1575600
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። መረጃ እና መልዕክት ፦ 0998999899 ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም 0979333111 @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ
የነዳጅ ዋጋ ጨምሯል ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዳጅ ዋጋ መጨመሩን ተዘዋውሮ ባደረገው ቅኝት አረጋግጧል።
ነጭ ናፍጣ በሊትር 163.09 ብር ገብቷል። ቤንዚንም በሊትር 142.41 ብር ሆኗል።
ከዛሬ መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ መደረጉን ማደያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ደብዳቤ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋን መሰረት በማድረግ ከመጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሬ መደረጉን ያስረዳል።
በደብዳቤው በተገለጸው መሰረት በሊትር፦
- ነጭ ናፍጣ 163.09 ብር
- ቤንዚን 142.41 ብር
- ኬሮሲን 151.39 ብር
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ 163.98 ብር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ 160.68 ብር
- የአውሮፕላን ነዳጅ 150.48 ብር ሆኗል።
በተጨማሪም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ከመሸ ሳሪስ አካባቢ ባሉ ማደያዎች ቅኝት ያደረገ ሲሆን፣ ማደያዎቹ ሽያጭ እያከናወኑ ያሉት በተሻሻለው ዋጋ መሰረት ነው።
የማደያዎቹ ሠራተኞች ቤንዚን 142.41 ብር፣ ነጭ ናፍጣ 163.09 ብር እየሸጡ፣ ሹፌሮችም በዚሁ መሰረት እየቀዱ መሆኑን አረጋግጠዋል።
መንግሥት በመጋቢት ወር የዋጋ ጭማሪ ያደረገው ከዛሬ 22 ቀን በፊት ነበር።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ/ም
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ከዛሬ መጋቢት 21 ጀምሮ የእጅ ስልክን በመደበኛ የሥራ ሰዓት መጠቀም ተከልክሏል " - ቢሮው
➡️ " ባለሙያዎች የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም የግብር ከፋዩ ጊዜ እንዲቃጠል የማድረግ ሁኔታ አለ ! "
የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ፣ ለሠራተኞቹ "ከዛሬ መጋቢት 21/2018 ዓ/ም ጀምሮ የእጅ ስልክን በመደበኛ የሥራ ሰዓት መጠቀም ተከልክሏል" ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የቢሮው የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ፣ " ሠራተኞች መደበኛ የሥራ ሰዓታቸውን ሲጀምሩ በተዘጋጀው ሎከር ስልኮቹን ማስቀመጥ፣ በየሥራ ክፍሉ ላሉ ዳይሬክተሮች ሰጥቶ ወደ ሥራ መግባት አለባቸው " ሲሉ ነግረውናል።
ለሥራ ስልክ መጠቀም ያለባቸው ግን ተለይተው እንደሚጠቀሙም ገልጸዋል።
ግብር ከፋዮች ከሚያሷቸው ቅሬታዎች መካከል አንዱ " ከስልክ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ ያለ ችግር " መሆኑን ጠቅሰው፣ በተለይ ግብር ከፋዩ አገልግሎት ለማግኘት በሚሄድበት ጊዜ " አንዳንድ ባለሙያዎች የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም የግብር ከፋዩ ጊዜ እንዲቃጠል የማድረግ ሁኔታ አለ " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በዚህ ጉዳይ " 7 ሺሕ ከሚደርሱ ሠራተኞች ጋር የጋራ መግባባት" ላይ የደረሱበት ነገር "በተለይ በመደበኛ የሥራ ሰዓት የእጅ ስልክን ከመጠቀም" እንዲቆጠብ መሆኑን በመግለጽ፣ ዓላማውም " የግብር ከፋዩን እርካታ ማረጋገጥ ነው " ብለዋል።
በእርግጥ ሠራተኛ የሥራ ሰዓትን በአግባቡ የመጠቀም ኃላፊነት አለበት፤ ግን በሥራ ሰዓት " አትጠቀሙ " ብሎ ህግ ማውጣት እንጅ እንዲሁ መከልከሉ መብትን መጋፋት አይሆንም ? በሚል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቅናቸው አቶ ሰውነት፣ " ከህግ ጋር የሚገናኝ ነገር የለም። ስልክ መጠቀም ከተፈለገ በየቅርንጫፉ መደበኛ ስልኮች አሉ መጠቀም ይቻላል " ሲሉ መልሰዋል።
" የግል ስልካቸውንም ቢሆን ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጭ (ለምሳሌ በምሳ ሰዓት ከ6 እስከ 7 ሰዓት ተኩል፣ በሻይ እረፍት፣ የግብር ከፋዩን አገልግሎት አሰጣጥ በማይሻማ መንገድ መጠቀም የሚቻልበት ሁኔታ አለ" ሲሉ አክለው፣ "ከመብት ጋር የሚያያይዘው ነገር ይኖራል ብየ አላምንም" ነው ያሉት።
የቢሮ መደበኛ ስልኮችን ለመደበኛ ግንኙነትም መጠቀም እንደሚቻል አስረድተዋል።
ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ፣ " ስልክ የመጎርጎር፣ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የመጣድ " እና መሰል ችግሮች መስተዋላቸውን አውስተው፣ በዋነኛነት ከባለጉዳዮች ጋር ፊት ለፊት ያሉ እና ከዚህ ጋር የተያያዙ ሠራተኞች ሥራቸው ላይ ትኩረት አድርገው ለግብር ከፋዩ ተገቢውን ክብር ሰጥተው ማገልግል ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
