thiqaheth | Unsorted

Telegram-канал thiqaheth - THIQAH

15262

ይህ ቲቃ (ታማኝ) ኢትዮጵያ የኢትዮጵያን ጨምሮ ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊ መረጃዎች የሚቀርቡበት ገጽ ነው።

Subscribe to a channel

THIQAH

"የአሜሪካ ውሳኔ ያሳስበኛል" - የአፍሪካ ህብረት

የአፍሪካ ህብረት የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር በአንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት ላይ ያሳለፈውን የጉዞ እግድ ውሳኔ ተቃውሞታል።

ህብረቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ "ሚዛናዊ አካሄድና ገንቢ ውይይት" እንዲደረግ ጠይቋል።

መመሪያው በአፍሪካና በአሜሪካ መካከል ያለውን የግለሰቦች ግንኙነት እና የንግድ ልውውጥ ይጎዳል ብሏል።

የአፍሪካ ህብረት የአሜሪካን ሉዓላዊ መብት እና የዜጎችን ደህንነት እንደሚያከብር በመግለጫው ጠቅሷል። 
#yen

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

ሳዑዲ አረቢያ ያለፍቃድ የሄዱ 269,678 የሃጂ ተጓዦችን ወደ መካ እንዳይገቡ አገደች።

ከታገዱት መካከል "23,000 የሚሆኑት የሳዑዲ ዜጎች ናቸው" ተብሏል።

ይህን ተከትሎም ሳዑዲ 400 የሀጂ ጉዞ አዘጋጅ ካምፓኒዎችን ፍቃድ ሰርዛለች።

በዘንድሮው የሀጂ ጉዞ ከ1.4 ሚሊዮን በላይ ተጓዦች መሳተፋቸውን የሀገሪቱ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።

በዚህ አመታዊ ሃይማኖታዊ በዓል ወቅት በየአመቱ ህጋዊ ያልሆኑ ተጓዦች ወ ደሳዑዲ እንደሚገቡ ባለስልጣናቱ ገልጸዋል። 
#thenewarab

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

"የዩክሬኑ መሪ ሰላም ይፈልጋል ብየ አላስብም" - ፑቲን

"ውይይት አድርገናል፣ ግን ወደ ሰላም የሚያመራ አይደለም" - ትራምፕ

ፕሬዝዳንት ፑቲንና የአሜሪካ አቻቸው ዶናልድ ትራምፕ ከአንድ ሰዓት በላይ የቆየ የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን ሁለቱም ወገኖች ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ዩክሬን በቦምብ ጣይ አውሮፕላኖቿ ላይ ላደረሰችው ጥቃት ሩሲያ እርምጃ እንደምትወስድ ለትራምፕ አሳውቀዋቸዋል።

"የዩክሬኑ መሪ ሰላም ይፈልጋል ብየ አላስብም" ያሉት ፑቲን፣ ትላልቅ መሰረተ ልማቶች መውደማቸውን ተናግረዋል።

ትራምፕ በበኩላቸው፣ ከፑቲን ጋር መወያየታቸውን ገልጸው፣ "ዩክሬን ስላደረሰችው ጉዳት ተወያይተናል፣ ግን ወደ ሰላም የሚያመራ አልነበረም" ብለዋል።

ትራምፕ፣ "ፑቲን በቅርቡ ለተፈጸመው ጥቃት ምላሽ እንደሚሰጥ በጥብቅ ነግሮኛል" ሲሉ ገልጸዋል።

ኪቭ እሁድ'ለት ከ100 በላይ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በመጠቀም የሩሲያ አየር ሀይል ላይ ጥቃት አድርሳለች።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሁለቱ ሀገራት በጥቃቱ ማግስት ባሳለፍነው ሰኞ በቱርክ ውይይት አድርገዋል። 
#thejapantimes

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

"እቅዱ አሜሪካ እያደረገች ያለውን የሰላም ጥረት ከግምት ያላስገባ ነው" - ድሮቲ ሺያ

"ያቀረባችሁት ወደ ሰላም የሚወስደንን ሳይሆን ለሽብርተኝነት እድል የሚሰጥ እቅድ ነው"  - እስራኤል

የጸጥታው ምክር ቤት በጋዛ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ያቀረበው እቅድ በአሜሪካ ውድቅ ተደረገ።

