ይህ በኡስታዝ ሱልጣን ኸድር እውቅና የተከፈተ ብቸኛው (official) ቻነል ሲሆን የእርሱ ትምህርቶችና አጫጭር መልእክቶች በየጊዜው የሚተላለፉበት ልዩ መድረክ ነው፡፡ አላህ መልካም ምንዳውን ይክፈለው፤ ከዕውቀቱም ተጠቃሚ ያድርገን! ትምህርታዊ ቁም ነገሮች ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ እንዲሁም ሐሳብና አስተያየት ካልዎት በዋትስ ኣፕ ይላኩልን! ♻: https://api.whatsapp.com/send?phone=
ኹፍ ላይ ስለማበስ
ያለንበት ወቅት ብርዱ የበረታበት ጊዜ ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ በኹፍ ላይ ወይም በካልሲ ላይ ስለማበስ ግንዛቤ ብንይዝ ለራሳችንም እንጠቀማለን፤ ሌሎችንም እንጠቅማለን፡፡
① ኹፍ ማለት ከስስ ቆዳ የሚዘጋጅ ከስር ጀምሮ እስክቁርጭምጭሚት ድረስ ወይም ከዚያም በላይ የሚሸፍን በእግር ልክ የሚዘጋጅ የእግር ልብስ ነው:: ስለዚህ ቁርጭምጭሚት የማይደርሱ አጫጭር ካልሲዎች ከኹፍ ውስጥ አይካተቱም ማለት ነው።
② በኹፍ ላይ ማበስ ማለት አንድ ሰው የተለመደውን የሶላት ውዱእ እያደረገ መጥቶ እራሱንና ጆሮውን ካበሰ በኋላ እግሮቹን ግን በማጠብ ፋንታ በእርጥብ እጅ አበስ ማድረግ ማለት ነው፡፡
③ የሚታበሰው ላይኛው እንጂ ታችኛው ማለትም ምድር የሚረግጠው ክፍል (ፋናችን) አይደለም፡፡ ዐልይ ኢብኑ አቢ ጧሊብ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡- “ዲን ባስተያየት ቢሆን ኖሮ ኹፍ ከላይኛው ክፍሉ ይልቅ የታችኛው ነበር የሚታበሰው፡፡ ነገር ግን የአላህ መልእክተኛን ﷺ የኹፋቸውን ላይኛውን ክፍል ሲያብሱ አይቻለሁ፡፡” [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 153] ስለዚህ አንዳንድ ሰዎች ታች እግራቸውን ማበሳቸው ከከፊል ምሁራን የተገኘ ቢሆንም መረጃ የሚደግፈው አይደለም ማለት ነው፡፡ በርግጥ ደካማ ስለሆነ እንጂ ነብዩ ﷺ “ከታችም ከላይም አብሰዋል” የሚል ሐዲስ አለ፡፡ [ዶዒፍ ሱነን አትቲርሚዚ፡ 77]
④ አለባበሱን በተመለከተ ከኺላፍ ለመውጣት ያክል ሁለት እግሮቹን አጥቦ ከጨረሰ በኋላ መልበሱ የሚሻል ቢሆንም በየተራ ቀኙን እንዳጠበ የቀኝ ኹፉን፣ ግራውን አጥቦ ሲጨርስ ደግሞ የግራ ኹፉን መልበስም ይችላል፡፡
⑤ በኹፍ ላይ ማበስ የሚቻለው በጦሀራ (ውዱእ) ላይ እያለ ኹፉ ከተለበሰ ነው፡፡ [አልኢስቲዘካር፡ 2/256] [አልሙግኒ፡ 1/361]
⑥ የሚታበስበት የጊዜ ርዝማኔ ለነዋሪና ለመንገደኛ የተለያየ ነው፡፡ ለመንገደኛ (ሙሳፊር) 3 ቀን እና 3 ሌሎቶች ሲሆን ሙቂም ማለትም በሃገሩ ላይ ተቀማጭ የሆነ ግን ለአንድ ቀንና ሌሊት ነው፡፡ (24 ሰዓት፡፡) [ሙስሊም፡ 276] ታዲያ ጊዜው መቆጠር የሚጀምረው ኹፉ ከተለበሰበት ወቅት ጀምሮ ሳይሆን ማበስ ከተጀመረበት አንስቶ ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ በሃገሩ ኗሪ (ሙቂም) የሆነ ሰው ዐስር ላይ ውዱእ አድርጎ ኹፉን ቢለብስና በዚሁ ውዱእ ዐስርን፣ መግሪብንና ዒሻን ቢሰግድ ከዚያም ኹፉን ሳያወልቅ ተኝቶ ማለዳ ላይ ውዱእ አድርጎ እግሩን ቢያብስ መቁጠር የሚጀምረው ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ነው፡፡
⑦ ኹፍን ማውለቅ ውዱእ አያበላሽም፡፡ የጊዜ ገደቡ ሳያልቅም ይሁን ከተጠናቀቀ በኋላ ኹፋችንን ብናወልቅ ሌሎች ውዱእን የሚያጠፉ ነገሮች እስካልገጠሙን ድረስ ውዱኣችን እንዳለ ነው፡፡
