❤️ልብን እንድታፈቅር ላደረገ አላህ♡ ♡ምስጋና የተጋባ ይሁን!!! አላህ ሀላሉን ይወፍቀን አሚን🙏 ለአስተያየታችሁ👉 @Fiamanillah2
قال ﺍﻟﻠﻪ ﺗﻌﺎﻟﻰ :
﴿ﺇِﻥَّ ﺍﻟﻠَّﻪَ ﻭَﻣَﻼﺋِﻜَﺘَﻪُ ﻳُﺼَﻠّﻮﻥَ ﻋَﻠَﻰ ﺍﻟﻨَّﺒِﻲِّ ﻳﺎ ﺃَﻳُّﻬَﺎ ﺍﻟَّﺬﻳﻦَ ﺁﻣَﻨﻮﺍ ﺻَﻠّﻮﺍ ﻋَﻠَﻴﻪِ ﻭَﺳَﻠِّﻤﻮﺍ ﺗَﺴﻠﻴﻤًﺎ﴾
[ ﺍﻷﺣﺰﺍﺏ : ٥٦ ]
አላህ እንድህ ብሏል:-
{አላህና መላዒካዎቹ በነብዩ ላይ ሰለዋት ያወርዳሉ እናንተ ያመናችሁ ሆይ በሱ (በነብዩ) ላይ ሰለዋትና ሰላምን አውርዱ {
የአላህ መልዕክተኛም ﷺ እንዲህ ይሉናል -:
" ﺃﻛﺜﺮﻭﺍ ﺍﻟﺼﻼﺓ ﻋﻠﻲ ﻳﻮﻡ ﺍﻟﺠﻤﻌﺔ ﻭﻟﻴﻠﺔ ﺍﻟﺠﻤﻌﺔ ﻓﻤﻦ ﺻﻠﻰ ﻋﻠﻲ ﺻﻼﺓ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻋﺸﺮﺍ
ﻭ ﺣـﺴـﻨﻪ ﺍﻷﻟﺒﺎﻧﻲ ﻓﻲ ﺍﻟﺴﻠﺴﻠﺔ ﺍﻟﺼﺤﻴﺤﺔ 1407
} # ጁምዐ_ቀንና_ጁምዐ_ሌሊትን በእኔ ላይ ሰለዋት አብዙ። በእኔ ላይ አንድ ጊዜ ሰለዋት ያወረደ ሰው በእሱ ላይ አላህ አስር ጊዜ ሰለዋት {ያወርድበታል
ﻗﺎﻝ ﺻﻠﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻴﻪ ﻭﺳﻠﻢ « ﻣَﻦْ ﺻَﻠَّﻰ ﻋَﻠَﻲَّ ﺻَﻼَﺓً ﺻَﻠَّﻰ ﺍﻟﻠﻪُ ﻋَﻠَﻴْﻪِ ﺑِﻬَﺎ ﻋَﺸْﺮًﺍ »
( ረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዳሉት:-መን ሶላ ዓለየ ሶላተን ሶለልሏሁ ዐለይሂ ቢሃ ዐሸራ ’ )
›› በኔ ላይ አንድ ጊዜ ሶላዋት ያወረደ አላህ በርሱ ላይ አስር ጊዜ ሶለዋት ‹‹ያወርድለታል
▄▀▄▀▄▀ ▄▀▄▀▄▀ ▀▄▀▄▀▄ ▀▄▀▄▀▄
ﺍﻟﻠَّﻬُﻢَّ ﺻَﻞِّ ﻋَﻠَﻰ ﻣُﺤَﻤَّﺪٍ ﻭَﻋَﻠَﻰ ﺁﻝِ ﻣُﺤَﻤَّﺪٍ ﻛَﻤَﺎ ﺻَﻠَّﯿْﺖَ ﻋَﻠَﻰ ﺇِﺑْﺮَﺍﻫِﯿﻢَ ﻭَﻋَﻠَﻰ ﺁﻝِ ﺇِﺑْﺮَﺍﻫِﯿﻢَ ﺇِﻧَّﻚَ ﺣَﻤِﯿﺪٌ ﻣَﺠِﯿﺪٌ
▄▀▄▀▄▀ ▄▀▄▀▄▀ ▀▄▀▄▀▄ ▀▄▀▄▀▄
# ቁርአን_ና_ሃዲሰ
ሼር በማድረግ ላልደረሰው በማድረስ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ
● ▄ ▅ ▆
እሷ:- ህልምህ ምንድነው?
እሱ:- አንቺ..!
እሷ :- እሺ ምን ማደረግ ትፈልጋለህ ?
እሱ:- አንቺን ማግባት
እሷ:- እሺ እኔን ከማግኘትህ በፊት ምን ነበር ህልምህ
እሱ:- አንቺን ማግኘት
#ሀላሊ😍
JOIN US
👇👇👇
@Zakiiir12
@Zakiiir12
«ዘካተ-ል-ፊጥር በሁሉም ሙስሊም ላይ ግዴታ የሆነ ዒባዳ እንጅ በፍላጎት የሚሰጥ ሶደቃ አይደለም!»