ለዚህ ውሳኔ ያደረሷቸው ችግሮችን ምንነት ስንጠቃቸው፣ " ከባለሙያዎች ስነምግባር፣ ከሰዓት አጠቃቀም ጋር ተያይዞ በግብር ከፋዮች የሚነሱ ችግሮች አሉ " ብለው፣ ችግሮቹን ለመቅረፍ " 24 የሚደርሱ አሰራሮች ተለይተው ወደ ተግባር ተሸጋግረዋል" ሲሉ አስረድተዋል።
" ከምሰጣቸው 23 ከሚደርሱት አገልግሎቶች አሁን ላይ 22 የሚደርሱት በቴክኖሎጂ እንዲደገፉ ለማድረግ ጥረት እያደረግን ነው " ያሉት አቶ ሰውነት፣ " በዚህም ግብር ከፋዩ በቤቱ ሆኖ አገልግሎት ማግኘት የሚችልበት ሁኔታ ለመፍጠር ጥረት እየተደረገ ነው" ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" የወረዳ ተሳታፊዎች ላይገኙ ይችሉ ይሆናል " - ምክትል ኮሚሽነር ሂሩት ገብረሥላሴ
⚫ " አይገኙም ሊባል የሚችልበት አግባብ የለም " - ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ፣ በትግራይ ክልል ማስኬድ ባለመቻሉ፣ የትግራይ ክልልን አጀንዳ ለማሰባሰብ የተሳታፊዎች ልየታ ከመጋቢት 23 እስከ 25/2018 ዓ/ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ገልጾ የወረዳ " ተሳታፊዎች ላይገኙ ይችሉ ይሆናል " በሚል ስጋቱን አሳውቋል።
የኮሚሽኑ ም/ኮሚሽነር ሂሩት ገብረሥላሴ፣ " በቀጥታ ማግኘት ያልቻልነው ወረዳ ተሳታፊዎችን ነው። ባለድርሻ አካላትን በተለያየ ጊዜ ስብሰባ አዲስ አበባም ይሁን መቐለ አግኝተናቸዋል " ብለዋል።
በትግራይ ክልል " ወደ 22 ኢንጌጅመንቶች " እንደዳደረጉ ገልጸው፣ " በኛ ግምት መደረግ የነበረባቸው ጥረቶች በሙሉ ተደርገዋል፤ ስራዎች ተሰርተዋል፤ ስብሰባዎች አድርገናል " ሲሉም ተደምጠዋል።
" ምንም ሥራ እንዳልተሰራ መቁጠር አይገባም ፤ ከፍ ያሉ ሥራዎች ተሰርተዋል " ያሉት ም/ኮሚሽነሯ፣ ኮሚሽኑ አሁንም በመጨረሻ ባደረገው ጥሪ የትግራይን ጉዳይ የሚያቀርቡ ተሳታፊዎች ይገኛሉ ብሎ እንደሚያምን ተናግረዋል።
" በአዲስ አበባም ይሁን በኢትዮጵያ ከትግራይ፥ የትግራይ ተወላጆችን ለማግኘት የሚደረግ ጥረት ነው። በዚህ አማካኝነት ድንገት የወረዳ ተሳታፊዎች ላይገኙ ይችሉ ይሆናል እንጂ ባለድርሻ አካላት መጥተው የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ እናምናለን " ነው ያሉት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የወረዳ ተሳታፊዎች በአጀንዳ ልየታ ላይገኙ እንደሚችሉ በስጋት ጠቅሳችኋል፤ አለመገኘታቸው ምን አሉታዊ ተፅዕኖ አለው ? ሲል የኮሚሽኑን ኮሚሽነር መላኩ ወ/ማርያምን ምላሽ ጠይቋል።
ኮሚሽነሩም፣ " አይገኙም ሊባል የሚችልበት አግባብ የለም። ምክንያቱም በክልሉ ለሚገኙ የወረዳ ማህበረሰብ ክፍሎች ሁሉ ተሳታፊዎቻቸውን እንዲልኩ የመጥሪያ ደብዳቤ ተልኳል " ሲሉ መልሰዋል።
" የጥሪው ወረቀት በጊዜያዊ አስተዳደሩ ጽሕፈት ቤት በኩል ለሁሉም ወረዳዎች እንዲደርሳቸው ተልኳል። 'አይገኙም' መባሉ ግምት ነው። ምናልባት ላይመጡ ይችሉ እንደሆነ በሚል ነው እንጅ በእርግጠኝነት አይመጡም ብሎ መደምደም አይቻልም" ሲሉ አክለዋል።
አዲስ አበባ በሚካሄደው የትግራይ ክልል ተሳታፊዎች ልየታ ወደ 400 ተሳታፊዎች ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ገልጻችኋል፤ ለሌሎች በፈቃዳቸው መሳተፍ ለሚፈልጉስ ክፍት ነው ? የሚል ጥያቄም፣ ለኮሚሽነሩ አቅርበናል።
ኮሚሽነር መላኩ በምላሻቸው፣ " በአንድ በይነ መረብ ላይ እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርበናል። እስካሁን 65 ሰዎች በፈቃደኝነት ተመዝግበዋል " ብለዋል።
የትግራይ ተወላጆች የሆኑ " በዚህ ሂደት ብንሳተፍ አስተዋጽኦ ልናደርግ እንችላለን " ብለው በራሳቸው እምነት ላሳደሩ ሰዎች እንዲመዘገቡ ጥሪ ማቅረባቸውን ገልጸው፣ " ምዝገባው ይቀጥላል። መቼ እንደሚያልቅ ግን እርግጠኛ አይደለሁም " ሲሉም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በተያያዘ፣ የትግራይ ክልልን አጀንዳ ለማሳባሰብ በአዲስ አበባ የተሳታፊዎች ልየታ ሊደረግ መሆኑ በአጀንዳውን ላይ ልዩነት እንደማያመጣ ሲገልጹ፣ " አጀንዳ በመስጠት ረገድ መቐለም ተካሄደ አዲስ አበባ የትግራይ ህዝብ የሚሰጠውን አጀንዳ ምንም የሚለውጠው ነገር የለም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" እስረኞችን ማስፈታት የኛ ሥራ አይደለም " - ኮሚሽኑ
እስረኞች ባልተፈቱበት እንዴት አሳታፊ ምክክር ማድረግ ይቻላል ? በሚል እስረኞችን ለማስፈታት ጥረት እንዲያደረግ በተደጋጋሚ ሲጠየቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ " እስረኞችን ማስፈታት አይደለም የኛ ሥራ " አለ።
ኮሚሽኑ ይህን ያለው ለሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳ ልየታ ያልተደረገበት ብቸውን የትግራይ ክልል የአጀንዳ ልየታ ከመጋቢት 23 እስከ 25/2018 ዓ/ም በአዲስ አበባ ከተማ ለማካሄድ መገደዱን በተመለከተ ማብራሪያ ለሰጠበት ወቅት ነው።
ሀገራዊ ምክክሩን በሙሉነት ለማስኬድ መጀመሪያ የእስረኞች መፈታት ጉዳይ ከምን እንደደረሰ እንደሁልጊዜው ኮሚሽኑ ተጠይቆ የነበረ ሲሆን፣ ለዚሁ ጉዳይ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ሙሉጌታ አጎ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ኮሚሽነር ሙሉጌታ አጎ ምን አሉ ?
