zemedkunbekelez | Unsorted

Telegram-канал zemedkunbekelez - Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

311892

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ 👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና 👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Subscribe to a channel

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

እንካችሁ የድል ዜና…!

"…እስክንድር የሚዘውረውና መሃይሙ መከታው በእንዝህላልነቱ ሠራዊቱን ለእስክንድር ነጋና ለሀብታሙ አያሌው አሳልፎ ከሰጠ በኋላ በሸዋ ፋኖና ዐማራ ነን በሚሉት ባለሀገሮቹ ላይ ደንቃራ በመሆን የሸዋ ዐማራን እንደ ፋኖ ወንደሰን ዓይነቱን ጀግና የምኒልክ ልጅ አይኑን በሳንጃ አውጥተው ከገደሉት በኋላ አንጋፋውን ደራሲና የመከታውን አባት አቶ አሰግድ መኮንን ለመግደል ሠራዊት ልኮ የነበረው የመከታው ጦር በራሱ ገመድ ራሱን አንቆ ከተንጠለጠለ በኋላ እና ከተፍረከረከ በኋላ የሸዋ ፋኖ የእነ መከታውን ጠባቂ የብራኑ ጁላን ሠራዊት ሲወቃው ውሏል። የመከታው ሰራዊትም ተከፋፍሏል። የእስክንድር ሴራም ከሽፏል።

"…በሸዋ ክፍለ ሀገር በዚህ በሁለት ቀን እልህ አስጨራሽ ውጊያ የጁላ ሠራዊት በደንብ ተገርፏል። በዚህ ትንቅንቅ የጁላ ሠራዊት ከአንኮበር እስከ ሀገረማርያም እና ጫጫ ድረስ በነበልባሉ የዐማራ ፋኖ የሸዋ ዕዝ በከሰም ክፍለጦር ከስሞ ቀርቷል። የሞተው እና የቆሰለው በየመንገዱ ተንጠባጥቧል። ከሞት የተረፈው አሁን በዚህ ሰዓት ከጫጫ ከተማ ወደ ደብረ ብርሃን አቅጣጫ እየፈረጠጠ እንደሚገኝ የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል። የጠላት 1ዙ -23 በጀግኖቹ የምኒልክ አርበኞች ተቃጥሏል። መሮጥ የማይሰለቸው ጠላት ትጥቁን እንደ አስከሬኑ እያንጠባጠበ እየፈረጠጠ ነው።

"…አዚምህን ገፍፌልሃለሁና ወጥረህ ውቃልኝ ሸዋ። ውቃው አልኩህ። የመከታውን ዶላር አድርቄዋለሁ። አስክንድርና ሀብታሙ ያዋጡት እንደሁ እናያለን።

• ቆይቼ እመለሳለሁ…! 💪✊💪🏿

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

• የሰማዕቱ የውባንተ ልጆች መግለጫ…

በወቅታዊ ጉዳይ
"ከዐማራ ፋኖ በጎንደር" የተሰጠ መግለጫ

"…የዐማራ ሕዝብ የገጠመውን መንግሥት መር የኅልውና አደጋ ለመቀልበስ ዱር ቤቴ፣ አራዊት ዘመዴ ካለ ዓመታት ተቆጥረዋል። በየቀጠናው ነጻነትን ሽቶ፣ ግፍን ተጸይፎ፣ ኅልውናውን አስቦ በሐቅ ላይ መሠረቱን አድርጎ የፈነነው አርበኛ ተቋማትን እያሳደገ ወደ አንድ ማዕከላዊ ተቋም ማምጣት አስፈላጊነቱ ውሎ ያደረ ሐቅ ነው። ይህንን ጉዳይ በወጉ የተረዱ የዐማራ ሕዝብ የኅልውና ታጋዮች አንድ ድርጅታዊ አታጋይ ተቋም ለማቆም በብርቱ ከሚደክሙ ቀጠናዊ ተቋማት መካከል "የአማራ ፋኖ በጎንደር" አንዱ ነው።

"…እንደ ተቋም አንድ ዐማራዊ ድርጅት እንዲፈጠር ያለን ጽኑ ፍላጎት ከንግግር ባለፈ በተግባርም ጭምር ዋጋ የከፈልንለተና የምንከፍልለት መሠረታዊ ጉዳይ ነው። ዳሩ ግን ተቋምን የምናዋልደው ለሕዝባችን ዘለቄታዊ ኅልውናን በማረጋገጥ ሂደት የጀመርነውን ትግል አንድ እርምጃ ወደፊት እንዲያስፈነጥር እንጅ ግለሰባዊ ክብርና ዝናን እንዲሁም መርኅ አልባ የሥልጣን ፍትወትን ለማስተናገድ እንዳልሆነ መላው ሕዝባችንና አርበኛው የሚገነዘበው ሐቅ ነው። መሠረታዊ ጉዳዩ ይህ ሆኖ እያለ "የዐማራ ፋኖ በጎንደር" አንድ ማዕከላዊ ድርጅት አዋልደናል በሚለው ውሳኔ ላይ እንደ ተቋም እንደሌለንበት ለሕዝባችንና ለመላው የትግል ጓዳችን ማስገንዘብ እንወዳለን።

"…ይሁን እንጅ ተቋማችን አንድ ዐማራዊ አታጋይ ድርጅት እንዲፈጠር ከሌሎች ጠቅላይ ግዛቶች ጋር የሚሠራ አመቻች ኮሚቴ መርጦ በመላክ በመርኅና በአሠራር የሚወለድ ተቋም እንዲፈጠር ብንሰይምም ከጅምሩ የአካሄድና የመርኅ ጥሰቶች ጭምር እንደነበሩበት በመሪያችን በኩል የይስተካከል አቋማችንን ብናሳይም ጉዳዩ ትኩረት ሳይሰጠው አድሮ እዚህ ደረጀ ደርሷል። ከዚህ ጉዳይ ጋር ተያይዞ በተለያዩ ግለሰቦች ጭምር በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የሚቀርቡ ጉዳዮች ተቋማዊ አሠራርንና መርኅን ከመጣሳቸው ባሻገር የተቋማችንን እንዲሁም የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት መምሪያውን ይሁንታ ያላገኙ መሆናቸውን ለመግለጽ እንወዳለን።

"…በጥቅሉ ሕባችንም መሬት ላይ የሚገኘው አርበኛም የሚፈልጉት በሐቀኛ ዓላማ፣ መርኅና መታገያ ጉዳይ ተቃኝቶ ለወንድማዊና ጓዳዊ አንድነት በርትቶ የሚሠራ ሕዝባችን ለገጠመው የኅልውና ጥያቄ ዘለቄታዊ መፍትሔ የሚሰጥ፣ በሕዝቡም በታጋዩም ዘንድ ቅቡልነት ያለውን ተቋምና ሐቀኛ መሪዎችን በመፍጠር ሂደት ውስጥ ሁሉም ወገን በስክነት ለውይይትና ለአንድነት እንዲተጋ ተቋማዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

"ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን"
የዐማራ ፋኖ በጎንደር
ቀን ሐምሌ 12/2016 ዓ.ም
ጎንደር፣ ዐማራ፣ ኢትዮጵያ!!!

"…ጎጃም፣ ወሎና ሸዋ ይቀጥላሉ… እየተደማመጥን። ✍✍✍

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

ከላይኛው የቀጠለ…✍✍✍ …ተመልከቱ ምርጫ አልተካሄደም። ሙሉ ጎጃም። ሙሉ ወሎ፣ ሙሉ ጎንደር፣ ሙሉ ሸዋ አልተሳተፈም። ከጎንደር በመሃላ ያሰራቸው የጋሽ መሳፍንቱ ሀብቴ ወልዴ፣ የጎንደሩ ኮሎኔል በግሌ ነው የደገፍኩት ይቅርታ ብሏል ያው ዘመነ ካሴን በግሉ ከመጥላት ነው የሚመስለው። ስኳድም ከጀርባው አለ። የእነ ባዬ ቡድንም መግለጫው እየተጠበቀ ነው። ከወሎ ገንዘብ ገቢ እንደተደረገላቸው የሚታሙትና የማከብራቸው ኮሎኔል ፈንታሁን ሙሀባው ናቸው የደገፉት። ከሸዋ መሃይሙንና ከምስኪኑ መከታው ነው ድጋፍ ያገኘው። በአጠቃላይ ሀብቴ፣ ሙሀባው እና መከታው። እስክንድር ውይይቱ ውስጥ ይግባ ብለው ያመጡትም ሙሀባው እና መከታው ናቸው። የመጀመሪያው የስብሰባ ቀን አሰግድ የእስክንድርን መኖር ሲያይ "አንተ ደግሞ እንዴት እና በምን መስፈርት ምክንያት እዚህ ልትገባ ቻልክ? ብሎ በመጠየቁ እስክንድር ክብሬ ተነክቷል በማለት ወጥቶ ነበር። ከዚያ ነው ኮሎኔሉና መከታው ሀብቴም ለምነው ያመጡትና የመለሱት። ቀጣሪዎቹም ተመለስ ሳይሉት አልቀረም።

"…ከጎንደር ውብአንተ እስክንድር ስር አልገባም በማለቱ ተገድሏል። ውባንተ እኔ የሀብታሙ አያሌው ወታደር አይደለሁም። በገንዘብ አልገዛም። መነሻዬ ዐማራ ነው በማለቱ ነበር የእነ ሀብቴ ቡድን በኢትዮ 251 በእነ ሙላት አድህኖ በኩል ስሙ ጠፍቶ ለመሞት የበቃው። 251 አሁን ሙላትን ገለል አድርጎ ሥራ የጀመረውም በዚያ በኩል በመጣበት ጦስ ነው። እኔ በግሌ ከሙላት ጋር በሰፊው አውርቻለሁ። እነ ሀብቴ በቀጥታ ውብአንተን ፋፍዴን ነው፣ ብአዴን ነው እንዲሉ ያደረጓቸው እነ እስክንድር እና ሀብታሙ አያሌው ናቸው። ውብአንተም ይሄንኑ ቃል በቪድዮ ተናግሮ ነው የሞተው። ከውባንተ ቀጥሎ እንዲገደል የታዘዘው አቶ አሰግድ ነው። መከታው አሰግድን እንዲገድል፣ በአሰግድ ስር ያሉ ጀግኖች ወንድሞቹን እንዲገድል መመሪያ ተቀብሎ ሥራ ጀምሯል። ፋኖ ወንደሰንን በጩቤ ነው እነ መከታው አይኑን ዘክዝከው አውጥተው፣ አንጀቱን ዘርግፈው የገደሉት። አሁን እነ መከታው በሸዋ ሕዝብ በጉልበት ነው ያሉት። አፄ ዮሐንስ ናቸው አፄ ተክለ ጊዮርጊስን ከገዳም አውጥተው አይናቸውን በጋለ ብረት አውጥተው በካራ ዘክዝከው የገደሉት። እነ መከታው ጋር ከአጠገባቸው የወሎ ኅብረት፣ ፀረ ኦርቶዶክስ አክራሪ እስላሞችና ጴንጤዎች በኃላፊነት አሉ። እናም በአሰግድ በኩል ያሉትን ኦርቶዶክሳውያን በጭካኔ ነው የሚያርዱት። አንደኛው ጴንጤ እንደውም ሽምግልና ላይ ለምን ትዋሻለህ አልኩት። ሃይማኖትህን ንገረኝ ስለው "በጌታ ነኝ" ነው ያለኝ። አቢይ አህመድ መከታው ጋር ነው። ከዋሸሁ እኔ ልቀጣ። አሰግድ ለጊዜው ከእስክንደር እና ከመከታው፣ ከአቤ ጢሞ፣ እናም ከኢዜማው መምህር ተብዬ ሰይፍ ከመታረድ አምልጧል። የኢዜማው ሰውዬ ማለት መግለጫውን ያነበበው ሰውዬ ነው። አሁን ሸዋ አሰግድን በመከታውና በእስክንድር ካራ በሀሰን ከሪሙ ልጆች ሰይፍ የሚያሳርደው አይመስለኝም። ሞተዋላ። የሚኒሊክ ልጆች። ሰምተሃል ሸዋ። ያበጠውን ነገር እያፈነዳሁት እመጣለሁ።

"…ሀብታሙ አያሌው፣ ብሩክ ይባስ፣ ወግደረስና ጌጥዬ መልሰው ስለሚዘበዝቡት ዝብዘባ እስቲ ልንገራችሁ። መጀመሪያ ምርጫ አልተካሄደም። እሑድ የማሰማችሁ የስብሰባው ጉደኛ የሆነ የድምጽ ቅጂ አለ። እዚያ ላይ ኢንጂነር ደሳለኝ ይሁን፣ አስረስ ይሁን፣ ሄኖክ ወይም ዝናቡ እንዲህ ብለው ይጠይቃሉ።

• እስክንድር ማንን ወክሎ ነው የሚመጣው? እገሌ  ሸዋን፣ እገሌ ደግሞ ጎጃምን፣ እገሌም ወሎን፣ እገሌ ደግሞ ጎንደርን ነው። ስለዚህ ከተሳተፍን እኛ ነን መሳተፍ ያለብን። ጎንደር ስላልተዋሃዱ ባዬና ሀብቴ፣ ወሎ ተዋህደዋል ተብሎም ምሬና ኮሎኔል፣ ሸዋም መከታውና አሰግድ፣ ጎጃም አንድ ቢሆንም በአንድ እንዳይቀርብ ሁሉም ሁለት ሁለት ስለሆኑ በአስረስ እና በዝናቡ ተወክለዋል። ስንት ሆኑ ማለት ነው። ወሎ፣ ጎጃም፣ ጎንደር ሸዋ። ሁለት ሁለት ሲያዋጡ ስምንት ይሆናሉ። እስክንድር የተጠየቀው እዚህ ጋር ነው። አንተ ከማን ጋር ነህ? ሀብቴ ጋር ጦር አለኝ ካልክና የዚያ ጦር መሪ ከሆንክ መሳተፍ የምትችሉት ከሁለት አንዳችሁ ናችሁ። በወሎም ወይ ሙሀባው ወይ አንተ ናችሁ። በሸዋም መከታው ወይ አንተ ናችሁ። ሦስቱም የኔ ናቸው የምትል ከሆነ ደግሞ ሦስቱም ምን ይሠራሉ? ነበር የተባለው። አያችሁ። አሁን ዝናቡና አስረስ ከጎጃም ሲወጡ፣ ከጎንደር ባዬ እምቢ ሲል፣ ከወሎ ምሬ፣ ከሸዋ አሰግድ እምቢ ሲሉ የሚቀሩት ማናቸው? ሀብቴ ከጎንደር፣ ኮሎኔል ሙሀባው ከወሎ፣ መከታው ከሸዋ። እስክንደር ራሱን አይመርጥ ነገር። ከየት አባታችሁ አምጥታችሁ ነው አምስት ለአራት ነው የተመረጠው የምትሉት? ሌባ ሁላ። ታዲያ ይሄን መሰሪ ሴራ መቃወም ቢያጸድቅ እንጂ ያስኮንናል እንዴ?