Читать полностью…የረመዷን ወር አለቀ ማለት___••••
👉ብርሀናማዉ የራህመት ወር ሊጓዝ ነዉ
👉መተዛዘን ሊቀር ነዉ
👉መስጂዶች ባዶ ሊሆኑ ነዉ💔😢
👉የሞባይል ፕሮፋይሎች ሊቀየሩ ሰአታቶች ቀሩት
👉አለባበሳችን ዲኑ ከሚፈቅደዉ ዉጭ ሊሆን ሸይጧን ሰአቱን እየተጠባበቀ ነዉ
👉ልደት ማክበራችንን (የተለያዩ ወንድና ሴቶች የሚቀላቀሉበትን ፕሮግራም) ልናዘጋጅ የሸይጧንን ሱና ልናስቀጥል ነፍስያ ቸኩላለች
ዋ ---ነፍሴ😭
ሼር አድርጉት
ሁሉም ራሱን ይጠይቅ
@Zakiiir12
የረመዳን 27ተኛ ለሊት
★★★★★★★★★★★
በለይለተል-ቀድር የሚሰራ ዒባዳ ከ83 ዓመት ዒባዳ የሚበልጥ ሲሆን ከነቢዩ ሰሀባዎች ውስጥ፥ ዑመር፣ ኢብኑ ዐባስ፣ኡበይ ኢብኑ ከዕብ፣ ሙዓዊያ፣ ሁዘይፋና ሌሎችም
ለይለተል-ቀድር የረመዳን 27ተኛ ለሊት ላይ ናት ይሉ ነበር!ይህች ለሊትም ዛሬ ቅዳሜ ምሽት ላይ ናትና እንበራታ!
#አደራ ለሁሉም ሙስሊም በመላክ ተባበሩ...
© ለምታቁት ሰው ሁሉ አድርሱ ሼር❤️
የቴሌግራም ቻናላችን ከስር በሊንኩ ይቀላቀሉ👇
/channel/Zakiiir12
ያአላህ የመጨረሻው ጁመአ በረመዷን አላህ ብሎ ቀጣይ አመት ነው እንጂ ረመዷን ከጁመከ ጋ በዚህ አበቃ💔 ረመዷኑን ልንሸኘው ነው እንደተናፈቀ አለቀ በሰራነው ምንጠቀም አላህ ያድርገን🙏👌👌👌👌👌👌👌
Читать полностью…🌙 #ረመዳን 24
لَيْلَةُ الْقَدْرِ خَيْرٌ مِّنْ أَلْفِ شَهْرٍ
መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺሕ ወር በላጭ ናት፡፡
(ቁርዓን 97:3)
#በዱዓእንበርታ 🧡🤲
© | ፍቅር እስከ ጀነት
#ሼር👇
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ ➤@Zakiiir12👈
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ለይለተል-ቀድር መሆኑን ባውቅ ምን ብዬ ዱዓእ ላድርግ?
እናታችን ዓኢሻ -ረዲየ አላሁ ዓንሀ- እንዲህ ብለዋል:–
የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ለይለተል-ቀድርን ባገኝ (ያቺ ለሊት ለይለተል-ቀድር መሆኖን ባውቅ) ምን ብዬ ዱዓእ ላድርግ? ብዬ ጠየቅኳቸው።
እሳቸውም:– « አላሁመ ኢነከ ዓፉዉን ቱሂቡ አል-ዓፍው ፈዕፉ ዓኒ » ( አላህ ሆይ! አንተ ይቅር ባይ ነህ ይቅርታንም ትወዳለህ ይቅር በለኝ) በይ አሉኝ።
(ቲርሚዚይ፣ኢብኑ ማጃህ፣ ኢማሙ አህመድ እና ሃኪም ዘግበውታል)
የቴሌግራም አድራሻችን:– T.me/Zakiiir12
የረመዳን የመጨረሻዎቹ 10 ቀኖች‼️
============================
✔️ የረመዳን የመጨረሻዎቹ አስርት ቀናት «ዐሽረል አዋኺር» ይሰኛሉ።
የረመዳን ቀናቶች ከሌሎቹ የአመቱ ቀናቶች የተለዩና የተባረኩ ናቸው።
የረመዳን የመጨረሻዎቹ አስርት ቀናት ደግሞ ከሌሎቹ የረመዳን ቀናት የተለዩና ድንቅ ናቸው።
*
የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ከምንጊዜውም በላይ በእነዚህ ቀናት ውስጥ ለየት ያሉ እንደነበሩ ከእናታችን ዐኢሻህ ረዲየልሏሁ ዐንሃ የተገኘ ሐዲሥ ይጠቁመናል።
👉ዐኢሻህ ረዲየልሏሁ ዐንሃ እንዲህ ትላለች፥
"كان النبي - صلى الله عليه وسلم - إذا دخل العشر أحيا الليل وأيقظ أهله، وجدَّ وشدَّ المئزر"
"(የረመዳን የመሸረሻዎቹ) አስር (ቀኖች) በገቡ ጊዜ፣
