1532594
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ
#AddisAbaba
" በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " - ገቢዎች ቢሮ
ከሐምሌ 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30/2018 ዓ/ም ድረስ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ነው።
በዛሬው ዕለት የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋይ ደንበኞች ግብራቸውን ማሳወቅ የጀመሩ ሲሆን እስከ ሐምሌ 30/2017 ዓም ድረስ ግብር ግብራቸውን እያሳወቁ ይቆያሉ።
ከዚህ ቀደም ከነበረው አሰራር ለየት ባለ መልኩ በየደረጃው ያሉ ግብር ከፋዮች በወጣላቸው መርሃ ግብር መሰረት ግብራቸውን እንዲከፍሉ እንደሚደረግ የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አቶ ሰውነት " ከዚህ ቀደም የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮች ከሃምሌ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ነበር የሚከፍሉት ዘንድሮ ይህ አሰራር ተቀይሮ ሃምሌን ለዝግጅት እንዲጠቀሙት እና ግብራቸውን ከ ነሐሴ 1 እስከ ጳጉሜ 5 ድረስ እንዲከፍሉ ተወስኗል አከፋፈላቸውም በስም ቅደም ተከተል ይሆናል " ብለዋል።
ዳይሬክተሩ በስም ቅደም ተከተል እንዲከፍሉ መደረጉ ግብር ከፋዩ ላይ መጨናነቆች እንዳይኖሩ እና ለብልሹ አሰራሮች እንዳይዳረጉ ያግዛል ነው ያሉት።
አቶ ሰውነት አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር በሰጡት ሃሳብ ምን አሉ ?
" የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋይ ደንበኞች በነሐሴ ወር የመጀመሪያው ሳምንት ላይ የስም ዝርዝራቸው ከ A-D ያሉ ግብር ከፋዮች የሚስተናገዱበት ፕሮግራም ወጥቷል፣ በዚህም መሰረት ግብር ከፋዩን በአራት ሳምንት በመከፋፈል አመታዊ ግብራቸውን እንዲያሳውቁ እና እንዲከፍሉ ይደረጋል።
የደረጃ 'ሀ' ግብር ከፋዮችን በሚመለከትም ከዚህ ቀደም ከሐምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30 የአመታዊ ግብራቸውን የመክፈያ እና የማሳወቂያ ጊዜያቸው ነበር።
እነዚህ ግብር ከፋዮችም ሐምሌ እና ነሃሴን ለዝግጅት ተጠቅመው መስከረም እና ጥቅምትን ግብራቸውን የሚከፍሉበት ፕሮግራም ወጥቷል።
ቢሮው በተለያዩ ጊዜያት ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ባደረጋቸው ውይይቶች ወቅት የተነሱ የተለያዩ ችግሮች ነበሩ እነዚህን የተጠቀሱ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ በጥናት የተለዩ 24 አይነት አዳዲስ አሰራሮችን ዘርግተናል ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል።
ለምሳሌ የኦዲት ጥራት ጋር ላይ ከአሰራር ጋር በተያያዘ ባሉ ክፍተቶች ምክንያት ሁለት ኦዲተሮች አንድ አይነት ፋይል ተመልክተው ውሳኔ ሲወስኑ ግን ሁለት አይነት ውሳኔ የሚወስኑበት አሰራር ነበር ይህንን ለማስቀረት የሚያስችል የአሰራር ስርአት ተዘርግቷል።
ከሂሳብ መዝገብ ጋር በተገናኘም የሂሳም መዝገብ መያዝ ያለባቸው ግብር ከፋዮች መዝገቡን ባለመያዛቸው በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ ነበር።
አፈጻጸም ላይ በነበረ ክፍተት ምክንያት በተለይም የደረጃ 'ሀ' እና 'ለ' ግብር ከፋዮች ያለ ሂሳብ መዝገብ ሲስተናገዱ የቆዩ ቢሆንም ከአሁኑ የ2017 ዓ/ም የግብር ማሳወቂያ ወቅት ጀምሮ ያለ ሂሳብ መዝገብ አይሰራም።
ሂሳብ መዝገብ ሳይዙ የሚመጡ ከሆነ ግን የሚወሰነው ውሳኔ አስተማሪ የሚሆን ይሆናል።
የግብር አሰባሰብ ስርአቱም ከእጅ ንክኪ በጸዳ መንገድ እንዲሆን በማሰብ የደረጃ 'ሐ' ግብር ከፋዮች በET-TAX በተሰኘ በተቋሙ በለማ መተግበሪያ እቤታቸው ተቀምጠው ግብራቸውን የሚያውቁበት እና የሚከፍሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
በSMS በሚደርሳቸው መረጃም በTelebirr እና CBE Birr ግብራቸውን መክፈል ይችላሉ።
የደረጃ 'ሀ' እና የደረጃ 'ለ' ግብር ከፋዮችም በተመሳሳይ E-TAX በተሰኘ መተግበሪያ እንዲከፍሉ እያደረግን ያለንበት ሁኔታ አለ ነገር ግን ሁሉም ወደዚህ አሰራር ስርአት ገና አልገቡም።
ከፍተኛ ግብር ከፋዮች 100 ፕርሰንት ወደዚህ አሰራር ስርአት ገብተዋል ቀሪዎቹ በየቅርንጫፉ እቅድ ተይዞ አብዛኛው ግብር ከፋይ ወደዚህ አሰራር እንዲገባ እየተሰራ ነው።
የኦዲት ጥራትን የሚያረጋግጥ የስራ ክፍል ተደራጅቷል ኦዲተሩ የወሰነው ውሳኔ ምን ያህል ጥራት አለው የሚለውን ያረጋግጣል ከፍተኛ ልዩነት ከተፈጠረም ግብር ከፋዩ እንዲከፈል ይደረጋል፣ ይህንን የወሰነው አካልም ተጠያቂ ይሆናል።
የግብር ከፋዩን ሂሳብ መዝግብ የሚያዘጋጁ ባለሞያዎች በሚመለከት ከዚህ ቀደም ከግብር ከፋዩ ጋር በመደራደር ከፍተኛ የሆነ ግብር የመሰወር ስራ የሚሰሩበት እና የተሳሳቱ ሰነዶችን የሚያቀርቡበት ሁኔታ ነበር።
በዚህ ጊዜ ግብር ከፋዩን ኦዲት አድርገን ገንዘቡን ብናስከፍልም የሂሳብ ባለሞያዎቹ ተጠያቂ የምናደርግበት አሰራር አልነበረም አሁን የሂሳብ ባለሞያዎቹም ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሰራር ዘርግተናል።
ኦንላይን ግብይትንም ለመቆጣጠር እና ግብር እንዲከፍሉ ለማድረግ የሚቻልበት የአሰራር ስረዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው።
ከማዕከል ሁሉንም ቅርንጫፎች ለመቆጣጠር የሚያስችል ካሜራ አስገጥመናል።
በዘንድሮ የግብር ማሳወቂያ እና መክፈያ ወቅት በገቢዎች ቢሮ 256 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba
@tikvahethiopia
#Ethiopia🇪🇹
አስገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያው መነሳቱ ለባንኮች ምን ትርጉም አለው ?
ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ባካሔደው ሶስተኛ ስብሰባ፣ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ከውሳኔዎቹ አንዱም የንግድ ባንኮች ሲገዙት ከነበረው የግምጃ ቤት ቦንድ ጋር የሚያያዝ ነው፡፡
ኮሚቴው፣ የንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ እንዲነሳ መወሰኑን አስታውቋል፡፡
ይህም የሆነው በአሁኑ ወቅት የመንግስት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉና መንግስት የበጀት ጉድለቱን ለማሟላት የውጭና ገበያ መር ከሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ ነው ብሏል፡፡
የንግድ ባንኮች ቦንድ እንዲገዙ ሲደርግ የነበረው አስገዳጅ መመሪያ በመነሳቱ፣ ለባንኮቹ ምን ፋይዳ አለው ? በማለት ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው አንድ ከፍተኛ የባንክ ባለሙያ፣ " አሰራሩ በባንኮች ዘንድ የገንዘብ እጥረት እንዲፈጠር አስተዋፅኦ ስለነበረው፣ ይህ ውሳኔ በጣም ጠቃሚ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡
የባንክ ባለሙያው በዝርዝር ምን አሉ ?