⑧ የማበሻ ጊዜውን ሳይጨርስ በፊት ኹፍን ያወለቀ ሰው እንደገና ቢያስገባም የማበስ ብይኑ ተቋርጧል:: ስለሆነም በዚህ ሁኔታ ላይ ያለ ሰው ውዱእ ቢያጠፋ እንደ ማንኛውም ውዱእ እግሩንም ጭምር ማጠብ እንጂ ካወለቀ በኋላ ባስገባው ኹፍ ላይ ማበስ አይችልም፡፡
⑨ ኹፉ ቀዳዳ ቢኖርበትም በላዩ ላይ እያበሱ መጠቀም ይቻላል፡፡ ቀዳዳ ካለው በላዩ ላይ ማበስ አይቻልም ያሉ ቢኖሩም መረጃ የሚደግፈው ግን አይደለም፡፡ ታላቁ ሰለፍ ሱፍያን አሥሠውሪ ረሒመሁላህ ኹፍን አስመልክተው “እግርህ ላይ እስካለ ድረስ አብስበት፡፡ የሙሃጂሮችና የአንሳሮች ኹፎች የተበሳሱ፣ የተቀዳደዱና የተጣጣፉ እንጂ ሌላ ነበሩ ወይ?!” ይላሉ:: [ሙሶነፍ ዐብዶርረዛቅ፡ 753]
ኹፍ የሚመለከተው ወዱእን ብቻ ነው:: ስለዚህ በጀናባም ይሁን በሌላ ምክንያት ትጥበት ግዴታ በሚሆንበት ጊዜ ኹፍን አውጥቶ ሙሉ አካልን ውሃ ማስነካት ግዴታ ስለሆነ በዚህ ጊዜ በኹፍ ላይ ማበስ አይቻልም፡፡ [ኢርዋኡል ገሊል፡ 104] ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ላሉ፡- “በኹፍ ላይ ማበስ ውዱእን ብቻ የሚመለከት ነው፡፡ እንጂ ከሙሉ የሰውነት ትጥበት ጋር ግንኙነት የለውም፡፡ በዚህ ላይ ኢጅማዕ አለ” ይላሉ፡፡ [አልፈትሕ፡ 206]
(10) እስካሁ በኹፍ ላይ ስለ ማበስ ያሳለፍናቸው በካለሲ ላይ ማበስንም የሚመለከቱ ናቸው::
(ኢብኑ ሙነወር፣ ታህሳስ 28/2009)
ሸይኽ ረቢዕ ለተቃናቃኞቻቸው እንዲህ ነበሩ።
Читать полностью….
⚠️ ማስታወሻ!
🔘 ዓሹራን ለመፆም ያቀዳችሁ!
ዛሬ ሙሀረም 1 ሲሆን
🗓 # ጁምዓ ጁለይ 4 ( ሰኔ 27) ሙሐረም 9ኛው እና #ቅዳሜ ጁለይ 5 (ሰኔ 28) ደግሞ ሙሐረም 10ኛው [ዓሹራ] ነው።
የዓሹራ ቀን ፆም በሐዲስ እንደመጣው ያለፈውን አንድ ዓመት ወንጀል ያሰርዛል። አሏህ ይወፍቀን።
📨 ሌሎችን በማስታወስ በአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ!
🌟 ብዥታና እውነታ!
👌 በአጥማሚዎች ሹቡሀት ላለመደናገር የሚያግዝ ወቅታዊ መልዕክት!
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ
🔗 Share Link
/channel/abujunaidposts/590
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
"…በዚህ አንቀጽ አላህ ተዓላ እርሱን የሚዘክሩ አማኞችን እርሱን ሲዘክሩ በፍርሃት፣ በስጋት እና በርጋታ ገልጿቸዋል። ይህም ከእምነታቸው ጥንካሬ እና ጌታቸውን በማክበራቸው እርሱ ፊት እንዳሉ... ያህል ሲለሚሰማቸው… የመነጨ ነው።
እንጂ……
እንደ አህያ ጩኸት የሚያናፉ፣ የሚጮሁ፣ አላዋቂዎች ተራው ሕዝብና ሙብተዲዎች እንደሚያደርጉት አይደለም። በዚህ ( ጭፈራ፣ፉጨት፣ጩሀት…) ውስጥ ለተሰማራ፤ ይህን ድርጊቱን "ወጅድ" "ኹሹዕ" ነው ብሎ የሚሞግትን ፡- አላህን በማወቅ፣ በመፍራት እና በማወደስ የመልእክተኛውንም ሆነ የባልደረቦቻቸውን ደረጃ ላይ አልደረስክም ይባላል። ”
📚ተፍሲሩ አልቁርጡቢ (7/328)
ኢብን ተይሚያ (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ይላሉ፦
'ሁለት የከሓዲዎች ጭፍሮች በተዋጉ ጊዜ፤ ሙስሊሙ በመጋደላቸው ይደሰታል፣ እናም "በደለኞችን አንዳቸውን በሌላው ላይ የሚሾም አላህ ምስጋና ይድረሰው!' ይላል።"
መጅሙዕ አልፈታዋ (27/546)
🌴🔊 مادة الفرق والأديان،الروافض 💿🌴
📚 ርዕስ :- ሺዓ(አር– ረዋፊድ)
🎙ማብራሪያ ፦ ኡስታዝ ሱልጣን ኸድር
📀 《ደርሱን ፊ ኡሱሊል ፊረቅ》
«ቁርኣን ሲከብዳቸው ወደ እንጉርጉሮ ሄዱ!»
