አባባል የኢማም አዝ-ዘርኑጂ) ግጥሞች የሚመደብ ሲሆን እውቀትን የመገብየት እርካታ ከማንኛውም ዓለማዊ ደስታ እንደሚበልጥ ይገልጻሉ።
ገጣሚው ሌሊቱን ሙሉ ተኝቶ ከማሳለፍ ይልቅ መጽሐፍትን በማገላበጥ እና ዕውቀትን በማጥራት የሚገኘው ድካም፣ ለሰው ልጅ በስሜት ደረጃ ከሚገኝ ከፍተኛ እርካታ (ፍቅር/መተቃቀፍ) የበለጠ ጣፋጭ እንደሆነ ይገልጻል።
ሁለተኛው ስንኝ፡ አንድን እጅግ አስቸጋሪ የሆነ የዒልም እንቆቅልሽ ወይም "አልፈታ" ያለን ጥያቄ ሲፈታ የሚሰማው የደስታ ስሜት፣ ወይን ጠጥቶ (ከመሰከር) በላይ መንፈስን እንደሚያድስ ይናገራል።
ማሳሰቢያ⚠️⚠️**
⛔️ዛሬ ሌሊት 27ኛው ሌሊት ነው፤ እሷም ለይለቱ አልቀድር ፍተኛ ተስፋ የሚጣልባት ሌሊት ናት። ይህች ሌሊት፤
- ከመጨረሻዎቹ አስረት ቀናት ውስጥ ናት፣
- ከቀሩት ሰባት ጎደሎ ያልሆኑ (ተጨማሪ) ሌሊቶች ናት፣
- ዊትር ጎዶሎ ( ኢተጋማሽ) ሌሊት ናት፣
- ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም በዚህ ሌሊት ከፍተኛ ጥረት ያደርጉባት ነበር፣
- ቤተሰቦቻቸውን ሰብስበው ለይል ሰላት (ቂያም) በጀመዓ አሰግደደዋቸዋል፣
- ሰሓቦቻቸውን በጀመዓ አሰግደዋቸዋል፣ ያ
- ቂያማቸውን ከዒሻ ጀምሮ እስከ ፈጅር አቅራቢያ ያራዝሙት ነበር፣
- ከሰሓቦች እና ከሰለፎቹ ውስጥ በነዚህ ሌሊት ለይለተ አል ቀድር መሆኗን እንደማያጠራጥሩ ተገልጿል፣
- ከቀደምት ሊቃውንትም የተወሰኑት ይህች ለሊት በትክክል ለይለተ ቀድር እንደሆነች ገልጸዋል፣
- ሌሎቹ ደግሞ ዊትር ሌሊቶች (21፣23፣25፣27፣29) መካከል የምትገኝ ስትሆን በብዛት ለይለተ አል ቀድር በየዓመቱ እንደምትለዋወጥ ተናግረዋል፣ ነገር ግን በብዛት በ27ኛው ሌሊት እንደምትከሰት ጠቅሰዋል፣
- ማስረጃዎቹም ሲሰባሰቡ ይህን አቋም ይደግፋሉ።
እደለ–ቢስ ሰውማ እሷን (ለይለተል ቀድር) ያጣ ነው!
📚የሸይኽ ሱለይማን አር-ሩሀይሊ (አላህ ይጠብቃቸውና)
ከትዊትር ገፃቸው ከለቀቁት ወደ አማርኛ የተተረጎመ ።