" ቦንዱ እንኳን ተነሳ፡፡ በቦንዱ ምክንያት ለአምስት አመት ታስሮ የሚቀመጥ ገንዘብ ነበር፡፡ ባንኮቹ ቦንድ የገዙበት ገንዘብ ከአምስት አመት በኋላ ነው የሚመለስላቸው፡፡
ይህ አስገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያ፣ በባንኮች የገንዘብ እጥረት/የሊኩዲቲ ችግር እንዲመጣ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ ለሊኩዲቲ ችግር መከሰት አንዱ መንስኤ የነበረው እሱ ነው፡፡
የሆነ ብድር በሰጠህ ቁጥር የተወሰነ ፐርሰንት ቦንድ እድትገዛ ትገደድ ነበር፡፡ ብድር በሰጠህ ቁጥር የብድሩን 20 በመቶ ቦንድ ግዛ ትባላለህ፡፡ እስከ 20 በመቶ እንድተገዛ ትገደድ ነበር፡፡ ለአንድ ሰው አምስት ጊዜ ካበደርክ ያስቀመጥከውን ገንዘብ በሙሉ ወሰደው ማለት ነው የቦንድ ግዢው፡፡ በዚህ መልኩ ባንኮች ብድር በሰጡ ቁጥር ተደራራቢ የቦንድ ግዢ ስለሚፈፅሙ እና ገንዘቡም የሚመለሰው ከአምስት አመት በኋላ ስለነበረ ለገንዘብ እጥረት አጋልጧቸዋል።
አሁን ይኼ በመቆሙ ትልቅ እፎይታ ነው የሚሰጣቸው፡፡ ለችግራቸው መፍትሔ ይሆናል፡፡ ለገንዘብ እጥረቱ ማስተንፈሻ ነው፡፡ ብሔራዊ ባንክ የወሰደው እርምጃ በእጅጉ አጋዥ ነው፣ የሚያስመሰግነው ነው፡፡
በቦንድ ግዢ ከባንኮች ሲሔድ የነበረው የገንዘብ መጠን፣ ባንኮቹ በሚሰጡት የብድር መጠን ላይ የሚመሰረት ነበር፡፡ አሁን ይሔ አሰገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያ በመቅረቱ፣ የባንኮቹን የገንዘብ እጥረት በምን ያህል መጠን ሊያቃልለው እንደሚችል ማወቅ ይከብዳል፣ ግን በእጅጉ ያቃልላል፡፡
ይሔ ጥሩ እርምጃ ሆኖ፣ የንግድ ባንኮች የሚሰጡት ዓመታዊ የብድር ዕድገት ጣሪያ ደግሞ አልተነሳም፡፡ ከ18 በመቶ እንዳይበልጥ የተቀመጠው የብድር ጣሪያ እስከ መስከረም ወር እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡
ብሔራዊ ባንክ በዚሁ እርምጃው ይህንንም 18 በመቶ የሚለውን የብድር ጣሪያ ቶሎ ቢያነሳው ጥሩ ነበር፡፡
የብድር ጣሪያው በባንኮች አሰራር ላይ ችግር እየፈጠረ ነው ያለው፡፡ ለምን ብትል ተበዳሪዎች ብድራቸውን ከመለሱ በኋላ በባንኮች ላይ በተጣለው የብድር ጣሪያ ምክንያት መልሰው እንደማይበደሩ ስለሚያውቁ የመጀመሪያውንም ብድራቸውን አይከፍሉም፡፡ ለባንክ የሚከፍሉትን እዳ ለሌላ አገልግሎት ያውሉታል፡፡
ይልቁንም ለባንክ መክፈል የነበረባቸውን ገንዘብ ለሌላ ንግድ እያገላበጡ ይጠቀሙበታል፡፡ ለዚህ ነው እዳ ውስጥ የሚገቡት፡፡ ባንኮቹ በተቀመጠው የ 18 በመቶ የብድር ጣሪያ ምክንያት ተጨማሪ ብድር መስጠት አይችሉም ብቻ ሳይሆን ቀድመው ያበደሩትን ገንዘብ ማስመለስ አልቻሉም፡፡
ብሔራዊ ባንክ ይህንን የብድር ጣሪያ የሚያነሳበትን ጊዜ በጉጉት ነው የምንጠብቀው፡፡ እርምጃው ለኢንቨስትመንትና ለስራ ፈጠራም አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡ የግሉ ዘርፍ ከባንኮች እየተበደረ ኢንቨስት ካላደረገ ኢኮኖሚው አይንቀሳቀስም፣ የስራ እድል ሊፈጠር አይችልም፣ ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖው ብዙ ነው፡፡ " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#NationalExam🇪🇹
#SocialScience
የ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል የማኀበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የመጀመሪያ ዙር ፈተና ዛሬ ከጥዋት ጀምሮ መሰጠት ተጀምሯል።
በወረቀት እና በኦንላይን የሚሰጠው የማኀበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም ይቆያል።
@tikvahethiopia
#AcademicCalendar
በመዲናዋ ለ2018 የትምህርት ዘመን የነባር እና አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ እንዲሁም የመፀሀፍ ስርጭት የሚካሄደው ከሐምሌ 1 እስከ ነሃሴ 23/2017 ዓ/ም መሆኑ ታውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ/ም የትምህርት ቀናትን ዛሬ ይፋ አድርጓል ለ11ዱም ክ/ከተማ የትምህርት ፅ/ቤቶች ልኳል።
በዚሁ ካላንደር መሰረት ምዝገባ ከሃምሌ 1 እስከ ነሔሴ 23 /2017 ዓ/ም ይካሄዳል።
መምህራን በትምህርት ቤታቸው ተገኝተው ሪፖርት የሚያደርጉበት እንዲሁም አጠቃላይ የመምህራን ጉባኤ የሚደረገው ነሃሴ 28 እና ነሃሴ 29/2017 ዓ/ም እንደሆነ ተመላክቷል።
ከነሃሴ 24 እስከ ጳጉሜ 5/2017 ዓ/ም ደግሞ የ7ኛና የ9ኛ ክፍል ከአዲስ አበባ ውጭ ለሚመጡ አዲስ ተመዝጋቢዎች ተማሪዎች ምዝገባ ይከናወናል።
መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ/ም የመጀመሪያው ቀን የመጀመሪያ መደበኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜ (day one class one) እንደሆነ ይፋ ተደርጓል።
በ2018 ዓ/ም የሚሰጠው የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እንደሚሰጥ በትምህርት ካላንደሩ ላይ ታሳቢ ተደርጓል።
(ሙሉውን ከላይ ይመለከቱ)
@tikvahethiopia
" ቡድኑ ትግራይን ለማተራመስና ኢትዮጵያን ለመውጋት ከኤርትራ መንግስት ጋር እየሰራ ነው " - ስምረት ፓርቲ
የኢፌዴሪ መንግስት ከኢትዮጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ የተሰረዘው ' #ህወሓት ' ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ እንጂ ማስታመም አይገባውም አለ ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ፓርቲ።
በቀድሞ የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበርና የትግል ጓደኞቻቸው በቅርቡ ከብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የቅድመ እውቅና ምዝገባ የተሰጠው ስምረት " ለህግ የማይገዛ ወመኔ " ሲል የገለፀው ህወሓት ትግራይን ለማተራመስና ኢትዮጵያ ለመውጋት ከኤርትራ መንግስት እየሰራ ነው " ሲል ከሶታል።
" ኋላ ቀር ቡድን " በማለት በገለፀው ህወሓት ምክንያት የትግራይ ህዝብ መልሶ ወደ ጦርነት እንዳይገባ የፌደራል መንግስት ሃላፊነቱ እንዲወጣ አሳስቧል።
" ከአሁን በኋላ በትግራይ ላይ የሚፈፀሙ ጥፋቶች ብቸኛው ተጠያቂ ከዓለም አቀፍና አገራዊ ህጎች የተቃረነው ወመኔው ኋላ ቀር ቡድን እና መሰሎቹ መሆናቸው የኢትዮጵያ መንግስት መገንዘብ አለበት " ሲልም ስምረት ፓርቲ ገልጿል።
" የሃይማኖት አባቶች ፣ የአገር ሽማግሌዎች ፣ ወጣቶች በአገር ውስጥና በመላ ዓለም የሚገኙ ትግራዎት ቡድኑ በስልጣን የሚቆይባቸው እያንዳንዱ ቀናት በህዝብ ላይ አስከፊ መከራና ስቃይ የሚያስከትሉ መሆናቸው በመረዳት ትግላችሁ አጠናክሩ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።
ፓርቲው ለታጠቀው ሰራዊት ባስተላለፈው ጥሪ " ሌት ተቀን የጦርነት ነጋሪት ከሚጎስመው ኋላ ቀር ቡድን ራሳችሁን በማራቅ ከሰላም ፈላጊ ህዝብ ጎን ተሰለፉ " ብሏል።
" ከአሁን በኋላ በትግራይ ህዝብ ላይ የሚፈፀም ወንጅልም ይሁን የሚቀሰቀስ ጦርነት በዝምታ ማየት በህዝብ ላይ የሚያስከትለው ከባድ አደጋ መዘንጋት ነው " ያለው ስምረት ፓርቲ " አደጋውን አስቀድሞ ለማስቀረት ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ሚናቸው ከወዲሁ እንዲወጡ " በማለት ለአገር አቀፍና ዓለምአቀፍ ተቋማት ጥሪውን አቅርቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia
አሁንም በSMS ጨዋታ ፈታ💬🎊 እያልን በየቀኑ እንሸለም! 🎁
ከሳፋሪኮም ቁጥራችን 'START’ ብለን ወደ 34000 በመላክ ወይም ወደ *799# በመደወል እንወዳደር! እናሸንፍ! በአንድ መልስ 1ብር ብቻ!
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
#Ethiopia🇪🇹
የሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ገበያ በሚቀጥለው ሳምንት ይፋዊ ግብይት ሊጀምር እንደሆነ ካፒታል ጋዜጣ አስነብቧል።
ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ( ስቶክ ገበያ) በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተሰምቷል።
ይህ እርምጃ ለአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ተነግሯል።
ገበያዉ በኖቬምበር 2023 በተደረገ የካፒታል ማሰባሰቢያ ዘመቻ 1.5 ቢሊዮን ብር በማሰባሰብ ከታሰበው ግብ በ631% በልጧል። ይህ ገንዘብ ከ48 የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ተቋማት የተገኘ ነው።
በሕዝብና በግል ሽርክና የሚሰራው አዲሱ የበይነመረብ ንግድ ልዉዉጥ መድረክን መንግሥት 25%፣ የግል ዘርፍ ደግሞ 75% ድርሻ አላቸዉ።
አሁን ላይ ገዳ ባንክ አ.ማ. እና ወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ. በገበያው ላይ ከተመዘገቡት ኩባንያዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የሰነደ መዋዕለ ንዋይ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ እስከ 50 ኩባንያዎችን፣ በአሥር ዓመታት ውስጥ ደግሞ ከ90 በላይ ንግዶችን ለማካተት አቅዷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
" የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ድምጽ አልባ በመሆናቸው ራሳቸውን በድምጽ ከአደጋ የሚከላከሉ በተለይም ዓይነ ስውርና መስማት የተሳናቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ትልቅ አደጋ ላይ ናቸው " - ማኅበሩ
የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ብሔራዊ ማኅበር ከአዲስ አበባ ብስራት ፕሮሞሽን ጋር በማበር፣ የመንገድ ላይ ደኅንነትን፣ የትራንስራንስፓርት ተሽከርካሪዎች እና የአገልገሎት መስጫ ተቋማት ተደራሽነት ችግር አካቶ የያዘ "ከቤት እስከ ጎዳና" በሚል ያዘጋጀውን ዶክመንትሪ ፊልም ለመንግስት አካላት በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል አቅርቧል።
በዚህም የትራንስፖርትና ሎጂስቲ ሚኒስቴር፣ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንትና ሌሎች ተቋማት ታድመው የነበረ ሲሆን፣ ማኀበሩም በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን በጥናታዊ ፅሑፍ ጭምር እነዚሁ አካላት ባሉበት አቅርቧል። ባለድርሻ አካላቱም የተለያዩ አስተያየቶችን በመስጠት የተነሱትን ክፍተቶች ለመቅረፍ ቃል ገብተዋል።
በመርሃ ግብሩ የተነሳው አንዱ ዋነኛ ጉዳይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በተለይ ለዓይነ ስውራን አደጋ የደቀኑ በመሆናቸው ሕግና ፓሊሲ በማውጣት መንግስት ትኩረት እንዲሰጥ የሚያሳስብ የነበረ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ወደ ኢትዮጵያ መግባት በዓይነ ስውራን የሚያስከትለው ጉዳት ምንድነው? ምንስ መደረግ አለበት? ያለው ክፍተትስ ምንድን ነው? ሲል ማህበሩን ጠይቋል፡፡
የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አበራ ረታ ምን መለሱ ?