ምክርቤቱ ያቀረበው "ያለምንም ቅድመ ሁኔታ አስቸኳይ ዘላቂ የተኩስ አቁም" እቅድ ከአሜሪካ ውጭ 14ቱ ሀገራት የድጋፍ ድምጽ ሰጥተውበታል።

በተመድ የአሜሪካ ቋሚ መልዕክተኛ ድሮቲ ሺያ፣ "እቅዱ አሜሪካ እያደረገች ያለውን የሰላም ጥረት ከግምት ያላስገባ ነው" ሲሉ ተችተዋል።

የእንግሊዝ ቋሚ መልዕክተኛ ባርባራ ውድዋርድ በበኩላቸው የእስራኤል ጦር ወደ ጋዛ የሚያደርገውን ወታደራዊ መስፋፋት ተቃውመዋል።

የእስራኤል መልዕክተኛ ዳኒ ዳኖን "ያቀረባችሁት ወደ ሰላም የሚወስደንን ሳይሆን ለሽብርተኝነት እድል የሚሰጥ እቅድ ነው" ሲሉ ነቅፈዋል። 
#asiaone

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

የአሜሪካ ደህንነት ቢሮ (FBI)፣ "የግብርና ሽብርተኝነት" ፈጽመዋል ያላቸውን ሁለት ቻይናውያንን በቁጥጥር ስር አዋለ።

ቢሮው ቻይናውያኑ ዜጎች ወደ አሜሪካ በሽታ አስተላላፊ ፈንገስ በማስገባታቸው እንደተያዙ አስታውቋል።

የአሜሪካ ፍትህ ቢሮ በበኩሉ፣ ተህዋሱ በግብርና ምርቶች ላይ በሽታ የሚያመጣ እና ምርትን የሚጎዳ መሆኑን አጣርቶ እንደደረሰበት አስታውቋል።

ፍትህ ቢሮው በሽታ አምጭው ተህዋስ በቢሊዮን ዶላር የሚገመት ኢኮኖሚያዊ ውድመት ያስከትላል ብሏል።
#telegraphindia

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

#Update

ሊ ጃይ ምዩንግ አዲሱ የደቡብ ኮሪያ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ።

በትናንትናው እለት ምርጫ ባካሄደችው ሴዑል የሊበራል ፓርቲው ሊቀመንበር ምዩንግ ማሸነፍ ችለዋል።

አዲሱ ፕሬዝዳንት በወታደራዊ አስተዳደር (martial law) ምክንያት የመልካም አስተዳደር ስርዓት መሸርሸር ታይቶባታል ለተባለችው ደቡብ ኮሪያ ድሞክራሲን ያሰፍናሉ የሚል ተስፋ ተጥሎባቸዋል።
#asiaone

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

በቱርክ ተከሰተ በተባለ መሬት መንቀጥቀጥ ከ70 በላይ ሰዎች ተጎዱ።

በቱርክ በሬክተር ስኬል 5.8 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱ ተሰምቷል።

ድንገት በተከሰተው አደጋ ከ70 በላይ የሚደርሱ ሰዎች መጎዳታቸውንም የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።

አደጋው የተከሰተው በሀገሪቱ ደቡባዊ ምዕራብ በምትገኘው የማርማሪስ ክልል መሆኑ ተገልጿል። 
#dailyausaf

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

ደቡብ ኮሪያ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ እያካሄደች ትገኛለች።

ላለፉት ስድስት ወራት በፖለቲካ አለመረጋጋት ውስጥ የቆየችው ደቡብ ኮሪያ በዛሬው እለት ሀገራዊ ምርጫ በማካሄድ ላይ ናት።

የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዮን ሱክ ዮዔል በህዳር ወር ባወጁት የወታደራዊ አስተዳደር (martial law) ምክንያት ከስልጣናቸው መነሳታቸው ይታወቃል። 
#cnn