ሌሊቱን ያነጉ (ሕያው ያደርጉ) ነበር፣ ቤተሰባቸውን ያነቁ ነበር፣ የሚጠነክሩና ሽርጣቸውን ያጠብቁ ነበር።"
[ቡኻሪ፥ 2014
ሙስሊም፥ 1174]
"ሽርጣቸውን ያጠብቁ ነበር!" የሚለው ገለጻ በዒባዳ ላይ ይታገሉና ይተጉ ነበር ለማለት ነው ተብሏል።
አንዳንድ ዑለሞች ደግሞ ሚስቶቻቸውን ይርቁ ነበር ለማለት የተፈለገበት የአሽሙር አገላለጽ ነው ብለዋል።
*
👉 አሁን ከርሷው በተገኘ ሌላ ሐዲሥ ላይ እንዲህ ትለናለች፥
"كان رسول الله - صلى الله عليه وسلم - يجتهد في العشر الأواخر ما لا يجتهد في غيره"
"(በረመዳን) የመጨረሻዎቹ አስርት ቀናት ውስጥ ነብዩ ﷺ በሌሎች (ቀናት) የማይታገሉትን ይታገሉ ነበር። (በዒባዳ ይበልጥ ይበረቱ ነበር።)"
[ሙስሊም፥ 1175]
||
ከነዚህ ሁለት ሐዲሦች የምንረዳው፤
ነብያችን ﷺ በመጨረሻዎቹ የረመዳን ቀኖች ከምንግዜውም በላይ በዒባዳ ይተጉ እንደነበር ነው።
*
እነዚህን የረመዳን የመሸረሻ አስር ቀናት ይበልጥ ልዩ ከሚያደርጋቸው ነገሮች መካከል አንዱና ዋናው፣
የመወሰኛዋ ሌሊት (ለይለተል ቀድር) በነዚህ አስርት ቀናት ውስጥ የምትገኝ መሆኗ ነው።
በዚህች የተባረከች ሌሊት የሚሰራ መልካም ስራ ከሰማኒያ ሶስት አመት በላይ ከሚደረግ ስራ በላይ ይበልጣል።
||
ስለዚህ በእነዚህ የተባረኩ ቀናት ውስጥ፣
ከምንጊዜውም በላይ ራሳችንንና ቤተሰባችንን በዒባዳ ልክ እንደ ነብያችን ﷺ ልንነቃና ልናነቃ ይገባል።
||
በነዚህ ቀናት ውስጥ ነቅተን የምንሰራው ስራ ጫት በመቃም ዲቤ እየወገርን መጨፈር ሳይሆን፣
የሚከተሉትን ነው።
✔️ ለይለተል ቀድርን መጠባበቅ፣
✔️ኢዕቲካፍ መውጣት፣
✔️ቁርኣን ይበልጥ ማብዛት፣
✔️በአላህ መንገድ ላይ ሶደቃ ማውጣት፣
✔️ሌሊቱን በዒባዳ ማሳለፍ (ሐይ ማድረግ)፣
✔️ቤተሰባችንን ማንቃት፣
✔️ሽርጥን ማጥበቅ፣
✔️ተሀጁድና ሌሎች ትርፍ ሶላቶችንም ጠንቅቆ መስገድ፣
እንዲሁም ሌላም ተጨማሪ ማንኛውንም መልካም የሚባል ተግባር ከወትሮው ይልቅ ይበልጥ ማብዛት።
||
የአላህ ፈቃዱ ከሆነ፣
ኢዕቲካፍ፣ ተሀጁድ፣ ለይለተል ቀድር እና ኢዕቲካፍ የሚሉ ርዕሶችን በተናጠል የምመለስባቸው ይሆናል።
አላህ ረመዳንን የምንጠቀምበት ያድርገን።
||
Murad Tadesse
*
ለይለቱል ቀድር‼️
==========
ክፍል:-①
#ሼር_አድርጉት
ለይለቱ-ልቀድር ማለት ምን ማለት ነው?
✍«ለይለተል ቀድር ማለት በአጭሩ የመወሰኛይቱ ሌሊት ማለት ነው፣ ይች ለሊት ትልቅ ቀድር ወይም ደረጃ ያላት ለሊት ናት በተጨማሪም ፍጡራንን የሚመለከቱ የአመቱ ውሳኔዎች የሚተላለፍባት ለሊት ናት።
||
የለይለቱል-ቀድር ደረጃዎች:-
①) ቁርኣን የወረደባት ለሊት ነች፡፡
አምላካችን አላህ እንዲህ ብሏል፡-
إِنَّا أَنزَلْنَاهُ فِي لَيْلَةِ الْقَدْرٌِ
እኛ (ቁርኣኑን) በመወሰኛይቱ ሌሊት አወረድነው፡፡
📒ቅዱስ ቁርኣን ሱራ አል-ቀድር (1)
②) በርሷ ላይ የተፈፀመ ዒባዳ ከሌሎች ለሊቶች በተለየና ምንዳው የበለጠ ነው።
አምላካችን አላህ እንዲህ ይላል፡-
لَيْلَةُ الْقَدْرِ خَيْرٌ مِّنْ أَلْفِ شَهْرٌٍ
መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺሕ ወር በላጭ ናት፡፡
📒ቅዱስ ቁርኣን ሱራ አል-ቀድር (3)
③) በርሷ ውስጥ መላእክት ኸይርን ይዘው ወደ ምድር ይወርዳሉ፡፡
አምላካችን አላህ እንዲህ ይላል፡-
تَنَزَّلُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ فِيهَا بِإِذْنِ رَبِّهِم مِّن كُلِّ أَمْرٌٍ
በርሷ ውስጥ መላእክትና መንፈሱ በጌታቸው ፈቃድ በነገሩ ሁሉ ይወርዳሉ፡፡
📒ቅዱስ ቁርኣን ሱራ አል-ቀድር (4)
④) ለሊቷ ዒባዳህ የሚበዛባት፣ ሰላም የሚሰፍንባት ለሊት ናት፡፡
አምላካችን አላህ እንዲህ ብሏል፡-
سَلَامٌ هِيَ حَتَّىٰ مَطْلَعِ الْفَجْرٌِ
እርስዋ እስከ ጎህ መውጣት ድረስ ሰላም ብቻ ናት፡፡
📒ቅዱስ ቁርኣን ሱራ አል-ቀድር (5)
⑤) የተባረከች ለሊት ናት።
አምላካችን አላህ እንዲህ ብሏል፡-
إِنَّا أَنزَلْنَاهُ فِي لَيْلَةٍ مُّبَارَكَةٍ ۚ إِنَّا كُنَّا مُنذِرِينٌَ
እኛ (ቁርኣኑን) በተባረከች ሌሊት ውስጥ አወረድነው፡፡ እኛ አስፈራሪዎች ነበርንና፡፡
📒ቅዱስ ቁርኣን ሱራ አድዱኻን (3)
⑥) በዚች ለሊት አላህ በአመቱ ውስጥ ያሉ የፍጡራኑን የእድሜ እና የሲሳይ ልኬታዎችን ይፅፋል፡፡
አላህም እንዲህ ብሏል፡-
فِيهَا يُفْرَقُ كُلُّ أَمْرٍ حَكِيمٌٍ
በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል፡፡
📒ቅዱስ ቁርኣን ሱራ አድዱኻን (4)
⑦) በዚያች ለሊት ምድር ላይ የሚኖሩት የመላእክት ብዛት ከጠጠሮች ብዛት የበዛ ነው፡፡
⑨) ለተጠቀመባትና አጅሩን ከአላህ ላሰበ ሰው ከወንጀል መማርያ ለሊት
ነች፡፡
ነብዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡-
«ለይለተልቀድር አምኖ እና አስቦ የቆመ ሰው ያለፈ ወንጀሉ ይታበስለታል»፡፡
📒ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
✔️ስለዚህ ይህቺን ወሳኝና እጅግ የላቀ ዋጋ ያላት ለሊት ለማገኘት የምንችለውን ሁሉ ልንጣጣር ሌሎችንም ልናበረታታ ይገባል፡፡
ኢብኑልቀይም (ረሒመሁላህ) ይችን ንግግር ተናገሩ:-
«ለይለተልቀድር በአመት ውስጥ የምትገኝ አንዲት ቀን ብትሆን እርሷን
ለማገኘት ስል አመቱን ሁሉ እቆም ነበር፡፡ #በረመዳን አስር ለሊቶች ውስጥ ከሆነችማ ምን ነካህ? እንዴት እዘናጋለሁ?!» አሉ።
♣️
✔️ለይለቱልቀድር የምትገኘው በየትኛው ጊዜ ነው?
ለይለተልቀድር የምትገኘው በረመዳን ብቻ ነው፣ ከረመዳንም ደግሞ በመጨረሻዎቹ አስሮች ውስጥ ነው፡፡ ይህንንም የሚያስረዳን ነብዩ (ሰለላሁ
ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ማለታቸው ነው፡-
«ይቺን ለሊት እየፈለግኩ የመጀመሪያውን አስር ኢዕቲካፍ አደረግኩኝ፣ ከዚያም መካከለኛውን አስር ኢዕቲካፍ አደረግኩኝ፣ ከዚያም (የሆነ አካል) መጥቶኝ "እሷ በርግጥም
የመጨረሻው አስር ላይ ናት" ተባለኝ» ማለታቸው ነው፡፡
*
ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) በሐዲሣቸው እንዲህ ብለዋል፡-
«በሱ (በረመዳን) ውስጥ ከአንድ ሺ ወር የምትበልጥ ለሊት አለች፣ የርሷን ኸይር
የተነፈገ በእርግጥም "ትልቅ ነገር" ተነፍጓል»፡፡
📒አስ-ሶሒሕ
♣️
✔️ ስለዚህ ወንድሞችና እህቶች ይቺ ታላቅ ለሊት እንዳታልፈን የምንችለውን ሁሉ ልንጥር ይገባል፡፡
ፁሁፍ ሲንዛዛ አልወድም እንዳላበዛባችሁ
ክፍል:-② ነገ ይቀጥላል…
④) ለይለቱል ቀድርና ምልክቶቹ?
⑤) ለይለተልቀድር በአይን ትታያለች?
⑥) የዚያች ምሽት ተወዳጅ ዱዓእ ምንድነው?
||
ሼር አድርጉት‼️
#ወሰላሙዓለይኩም
==========
✍Yasin M...