" መንግስት በጣም የሚደነግበት ቦታ ቢኖር እዚህ ኤሪያ ላይ ነው፡፡ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር ይሄንን ጉዳይ ስናወራቸው ምንም ያላሰቡበት ነገር እንደሆነ ነው የነገሩን።
የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ድምጽ አላባ/ድመጽ አልባ አድርጎ መንዳት የሚችሉ ናቸው፡፡ ይሄ ሲሆን ግን እይታ የሌላቸው ነገር ግን ራሳቸውን በድምጽ ከአደጋ የሚከላከሉ በተለይም ዓይነ ስውርና መስማት የተሳናቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ትልቅ አደጋ ላይ ናቸው።
መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ለመቀየር እቅድ ይዟል። ይሄንን እቅድ ሲይዝ ግን ቀጥታ የጉዳቱ ሰለባ የሆኑትን ዓይነ ስውራንን ያገናዘበው ፖሊሲም፣ ሕግም ስታንዳርድም የለም፡፡ ይሄ ጉዳይ በአሜሪካ ምክር ቤት ክርክር ተደርጎበት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሙሉ ለሙሉ ድምጽ ሊኖራቸው እንደሚገባ አስገዳጅ ሕግ ወጥቶለታል።
በኢትዮጵያ ግን ለነዳጅ የምናወጣውን የውጭ ምንዛሬ ስለሚያስቀርልን፣ ኢንቫይሮመንታሊ ፍሬንድ ስለሆኑ በሚል እሳቤ ተሸከርካሪዎቹን ወደ ሀገር ውስጥ እያስገባናቸው ነው።
መግባቱን ይግቡ ግን ቴክኖሎጅው ሁሉም ነገር የተገጠመለት ነው፤ ነገር ግን እኛ ጋር የሕግና የፖሊሲ ማዕቀፍ ስለሌለ ዝም ብለን አስገብተን በመንገድ ላይ ጥቅም እንዲሰጡ እያደረግናቸው ነው ያለነው፡፡ ይህ ለዓይነ ስውራን አደገኛ የሆነ አካሄድ ስለሆነ መንግስት ሊያስብበት ይገባል፡፡
ምክንያቱም ተሽከርካሪዎቹ ድምጽ ስለሌላቸው መጥተው ሲገጩን ብቻ ነው የምናውቀው፡፡ አንድ ዓይነ ስውር በሚጓዝበት ወቅት አደጋ መኖርና አለመኖሩን የሚለየው ድምጽ በመስማትና በነጭ ብትሩ በመዳበስ ነው" ብለዋል።
በአጠቃላይ በዘርፉ ስላለው ችግር ሲያስረዱም፣ "የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎቹ ድምጽ ስለሌላቸው ዓይነ ስውራን ራሱ ቢገቡባቸውና/ቢጋጩ የአሽከርካሪዎች ኃላፊነት ከፍተኛ ድርሻ ስለሚይዝ ሊጣል የሚገባው ካሳ ሊቀንስልኝ ይገባል በሚል ክርክር ውሳኔው ምንድን ነው? በሚለው ዙሪያ በዓይነ ስውራን ወገኖች ረገድ ሕግ የለም " ነው ያሉት።
የመፍትሄውን ሃሳብ በተመለከተ ለጊዜው መንግስት በዚሁ ረገድ ሰርኩላር በትኖ የቁጥጥር ስልቱን መንደፍና መተግበር፣ በዘላቂነትም የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን በተመለከተ ሕግና ፖሊሲ እንዲያወጣም አሳስበዋል፡፡
(ተጨማሪ አለን በቀጣይ ይቀርባል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ፈጣሪ ጠብቋቸዉ እንጂ ጉዳቱ የከፋ ሊሆን ይችል ነበር " - የብርብር ከተማ ፖሊስ
ሀገር አቀፍ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሲጓዝ የነበረ መኪና የትራፊክ አደጋ አጋጥሞት በሰዉና በንብረት ጉዳት መድረሱን የብርብር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር ምትኩ ፉላሞ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋዉ የደረሰዉ ከቦሮዳ ወረዳ ሀገር አቀፍ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሚሄዱ የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ይዞ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-09846 ደሕ የሆነ FSR መኪና ከአርባምንጭ ወደ ወላይታ ሶዶ ከተማ ይጓዝ ከነበረ ኮድ 3-32326 ኦሮ ከሆነ የሕዝብ ማመላለሻ ጋር በመጋጨቱ እንደሆነ አዛዡ አስታዉቀዋል።
በአደጋው በ5 ሰዎች ላይ ከባድ እና በ23 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን የገለፁት አዛዡ ተጎጅዎችም በብርብር መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለህክምና መወሰዳቸዉን ገልፀዋል።
" ከቦታዉ ዳገታማነትና ከመኪኖቹ ፍጥነት አንፃር ሊደርስ ይችል የነበረዉ አደጋ ዘግናኝ ይሆን ነበር " ያሉት ፖሊስ አዛዡ " ፈጣሪ ጠብቋቸዉ የሞት አደጋ እስካሁን አልተከሰተም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
🕊#Peace
" የትግራይ ፓለቲከኞች ሃላፊነት ከጎደለው የመተላለቅ እንቅስቃሴ ተቆጠቡ " - ጉባኤው
" በትግራይ የእርስ በርስ መተላለቅ የሚጋብዝ ፕሮጀክት የተወገዘና ተቀባይነት የሌለው ነው " አለ የትግራይ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ።
ጉባኤው የትግራይ ፓለቲከኞች ሃላፊነት ከጎደለው የመተላለቅ እንቅስቃሴ እንዲቆጠቡ ሲል በፅኑ ተማፅኗል።
" ህዝብን በማሳተፍ ለሰላም ፣ ለፍቅር ለፍትህና ለአንድነት እሰራለሁ " ሲል ያሳወቀው ጉባኤው " በመሪዎች መካከል የተፈጠረው ተግባብቶ ያለመስራት ችግር ህዝቡ ለስደት፣ ለመፈናቀልና ለሞት የዳረገ የሚወገዝ ተግባር ነው " ብሏል።
" ገና ከጦርነት ባለገገመች ትግራይ ትግራዋይ ከትግራዋይ ለመተላለቅ ያለመ ፕሮጀክት ተደግሷል " ያለው ጉባኤው " ይህ አደገኛ ፕሮጀክት ለትግራይ ህዝብ ታሪክ የማይመይጥን ነው " ብሎታል።
በአገር ውስጥና በመላ ዓለም የሚገኝ ትግራዋይ ሆደ ሰፊና አስተዋይ እንዲሆን መክሮ " በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ በጋራ እንቁም " ሲል ጥሪ አቅርቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ስለተፈጠረው ስህተት ህዝባችንን ይቅርታ እንጠይቃለን። ለአርቲስት አንዷለም ጎሳ የሰጠነው ሽልማት ተሰርዟል ! " - ፋውንዴሽኑ
የሀጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ባዘጋጀው 4ኛው የሃጫሉ አዋርድ ላይ በምርጥ ወንድ ድምጻዊ ዘርፍ አሸናፊ አድርጎ የመረጠውን የአርቲስት አንዷለም ጎሳን ሽልማት መሰረዙን ገልጿል።
ሽልማቱ በተለይም የወጣት ቀነኒ አዱኛ ጥቃትን የሚያመለክቱ ፎቶዎችና ቪዲዮዎች በስፋት በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ከተለቀቁ በኋላ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል።
በዚህም ሽልማቱ እንዲነሳ የ24 ሰዓት የማኅበራዊ ሚዲያ ንቅናቄዎች ሲካሄዱ ነበር። ውሳኔውም ይኸው የሰዓት ገደብ ካበቃ ከሰዓታት በኋላ የተላለፈ ነው።
ፋውንዴሽኑ በመግለጫው ሽልማቱን ጉዳዩን ከሚመለከተው የህግ አካል የተጻፈ ደብዳቤ ይዘን የሸለምን ቢሆንም ከህዝብ በደረሰን አስተያየት ውሳኔያችን ስህተት ሆኖ አግኝተነዋል ሲል ገልጿል።
አክሎም " ስለተፈጠረው ስህተት ህዝባችንን ይቅርታ እየጠየቅን ለአርቲስት አንዷለም ጎሳ የሰጠነው ሽልማት የተሰረዘ መሆኑን እናሳውቃለን " ሲል አስታውቋል።
Via @TikvahethMagazine
#SafaricomEthiopia
🌐 ቅመም ማይፋይ በአዲስ ዋጋ መጥቷል 🙌
💨⚡ እስከ 7 ሰዓት የሚቆይ የባትሪ አቅም ያለውና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን ይዞ በአንዴ እስከ 8 ሰው ድረስ የሚያስጠቅመውን ልዩ ቅመም MIFIን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም!
🍰 ለ30 ቀን ከሚቆይ ነጻ 30ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር 😊
ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት⚡
#OFC
" በ2018 ምርጫ ለመሳተፍ የምንወስነው እነዚህ መሠረታዊ ጥያቄዎች ምላሽ በማግኘታቸው ላይ የተመሰረተ ነው " - ኦፌኮ
የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የውጭ መረጃ አሰባሳቢ ልዑክ ጋር በዋና ፅ/ቤቱ መወያየቱን ገለጸ።
ፓርቲው ውይይቱ የነበረው በ2018 ዓ/ም የሚካሄደው 7ኛው አጠቃላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምርጫ ላይ እንደሆነ አመልክቷል።
" ምርጫው ቁልፍ እና ወሳኝ የተባሉ ጥያቄዎችን አቅርቢያለሁ " ብሏል።
ኦፌኮ " ነጻ፣ ፍትሃዊ እና ተአማኒነት ያለው የምርጫ ሂደት እንዲረጋገጥ መንግስት ሊያሟላቸው የሚገባቸውን መሰረታዊ ጥያቄዎችን እንዲሁም የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀውስ አስመልክቶ ዝርዝር እና የማያዳግም ግምገማ አቅርበናል " ብሏል።
በውይይቱ ላይ እነማን ተገኙ ?
ኦፌኮን በመወከል ፦
- የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና
- የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሱልጣን ቃሲም ተገኝተዋል።
የተባበሩት መንግስታት ልዑካን ቡድን አራት አባላት የያዘ ሲሆን ፦
- በተመድ የአፍሪካ ህብረት ቢሮ (UNOAU) የምርጫ ድጋፍ ክፍል ዋና ኦፊሰር አኪንየሚ ኦ. አዴግባላን
- በኢትዮጵያ የተመድ የነዋሪ አስተባባሪ ጽ/ቤት የሰላምና ልማት አማካሪ ዶ/ር ዘቡሎን ሱይፎን ታክዋን እንዲሁም ሌሎች ሁለት ቁልቅ የተመድ ልዑካን አካትቷል።
ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ምን አሉ ?