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

ሩሲያና ዩክሬን ከ300 የሚበልጡ የታገቱ ህፃናትን ለመልቀቅና በሌሎች ጉዳዮች ተስማሙ።

የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀካን ፊዳን ስብሰባው በመሪዎች ደረጃ ንግግር የሚጀመርበት ሁኔታ እንድፈጠር ያለመ ነው ብለዋል።

የሰብዓዊ እርዳታ እንድዳረስና የእስረኞች ልውውጥ እንድደረግ አሳስበዋል።

ቱርክ ግጭቱን ለመፍታት የትኛውንም አስፈላጊ ነገር ለማድረግ ዝግጁ ናት ያሉት ፊዳን፣ ዘላቂ የተኩስ አቁም ለማድረግ የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ይገባል ብለዋል።

የሁለቱ ሀገራት ልዑካን ከአንድ ሰዓት በላይ በዝግ ከተወያዩ በኋላ በምን ተስማሙ?

-ግዛታቸውን አልፎ የሚገኘውን ጦራቸውን ለማስወጣት፣
-የሚቀርቡ የውጭ ወታደራዊ ድጋፎችን ለማቆም፣
-የሦስተኛ ወገን ጦር እንዳይሳተፍ ለማድረግ ሁለቱም ሀገራት ተስማምተዋል።

እንጂሁም፦ በሩሲያ ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ለማንሳት (ከጦርነቱ መጀመር በኋላ በአውሮፓ ሀገራት የተጣለባት)፣

የተጎዱና የቆሰሉ ወታደሮችን ለመለዋወጥ: ይህን ለማድረግ እንዲያስችል በተወሰኑ ግንባሮች የ2/3 ቀን ተኩስ አቁም ለማወጅ፣

ከ300 የሚበልጡ የታገቱ ህፃናትን ለመልቀቅ (በቅርቡ ሩሲያ 101 ዩክሬን 20 ህፃናትን ለቀዋል) ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
#sputniknews

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

በኤትና ተራራ እሳተ ገሞራ ተከሰተ።

በሰሜን ጣልያን የሲሲሊ ግዛት በሚገኘው በዚህ ተራራ ዛሬ ድንገተኛ የእሳተ ገሞራ መፈንዳቱን የጣልያን ብሄራዊ ጃዖፊዚክስ ኢኒስቲትዩት(NIG) ገልጿል።

በእሳተ ገሞራው ውሃ እና ሰልፈር ዳይ ኦክሳይድ የተሸከሙ ከፍተኛ ብናኝ እና ጋዝ ወደ ሰማይ ሲወጣ ታይቷል ብሏል።

በስፍራው የነበሩ ቱሪስቶች ከአካባቢው በሩጫ ሲያመልጡ መመልከታቸውን የዓይን እማኞች ተናግረዋል።

የኤትና ተራራ በተደጋጋሚ ለእሳተ ገሞራ ተጋላጭ ከሆኑ የአውሮፓ ተራራዎች ውስጥ ቀዳሚው መሆኑን ኢኒስቲትዩቱ አስታውቋል።
#mailonline #theherald

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

ካሮል ናውሮኪ የፖላንድን ብሄራዊ ምርጫ አሸነፉ።

"የፖለቲካ ልምድ የላቸውም" የሚባሉት "ቀኝ ዘመሙ" የታሪክ ባለሙያ ናውሮኪ አዲሱ የፖላንድ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል።

የ42 አመቱ ናውሮኪ 50.89% ድምፅ በማግኘት ነው ምርጫውን ማሸነፍ የቻሉት።
#indiatoday

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

ዩክሬን 40 የሩሲያ ጦር ጄቶችን መትታ ጣለች።

ዩክሬን ጥቃቱን በሩሲያ ግዛት ገብታ እንደፈፀመችው አንድ የሀገሪቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር ተናግረዋል።

ኪቭ ይህን እርምጃ ለመውሰድ 18 ወራት እንደፈጀባት አመራሩ አብራርተዋል።

ዩክሬን ጥቃቱን እንደፈፀመች ያረጋገጠው የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር፣ በኢርኩትስክ ክልል ዘልቃ መግባቷን አስታውቋል።