(751 ዓ.ሂ ላይ የሞቱት ታላቁ ኢማም ኢብኑል ቀይ'ዪም ንግግር ነው ። )
“አላህ ለባሪያው መልካምን በሻ ጊዜ ፣ አንደበቱን በነቢዩ አለይሂ ሰሏት ወሰላም በማውረድ ላይ ያገረዋል።”
(ኢብኑል ጀውዚ)
ሰለዋት እናብዛ ጁምዓም አይደል?!
በነገው እለት ይህን ዱዓ እንዳንረሳ!
اللهمَّ أَصْلِحْ لي دِينِي الذي هو عِصْمَةُ أَمْرِي ، و أَصْلِحْ لي دُنْيايَ التي فيها مَعَاشِي ، و اجعلِ الموتَ رحمةً لي من كلِّ سوءٍ
♻የዐረፋ ቀንን መፆም የሁለት ዐመታት ኃጢኣትን ያስምራልና ካሁኑ ኒያችንን እናስተካክል።
የአላህ መልእክተኛ ﷺ
ߔ蠙˜癄 الرسول ﷺ :
" صيامُ يومِ عرفةَ ، أَحتسبُ على اللهِ أن يُكفِّرَ السنةَ التي قبلَه، والسنةَ التي بعده "
«የዐረፋ እለት ፆም… ከዚህ አመት ቀድሞ ያለውንና የቀጣዩን ኣመት እንደሚያስምርልን ከአላህ ኣስባለሁ።» ብለዋል።
【ሰሂሁ-ሙስሊም: 1162】
ይህንን በማስመልከት ሸይኽ ሷሊህ አልዑሰይሚን [ረሂመሁላህ] “የዐረፋ እለት ፆም ያለፈው አመትንና የቀጣዩ አመትን ያስምራል። ሲባል ጥቃቅን ሀጢኣቶችን ብቻ የሚመለከት ነው። ከባባዶቹ ወንጀሎችን በተመለከተ የግድ ንስሃ መግባት ተውበት ማድረግ ይገባል።” ብለዋል።
【ፈታዋ ኑ…ሩን አለ-ድ'ደርብ: የካሴት ቁጥር ☞328】
በመሆኑም በዚሁ አጋጣሚ ከሐጢኣቶቻችን በመፀፀት ወደ ጌታችን በመመለስ ተውበት ከማድረግ ጋር የነገዋን የአረፋ እለት በፆም እናሳልፍ። የሰው ልጆች ነንና ከወንጀል ስለማንፀዳ ወንጀሎቻችንን እናራግፍ።
♻የዐረፋ እለት ዱዓእ ከሌላው ቀን የተሻለ የሆነ ዱዓእ ነውና እጆቻችንን እናንሳ።
የአላህ መልእክተኛ ﷺ
ߔ虂ال الرسول ﷺ :
" خيرُ الدعاءِ دعاءُ يومِ عرفَةَ وخيرُ ما قلْتُ أنا والنبيونَ من قبلي لا إلهَ إلَّا اللهُ وحدَه لا شريكَ له له الملكُ وله الحمدُ وهو على كلِّ شيءٍ قديرٌ "
«ከዱዓኦች በላጩ የዐረፋ እለት ዱዓእ ነው። እኔም ሆንኩ ከኔ በስተፊት የነበሩት ነቢያት ከተናገሩት መካከል በላጩ ቃል "ከአላህ በስተቀር በሀቅ ሊመለክ የሚገባው አምላክ የለም… እሱም ብቸኛና አጋር የሌለው ነው … ንግስናም ምስጋናም ለሱ የተገባ ነው … እሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ የሆነ ነውና።" የሚለው ቃል ነው።» ብለዋል።
【ሰሂሁ-ቲርሚዚይ: 3585, አል-አልባኒም ሀሰን ብለውታል】
ሸይኽ ዶክተር ሷሊህ ፈውዛን አል-ፈውዛን [ሀፊዘሁላህ] ስለዚህ ዱዓእ ሲያስረዱን☞
«የዐረፋ እለት ዱዓእ ሐጃጆችንም ሀጅ የማያደርጉትንም የሚያጠቃልል ነው። የሀጃጆች ግን ለየት ይላል። ምክንያቱም እነሱ ብልጫ ባለው ስፍራ ኢህራም ለብሰው በዐረፋ ምድር ቆመዋልና።» ብለዋል።