" ኦፌኮ በ2018 ምርጫ ላይ መሳተፉ ሙሉ በሙሉ በመሠረታዊ እና በተጨባጭ ለውጦች ላይ የተመሰረተ ነው።
ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ድምፅ የመስጠት ቴክኒካዊ ሂደት ብቻ አይደለም፤ የዲሞክራሲያዊ ሂደት ውጤት ነው። ይህ ሂደት ዛሬ በኢትዮጵያ የለም። በጦርነት እና በፖለቲካ ስደት ውስጥ ተአማኒነት ያለው ምርጫ ማካሄድ አይቻልም። " ብለዋል።
ኦፌኮ፣ ተመድ ዲፕሎማሲያዊ ተጽዕኖውን ተጠቅሞ እንዲያስፈጽም በማሳሰብ ለመንግስት የሚቀርቡ ዝርዝር ጥያቄዎችን አቅርቧል።
በኦፌኮ የቀረቡ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምንድናቸው ?
➡️ በኦሮሚያና በመላ ኢትዮጲያ ሰላም ፣ በክልሉ ያለውን አውዳሚ ግጭት ለማስቆም በመንግስት ኃይሎች እና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሰ) መካከል በአለም አቀፍ ታዛቢዎች የሚረጋገጥ አፋጣኝ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ።
➡️ ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች መፍታት፣ የኦፌኮ አባላትን፣ አመራሮችንና ደጋፊዎችን ጨምሮ በመላ አገሪቱ የታሰሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች፣ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ።
➡️ በነጻነት የመንቀሳቀስ ዋስትና፣ በተቃዋሚዎች ላይ የሚደርሰው ማስፈራራት፣ ወከባና እስራት እንዲቆም። ኦፌኮ የፓርቲ ጽ/ቤቶችን በነጻነት የመክፈትና የማንቀሳቀስ እንዲሁም ከሃገር ውስጥ አስተዳዳሪዎችና ከጸጥታ ኃይሎች ምንም አይነት ጣልቃ ገብነት ሳይኖር ህዝባዊ ስብሰባዎችን የማድረግ መብት እንዲከበርለት ጠይቋል።
በተጨማሪ፦
➡️ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ የፌደራል ፖሊስ እና የክልል የጸጥታ ኃይሎች አመራሮች በፖለቲካው ሂደት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ገለልተኛ ለመሆናቸው በይፋ ቃል የሚገቡበት እና ጥሰቶችን የሚመረምር ገለልተኛ አካል የሚቋቋምበት ስምምነት እንዲፈረም።
➡️ ከምርጫ በፊት የሁሉም ፓርቲዎች ውይይት፣ በገዥው ፓርቲ እና በሁሉም ዋና ዋና ተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ግልጽ የሆነ የምርጫ ፍኖተ ካርታ ላይ ለመስማማት የሚያስችል ይፋዊ ውይይት እንዲካሄድ።
➡️ የምርጫ ቦርድን እንደገና ማቋቋም፣ ገለልተኝነቱን ለማረጋገጥ ሁሉም ዋና ዋና የፖለቲካ ፓርቲዎች በሚሳተፉበት ግልጽና አካታችነት ላይ በተመሰረተ ሂደት ኮሚሽነሮችን በመሾም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) እንደገና እንዲዋቀር።
➡️ አሁን በስራ ላይ ያለውንና አሸናፊ ሁሉን የሚወስድበትን የአብላጫ ድምፅ የምርጫ ሥርዓት መሠረታዊ በሆነ መልኩ መከለስ። ሁሉም ማህበረሰቦችና የፖለቲካ ቡድኖች በፓርላማ ውስጥ ፍትሃዊ ውክልና እንዲኖራቸው ለማድረግ ወደ ተመጣጣኝ ውክልና (MMP) የምርጫ ሥርዓት እንዲሸጋገር።
➡️ ገዥው ፓርቲ በመገናኛ ብዙኃን ላይ ያለውን የበላይነት በማስቀረት ሁሉም የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመንግስት ሚዲያዎች (EBC, OBN የመሳሰሉት) ላይ ፍትሃዊ እና እኩል የአየር ሰዓት እንዲያገኙ የሚያስችል በገለልተኛ አካል የሚመራ ህጋዊ ማዕቀፍ እንዲዘረጋ።
➡️ በሂደት ላይ ያለው ብሔራዊ ምክክር ሁሉንም የፖለቲካና የትጥቅ ቡድኖችን ያካተተ እንዲሆንና እንደ ፌዴራሊዝምና የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ባሉ መሠረታዊ ጉዳዮች ላይ የሚያስተላልፋቸው ውሳኔዎች አስገዳጅ እንዲሆኑ ማድረግ።
የሚሉትን ጥያቄዎች በይፋ አቅርቧል።
የተመድ ልዑካን ቡድን የምርጫውን ቅድመ-ሁኔታዎች የመገምገም ኃላፊነት የተሰጠው መሆኑን ያመለከተው ኦፌኮ ቡድኑ የቀረበለትን ሃሳብ በትኩረት እንዳዳመጠው ገልጿል።
ኦፌኮ በ2018 ምርጫ ለመሳተፍ የሚያደርገው ውሳኔ እነዚህ " መሠረታዊ " ያላቸው ጥያቄዎች ምላሽ በማግኘታቸው ላይ የተመሰረተ እንደሆነ አሳውቋል።
መረጃውን የላከው የኦፌኮ የህዝብ ግንኙነት ፅ/ቤት ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#Ethiopia🇪🇹
" አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም ! " - የምክር ቤት አባል
በገቢ ግብር ማሻሽያ አዋጅ ላይ ዝቅተኛ የግብር ከፋይ መነሻ ደመወዝ 5,000 ብር እንዲሆን በምክር ቤት ተጠየቀ፡፡
ይህ ጥያቄ የተጠየቀው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዛሬ ከሰዓት በጠራው ልዩ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡
አሁን በስራ ላይ ያለው የገቢ ግብር አዋጅ ከዘመኑ የኢኮኖሚ ሁኔታ አብሮ እንደማይሄድ እና ከዲጂታል ኢኮኖሚ ጋር እንደማይጣጣም በአዋጁ ላይ በቀረበው አጭር ማብራርያ ተመላክቷል፡፡
የማሻሽያ አዋጁን በተመለከተ ሃሳብ የሰጡት የምክርቤት አባሉ አቶ ባርጠማ ፍቃዱ ምን አሉ ?
- በአዋጁ አንቅጽ 11 ላይ የቀድሞው ተሰርዞ አዲስ ሃሳብ ገብቷል። ከዚህ በፊት ተቀጣሪ ከደሞዘ የሚከፍለው ግብር ከ600 ብር በላይ ጀምሮ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው አዋጅ ግን ከ600 ብር ወደ 2,000 ብር አድጓል።
- በመሰረቱ 2 ሺ ብር አሁን በአገራችን የሚቀጠር ሰው የለም።
- ከዚህ ቀደም በመንግስት ተቋም ጽዳት ፣የጉልበት ስራ እና የመሳሰሉ ስራዎች ነበሩ ከ600 ብር እስከ 1,000 ብር ደሞዝ አሁን ባለው ሁኔታ ከ4,500 ብር በላይ ነው ቅጥር ያለው።
- አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም።
- ቢያንስ እንኳን ዝቅተኛ ተቀጣሪው ከግብር ነጻ ቢሆን ጥሩ ነው።
- ግብር ከፋይዉም ከ5,000 በላይ ያለው ስራተኛ ቢሆን።
- የ35 በመቶ ግብር እንዲከፍል የተቀመጠው ከ14ሺ 100 በላይ ነው። ይህም ከወቅቱ ገበያ አንጻር ሲታይ ምንም ነው፤ በዚህ ላይ 35 በመቶ ግብር ሲቆረጥበት ደግሞ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ ወደ 20 ሺ በላይ ከፍ ቢል።
- በስራ ላይ ባለው አዋጅ #መነሻ_ግብር 10 በመቶ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው ረቂቅ አዋጁ ግን 15 በመቶ ብሎ ነው የሚጀምረው ይህም ወደ ቀድሞው ወደ 10 በመቶ ቢመለስ ሲሉ ጥሩ ነው።
የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን በስራ ላይ ባለው አዋጅ ላይ ያለው ከፍተኛ ግብር የሚከፈልበት ደሞዝ በተሸሻለው አዋጅ የዝቅተኛ ግብር መነሻ እንዲሆን መጠየቁ ይታወሳል።
ኮንፌደሬሽኑ የሰራተኛውን ኑሮ ያገናዘበ የገቢ ግብር ማሻሽያ እንዲደረግም ጠይቆ ነበር፡፡
ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህበረተሰብ ክፍል ፦
- የሚያርፍበትን የግብር ጫና መቀነስ፤
- የግብር መሰረትን ማስፋት፤
- የግብር ስርአቱ ላይ የሚታዩ የፍትሃዊነት ችግሮችን መቅረፍ፤
- የአነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች የግብር አከፋፈል ስርአት ቀላል እንዲሆን ማድረግ፤
- ከአዋጁ አላማዎች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡
ም/ቤቱ እነዚህን እና ሌሎች ከአባላት የተነሱ ሃሳቦች ታክለውበት ረቂቅ አዋጁ ለፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳይዎች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መርቶታል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
🔵🛜 የDSTV ተወዳጅ ቻናሎችን ከፋይበር ኢንተርኔት ጋር ያግኙ!!
በስማርት ቲቪዎ የዲ.ኤስ.ቲቪ ስትሪም መተግበሪያ በመረጡት ጥቅልና የዳታ ፍጥነት DSTVን በቤትዎ ፋይበር ያጣጥሙ።
🎬 #ጎጆ_ጥቅል ከ70 በላይ ተወዳጅ ቻናሎችን በወር ከ929 ብር ጀምሮ!
💁♂️ እስከ 26.5% በሚደርስ ቅናሽ የቀረቡትን የፋይበር ብሮድባንድ እና የዲ.ኤስ.ቲቪ ጥቅሎች ይግዙ፤ በአማራጭ ይዝናኑ።
ℹ️ ስማርት ላልሆኑ ቲቪዎች STB (Set-Top Box) ለማግኘትና አገልግሎቱን ለመጠቀም የአገልግሎት ማዕከሎቻችንን ይጎብኙ!