ሩሲያ እና ዩክሬን በነገው እለት በቱርክ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል። 
#thewashingtontimes   #dailyausaf

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

#Update

የሟቾች ቁጥር 151 ደርሷል።

በናይጄሪያ የደረሰው የጎርፍ አደጋ አድማሱን እያሰፋ መምጣቱን የሀገሪቱ አስቸኳይ ጊዜ አስተዳደር (SEMA) አስታውቋል።

ጎርፉ 380 ኪሎሜትር መሸፋኑን የገለፀው አስተዳደሩ ሌሎች ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች የማፈላለግ ስራው ቀጥሏል ብሏል።

በዚህ ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ከ3000 የሚበልጡ ዜጎች መፈናቀላቸው ተገልጿል።

በተመሳሳይ መልኩ 500 የሚደርሱ መኖሪያ ቤቶች በጎርፍ ተወስደዋል ተብሏል።
#associatedpress #pbsnews #telegraphindia

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

ዩክሬን በ11 የገጠር ቀበሌዎች የሚገኙ ዜጎቿን ለቀው እንዲወጡ አሳሰበች።

ዜጎቹ እንዲለቁ ማሳሰቢያ የተሰጠባቸው ሁሉም ቀበሌዎች ዩክሬን ከሩሲያ ጋር በምትዋሰንበት ድንበር አካባቢ የሚገኙ ናቸው ተብሏል።

ውሳኔው ሩሲያ በነዋሪዎቹ ላይ የምታደርሰው የቦምብ ጥቃት ባለመቋረጡ የተላለፈ መሆኑ ተገልጿል።
#france24

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

"ፑቲን ከእሳት ጋር እየተጫወተ ነው" - ፕሬዝዳንት ትራምፕ

ዶናልድ ትራምፕ ፕሬዝዳንት ፑቲንን "ከመጥፎ ነገር እየጠበኩት ነው" አሉ። ፑቲን ከእሳት ጋር እየተጫወተ ነው"ም ብለዋል።

ፕሬዚዳንቱ አክለውም "ፑቲን ያላወቀው ነገር ቢኖር፣ እኔ ባልኖር በሩሲያ ላይ በጣም ብዙ መጥፎ ነገሮች ይፈጠሩ ነበር" ብለዋል።

ይሁን እንጂ "መጥፎ" ያሏቸውን ነገሮች ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

ትራምፕ የሩሲያ መንግስት በዩክሬን የሚፈጸመው ጥቃቶችን ማስቆም አለመቻሉንም ተችተዋል። 
#rawstory

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

"በአየርላንድ ያለፍቃድ ለሚኖሩ ሁሉ ግልጽ መልዕክት ነው" - ጂም ኦካላጋን

አየርላንድ 25 የናይጄሪያውያ ዜጎችን ወደሀገራቸው መለሰች።

የአየርላንድ የፍትህ ሚኒስትር ጂም ኦካላጋን "አየርላንድ የምታስተናግደው ህግን መሰረት ያደረገ ፍልሰት ብቻ ነው" ብለዋል።

አየርላንድ 2025 ከገባ በኋላ "ህጋዊ አይደሉም" ያለቻቸውን 106 ናይጄሪያውያንን ወደሀገራቸው መልሳለች።

ወደ ሀገራቸው ከተመለሱት ውስጥ 5 ህፃናት፣ 21 ወንዶችና 9 ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል። 
#breakingnewsie

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

ዶናልድ ትራምፕ የሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ቪዛ እገዳ መመሪያን በፊርማቸው አጸደቁ።

መመሪያው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሁንም በሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎችን ቪዛ እንዲያግድ ስልጣን የሚሰጥ ነው ተብሏል።

የትራምፕ አስተዳደር በቅርቡ ለሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ ሲሰጥ የነበረውን 450 ሚሊዮን ዶላር በጀት አቋርጧል።