ከድምፃቸው በቀጣዩ ሊንክ ያድምጡ⇣
http://www.alfawzan.af.org.sa/sites/default/files/240.mp3
♻የዐረፋ እለት ከእሳት ነፃ የሚኮንበት ቀን ነው። በእለቱም በዐረፋ ምድር ለተገኙት ሀጃጆች ብቻ ሳይሆን ለመላው ሙስሊም ከእሳት ነፃ መውጫ ነውና ከወዲሁ በተውበትና በዒባዳ ነቃ እንበል።
ነቢዩ ﷺ
النبي ﷺ :
" ما من يوم أكثر من أن يعتق الله فيه عبدًا من النار من يوم عرفة، وإنه ليدنو ثم يباهي بهم الملائكة فيقول: ما أراد هؤلاء"
«አላህ ከባሮቹ መካከል በብዛት ከእሳት ነፃ ከሚያደርግባቸው እለታት ከዐረፋ እለት የበለጠ የለም። አላህም በእለቱ ወደነሱ ይቀርባል። መላኢኮቹንም እነዚያ ሰዎች ምን ፈለጉ ይላቸዋል።» ብለዋል
ߓף ሰሂሁ-ሙስሊም: 1348】
ልእለ ሀያሉ ጌታችን የያንዳንዳችንን ፍላጎትና አላማ እያወቀ ለመላእክት ጥያቄ ማቅረቡም በእለቱ የሚለምኑትን ባሮቹን ለመላእክቶች ለማሳወቅና ለማስመስከር ነው።
ሃፊዝ ኢብኑ ሀጀር [ረሂመሁላህ]
«የዐረፋ ቀን ከእሳት ነፃ የሚወጣበት ቀን ነው። አላህ (በሀጅ ተግባር) በዐረፋ ምድር የቆመን ሰው ከእሳት ነፃ ይለዋል። በዐረፋ ምድር ያልተገኘን በተለያዩ ሀገራት የሚገኙትንም ሙስሊሞች በእለቱ ከእሳት ነፃ ያደርጋቸዋል። ለዚህም ሲባል ነው ከዐረፋ እለት ቀጥሎ ያለውን ቀን በሀጅ ላይ ለተሳተፉትም ላልተሳተፉትም በያሉበት ሀገሮቻቸው ለመላው ሙስሊሞች የዒድ ቀን ያደረገው። ይህም ከእሳት ነፃ በመውጣቱና ከአላህ ምህረትን በማግኘቱ ረገድ ሁሉም ስለሚጋሩ ነው።» ብለዋል።
ߓң ለጧኢፉል-መዓሪፍ… ሊኢብኒ-ረጀብ አል-ሀንበሊይ】
---------
ዛሬ ዙል ሂጃህ 7 ነው።
ተክቢራችሁ እስከ ሰማይ ጣራ እስኪደርስ!
ተክቢራ አድርጉ።
የሙስሊሞች ስብስብ ሆይ!
የአላህ ውዴታ በወላጆች ውዴታ ውስጥ ነው፣ የአላህ ቁጣም በወላጆች ቁጣ ውስጥ ተያይዟል።
ዓብደላህ ኢብን ዓምር (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዳስተላለፉት፦ ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦
"የጌታ ውዴታ በወላጅ ውዴታ ውስጥ ነው፣ የጌታም ቁጣ በወላጅ ቁጣ ውስጥ ነው።"**
(ተርሚዚ ዘግበውታል)
#كبروا_كبروا...☄
الله أكبر الله أكبر؛ لا إله إلاّ الله؛ الله أكبر الله أكبر؛ ولله الحمد.
كبروا ليبلغ تكبيركم عنان السماء
كبروا فإن الله عظيم يستحق الثناء
t.me/sultan_54
📚 የልዩነት(መከፋፈል) መፍትሔዎች
👉 በሙስሊሞች መካከል መከፋፈል ከመከሰቱ በፊት በምን እንከላከል ልዩነቶች ወይም መከፋፈል ከተከሰተስ ምን እናድርግ ?
👉 ሙስሊሞችን ለመለያየት ወይም መከፋፈል እየዳረጉ ያሉት ሊያለያዩ የሚችሉ ነጥቦች ናቸው ?