"…አበበ ገላው በየቀኑ ዩቲዩብ ይከፍት ነበር፣ የለንደን ፋኖ ፔጅ ነበር በየቀኑ ሰብስክራይብ የሚያደርጉለት። ሰሞኑን ግን የለንደን ፋኖዎች ሴራው ሲደብራቸው በየቀኑ ሰብስክራይብ ማድረግ ያቆማሉ። የሚያስቀው ነገር ከዚያን ቀን ጀምሮ በየቀኑ ይዘጋ የነበረው የአቤ ዩቲዩብ እነሆ አሜሪካ ሳትዘጋባቸው ቀረች። አይ አሜሪካ። የሥራሽን ይስጥሽ። አበበ በለው ግን እኔ ዘመዴ በደንብ ነው እስክስ የማስደርግህ። እመነኝ የሀረር ልጅ ነኝ። ከዚያም ደጃች ውቤ ማርገጃ ያደግኩ የድሮ አራዳ ነኝ። አንተና ሀብታሙማ አትሸውዱኝም። ማርያምን አሳይሃለሁ።

"…አፈንግጠው የወጡትን በሙሉ አናግሬአቸዋለሁ። በሚዲያም ቀርበው እውነቱን ለመናገር ቃል ገብተውልኛል። መግለጫም ዛሬ መልቀቅ ይጀምራሉ። እስክንድርም አሁን ያፈነገጡትን እንዴት ማረቅ እንደሚቻል አንገቱን ቀብሮ እየሰላ ይሆናል? ወገን ይህ አርግጠኛው ሥዕል ቢሆንም ዐማራው አሁንም በላይ አምላኩን በምድርም ነፍጡን ካልተማመነና የሚጃጃል ከሆነ መሰሪዋ አሜሪካ ባታሸንፈውም ነገር ግን ደም ልታፋስሳቸው ትችላለች። እስክንደር አሁን ለብልጽግና ትልቁን ሥራ ሠርቶአል። የሚቀረው መደራደርና ማታኮስ ብቻ ነው።

• በጎንደር ሀብቴንና ባዬን፣ በጎጃም ዘመነንና ማስረሻን፣ ኮሎኔል ጌታሁንን፣ በወሎ ምሬንና ኮሎኔል ሙሀባውን፣ በሸዋ አሰግድንና መከታውን ለያይቷል። ማታኮስም፣ ማገዳደልም ጀምሯል። ሃቁ ይሄ ነው። እነ ሀብታሙ በሻህ፣ ቦርከና ላይ የጻፈው ፕሮፌሰሩ ሶዬ በግልጽ መነሻዬ ዐማራ፣ መድረሻዬ ዐማራ የሚሉትን የገቡበት ገብቶ መደምሰስ ነው እንደተባለው ነው የመከታው ጦር በሸዋ ከመከላከያ ጎን ቆሞው ከአሰግድ ጦር ጋር መዋጋት የጀመሩት። ይሄ እውነት ነው። መከታውና እስክንድር የራሳ ተዋጊ ገበሬዎችን ሰብስበው እስክንድር በፓወር ፖይንት እንዲህ እያለ ነበር ያስተማራቸው። "ዘመነ ካሤ ብአዴን ሆኖ ለመንግሥት ገብቷል። ምሬ ወዳጆ፣ አሰግድ መኮንን፣ ኢንጂነር ደሳለኝ ለመንግሥት አድረው ከድተውናል። ከጎንደርም እንደዚያው፣ ሸዋ ከእኔ ጎን መቆም አለበት እያለ ነበር የሰበካቸው። አሁን ገበሬው ነቅቷል። የራሳ ገበሬ ከመከታው እጅ ወጥቷል። የአቤ ጢሞ ጦርና ጥቂት ሰው ነው የቀረው። ጀግናው የመሀመድ ቢሆነኝ ጦርም ሸዋን ይከዳል ተብሎ አይጠበቅም። ክብር ነው ያለኝ። ያምሆነ ይህ ግን ዐማራው ድብን አድርጎ ያሸንፋል። ማርያምን፣ አዛኜን ያሸንፋል። ዐማሮቹ ተሰብስበው ወስነው ስንዴው ከገለባው ተለይቶ አንድ ሆነው ይመጣሉ። አሰግድን ማውረድ፣ ዘመነን ማውረድ፣ ባዬን፣ ምሬን ማውረድ የዐማራ ፈንታ እንጂ የግንቦቴና የብልፄ አይደለም። አራት ነጥብ።

• ድል ለዐማራው ፋኖ…!
• ድል ለተገፋው ለዐማራው ሕዝብ…!

• ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው ከራየን ወንዝ ማዶ።

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"ርዕሰ አንቀጽ"

"…እስክንድር ነጋ በፈጠረው ሁከት እነ አበበ በለው እና ሀብታሙ አያሌው ተናበው በፈጠሩት ረብሻ ለዐማራ ሕዝብ በፈጠሩለት አጀንዳ ሲራኮት ህወሓት ወያኔ በኦሮሙማው መከላከያ እየተመራች ወደ ወሎ ራያ የትግሬ ታጣቂዎችን በገፍ እያስገባች ነው። ትግሬዎቹ በኦሮሙማው ጦር እየተመሩ እንዴት እንደሚዝቱ፣ ዐማራን እንዴት እንደሚሳደቡም ከዚያው ከትግሬዎቹ ቤት የተሰረቀ ቪድዮ አግኝቻለሁና እለቅላችኋለሁ። ዐማራን በእስክንድር በዘመዳቸው በኩል አጀንዳ እየሰጡ ዐማራው በዚያ ላይ ሲራኮት እነሱ በጎን ሥራቸውን እየሠሩ ነው። አንድም ቀን ስለ ራያ፣ ስለ ወልቃይት፣ ስለ ደራ፣ ስለመተከል ዐማራና የዐማራ ርስትነት ሞግቶ የማያውቀው፣ በዐማራ ትግል ላይ ያልነበረው። ፋኖነት የዐማራ አይደለም ብሎ በአደባባይ የሚሞግተው እስክንድር ነጋ የፋኖ መሪ ካልሆንኩ ብሎ ሲበጠብጥ ወያኔና ኦሮሙማ በጎን ሥራቸውን እየሠሩ ነው። ደግነቱ የእነ እስክንድር ነጋ አጀንዳ ሳይወለድ የሞተ ነው። ሞቷል። እናም ይሄን የዐማራ ትግል ጠላፊ ጉዳይ አጀንዳውን በስሱ እያነሱ ወደ ገደለው ወደ ቀደመው ትግል መግባት ነው።

"…በነገራችን ላይ አበበ በለው በእኔ በዘመዴ ጉዳይ ጨርቁን ጥሎ ማበዱን እያየሁ ነው። የፖለቲካ ቅማንቴው ፀረ ዐማራ በግድ ወደ ዐማራ ትግል ያመጣነው ሰው እብድ እየሆነ እያየሁት ነው። እኔ ራሱ በጋበዘኝ ሚድያው ላይ ነው የዐማራን ሕዝብ ድንዙዝነት፣ አለመንቃት ጠቅሶ ምን ይሻላል? ብሎ ሲጠይቀኝ "ሕዝቡ ምን ያድርግ? አንተ ሚድያውን የያዝክ ሰውዬ አይደለህ እንዴ ኢትዮጵያኒስቱ ካምፕ ውስጥ ተቀርቅረህ ለዐማራ ድምፅ ሳትሆን፣ ዐማራው በአንተ ፕሮፓጋንዳ ጭምር በግንቦቴዎች ኪሱ እንዲጠብ፣ እንዲዘረፍ ስታደርግ የኖርክ። አንተ ሳትነቃ እንዴት ሕዝቡ አልነቃም ትላለህ? በግድ አይደል እንዴ በውትወታ አሁን በቅርብ ዐማራ ነኝ ብለህ ደፍረህ መናገር የጀመርከው ብዬዋለሁ። አላማሁትም። እውነቱም ይሄ ነው። አዳሜ ከርሱንና ገንዘቡን ሲያሳድድ ወገኑን ረስቶ ቆይቶ አሁን መጥቶ ያዙኝ ልቀቁኝ ሲል ያሳፍራል።

"…ሀብታሙ አያሌው በግልጽ ተናግሯል። እኔ አዲስ አበቤ ነኝ። ከኢትዮጵያዊነት ወርጄ የዐማራ ብሔርተኛ ልሆን አልችልም ነበር ያለው። ፋኖነት የዐማራ አይደለም ብሎ የሚሟገትን መነሻዬ ዐማራ፣ መድረሻዬ ኢትዮጵያ ብሎ ዐማራን እንደ ኩሊ፣ እንደ ወዛደርነት ተጠቅሞ እንደ ወያኔ ሞቶ ተዋግቶ 4ኪሎ እንዲያደርሰው በብር እየገዛው ያለውን እስክንድር የተባለ አድሮ ቃሪያ ፀረ ዐማራ ግለሰብ ይዘው የሚንገታገቱትም ለዚህ ነው። ይሄንን ነው የተቃወምነው። እየተቃወምኩ ያለሁትም ይሄንኑ ነው። አበበ በለው ስሜን እየጠቀሰ፣ መረጃ ቲቪን እየጠቀሰ ሲያቀረሽ ያመሸበትን ቪድዮ አይቼዋለሁ። የፋኖ መሪዎች ሆይ እባካችሁ ዘመድኩንን ከትግሉ አስወጡልን አላለም? ይሄ ድራሚስት ቀልደኛ። በዐማራ ስም የሚነግድን ነጋዴ ሁሉ የንፁሐን ደም ይፋረደዋል። እኔ የዘመነ ደጋፊም፣ የአሰግድ፣ የመከታው፣ የምሬ፣ የባዬና የሀብቴም የግል ደጋፊ አይደለሁም። ልሆንም አልችልም። እኔ ሴራውን ነው የማጋልጠው። አለቀ። የሚገርመው ኢትዮ 360 ላይ በኤርሚያስ ጋባዥነት፣ በሀብታሙ አያሌው ፈቃጅነት መጥቶ ያገለግል የነበረው የሀረርጌው ኦነግ ወዳጄ ሞገስ ዘውዱ ተሾመም እያበደብኝ ነው። ኧረ ጉድ ነው።

"…የመከታውን ውሸት በመረጃና በማስረጃ አሰጣዋለሁ። የይፋትን ሕዝብ ብሶት፣ እንግልት፣ መዘረፍ አጋልጣለሁ። በአሰግድም፣ በመከታውም ለተሠሩ ስህተቶች ምህረት የለኝም። መከታው ያልተማረ ስለሆነ ብዬ ንቄው አላውቅም። እንደውም ትህትናው የሚማርከኝ ሰው ነው። በመረጃ ቲቪ መርሀ ግብሬ የአሰግድን እንቅስቃሴ ያሳየሁበትን ቀን አላስታውስም። ሁሌ የመከታውን ቡድን ነበር የማሳያው። መከታው በእስክንድር እየተመራ ሸዋን ለኢትዮጵያኒስት ኃይሉ አሳልፎ ሽጦታል። እሱን ነው የምዋጋው። ኮሎኔል ፋንታሁን ሙሀባውን እስከአሁን አክብሮቴም እንዳለ ነው። መጨረሻውን እስካውቅ ጥቂት ጊዜም እጠብቃቸዋለሁ። ሀብቴንም እንደዚያው። ሀብታሙ አያሌውና እስክንድር አያዋጡትም። ሰኔ አስራ አምስት ከተነሣ እስክንድርም አብሮ ነው የሚነሣው እንጂ ነጥሎ ማንሣት ትክክል አይደለም። አጥብቄ እቃወመዋለሁ። እንደውም አሁን ያሉት አወዛጋቢ የፋኖ መሪዎች ከጥቂቶቹ በቀር ገለል ብለው አማካሪ ሆነው በመቀመጥ ቦታውን ለወጣቶች መስጠት አለባቸው ባይም ነኝ እኔ። አድካሚ ቢሆንም መሞከሩ አይከፋም ባይ ነኝ። እንጂ አንድም ድርጅት መርቶ የማያውቅ ቅጥረኛ አፍራሽ ቀውስ ሰውዬ ከመንገድ አምጥቶ የዐማራን ትግል ማስጠለፍ ኃጢአትም፣ ወንጀልም፣ ግፍም፣ በደልም፣ እልም ያለ ክህደትም ጭምር ነው። ዘመነን መጥላት መብት ነው። ዘመነን ገፍቶ ለመጣል ግን ሴራ አያስፈልግም። ዘመነን በዚህ መልክ መግፋት አደጋው ከፍ ያለ ነው። ዘመነ ሁለት ሽፍታ የሚመራ አይደለም። ዘመነ ቤተሰቦቹ በዚህ ጦርነት የተሰዉበት ሚልዮን የጎጃም ዐማራዎችን የሚመራ መሪ ነው። ዘመነን በውይይት በሠራዊቱ ውሳኔ ይሾማል ይሻራል እንጂ በዶላር ኃይል በሚዲያ ጩኸት፣ በጎጤ፣ በእስኳድና በእነ ሀብታሙ አያሌው ትብተባ ሊገፋ አይገባም። እውነቱ ይሄ ነው።

"…የፖለቲካው ቅማንት፣ የአገው ሸንጎው፣ የወያኔና የኦነግ፣ የግንቦቴም ፔጆች "አሁን ለዐማራ አንድነት እንቅፋት የሆነው ዘመድኩን ነቀለ ነው" ብለው ሲጮሁብኝ ዐማራው መጠርጠር የማይችል ግኡዝ ይመስላቸዋል እንዴ? እኔማ ሽብልቅ ነው የሆንኩባቸው። አላላውስ ነው ያልኳቸው። ፎቶዬን ዘቅዝቀው ሲያለቅሱ ሳይ እኔ ጮቤ ነው የምረግጠው። እንኳን እነሱ ሌሎች ነገርየው ቆይቶ የሚገባቸው 1G ዐማራ መሳይ ዐሞሮች እንኳ ቢናገሩኝ አይከፋኝም። ስንትና ስንት 5G ዐማሮች በሞሉበት ምድር ላይ ለዋን ጂ ዐማራም አልገረምም። ዋናው ነገር የማነሳው ሓሳብ ውኃ ይቋጥራል ወይ? ሚዛን ይደፋል ወይ ነው ጥያቄ ሆኖ መቅረብ ያለበት። የምለካው በቆቱነቴ ሳይሆን በሓሳቤ ነው። ሓሳቤ ገዢ ካገኘ አሸናፊ ነኝ። ሓሳቤ ገዢ ካላገኘ ደግሞ ኪሳራው ለእኔው ነው። ሓሳቤን የሚቃወሙ ሰዎች ፎቶዬን ዘቅዝቀው ዋይዋይ ስላሉ ሓሳቤ ኮካኮላ ከሆነ ከመሸጥ ወደኋላ አይልም። ገዢ ሳጣ ራሴው ሱቄን ዘግቼ እጄን አጣጥፌ እቀመጥ የለም እንዴ። እስክንድርን ተናገርክብኝ ብሎ ስኳድ፣ ጎጤ፣ ግንቦቴ ስለተንጫጫ ወይ ፍንክች። ጧ በል። ፈንዳ። 

"…እስቲ ወደ እስኬው ታናሹ እስክንድር ሴራ እንምጣ። አንድ ሰው ከሀዲ ሆኖ ከተገኘ የተቆጨው ሰው "ድሮም ቀልቤ አልወደደውም ነበር" አይደል የሚባለው። ይሄ ሰው እኔን እኮ ለማጃጃል ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም። እኔ ሁለት ቀን አንዴ ከሄኖክ ዘሀበሻ ጋር፣ አንዴ ከሰይፉ መብረቅ ጋር ለጥቂት ደቂቃ በአካል ያየሁት ሰው ኢትዮ 360 ላይ ዘመዴ የነፍስ መምህሬ ነህ ሲል ውስጤ ሳይታዘበው የሚቀር ይመስላችኋል እንዴ? ያቺ እኔን ማሰሪያ ነበረች። ልክ አቢይ አሕመድ ሲሳይ አጌናን፣ ታማኝ በየነን፣ ዳንኤል ክብረትን፣ ነቢዩ ባዬን አንቆለጳጵሶ ድባቅ እንደመታቸው፣ የዘላለም ባሪያዎቹ እንዳደረጋቸው እኔንም እስኬው ዶክመንተሪ ሊሠራብኝ ነበር የፈለገው። እኔ ዘመዴ ግን ቋሚ ጠላትም፣ ቋሚ ወዳጅም ስለሌለኝ መልካም ሥራን ብቻ አይቼ የማወድስ፣ ክፉ ሥራን አይቼ ደግም ጥንብ ርኩስህን የማወጣ፣ አይስክሬም ሳይሆን መቅመቆ፣ መተሬ፣ ሬት፣ በረኪና፣ ቃሪያ በሚጥሚጣ፣ ዳጣ ነጋዴ ስለሆንኩኝ ምህረት ብሎ ነገር አላውቅም። ሼም ብሎ ነገር አይቆነጥጠኝም። ትናንት እንዲህ ብዬ ነበር ዛሬ ብሎ ነገር እኔ ጋር የለም። ትናንትም በምክንያት፣ 👇ከታች ይቀጥላል…✍✍✍

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

“…በሰነፍ እጅ የጥበብ መግዣ ገንዘብ መኖሩ ስለ ምንድር ነው? ጥበብን ይገዛ ዘንድ አእምሮ የለውምና።” ምሳ 17፥16 "…እውነትን ግዛ አትሽጣትም፥ ጥበብን ተግሣጽን ማስተዋልንም።” ምሳ 23፥23

"…እንደምን አደራችሁ?
"…እንደምን አረፈዳችሁ?
"…እንደምን ዋላችሁ?
"…እንደምን አመሻችሁ?