እርምጃውን ያወገዘው ዩኒቨርስቲውም የትራምፕን አስተዳደር በፍርድ ቤት እንደሚከስ አስታውቋል።

አሜሪካ በሁሉም ሀገራት የሚገኙ የአሜሪካ ኤምባሲዎች ለተማሪዎች የቪዛ ቀጠሮ እንዳይሰጡ ከአንድ ሳምንት በፊት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ አሳስቦ ነበር። 
#telegraphindia

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

የትራምፕ አስተዳደር በ12 ሀገራት ላይ ሙሉ በሙሉ በ7 ሀገራት ላይ ደግሞ ከፊል እገዳ ጣለ።

ትራምፕ "የውጭ ሽብርተኞችን" ለመከላከል የውጭ ሀገራት ዜጎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ በሚል የወጣው አዋጅ ላይ ፈርመዋል።

በዚሁ መሠረት ኤርትራ፣ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ሊቢያ፣ የመን፣ ቻድ፣ ኮንጎ፣ ኢኳቶሪያል ጊኒ፣ ኢራን፣ አፍጋኒስታን፣ ማይናማር እና ሄይቲ ሙሉ ለሙሉ እገዳ የተጣለባቸው ናቸው። 

ከፊል እገዳ የተጣለባቸው ደግሞ ቡርንዲ፣ ሴራሊዮን፣ ቶጎ፣ ኩባ፣ ሌኦስ፣ ቱርኪሚስታን  እና ቬንዙዌላ ናቸው።
#timeslive

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

"የኑክሌር ምርት የብሄራዊ ክብር ጉዳይ ነው" -  ኢራን

የኢራን መሪ አያቶላህ ኮሚኒ በኑክሌር ጉዳይ አሜሪካ ያቀረበችውን እቅድ ውድቅ አደረጉ።

ለአምስት ዙር በቀጠለው የሁለቱ ሀገራት ውይይት ዋሽንግተን ኢራን የዩራኒየም ምርቷን እንድታቆም ጠይቃለች።

ይህን ተከትሎ ኮሚኒ በሰጡት አስተያየት ከአሜሪካ በኩል የቀረበው እቅድ "100% ተቃራኒ ነው" ብለዋል።

በኦማን አሸማጋይነት የተደረጉት ውይይቶች ያለስምምነት መጠናቀቃቸው ተገልጿል።
#foxnews

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

በፓኪስታን ከ100 በላይ እስረኞች አመለጡ።

በፓኪስታን የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ መከሰቱን ተከትሎ ከአደጋው ለማምለጥ የሞከሩ ሰዎች እስርቤቱን ሰብረው መውጣታቸው ተገልጿል።

በካራቺ ከተማ በተከሰተው አደጋ በድምሩ 216 እስረኞች አምልጠው የነበረ ሲሆን 78 ቱን መመለስ መቻሉን ባለስልጣናት አስታውቀዋል።

እስረኞች ለማምለጥ ሲሞክሩ በነበረ የተኩስ ልውውጥ አንድ ታራሚ ሲሞት ሶስት ሶስት ፖሊሶች ቆስለዋል ተብሏል።
#thenation

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

"አስቀያሚ ነው" - ኤለን መስክ

"አስተያየቱ የፕሬዝዳንት ትራምፕን ውሳኔ አይቀይረውም" - ዋይትሐውስ

ቢሊየነሩ መስክና ፕሬዝዳንት ትራምፕ የመጀመሪያ ትችት አዘል ሀሳብ ተለዋወጡ።

በቅርቡ ከመንግስታዊ ሀላፊነት የተነሱት መስክ ትራምፕ በተለያዩ ሀገራት ላይ የሚያሳልፉትን የታሪፍ ውሳኔ "አስቀያሚ" ሲሉ ወቅሰዋል።

ቢሊየነሩ የቴስላ ባለቤት ታሪፉ "የአሜሪካን ኢኮኖሚ ይበልጥ ያዳክመዋል" ብለዋል።

ከመስክ ለቀረበው ወቀሳ ምላሽ የሰጡት የዋይትሐውስ ቃል አቀባይ ካሮሊን ሌቪት "ፕሬዝዳንት ትራምፕ መስክ ምን ለማለት እንደፈለገ ይገባቸዋል" ብለዋል።