👉 ሊያለያዩ የሚችሉ ነጥቦች ምንድን ናቸው ልናልፋቸውስ የምንችለው ነጥቦችስ ምንድን ናቸው ?
👉 "በተስማማንበት ነገር እንሰባሰብ ባልተስማምንበት ነገር አንዱ ለሌላው ኡዙር ይስጥ የሚለው መርህ" ትክክለኛ ነው ?
🎙 በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ
🔖 በኦዲዮ (MP3)
/channel/ustazilyas/889
ይህ በስፋት ሚዲያ ላይ እየተዘዋወረ የሚገኘው ምስል የሸይክ ረቢዕ ኢብኑ ሃዲ አል-መድኸሊ አይደለም፣ ይልቁንም የሸይክ አሕመድ ኢብኑ ዐብደህ ጃቢር መድኸሊ ምስል ነው። እርሳቸውም ሳውዲ ዓረቢያ ውስጥ የሚገኝ መድኸሊ የሚባል ጎሳ ታዋቂ ሰው ናቸው።"**
رحم الله الشيخ ربيع بن هادي رحمة واسعة
وغفر له
🔴 የዛሬው የጁምዓ ኹጥባ
🎙 خطبة الجمعة
عقيدة أهل السنة و الجماعة ٢
✨ የአህሉ አስ' ሱነቲ ወልጀማ0ህ
ዐቂዳ 2
⚠️ሊደመጥ የሚገባ ኹጥባ❗️
💥ከ0ርሹ በላይ ስለመሆኑ የተዳሠሠበት
💥 እንዲሁም የመጀሊስ ምርጫን አስመልክቶ ማንን እንምረጥ !
🎙በኡስታዝ ሱልጧን ኸድር
💫የአጅሩ ተካፋይ እንድንሆን ሼር!
🕌 ቃሊቲ ሀምዛ መስጂድ
🗓 ሙሐረም 9/1447 አ/ሂ
http://t.me/kalityhamzamesjid
👆🏻👆🏻👆🏻
🔖 የሶሓቦች ደረጃ
🎙 በኡስታዝ ሱልጧን ኸድር
Share link
/channel/nesihastudio/2283
የነሲሓ ኢስላማዊ ስቱዲዮ ሙሐደራዎችና ቂርዓቶች የሚቀርቡበት ቻናል
👇🏼👇🏼👇🏼
/channel/nesihastudio
መስጂዶች የተገነቡት ሀያሉን አምላካችን አላህን ለማውሳት፣ ሶላት ለመስገድ ሲሆን በውስጣቸውም ደዕዋ፣ ስብከት እና ሸሪዓዊ እውቀት የማስፋፋት ስራ ይከናወናል እንጂ የግል እና የአለማዊ ጥቅም መዳረሻ መሆን የለባቸውም።
የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
🔘«መስጂድ ውስጥ ማንኛውንም ነገር የሚሸጥ ወይም የሚገዛ ሰው ካያችሁ፡- አላህ ንግድህን አትራፊ አያደርግልህ በሉት።»
📚(ቲርሚዚ ዘግበውታል)
“ልጆቻቸው ቁርኣን እስከተማሩ ድረሰ፤ ይህ ኡማ ኸይር ላይ ነው።”
ዐብዱላህ ኢብኑ ዒሣ
📚موسوعة ابن أبي الدنيا(7/75)
💥 ከ ሠ ለ ፎ ች ማ ኅ ደ ር💥
ተውሂድ የፅናት፣ የጥንካሬ፣ የንቃት፣ የጉብዝናና የስኬት ቀዳሚውና ዋነኛው ሞተር መሆኑን የሚያሳይ ራስን የሚያስታዝብ የሠለፎች ወግ
※ ዘጋቢ:- ኢብኑ ቁዳማ አልመቅደሲይ
※ ተራኪ:- አብዱልዋሂድ ቢን ዘይድ
※ ባለታሪክ:- በተውሂድ የነገሰ ደግ ባሪያ
※ ምንጭ:- ኪታቡ-ተዋቢን ገፅ 179
※ ታሪክ:- የተውሂድ ላይ ፅናት
አብዱልዋሂድ ቢን ዘይድ ከሀሰን አልበስሪይ ተማሪዎች አንዱ ናቸው። በሒጅሪያ 177 ከዚህ ዓለም ተለይተዋል። በህይወት ዘመናቸው ያጋጠማቸውን ታሪክ እንዲህ ያጫውቱናል ረሂመሁሙላህ☞
«ባንድ ወቅት በመርከብ ተሳፍረን እየተጓዝን ሳለ ነፋሱ ወደ ደሴት ገፍቶ ወሰደንና ከመርከቧ ወረድን። እዚያች ደሴት ላይ አንድ ሰው ጣዖት እያመለከ አየነውና ወደሱ ሄደን "አንተ ሰው ምንድነው የምታመልከው?" ብለን ጠየቅነው። እሱም ጣዖቱን አሳየን።
እኛም "ይኸኮ የሚመለክ አምላክ አይደለም።" ስንለው "እናንተስ ምንድነው የምታመልኩት?" ኣለን።
"አላህን ነው የምናመልከው።" ስንለው
"አላህ ምንድነው?" ሲል ጠየቀን።