"…እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"…በቀለ ገርባ ፥ በጽንፈኝነቱ ወያኔ የሚወደው፥ ግን የወያኔን ስልጣን በመጋፋቱ ወህኒ ያወረድውው ሰው ነው። በቀለ ራሱን ከአማራ ጋ’ በምንም መልኩ ማስታረቅ የማይሻ፥ ፍጡም አማራ ጠል ሰው ነው። ባንድ የታሪክ አጋጣሚ ግን በቀለ ከስክንድር ነጋ ጋ ( ከስር በተፈታ ሰሞን አብሮ ወደ አሜሪካ መጥቶ ነበር)። አማሪካ ከደረሱ በሗላ ግን በቀለ ከስክንድር ጋ የታቀደለትን ቱር ሰርልዟል። በወቅቱ ምክኛቱ ስክንድር ሳይሆን ፥ ዝግጁቱን ያዘጋጁት ግንቦት ሰባቶች መሆናቸውን ና ጃዋር ደስተኛ ስላልሆነ ተው ስላለው ‘ንደሆነ መረጃው ደርሶኝ ነበር።

አጋጣሚ ፫

"…አሳምነው ፥ ምግባሩ፥ አምባቸው በተገደሉበት ወቅት ‘ስክንድር ባህር ዳር  ነበር። አብይ አህመድ ግድያውን ሲያቀነባብር፥ የስክንድርን እግር ተከትሎ ብቻ ሳይሆን ፤ አሳምነው ‘ስክንድርን ለመቀበል ልዩ ሃይሉን አስታጥቆ ላይ ታች በሚልበት ጊዜ ነበር። ታይሚንጉ ያጋጣሚ ወይስ በእቅድ??? I know starts to question!’

አጋጣሚ ፬

"…የነ አምባቸው እና አሳምነውን መገደል ተከትሎ ‘ስክንድር በመኪና ወደ አዲስ አበባ ሲመለስ፥ በተጠመደ መትረይስ በሉት ተብሎ ኬላ ላይ ያለው ሰው ግን ‘ስኪ ላጣራ በማለቱ ፥ ‘ስክንድር ሊተርፍ ‘ንደቻለ ሰምተናል። ትእዛዝ ተሰጥቶት ትእዛዙን ያልፈጠመ ሰው እጣ ፈንታው ሞት ንደሚሆን እያወቀ አድርግ የተባለውን የበላይ ትእዛዝ ያላደረገው በነብሱ ፈርዶ ነው ??? ከዚያ ውሳኔው በሗላ የበላይ ትእዛዙን ያላከበረው ሰው ስክንድርን እናንተ ናችሁ ‘ንዴ ሂዱ በቃ ካላቸው በሗላ ስራውን ያለ ምንም መሸበር ‘ንደቀጠለ ‘ስክንድር በቃለ መጠይቁ ላይ ነግሮናል። ይቻላል ወይ !!! I started to question!

አጋጣሚ ፭

"…እስክንድር አማሪካ መጥቶ የመጨረሻውን የባልደራስ ስብሰባ ካደረገ በሗላ ፥ ለጋዜጠኛ ብሩክ ይባስና ኤርሚያስ ለገሰ አዲስ አበባ ‘ንደገባ ራሱን ከባልደራስ አባልነት አስገልሎ ጫካ ንደሚገባ ነግሯቸው ነበር። ይህ መረጃ ወደኔ የደረሰው ስክንድር ገና አማሪካ እያለ ነበር። ስክንድር ቦሌ ኤርፖርት ‘ንደደረሰ “አይዙኝም እሰወርባቸዋለሁ!” ‘ ንዳለኝ መሰወር ችሎ ነው ወይስ ጉዳዪ ሌላ ነበር። I need to look deep in to this !!!

አጋጣሚ ፮

"…ባህርዳር ማረሚያ ቤት ከስር ከተፈታ በኋላ፥ በቅርብ የማውቃቸው የባህር ዳር ልጆች የዛኑ ቀን ማታ ወደ ጎንደር ይዘውት ሲሄዱ ደውለውልኝ ስክንድርን አነጋግሬው ነበር። በወቅቱ ስክንድርን ሳናግረው የተሰማኝ ነገር ቅንነት ብቻ ነበር። አሁን ላይ ሳስበው ግን፥ ንዴት ከባህር ዳር ንደወጣ ና በያንዳንዷ ደቂቃ ውስጥ ስለነበረው የጉዞ ሁኔታ ሳስብ፥ መንግስት ( የ አብይ አይነት መንግስት ) ንዴት ከመረጃው ባዳ ሊሆን ቻለ።  ጫካ ገገባ በኋላ ስለተፈጠሩ ነገሮች በዝርዝር እመለስበታለሁ በማለት ጥያቄው መጠየቅ ጀምሯል። ሌሎችም ይቀጥላሉ ብዬ እጠብቃለሁ።

• ድል ለዐማራ ፋኖ…!
• ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…!

• ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው ከራየን ወንዝ ማዶ።

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"ርዕሰ አንቀጽ"

"…አለባብሰው ቢያርሱ በአረም ይመለሱ ይላሉ አበው። እውነት ነው። ሰነፍ ገበሬ መሬቱን ነካ ነካ አድርጎ አረስኩ ብሎ ጉድ ይሆናል። ምርት አያገኝም። ፍሬም የለው። ጎበዝ ገበሬ ግን መሬቱን ደጋግሞ ያርሰዋል። ያገላብጠዋል። ድካም አለው። ላቡ ይፈሳል። አድካሚም አሰልቺም ነው። እንዲያ አድርጎ ማረሱ ግን ጥቅም እንጂ ጉዳት የለውም። በደንብ ከታረሰ መሬት ፍሬው ብዙ ነው። አረሙ ባይቀርም ቀላል ነው።

"…ስትሄድ እንቅፋት ሆኖ የደፋህ የዘረረህ ድንጋይ ስትመለስም መልሶ እዚያው ቦታ ላይ ከመታህና በአፍጢምህ ከደፋህ እንቅፋት ሆኖ የመታህ ድንጋይ ሳይሆን ድንጋዩ ራስህ ነህ። ሰው አንዴ፣ ሁለቴ፣ ቢበዛ ሦስቴ መሸወድ ያለ ነው። እድሜ ልክ መሸወድ ግን የጤነኛ ሰው ምልክት አይደለም። ጠበል ወይ ሐኪም መሄድ አለብህ።

"…አንዳንዱ በሐሰት ምላሱ ከብሮ፣ በሕዝብ ምላስ ይሾማል። አንዳንዱ በማስታወቂያ ብዛት፣ በፕሮፓጋንዳ ጋጋታ ጀግና ሆኖ እንዳይወርድ ሆኖ ከላይ ይሰቀላል። ስህተት ቢሠራ እንኳ አይነኬ እንደ ታቦት ቅዱስ ሁላ ያደርገዋል። እየረበሸም፣ እየበጠበጠም፣ እያወከም ቢሆን እሱን አትናገሩት፣ አትንኩት፣ አትተቹት ይባላል። አሸማቃቂው ብዙ ነው። አስቀድሞ ሕዝብ አንጀት ውስጥ ተጎዝጉዞ ገብቶ የሆነ ሥፍራ ላይ የሆነች ሚጢጢዬ ዙፋን ከሠራና እሷ ላይ ቁጢጥ ካለ በኋላ በቃ እንደ ንጉሠ ነገሥት አይነኬ አይነኬ እንዲጫወት ያደርገዋል።

"…ይሄን አፍራሽ ሾተላይ የዲያብሎስ ፈረስ፣ ፀረ ሕዝብ፣ ፀረ ዐማራ የሆነ የወንበዴዎች አለቃ ለመጋፈጥ እንደ እኔ ዓይነት በገዛ ፈቃዱ  በላዩ ላይ ፈርዶ ጋጠወጥ፣ ባለጌ፣ ስድአደግ እብድ እብድ የሚጫወት የሐረርጌ መራታ ካልሆነ በቀር ነገርየውን ለመጋፈጥ እንዲህ ቀላል አይሆንም። ስድብ የማይፈራ፣ ቅሽሽ የማይለው፣ ከእውነት ጋር የተጣበቀ ወርዶ የሚያዋርድ፣ የሚያወራርድ ፈጣጣ በመረጃና በማስረጃ የሚሞግት ሰው ያስፈልገዋል። ያንጊዜ የመጀመሪያውን አንዲት አብሪ ጥይት እኔ ሳበራ እኔን ለመቃወም ጅሉም፣ የተገዛው ሞኙም ማገናዘብ የሚሳነው ጅላንፎውም አንዴ ሲንጫጫብኝ ከዳር ቆሞ የሚያየው የደመራውን እንጨት መውደቂያ ስፍራ እያየ ታዝቦ የሚቆዝመውም የትየለሌ ነው። አንዳንዱ መሀል ሰፋሪ ደግሞ አንተም ተው አንተም ተው እያለ ሽማግሌ ሽማግሌ ለመጫወት ይዳክራል። ብቻ ምንአለፋችሁ የሚንጫጫው ሰው ብዙ ነው። የእኔ ሥራም እያሠለስኩ ጥይት እየቆጠብኩ መተኮስ ነው።ጥቂት በጥቂት እያደረግኩ እያለማመድኩ፣ እያለማመድኩ፣ ጥቂት በጥቂትም መጥኜ አጀንዳ እየሰጠሁ ቀስበቀስ ገዝግዤ፣ ገዝግዤ ወቅቼ ሳሳርፈው ያነዜ ከዳር ቆሞ ሲሰድበኝ፣ ሲተቸኝ፣ ባይሰድበኝም እንኳ ዘመዴ ምን ነካው? እያለ በሆዱ ሲያማኝ የሚከረመው ሁላ በወደቀው ዛፍ ላይ ምስር ለማብዛት ተሰልፎ ይመጣል። እኔ ያለ ጥበብ፣ ያለ ዕውቀትም በዘፈቀደ እመርግ የነበረውን የጭቃ ዥራፌንም በማሽን የሚጠቀሙ የሚቆርጡም ጠቢባን ይመጣሉ። የድል አጥቢያው አርበኛም ተግተልትሎ መጥቶ ይረከበኛል።

"…የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አዘጋጅታ የነበረውን የተጠለፈ፣ የመከነውን የመስከረም አራቱን ሰላማዊ ሰልፍ ይቁም ስትል እስክንድር ነጋ ፎገላ። ቤተ ክርስቲያኗ ብታቆምም እኛ እንወጣለን ብሎ ጓ አለ። ቢመከር፣ ቢዘከር አሻፈረኝ አለ። ቢጨንቀኝ እንዲህ ብዬ በፌስቡክ ገጼ ላይ ጻፍኩኝ። "እረፍ እንጂ ሶዬ። የሰኔ 15ቱ የደም ማፋሰስ ሴራ አይበቃህም እንዴ? ነግሬሃለሁ እረፍ" ብዬ ጻፍኩኝ። ምድር ተገለባበጠ። ስማቸውን መጥቀስ አስፈላጊ ያልሆነ አንድ መነኩሴ አባቴ ደወሉልኝ። ዘመዴ እስክንድር አቆማለሁ ዘመዴ ያቁምልኝ፣ አስቁሙልኝ ብሎኛል ብለው አማላጅ ሆነው መጡ። ዘመዴ ያቆማል አቁም አሉኝ። አቆሙኩ። እሱም አቆመ። ይሄ ለምን ትዝአለኝ መሰላችሁ። ከስንት ዘመን በኋላ የእስክንድር አክባሪ፣ ባለ አእምሮው ወዳጄ ሄኖክ የሺጥላ ዛሬ በፌስቡክ ገጹ ጽፎት ሳይ ጊዜ ነው። እኔ ጀምሬዋለሁ። አሁን ዐዋቂዎች እስክንድርን እየመረመሩ ያክሙታል።

"…እስክንድር በአባቱ በኩል በደቡብ ጎንደር ከተንቤን የሚመዘዝ ትግሬ ዘር ያለው ነው የሚሉ አሉ። ተክለ ሰውነቱ፣ ተብታባነቱ፣ አማርኛን አሳክቶ ያለመናገሩ ሲታይ አዲስ አበባ የተወለደ የአዲስ አበባ ልጅም አይመስልም። መቼም የደም ነገር አይለቅም አይደል? ትግሬ ነው የሚሉት ይሄን እየጠቀሱ ነው። እስክንድር ለትግሬነቱ በመታሰር ዋጋ የከፈለ፣ መዐህድን ያፈረሰ፣ ፕሮፌሰር መስፍንን ሰልሎ ያሳሰረም ነው ብለው የሚከሱት አሉ። ይሄን እኔ አላውቅም። መኢአድንም፣ ዐብንንም ሳይቀር ያፈረሰ ሾተላይም ነው ይሉታል። እስክንድር በእናቱ በኩል ወለጋ ተወልደው ያደጉ የጉራጌ ልጅ ነውም ይሉታል። ከደቡብ ጎንደሬ ዘሬ ትግሬ እና የከወለጋ ተወላጅ ዘረ ጉራጌ አዲስ አበባ የተወለደ ነው ይሉታል ዘሩን እናውቃለን የሚሉ ሞጋቾች። እስክንድር ባልደራስን ሲያቋቁም አብዛኞቹ ትግሬና ጉራጌ፣ ኦሮሞና የፖለቲካው ቅማንት፣ የሸዋ የቱለማ ኦሮሞ ነው ሰብስቦ ወደፊት ያመጣው የሚሉም አሉ። ጥቂት ዐማሮች አሁንም ፍዳ እያዩ ነው። እስክንድር እስርቤት በነበረ ጊዜ ከአቶ ስብሃት ነጋም ጋር በጣም ተግባብተው ያወሩ እንደነበር ያየህሰው ሽመልስ በመጽሐፉ አሳምሮ ጽፎታል። እስክንድር በዘመነ ወያኔ መርጦ ያገባው የኢሮብ ትግሬ ናት የምትባለውን ወሮ ሰርካለምን መሆኑም ይታወቃል። የእስክንድር ልጅ ምንም እንኳ አሁን አሜሪካዊ ቢሆንም በአባቱ ትግሬና ጉራጌ፣ በእናቱ ትግሬ ነው ማለት ነው። ትግሬ የዐማራ መሪ እንዴት ይሆናል? ነውር አይደለም እንዴ?