"አስተያየቱ የፕሬዝዳንት ትራምፕን ውሳኔ አይቀይረውም" ሲሉም አክለዋል።  
#outlookus

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 21 ንጹሐን በግፍ ተገደሉ።

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሂውማን ራይትስ ዋች (HRW) በጎማ ከተማ የ11 ሰዎች አስክሬን መገኘቱን አስታውቋል።

ድርጅቱ ግድያውን የፈጸመው በሩዋንዳ የሚደገፈው አማፂው የኤም 23 ቡድን ነው ብሏል።
#africannews

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

"በሰብዓዊ መብት ጥሰት" ምክንያት የጠ/ሚ አቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንግሊዝ ጉብኝት ውድቅ ተደረገ።

ጠቅላይ ሚኒስቴር ኬር ስታርመር የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይን የጉብኝት ጥያቄ ውድቅ አድርገዋል ተብሏል።

"በሰብዓዊ መብት ጥሰት" ምክንያት ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) በእንግሊዝ ሊያደርጉት ያሰቡትን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ውድቅ መደረጉ ነው የተገለጸው።

የሜትሮፖሊታን ፖሊስ የአባይን የጉዞ ደህንነት ሽፋን አልሰጥም ማለቱም ተሰምቷል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ስታርመር ውሳኔ እንግሊዝ በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ መብት አያያዝ እንዳሳሰባት ማሳያ ነው ተብሏል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ በቅርቡ በአውሮፓ ሀገራት ባደረጉት ጉዞ በፈረንሳይ፣ ሮም እና ጣልያን ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገዋል።
#thehabesha

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

ሩሲያ እና ዩክሬን ተጨማሪ እስረኞችን ለመልቀቅ ተስማምተዋል።

የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች ዛሬ በቱርክ ሁለተኛውን ዙር ውይይት አካሂደዋል።
#SputnikAfrica

(ዝርዝሩን ይዘን እንመለሳለን)


@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

#Update

በናይጄሪያው ጎርፍ የሟቾች ቁጥር ከ200 እንዳሻበቀ፣ 500 ሰዎች ያሉበት እንደማይታወቅ፣ የሟቾች ብዛት 700 እንደሚደርስ ተነገረ።

በናይጄሪያዋ ሞካዋ ከተማ በጎርፍ ምክንያት የሟቾች ቁጥር ከ200 በላይ እንደሆነ፣ ቁጥሩ እስከ 700 እንደሚደርስ ቢቢሲ ዘግቧል።

ዘገባው፣ “እስካሁን 500 ሰዎች የደረሱበት አለመታወቁን ተከትሎ የአካባቢው ባለሥልጣን ለቢቢሲ እንደተናገሩት፣ በሕይወት የሚገኝ ሰው ከዚህ በኋላ አይኖርም በሚል እምነት የነፍስ አድን ጥረቱ ተቋርጧል” ብሏል።

በአካባቢው ተላላፊ በሽታ እንዳይዛመት በጎርፉ የተቀበሩ ግለሰቦችን ቆፍሮ በማውጣት ተገቢው የቀብር ሥነ ሥርዓት ማከናወን በቅርቡ እንደሚጀመር የሞካዋ አካባቢ አስተዳዳሪ ሙሐመዱ አሊዩ ተናግረዋል።

ባለቤቱ እና ጨቅላ ልጁ በጎርፍ የተወሰዱበት አዳሙ ዩሱፍ የተባለው ግለሰብ "ቤተሰቤን ጎርፍ ሲወስድ ምንም ማድረግ ሳልችል ቆሜ ተመልክቻለሁ። እኔም መዋኘት በመቻሌ ነው የተረፍኩት" ሲል ገልጿል።

እ.አ.አ በ2022 በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከ600 በላይ ሰዎች ሲሞቱ፣ 1.3 ሚሊዮን የሚሆኑ ህዝቦች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
#BBC

