የሁለቱን አንጃዎች የእርቅ ዜና ስትሰሩ የነበረውን ጥል እንዲህ ቀላል አደረጋችሁትሳ ?
👇
" በቃ የሚበቃንን ያህል ተቧቅሰናልና ምንም እንዳልተፈጠረ ቆጥረን ወደየስራችን እንሂድ "
( ለዛውም በአንድ መኪና? ደጀን ? መቀሌ ? 😂)
የታደሰ ወረደ ሲገርመን የሃይማኖት ግርማ ይምጣብን ?
እስኪ ምቱት ....2 ሚሊዬን ድርሃም ማለት ስንት ሚሊዬን ብር ማለት ነው ግን ?
ታደሰ ወረደ ግን ውለታ አይረሳም !!
ሆሆ ...ቲማቲም ይበል ? ..😂😂
...እስኪ - Goodnight !
" ዶናልድ ትራምፕን አለመታዘዝ ፈጣሪን አለመታዘዝ ማለት ነው"
- አዲሷ የዋይት ሃውስ የእምነት መሪ (faith leader) Paula white
P.s
እውነት ለመናገር ዶናልድ ትራምፕ እንደ አንዳንዶቹ የአገር መሪዎች የሃይማኖት ፀር አይደለም።እንደውም አማኝ ነው።እንደው እኔን የሚገርመኝና ሁሌም የምጠይቀው ነገር ' ይቺ አሜሪካ የምትባል አገር ብዙ የሚያነጋግሩና ከተለምዶው የወጡ ክስተቶችን በየጊዜው የማስተናገዷ ነገር በአጋጣሚ ነው ወይስ በእቅድ ነው ? ' የሚለው ነው 😎
ጥሪ ከህወሓት ጋር እየሰራችሁ ለምትገኙ ወንድምና እህት የወልቃይት ጠገዴ ጠለምት ተወላጆች !
በአሁኑ ወቅት የህወሓት አመራሮች በስልጣን ሽሚያ እርስ በራሳቸው መስማማት ተስኗቸው ከፍተኛ ትንቅንቅ ላይ መሆናቸውን ከእናንተ በላይ ነጋሪ የለም። በዚህ ሳብያም እነዚህ አካላት የመጡበትን የዘር ግንድ ቆጥረው የእኔ ወደሚሉት ህዝብ ተጠግተዋል። እሱ ብቻ አይደለም ህዝቡም ተቀብሎ ዋሻ ሁኗቸዋል ።
የራያ ህዝብ እምቢተኝነቱ አይሏል ። ይህን ጊዜ እናንተን አሰብን ! ወደ አካባቢያችሁ ተመልሳችሁ የበደላችሁትን ህዝብ ይቅርታ በመጠየቅ ባላችሁ ሞያና እውቀት አገራችሁ ገብታችሁ የምታገለገሉበት ቀን ዛሬ ነው !!
ምክንያቱም ትግራይ ውስጥ እናንተ ባዳዎች ናችሁ ። አገራችሁ ግቡ !
ይህን ጥሪ ችላ ልትሉት ትችላላችሁ።
በድጋሚ የወልቃይት ጠገዴ ጎንደሬ አማራ ህዝብን በህወሓት ለማስበላት ፊት አውራሪ ሆነን እንመጣለን ብላችሁ ግን እንዳታስቡት ትመከራላችሁ።
በደብረፅዮንና በቮድካው አንጃዎች መካከል ያለው... current state of affairs !
.
Night !
"ዶላርን አንጠቀምም ካላችሁ ማዕቀብ እጥላለሁ - ወደ አሜሪካ በምትልኩት ምርቶቻችሁም ላይ ታሪፍ እጨምራለሁ" የሚለው የአሜሪካ ዛቻ 32 ሰከንድ ብቻ በፈጀ አጭር ቪዲዮ ሲብራራ ....
እስኪ ....Goodnight !!
እግረ መንገድ ...