==========
ቻናሉን ያልተቀላቀላችሁ ተቀላቀሉ👇
/channel/Zakiiir12
ረመዷን - 17
******
ረመዷን 17 በኢስላም ታሪክ ልዩ የታሪክ ቀን ነው፤ ታላቁ የበድር ጦርነት።
በድር እውነትም እንደ ሥሙ በድር ነው፤ ሙሉ ጨረቃ ነው፡፡ የመጀመርያዎቹ የነቢ ሙሐመድ ተከታይ ሙስሊሞች በአሳዳጅ ጠላቶቻቸው ላይ ትልቁን ድል የተቀዳጁበት ቀን ነው፡፡ በዚህ ቀን ዉስጥ
- እውነት ሀሰትን አሸነፈ፣
- ብርሃን ጨለማን ገረሰሰ፣
- ኢማን በክህደት ላይ ነገሠ፣
በዚህ ቀን ዉስጥ የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) ኩታቸው ከላያቸው ላይ እስኪወርድ ድረስ አምላካቸዉን ቆመው ለመኑ፤ ፈጣሪያቸዉን አብዝተው ተማፀኑ፡፡ ለደካማ አማኞችህ ድልን ስጥ አሉ፡፡ አላህም የነቢያቸዉን ዱዓ ሰማ፣ በሱ ያመኑትን ረዳ፣ አምባገነኞችን ሰበረ፣ ጨቋኞችን ደመሰሰ፣ ትእቢተኞችን አዋረደ፣ ጉረኞችን አሳፈረ፡፡
በበድር ዉሎ ጥራት ብዛትን አሸንፏል፣ ኢማን ኩፍርን አክስሟል፣ ደካማ ጠንካራ ነኝ ያለዉን ድል ነስቷል፡፡
የበድር ዉሎ የተዓምር ዉሎ ነበር፡፡ ታሪኩ አይጠገብም፣ ትንግርቱ ተቀድቶ አያልቅም፣ አላህ ሙስሊሞችን በመላእክት ሠራዊት ጭምር አገዘ፣ ትላልቅ የቁረይሽ ባለሟሎችን ገነደሰ፡፡
በድር - አላህ (ሱ.ወ) ሁሌም ከደካማ አማኞቹ ጋር እንደሆነ ያስታዉሰናል፡፡ ታሪኩን አጥኑ፣ ገድሉን አስተንትኑ።
Muhammed Seid Abx
@Zakiiir12
አሰላሙ ኣለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ። ወንድሞችና እህቶች እንዴት ናችሁ?
ሁላችሁም እንደምታውቁት ያለነው በተከበረው የረመዳን ወር ውስጥ ነው። በዚህ በተከበረ ወር አላህ (ሱ.ወ) ዱዓችንን እነደሚሰማን ከመቼውም ጊዜ በተሻለ እርግጠኛ ልንሆን ይገባል። እየፆምን፣ ሌሊቱን ከኢማሞቻችን ጋር እየቆምን አቅም በፈቀደው ሁሉ ሰደቃ እየሰጠን እና ወደ አላህ የሚያቃርቡን መሰል ተግባራትን እያከናወንን መሆኑን እርገጥ አነበል። ስለሆኑ ከአላህ (ሱ.ወ) እዝነቱን እንከጅላልን። ሀገራችን ያለችበት ሁኔታም በጣም አሳዛኝ እንደሆነ ከሁላችንም የተሰወረ አይደለም። ህዝበ ሙስሊሙ ያለበት ተጨባጭ በጣም ያሳዝናል የመጣብንን በላእ(ፈተና) ከዱዓ ውጭ የሚመልሰው ነገር ስለሌለ በዱዓ እንበርታ ለማለት እወዳለሁ። ዱዓ በኢስላም ትልቅ ቦታ ስለመኖሩ ማሳያ ቁርአን መጀመሪያ ሱረቱል ፋቲሃ በዱዓ ጀምሮ በሱረቱ ናስ መጨረሻ ላይ በዱዓ ይጨርሳል። ይህ መልእክት ለኛ ትልቅ ቁም ነገር አዘል ነው። ዱዓ ለዱንያም ሆነ ለአኼራ ህይወታችን ቁልፍ ነው። "ዱዓ እራሱ ዒባዳ ነው" ይላሉ ነብዩ (ሰዐወ)
ነብዩ ሙሀመድ ዓልይሂ ሶላቱ ወሰላም ሶስት (3) ሰዎች ዱዓቸው አይመለስም ይላሉ . . . እነሱም ፍትሃዊ የሆነ ኢማም (መሪ)፣ ፆመኛ በሚያፈጥርበት ወቅት እና የተበዳይ ዱዓ ናቸው። እኛም ፆመኞች ሆነን ጥሪያችን ተቀባይነት አለውና በዱዓችን እንበርታ።
ሀገራችንን አላህ ሰላም ያድርግልን።
Dr mohammedzien
አብሽሪ እህቴ ይህም ያልፋልን!
አቡ ዳውድ ኡስማን
የራሳቸውን እና የቤተሰባቸውን ህይወት ለመቀየር ከቤተሰባቸው እና ከሃገራቸው ተሰደው በአረብ ሃገራት በስራ ላይ የሚገኙ እህቶቻችን በተለይ በዚህ ባለንበት የረመዳን ወር እጅግ ስራ የሚበዛባቸው እና የሚደክሙበት ወቅት ነው::
ሌላው ፆሙን በተለያዩ ኢባዳዎች ለማሳለፍ ሲጥር እህቶቻችን ግን በማድቤት ስራ ለኢፍጣር ምግብ ሲያዘጋጁ፣ከተፈጠረም ቡሃላ ሲያነሳሱ እና ሲያጣጥቡ አምሽተው ከዛም አልፎ ለሱሁር እየተነሱ ሌላውን ፆም ያሲዛሉ::
ይህን ሁሉ ልፋት በሃገር ቤት ላሉት ለቤተሰቦቻቸው ህይወት መቃናት በማሰብ ነው!
አብሽሪ እህቴ ይህም ያልፋል!
እህቶቻችንን የድካማቸውን እና የልፋታቸውን ውጤት የሚያገኙበት ፣ሃሳባቸው ተሳክቶ ለሃገራቸው የሚበቁበት ፣እየለፉ ያሉትን ልፋትም ኒያቸው አምሮ ታላቅ ምንዳ ከአላህ የሚያገኙበት ረመዳን ፆም አላህ ያድርግላቸው!