" እስረኞችን ማስፈታት አይደለም የኛ ሥራ። አጠቃላይ በዐዋጅ አንቀጽ 9 ላይ ኮሚሽኑ ምን ይሰራል? የሚለውን ያስቀመጠበት አግባብ አለ።
እንደዚያም ሆኖ ግን ለስራችን መሳካት፣ ያለአግባብ የታሰሩ ሰዎች ቢኖሩ ለመንግስት ማሳሰቢያ ሰጥቶ እንዲፈቱ የማያደርግ ጉዳይ ጥሩ ስራ ሊሆን ይችላል።
ግን ሁልጊዜ ሲነሳ የነበረው፥ እስር ቤት ያሉ ሰዎችን እንዴት አድርጋችሁ ነው ወደ ምክክር የምታመጡት? የሚለውን በተመለከተ፥ ፍርደኞች ሆነው ፍርድ አርፎባቸው የታሰሩ፤ የተለያዩ ወንጀሎችን በመፈጸም የታሰሩ እና ምርመራ ላይ ያሉ፤ በአጠቃላይ ደግሞ በህግ እና በስርዓት መሰረት የሚከሰሱ እና በመከሰስ ላይ ያሉ፤ ጉዳያቸው እየተመረመረ የሚፈቱ ሰዎች አሉ።
ስለዚህ በአጠቃላይ እስረኞችን ማስፈታት የሚባል ነገር ላይ ጥንቃቄ እንዲወሰድ ማድረግ ተገቢነት አለው።
በዋናነት እስረኞች ይፈቱ በምንልበት ጊዜ ወንጀል የፈጸሙ፣ በአጠቃላይ ሰው የገደሉ፣ በተለያዩ ምክንያት የታሰሩ ሰዎች እናስፈታለን ብንል ተመልሶ ደግሞ አገርን ወደማተራመስ ይገባል። ወንጀለኞች እንዲነግሱ የማድረግ ጉዳይ ሊኖር ስለሚችል ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል " ሲሉ ተደምጠዋል።
" የትኞቹ ናቸው የሚፈቱት ? የሚለውን ማሰብ አስፈላጊ ነው " የሚሉት ኮሚሽነር ሙሉጌታ፣ በጅምላ ሲነሳ የነበረው " ያለአግባብ የታሰሩ ሰዎችን የማስፈታት " ጉዳይ ብቻ መሆኑን ጠቅሰው፣ " በጅምላ እስረኞችን ማስፈታት የሚባል ጉዳይ ይነሳል፤ እሱን ለይቶ ማወቅ ያስፈልጋል " ብለዋል።
" በሀገር ደህንነት እና ሰላም ችግር የሚፈጥሩ ሰዎች ካሉ የማይጠየቁበት፣ የማይታሰሩበት ምክንያት አይኖርም " ሲሉም ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ም/ ፕሬዜዳንት አቶ አማኒኤል አሰፋ፣ የአገራዊ ምክክር ኮሚሽንና የምርጫ ቦርድን "የመንግስትን ስክሪፕት በማንበብ የትግራይን ህዝብ ሁኔታ አዛብተው እያቀረቡ ነው" ሲሉ ተቹ።
ኮሚሽኑ ከመጋቢት 23 እስከ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ለሚያካሂደው " የትግራይ አጀንዳ ማሰባሰብያ " መድረክ እውቅና አልሰጡም።
" መሰረታዊ ጥያቄዎች ማለትም የተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስና የግዛት አንድነት ፣ ራስን በራስ ማስተዳደር መሰረታ መብቶች ሳይመለሱ በስመ ምክክር በአዲስ አበባ የራሳችሁ ሰዎች በአደራሽ ሰብስባችሁ የምትፈልጉት በመስማት ' ትግራይ መከረች ' ብላችሁ ራሳችሁን ለማጽናናት ማቀዳችሁ በራሱ የምክክር ኮሚሽኑን መውደቅ ያሳያል " ብለዋል።
ኮሚሽኑ በትግራይ ያለው ሁኔታ አመቺ ባለመሆኑ ውይይቱን በአዲስ አበባ ለማድረግ መወሰኑንና 400 ተሳታፊዎች እንደሚገኙ አስታውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
እንስቷን በስለት በማስፈራራት በቡድን የደፈሩት 2 ግለሰቦች በ10 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጡ።
የወንጀል ድርጊቱ በትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ሕንጣሎ ወረዳ ሕዋነ ቀበሌ ነው የተፈፀመው።
ግለሰቦቹ ሀምሌ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ከስራ ወደ ቤት በመጓዝ የነበረችው ተበዳይ እንስት በማፈን እና በስለት በማስፈራራት የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈፅመዋል።
የወንጀል ድርጊቱ የፈፀሙት ግለሰቦች እጅ በፈንጅ ባለመያዛቸው ምክንያት የፓሊስ የምርመራ ሂደትና ፍርድ ለመስጠት ረጀም ጊዜ መውሰዱ ተገልጿል።
የወንጀል ድርጊቱ መፈፀማቸው በሰው ምስክርና ማስረጃ መረጋገጡ ተከትሎ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን ማእከላይ ፍርድ ዛሬ መጋቢት 18/2018 ዓ.ም ባዋለው ችሎት ሁለቱ ወንጀለኞች እያንዳንዳቸው በ10 ዓመት ፅኑ እስራት ቀጥቷል።
ተበዳይዋ ፍርድ ቤቱ የሰጠው ውሳኔ በማመስገን የተፈፀመባት የወንጀል ድርጊት ያስተባበረ ግለሰብ በህግ ቁጥጥር ስር ውሎ ነፃ መለቀቁ እንዳሳዘናት ገልፃለች።