ጄኔራል ፍስሃ ኪዳኑ(ማንጁስ) በትግራይ ጊ/አ የፀጥታ ሃላፊ ነው።በጊዜያዊ አስተዳደሩ የበላይ ሃላፊውን 'ቮድካውን' ከስልጣን ለማስወገድ ሌት ተቀን የሚባዝን የደብረፅዮን ባለሟል ነው። ይህ ደብዳቤ በራሱ በቮድካው የተሾሙትን የካቢኔ አባላት ለማስወገድ አስቦ ለሰኞ ጥሪ ያደረገበት ደብዳቤ ነው።
ይኼውልህ ...ከተሰጠህ የስራ መደብ ውጪ በተቃራኒው ከቆምክና በሌላ የሴራና የሸፍጥ ድር ከተተበተብክ እንዲህ ነው የምትሆነው - ደብዳቤ መፃፍ ሁላ ያቅትሃል።እራስህ ላኪ ሆነህ ለፃፍከው ደብዳቤ ተቀባዩ ራስህ ትሆናለህ።ላኪም ተቀባይም!
😂
ከአራት አመት በፊት ዳንኤል ብርሃኔ የዲጂታል ወያኔ ፊታውራሪ እያለ ከበቃሉ አላምረው ጋር እየተጨዋወቱ ነው ....
በዚህ ጨዋታቸው መካከል ላይ ዳንኤል ብርሃኔ " ወልቃይት (ወፍአርግፍ) ውስጥ ኮረብታው አካባቢ ከሚኖሩት ጥቂት ሰዎች ውጪ አማርኛ የሚናገር ሰው'ኮየለም " እያለ ሲበጠረቅ የበቃሉን መፍነሽነሽ ተመልከቱ እስኪ።
ቪዲዮን እስከመጨረሻ ተመልከቱት .....ለወራት ስትመኘው የነበረውን የትዳር ጥያቄ የተሰነዘረላት አንዲት አፍቃሪ ፊቷ ላይ ሊነበብ የሚችለውን የመፍነሽነሽ ስሜት እኮ ነው ከበቃሉ ፊት ላይ የሚነበበው።
አይነበብላችሁም ?
ዶክተሩ ካበደ ያበደውን ሁላ ማን ሊያክመው ነው ግን ??
ይህ ደቅዳቂት ነገር ዶ/ር ሃየሎም ይባላል! ! የደብረፅዮን ቀንደኛ ደጋፊ ነው።
ምን እያለ ነው ግን ? እስኪ ለማንኛውም ስሙት 👇
///መቼም የማልሰማው የለም።ትናንት ጌታቸው ረዳ በፍርሃት ሲንቀጠቀጥ አድሯል አሉ።ከፍርሃቱ የተነሳ ያንን ጂኑን ሲልፍ ነው ያደረው።ስማኝ አንት መሃይም ደንቆሮ ትግራዋይ - የኛ ጄኔራሎች እኮ ጌታቸው ረዳን ይቅርና ምስራቅ አፍሪቃን መድምሰስ የሚችሉ ናቸው።በነገራችን ላይ የመሃይም አይኖች እኮ ጎላ ጎላ ያሉ ናቸው። ደብረፅዮንን ግን አይታችሁታል? የደብረፅዮን ዓይኖች እኮ በመነፅር የተከለሉ ናቸው።ምሁር ማለት እንደዛ ነው።ልክ እንደ መለስ አንባቢ ነዋ።አሁን ፃድቃን ጄኔራል ነው ? - እኔ ዶክተር ሃየሎም ከፃድቃን በላይ ጄኔራል ሆኜ መምራት እችላለሁ።በፖለቲካውም ቢሆን እኔ ከጌታቸው ረዳ በላይ ፖለቲከኛ ነኝ ///
**ዶክተሩ ካበደ ያበደውን ሁላ ማን ሊያክመው ነው ግን ??
ጓደኛዬ ፣ ወንድሜ ጎኔ ....ልቤን ሰበርከው ።
አድምጠው ሰረበ - ነብስህ በሰላም ትረፍ !
Let me be ,for once, an innocent 'rude' .
የደቂቀ ስብሃት ነጋ የ"አባይ ትግራይ" ህልም ይሳካልን ?
እስኪ......Goodnight !
ከኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በኋላ ከህወሓት የተባረሩበትን ሁኔታ ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ሲያስረዱ👇
// መለስ ዜናዊ "እያበላና እያለቀሰ" ነው አባላቱን በማሳመን ድጋፍ ያሰባስብ የነበረው ።ለነገሩ ያኔ እነሱ ቀድመው ባያሰናብቱኝ ኖሮ እኔው እራሴ ህወሓትን ለመልቀቅ ውሳኔ ላይ ደርሼ ነበር //
- ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ
ዛሬ ጧት ደብረፅዮን (አደመ) ባሰማራቸው ታጣቂዎች የተሞከረው መፈንቅለ ሬዲዮ ጣቢያ ከሸፈ 😂
የከተማዋ ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል ተብሏል።
ደብረፂዮን "ደርግ ሲጠቀምበት የነበረውን ሬዲዬ ጣቢያ ......ተቆፃፂሩ " ብሎ ሰበር እንዳልሰራ ዛሬ "ቮድካው ሲጠቀምበት የነበረውን የመቀሌ FM 104.4 ሬዲዮ ጣቢያ ጀግናው የድንኩል ሰራዊት ዛሬ ግንቦት ሃያ ተቆፃፂሩ"
ብሎ ዜናውን ሊሰብር ለጥቂት ...😂😂
ዳደ ደስታ እና Co. - የአቦይ ስብሃትን ሴራ ሸፍጥና ተንኮል ወርሳችሁ የለ? ከዘራውን'ማ ተዉላቸው እንጂ 😂
Читать полностью…የጎረሰውን የሚተፋው የአገሪቱ የሶሻል ሚዲያ ውሪ "በሁለቱ የወያኔ አንጃዎች መካከል እርቅ ሊወርድ ነው" በሚል ዜና ፕላትፎርሙን አጨናንቀውት አየሁ።
ምንም ፕሮፌሽናሊዝም የማይነካካቸው የአገራችን የዩቲዩብ ሲቪል ጋዜጠኞችም ይሄንኑ ይዘው አላዘኑብን።
እነ...
-ጉዕሽ (የአለም ገብረዋህድ አማች)
- ዳደ ደስታ (የአቦይ ስብሀት ከዘራ ወራሽ)
- ዶር ዘረሰናይ ( በጦርነቱ ጊዜ በውጪ አገር የወያኔ ተወካይ የነበረ)
- ጄ/ል ጆን መዲድ( ለደብረፂዮን የወገነ)
ወዘተ የመሳሰሉት ሰዎች ሽማግሌ ናቸው በተባሉበት በዚህ ሂደት ላይ ምን አይነት ሽምግልና ሊኖር እንደሚችል ለኔ ግልፅ አይደለም።
እነዚህ ሰዎች ቮድካው የሚመራውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን እንዴት ማፍረስ እንደሚቻል በአቦይ ስብሃት ሰብሳቢነት ለወራት በተከታታይ ሲመክሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው።ይሄንን እውነታ ደግሞ ቮድካው አሳምሮ የሚያውቀው ሃቅ ነው።
እኔ ሁለቱ አንጃዎች ታርቀው የትግራይ ህዝብ ሰላም ቢያገኝ ምኞቴ ነው።መታረቅ እያለ መጣላትን ምን አመጣው? 😎
ሆኖም ግን የኔ ምኞት ሌላ ... የተወራው የእርቅ ሂደት ደግሞ ሌላ ናቸው።
ባጭሩ ነገና ተነገ ወዲያ ሌላ ወሬ ትሰማላችሁ!!
Mark my words - ይቺን የኔን ሃሳብ መዝግባችሁ ያዟትና ኋላ ላይ እናወራርዳታለን።
ማርያማዊትን ምን ነካት ግን ? የባጀተችበትን ደረማመሰችው እኮ !
ፀላኤ ሰናይ ርቋታል 😂
ዋይት ሃውስ ውስጥ አንድ "የእምነት መሪ" የሚል የስራ ሮል አለ።
Paula white የዚህ ቢሮ ሃላፊ ሆና በዶናልድ ትራምፕ ተሹማለች።
-------
Paula Michelle White-Cain is an American televangelist, apostolic leader in the Independent Charismatic movement, and a proponent of prosperity theology.