"…ልብ በሉ የእስክንድር ወዳጆች ፀረ ዐማራው እነ በቀለ ገርባ ናቸው። ከታች ሄኖኬ እንደጻፈው ጃዋር የእስክንድር አድናቂ ነው። ቤተልሄም ታፈሰ የእስክንድርና ኦሮሞው የሻአቢያ አሽከር አንዳርጋቸው ጽጌን ወዳጆች እንደሆኑ እንደነገራት በአዲሱ መጻፏ ጽፋለች። እስክንድር ሃገር ሲበጠብጥ፣ ጀግና ጀግና ሲጫወት፣ የዳያስጶራ ዶላር ለተፈለገው ግብ እንዳይውል መሃል ላይ ደንቃራ ግድብ በመሆን ሲያነጥፍ የከረመ ሾተላይ ሰው ነው። እስክንድር በውጭ በስለላ ድርጅት ይደገፋል በሚባለው በዓለም ብርሃን ተደግፎ ደብረ ኤልያስ ላይ ሣልሳዊ ቴዎድሮስ ነኝ ብሎ ሊቀባ እና ልግሥና ሊፈጽም፣ ወንቅሸት ሄዶ አባ ዮሐንስ ሂድ ከዚህ ቀውስ ብሎ እንዳባረረውም ተጽፏል። እስክንድር ለንግሥና መቀባት ከጫፍ ደርሶ የነበረ አቢይ አቁም ቢለው እምቢ ስላለው ገዳሙን ያስደበደበ ጨካኝ አረመኔ የሆነ ሰው ነው።

"…እስክንድር ጎጃምን ለሁለት፣ ጎንደርን ለሁለት፣ ወሎን ለሁለት፣ ሸዋን ለሁለት የከፈለ የዐማራ ጠላት ነው። እስክንድር የገባበት ድርጅት ይፈርሳል፣ አቢይ አቅፎ የሳመው ሰው ይሞታል። ሁለቱም መልአከ ሞት ናቸው። ቢቢሲን እንዲያናግር ያዘጋጁለት ትግሬዎቹ እነ እስታሊን ናቸው። ወያኔ በእስክንድር በኩል፣ ብልፅግናም በእስክንድር በኩል ፋኖን መክፈል እንደሚችሉ ያስባሉ። መሃይሙ መከታውን ይዞ ሸዋን እየዘረፈ፣ የሸዋን ጀግኖች ወያኔ ከፈጀችው በላይ እየፈጀ አለ። ሰሞኑን እንኳ በመከታው ትእዛዝ ይዘው አፄ ዮሐንስ ንጉስ ተክለ ጊዮርጊስን በጩቤ አይኑን አውጥቶ፣ ሆዱን ዘርግፎ እንደገደለው ነው የገደሉት። የብልጽግና የጦር መሪ ማርከው የሚለቁት እነ መከታው የሸዋ ልጆችን ግን በዘረ ትግሬው እስክንድር የሳዲስትነት ጭካኔ ያስገድላሉ። የመከታው፣ ጦርን ከሰውነት ጠባይ አውጥቶ እንስሳ፣ እንደ ወያኔና ኦነግ ጨካኝ ትውልድ ፈጥሯል። አጭበርባሪው መከታውን የሚጋልበው እስክንድር በብአዴን ተደግፎ ነው። በመረጃና በማስረጃ እመጣበታለሁ። 👇ከታች ይቀጥላል…✍✍✍

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

መልካም…

"…እንደተለመደው እግዚአብሔርን ያመሰግን ዘንድ ይጠበቅ የነበረው 1ሺህ ሰው ሞልቷል። ከምስጋና ቀጥሎም የምንሄደው ወደ ርዕሰ አንቀጻችን ነው።

"…ከዚያ በፊት ግን ለአዲስ ገቢ የፔጄ ደንበኞች ማሳቢያ አለኝ። ጠዋት የእግዚአብሔር ሰላምታ በሚሰጥበት ሰዓት የእግዚአብሔርን ስም በትክክል ያለመጻፍ ጽሑፍን በማንሳት ያስቀጣል። በመሃል እኔ ዘመዴን አንበሳ፣ ሚዳቆ ዝሆን እያሉ ማመስገንም እንዲሁ። መሳደብ፣ ፀያፍ ነገር መናገር፣ መደዴ መሆን ግን ድልት፣ ቡልክ፣ ቡን፣ ቅስፍ ያስደርጋል። ፔጄ ይናፍቃችኋል። በወሬ ጠኔ ትደፋላችሁ። በምስጋና ሰዓት ምስጋና ብቻ። እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ። ሌላ ዝብዘባ የለም።

"…እናንት ግምቦቴ፣ ኢዜማ፣ ኦነግ፣ ወያኔ፣ ብአዴን፣ የፖለቲካው ቅማንቴ፣ አገው ሸንጎ ግን ወዘተ እዚያ በለመዳችሁበት። ክፍት አፋህን በመክፈት ቤቴን ለመረበሽ ተንቀዥቅዠህ ስትመጣና ፔጄ ላይ ጥሬ ካካህን ለመዘፍለል ገና ስትሞክር ወገብ ዛላህን ብዬ ነው ቀስፌ የማስወግድህ። አይደለም እኔን በፔጄ ላይ ሌላ አስተያየት ሰጪን መሞገት እንጂ መሳደብ ነውር ነው ያስቀስፋል። ቢጫ ካርድ እንኳን የለውም።

"…ብታምኑም ባታምኑም ከ5 መቶ ሺ በላይ ባለጌ ሰዎችን ቀስፌ ማባረሬን የቲጂ መንደር ሪፖርት ያሳየኛል። ይቀጥላል። ተሟጋች ተቃዋሚ ግን ይበረታታል። ተሳዳቢ ክፍትአፍ ባለጌ ግን ይቀሰፋል። ሰምታችኋል። ልክህን ነው የማስይዝህ። ጨምላቃ ሁላ። ፈልገኸኝ እንጂ የመጣኸው ፈልጌህ አልመጣህም። ቤቴ ገብተህ አሳዳጊ እንደበደለው፣ እንደ ቦርኮ አፌን እከፍታለሁ ማለት አይፈቀድም። በጨዋ ደንብ ነው መሞገት። ለጨዋ የተቃዋሚ ሓሳቦች አክብሮት አለኝ። እናቴን እየሰደብክ ልሰማህ አልችልም።

"…ሰሞኑን ግን ርዕሰ አንቀጼ ሁሉ እስክንድር በተባለ የዐማራ ትግል አጨናጋፊ ሾተላይ ዙሪያ ነው የሚሆነው።

• ዝግጁ…?

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"…በመረጃ ቴሌቭዥን እና በቲክቶክ ፔጄ መርሀ ግብሬን ጀምሬአለሁ።

"… አላችሁ አይደል…?

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"…እደግመዋለሁ… ማርያምን አዛኜን ዐማራ ድብን አድርጎ ያሸንፋል። ያውም በዝረራ ያሸንፋል።

"…የእነ ሀብታሙ አያሌው፣ የአበበ ገላው በቀቀን የ ቲዊተሯ አክተር ደንፍታብኝ ልትፈነዳ ነው። አንቺ እስክንድርሽን አዝለሽው ዙሪ፣ እኔ ደግሞ የእስክንድርን ሴራ ፍርስርሱን አወጣዋለሁ። እናንተ ተሰብስባችሁ ደረት እየመታችሁ አልቅሱ፣ እኔ መራታው እየዞርኩ ልቅሶ እደርሳችኋለሁ። አለቀ፣ ደቀቀ።

"…ዛራ ሚዲያ፣ ኢትዮ 360 ሚዲያ፣ ሚኒሊክ ቴሌቭዥን፣ አዲስ ድምፅ ሚዲያ አበበ በለው፣ ስታሊን፣ ሀብታሙ አያሌው፣ ኮምፓስ ኤርሚያስ ለገሰ ዋቅጅራ፣ ጋሻ ሚድያ፣ ኢየሩስ ተክለ ጻድቅ፣ ጌጥዬ ያለው፣ ወግደረስ ጤናው፣ ወንደሰን የእስክንድር ነጋ የአክስት ልጅ የኡጋንዳው ወንዴ ጫቱ፣ የኦነግ፣ የወያኔ፣ የብልጽግና፣ የብአዴን፣ የፖለቲካው ቅማንት፣ የአው ሸንጎ ኧረ ስንቱ፣ ኧረ ስንቱ እንዲህ እንደ ግሪሳ ዘምታችሁብመኝ እኔ ግን ወይ ንቅንቅ።

"…ልድገምልሽ ልዩዬ በሕይወት እያለሁ ቅዱሱ የዐማራ ትግል በሴራ አይረክስም። አይፈርስምም። እኔ ብቻዬን ዐማራ ላይ የፋኖን ትግል ለማፍረስ የሚሠራን ሴራ ድምጥማጡን ለማጥፋት እኔ ዘመዴ ተሰድቤም፣ ተገፍቼም በቂ ነኝ።

• ወጥር ዘመዴ አንድ ለእናቱ ሺ ለጠላቱ፣ አንበሳ ዘመዴ አሳራቸውን አብላቸው። በርታ ዘመዴ አንተ የሥላሴ ባርያ፣ የድንግል አሽከር፣ የምሥራቁ ሰው የሐርርጌው መራታ አንተ ቆቱ ዘመዴ ባለማዕተቡ የተዋሕዶ ልጅ ወጥር አልኩህ።

"…ለማንኛውም የዐማራ ፋኖ ትግል ድኗል። የእነ እስክንድር የግንቦቴዎች እና ፌክ ኢትዮጵያኒስት የብልጽግናም ቡድን ሴራው ከሽፏል። አዲሱ የእነ መከታው፣ የእነ ኮሎኔል ሙሀባው፣ የሀብቴ ወልዴ ድርጅት ሞቶ ተወልዷል። አለቀ። እደግመዋለሁ… ማርያምን አዛኜን ዐማራው ድብን አድርጎ ያውም በዝረራ ያሸንፋል።

• አሁን ኢንተርኔቱን ዝጋው። 😂😂

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"…ቀጥሎ ስለ ወዳጄ አርበኛ ሀብቴ ነው የምጽፈው። አንድ ከኤርትራ፣ ሁለት ከኡጋንዳ ሆነው በዘመነ ካሴ ጥላቻ ብቻ ሰክረው ትግሉን ለእብዱ፣ ለቀውሱ እስክንድር አሳልፎ እንዲሰጥ ስላደረጉት ሁለት ጅል መሰሪዎች ጭምር ነው የምጽፈው።

• አላችሁ አይደል…?

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

ያዝ እንግዲህ…😂

"…ዳግማዊ አቢይ አሕመድ አንድ እብድ፣ አንድ ወፈፌ ታላቁን የዐማራ ሕዝብ እንዲህ ሊጫወትበት ሲፍጨረጨር እያየሁማ ዝም አልልም።

"…አጅሬ እስክንድር ከእስር ቤት ከወጣ በኋላ ጉብኝት በሚል ሰበብ ሁሉም የፋኖ አደረጃጀቶች ጋር ይሄዳል። ከጎንደር የጋሽ መሳፍንትን አማኝነት ያያል። በዚያ መንገድ ገባባቸው፣ አስማላቸው፣ ጎንደሬ ለማዕተቡ ሟች ነው ይኸው እነ ሀብቴን የመሰሉ ጀግኖችን አፍዘው፣ አደንግዘው የእስክንድር ባሪያ አድርገዋቸው ቀሩ። እስክንድር የጋሽ መሳፍንትን የቆሰለ ልጅ አዲስ አበባ ድረስ ወስዶ አሳክሞ፣ አሜሪካ የያዘችው ገንዘብም ሲለቀቅልኝ እሰጣችኋለሁ ብሎም ነው አስሮ የያዛቸው።

"…እስክንድር ዘመነ ጋር ሲሄድ ዘመነ የተማረ ቢሆንም ሁሉን አማኝ፣ ፎልፏላ፣ ሆደ ቡቡ፣ ሃይማኖተኛ፣ አስሬ ለክቶ አንዴ የማይቆርጥ መሆኑን በደንብ አየ። ሳያርቅ ሳያቀርበውም በሃብታሙ አያሌው በኩል ማርያምን እኔና እስክንድር አንለያይም እያስባለው ለጉሞት ቆየ።

"…እነምሬ ጋር ሲሄድ እነምሬ አድንቀውት ግን እንደ ጎንደርና ጎጃም ልባቸውን ሳይከፍቱለት ሸኙት። ከወሎ መልስ ሸዋ መጣ። በሸዋ ያገኘው በአንድነት የነበሩትን አሰግድና መከታው ነበር። እስክንድር እንደ አቢይ አህመድ የተማረ ሰው ጠልና ሰብሳቢ ነውና አሰግድ ፊደል የቆጠረ፣ በውትድርናውም ውስጥ ኮማንደር የሆነ፣ ደራሲና ሀያሲ ብስል ፖለቲከኛ መሆኑን አየ። መከታው ከሁለተኛ ክፍል ይበሉኝ ከ8ተኛ ክፍል ትምህርቱን ያቋረጠ ምስኪን መሆኑንም ተመለከተ።

"…በመጨረሻ ታናሹ ማረፊያው መከታው ጋር እንዲሆን ወሰነ። መከታው ጋር ሆኖ መጀመሪያ አሰግድንና መከታውን ለያየ። ጎጃም ተሻግሮ ዘመነ ላይ አሳመፀ፣ ጎንደርን ለ2 ከፈሎ አገዳደለ፣ ይኸው ወሎን ሰነጠቀው። እኔ ዘመዴ ከነከስኩ ነከስኩ ነው ሳላደማማ መፋታት መች ዐውቅና።

💪 አይደለም እንዴ?