👉 እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ ይመልከቱ: https://youtu.be/5u0r_t7_WGA
#DSTV
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
" ህልምን ለማሳካት ቆራጥ መሆን ያስፈልጋል " - ከሶስተኛ ልጃችው ጋር ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተቀመጡት የ52 አመቱ አባት
ዛሬ ከሶስተኛ ልጃቸው ጋር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና እየወሰዱ ያሉት የ52 አመቱ አባት አቶ ግዛው መኮነንን ነዋሪነታቸው በምዕራብ ጎንደር ዞን በአዳኝ ሀገር ጫቆ ወረዳ ነው።
ከሚኖሩበት ነጋዴ ባህር ከተማ ህዝብ ተሰብስቦ " መልካም እድል " ብሎ መርቆ ወደ ጎንደር ዮንቨርስቲ ከልጃቸው ጋር ሸኝቷቸዋል።
አቶ ግዛው መኮነን የ5 ልጆች አባት ሲሆኑ የ52 አመት የእድሜ ባለጸጋ ናቸው።
" በ1979 ዓ.ም የ6ተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ ያውም ጎበዝ አንድ አንደኛ የምወጣ ተሸላሚ ተማሪ ነበርኩ ግን በወቅቱ አስገዳጅ በሆነ ምክንያት ትምህርቴን አቋረጥኩ " ይላሉ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ።
አቶ ግዛው " ትምህርቴን እንዳቋርጥ ያስገደዱኝ ወላጆቼ ናቸው በወቅቱ ደርግ በግዳጅ ለውትድርና ወጣቱን ይመለምል ነበር ያኔ ወላጆቼ ወደ በርሃ እንድገባ አስገደዱኝ ማለትም 1979 ዓ.ም ከአራት አመት የበርሃ ቆይታ በኃላ ወደ ትውልድ ከተማየ ስመለስ በ1983 ዓ.ም ማለት ነው ጏደኞቼ የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሆነው አገኘኃቸው " ብለዋል።
" በዚህ ልዩነትማ ትምህርት አልጀምርም አንዴ ኃላ ቀርቻለሁ ብየ ሚስት አገባሁ ከዛም በተከታታይ 5 ልጆችን ወለድኩ ልጆቼን ለማሳደግም በግብርና ኃላም በንግድ ስራ ተሰማራሁ 5ተኛ ልጄን ከወለድኩ በኃላ የዛሬ 6 አመት ማለት ነው በማታው ትምህርት ክፍል ካቆምኩበት 6ተኛ ክፍል ቀጠልኩ በርትቼ በማጥናትም ለዛሬ ፈተና ደርሻለሁ " ሲሉ ገልጸዋል።
አቶ ግዛው ያኔ አብረዋቸው የተማሩ ጏደኞቻቸው እስከ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የደረሱ እንዳሉና በሚኖሩበት አካባቢም ፖሊስና መምህር ሆነው ህዝብን ሲያገለግሉ ሲመለከቱ ይቆጩ እንደነበር ይናገራሉ።
እሳቸው እንደሚሉት በግብርና ስራ ልጅን የማሳደግ ኃላፊነት ይዘው ህይወታቸውን ቢገፉም ጎን ለጎን የትምህርያቸው ጉዳይ ያንገበግባቸው ነበር።
የአቶ ግዛው የመጀመሪያ ልጃቸው በንግድ የተሰማራ ሲሆን ሁለተኛ ልጃቸው የግብርና ኤክስቴንሽን ሰራተኛ ናት ሶስተኛ ልጃቸው ዛሬ ከእርሳቸው ጋር በጎንደር ዩንቨርስቲ ሀገር አቀፍ ፈተናውን እየወሰደ ነው ፤ አራተኛና አምስተኛ ልጆቻቸው ተማሪዎች ናቸው።
" ህልም ለማሳካት ቆራጥ መሆን ያስፈልጋል " የሚሉት አቶ ግዛው ፈተናውን ለመውሰድ በቂ ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸውን እና ከልጃቸው ጋር እስከ እኩለ ሌሊት አብረው ሲያጠኑና ሲረዳዱ መክረማቸውን ተናገረዋል።
ለዩንቨርስቲ መግቢያ የሚያበቃ ውጤት ለማምጣት መዘጋጀታቸውን ውጤቱ ቢመጣም ዩኒቨርሲቲ ለመግባት መዘጋጀታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyBahirdar
@tikvahethiopia
#Update
" የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል ! " - ሂደቱን የሚከታተሉ ታዛቢዎች
አሁንም የእንስት ዘወዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል የፍርድ ውሳኔ ሌላ ቀጠሮ ተይዞለታል።
የግድያ ወንጀሉ ከተፈፀመ የፊታችን ነሀሴ ወር የሚከበረው የአሸንዳ 2017 ዓ.ም በዓል ሁለት ዓመት ይሞላዋል።
አሰቃቂ የግድያ ወንጀሉ የአሸንዳ በዓል በሚከበርበት ወርሃ ነሀሴ 2015 ዓ.ም ነበር የተፈፀመው።
የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ችሎት የትላንት ውሎ ምን ይመስል ነበር ?
የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል በመመልከት ላይ የሚገኘው የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም በተከሳሾች ላይ ያስተላለፈው ውሳኔ ላይ ጥፋተኛ የተባሉት ግለሰቦች የሚያቀርቡት የፍርድ የማቅለያ ለመስማት ነው ለሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም የተቀጠረው።
የችሎቱ ዳኞች በያዙት ቀጠሮ ተከሳሾች ለፍርድ ማቅለያ የሚሆናቸውን የህክምናና ሌሎች ሰነድ እንዲያቀርቡ ባዘዙት መሰረት በጠበቃቸው በኩል አቅርበዋል።
አንደኛ ተከሳሽ የልብ ህመም ታማሚና የኪንታሮት ህመምተኛ ፣ ሁለተኛው ተከሳሽ ደግሞ የስኳርና የኪንታሮት ህመምተኛ መሆናቸውን በቃል ቢገልጹም በሃኪሞች ማስረጃ እንዲረጋገጥ ለሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።
በግድያ ወንጀሉ በመፈፀመ የተጠረጠሩ ሁለቱ ወጣቶች ሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ/ም በሃኪም የተረጋገጠ የፅሁፍ ማስረጃ ያቀርቡ እንደሆነ ያኔ የሚታይ ሆኖ የችሎት ሂደቱን የተከታታሉ የሚድያ ባለሙያዎች ፣ የሴቶች ጥቃት እንዲቆም የሚሰሩ ግለሰቦችና ተቋማት " ይህንን ሁሉ በሽታ ተቋቁመው ይህን መሰል ዘግናኝ ግድያ ለመፈፀም እንዴት ጉልበትና አቅም አገኙ ? " የሚል ጥያቄ ጭረዋል።
የችሎቱ የውሎ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያ የተከታተሉ በርካቶች የፍርድ ሂደቱ ለሁለት አመታት መራዘሙ በመቃወም " የዘገየ ፍትህ እንዳልተሰጠ ይቆጠራል " ብለዋል።
የአሰቃቂ የግድያ ወንጀሉ የፍርድ ሂደት ሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም መቋጫ ይብጀለት ይሆን ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ጉዳዩ ተከታትሎ ያቀርባል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#Wolaita
ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በም/ማዕረግ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነ ተሾሙ። ወ/ሮ እታገኝ ሀ/ማሪያምን ደግሞ የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ ሆነዋል።
የወላይታ ዞን ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደዉ አስቸኳይ ጉባኤ የተለያዩ ሹመቶችን አፅድቋል።
በዚህም ፦
1. ረ/ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በም/ማዕረግ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ
2. አማረ አቦታ (ዶ/ር) የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ
3. አቶ ተስፋሁን ታዴዎስ የወላይታ ዞን ም/አስተዳዳሪና የከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ
4.ወ/ሮ እታገኝ ሀ/ማሪያምን የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ አድርጎ በሙሉ ድምጽ ሾሟቸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
#HoPR🇪🇹
" ድንጋጌውን ' ትክክል ነው ' ብለው ሲከራከሩ የነበሩ የፓርላማ አባላት ነበሩ፤ ዛሬ ደግሞ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ መደገፋቸው በአንድ ራስ ሁለት ምላስ ያስብላል " - የፓርላማ አባል
በወንጀል የተገኘ ንብረትን ህጋዊ ማስመሰል እንዲሁም ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን " በሽፋን ስር " ሆኖ የመመርመር ኃላፊነት የተሰጠው ሰው፤ " ከግድያ በስተቀር " የሚፈጽማቸውን የወንጀል ድርጊቶች ከተጠያቂነት ነጻ የሚያደርገው ድንጋጌ ተሰረዘ።
ድንጋጌው የተሰረዘው አዋጁ " በሰፊው እንዲተረጎም ስለሚያደርግ " እና በአተገባበሩም ላይ " አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያስከትል ስለሆነ ነው " ተብሏል።
አወዛጋቢው ድንጋጌ ተካትቶ የነበረው፤ በወንጀል የተገኘ ንብረትን ህጋዊ ማስመሰል እንዲሁም ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በወጣ አዋጅ ላይ ነበር።
አዲሱ አዋጅ በፓርላማ የጸደቀው ሰኔ 10፤ 2017 ዓ.ም. ነበር።
የተሰረዘድ ድንጋጌ " በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራ ወይም በቁጥጥር ስር የሚደረግ ማስተላለፍን እንዲያስፈጽም የተመደበ ሰው፤ በግዴታው ላይ እያለ ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት እና ከፈቃዱ ውጭ ሆኖ ከግድያ ወንጀል በስተቀር ለሚፈጽመው የወንጀል ድርጊት የወንጀል ክስ አይቀርብበትም " ይላል።
አዋጁ በጸደቀበት ዕለት የውሳኔ ሃሳብ ለፓርላማ አባላት ያቀረበው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚቴ፤ ድንጋጌው እንዲካተት የተደረገው " ልዩ የምርመራ ስራን " " ውጤታማ የሚያደርግ በመሆኑ "ምክንያት እንደሆነ ገልጾ ነበር።
ቋሚ ኮሚቴው " ልዩ የምርመራ ዘዴን " በመጠቀም ስራውን የሚያከናውን ሰው፤ " የህዝብን ጥቅም ለማስጠበቅ የሚሰራ መሆኑን " እንደ ደጋፊ ምክንያት አቅርቦ ነበር።
ይሁንና ቋሚ ኮሚቴው ዛሬ ሰኞ ሰኔ 30 በተደረገ የተወካዮች ምክር ቤት ልዩ ስብሰባ ላይ፤ ድንጋጌው እንዲሰረዝ የሚያደርግ የውሳኔ ሃሳብ አቅርቧል።
ድንጋጌው " አዋጁ በሰፊው እንዲተረጎም የሚያደርግ እና አተገባበሩ ላይም አሉታዊ ተጽእኖ የሚያስከትል ስለሆነ፤ አዋጁ ለህትመት ያልበቃ እና በሂደት ላይ ያለ በመሆኑ፤ ቀሪ እንዲሆን ይህ የውሳኔ ሀሳብ ቀርቧል " ብሏል።
የውሳኔ ሀሳቡ በአንድ ድምጽ ተዐቅቦ ፀድቋል።
የፓርላማ አባላት ምን አሉ ?