ግልፅ መልዕክት (በቃላት ያልተሽሞነሞነ ጥሬ ጥሪ)
ሁሉም ከወገኑ ጋር እየተሰለፈ ባለበት ባሁኑ የትግራይ ፖለቲካ ውስጥ ለወያኔ ያደሩት የወልቃይት ጠገዴ ሰዎች ዛሬም ልብ አለመግዛታቸው ምን አይነት መረገም እንደሆነ ምንም ሊገባኝ አልቻልም።
አሁን አሁን ሳስበውማ "ጭራሽ መንገድ መሪ ሆነው ለመምጣት እያሰቡ ይሆን ?" እያልኩ መጠርጠር ጀምሬያለሁ። ሃሳባችሁ እንዲያ ከሆነ ይቅርባችሁ አታስቡት።ካልሆነ ግን አሁንም ከወገናችሁ ጋር ተቀላቅላችሁ ህዝባችሁን የምትክሱበት በር አሁንም ክፍት ነውና እድሉን ተጠቀሙበት።
👇
- ርስቁ አለማው
-ተኪኡ ምትኩ
- ፈረደ የሺወንድም
- ገዛኢ ዳኘው
- ልዕልቲ ሽባባው ...ወዘተ
እንዲሁም ምንም እንኳን በቁጥር ጥቂት ብትሆኑም በወያኔ ወታደራዊ አደረጃጀት ውስጥ ያላችሁ የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆችም ይህንን መልካም ዕድል ተጠቀሙበት ።
Colombia’s President has confirmed that USAID, along with other US agencies, fund and control entire sections of the country’s police and military. These security forces have committed many human rights abuses in the Americas over the years.
Читать полностью…"የትግራይ ህዝብ የመገንጠል መብቱን ለመጠቀም ወስኗል" እያለ ነው አቶ ስዬ አብርሃ ።
ስዬ አብርሃ በርካታ ጉዳዮችን አንስቷል።
እስኪ ለማንኛውም 👇
/// ጥምረት ጥምረት እየተባለ ነው።ማን ከማን ጋር ነው የሚጣመረው።ባለፉት አመታት ብዙ ነገር ተበላሽቷል ።በትግራይና በአማራ የታጠቁ ሃይሎች መካከል ስለታሰበው ጥምረት ይቅርና የአማራ ሃይሎች እንኳን ይህ ነው የሚባል ጥምረት የላቸውም።ሌላው ቀርቶ ተጣምረን በመታገል የምንታወቀው እኛ ተጋሩም እኮ ዛሬ ላይ አንድ አይደለንም።ኦሮሞም እንደዛው ተመሳሳይ ነው።በጣም የሚገርመው ደግሞ ኢሳያስ አፈወርቂን ሸምጋይ በማድረግ የሚፈጠር ጥምረት ምን አይነት ነው ? የትግራይ ህዝብ የራስን እድል በራስ የመወሰን መብቱን ተጠቅሞ የወደፊት እጣ ፈንታውን ለመወሰን መቁረጡ በኢሳያስ አፈወርቂ ዘንድ እንደማይወደድ እየታወቀና የኢትዮጵያን ህገመንግስት ከጅምሩም አምርሮ እንደሚጠላው እየታወቀ ኢሳያስ ይደግፈናል ብሎ ማሰብ ምን አይነት ድንቁርና ነው ?ምን አይነት እብደት ውስጥ ነው የገባነው? ///
ደብረፄን ...፣
ሃዲአ አላ እወ ለብዘበኔ፤
ጌታቸው ....፣
እንድዕላላቸው ፤
===================
ቆይ እስኪ ግን "የደብረፅዮን አንጃና ሻዕቢያ በፍቅር 'እፍ ክንፍ' ብለዋል " እሚባለው ነገር የምር ሆነ ማለት ነው እንዴ ?