አሚን @Zakiiir12
ይደመጥ
ሼህ ሙሀመድ ሀሚዲን በግልፅ ሙነሺዶችንና ነሺዳን በተመለከተ መልስ ሰጡ
@Zakiiir12
የረመዷንን ሌቦች ተጠንቀቁ
አንደኛው ሌባ ፡-
ቴሌቭዥን ፡ ለሥጋም ሆነ ለመንፈስ ከፍታ አጋዥ ካልሆኑ የረመዷን ሙሰልሰላቶችን እና አዘናጊ ድራማዎችን ተጠንቀቁ፤ የረመዷን ዉድ ጊዜያት ለዉድ ነገሮች መዋል አለባቸው፡፡
ሁለተኛው ሌባ ፡-
ስልክ፡፡ ብዙ ማውራት ለብዙ ስህተት ያጋልጣል፣ ትርፍ ንግግር ወደ ሀሜትና ያልታሰቡ ወንጀሎች ይመራል፤ ለተሻለ ምንዳ በረመዷን በንግግር ጭምር ቁጥብ መሆን ያስፈልጋል፡፡
ሦስተኛ ሌባ ፡-
ወጣ ገባ ማብዛት/መዞር፡፡ በረመዷን ከመስጊድ እና ከቤት የበለጠ ማረፊያ የለም፡፡ ወደ ከተማም ይሁን ወደ ገበያ ያለበቂ ምክንያት ወጣገባ ማብዛት ዐይንንም ሆነ ጆሮን ያልሆነ ነገር ይጥላል፡፡ ፆምን ይሰርቃል፤ ምንዳዉንም ያጓድላል፡፡
አራተኛ ሌባ ፡-
ማምሸት፡ ያለምክንያት ማምሸት ኪሳራ እንጂ ትርፍ የለዉም፡፡ የረመዷን ምሽቶች ምርጥና ዉብ ናቸው፡፡ በቁርኣን፣ ዚክር እና በተለያዩ ዒባዳዎች መዋብ አለባቸው፡፡
አምስተኛ ፡-
ኩሽና ፡፡ በተለይ ለሴቶች፡፡ ሙሉዉን ረመዷን ማዕድ ቤት የሚያሳልፉ ቁርኣንን፣ ሶላትና ዚክርን የረሱ ብዙ ናቸው፡፡ ረመዷን የፆም ወር ነው፡፡ ትልቁን ትኩረት ለሆድ መስጠት ዓላማዉን መሳት ነው የሚሆነው፡፡
ስድስተኛ ሌባ ፡-
ስስት ፡፡ የረመዷን ዉስጥ ሶደቃ ምንዳው ትልቅ ነው፡፡ ስስት ግን ምንዳን ያስከለክላል ፤ አጅርን ያሳጣል፤ መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡
ሰባተኛ ሌባ ፡-
ሥራ መፍታት፡፡ ሙእሚን ሁሌም ጠቃሚ በሆነ ሥራ ላይ መገኘት አለበት፡፡ ያለ ምንም ምክንያት ጊዜን ማቃጠል ዕድሜን ሳይጠቀሙበት ማሳለፍ የኪሣራዎች ሁሉ ትልቁ ኪሣራ ነው፡፡
ስምንተኛ ሌባ ፡-
ሶሻል ሚዲያ፡፡ ዛሬ ላይ የብዙዎቻችን ችግር ሆኗል፡፡ በቤትም ሆነ በመስጊድ ሳይቀር ትልቅ ትኩረት ሰጥተነው ጊዜያችንን እየጨረስንበት ነው፡፡ በዚህም ከዚክር፣ ከቁርኣን፣ ከዱዓ እንዳንጠቀም ሆነናል፡፡ እንጠንቀቅ፡፡
http://t.me/Zakiiir12
"የፍቅር መጀመሪያው ትዳር
ሲሆን መጨረሻው ደሞ ጀነት ነው"
𝕛𝕠𝕚𝕟 𝕦𝕤
👇👇👇
@zakiiir12
@Zakiiir12
እንኳን ለ1442ኛው የዒዱል ፊጥር በዓል አላህ በሰላም አደረሳችሁ!
ዒዱኩም ሙባረክ!
ተቀበለላሁ ሚንና ወሚንኩም!
ሰበር‼
======
✍ በሳዑዲ ዓረቢያ ዛሬ የሸዋልን ጨረቃ ማየት ስላልተቻለ፤
ነገ ረቡዕ የረመዷን ማሟያ 30ኛ ቀን ሲሆን ከነገ በኋላ ሐሙስ ሸዋል 1 ዒደ-ል-ፈጥር እንደሚሆን ሳዑዲ አሳውቃለች።
አል-ሐምዱ ሊላህ‼
عاجل:
تعذر رؤية هلال شوال في تمير ، والخميس أول أيام عيد الفطر بالسعودية .
BREAKING NEWS
ሳይደክሙና ሳይሰለቹ ረበና.. ረበና... ረበና... ያሉ ምላሶች፣ ምላሽን ማግኘታቸው አይቀሬ ነው!
አላህ የማይሰለች ምላስ፣ የማይደክም ልብ ይስጠን!👉 @Zakiiir12
Watch "Emotional Beautiful Dua Qunoot Crying 2021 | with English Translation by Sheikh Abdur Rahman Sudais" on YouTube
https://youtu.be/g-KoNqwzWK8
ምን ልበል በአላህ ብቻ እዩት እና ...