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የፓርላማ ተወካይ አቶ ባርጠማ ፈቃዱ ፦
" አዋጁ ተመልሶ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መምጣቱ የምክር ቤቱን አቅም ጭምር የሚያሳይ ነው።
አዋጁ በሚጸድቅበት ወቅት ድንጋጌውን ' ትክክል ነው ' ብለው ሲከራከሩ የነበሩ የፓርላማ አባላት ነበሩ፤ ዛሬ ደግሞ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ መደገፋቸው በአንድ ራስ ሁለት ያስብላል " ብለዋል።
ሌላ የፓርላማ አባል ፦
" አዋጁ በሚጸድቅበት ጊዜ በድንጋጌው ላይ በመሰረታዊነት ክርክር ተደርጓል። በድንጋጌው ላይ የተለያየ መልክ ያለው ጫጫታ በብዛት ሲሰማ ነበር።
በምርመራ ወቅት የሚመረምረው አካል አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ባለበት ጊዜ፤ ከዚህ ውጪ ሊያደርግ የሚችለው ጉዳይ እንደሌለ፣ ዋስትና ሊያገኝ እንደሚገባ በደንብ ማብራሪያ የተሰጠበት ጉዳይ ነበር።
ድንጋጌው ከአዋጁ ውስጥ እንዲወጣ ሲደረግ፤ መርማሪዎች የተሰጣቸውን ዋስትና የሚያስቀር በመሆኑ ቀድሞ የጸደቀው ባለበት ቢቀጥል ይሻል ነበር።
የሚመረምሩ ሰዎች፣ አደገኛ ችግር ውስጥ ባሉበት ሁኔታ ውስጥ፤ የእዚህ አይነት ዋስትና ሊያገኙ የማይችሉ ካልሆነ ሊመረምሩ ፍቃደኛ ይሆናሉ ወይ? ሊገቡ ፍቃደኛ ይሆናሉ ወይ? የሚመረምሩ ሰዎች አደገኛ ችግር ውስጥ ባሉበት ሁኔታ ውስጥ ዋስትና የማንሰጣቸው ከሆነ፤ እንደዚህ አይነት risk ሊወስድ የሚችል አካል ላይኖር ይችላል። " ብለዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ምን አሉ ?
" ለእንደዚህ አይነት የምርመራ ስራዎች ዋስትና የሚሰጥ ህግ አለ። ዋስትና መስጠት እና ሌላ ነገር እንዲያደርግ ማድረግ የተለያየ ነገሮች ናቸው። ድንጋጌው መሰረዙ ተገቢ ነው። "
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገጽ ነው።
@tikvahethiopia
#Tigray
" በትግራይ በኩል የሚከፈት ጦርነት የለም ፤ ከሌላው ወገን የሚተኮስ ጥይት እንዳይኖር ጥንቃቄ ያሻል " - የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት
" በትግራይ በኩል የሚከፈት ጦርነት የለም ፤ ከሌላው ወገን በተሳሳተ ውሳኔ ትግራይ የሚተኮስ ጥይት እንዳይኖር ጥንቃቄ ያሻል " ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ተናገሩ።
ፕሬዜዳንቱ " ሁሉም ነገር በሰላማዊ መንገድ ይፈታል ብለን ስለምናምን በትግራይ በኩል የሚጀመር ትንኮሳ እና ጦርነት አይኖርም " ብለዋል።
" በክልሉ ደቡባዊ ዞን ያለው ችግር የመላው ትግራይ እንጂ የአከባቢው ብቻ አይደለም " ያሉት ፕሬዜዳንት ታደሰ " ጊዚያዊ አስተዳደሩ በዞኑ ካለው አስተዳደር በመነጋገር በሰላማዊ መንገድ ይፈታዋል " ሲሉ ተናግረዋል ።
ራሱን " የትግራይ የሰላም ሃይል " በሎ ከሚጠራውና በዓፋር ክልል ሆኖ የትጥቅ ትግል ከሚያካሂደው ሃይል ጋር ያለውን ችግር " በሰላማዊ ውይይት ይፈታል " ያሉ ሲሆን " ከዚህ ውጪ ያለው አማራጭ ግን ህዝብን ለአደጋ የሚዳርግ ስለሆነ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል " ብለዋል።
" የትግራይ ሉአላዊነት ተደፍሮ ተፈናቃዮችና ስደተኞች ወደ ቄያቸው ባልተመለሱበት ሁኔታ ላይ ተሆኖም ችግሮች በሰላማዊ መንገድ የመንፍታት ጉዳይ አንደኛ አማራጫችን ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
" ተፈናቃዮችና ስደተኞች ወደ ቄያቸው መመለስ ከሁሉም ስራዎቻችን ቅድምያ የምንሰጠው ነው ጉዳዩ ጊዜ በወሰደ ቁጥር የሰላም በር እንዳያጠብ የፌደራል መንግስት የበኩሉን ሃላፊነት በመወጣት ችግሩ እንዲፈታ ጥሪ እናቀርባለን " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#Update
19 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶበታል !
ታዳጊዋ አያንቱ ቱና ላይ የግበረስጋ ድፍረት የፈጸመው ግለሰብ በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።
በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሻፋሞ ወረዳ የ13 ዓመቷን ታዲጊ አያንቱ ቱና ላይ የግብረስጋ ድፍረት ወንጀል በመፈጸም የተጠረጠረውና በፖሊስ ተባባሪነት ጭምር አምልጦ ከ1 ዓመት በላይ ተሰዉሮ የነበረዉ ወጣት በቲክቫህ ኢትዮጵያ ላይ መረጃው ከተሰራጨ በኋላ በተደረገ ክትትልና ፍለጋ ተጠርጣሪዉ በቁጥጥር ስር ዉሎ ክስ ተመስርቶበት እንደነበር የአያንቱ ታላቅ ወንድም ወጣት ጴጥሮስ ቱና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ይኸው ግለሰብ አርብ ዕለት ፍርድ ቤት ቀርቦ ዉሳኔ እንደተላለፈበት የአያንቱ ወንድም ተናግሯል።
የሻፋሞ ወረዳ ዐቃቤ ሕግ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደምሴ ፉና ስለጉዳዩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲያስረዱ " የወረዳዉ ፖሊስ እና ዐቃቤ ሕግ በተከሳሹ ላይ ያቀረቡትን ጠንከር ያለ ምርመራ፣ የሰነድ እንዲሁም የሕክምና ማስረጃዎችን የተመለከተዉ የወረዳዉ ፍርድ ቤት ግለሰቡን ጥፋተኛ ነዉ በማለት በ19 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል " ብለዋል።
" ተጠርጣሪዉ በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በማቆያ ዉስጥ የምትገኘዉ አያንቱ ደፋሪዋ እንደተያዘ ከተነገራት በኋላ ጥሩ መሻሻል ታይቶባታል " የሚለዉ የታዳጊዋ ወንድም ጴጥሮስ " ከዚህ በኋላ ከማቆያ ወጥታ ወደ ትምህርት ገበታዋ ትመለሳለች " ብሏል
" የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ ለታዳጊዋ ድምፅ ለሆናችሁ ሁሉ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ " ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
" ከ47 በመቶ በላይ አሽከርካሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ከፍጥነት ወሰን በላይ ነው የሚያሽከረክሩት ! "
የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ማኀበር ዘርፉን በተመለከተ አዘጋጅቶት በነበረው መድረክ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራፊክ ማኔጀመንት ባለስልጣን መጥተው የነበሩት አቶ ደረጀ የተባሉ አካል " በየዓመቱ ከ2000 እስከ 300ዐ ለሚሆኑ አሽከርካሪዎች ስልጠና እንደሚሰጡ፣ ኢንፍራስትራክቸር በተለይ ለአካል ጉዳተኞች በልዩ ሁኔታ ተይዞ መሰራት እንዳለበት፣ አቅም በፈቀደ መልኩ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
" ነገር ግን የትራፊክ ግጭቱ ስታቲስቲክሱ ሲታይ በዓመት አዲስ አበባ ከተማ ብቻ 401 ሰው ይሞታል። በአመት 401 ሰው ይሞታል ማለት በቀን ከ1 ሰው በላይ ይሞታል ማለት ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው የሚፈጠረው ግጭት ደግሞ መቆጣጠር የሚቻል፤ በሰዎች ስህተት የሚፈጠር እንደሆነ ነው መረጃዎች የሚያሳዩት "ብለዋል።
" አንድ ክርክር አለ የትራፊክ አደጋ ነው ወይስ ግጭት ነው? የሚል። ከ95 በመቶ በላይ በሰዎች ባህሪ ላይ ሰርተን ለውጥ ማምጣት፤ የመንገድ ደህንነትን ለማረጋገጥ የወጡ ህጎችን ማክበር የምንችል ከሆነ ግጭቶችን መቀነስ የምንችልበት እድል ሰፊ ስለሆነ አደጋ ተብሎ ሊያዙ የሚገባ አይደሉም የሚል መከራከሪያ ይነሳል " ነው ያሉት።
" እውነት ነው፤ አንደኛው በአዲስ አበባ ላይ የግጭት አደጋ ምክንያት ከፍተኛ ፍጥነት ነው። ከ47 በመቶ በላይ አሽከርካሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ከፍጥነት ወሰን በላይ ነው የሚያሽከረክሩት " ብለው፣ " ስለዚህ አንድ አካል ጉዳተኛ ዜብራ መንገድ እያቋረጠ እያለ በፍጥነት የሚመጣ አሽከርካሪ ተሽከርካሪውን ተቆጣጥሮ ከአደጋው ሊታደገው አይችልም " ሲሉም ተናግረዋል።
በመዲናዋ በመኪና አደጋ ግጭት ጭምር በየጊዜው የበርካቶች ሕይወት እንደሚያልፍ፣ በተለይ ዓይነ ስውራን ደግሞ ለዚህ ተጋላጭ እንደሆኑ ይነገራል፤ ጥናት አድርጋችሁ ነበር? ማኀበሩ ባለው መረጃ መሠረት ስንት ዓይነ ስውራን በዚሁ አደጋ ሞተዋል? ስንልም የኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ማኀበርን ጠይቀናል።
የማበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አበራ ረታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ምላሽ፣ " የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአካል ጉዳተኞች ሰብዓዊ መብቶች ቃል ኪዳን አካል ጉዳተኞችን በተመለከተ ዳታ ሊኖራቸው እንደሚገባ በመንግስታት ላይ ግልጽ የሆነ ግዴታ ይጥላል። ነገር ግን በመንግስት በኩል እንደዚህ አይነት የተደራጀ አሰራር የለም " ብለዋል።
" እንደ ኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን ማኅበር ከጥር 18 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ ብዙ የመኪና ሞት አደጋዎች መድረሳቸውን ያለን መረጃ ያሳያል (ይህ ከአዲስ አበባ ውጪ የሚያጋጥሙትን የሚያካትት አይደለም)። አደጋው ከፍተኛ ነው ማለት እንችላለን " ብለዋል።
" በጥር 18/2016 ዓ/ም አንድ የሞት አደጋ ሁለት ከባድ የአካል ጉዳት፣ በመጋቢት ለሚኩራ አንድ የሞት አደጋ ደርሶ ነበር፣ በሚያዚያ ወርም የሞት አደጋ ደርሷል፣ በመስከረም 2017 ዓ/ም በዓይነ ስውራን ላይ የሞት አደጋ ደርሷል፤ በሚያዚያ 2017 ዓ/ም በኮየ ፈጬ አንድ የሞት አደጋ ተመዝግቧል። አደጋው ከፍ እያለ እንደሆነ ነው የሚያሳየው " ነው ያሉት።
የችግሩ ምክንያቶች ሁለት እንደሆኑ በጥናት መዳሰሱን ገልጸው፣ "አንደኛው የኢንፍራስትራክቸር ችግር፤ ሁለተኛ ደግሞ Unsafe የሆነ የአሽከርካሪዎች አነዳድ እንደሆነ በጥናቱ ተመልክቷል" ሲሉም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ቶምቦላ ዛሬ እስከ 11 ሰዓት ብቻ!