ህግ ጉዳዩ መልሶ እንዲመረምረው ተማጽናለች።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከዞን ኮሚኒኬሽን ነው ያገኘው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ወደ 1,900 መርከቦች መሄጃ አጥተው ቆመዋል።
ከየካቲት 21/2018 ዓ/ም ጀምሮ አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ የሰነዘሩትን መጠነ ሰፊ ጥቃት ተከትሎ በዓለም የንግድ መስመር ላይ ከፍተኛ ቀውስ ተፈጥሯል።
በዚህም ምክንያት 1,900 የሚጠጉ የንግድ መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ እና በፋርስ ባህረ ሰላጤ አካባቢ መንቀሳቀስ አቅቷቸው ቆመዋል።
ቴህራን " ከጥቃት አድራሾቹ አገራት ጋር ንክኪ ያላቸው መርከቦች ወሳኝ በሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ እንዳያልፉ " በመዝጋቷ የባህር ላይ እንቅስቃሴው ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ሊቆም ችሏል።
መንቀሳቀሻ አጥተው ከቆሙት መርከቦች መካከል ፦
° የነዳጅ ጫኝ፣
° የኬሚካል እና የንግድ ዕቃዎች የያዙ ግዙፍ መርከቦች ይገኙበታል።
ይህም በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋና የአቅርቦት ሰንሰለት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል።
መረጃው የአናዱሉ ዜና ወኪል ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ ⚠
" ውጭ ሀገር እንልካችኋል " የሚሉ ህጋዊ ፈቃድ የሌላቸውን ዘራፊዎች ተጠንቀቁ።
በሀገራችን ወጣቱ ያለበትን የኑሮ ፈተና እንዲሁም ዜጎች አሁን ላይ ካለው የኑሮ ክብደት አንፃር ለራሳቸውና ለቤተሰባቸው ሲሉ በፍጥነት ገንዘብ ለማግኘት የሚያደርጉትን ከፍተኛ የህይወት ትግል እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ድሃውን ለመዝረፍ የተሰማሩ ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያው ላይ እንደ አሸን ፈልተዋል።
" ውጭ አገር እንልካለን " በሚሉ አጭበርባሪዎች ያላችሁን በላባችሁ ያገኛችሁርን ፣ ተበድራችሁ የመጣችሁትን እንዳታጡ ጥንቃቄ አድርጉ።
ያስተውሉ ፦
1. ንግድ ፍቃድና ቢሮ ስላላቸው ብቻ አትመኗቸው።
አንዳንዶቹ ለጥቂት ወራት ቢሮ ተከራይተውና የሰው ፍቃድ ወይም የራሳቸውን ፍቃድ ይዘው የብዙዎችን ገንዘብ ሰብስበው ይሰወራሉ። ስለሆነም የድርጅቶቹን ማንነት በደምብ #አጣሩ።
2. ገንዘብ በባንክም ቢሆን በጭራሽ እንዳታስገቡ። በካሽ እጅ በእጅ ስጡን ካሉ በፍጹም እንዳታምኗቸው።
" ቪዛ ተመትቷል" በሚል ማታለያ በባንክ አካውንታቸው ብር እንድታስገቡ ካደረጉ በኋላ ስልካቸውን ዘግተው የሚጠፉ አሉ። አልያም በካሽ እጅ በእጅ ስጡን ካሉ ገንዘባችሁን ይዘው ለመሰወር ብቻ ነው።
በሕጋዊ መንገድ ሳትሄዱ ምንም ክፍያ አትፈጽሙ።
3. የቲክቶክ፣ በፌስቡክ ፣ ቴሌግራም ወይም ሌሎች ሚዲያዎች ላይ የሚተላለፉ የተጋነኑ ማስታወቂያዎችን አትመኑ።
• " በአጭር ቀን እንልካችኋለን " ፣
• " ያለ ስልጠና እንልካችኋለን " ፣
• " ያለ ምንም ትምህርት እና ክህሎት ትሄዳላችሁ "
• " ከፍተኛ ደመወዝ ታገኛላችሁ " የሚሉ ማባበያዎች የሌቦች ወጥመድ ናቸው።
4. ታዋቂ ሰዎችን ታዋቂ ብቻ ስለሆኑ አትመኑ። እነሱ አሉ ማለት ብቻ እውነት ነው ማለት አይደለም።
አርቲስቶች ወይም ታዋቂ ሰዎች ስለተከፈላቸው ብቻ ማስታወቂያ ሊሰሩ ይችላሉ፤ የእነሱ መኖር የድርጅቱን ታማኝነት አያረጋግጥም። ስለዚህ ስለ ድርጅቱ በደምብ አጣሩ።
5. ዋና ፓስፖርታችሁን አሳልፋችሁ አትስጡ።
" ቪዛ ለማስመታት " ወይም " ሂደት ለመጀመር " በሚል ሰበብ ዋና ፓስፖርታችሁን ተቀብለው ለወራት ሊያንገላቷችሁ እና ሊያስፈራሯችሁ ይችላሉ። የፓስፖርት ፎቶ ኮፒ ብቻ መስጠት ይበቃል፤ ዋናው ፓስፖርት ጉዞው ተረጋግጦ አሻራ እስኪሰጥ ድረስ በእጅዎ መቆየት አለበት።
⚫ ማንኛውንም ክፍያ ከመፈጸማችሁ በፊት ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወይም በአቅራቢያዎ በሚገኝ የሥራ ስምሪት ቢሮ በመሄድ የድርጅቱን ትክክለኛነት አረጋግጡ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
የማህበራዊ ሚዲያ ኮንተንት ክሪኤተር ነዎት?