"አላህ ማለት ያ ዙፋኑ በሰማይ ሆኖ ስልጣኑ ደግሞ በምድርም ያለውና ውሳኔው በህይወት ባሉትም በሞቱትም ላይ የሆነው ነው።" ኣልነው።
ቀጠለና "እንዴት ኣወቃችሁት?" ኣለን።
"ይኸ ታላቅ የሆነ ንጉስና ሃያል ፈጣሪ የተከበረ መልእክተኛውን ወደኛ ላከልንና ይህን ጉዳይ ነገረን።" ስንለው
"ታዲያ መልእክተኛው ከምን ደረሰ?" ኣለን።
"መልእክቱን ኣደረሰን ከዚያም አላህ ህይወቱን ወደራሱ ወሰደው።" ኣልነው።
"ታዲያ የሆነ ምልክት እናንተ ዘንድ አልተወምን?" ሲለን
"እንዴታ… ትቷል እንጂ።" ኣልነው።
"ምንድነው የተወው? " ኣለን
እኛም "ከሃያሉ ንጉስ የተሰጠውን መፅሃፍ ትቶልናል።" ኣልነው።
"የንጉሱን መፅሃፍ አሳዩኝ። መቸም የንጉሶች መፅሃፍ የግድ ቆንጆ መሆን አለበት።" ኣለንና ቁርኣንን አምጥተን ሰጠነው።
ከዚያም "ይኸንን መፅሃፍ ኣላውቀውም።" ኣለን። እኛም ከቁርኣኑ ምዕራፎች አነበብንለት። ንባቡን በቀጠልን ቁጥርም እሱ ያለቅሳል። እኛም ምዕራፉን እስክንጨርስ እናነብለታለን እሱም ያለቅስ ነበር።
ከዚያም "የዚህ ንግግር ባለቤት ላይ ማመፅ ትዕዛዙን መጣስ አይገባም።" ኣለን። ወዲያውም እስልምናን ተቀበለ። እኛም የኢስላምን ህጎችና ደንቦች እንዲሁም ቁርኣንን አስተማርነውና በመርከባችን አሳፍረነው ይዘነው ሄድን።
ታዲያ በመጓዝ ላይ ሳለን መሸብንና ሲጨልም በየመኝታችን ተኛን። ይህን ግዜ "ይኸ ያመላከታችሁኝ አምላክ ሌሊቱ ሲጨልም ያንቀላፋል እንዴ?" ኣለን።
"አንተ የአላህ ባርያ ሆይ! እሱማ ህያው የሆነ ሁሌም ያልለ ሃያል ነውና አያንቀላፋም።" ኣልነው።
" ታዲያ ጌታችሁ የማይተኛ፣ የማያንቀላፋ ሆኖ ሳለ እናንተ የምትተኙ ከሆነ የማትረቡ ባሮች ናችሁ ማለት ነው።" ኣለንና እኛን ትቶን አላህን ማምለኩን ተያያዘው።
ሃገራችን እንደደረስንም ለጓደኞቼ "ይኸ ሰው ወደ እስልምና በቅርብ የገባና ለሃገሩም እንግዳ ነው።" ብዬኣቸው ገንዘብ ሰብስበንለት ነበርና ወስደን ስንሰጠው "ምንድነው እሱ?" ኣለን።
"ለሚያስፈልጉህ ጉዳዮች ማስፈፀሚያ ታውለዋለህ" ኣልነው።
"ላ ኢላሀ ኢለላህ" ከአላህ በስተቀር በሀቅ ሊመለክ የሚገባው አምላክ የለም! በባህር ደሴቶች ላይ ሳለሁ እሱን ትቼ ጣዖትን ሳመልክ እንዲሁ ያልተወኝ ጌታዬ አሁን እሱን አውቄ ሳለሁ ይተወኛልና ነው እርዳታ የምታደርጉልኝ?! " ኣለንና ለሚያስፈልገው ጉዳይ ሁሉ ለራሱ ወጪውን ለመቻል ተንቀሳቅሶ መስራት ጀመረ። በዚሁ መልኩ እስኪሞት ድረስ ከታላላቅ ሷሊሆች አንዱ ሆኖ ይኖር ነበር። [ረሂመሁላህ]
ከግዜያት በኋላ "ያ ሰው እኮ በጣም ታምሞ በሞት አፋፍ ላይ ነው" በሚል ተነገረኝና ልጠይቀው ሄድኩኝ "የሚያስፈልግህ ነገር አለ ወይ" ብዬም ጠየቅኩት። "የሚያስፈልገኝንማ ያ ወደዚያች ደሴቴ እንድትመጡ ያደረጋችሁ ፈፀመልኝ።" ኣለኝ።
እሱ ዘንድ ቆየሁና እንቅልፌ መጥቶብኝ አይኖቼ ሲያሸልቡ እዚያው ተኛሁ። በዚሁ አጋጣሚ ስለሱ ህልም አየሁኝ። ከዚያም ጭንቅ ብሎኝ ስነቃ ከዚህች ዓለም ተለይቷል።
ከዚያም አጠብኩት፣ ከፈንም አለበስኩትና ቀበርኩት። እለቱ መሽቶ ሲጨልም ተኛሁ። በህልሜም ከአንዲት ውብ ልጃገረድ ጋር ሆኖ ተቀምጦ ባለበት
{وَالْمَلائِكَةُ يَدْخُلُونَ عَلَيْهِمْ مِنْ كُلِّ بَابٍ سَلامٌ عَلَيْكُمْ بِمَا صَبَرْتُمْ فَنِعْمَ عُقْبَى الدَّارِ}[الرعد: 23 – 24] .