አዎ! "በ11ኛው ሰዓት ገዝቼ ዛሬ በ11 ሰዓት አሸነፍኩ!" ሊሉ ይችላሉ።
አፍሪካ ህብረት አጠገብ ጃምቦ ሪል ስቴት ያስገነባው ባለ 12 ፎቅ ህንጻ ውስጥ ያሉትን እጅግ ዘመናዊ ባለ ሶስትና ሁለት መኝታ አፓርትመንት ቤቶች እንዲሁም ተወዳጆቹን ቮልስዋገን ID.6 እና BYD Song Plus SUV መኪናዎችን የራስዎ ማድረግ አይፈልጉም?
የቤቶቹ አድራሻ https://maps.app.goo.gl/mgqFwSerUqyBnrZL6?g_st=aw ይሄ ነው። ተገንብተዋል ይገቡባቸዋል! መኪኖቹም ተዘጋጅተዋል ያሽከረክሩዋቸዋል!
እንግዲያውስ ዛሬ እስከ 11 ሰዓት ብቻ በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት የሚወጣውን የቶምቦላ ሎተሪ በ100 ብር በቴሌብር ሱፐር አፕ ሰዓቱ ሳይደርስ አሁኑኑ ይግዙ!
ይቅናዎ!
ለበለጠ መረጃ በ +251977717272 ፣
+251950189808 እና
+251950199808 ይደውሉ!
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት!
" ከልጅ ልጄ ጋር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ በመብቃቴ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል" - የዕድሜ ባለፀጋዉ አቶ ማኖ ማገሶ
➡️ " ከአምስተኛ ክፍል የወረዳ አልፎም የአዉራጃ አስተዳዳሪ ሆኜ ነበር ፤ ትክክለኛዉ ዕድሜዬ 91 ነዉ ! "
አቶ ማኖ ማገሶ የ85 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ሲሆኑ ዘንድሮ በሁለተኛዉ ዙር የፈተና ፕሮግራም ከካቻ ካሻሶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ካቀኑ የ12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ዉስጥ አንዱ ናቸዉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም በልጃቸዉ በኩል አግኝቶ አነጋግሯቸዋል።
ከልጅ ልጃቸዉ ጋር ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምጣታቸዉን ገልፀዉ " ትምህርት በዕድሜ ሊገደብ አይገባም " ሲሉ ሃሳባቸው አጋርተዋል።
የ5 ወንዶችና የ6ሴቶች የ11 ልጆች አባት እንደሆኑ የገለፁት አቶ ማኖ በንጉሱ ዘመን በሁለት ዓመት ዉስጥ በነበራቸዉ ቀልጣፋ የትምህርት አቀባበል ክፍል እያጠፉ 5ኛ ክፍል መድረሳቸዉንና ከ5ኛ ክፍል ተወስደዉ የቦንኬ ወረዳ አመራር ተደርገዉ ተሹመዉ እንደነበርና ባሳዩት ጠንካራ አመራርም የቀድሞው የጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር በጋርዱላ አውራጃ የገበሬ ማኅበር ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው ይሰሩ እንደነበር አስታዉሰዋል።
በኋላም ደርግ መንበረ ስልጣኑን ሲይዝ ለእስር ተዳርገዉ ለ21 ዓመታት በአርባምንጭ ማረሚያ ታስረዉ መቆየታቸዉንና ደርግ ከወደቀ በኋላ ከማረሚያ ወጥተዉ ልጆቻቸዉን በማስተማር ቦታ ቦታ ካስያዙ በኋላ አቋርጠዉ የቆዩትን ትምህርት በመቀጠል ዘንድሮ በትምህርት መረጃ ላይ 85 ዓመት እሳቸዉ " ትክክለኛ ዕድሜዬ ነዉ " በሚሉት 91 ዓመታቸዉ ለዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ከልጅ ልጃቸዉ ጋር አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምጣታቸዉን ገልጸዋል።
ለትምህርት ካላቸዉ ጥልቅ ፍቅር የተነሳ በአመራርነት ዘመናቸዉ በርካታ ትምህርት ቤቶችን እንዳስገነቡ የገለፁት አቶ ማኖ እሳቸዉ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት አግብተዉ ትምህርታቸዉን አቋርጠዉ የነበሩ ልጆቻቸዉን ጭምር ከተፈቱ በኋላ ከባሎቻቸዉ ጭምር እንዲማሩ አድርገዉ በአሁኑ ሰዓት በመንግስት ስራ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
" ከልጅ ልጄ ጋር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ በመብቃቴ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል፤ ጥሩ ዉጤት አምጥቼ ዩኒቨርሲቲ እገባለሁ " ብለዋል።
" ትምህርት በእድሜ የማይገደብ የሕይወት ምግብ ነዉ " ሲሉ አስተያየታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአቶ ማኖ ማገሶን ፅናታቸውን እያደነቀ መልካም ፈተና እንዲሆንላቸው ይመኛል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
" ወደ 80 ሚሊዮን ብር የሚመት ንብረት ነው በታጣቂዎቹ የወደመው። ይሄ ለፋብሪካችን ቀላል ሀብት አይደለም " - ፊንጫ ስኳር ፋብሪካ
" ታግተው የነበሩ 17 ሠራተኞች ተለቀዋል ! "
በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን ሱሉለ ፊንጫ ወረዳ ታጣቂዎች የፋብሪካውን ሠራተኞች አታግተው ወስደው እንደነበርና በተሽከርካሪዎቹ ላይ ቃጠሎ እንዳደረሱበት ፊንጫ ስኳር ፋብሪካ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ታጣቂዎች በፋብሪካው ፈጸሙት ስለተባለው እገታ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ ኃይለማርያም፣ " 17 ሰዎች ትላንትና ማታ ተለቀው ወደ ቤተሰባቸው ገብተዋል። ጥቃቱ ትክክል ነው ተፈጽሟል። ሥራ ቦታ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ናቸው አግተው የወሰዷቸው" ሲሉ ነግረውናል።
" በአንድ ሎደር እና ሀይሉክስ ቶዮታ ተሽከርካሪዎች ነው ውድመት የደረሰው " ያሉ ሲሆን፣ ታጣቂዎቹ የእገታ ጥቃቱና የንብረት ውድመቱ ያደረሱት ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ መሆኑ ተመልክቷል።
የንብረት ውድመቱ በገንዘብ ሲተመን ምን ያክል እንደሆነ ላቀረብንላቸው ጥያቄ አቶ መንግስቱ፣ " ወደ 80 ሚሊዮን ብር የሚመት ንብረት ነው በታጣቂዎቹ የወደመው። ይሄ ደግሞ ለፋብሪካችን ቀላል ሀብት አይደለም " ሲሉም የጉዳቱን ክብደት አጽንኦት ሰጥተውበታል።
" የሚያሳዝን ነገር ነው። ድርጅቱ በደንብ ወደ ሥራ ተመልሶ እየሰራ ባለበት ወቅት ባልተጠበቀ ሁኔታ ነው ይሄ ጉዳት የደረሰው " ሲሉም ሁነቱን አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ታጋቾቹን በምን መልኩ ነው ከእገታ ማስለቀቅ የተቻለው? አጋቾቹ ከፍተኛ ገንዘብ እየጠየቁ እንደነበር ተሰምቷል፤ ሠራኞቹ የተለቀቁት ገንዘብ ተከፍሎ ነው ? ሲል ሥራ አስኪያጁን ጠይቋል።
እሳቸውም፣ " የኛም ሠራተኞች ሥራ ላይ ነበሩ፤ ጉዳቱ እንደተሰማ የጸጥታ አካላት ከፍተኛ ርብርብ አድርገዋል። የፌደራል ፓሊስና ኮማንዶ ኃይልም ሰፊ ርብርብ አድርገው በሄዱበት ቦታ ሂዶ ሰዎቹን ለማዳን ተሳትፈው ነበር በእለቱ ግን ማግኘት አልቻሉም " ሲሉ መልስ ሰጥተዋል።
" በማግስቱ የመከላከያ ኃይልም ተጨምሮ ሰፊ የሆነ ውይይትና ሰፊ አሰሳም አድርጓል። ግን ታጋቾቹ በራሳቸው ጊዜ ተለቀዋል የሚል መረጃ ስላገኘን የፋብሪካው አመራሮች ሰዎቹ አለን ካሉበት ቦታ ላይ ሂደው በመኪና ይዘዋቸው መጥተዋል " ሲሉም አክለዋል።
የገንዘብ ጥያቄውን በተመለከተ በሰጡን ምላሽ ደግሞ፣ " እሱን ማጣራት ይፈልጋል። እኔም እንዲህ አይነት መረጃ ሰምቼ ነበር፤ ግን ሰዎቹ ድንጋጤ ላይ ስለነበሩ እንኳን ደኀና ገባችሁ ከማለት ውጪ እንደከፈሉና እንዳልከፈሉ መጠየቅ/ማረጋገጥ አልተቻለም " ብለዋል።
" በድርጅቱ ሀብት ጉዳት የሚያደርሱ፣ አገዳን የሚያቃጥሉ ኃይሎችን ህዝቡ ከራሱ ነጥሎ ማውጣት አለበት። ሰላም ሆኗል ብለን ተስፋ ስናደርግ ችግር ያጋጥማል። ከህዝቡ ውስጥ ሆኖ መሳሪያ ታጥቆ ብቅ ጥልቅ እያለ የድርጅቱን ሀብት የሚያወድመውን ኃይል ተው ሊል ይገባል " ሲሉም ማህበረሱ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲወጣ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት
የሁለት ወር የክረምት ስልጠናዎች ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ይጀመራሉ።
የስልጠናዎቹ ዓይነት:
👉 Modern Accountancy (ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ)
👉 Import and Export
👉 Mern Stack Website and Mobile Application Development
👉 Computer Programming and Database
👉 Advanced Graphic Design, Video Editing, Motion Graphic and Digital Marketing
👉 Art (Film Acting, Writing and Modeling)
👉 Painting, Drawing and Sculpture
👉 Journalism
👉 Interior Design
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram
sage_training_institute">Tiktok
Linkedin
24 ሰዓታት ቀሩት!