ሱብሀን አላህ
ቁርዓን ተዓምረኛው የአላህ ቃል !!
ቁርአን ሰምተውት ማይጠግቡት ተአምረኛው የአላህ ቃል ነው ፤ ቁርአን ለሙዕሚኖች የቀልብ መርጋጊያ ለኢማናቸው መጨመሪያ የሚሆናቸው የጌታችን የአላህ ቃል ነው !!
"ቁርኣንን አያስተነትኑምን ከአላህ ሌላ ዘንድ በነበረ ኖሮ በርሱ ውስጥ ብዙን መለያየት ባገኙ ነበር፡፡" (ቁርዓን 4:82)
@Zakiiir12
🌙 #ረመዳን 23
اللهم إنك عفو تحب العفو فاعف عني
አላህ ሆይ! አንተ ይቅር ባይ ነህ
ይቅርታንም ትወዳለህ ይቅር በለኝ 🤲
© |ፍቅር እስከ ጀነት
#ሼር👇
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ ➤@Zakiiir12👈
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
የተሀጁድ ሶላት‼️
=============
✍️ ተሀጁድ በሌሊቱ ክፍለ ጊዜ የሚሰገድ ሶላት ነው።
1) ወቅቱ፥
========
ከዒሻእ ሶላት ሱንና በኋላ እስከ ሌሊቱ መጨረሻ ድረስ ፈጅር ከመውጣቱ በፊት ባለው ጊዜ መካከል ይሰገዳል።
ነገር ግን ከእንቅልፉ መንቃት ለሚችል ሰው ወደ ሌሊቱ አንድ ሶስተኛ የመጨረሻ ክፍል ማዘግየቱ በላጭ ነው።
ይህን በተመለከተ ከእናታችን ዐኢሻህ ረዲየልሏሁ ዐንሃ የተላለፉ ሐዲሦች ይጠቁማሉ።
ከጃቢር ኢብኑ ዐብዲልላህ የተገኘ ሐዲሥም "ሶሒሕ ሙስሊም: 755" ላይ አለ።
ከአቢ ሁረይራህ በተገኘ ሐዲሥም "ሙስነድ ኢማም አሕመድ: 14/46" ላይ አሕመድ ሻኪር ዘግበውታል።
*
2) ብይኑ፥
=======
የተሀጁድ ሶላት ሱንና ነው።
ግደታ አይደለም። ግን በረመዳን ሲሆን ደግሞ ምንዳው እጥፍ ድርብ ይሆናል።
አላህ በቁርኣን ላይ እንዲህ ይላል፥
"ከሌሊትም ላንተ ተጨማሪ የሆነችን ሶላት፣ በርሱ (በቁርአን) ስገድ፤ ጌታህ ምስጉን በሆነ ስፍራ በእርግጥ ያቆምሃል። "
[አል ኢስራእ፥ 79]
*
3) ብዛቱ፥
========
የረከዓው ብዛት ገደብ የለውም።
ዝም ብሎ ሁለት ሁለት ብቻ መስገድ ነው።
ግን ረሱልሏህ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አስራ አንድ ረከዓ ይሰገዱ እንደነበር ሐዲሥ የሚያመላክት ሐዲሥ አለ።
አስራ ሶስት የሚልም አለ።
*
4) የአሰጋገድ ሁኔታ፥
================
ሁለት ሁለት ረከዓ በመስገድ በመሃል ማሰላመት፣ ከዚያም ቀደ ቀጣዩ መሄድ።
*
5) ቁርኣን ሲቀራ ሶላት ላይ ድምጽ የማውጣትና ያለ ማውጣት ጉዳይ፥
===================================================
ቢያወጣም ባያወጣም ችግር የለውም።
ግን መስጅድ ላይ ከሆነ ሌላውም ሰው ሲሰማ እንዲጠቀም ድምጽ ተወጥቶ በጀህር ይሰገዳል።
*
6) ከቂያመ ለይል ጋር ልዩነቱ ምንድን ነው??