በውጪ ለሚኖሩ ኤርትራውያን በተዘጋጀው በዚህ የሙዚቃ ድግስ ላይ የቀረበው የዚህ ሙዚቃ ጠረን እንዲያ እንዲያ የሚሸት ነው 😂
የሙዚቃው ተቀራራቢ ትርጉም...👇
ደብረፅዮን .... ፣
ዘንድሮ አለ ነገር -- ይኖራል አዎን ፤
እነ ጌታቸው .....፣
እንጃለታቸው ፤
///የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ጥያቄ ትክክለኛ ጥያቄ ነው።በመጀመሪያ ግን የወልቃይት ጠገዴ መሬት ወደ ትግራይ መመለስ አለበት። መሬቱ ወደ ትግራይ ከተመለሰ በኋላ ግን ወያኔ የህዝቡን ጥያቄዎች ለማስተናገድ ቃል መግባት ይኖርበታል ///
- በቃሉ አላምረውና ለመጀመሪያ ጊዜ ያየሁት አንድ ሌላ ጅል
=============
በቃሉ አላምረው እና መሰል አፍቃሬ ወያኔውያን በወልቃይት ጠገዴና ጠለምት የአማራ ህዝብ ላይ ሲያጧጡፉት የባጁት ተከታታይ አሉታዊ ዘመቻዎች እንዲሁ የተሰሩ አልነበሩም። ማሟሟቂያዎች ነበሩ።
ያ ሁሉ መጋጋጥና መላላጥ እዚህ ድምዳሜ ላይ ተደርሶና ተወስኖ አቋም ለመያዝ ያለመ እንደነበር ለማወቅ ልክ እንደበቃሉ አላምረው ትንኝ መሆንን አይጠይቅም።
(edited - ተንታኝ ለማለት ነው )
ትግላችን ዳገቱ ላይ ነው፣ ወልቃይት ጠገዴ አማራ ነው!!
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ አሸተ ደምለው ተድላ በድጋሚ የብልጽግና ምክርቤት አባል ሁነው ተመርጠዋል።
አዲ ክልተ ??
ለዘፀአት የደረሰው መልዕክት... "ከአዲ ነብርኢድ - ጎድፋይ - አዲ ክልተ ወደ ኤርትራ የሚወስድ አዲስ የፒስታ(የጠጠር) መንገድ እየገነቡ ነው" ይላል።
-------------------------
እኔስ ከአንድ ወር በፊት Dec 19 ላይ ምን ብዬ ነበር ?
ወያኔ የተመሠረተበትን አላማና ድብቅ አጀንዳውን በከፊል ለመረዳት ይሄንን ያዳምጡ።
አሁን የወያኔ ወራሽ ነን የሚሉት እነ ደብረፅዮን ይህ የአቦይ ስብሃት አቋምና እሳቤን የሚያራምዱና የሚያስቀጥሉ ናቸው።
አቦይ ስብሃትና መለስ ዜናዊ " ዛላምበሳና ባድመ ለ20 እና ለ30 ዓመታት ከሻዕቢያ ጋር ቢቆዩ ምን ችግር አለው ታዲያ" እንዲሉ ያስገደዳቸው ሌላ ሳይሆን ደማቸው ውስጥ የተዋሃደው የ"አባይ ትግራይ " እሳቤ ነው።
የማታ ማታ የአባይ ትግራይ ምስረታ እውን መሆኑ አይቀርም የሚል ፅኑ አቋም ነበራቸው።
P.S
መተማን እስከ ቤንሻንጉል ድረስ ባካለለውና ወያኔ ባሰራው የታላቋ ትግራይ ካርታ ላይ የተወሰኑትን የአማራ ክልል መሬቶች ለሱዳን መንግስት በአደራ መልክ እንደሰጡስ ታውቁ ነበር ?