ከዩቲዩብ እና ከሌሎች ማህበራዊ ሚዲያ መተግበሪያዎች የሚላክልዎ የማረጋገጫ ደብዳቤ፣ የክፍያ ማስታወቂያ ወይም ሌሎች አስፈላጊ ሰነዶች ለመቀበል አስበዋል ?
እንግዲያዉስ የኢትዮጵያ ፖስታ ዘመናዊ መፍትሄ የሆነዉን የ“Virtual P.O. Box” (ሳጥን አልባ የመልዕክት አገልግሎት) ይዞሎት መቷዋል፡፡
🔹 የተረጋገጠ እና ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት
🔹 መልዕክቶችዎን በማንኛውም ቦታ እና በማንኛውም ሰዓት ማግኘት የሚያስችልዎ
🔹 ፈጣን ማሳወቂያ እና ቀላል አስተዳደር
📱 ዛሬውኑ መተግበሪያውን ከአፕስቶር ወይም ከፕሌይ ስቶር "VIRTUAL POST" ብለው በማውረድ
አልያም 👉በ app.ethio.post በመግባት በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ይመዝገቡ። — አንድም አስፈላጊ መልዕክት እንዳይዘገይ!
ለበለጠ መረጃ በነጻ የስልክ መስመር 8536 ይደውሉልን ወይም በቴሌግራም @etpccsbot ያግኙን።
#Ethiopost #virtual po box
Follow us on our social media platforms
Facebook | Telegram | LinkedIn | Twitter | Instagram | Pinterest (Philately) | ethiopostal">TikTok |
#አለርት_ኮፕሬንሲቭ_ስፔሻላይዝድ_ሆስፒታል 👏
ከአሰቃቂ የጅብ ጥቃት መትረፍ የተቀናጀ የህክምና እርዳታ ውጤት !
አንድ ህጻን በጅብ ጥቃት ምክንያት በደረሰበት ከፍተኛ የፊት አካል ጉዳት ምክንያት ወደ አለርት ኮፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከክልል በሪፈር ይላካል።
በጥቃቱ ምክንያት ህጻኑ ሁለቱንም ዓይኖቹን ያጣ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ማየት አይችልም። ከዚህ በተጨማሪ በዓይን አካባቢ፣ በግንባር እና በሁለቱ ጉንጮች ላይ ያለው ቆዳ በጣም ተጎድቶ ነበር። የላይኛው መንጋጋ (maxilla) ከፊል ጠፍቶ የቀሩት አጥንቶች ደግሞ ተሰባብረው ነበር።
ህጻኑ ወዲያውኑ ወደ ህጻናት ጽኑ ህክምና ክፍል (PICU) በመግባት የህይወት አድን ህክምና ተደርጓል። እንዲተነፍስ በአንገቱ በኩል ቀዳዳ በመክፈት (Tracheostomy) ተደርጓል።
በቀጣዮቹ ቀናት የቀዶ ጥገና ቡድኑ ኢንፌክሽንን ለመከላከል እና የሞቱ ቲሹዎችን ለማስወገድ ተከታታይ የጽዳት ሂደቶች (debridement) አከናውኗል።
ቁስሉ ለተሃድሶ ቀዶ ህክምና ዝግጁ ከሆነ በኋላ የፊት ተሃድሶ ስራዎች ተጀምረዋል ፦
1. የቆዳና ቲሹ ንቅለ ተከላ (Free Tissue Transfer)
የፕላስቲክ እና ተሃድሶ ቀዶ ጥገና ባለሙያዎች ከህጻኑ ጭን ላይ 7 ሴ.ሜ x 17 ሴ.ሜ መጠን ያለው ቆዳና ስጋ ከነ ደም ስሩ በመውሰድ ወደ ፊት ተተክሏል። ይህም በጥቃቅን የደም ስር ቀዶ ጥገና (Microsurgery) ቴክኒክ ከፊት ያሉ የደም ስሮች ጋር ተገናኝቶ ተሰርቷል።
2. የአጥንት ተሃድሶ ህክምና
የተሰባበሩት የመንጋጋ አጥንቶች ተስተካክለው የፊት ቅርጽ እንዲመለስ በታይታኒየም ፕሌት እና ስክሩ ተደግፈዋል።
እስካሁን ድረስ ህጻኑ ቢያንስ 8 ቀዶ ጥገናዎችን ያከናወነ ሲሆን፣ በቀጣይም ተጨማሪ የፊት ተሃድሶ ስራዎች ይፈልጋሉ። በአሁኑ ወቅት ህጻኑ በመሻሻል ላይ ይገኛል።
ይህ ክስተት የተቀናጀ የህክምና ቡድን (Multidisciplinary Team Approach) ያለውን ትልቅ ፋይዳ እንደሚያሳይ ተገልጿል።
የህጻናት ሐኪሞች፣ የጽኑ ህክምና ባለሙያዎች፣ የጠቅላላ ቀዶ ጥገና እና የፕላስቲክ እና ተሃድሶ ቀዶ ጥገና ስፔሻሊስቶች በተቀናጀ መልኩ በመስራት የህጻኑን ህይወት ለማዳን እና የፊቱን ቅርጽ ለመመለስ ተግተዋል።
ነገር ግን ይህ አደጋ ብቸኛው አይደለም፤ በአሁኑ ጊዜ በተመሳሳይ የጅብ ጥቃት ጉዳት የደረሰበት ሌላ ህጻን በሆስፒታሉ ተጨማሪ ቀዶ ህክምና በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
ህፃናትን ከጅብ ጥቃት ለመጠበቅ ማህበረሰቡ ህፃናትን ብቻቸውን ባለመተው፣ ንቁ እንክብካቤ በማድረግ እና የመከላከያ እርምጃዎች መውሰድ እጅግ አስፈላጊ ነው።
የተሃድሶ ቀዶ ጥገና (Reconstructive Microsurgery) የጠፋውን መልክና ተግባር ሊመልስ ቢችልም፣ ከሁሉ በላይ ግን አደጋን ከመጀመሪያው መከላከል ነው ዋናው መፍትሄ።
በቀዶ ጥገናው የተሳተፉ ባለሙያዎች፦
• ዶ/ር አብዱረዛቅ አሊ – የፕላስቲክ፣ ሪኮንስትራክቲቭ እና ማይክሮሰርጅን (መሪ ሀኪም)