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

"ከ30 በላይ እርዳታ ፈላጊዎች በእስራኤል ተገድለዋል" - የጋዛ ጤና ሚኒስቴር

"የደረሰ ጉዳት የለም፣የእርዳታ ስርጭቱ በሰላም ተጠናቋል" - የጋዛ ሰብዓዊ ፋውንዴሽን

የእስራኤል ጦር በራፋህ የእርዳታ ጣቢያ ምግብ በመጠባበቅ ላይ በነበሩ ንፁሃን ላይ ጥቃት ማድረሱን የጋዛ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

በዚህ ጥቃት ከ30 በላይ ሰዎች ሲሞቱ፣ 170 የሚደርሱት መጎዳታቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

የጋዛ ሰብዓዊ ፋውንዴሽን (GHF) በበኩሉ ደረሰ የተባለውን ጉዳት "በእርዳታ ወቅት ሰዎች በስነስርዓቱ ተከፋፍለው ሂደዋል" በማለት በተንቀሳቃሽ ምስል የታገዘ ማስተባበያ ሰጥቷል።

የእስራኤል ጦርም በተመሳሳይ "በንፁሃን ላይ የተቃጣ እርምጃ የለም" ሲል የቀረበበትን ውንጀላ ውድቅ አድርጓል።

አንድ የአይን እማኝ ግን "የእስራኤል ወታደሮች በሺዎች የሚቆጠሩ እርዳታ ጠባቂዎች ላይ ተኩስ ከፍቶ ነበር" በማለት ጥቃቱ መፈጸሙን አረጋግጠዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ እስራኤል ሆስፒታል ላይ በፈፀመችው ጥቃት 54 ሰዎች መገደላቸውንና የኩላሊት መታጠቢያ ማሽንን ሙሉ በሙሉ ማውደሟን ተመድ አስታውቋል።
#cnn #aljazeera

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

በጃፓን በሬክተር ስኬል 6.1 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ።

አደጋው የተከሰተው በሰሜን ጃፓን ሆካይዶ ግዛት በምትገኘው ኩሺሮ ከተማ መሆኑን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ (USGS) አስታውቋል።

እስካሁን በመሬት መንቀጥቀጥ አደጋው የተመዘገበ ጉዳት የለም ተብሏል።

የጃፓን ባለስልጣናት የመሬት መንቀጥቀጡን በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያም ሆነ ማስጠንቀቂያ አልተሰጠም።
#yenisafaq

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

#ቪዲዮ፦ ግብፅ በበረዶ አዘል ከባድ ዝናብና ከባድ አውሎ ነፋስ ተመታች።

እስክንድርያ ከተማ በበረዶ ስትጥለቀለቅ፣ በአውሎ ነፋስ ስትታመስ ተስተውላለች።

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

የእስራኤል ወታደሮች በዌስት ባንክ የውጭ ምንዛሬ ቢሮዎች ላይ "ወረራ" ሲፈጽሙ በንጹሐን ላይ ሞትና መቁሰል አጋጠመ።

በወረራ በያዙት ዌስት ባንክ አስለቃሽ ጭስ በመጠቀም በወሰዱት የኃይል እርምጃ አንድ ፍልስጤማዊ ህይወቱ ሲያልፍ 30 የሚደርሱት ቆስለዋል።

የራማላህ፣ ናቡልስ፣ ቤተልሔም እና ጄኒን ከተሞች ውድመት ደርሶባቸዋል ተብሏል።
#aljazeera

@ThiqahEth

Читать полностью…

THIQAH

21 የግሪክ የባሕር ጠባቂዎች የስደተኞች መርከብ ላይ አደጋ በማድረስ ወንጀል ተከሰሱ።

ከተከሳሾቹ መካከል አራቱ ባለስልጣናት መሆናቸው ተገልጿል።

ተጠርጣሪዎቹ የተከሰሱት በ2023 የ650 ሰዎችን ህይወት በቀጠፈው የጀልባ አደጋ እጃቸው አለበት በሚል ነው ተብሏል።

በተጨማሪም 750 ስደተኞችን ከሊቢያ ወደ ጣልያን ለማስገባት ጉቦ ተቀብለዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል። 
#upi

@ThiqahEth

Читать полностью…
Subscribe to a channel