የወያኔ ሁነኛ ወዳጅ የነበረው ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የ11 አመት እስራት ተፈረደበት።
-- ታስታውሱ እንደሆነ ባለፈው የትግራዩ ጦርነት ወቅት እሱ የኒውጀርሲ ሴናተር እያለ የተለያዩ HR ሪዞሉሽኖችን በማርቀቅና በማስተባበር ኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብና የውግዘት ውሳኔ እንዲተላለፍ ለኮንግረሱ የሚያቀርብና ጫና ያደርግ የነበረ ሰው ነው።
አሁን የተከሰሰበት ወንጀልም የሚጠቁመው እሱን ነው።
ክሱ "በአይነትና በብር የተለያዩ ጉቦዎችን እየተቀበለ ስልጣኑን በመጠቀም በኮንግረሱ ውሳኔዎች ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ የውስጥና የውጪ ተልዕኮዎችን በማስፈፀም" የሚል ነው።
በትናንትናው ዕለት የተከናወነው የምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሰላማ ወደ ወልቃይት ጠገዴ ጉብኝት በርካታ ታሪካዊና ፖለቲካዊ ትርጉሞችን የያዘ ነው።
ይህ ጉብኝት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ጎንደር ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊ፣ ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስር የሚያሳይ ሲሆን፣ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተፈጠረው የማንነት ጥያቄና የፖለቲካ ውጥረት አውድ ውስጥ ሲታይ ይበልጥ ጠቀሜታ አለው።
ወልቃይት ጠገዴ ለረዥም ዘመናት የጎንደር አካል እንደነበር ይታወቃል። ነገር ግን ከ1984 ዓም ጀምሮ ያለ ህዝቡ ፈቃድና ይሁንታ በጉልበት በትግራይ ክልል ውስጥ እንዲካተት በመደረጉ ምክንያት ነዋሪው ህዝብ ማንነቱን በተመለከተ ከፍተኛ ግጭት ውስጥ መግባቱም በዓለም የታወቀ ሐቅ ነው ።
ይህ ጉዳይ የወልቃይት ጠገዴን ህዝብ ከጎንደር አማራ ህዝብ ለመለየት የተደረጉ ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ተከትሎ የተፈጠረም ነው።
* ትናንት በአቡነ ሰላማ ወደ ወልቃይት ጠገዴ የተደረገው ጉብኝት የሚያመለክተው፡-
1ኛ. * ታሪካዊ ትስስር:
ይህ ጉብኝት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ጎንደር ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊና መንፈሳዊ ትስስር የሚያረጋግጥ ነው።
2ኛ. * የማንነትና አንድነት ማሳያ :
አቡነ ሰላማ በአካባቢው መገኘታቸው የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ጎንደር ጋር ያለውን ማንነታዊ ትስስር ማረጋገጫ ነው።
3ኛ. * የቤተክርስቲያን አንድነት:
የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድነት ላይ ያለውን እምነት ያሳያል።
እንደሚታወቀው በቅርቡ የትግራይ ክልል የራሱን ሲኖዶስ በማቋቋም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድነት ላይ ስጋት ፈጥሯል።
ይህ ደግሞ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብን ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ክርስቲያኖችን አሳዝኗል ።
የአቡነ ሰላማ ጉብኝት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ አንድ ፓትርያርክ አንድ ሲኖዶስ የሚለውን የቤተክርስቲያን መርህ በመደገፍ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድነት ላይ ያለውን እምነት አረጋግጧል።
* መደምደሚያ*
በአቡነ ሰላማ የተደረገው ጉብኝት በወልቃይት ጠገዴ ስላለው የማንነት ጥያቄና የፖለቲካ ውጥረት ብቻ ሳይሆን፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድነት ላይም ጠቃሚ አስተዋጽኦ ያደርጋል።
ይህ ጉብኝት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ከጎንደር ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊ፣ ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስር የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ በተመሳሳይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድነት ላይ ያለውን እምነት ያጠናክራል።
#ወልቃይት_ጠገዴ #ጎንደር #አንድ_ሲኖዶስ #አንድ_ፓትሪያርከ
@hilinaazeze (via FB)
አይይ --- እንዳማሩ አይሞቱ !
ቱጃሯ ወያኔ ጠብሿታል ማለት ነው።
"100 ብር ካልከፈላችሁ አትፈተኑም"
👇
- የማይቅነጣል የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ናቸው።ዛሬ ፈተና ነበራቸው።ለፈተናው 100 ብር ካልከፈላችሁ አትፈተኑም ተባሉ።ተማሪዎቹም "የምን ክፍያ ነው ? አንከፍልም" ሲሉ መለሱ ።በዚህ ምክንያት ግርግር ተነሳ።ታጣቂዎች በጥይት ተኩስ ተማሪዎቹን ከበተኑ በኋላ እየተከተሉ በዱላ ደበደቧቸው ።
ዘኢትገርም 😂