• ዶ/ር አታክልቲ ባራኪ – የፕላስቲክ፣ ሪኮንስትራክቲቭ እና የእጅ ቀዶ ጥገና ሀኪም
• ዶ/ር ዘቢባ መካ – የፕላስቲክ ሪኮንስትራክቲቭ ሀኪም
• ዶ/ር ተስፋሁን አሊ – ሬዚደንት
• ዶ/ር ዮሃንስ ኤሊያስ – ፌሎው
• ሲራጅ ሙሼ – ማደንዝዣ ባለሙያ
• ናትናኤል ብርሃኑ – ነርስ
• ጫልቱ ተገኔ – ነርስ
• አለሙ ቦጋለ – ነርስ
• ኪሩቤል እሸቱ – ፖርተር
• አባይነው ሰውነት – ፖርተር
• ዘቢደር ፈንቴ – ጽዳት
• እና ሌሎች በርካታ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
(አለርት ኮፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል)
@tikvahethiopia
#Update
ፕሬዝዳንት ትራምፕ 15 ነጥቦችን የያዘ ዕቅድ ለኢራን መላካቸው ሲዘገብ ፤ ኢራን በበኩሏ " ጦርነቱ የሚያበቃው እራሴ ስወስን እና የራሴ ቅድመ ሁኔታዎች ሲሟሉ ብቻ ነው " የሚል መልስ ሰጥታለች።
ዛሬ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ትልቅ መነጋገሪያ የሆነው የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱ እንዲያበቃ 15 ነጥቦችን የያዘ ዕቅድ ለኢራን መላካቸው ነው።
የስምምነት ነጥቦቹ ይፋ አልወጡም።
ቻናል 12 የተባለው የእስራኤል የቴሌቪዥን ጣቢያ ግን በትራምፕ ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ናቸው ያላቸውን የሚከተሉትን ነጥቦች አስቀምጧል፦
- በናታንዝ፣ ኢስፋሃንና ፎርዶ የሚገኙ የኒውክሌር ተቋማት ሥራ እንዲያቆሙ እና እንዲወድሙ እንዲደረጉ
- በኢራን ውስጥ የሚከናወኑ የኒውክሌር መረሃ ግብሮች ግልጽ እና ዓለም አቀፍ ቁጥጥር እንዲደረግባቸው
- ኢራን በቀጣናው ያሉ ታጣቂ ቡድኖችን መርዳት እና ማስታጠቅ እንድታቆም
- የተከማቹ የኒውክሌር ቁሶችን በሙሉ ማውደም
- ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት ለመሆን ፈጽሞ ላለመሞከር ቃል እንድትገባ
- ምንም ዓይነት የኒውክሌር ቁስ በኢራን ውስጥ እንዳይዳብር፣ የዳበሩትም ለዓለም አቀፉ ተቋም እንዲሰጡ
- የሆርሙዝ ወሽመጥ ክፍት እንዲሆን እና " ነጻ የባሕር ቀጣና " እንዲሆን ማድረግ
- የኢራን ሚሳዔል በመጠን እና በሚደርስበት ርቀት ውስን እንዲሆን እና እራስን ለመከላከል ላይ ብቻ እንዲውል
በዚህ ዕቅድ ውስጥ ኢራን የሚከተሉትን ድጋፎች ከስምምነቱ የምታገኝ ይሆናል፦
• ኢራን ቡሽሄር ውስጥ ለኤሌክትሪክ ማመንጫነት ለምታካሂደው የኒውክሌር ግንባታ አሜሪካ ድጋፍ ታደርጋለች።
• በኢራን ላይ የተጣሉ ሁሉም ማዕቀቦች እንዲነሱ ይደረጋሉ
አዲስ ሊጣሉባት የሚችሉ ማዕቀቦች ይቀራሉ።
• በተጨማሪም በሁለቱ ወገኖች መካከል ድርድር በሚደረግበት ጊዜ ለአንድ ወር የሚቆይ የተኩስ አቁም ይኖራል ተብሏል።
ነገር ግን ከዋይት ሐውስ አስካሁን ምንም ዓይነት ዝርዝርም ሆነ ማረጋገጫ አልተሰጠም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ኢራን ምላሽ ሰጥታለች።
የኢራን መንግሥት በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኩል የቀረበውን የድርድር ዕቅድን ውድቅ አድርጓል።
ኢራን " ጦርነቱን የሚያበቃው እራሴ ስወስን እና የራሴ ቅድመ ሁኔታዎች ሲሟሉ ነው " ብላለች።
ኢራን መሟላት አለበት ያለቻቸውን የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ነው።
➡ በጠላት የሚፈጸመው " ወረራ እና ግድያ " ሙሉ ለሙሉ መቆም።
➡ ጦርነቱ በድጋሚ በኢራን ላይ እንደማይከፈት የሚያረጋግጥ አስተማማኝ ሁኔታ መፍጠር።
➡ የተረጋገጠ እና በግልጽ የሚታወቅ በጦርነቱ ለደረሰው ጉዳት እና ካሳ መክፈል።
➡ በቀጣናው ባሉ ቡድኖች ላይ የተከፈቱት ሁሉም ጦርነቶች እንዲቆሙ ማድረግ።
➡ ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ ላይ ያላትን መብት እና ሉዓላዊነት ዓለም አቀፍ ዕውቅና መስጠት።
የኢራን ባለሥልጣናት እስካሁን ድርድር የሚባል ነገር አለመጀመሩን አሳውቀዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉
ለመጀመርያ 6ት ጉዞዎች 20% ቅናሽ
እስከ 30% በተሻለ ዋጋ የተሻለ ጉዞ በYango ይጓዙ
#ታርጋ