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

መልካም…

"…ዘወትር ያመሰግን ዘንድ የሚጠበቀው 1ሺ ሰው ከወትሮው በተለየ ዛሬ ሁኔታ በፍጥነት ሞልቷል። 😂 እግዚአብሔር ይመስገን።

"…ይህ የምታዩት ፎቶ ደቡብ አፍሪካ በሄድኩ ጊዜ ኔልሰን ማንዴላ ታስሮበት የነበረውን የሮቢን ደሴት ከጎበኘሁ በኋላ በኬፕታውን ከተማ አናት በቴብል ማውንቴን ላይ የተነሣሁት ፎቶ ነበር። ካሜራ ማኖቹ ተሼና አባ ነበሩ።

"…ፎቶውን ስነሣ በአንደበቴ እናገር የነበረውን ቃል አሁን ድረስ አልረሳም። በህወሓት ኢህአዴግ፣ በጥልቁ ዓለም ሰዎች ይደገፉ ከነበሩትና በወቅቱ በሕዝብ ዘንድ ቅቡል ከነበሩት ከእነ በጋሻው፣ ዘርፌ፣ አሰግድና ትዝታው ምድረ ተሃድሶ ጋር ብቻዬን ጉረንቦ ለጉረንቦ ተናንቄ እፋለም የነበረበት ወቅት ስለነበረ እንደማሸንፋቸው እርግጠኛ መሆኔን እየተናገርኩ የተነሣሁት ፎቶ ነበር። ሁል ጊዜ የአሸናፊነት ስሜት ሲሰማኝ ፈልጌ የማየው ይሄን ፎቶ ነው።

"…ትናንት ብዙ ሰዎች በቲጂ ፔጄ ላይ በአፋቸው እንዲያስታውኩና እንዲጸዳዱ ፈቅጄ ከዳር ቆሜ ሲበለሻሹ እያየሁ ነበር። የብልፅግና፣ የወያኔ፣ የኦነግ፣ የግንቦት ሰባት፣ የባልደራስ፣ የግንባሩ፣ የሠራዊቱ፣ የፌክ ኢትዮጵያኒስቱ፣ የዓለም ብርሃን ሃይማኖት፣ የፖለቲካ ቅማንት፣ የአገው ሸንጎ፣ የብአዴን ሰዎችና ደጋፊዎች እንደ ግሪሳ ሲሰፍሩብኝ እያየሁ አሸናፊነቴን እያስታወስኩ እስቅ ነበር። ለዚያ ነው ያስታውኩ ዘንድ የፈቀድኩላቸው። ዛሬ ግን እንዳያችሁት በምስጋና ሰዓት ማስታወክ ስድብም ካካ እፉ ሆኖ ስለማይፈቀድ ቀስፌ ቤቴን አጽድቼዋለሁ።🔥🔥

"…እኔ ዘመዴ ሳልጋበዝ በስብሰባው ላይ ተሳታፊ ነበርኩ። ጄ/ል ተፈራ ማሞ በደስታ ሲቦርቅ፣ ሙሀባው፣ መከታው፣ ኮ/ል ታደሰ ሲደሰቱ፣ ዝናቡ ሲቆጣ ሁሉንም ቀድቻቸዋለሁ። እናንተም ትፈርዱ ዘንድ በመረጃ ቴቪ ሙሉውን እለቅላችኋለሁ። ጠብቁኝ።

• ማርያምን ሴረኞችን ብቻዬን አሸንፋቸዋለሁ።  

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

አቋሜን ስለማሳወቅ…

"…እኔ ዘመድኩን በቀለ አክሊለ ገብርኤል የሥላሴ ባርያ የድንግል አሽከር፣ የሐረርጌው መራታ፣ የምሥራቁ ሰው፣ ባለማዕተቡ የተዋሕዶ ልጅ፣ አንድ ለእናቱ ሺ ለጠላቱ የዐማራ የነፍጠኛው ወዳጅ ወድጄና ፈቅጄ ማንም ሳያስገድደኝ እነዚህ በምሥሉ ላይ ከሚታዩአቸው የዐማራ ሕዝብ ፋኖዎች ጎን የምቆም መሆኔን በታላቅ ወኔና በታላቅ ድፍረት ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ።

"…የኮመንት ሳጥኔን ክፍት ያደረግኩት አውቄ ነው። ዝንቦቹን ለማጥመድ ስለፈለግኩ ነው። የወያኔ፣ የግንቦት ሰባት፣ የግንባሩ፣ የፖለቲካው ቅማንት፣ የአገው ሸንጎ፣ የብአዴን፣ የብልጽግና፣ የዓለም ብርሃኖች፣ ኦነጎች፣ ዲቃላዎች ስለተንጫጩ ንቅንቅ አልልም። እነዚህን በምሥሉ ላይ የምታዩአቸውን በገንዘብ ያልተገዙ፣ ከነ ድክመታቸው እና ከእነ ስህተታቸው አብሬአቸው የምቆም መሆኔን አረጋግጣለሁ።

"…በስድስት ዓመት ውስጥ ከዛሬው ጋር 5 ድርጅት መሥርቶ ሲያፈርስ ከነበረ አፍራሽ ግለሰብ ጎን የማልቆም መሆኔንም አረጋግጣለሁ። 1- የአዲስ አበባ ባላደራ ምክርቤት ሊቀመንበር፣ 2- የባልደራስ ፓርቲ ሊቀመንበርነ፣ 3- የዐማራ ሕዝባዊ ግንባር ሊቀመንበር፣
4 -የዐማራ ሕዝባዊ ሠራዊት ፋኖ ሊቀመንበር፣
5- የዛሬው ራሱን በራሱ የመረጠውን የዐማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ሊቀመንበ ተብዬውን ሌላው አቢይ አሕመድ እብዱ፣ የወደቀው መላክ እስክንድር ነጋ አጥብቄ በመቃወም የምሞግት መሆኔንም አረጋግጣለሁ።

"…በጥዋቱ ጥቅስ አቋሜን እቋጫለሁ። “…ሸለቆው ሁሉ ከፍ ይላል፥ ተራራውና ኮረብታውም ሁሉ ዝቅ ይላል፤ ጠማማውም ይቃናል፥ ስርጓጕጡም ሜዳ ይሆናል፤” ኢሳ 40፥4

"…አዛኜን ዐማራ ድብን አድርጎ ያሸንፋል። ተንጫ ምድረ በጭባጫ ሁላ። ማርያምን እኔ ዘመዴ ብቻዬን ክፍለጦር ነኝ። አዛኜን እንቅልፍ ነው የማሳጣችሁ። እናትማ እኔን ወለደች። 😂😂😂✍✍✍

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

😂 ሳንቀደም እንቅደም መሆኑ ነው። 😂

"…የፖለቲካ ፓርቲ ኢንኪዩቤተሩ እስክንድር ነጋ እኔ ገና ተናግሬ ሳልጨርስ በዓመት ውስጥ ሦስተኛውን ድርጅት ዛሬ መሠረተ። የእስክንድር ሚስት የሥጋ ዘመድ ነው የሚባለው የዛራ ሚድያው የዓድዋው ትግሬ እስታሊን ገብረ ሥላሴና የሀብታሙ አያሌው ኢትዮ 360 ሚዲያም ይኸው በሰበር ዜና ከች አሉ።

"…ያው እንደተናገርኩት ነው የሆነው። ጎንደር የጋሽ መሳፍንት ግሩፕ በእነ ሀብታሙ አያሌውንና በሌሎች ሚዲያ በኩል ስሙን ካስጠፉት በኋላ ሜጀር ጀነራል ውብአንተ ተገደለ። ውብአንተ እኔ የሀብታሙ አያሌው ወታደር አልሆንም እንዳለ ነው የተገደለው።

"…የዛሬ ሳምንት ደግሞ እስክንድር ተጠግቶት ያለው የመከታው ፋኖ የሸዋ ፋኖውን መሪ አቶ አሰግድ ለመግደል ሰራዊት ተልኮ ዐማራ ለዐማራ ከሚጫረስ ብሎ አቶ አሰግድ ማጀቴን ለቅቆ አፈገፈገ።

"…እስክንድር ነጋ ዘመነን ለመገልበጥ ወንድሙን ማስረሻ ሰጤን አምጥቶ የጎጃም ፋኖ ላይ ሽብልቅ ከተተ፣ ኮሎኔል ጌታሁንን ከጎጃም ፋኖ በብዙ ሚልዮን ብር ወደራሱ ገንጥሎ ወሰደ።

"…እስክንድር አንድ የሆነውን የወሎ ፋኖን በብር ኃይል ለ2 ከፈለ። ከፈለናም በብአዴን እርዳታ፣ በብልፅግና ድጋፍ፣ በእነ እስታሊን ና በእነ ናትናኤል መኮንን በግንቦቴና በግንባሩ ሰዎች ግርግር በዛሬው ዕለት የዐማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት የሚል መስርቶ ራሱንም ሊቀመንበር አድርጎ ከች አለ። እስታሊንም የተላከለትን የድምጽ ቅጂ በሰበር ዜናው ለቀቀው።

"…እስክንድርን አስራው ጀግና ያደረገችው ወያኔ፣ እስክንድርን ባህርዳር ይዞት ተነጋግሮ ተስማምቶ የፈታው ብአዴንና ብልጽግና የዐማራ ትግል የተጠለፈ፣ ፕሮፌሰር አሥራት ዛሬ ድጋሚ የተገደሉ እስኪመስሏቸው ጮቤ ረገጣ ላይ ናቸው። 😂 ወዳጄ እነ አኪላ ለምን እንደሚጠሉ ዛሬ ገባችሁ አይደል?

• እህሳ ምን ታስባላችሁ? እስቲ ተንፕሱ።

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

• ወለይ ምን ኡኖ ኖ…?

"…ኢትዮ 360 ባለቤቶቹ የሉ ሆኖ ነው እንዴ የዓድዋው ትግሬ እንዲህ የሚራወጠው። እስክንድር፣ እስክንድር ብሎ ሊሞት እኮ ነው። ምን ጉድ ነው? ሀብታሙ ያፈረበትን፣ ብሩክ የተደበቀበትን፣ ነውር ጌጧ ጄሪ ብቻዋን የምትዝረከረክበትን ሳይወለድ የሞተውን የእስክንድርና የመከታው፣ የኮሌኔል ሙሃባንና የጋሽ መሳፍንትን ድርጅት ምን ይሁን ነው የሚለው?

"…ስለ ወልቃይት፣ ስለ ራያ፣ ስለመከተል፣ ስለ ደራ ትንፍሽ የማይለውን የፓርቲ ኢንኪዩቤተር እስክንድር ነጋን የጋሽ አቦይ ስባት ነጋ ልጅ ምን ፍጠር ነው የሚለው? በቃ አልቻለም፣ አልቻለም። ተፋቱት።

"…እስክንድር ሸዋ ላይ ተቀምጦ በፈጠረው አጀንዳ ወራሪው የትግሬ ሠራዊት ራያን ወርሮ ያስጨንቃል። እነ እስታሊን ደግሞ እስኪው ሀወይ ፅቡቅ ደሀን ደሃንአሎ ማለት ምን ማለት ነው። ኧረ ኩፍ በሉ። ዋይ ሙንዱኖ መጨማለቅ። ወይስ ወያኔ እስክንድርና ድርጅቱ ላይ ኢንቨስት አድርጋ ይሆን እንዴ? ወይኔ ብሬ ይመስላል የወለይ ጩኸት።

"…ወፍ የለም።

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

መልካም…

"…ከዚህ ልጥፍ በኋላ ቁጥሩ ካልጨመረ በቀር እስከአሁን ድረስ 13 ሰዎች ብቻ የተናደደቡት ርዕሰ አንቀጽ መሆኑን የቲጂ መንደር ሪፖርት እያሳየኝ ነው። እበድ ምድረ ሌባ ሁላ። ጨበርበርቱ…ወዪ…

"…የሀረርጌው ወደ ገቦ ነፍጠኛ ኦነግ ሞገስ ዘውዱ ተሾመም እንደረገጠኝ አሁን ገና አይደል እንዴ የማየው። ኮሜንታተሮችስ እንዴት አሉኝ ይሆን ብዬ ስገባ ከምር ተጽናናሁ። ተብታቢት የኦነግ ገረድ የነፍጠኛዋ ልጅ ገሌዋ ሞገሴም ኩም ብላ አየኋት። ዘንድሮ ለመሽንኮች አልተሳካም።

"…ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ አዲስ አበባ መታየቱ እየተወራ ነው። የመከታው ጦር እያፈነገጠ ነው። ወሎም ጦሩ ከእነ እስክንድር እቅፍ አፈግፍጓል። ጎንደርም አውላላ ሜዳ ላይ ቀርተዋል። ወፍ የለም።

"…አገዛዙ ከጎጃም ዘመነ ጦር ላይ፣ ከሸዋ የአሰግድ ጦር ላይ፣ ከወሎ የምሬ ጦር ላይ፣ ከጎንደር የባዬ ጦር ላይ ከእስክንድር ወዳጅ ነን ካሉት ጋር በመሆን ዘመቻ ሊጀምር መሆኑም ተነግሯል። ወደ ጎጃምና ሸዋ ሠራዊት እየገባ ነው። ቡልጋ የገባው ተደምስሷል። ጎጃሙ የገባውም አይወጣም። ራያ መንገድ ተዘግቶ ሕዝቡ የወያኔ ጦር ይውጣልን ብሎ እየቀወጠው ነው።

"…ተራው የእናንተ ነው። በጨዋ ደንብ ሓሳባችሁን አንሸራሽሩ። ንዴትም ቢሆን ስትተነፍሱት ነው የሚለቃችሁ። በጨዋ ደንብ ይሁን እንጂ በእኔ ቤት የመናገር ገደብ የለም። እኔ ዲሞክራት ነኝ። እኔ ብቻ ተንበጫብጬ ሌላው ዝም እንዲል አላደርግም። በጨዋ ደንብ እስክንድርን ደግፋችሁም ሓሳብ ስጡ። መብታችሁም ነው። ስድብ ግን፣ ካካ ነው። እፉ ነው።

• 1…2…3…ጀምሩ…

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

ከላይኛው የቀጠለ… ዛሬም በምክንያት ነው እኔ የምንቀሳቀሰው። አለቀ።

"…ወደ ኋላ ልውሰዳችሁ። ጥቅምት 2/2012 ዓም እሁድ በጠዋቱ በመስቀል አደባባይ ታላቅ የተባለ የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚደረግ የያኔው ባለአደራው መሪ የነበረው አቶ እስክንድር ነጋ በሚዲያ ማስታወቂያ ያስነግራል። ሰላማዊ ሰልፍ ፈቅዶ የማያውቀው የአቢይ አህመድ ካቢኔም ሆነ የአዲስ አበባ የከንቲባ ጽሕፈት ቤት ደግሞ ሰልፉ ያልተፈቀደና ሕገወጥ እንቅስቃሴን እንደማይታገስ ይለፍፋል። የሰልፉ መሪ አስኬው ደግሞ በበኩሉ ሰልፉ እንደማይቀርና ሕዝቡ ፈርቶ ቢቀርም እንኳ እርሱ ብቻውን ባንዲራ ይዞ ሰልፍ እንደሚወጣ ይፎክራል። ቀኑ እየቀረበ ሲመጣ ሰልፉን ለመቀላቀል የዐማራ ወጣቶች ከክልላቸው ሊመጡ ይችላሉ በሚል ከመስከረም 30 ጀምሮ በጎጃም መስመር ቄሮ መንገድ መዝጋት ሲጀምር በደብርሃን መስመር ደግሞ በማግሥቱ በ1/2/2012 ዓም ቀኑን ሙሉ ከዐማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የሚገባውንም ሆነ የሚወጣው ሕዝብ አናቀሳቅስም በማለት ከሰንዳፋ እስከ አሌልቱ ድረስ ይቀውጡታል። በዚህ ዕለት ነበር ምን ያህል ቄሮና የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ተናበው እንደሚሠሩም የታየው። አስታወሳችሁ አይደል?