==================================
ተሀጁድ ሶላት መስገድን ብቻ ይመለከታል።
ቂያመ ለይል ግን ሶላት መስገድን ጨምሮ በሌሊቱ ክፍለ ጊዜ ዚክር ማድረግን፣ ቁርኣን መቅራትንና ሌሎችም ሰናይ ተግባራትን መፈጸምን ያካትታል።
*
ሸይኽ ኢብኑ ባዝ ስለዚህ ጉዳይ ተጠይቀው የመለሱትን መልስ "መጅሙዑል ፈታዋ ሸይኽ ኢብኑ ባዝ፥ 11/317" በስፋት መመልከት ይቻላል።
||
በተጨማሪም፥
አል መውሱዓቱ ፊቂህይያህ፥ 34/117, 2/232
ተልኺሱል ሐቢር፥ 2/35
ተፍሲሩል ቁርጡቢይ፥ 10/307 ላይ በስፋት መመልከት ይቻላል።
||
Murad Tadesse
ረመዳን 19, 1440 ዓ.ሂ
May 24, 2019 G.C
@Zakiiir12
ረመዷን - 18
**
ሦስት ወሣኝ ሰዓታት
ረመዷን ዉስጥ ዱዓ ሊረሳባቸው የማይገቡ ሦስት ወሣኝ ሰዓታት እንዳሉ ስታዉሳችሁ ወደድኩ፡፡
1ኛ) በሚያፈጥሩበት ሰዓት ፡- ፆመህ አምልኮዎች ወደ አላህ የምንቃረብባቸው ተግባራት ናቸው። ትዕዛዙን ተቀብለህ፣ ዉዴታዉን አስበህ፣ እዝነቱን ከጅለህ ነው ፆም የዋልከው። ተርበህና ተጠምተህ ነው የዋልከው።
በምታፈጥርበት ጊዜ ጥቂት ደቂቃዎችን ትንፋሽ ዉሰድና ዱዓ አድርግበት። በተራበ አንጀትህ፣ በተጠማ ሆድህ፣ በደረቁ ጅማቶችህ ወደ አላህ እጅህን ዘርጋ፤ ጉዳይህን ተናገር። ዱዓ ለራስ ነው፣ እጅህን እንዳትዘረጋ፣ በአንደበትህ እንዳትማፀን የሚያደርግህን መሳነፍ ታገል፣ ለሰከንዶችም ቢሆን ፣ እየበላህም ቢሆን ያ ረብ በል።
ፆምያለሁ፣ ግዴታዬን በስኬት አጠናቅቄያለሁ ብለህ አትኮፈስ። ዱንያ አኺራን ለማስተካከል፣ ያጎደልከው እንዲሞላ፣ ያበላሸኸዉን ለመጠገን፣ አምልኮህ ተቀባይነት እንዲያገኝ ... ዱዓ ሁሌም አስፈላጊ መሆኑን አስታውስ።
2ኛ) በሱሑር ሰዓት፡-
ከሱብሒ ሰዓት በፊት ያለዉና የየሌሊቱ የመጨረሻው ክፍል አላህ ዱዓን የሚቀበልበት ሰዓታት ናቸው፡፡ ጭር ባለው በዚህ ልዩ የሌሊት ጊዜ ዉስጥ ከርሱ ምህረትን የሚለምኑትን ባሮቹን አወድሷል። አትዘናጋ ከተወዳሽ ባሮቹ አንዱ ሁን። አንዴም ቢሆን 'አስተግፊሩላህ' በል። የቀደሙትን የረመዷን ሌሊቶች ተዘናግተውባቸው አሳልፈው ከሆነ በተቀሩት ቀናት ያስታውሷቸው። በሱሑርና በፈጅር መካከል አይተኙ። ሰዓቱ ይሁን ወሩ የሚነቁበት እንጂ የሚተኙበት ሰዓት አይደለምና፡፡
3ኛ) ከሱብሒ በኋላ ፀሐይ እስከምትወጣበት ጊዜ ያለው ሰዓት፡- በሌላ ጊዜም ቢሆን በነኚህ ሰዓታት አለመተኛት ይወደዳል። ስለሆነም አለመተኛትን ልማድዎት ያድርጉ፤ ይህ ጊዜ ወሣኝ የዚክር እና የዱዓ ሰዓት ነው፡፡ የቀን ዉሎ እንዲያምር፣ ኻቲማ እንዲሰምር፣ ሪዝቅ እንዲሰፋ፣ ዱዓና ዚክር ይደረግበታል፡፡ ነብያችን (ሶ.ዐ.ወ) በዚህ መንገድ ኖረዋል። ደጋግ አበዉም ፈለጋቸዉን ወርሰዋል።
የተነፈገ ሰው ማለት ዱዓን የተነፈገ ነው። በራስህ ጉዳይ አትሰስት።
#ሼር👇
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
Tᴇʟᴇɢʀᴀᴍ ➤/channel/Zakiiir12👈
━━━━━━━━━━━━━━━━━━
አዲስ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎች ምደባ ይፋ ተደርጓል‼️
ምደባችሁን ለማየት👇
http://result.neaea.gov.et/home/placement
👇👇👇👇👇
@Zakiiir12
إِنَّ ٱللَّهَ وَمَلَٰٓئِكَتَهُۥ يُصَلُّونَ عَلَى ٱلنَّبِىِّ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ صَلُّوا۟ عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا۟ تَسْلِيمًا
አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡ [ሱረቱል አህዛብ፣56]
اللهُم صلِ وسلم على نبينا مُحمد.
(ረመዳን + ጁምዐ)ሙባረክ!❤️
@Zakiiir12
ያ አላህ እናታችንን አንተ ዉደዳቸዉ❤️ በእድሜ ከፍተኛ የሚባሉት እናት ቁርአንን ምን ያክል ጓደኛ አድርገዉታል
ይገርማል😳 እኛስ የት ነን??
@Zakiiir12
የአላህ ተአምሩ ብዙ ነዉ!!!
የሱረቱል ካህፍ የመጀመሪያ አንቀፆች በጣፋጭ ህፃን ልጅ አንደበት
ዕለቱ ጁምዓ ነው ሱረቱል ካህፍን መቅራት እንዳንዘነጋ ለማስታወስ ነው
ማሻ አላህ👍
@Zakiii12
«አላህ ሆይ… ሁለንተናችን ሳይስተካከል፣ ወንጀላችን ሳይማር፣ ዒባዳችን ተቀባይነት ሳያገኝ፣ ምኞታችን ሳይሟላ ከረመዳን የምንወጣ አታድርገን!»
#ያ_ረብ!
#ረመዳን_6
:¨·.·¨: ❀
·. @Zakiiir12