“ በመታገሳችሁ በናንተ ላይ ሠላም ይስፈን እያሉ በሁሉም በሮች መላእክት (ሊያበስሯቸው) ወደነሱ ይገባሉ። ከበስተኋላም የተዘጋጀላችሁ ሀገር ምንኛ ያማረ ነው።” የሚለውን የቁርኣን አንቀፅ ሲያነብ በህልሜ አየሁት።» ሲሉ አብዱልዋሂድ ቢን ዘይድ መልካም ገጠመኛቸውን አካፈሉን። ረሂመሁሙላሁ አጅመዒን።
[ كتاب التوابين: 179]
ከዚህ ታሪክ እንደምንረዳው አንድ ሰው የተውሂድ መልዕክት በትክክል ገብቶት፣ የሚፈፅመውን የአምልኮ ተግባር ሁሉ ለብቸኛው ፈጣሪ ጌታችን ብቻ ካደረገና ከጣዖት አምልኮ ከራቀ በዚህች አለም ሆነ በወዲያኛው ዓለም የተሳካ ህይወትን እንደሚጎናፀፍ ነው።
ተውሂድን የያዘ ግንዛቤው የተስተካከለ ነው። ተውሂድን ያነገበ ስለ ዱንያው አይጨናነቅም። በሰውም ላይ ሸክም አይሆንም። ኑሮውን ለማሸነፍ ጥሮ ግሮና ይህን ያመቻቸለትን ጌታውን አመስግኖ በደስታ ይኖራል።
የተውሂድ ትምህርት ውስብስብና ከባድ አይደለም። ለዚህም ነው ያ ዘላን ገጠሬ በእንግዶች የተነገረውን ነገር ወዲያውና በቀላሉ የተረዳው። እያደረግክ ያለኸው አምልኮት ነው። የምታመልከው ደግሞ ፍጡርን ነው። ፍጡር ደግሞ ሊመለክ አይገባውምና ይኸን ትተህ አምልኮ የሚገባውን አምላክ ተገዛ ሲሉት። ሳያወላውል ነው ስህተቱን የተረዳውና ይኸንን በምን አወቃችሁ ሲል ተገርሞ የጠየቃቸው።
ተውሂድ በልቡ የሰረፀ ሰው እዩኝ እዩኝ አይልም። ራሱንም ከፍ አድርጎ ሰዎች በዙሪያው እንዲሰበሰቡ፣ ስጦታና ሰደቃ እንዲያበረክቱለት፣ የሚናገረውን እንዲቀባበሉለት የሚጥር ሳይሆን ባገኘው አጋጣሚ ጌታው ከሱ የሚፈልገውን በመፈፀም በአምልኮ ላይ ፀንቶ ይጓዛል። አላህ ግን የዚህ አይነቱ ባሪያው በሰዎች ዘንድ ቦታ እንዲኖረውና በመልካም አማኝነቱ እንዲዘከር ያደርገዋል። በውናቸው ሆነ በህልማቸው መልካሙን እንዲያዩለት ያደርጋልም።
≅≅≅≅≅≅≅≅≅
🍎የቁርኣን ግብዣ
ሱረቱ አን'ነበእ
🇪🇹ቃሪዕ:–ኢብራሂም ኸይረዲን
«ሰውዬውን ቁርኣንን ሳያዳምጥ፤ በሙዚቃ መሳሪያ የታጀቡ እንጉርጉሮ እና ሙዚቃ የማድመጥ ናፍቆት ዝንባሌው ኖሮት ካየኸው፣
ይህ ቀልቡ ከአላህ ቃል ፍቅር ባዶ ለመሆኑ ጠንካራ ማስረጃ ነው።»
(ኢብኑል ቀዪም)
ዙልሂጃ 11 የዒድ ማግስት"የውሙል ቀር" ማለትም ሁጃጆች ሚና ላይ ተረጋግተው የሚቀመጡበት ዕለት ሲሆን ይህንን ቀን አስመልክተው የአላህ መልክተኛ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
🔖"አላህ ዘንድ ከሁሉም ከቀናቶች በላጩ ቀን የውሙ ነሕር(የዒደል አድሓ ቀን) ነው።በመቀጠልም የውሙል ቀር።" 📚አቡዳዉድ ዘግበውታል አልባኒ ሰሒህ ብለውታል።