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ወጥነት ያለዉ አዲስ የታርጋ ለውጥ ለማድረግ ሲያከናውን የቆየውን የቅድመ ዝግጅት ስራ አጠናቆ በቅርቡ አዲስ የተሸከርካሪ ሰሌዳ መለያ ቁጥር (ታርጋ) መስጠት እንደሚጀምር አስታወቀ።
የታርጋ መስጠት ስራዉ ከመጀመሩ በፊት ግለሰቦች ወይም ተቋማት የሚፈልጓቸዉን የሰሌዳ ቁጥሮች አጫርቶ ላሸነፉ አካላት ለመስጠት እንደሚፈልግ ገልጿል።
የስርጭት ስራዉ ከመጀመሩ በፊት ግለሰቦች ወይም ተቋማት የሚፈልጉትን ቁጥር በመለየት በሚኒስቴር መስሪያቤቱ 5ኛ ፎቅ በመቅረብ ከ17/07/18 ዓ/ም ጀምሮ ባለዉ አንድ ሳምንት ጊዜ እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።
መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት
የጋዜጠኝነት ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን።
በስልጠናው:
👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሖች፣ የሚዲያ አይነቶች እና የጋዜጠኝነት ዓይነቶች
👉 የዜና አሰራር እና የቃለመጠይቅ አደራረግ
👉 የመዝናኛ ፕሮግራም ጋዜጠኝነት፣ የፕሮግራም ዝግጅት፣ የማስታወቂያ አሰራር እና ዶክመንተሪ ዝግጅት
👉 የሞባይል ጋዜጠኝነት እና YouTube Journalism አካቷል፡፡
ስልክ ፦ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: /channel/sagetraininginstitute
Tiktok: sage_training_institute" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
#Iran
#StraitofHormuz
ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን ሙሉ በሙሉ እንዳልዘጋችው እየገለጸች ትገኛለች። ይሁን እንጂ መተላለፊያውን ለመጠቀም ጥብቅ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጣለች።
እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ምንድናቸው ?
በዋነኝነት ኢራን የሚፈጸምባትን ጥቃት የማይደግፉ እና ከጥቃት ፈጻሚዎቹ ጋር ግንኙነት የሌላቸው ሀገራት መርከቦች ማለፍ እንደሚችሉ ገልጻለች።
ማንኛውም አይነት መርከብ ሆርሙዝን ከመሻገሩ በፊት ከኢራን የሚመለከታቸው አካላት በተለይ ከእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል/IRGC ጋር አስቀድሞ መገናኘትና ፈቃድ ማግኘት ይኖርበታል።
የጭነት መርከቦች በኢራን የቁጥጥር ቀጠና ውስጥ በሚያልፉበት ወቅት ለማንነት ማረጋገጫና ለጭነት ምርመራ ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው ኢራን ገልጻለች።
"ጠላት" የተባሉ ሀገራት ዕጣ ፈንታ ምንድነው ?
ኢራን " በጠላትነት " የፈረጀቻቸው ሀገራት በተለይም አሜሪካና እስራኤል እንዲሁም የእነርሱ አጋር የሆኑ ሀገራት መርከቦች በሰርጡ እንዳያልፉ ጥብቅ እገዳ ጥላባቸዋለች።
የሀገሪቱ ወታደራዊ አዛዦች " ጥቃት ከቀጠለ ሙሉ በሙሉ እንዘጋዋለን " የሚል ማስጠንቀቂያ ደጋግመው እየሰጡ ይገኛሉ።
መርከቦች ሲያልፉ ለኢራን ይከፍላሉ ?
አንዳንድ መርከቦች ለደህንነቱ የተጠበቀ መተላለፊያ እስከ 2 ሚሊዮን ዶላር እንዲከፍሉ እየተጠየቁ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ሀገሪቱ ግን በይፋ ወጥታ ያለችው ነገር የለም ፤ በህንድ ያለው የኢራን ኤምባሲም " 2 ሚሊዮን ዶላር ይከፈላል " የሚባለውን መረጃ ምንም መሰረት የሌለ እንደሆነ በመግለፅ አጣጥሎታል።
እንደ ህንድ ፣ ቻይና ፣ ፓኪስታን እና ጃፓን ያሉ ሀገራት መርከቦች ከቴህራን ጋር በሚያደርጉት ቀጥታ ግንኙነት መተላለፍ መቻላቸው ተዘግቧል። ለምሳሌ በቅርቡ ሁለት የህንድ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች በተለየ ሁኔታ ማለፍ እንደቻሉ ተነግሯል።
የሰርጡ አለመረጋጋት የዓለምን የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሻቅብና የመርከብ መድን ዋጋ ከ4 እስከ 6 እጥፍ እንዲጨምር አድርጓል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የብሉምበርግ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ መካከለኛው ምስራቅ አቋርጧቸው ከነበሩ በረራዎች መካከል የትኞቹን በድጋሚ አስጀመረ ?