"…በመንገዱ መዘጋት ምክንያት የተሽከርካሪው ሰልፍ፣ የፍተሻው ወከባና እንግልት አስጨናቂ ነበር። የሀኪም ቤት ቀጠሮ፣ የውጭ ሀገር በረራ ያላቸው በሙሉ ታግደው ቀሩ። ሆኖም ግን ከምሽቱ 12:00 ሰዓት አካባቢ ኬላው ተነሣ። ሕዝቡም ወደ አዲስ አበባ መግባት ተፈቀደለት። ምክንያቱ ምንድነው ሲባል፣ ታላቁ አስኬው፣ ብረቱ እስኬው፣ አይሰበሬው እስኬው፣ የባላደራው ሊቀመንበር በአለቀ ሰዓት "ለሰላም ሲባል" ሰልፉን ሰርዤዋለሁ ማለቱ እንደሆነ በሬዲዮ ተነገረ። ያ  ብቻዬንም ቢሆን አልቀርም ያለው ያ እንደ መቅደላው ቴዎድሮስ ሽጉጤን እጠጣለሁ ያለው አገኘሁ ተሻገርን የመሰለ ሶዬ፣ ያ አንድ ሰውና አንድ ጥይት እስኪቀር እዋጋለሁ ሲል የነበረው መንጌ የሆነ ሶዬ፣ ያን ሁሉ ሁከት ካስነሳ በኋላ "ሸወድኳችሁ" በሚመስል ቀልድ እጥፍ ማለቱ የሚረሳ አይደለም። እስኬ ብረቱ እጥፍ ነው። አክሮባቲስት።

"…ሌላው በበትላንቱ ርዕሰ አንቀጼ ላይ አንድ ከአስተያየት ሰጪዎቼ መካከል አንዱ "አስኬው የCIA ተላላኪ እንደሆነ መጠርጠሩን" ጽፎ ተመለከትኩት። እናም እኔም ሓሳቡን ገዝቼ እንዲህ ብዬ ስጋቴን ባስቀምጥስ ምን ይለኛል። ምንም…

፩ኛ፦ እስክንድር ነጋ ከእስር ከወጣ በኋላ በመጀመሪያ ሥራውን ያደረገው ወደ ቀደምት ፋኖዎች ዘንድ እየዞረ በምስጋና ሰበብ ያደረገውን ጉዞ "የትጥቅ ትግል የማይቀር መሆን አለመሆኑን ምርምር ለመሥራት ነበር ብዬ ብወስድስ? ዘመነ ካሴን በዚህ ጉዳይ ሳነጋግረው የገለጸልኝም እንዲህ በማለት እንደነበር አስታውሳለሁ። "ዘመዴ ድብ አንበሳ እኔና እስክንድር ተቀምጠን በቀጥታ የጠየቀኝ ይሄንን ነበር። ትጥቅ ትግል አይቀሬ ነው ብዬም ነግሬዋለሁ" ነበር ያለኝ። ሌሎቹም ምን እንዳሉት አላውቅም። ዘመነ ግን ይሄን አረጋግጦልኛል።

፪ኛ፦ እስኬው ብረቱ ከዐማራ ፋኖ አራቱም ጠቅላይ ግዛት ጉብኝት በኋላ የሪሰርች ጽሑፉን ይዞ በቀጥታ የሄደው ወደ አሜሪካ ነው የገባው። እዚያም እንደገባ የጥናቱ ውጤት ያሳሰባቸው አለቆቹ በምሥራቅ አፍሪካ ትልቅ ሕዝብ ያላት ሀገር ከቁጥጥራቸው ውጭ እንዳትሆን በመስጋትና ይሄ የማይወዱት ዐማራ የተባለ ፑቲን የሆነ ሕዝብ የሚያደርገውን የትጥቅ ትግል በቅርብ መከታተልና መቆጣጠር እንዲቻል ራሱ አስኬውን ጫካ ገብቶ፣ ተመሳስሎና የመሪነቱን ቦታ ተቆናጥጦ ወደሚፈልጉት አቅጣጫ እንዲያደርስላቸው ተላከ ብዬ ብጠረጥርስ ምን ይለኛል?

፫ኛ፦ አቢይ አሕመድ በፋኖና በዐማራ ድጋፍ ወያኔን ማሸነፉን ረስቶ ፋኖን በአንድ ሳምንት አጠፋዋለሁ እመኑኝ ብሎ ለቀጣሪዎቹ ቃል ቢገባም ፋኖ የማይቀመስ ሆኖ እንኩትኩቱን ሲያወጣው አማሪካ አየች።እናም የፋኖው መጠናከር ያሰጋት አሜሪካ በቅርቡ በአዲስ አበባው ተወካይዋ በአማሪካው አምባሳደር በማሲንጋ በኩል "ፋኖ ነኝ በሚል ራሱን የሚጠራው ቡድን ከድርድር ውጪ አያዋጣውም' በማለት ለዘገዩባት የጫካ ወኪሎችዋ ለእነ እስኬው "ከእጃችሁ እንዳይወጣ" ፍጠኑ በሚል ማስጠንቀቂያ መልዕክት ላከችም እንበል።

፬ኛ፦ ከዚያ እኔ ዘመዴ እስክንድርን "ለፋኖ የተሰበሰበውን ገንዘብ የት አደረስክ? ገንዘቡ ፋኖን መግዣና መከፋፈያ አደረክው ስለው ገንዘቡንማ አሜሪካ ይዛዋለች ብሎ በወኪሎቹ በኩል የነገረን እስኬው ዝም ጭጭ ጮጋ ብሎ የከረመው አስኬው የአለቆቹን ድምፅ በአንባሳደሩ በኩል ሲሰማ ከተደበቀበት ስፍራ ፈጥኖ በመውጣት "እነ እስታሊን ባዘጋጁለት በቢቢሲ አፋን እንግሊፋ በኩል በሚገባቸው ቋንቋ አናገራቸው። "መልእክቱም እንዲህ የሚል ነበር በፈረንሳይኛ "የተበታተነውን የፋኖ አመራር ወደ አንድ ለማምጣት ትንሽ አስቸግረውኝ ነው፣ እባካችሁ ትንሽ ታገሱኝ። አሁን ቀሽም ቀሽሙን ይዤዋለሁ። በትምህርት ደካሞቹን ከሸዋ መከታውንና ከጎንደር ሀብቴን፣ ኮሎኔሉ ገንዘብ ነው የሚፈልገው እሱን አፍጥኑልኝ፣ የጎንደሩ ኮሎኔል ፋፍዴን ነው፣ ሰኔ 15ን አስቦ ዘመነን ለመታገል ይመቸኛል፣ ሌሎቹንም እየደለልኩ ነው። እናም አፋጥነዋለሁ ታገሱኝ በሚል መልክ መግለጫውን ለቆ እንደገና አንገቱን ቀብሮ ሥራውን ቀጠለ።

፭ኛ፦ ታናሹ እስኬው ከሁለት የግንባርና ሠራዊት መሪነት መክሸፍ በኋላ የወጣው ብር ወጥቶ በሦስተኛው ሙከራ የአመራሩን ቦታ ለመቆናጠጥ ከአራቱም የዐማራ ግዛት በብር ተገዝቶም፣ ተከፍሎት የተገኘው ስብስብ በቂ እንደሆነ በማመን ወደ ማደራጀት ተገባ። ፍርዬም ስብሰባው እንዳይደነቃቀፍ ኢንተርኔቱን ለቀቀችለት። የባልደራስ ልጆች አስመራጭ ሆኑ። የኢትዮ 360ው ጋዜጠኛ ወግደረስ እና ጋዜጠኛ ጌጥዬ ያለውም አስመራጭ ሆኑ። ኤርምያስ ለገሰ፣ የኢንሳ ሰዎችም ስብሰባውን በላይቭ እንዲከታተሉት ሆነ። ሀብታሙ አያሌው፣ የግንባሩ ሰዎችና ግንቦቴዎችም ለፕሮፓጋንዳ ሥራው በሚገባ ተዘጋጁ። አበበ በለውም እንዳቅሚቲ ተዘጋጀ። ማርሸት ፀሐዩ በጠበጠው። አደፈረሰው። እንደገና ማርሸትን አስወግደው በምክትል ሰብሳቢውና በፀሐፊው አማካኝነት ስብሰባው ቀጠለ። ምክትሉ ዋና ሰብሳቢ ሆነ። ማርያምን ምስጢር ልንገራችሁ። (ምክትሉ መስፍን ነበር። መስፍንን አስቀምጠው ተስፋዬ የሚባል ልጅ ነው ኮሎኔል ፈንታሁን ሙሀባው እንደመስፍን እንዲተውን ያደረጉት" እንደዚያ ነው አሁን የሚሉኝ። መስፍን የጋሽ አሰግድ ደጋፊ ነው ተብሎ ስለሚታመን ነው እንዲያ ያደረጉት ተብሏል። ዘግይቶ የደረሰኝ ነው። አያችሁ ሌብነት። አበበ በለው፣ ሀብቴ ወልዴ፣ ኮሎኔል ፈንታሁን ሙሀባው፣ ሀብታሙ አያሌው። መከታው ታሪክ ይጠይቃችኋል። ይሄ ዐማራን መካድ ነው። ሃይማኖት የላችሁም እንዴ? ኧረ በማርያም።

"…እንቀጥል በስብሰባው መሰናክል ሆኖ የተገኘው "መስፈርት" የሚባል ማነቆን በድምፅ ብልጫ ትሻራለህ የሚል መስፈርት እናስቀምጥለት በሚል መሃላ ኢግኖር ተደረገ። መሪነቱን መያዝ የግዴታ ግዴታ መሆኑን ያልተረዱለት እነ ዘመነ፣ ባዬ፣ ምሬና ኢንጅነር ደሳለኝ ከስብሰባው ራሳቸውን ቢያገሉም ከላይ የመጣ ትእዛዝ ነውና እስክንደርን በአብላጫ ድምፅ ተመርጠሀል በሚል እንቋጨው፣ ቀሪው በፕሮፖጋንዳው የሚጠነክር ጉዳይ ነው ተባለና ድራማው በዚህ ተጠናቀቀ።

"…እነሱ ያላሰቡትና ያልገመቱት ነገር እኔም በስብሰባው ላይ ተደብቄ ተጋብዤ መገኘቴን ነው። እነሱ ስብሰባው አይቀዳም እናም እንደፈለግን እንፏልላለን ብለው ነበር የወሰኑት። የዐማራ አምላክ ደግሞ እኔን በመሃላቸው አስቀመጠና ሥራውን ሠራ። ሴራውንም አፈረሰው። ተመልከቱ ምርጫ …👇ከታች ይቀጥላል…✍✍✍

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

መልካም…

"…ዘወትር ያመሰግን ዘንድ የሚጠበቀው 1ሺ አመስጋኝ አሁን ሞልቷል። እንዲያውም 9መቶ ጭማሪ አሳይቷል። እግዚአብሔር ይመስገን። ከምስጋናው በኋላ በቀጥታ የምንሄደው ወደ ተለመደው ርዕሰ አንቀጻችን ዘንድ ነው።

"…የዛሬው ርዕሰ አንቀጻችንም የታናሹ የእስክንድር ነጋና የሴረኛ፣ ቅጥረኛ ጓዶቹን ሴራ ነው በድፍረት ለማፍረስ የምላላጠው። አበበ በለው እንኳ ከመደንበሩ የተነሣ በቀለ ዘመድኩን እስኪለኝ ድረስ ነው ነርቫቸውን የበጠስኩት። ሦስት መጽሐፍ የደረስኩ እኔን፣ ስንትና ስንት የቤተ ክርስቲያን መዝሙራትን የደረስኩ እኔን ዘመዴን እንግሊዝኛ አቀላጥፌ አለመናገሬን ያቺን ድክመቴን ተጠቅሞ አቤ እንኳ እስክስታ ወረደብኝ። አቤ ግን ወቀጣህ ተመችቶኛል። ስሜን ግን አስተካክልልኝ። በለው አቤ እማጸንሃለሁ። ስሜን አስተካክል። ሁለት ሰዓት ማውራት እንጂ ሁለት መስመር መጻፍ የማይችል ሰው እኔ ክፉ አልናገርም። እንዳልነክስህ እንጂ ከነከስኩ አልፋታም። ወዳጆች አቤን ምከሩልኝ። የማታውቀው ነገር አለና አትዘባርቅ በሉልኝ።

"…እስኬውን ዛሬም እዠልጠዋለሁ። ሱሪውን ዝቅ አድርጌ ነው እንደ ልጅ በሳማ የምለበልበው። በጦማር ሳማ ነው ታዲያ። ጫካ ገብቶ፣ ሚስቱን ትቶ አይሠራም። ድርድር በፋኖ ስም ካካ ነው። እፉ ነው። አለቀ።

"…ሀብታሙ አያሌው ብዙ ነጥብ እየጣለ ስለሆነ ብዙም አልሄድበትም። ለምኜ፣ አስለምኜው አልሰማ ያለ ስለሆነ ሠራዊቱ የሚለውን የእሱን ሠራዊት ታቅፎ እንዲቀር አድርገን እስክናስቀረው እንዲሁ እያስለፈለፍኩ ሙድ እየያዝኩበት እንቀጥላለን። ዛሬም ራቁቱን ያስቀረዋል ርዕሰ አንቀጼ።

"…በጎንደር እስክንድርንና ሀብታሙን ባለመደገፉ የተገደለው ውብአንተ አሁንም እስክንድርና መከታው ሊገድሉት ስለሚያሳድዱት አሰግድም ጀባ እላችኋለሁ።

• ለማንበብ፣ አንብባችሁም አስተያየት ለመስጠት ዝግጁ ናችሁ ወይ…?