ዛሬ-የዕድል ትኬትዎን ይግዙ-ነገ ይሽለሙ!
ባለ 3 እና ባለ 2 መኝታ መኖሪያ ቤቶች በተጨማሪ ለዓመታት ከሚቆዩ የገንዘብ ሽልማት ጋር!
ቮልስዋገን ID 6 እና BYD–SUV መኪናዎች በተጨማሪ ለዓመታት ከሚቆዩ የገንዘብ ሽልማት ጋር!
ሌሎችም በርካታ ሽልማቶች እርስዎን ይጠብቃሉ፡፡
እንዳያመልጥዎ! ዕጣው ነገ ይወጣል!
ነገ እሁድ የሚወጣውን ቶምቦላ በ ethiolottery.et ላይ እና በቴሌ ብር ሱፐር አፕ አሁኑኑ ይግዙ!
ለበለጠ መረጃ በ +251977717272፣
+251950189808 እና
+251950199808 ይደውሉ!
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት!
#Ethiopia🇪🇹
በግለሰቦች፣ በብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች መካከል " ስጋት፣ ግጭትን፣ ጥርጣሬን እና አለመተማመንን የሚፈጥር ድርጊት ፈጽሟል " ያለውን የፖለቲካ ፓርቲ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከምዝገባ እንዲሰርዝ ስልጣን የሚሰጥ የአዋጅ ማሻሻያ ለፓርላማ ቀረበ።
ቦርዱ የሌላ ፖለቲካ ፓርቲን " ህጋዊ እና ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ያደናቀፈ " የፖለቲካ ፓርቲ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ የመውሰድ ስልጣንም በአዋጅ ማሻሻያው ተሰጥቶታል።
ላለፉት አምስት ዓመታት በስራ ላይ የቆየውን " የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነምግባር አዋጅ " ያሻሻለው የህግ ረቂቅ ለፓርላማ ቀርቧል።
ዛሬ በአዋጅ ማሻሻያው ላይ የፓርላማ አባላት መታየት ያለባቸውን ጉዳዮች በጥቂቱ ካቀረቡ በኋላ በዝርዝር እንዲታይ ለምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርተውታል።
ያለምንም ተቃውሞ እና ድምጸ ተዐቅቦ ለቋሚ ኮሚቴ የተመራው ይህ የአዋጅ ማሻሻያ ከተዘጋጀባቸው ምክንያቶች አንዱ፤ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስፈጸመው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት የተስተዋሉ " የህግ ክፍተቶች " እንደሆነ የህግ ረቂቁን ለማብራራት በቀረበ ሰነድ ላይ ተጠቅሷል።
በዝርዝር ያንብቡ : https://ethiopiainsider.com/2025/16239/
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገጽ ነው።
@tikvahethiopia
“ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአየር ትራንስፓርት ትኬት ከኔ ብቻ ካልገዛችሁ በማለቱ የጉዞ መስተጓጎል እየፈጠረነብን ነው” - የውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት ኤጀንሲዎች
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በቅርቡ በጀመረው አሰራር መሠረት በሕጋዊ መንገድ ወደ ውጩ ሀገር ለሥራ ለሚሄዱ ተጓዦች በግዴታ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የጉዞ ትኬት ካልገዛችሁ ለጉዞ የሚያስፈልጋቸው የማለፊያ ኪው አር ኮድ እንደማይሰጣቸውና ጉዟቸውን እንደማያጸድቅ መወሰኑን በውጪ ሀገር የሥሪ ስምራት የተሰማሩ ኤጀንሲዎች ተቃወሙ።
"የአየር ትራንስፓርት ትኬት ከኔ ብቻ ካልገዛችሁ በማለቱ የህጋዊ የጉዞ መስተጓጎል እየፈጠረብን ነው" ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ "ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰሞኑን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካዘጋጀው አወዛጋቢ ረቂቅ አዋጅ ጎን ለጎን ሰሞኑን ህጋዊ ኤጀንሲዎችን በተለያየ መንገድ ለምን ማዋከብና አሰራሮችን መለዋወጥ እንዳስፈለገው ግራ አጋብቶናል" ብለዋል።
የውሳኔውን ጉዳት ሲያስረዱም፣ "ከዚህ በፊት ስንገዛበት ከነበረው ትኬት ዋጋ እስከ 25 ሺሕ ብር ጭማሪ በሲስተሙ አለ፤ በቃ መቁረጥ የምትችለው በዛ ብቻ ነው" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
“ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተቋቋመለት ዋነኛ አላማ አንፃር ወደ ውጪ የጉዞ ትኬት ሽያጭ ውስጥ ከመግባቱ በተጨማሪ ዜጎች በፈለጉት ህጋዊ ቦታ ትኬት ገዝተው የመጓዝ መብታቸውን የሚገድብና የነጻ ገበያ መርህን በግልጽ የሚጣረስ ነው" ሲሉም ተቃውመዋል።
ቅሬታ አቅራቢዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ?
“ዋጋው እጅግ በጣም ንሮብናል፤ መናሩ ብቻ አይደለም፤ ከዚህ በፊት ትኬት ስንቆርጥ ብር ስለማናገኝ ከትኬት ኦፊሶች በብድር ነበር የምንቆርጠው፡፡ አሁን ግን ዋጋውም ጨምሮ ካሽ ብቻ ነው የምንቆርጠው፤ ይሄ ራሱ ሌላ የራስ ምታት ነው ለኛ፡፡
ገና ገንዘብ ባልተቀበልነው ሰው ላይ ነው እንድንከፍል እያስገደዱን ያሉት፡፡ ከትላንት ወዲያ የጸደቀ አዋጅ አለ፤ ግን ይሄን ነገር አዲሱ አዋጅም የድሮውም አያውቀውም ሙሉ ለሙሉ ከሕግ ውጪ ነው፡፡ በሕግ ያልተሰጠው ሥራ ውስጥ መግባቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጭ ርቆ ሲሄድ ዋና ሥራውን መዘንጋት ይጀመራል፡፡
በአዋጅ የተሰጠውን የሠራተኞችን መብት የሚከታተል ሌቨር አታች ያልመደበ መስሪያ ቤት ነው ትኬት ካልቆረጥኩ ብሎ እየተሟሟተ ያለው፡፡ በሌላ በኩል ቢያንስ ተጨማሪ 60 ዶላር ትከፍላላችሁ እየተባልን ነው፡፡ ለማን ነው የምንከፍለው? ሲሉ ጠይቀዋል።
ታዲያ መፍትሄ ምንድን ነው ትላላችሁ?
“ባጭሩ ሲስተም ላይ ትኬት መቁረጥ የሚለው ነገር አስገዳጅ መሆኑ መቆም አለበት፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መሠረታዊ የሆነ ሥራ ሰርቶ ጨርሷል ብለን አናምንም፡፡ መሆን ካለበት የራሱን መሠረታዊ ሥራ ይስራ፡፡ ግን ትኬት እኔ ጋር መቆረጥ አለበት ካለ ኦፕሽናል ነው መሆን ያለበት፡፡ ኦፕሽናሊ ያስቀምጠው አወዳድረን ጥሩ ነገር ካገኘን እንሄዳለን፡፡
ግዴታ ግን ትኬት ካልቆረጣችሁ የሠራተኞች መውጫ ኪው አር አልሰጣችሁም ማለት ከጀመረ በጣም አሳሳቢ ነው፡፡ መንግስት አስተዳዳር ነው እንጅ ንግድ ውስጥ አይገባም። ግን መስራት አለበት፤ ትኬት ቆረጣ መግባት አለበት ካሉ ኦፕሽናል በሆነ መልኩ ነው እንጅ ግዴታ በመስሪያ ቤቱ ካቆረጣችሁ መውጫ አንስጥም የሚሉ ከሆነ በጣም አደገኛ ነው” ብለዋል።
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ምላሽ የሚጠይቅ ይሆናል)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ዋሪት ፈርኒቸር
የፋይበር ትራሶች የመተንፈስ አቅም እና የአከርካሪ አጥንት ማስተካከልን
እና ማንኮራፋትን የመቀነስ አቅም አላቸው::
እንግዲያውስ በአንድ ቦታ ምቾት፣ ጤና እና ምርታማ ወደሚሆኑበት
ወደ ማሳያ ክፍሎቻችን በመምጣት ይጎብኙን !
* 22 - ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ - ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ - ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* አዳማ - ሶረቲ ሞል
* ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት
*ወሎ ሰፈር- Ethiolife life real estate
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ!
ለተጨማሪ መረጃ: 0911210706 / 07
https://web.facebook.com/WARYTZE
https://www.instagram.com/warytfurniture
/channel/warytfurniture
warytzefurniture" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@warytzefurniture