🔖አቡ ሙሳ አልዐሽዐሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) የዒድ ቀን ኹጥባ ሲያደርጉ እንዲህ ብለዋል፦
"ከዐረፋ ቀን በመቀጠል ሦስቱ ቀን የዚክር ቀናት በነዚህ ቀናት የሚደረግ ዱዓ ተቀባይነት አለው።ስለዚህም ክጃሎታችሁን ወደ አላህ ከፍ አድርጉ ።" 📚【ተፍሱሩ አጠበሪይ (4/203—206)】
🔖ዒክሪማ (ረዲየላሁ አንሁ) እንዲህ ብለዋል ፦
"ሰሓቦች በነዚህ አያም ተሽሪቅ ቀናት ይህን ዱዓ ያበዙ ነበር። "ረበና አቲና ፊ ዱንያ ሐሰነተን ወፊል አኺራ ሐሰነተን ወቂና አዛበ አንናር።"
📚【ኢብኑ ረጀብ (ለጣኢፍ አልመዓሪፍ)】
የሴቶች አረፋ በሚል ማረድ በሸሪዓዊ እይታ እንዴት ይታያል?
በሸይክ ኢልያስ አህመድ ፊዘሁሏህ
t.me/sultan_54
በዚህ አመት ሐጅ ማድረግ ያልቻላችሁ ኢብኑ ረጀብ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለዋል፡-
«√ ዐረፋህ ተራራ ላይ የመቆም እድል ያላገኘ፣ በሚያውቀው የአምላኩ ወሰን ላይ ታቅቦ ይቁም።
√ በሙዝደሊፋም ማደር ያልቻለ ሰው እሱ ዘንድ ይቃረብበት ዘንድ ለአምላኩ ታዛዥ ሆኖ ይደር።
√ ስጦታንም በሚና ማረድ ያልቻለው ሰው ለአምላኩ ሲል ፍላጎቱን ይረድ (ዝንባሌውን ይቃረን)።
√ ወደ ቤቱ (ከዕባህ) ድረስ በርቀት ምክንያት መድረስ ያልቻለም ከደም ስሩ ቅርብ ወደ ሆነው የቤቱ ጌታ ዘንድ ይከጅል።»
[ኢብኑ ረጀብ: ለጣኢፉ-ል-መዓረፍ: ገፅ 633]
ተክቢራ
በቃሪእ ሰዕድ አልጋሚዲይ ድምፅ
احيوا سنة التكبيــــــــــر
وذكــــــــــروا بها
الله اكبر ، الله أكبر ، الله أكبر
🍃 لاإله إلا الله 🍃
الله أكبـــــــر ، الله أكبـــــــر
🍃 ولله الحمد 🍃
🌸🍃
/channel/sultan_54
🔴 የዛሬው የጁምዓ ኹጥባ
🎙 خطبة الجمعة
عقيدة أهل السنة و الجماعة
✨ የአህሉ አስ' ሱነቲ ወልጀማ0ህ
ዐቂዳ
⚠️ሊደመጥ የሚገባ ኹጥባ❗️
🎙በኡስታዝ ሱልጧን ኸድር
💫የአጅሩ ተካፋይ እንድንሆን ሼር!
🕌 ቃሊቲ ሀምዛ መስጂድ
🗓 ዙል ሒጃ 3/1446 አ/ሂ
http://t.me/kalityhamzamesjid
«በትክክለኛው እና ሚዛን በሚደፋው አቋም፤
ጥፍር እና ፀጉር መቁረጥ ክልከላ ኡድሂያ የሚያርደውን አካል (አባወራውን) ብቻ እንጂ መላ ቤተሰቡን አይመለከትም። በተለይም ገንዘቡን አውጥቶ ኡድሒያ የገዛውን ሰው።»
✍(ኢብኑ ባዝ)
📚ፈታዋ ኢስላሚያ (2/316
“ሰላት በሸሪዓችን ከተደንገገበት ሚስጥሮች አንዱ ከዱንያዊ ችግሮች፣ መከራዎች እና ጭንቀቶች እረፍት በማድረግ (በመገላገል) ወደርሷ ለመጠጋት ነው።”
(ኢማሙ አሽ ሻጢቢይ)