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

መልካም…

"…18 😡😡 ብው ብሎ መቆጣቱን ቴሌግራሜ በነገረኝ ሰዓት ነበር ምሥሉን ያስቀረሁት። አሁን የተቆጣው ሰው ቁጥር ሳይጨምር አይቀርም። 😂😂😂። ይውጣላቸው።

"…ትልቅ መርሀ ግብር ላይ እንግድነት ተጠርቼ እዚያ ነው የዋልኩት። እንደልቤ በቲጂ ሰፈሬ መመላለስ አልቻልኩም። የምሳ ግብዣ ምናምኑ ላይ ነው ወጣ እያልኩ ርዕሰ አንቀጹን እንኳ ጽፌ የለጠፍኩላችሁ። አሁን ዝግጅቱ አልቋል። ወደቤቴ ከመሄዴ በፊት ከራየን ወንዝ ዳር ቁጭ ብዬ የአውሮጳ በጋ ምሽት ፀሐይና አየር እየተቀበልኩ በኮመንታችሁ ልዝናና።

"…ረጅም ወክ በልቻለሁ። 😁 አሁን የአስተያየት መስጫ ሰንዱቄን ከፍቼ እስከ መኝታ ሰዓቴ ድረስ አስተያየታችሁን ልኮምኩም። የተናደ😡ዳችሁ ሰዎች ብትኖሩም በቤቴ መሰንበት ካማራችሁ ተረጋግታችሁ በጨዋ ደንብ ሓሳባችሁን መግለጽ ትችላላችሁ። የተፈቀደም ነው።

"…1…2 3✍✍✍ ጀምሩ

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

👆ከላይኛው የቀጠለ✍✍✍ …የሸዋ ዐማሮችን
የእነመከታው ቡድን እንዴት እንዳማረረ በማስረጃ እመጣበታለሁ። እስክንድር ዙሪያ፣ ከነመከታው ጋር የተከማቹት የሀሰን ከሪሙ የወሎ ሕብረት ሰዎች መሣሪያ ታጥቀው ተሰልፈዋል። እስክንድርም እነሱም ግን ይሸነፋሉ።

"…ሀብታሙ አያሌው ፀረ ዐማራ ግንቦቴም ወያኔም ነው። በወሎዬነት ሰበብ የዐማራን ትግል እየሸጠ ያለ ሰው ነው። ወሎ ይወለድ እንጂ ሀብታሙም ወይ ትግሬ አግብቷል፣ አልያም እሱም ራሱ ትግሬነት አለበት። አበበ በለው ፀረ ዐማራ ነው። የፖለቲካው ቅማንት አቀንቃኝ እንደሆነ ነው የሚነገርለት። ብሩክ ይባስ የደቡብ ጉራጌ ነው ተብሏል። ኢየሩስ ትግሬ ትሁን ዐማራ አላውቅም። እስክንድርን የከበቡት በሙሉ ፀረ ዐማሮች ናቸው። አዎ ይሄ ፀረ ዐማራ የግንቦቴ ካምፕ መፍረስ አለበት። የገንዘብ ምንጩም መድረቅ አለበት። የዐማራ ትግል በድፍረት መገምገም አለበት። ትግሉን መምራት ያልቻሉ እንደ ዘመነ ካሴ አይነት ሰዎችም ይሁኑ እንደ አሰግድ አይነቶቹ ይገምገሙ። ምሬም ይሁን ሀብቴ፣ ባዬም ይሂን ይገምገም። ይገምገሙና የሚችሉት ይቀጥሉ። ያልቻሉ ደግሞ ለወጣት አርበኞች ሥፍራውን ይልቀቁ። እንደ እስክንድር ዓይነቱ ፀረ ዐማራ ግን ከዐማራ ትግል በጊዜ ገለል ማለት አለበት። ወደ ጠበል ወይ ወደ አማኑኤል።

"…እስክንድር ሚስቱ ትግሬ ናት። የእስክንድር ገንዘብ አሰባሳቢ ዶር አምሳሉ ወንድሙ የደቡብ ጎንደር አስተዳዳሪ የሆነ ብአዴን ነው። እስክንድር ጎንደር ሲሄድ ያረፈው ዶር አምሳሉ እናት ቤት ነው። የእስክንድር ሚስቱ ትግሬ፣ የዶር አምሳሉ ሚስት ዳውን ዳውን ኢትዮጵያ የምትል ሰልፈኛ ትግሬ፣ ዶር አምሳሉ ግንቦት ሰባት የብርሃኑ ነጋ ጓደኛ፣ የአንዳርጋቸው ጽጌ ወዳጅ፣ ዶር አምሳሉ የባልደራስ ገንዘብ አሰባሳቢ ትግሬ ሚስቱ የባልደራስ ገንዘብ ቆጣሪ። ባልደራስን አፍርሶ ግምባሩ ብሎ ሲመጣ አሁንም የግንባሩ ገንዘብ ሓላፊ የትግሬዋ ባል ግንቦቴው ዶር አምሳሉ። ሚልዮን ዶላር ከሰበሰቡ በኋላ የዐማራን ኪስ አራቁተው ሲያበቁ ለፋኖ ገንዘብ እንዳይደርግ አድርገው ትግሬዎቹ እነ እስክንድር ነጋ፣ ቅማንቴው አበበ በለው፣ ኢህአዴጉ ሀብታሙ አያሌው ትግሉን አሳስረው ሽባ አድርገው ሲያስቀሩትም ሓላፊው ብአዴን ግንቦቴው የትግሬዋ ባል አምሳሉ ነበር። ግንባሩ ፈርሶ ሠራዊቱ ብሎም ሲመጣ አሁንም ሙሉ ውክልና የተሰጠው ለዶር አምሰሳሉ ነበር። አይገርምላችሁም? እስክንድር ነጋ እኮ ኢህአዴግ ግንቦቴውን ኦሮሙማውን ኤርምያስ ለገሰ ዋቅጅራን አምጥቶ የባልደራስ ባለሥልጣን ያደረገ ጨካኝ ገገማ የሆነ ሰው ነው። የዐማራን ሕዝብ አዋራጅ የተለከፈ ቀውስ እኮ ነው። ማርያምን እኔ አልፋታውም። ፌስታል ይዞ፣ ወንዝ ውስጥ ቆሞ በፎቶ ቦለጢቃ ያጀዘበን ሌላኛው አቢይ አሕመድ እኮ ነው። እኔ ዘመዴ ከእስክንድር ጎን ነን የሚሉትን በሙሉ እፋለማቸዋለሁ። አሁን የዐማራ ትግል ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል። እስክንድር በዐማራ ስም መደራደር፣ ዐማራን መምራትም አይችልም። ቀውስ ትግሬ የሆነ ሰው በፍጹም አይቻለውም። እስክንድር ስለወልቃይት ሲያወራ፣ ስለ ራያ ሲያወራ፣ ስለ መከተል፣ ስለ ደራ ሲያወራ ሰምተኸው ታውቃለህ? አታውቅም። እንዲያውም በእነ ስታሊን በኩል ሰበር ዜና አሠርቶ ይኸው ራያን ሲያስወርር ነው ያመሸው። እስክንድር ዘረ ትግሬው የዐማራ ከፋፋይ ጋግርት፣ ውግምት ነው። ምንቆርጦት ስለ ወልቃይት፣ ደራ፣ መተከል፣ ራያ ያወራል? ድል ለዲሞክራሲ ይልኛላ ይደምክርሰውና።

"…አሁን እኔ ላይ የሚንጫጩትን ልብ ብላችሁ ተመልከቱ። ጥንብ ግንቦቴዎች። ፈትፋች የግንቦቴ ጉራጌዎች ናቸው። የበቀደሙን መግለጫ ያነበበው እኮ የመከታው ሰውዬ መምህር የሚባለው የኢዜማ አባል እኮ ነው። ፋኖ ይፈርሳል ብሎ በድፍረት የተናገረ። ቪድዮው አለኝ። የመከታው ግሩፕ በግንቦቴ ቲክቶከሮች እንዲህ የሚደገፈው እኮ እስክንድር የግንቦቴ ቡችላ ስለሆነ ነው። በዝርዝር እመጣበታለሁ። አሁን ወደ ወዳጄ ሄኖክ የሺጥላ አንሰላሳይ፣ ጠያቂ ጦማር ልመልሳችሁ። ደፈር ብለን እንነጋገር። በውስጥ ጨርሱ፣ ዐማራ ይከፋፈላል ወዘተ፣ ጠላት ደስ ይለዋል የሚባል ነገር አይሠራም። የሞቀ ቤቱን ጥሎ በረሃ ገብቶም አይሠራም። በ6 ዓመት ሦስት ሚዲያ አምስት ፓርቲ የመሠረተ ይሄን የፓርቲ ኢንኩዩቤተር የሆነ ተብታባ ሰው እታደገዋለሁ የሚል መብቱ ነው። እኔም እገፋበታለሁ።

"…እንዲያው እኮ እግዚአብሔር ዐማራን ስለሚወደው ነገርየውን በጊዜ አንሥቶ ለግምገማ አቀረበው፣ በእኔ በኩልም አፈነዳው እንጂ ተዘናግተህ አልቆልህ ነበር እኮ። አሁን ግን በፍጹም አትፈሩ። ደፍራችሁም ተነጋገሩ። አታዩም እንዴ ፀረ ዐማራው ቹቹ ነሪ ትናንት ሲሰድበኝ ብዙ ሰው ምን ነክቶት ነው ሲል እያየሁ ነበር። ቹቹ እኮ ልክ ነው። የእስክንድር እናት ጉራጌ ከሆነች ቹቹ ለእስክንድር አግዞ ባይሰድበኝ ነበር የሚገርመው። የፖለቲካው ወያኔ ወለዱ ቅማንቶች፣ አገው ሸንጎዎች ቢሰድቡኝ አይግረማችሁ። ፎቶዬን ዘቅዝቀው ቢሰድቡኝ አይድነቃችሁ። ጉሮሮአቸው ላይ ስለቆምኩ ነው። እኔን የጎጃም ያውም የዘመነ ደጋፊ አድርገው የሚቆጥሩም አሉ። እኔ ግን አይነኬ የሚመስለውን ዘመነ ካሤንስ መቼ ለቀቅኩት እና ነው ደጋፊው የምሆነው። እኔና ዘመነ ገና ቁጭ ብለን ተግባብተን የምንመክርበት ትልቅ አጀንዳም አለን። ዘመነም ከወዲሁ ተተኪ እንዲያዘጋጅ ንገሩት። በዝሆኖች ፍጥጫ ሳሩ መጎዳት የለበትም።

"…ዘመነ በቀደም በእስክንድር ሴራ የጎጃማ ፋኖን አጠቃላይ የጦር መሣሪያውን እና አደረጃጀቱን መንግሥት እየሠማው አሳልፎ ሰጥቷል። የብሔራዊ መረጃ አገልግሎት በእነ መከታው ስልክ ሁሉን ነገር ሰምቶ መዝግቦታል። ኤርሚያስ ለገሰ በእስክንድር በኩል የስብሰባው ተሳታፊ ሆኖ እንዲዘግብ ተደርጓል። ሀብታሙም ነበረ። እኔም ነበርኩ። እነሱ የማያውቁት እኔ መኖሬን ነው። ዘመነ በጅልነት፣ ወይም ሆን ብሎ ይሄን ከባድ ስህተት ፈጽሟል። አሁን የጎጃም ፋኖ አደረጃጀቶች ለዚህ ጥፋት የሆነ መላ ማበጀት ይኖርባቸዋል። የታክቲክ ለውጥ ልታደርጉ ይገባል። ገና ከዘመነ ጋርም የምናወራርደው አስደንጋጭ ሂሳብ አለን። በአዳኜ የዐማራ ትግል ላይ ዐውቆም ይሁን ሳያውቅ እንቅፋት የሚፈጥር ማንም ይሁን ማን ወላዲተ አምላክ ምስክሬናት አልፋታውም። በመረጃና በማስረጃ በምሥልና በድምጽ ይፋ አድርጌ ፍርዱን ለሕዝብ ነው የምሰጠው። ማንም አይቀረኝም። የዐማራ ትግል መዳኛዬ ነው። መጽደቂያዬ ነው። ገነት መንግሥተ ሰማያትም መግቢያዬ ነው ብዬ ወስኛለሁ። ወሰንኩ፣ ወሰንኩ ነው። አበቃ። በሰፊው እመለስበታለሁ።

"…ሄኖክ የሺጥላ እንዲህ አለ…

"…አንዳንድ ነገሮች አጋጣሚ ይመስሉኝ ነበር። በንጽህናም ግጥምጥሞሽ ናቸው ብዬ ዐስብ ነበር።

ለምሳሌ የሚከተሉት

አጋጣሚ ፩

"…ጃዋር ማንንም ተዋዋሚ በህይወቱ ሲያወድስ ሰምተነው አናውቅም። ጃዋር ክርር ባለ ክህደቱ ነው የሚታወቀው። በመሰረቱ ጃዋር እውቅናን ያገኘው በእውቀት ላይ የተመሰረት ውሸት በመንዛት ነው። ታሪክን ለፍላጎቱ አጣሞ፤ ንባብን ና ሁኔታን በማዳቀል ፤ የ አማራ ህዝብ ላይ እልቂት ካወጁት ግምባር ቀደም የኦሮሙማ ሃይሎች አንዱ ነው። ንዲህ ያለው ጽንፈኛ ግን ስክንድር ነጋን ሲያወድስ አስተውለናል። ባጋጣሚ ወይስ በፕላን?

👇ከታች ይቀጥላል…✍✍✍

👆ከላይኛው የቀጠለ…✍✍✍

አጋጣሚ ፪

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"…መከታው ከመደንገጡ የተነሣ ይሄንን መሣሪያ ይዞ ፎቶ ተነሥቶ በፌስቡክ ሠራዊቱ በኩል አስለቅቋል። የሚገርመው ግን ይሄንን መሣሪያ መከታው ማርኮት አይደለም። ገዝቶትም አይደለም። ምስጢሩን እኔና እነሱ ብቻ ነን የምናውቀው። ማጭበርበር፣ ፌክ ፕሮፓጋንዳ ከእንግዲህ አይሠራም። ይልቅ መሣሪያውን ለልጁ መልሱለት። 😂 ሌባ ሁላ።

"…በገዛ እጃን የጀግንናቸው የጎረምሳ ዘራፊ ወንበዴ ሁላማ አይቀልድብንም። የሰገጤ መጫወቻማ አንሆንም። የዐማራ ትግል መንግሥተ ሰማያት መግቢያዬ ነው። እናም እሾህ አመኬላውን ሁላ ነቅዬ መንግዬ ለማውጣት ያለ እረፍት እፋለመዋለሁ።

• ውይ ይቅርታ ከ10 ደቂቃ በኋላ ምን የመሰለች ፈውስ የሆነች ርዕሰ አንቀጽ እለቅባችኋለሁ።

• አላችሁ አይደል?

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"…በልቡ ሰባት ርኵሰት አለበትና በቃሉ አሳምሮ ቢናገርህ አትመነው። ጠላትነቱን በተንኰል የሚሸሽግ፥ ክፋቱ በጉባኤ መካከል ይገለጣል። ጕድጓድን የሚምስ ይወድቅበታል፤ ድንጋይንም የሚያንከባልል ይገለበጥበታል።” ምሳ 26፥ 25-27

"…እንደምን አደራችሁ?
"…እንደምን አረፈዳችሁ?
"…እንደምን ዋላችሁ?
"…እንደምን አመሻችሁ?

"…እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"…ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር

"…የጠላትን ሴራ አፈርስ ዘንድ ዛሬ ምሽት 2:15 ላይ በመረጃ ቲቪ ነጭ ነጯን እነግራችሁ ዘንድ ከተፍ ብዬ እመጣለሁ። በሴራ የተሞላውንና በዐማራ ጠላቶች ዘንድ ጮቤ ያስረገጠውን በ6 ዓመት ውስጥ አምስተኛውን ሳይወለድ የሞተ ድርጅት የሊቀመንበርነት ምርጫን በተመለከተ የስብሰባውን የድምጽ ቅጂ አብረን እንሰማዋለን። 

• ቲክቶክ 👉🏿 zemedkun.b" rel="nofollow">http://tiktok.com/@zemedkun.b

• ትዊተር 👉 https://twitter.com/MerejaMedia

•በራምብል 👉 https://rumble.com/c/Mereja/live
• ዩቲዩብ 👉 https://www.youtube.com/watch?v=Ckr-2zuIPos

• ሻሎም… ሰላም…!

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"…መልካም…

"…ስብሰባ ላይ ነበር የቆየሁት። ጨርሼ ተመልሻለሁ። አገዛዙ ኢንተርኔቱን የከፈተው በውጊያ፣ በጦርነት ያልቻለውን የዐማራ ፋኖ ትግል በእስክንድር ነጋና በዘመነ ካሴ ንትርክ አፈር ከደቼ ሊያበላው ፈልጎ ነበር። የዐማራ ትግል ግን ከዘመነ ካሴ በውቄም፣ ከእስክንድር ነጋ ፈንታም በላይ ነውና ይሄን ቅዱስ ትግል ምንም ማንም ምድራዊ ኃይልና ምድራዊ ሴራ ሊያስቆመው፣ ሊያፈራርሰው አይችልም። ይሄን እኔ አረጋግጥላችኋለሁ። እስክንድርም ዘመነም ከዐማራ ፋኖ ትግል በታች ናቸው። ያለ እስክንድርና ያለ ዘመነም የዐማራ ፋኖ ትግል ግቡንም ይመታል። እንዲህ ነው እኔ መራታው የማምነው።

"…እናም አሁን እጽፈዋለሁ ብዬ የነበረውን የገራገሩን፣ የጀግናው አርበኛ ሀብቴ ወልዴን ጉዳይ እና ይሄን የማፍያ ስብስብ አደገኛ የዐማራ ትግል ጠላፊ ቡድን ያደረገውን የምርጫ አካሄድ በስብሰባው ላይ ተገኝቼ የቀዳሁትን ሙሉ የድምጽ ቅጂ ዛሬ ማታ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት 2:00 ሰዓት ጀምሮ በመረጃ ቴሌቭዥን እና በእኔ ቲክቶክ ገፅ የቀጥታ ስርጭት ላይ አቀርበዋለሁ።

"…እገሌ ምን አለ? እገሌ ምንአደረገ ብላችሁ በተባራሪ ወሬ ምን አጨቃጨቃችሁ? ፍርጥ፣ ዝርግፍ አድርጌ እገላግላችሁ የለ። እንደዚያ ነው።

"…ኤርትራ ያለው የሀብቴ ወልዴ ጥይት አቅራቢ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌም አታሸንፍም። ኡጋንዳ ያላችሁ ሁለት የዘመነ ካሴ የግል ፀበኞች ሀብቴ ወልዴን ከጎንደር፣ ኮሎኔል ጌታሁንን ከጎጃም ከጎጃም እዝ ነጥላችሁ አስወጥታችሁ፣ ሁለት ሚልዮን ብር በባንኩ እንዲገባ ካደረጋችሁ በኋላ ለእስክንድር እንደሸጣችኋት አትቀሯትም። ዘመነን ካልቻለ መቀየር እንጂ ዘመነን በመጥላት የጎጃምን ትግል አፈር ከድሜ ለማብላት እንዲህ ማድረግ ተገቢ ነው ብዬ አላምንም።

"…የዐማራ ፋኖ ትግል ድኗል፣ የሴረኞች ሴራም ፈራርሷል። ብራቮ ዘመዴ። ✊💪🏿

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

"…የመከታው ቀኝ እጅ ናት። ከ8ንት ነው ከ10ኛ ክፍል ማለፍ ሲያቅታት ወደ አረብ ሀገር ትሄዳለች። እዚያ ጂኒ ይለክፋትና የሸዋ ዐማሮች ሳንቲም አዋጥተው ለጠበል ወደ ሸዋ ይልኳታል። በሸዋ ጠበል እየተመላለሰች መከታውን ታገኘዋለች። መኬ ቁመናዋን ሲያይ ወሴ ነገር ናትና የሴቶች ጦር ሓላፊና የሸዋ የመከታው ጦር ሕዝብ ግኑኝነት ሓላፊ ማለት ነው።

"…መቅደስ ወይም በትግል ስሟ ባርች ነፃ የኢንተርኔት የአየር ሰዓት ኦህዴድ ይሰጣትና እስክንድር እየጻፈ የሚሰጣትን እንድትለጥፍ ይደረጋል። ቲክቶክ ከፍታም ቀኑን ሙሉ እንድትጣድም ይደረጋል። ልጅቷ የሰፈረባት አጋንንት ከእስክንድር አጋንንት ጋር ተዳምሮ ሸዋን ማመስ፣ እኔንም እስኬው በእሷ ላይ አድሮ መስደብ ይጀምራል።

"…በጎንደር ሀብታሙና እስክንድር ውባንተ በእናንተ ስር አልገባም ስላለ አዋክበው እንዳስመቱት ሁሉ በሸዋም አሰግድ እንቅፋት ስለሆነባቸው ቦርከና ሚዲያ ላይ ፕሮፌሰሩ እንደከተበው መነሻዬ ዐማራ፣ መድረሻዬም ዐማራ የሚሉት ይመቱ እንዳለው እስክንድርና መከታው አሰግድ ይመታ ዘንድ ይወስናሉ። ከዚያም በዚህች ልጅ በኩል ነውረኛ ቃላት ተጠቅመው አሰግድን ያዋርዱታል። ሊገድሉት ሲሄዱ አሰግድን ሕዝቡ ያሸሸውና እንደ ውብአንተ ሳይሞት ይቀራል።

"…አሁን ጀነራል ተፈራ ማሞን እንዴት ትላንት እንደተጫወቱበት እንደሸወዱት ማርያምን ዛሬ ማታ በመረጃ ቴሌቭዥን አሳያችኋለሁ። በጣም ነው የተናደደው። ዘመዴ "ምን አለ?" ያሉት ፋኖዎች በሙሉ ዘመዴ ጓ ማለቴን ሲያዩ ኮሎኔል ሙሀባውም ሸርተት፣ የጎንደሩም ኮሎኔል ታደሰ እኔ አልመረጥኩም ማለቱ ተሰምቷል። የመከታው ጦር ወደ ሌላ ይገባል። ምስኪኑ መከታውም ከፋኒት ባርች ጋር እያዘንኩለት ሜዳ ላይ ከእስኬው ጋር ይቀራል። ባርች ግን እንደ ማርሸት ሳልገባላት ቀድማኝ ተፈጠፈጠች።

• ማርያምን ዐማራ ግን በዝርራ ያሸንፋል።

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

የዘመነ መልእክት ነው

"…የብልጽግናን ሠራዊት እንኩትኩቱን የጎጃም ዐማራ ፋኖን አግልለህ እንዴት ነው እድሜ ልኩን ድል ለዲሞክራሲ እያለ ሲያዝገን የነበረ፣ ፖርቲ እየፈለፈለ በማምከን የሚታወቅ ሰው፣ የዐማራ ሕዝብ በነፍጤ ነው ለውጥ የማመጣው፣ ነፃነቴን የምቀዳጀው ብሎ ጫካ ሲገባ ተከትሎ ገብቶ፣ ተኩሶ የማያውቅ፣ ድሮኗ እየጠበቀችው፣ እሱ ሰው መስሏቸው የረዱት በሙሉ በድሮን እየተጨፈጨፉ፣ ከደንበጫ ሸዋ ድረስ በእግር 3 ወር የሚፈጅ መንገድ በግማሽ ቀን ገባ እየተባለ 😂 ብአዴንና ብልጽግና አድራሽ ፈረስ አድርገው የሚጋልቡት ሰው በዚህ መጠን የዐማራ ትግል ላይ ይቀልዳል?

"…የሌሎቹን የጋራ መግለጫ እየጠበቅኩ ነው። ምስጋናው አንዷለምን ጨምሮ ይሄን ትግል ለመጥለፍ ብአዴናዊ ጠባያቸውን ይዘው የገቡት ሁሉ ከሠራዊቱ ውክልና ይሰናበታሉ ብዬ እጠብቃለሁ። የዐማራ ፋኖ ትግል እሳት ለብሶ፣ እሳት ጎርሶ እንደ ንሥር ታድሶ ይወጣል።

"…አገዛዙ ኢንተርኔቱን የከፈተው ለዚህ ተግባሩ ነበር። ጄነራል አበባው ታደሰ ሰሞኑን የምሥራች ጠብቁ ፋኖን ለሁለት እንከፍለዋለን አለ ተብሎ የተነገረውም ይሄንኑ ለማለት ነው። የሚከፈል ፋኖም የለም። ተዋጊ አርበኞቹ ከቦታቸው ዝንፍ ሳይሉ እንዳሉ ናቸው። በስብሰባው ላይ ሻለቃ ዝናቡ የተናገረው ነገር አስደማሚ ነው። በመረጃ ቲቪ ሰምታችሁ ትፈርዳላችሁ። የበለጠ ነው ያከበርኩት። ዝናቡን የእነ አስረስና የእነ ዘመነ ካሴ እንዝህላልነት፣ የባህታዊ ፖለቲካ ቀፍድዶ ባያስረው ኖሮ ከዚህም በላይ በጀግንነት ተአምር መሥራት የሚችል ነበር። ኮሎኔል ጌታሁን ከዘመነ ካሴ ጋር እንዳይገናኝ አድርገው ከእስክንድር ስር እንዲለጠፍ ያደረጉት ከዘመነ በታች ያሉ ኮተታሞች ናቸው። እሱም ይሰተካከላል ብዬ አምናለሁ።

• የዘመነ የእጅ ጽሑፍ ያልተነበባችሁ በኮመንት ሰንዱቁ ውስጥ ታነቡት ዘንድ አስቀምጥላችኋለሁ።

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

“…የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ።” ማቴ 7፥15

"…እንደምን አደራችሁ?
"…እንደምን አረፈዳችሁ?
"…እንደምን ዋላችሁ?
"…እንደምን አመሻችሁ?

"…እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

ኦነጎቹ ምነው አበዱብኝሳ…?

"…የግንቦቴው፣ የግንባሩ፣ የሠራዊቱ፣ የአገው ሸንጎው፣ የወየንቲው፣ የፖለቲካው ቅማንት፣ የኦሮሙማው ብልጽግናዎች እኔ ላይ መጮሃቸው የተለመደ ነው። ኦነጎቹ ምናቸውን ብነካው ነው እንዲህ ዋይ ዋይ ብለው የሚጮሁብኝ?

"…ለማንኛውም ወያኔ እስክንድርን በማሰር በመፍታት አጀገነችው። አቢይ ሲመጣ እኔ ነኝ የምነግሰው ሲል እስክንድር በአቋራጭ ለንግሥና ደብረ ኤልያስ ሄዶ ሊቀባና ሳልሣዊ ቴዎድሮስ ሆኖ ሊመጣ ከጫፍ ሲደርስ አቢይ ተመስገን ጥሩነህን አስልኮ እንዳይቀቡት ቢልም ይነግሣል ብለው የፈሩት እነ አቢይ ደብረ ኤልያስን አወደሙት። ብአዴን የያዘውን እስክንድርን አጀግኖ ተዋጋኝ ብሎ ለቀቀው።

"…የዐማራ ፋኖን የገንዘብ ምንጭ ያደረቀው እስክንድር ነጋ ዛሬ አዲሱን ድርጅቱን ከማወጁ በፊት ያለፈው እሁድ የሥላሴ ዕለት ብልፅግና በዐማራ ክልል ኢንተርኔት ለቀቀ። ከ3 ቀን በኋላ ዛሬ ደግሞ ምሬ ወዳጆ፣ ዘመነ ካሴን፣ ባዬ ቀናው፣ አሰግድ መኮንን፣ እነ ኢንጅነር ደሳለኝ በሌሉበት፣ ኮሎኔል ሙሀባው ጋር ባለ በመስፍን ወይም ተስፋሁን በተባለው ሰብሳቢ ከኮንፈረስ ኮል ስብሰባው ተባረው በሀብቴ፣ በመከታውና በኮሎኔል ፈንታሁን ሙሀባው አማካኝነት እስክንድር ነጋ በዓመት ውስጥ ሦስተኛውን ድርጅቱን ፈጥሮ መሪ ሆኖ ከቺሳ ብሏል። 😂😂😂

"…አንድም ቦታ ሳይዋጋ በመከታው ጦር ሲጠበቅ የከረመውና የዐማራ ፋኖን መርቼ ካልነገሥኩ ሞቼ እገኛለሁ ባዩ እስክንድር ነጋ አሁን በዐማራ ፋኖ ስም ሊደራደር አስፍስፎ መጥቷል። ነገር ግን አይቻልም። አጭቤ ሁላ እፋታህ መስሎሃል።

"…ሙሉ የስልክ ኮንፍረንሱን ትስቁ ዘንድ እለቀዋለሁ። ሁሉም ነገር እንዲህ እየጠራ መምጣቱ ሸጋ ነው። ግቦቴም፣ ኦነጌም ወየንቲም ተንጫጫብኝ። ዐማራ እንደሁ ድብን አድርጎ ያሸንፋል። ቃሌ ነው ሴራውም ሁሉ እንደ እንቧይ ካብ ይፈርሳል።

Читать полностью…

Zemedkun Bekele (ዘመዴ)

👆ከላይኛው የቀጠለ… ✍✍✍ …ለቅቆ እነ አኪላን ዝምበሉ ማለትም ልክ አይሆንም። የግንባሩ፣ የፒለቲካው ቅማንቴ፣ የፖለቲካው አገው ሸንጎ፣ የኦሮሙማው እና የትግሬው የሚዲያ ሠራዊት የእነ አሰግድ ፋኖ ላይ ተቀናጅቶ ከብልጽግና ሠራዊት ጋር እየዘመተባቸው እያየሁ እነ አኪላን ከተጀመረው ብሽሽቅ ራሳችሁን አግልሉ ማለት አይቻልም። ብሽሽቅ ብሽሽቅ ነው። አንዱ አብሻቂ እንደፈለገው በጀት ተመድቦለት ሌላኛውን ያብሽቅ፣ ሌላኛው ግን ዝም ይበል ይባላል እንዴ? እነ አኪላን መመከር መገሰጽ ያለብኝንም በነገው ዕለት በይፋ በርዕሰ አንቀጼ እመጣበታለሁ። ይሰሙኛል ብዬም ተስፋ አደርጋለሁ።

"…ይሄኛው ርዕሰ አንቀጽ እንደ መንደርደሪያ ነው። እንደ መግቢያ ማለት ነው። አፒታይዘር በሉት። ዋናው ይከተላል። እኔ የሓሳብ ነጋዴ ነኝ። ኮሶ የሆነ ሓሳብ ሻጭ ነኝ። የሆድህን ፀረ ዐማራ ትላትል ከአእምሮህ ሁላ ፍቄ የማወጣልህ የማሽርህ ኮሶ ነጋዴ ነኝ። አይስክሬም መብላት እንጂ መሸጥ አይሆንልኝም። አልታወቅበትም። ዕጣ ክፍሌም አይደለም። ነጭነጯን ዘርግፌ አዳሜና ሔዋኔ መስቀል እንዳየ አጋንንት፣ ፀበል እንደነካው ሰይጣን ሲያጓራ እንደማየት የሚያስደስተኝ ነገር የለም። እንደ ዘመነ አይነቱ ስተቸው፣ እንደ ምሬ፣ አይነቱ ስተቸው እልል ብሎ ትችቱን ተቀብሎ ወደፊት ይስፈነጠራል። እንደ እስክንድር አይነቱ አቦ አቦ፣ ጎሽ ጎሽ የለመደ የባርያ ጠባይ ያለው ደግሞ ጀግንነቱ በመዋጮ፣ በድርጅት የመጣ ስለሆነ ሲተች ይደናበራል። ከትችቱ ለመራቅ ቅጥረኛ ገዝቶ ያሠማራል። እኔ ደግሞ ወይ ፍንክች፣ ወይ ንቅንቅ እስከመጨረሻው ውግም።

“…ሸለቆው ሁሉ ከፍ ይላል፥ ተራራውና ኮረብታውም ሁሉ ዝቅ ይላል፤ ጠማማውም ይቃናል፥ ስርጓጕጡም ሜዳ ይሆናል፤” ኢሳ 40፥4

• ድል ለዐማራ ፋኖ…!

• ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…!

• ድርጅቱ ዘመዴ ነኝ አሸበርቲው ከራየን ወንዝ ማዶ

Читать полностью…
Subscribe to a channel