በመካከለኛው ምስራቅ በተከሰተው ግጭት ምክንያት በርካታ አየር መንገዶች ወደ ቀጠናው ያደርጉት የነበረውን በረራ በጊዜያዊነት ማቋረጣቸው ይታወቃል።
በሳምንት ከ 100 በላይ ምልልሶችን ያደርግ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግጭቱ ከተቀሰቀሰበት ጊዜ አንስቶ ወደ መካከለኛው ምስራቅ እና ገልፍ ሃገራት ያደርጋቸው የነበሩ በረራዎችን ካቋረጡ አየር መንገዶች መካከል አንዱ ነው።
ለሳምንታት ተቋረጦ የቆየው በረራ ወደ አንዳንድ የቀጠናው አካባቢዎች በድጋሚ ማስጀመሩን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሳውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዛሬው ዕለት ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ "የመሻሻል ነገሮች በምናይባቸው አካባቢዎች በተወሰነ ደረጃ በረራ እንደገና አስጀምረናል" ብለዋል።
በረራ የጀመረባቸው አካባቢዎች :-
• ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ውስጥ ዱባይ በቀን አንድ በረራ ፣
• አቡዳቢ በቀን አንድ በረራ ፣
• ሻርጃ በቀን አንድ በረራ
• ሳውዲ አረቢያ (ደማም ከተማ) በቀን አንድ በረራ
• ጆርዳን አማን በቀን አንድ በረራ ናቸው።
ይሁን እንጂ አቶ መስፍን ዶሃ (ኳታር)፣ ባህሬን፣ ኩዌት እንዲሁም ቴላቪቭ እና ቤሩት በረራ እንደተቋረጠባቸው መሆኑን አሳውቀዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዝርዝር ምን አሉ ?
" እንደሚታወቀው በገልፍ አካባቢ ጦርነት ከተጀመረ አንድ ወር አካባቢ ሆኖታል።
ጦርነቱ ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ገልፍ እና መካከለኛው ምስራቅ አገሮች የሚያደርገውን በረራ በተወሰነ ደረጃ ለጊዜው አቋርጧል።
ይህ በመሆኑ ምክንያት ወደ መካከለኛው ምስራቅ እና ገልፍ የሚሄዱ መንገደኞች እያጓጓዝን አይደለም፤ ያ በመንገደኛ ቁጥራችን ላይ የተወሰነ ተፅዕኖ ያሳድራል።
ይሁን እንጂ በሌሎች በምንበርባቸው ዓለም አቀፍ መዳረሻዎቻችን ላይ ያለንን በረራ በማጠናከር ከዚህ ከገልፍ እና መካከለኛው ምስራቅ ያጣነውን መንገደኛ ቁጥር ሌላ ቦታ በመብረር በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ለማካካስ ሞክረናል።
በዚህ መንገድ እየቀጠልን ነው፤ ሁኔታውን እየተከታተልን ነው የመሻሻል ነገሮች በምናይባቸው አካባቢዎች በተወሰነ ደረጃ በረራ እንደገና አስጀምረናል ያ እየቀጠለ ነው ያለው።
በረራ ተቋርጦ ከነበረባቸው መካከል አሁን መብረር የጀመርንባቸው ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ውስጥ ዱባይ በቀን አንድ በረራ እያደረግን ነው፣ አቡዳቢ በቀን አንድ በረራ እያደረግን ነው፣ እንዲሁም ሻርጃ በቀን አንድ በረራ እያደረግን ነው።
በተጨማሪም ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ደማም የምትባል ከተማ አቋርጠን ነበር እሱን በረራ ቀጥለናል።
ይሁን እንጂ ዶሃ (ኳታር) ፣ ባህሬን ፣ ኩዌት እንዲሁም ቴላቪቭ እና ቤሩት በረራ እንዳቋረጥን ነው።
እንግዲህ በረራ ስናቋርጥ የበረራ ደህንነትን ትክክለኛ ትንተና አካሂደን ያለውን ሁሉ መረጃ አገናዝበን መብረር ሴፍ (safe) ነው የምንል ሲሆን ብቻ እንበራለን።
በተጨማሪም ጆርዳን አማን አቋርጠን ነበር እሱን ሁለት በረራ ነበረ አሁን በአንድ በረራ ጀምረናል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
#Update
#MiddleEastWar
ግዙፉ የዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ ናይጄሪያን ከዓለም አቀፍ የዋጋ ንረት ሊታደጋት እንዳልቻለ ተነገረ።
የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያን እያናወጠ ባለበት በዚህ ወቅት በነዳጅ ሀብቷ በምትታወቀው ናይጄሪያ የችርቻሮ የነዳጅ መሸጫ ዋጋ በታሪክ ከፍተኛ ነው የተባለ ጭማሪ አሳይቷል።
ግዙፉና በቀን 650 ሺህ በርሜል የሚያጣራው የዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ በሙሉ አቅሙ ስራውን እየሰራ ቢሆንም ሀገሪቱን ከዓለም አቀፍ የዋጋ ንረት ሊታደጋት አልቻለም።
በናይጄሪያ በአሁኑ ወቅት አንድ ሊትር ነዳጅ እስከ 1,500 ናይራ (168 ብር) እየተሸጠ መሆኑን ከሀገሪቱ ሚዲያዎች የተገኘ መረጃ ያሳያል። በአንድ ወር ውስጥ ብቻ የ50 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል ተብሏል።
የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ከ110 ዶላር በላይ እንዲሸጥ አድርጎታል።
የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ ድፍድፍ ነዳጁን የሚገዛው በዓለም አቀፍ የገበያ ዋጋ በመሆኑ የማምረቻ ወጪው በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።
በሆርሙዝ ያለው እንቅስቃሴ በመስተጓጎሉ የባህር ላይ ትራንስፖርት ስጋት እንዲጨምር ፤ ነዳጅን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ለማጓጓዝ የሚጠየቀው የኢንሹራንስ ክፍያ እንዲንር አድርጓል።
የናይጄሪያ ገንዘብ (ናይራ) ከዶላር አንጻር ዋጋው እየቀነሰ በመምጣቱ በሀገር ውስጥ የሚመረተው ነዳጅ እንኳ በዶላር ተሰልቶ ለገበያ ሲቀርብ ዋጋው እንዲጨምር አድርጎታል።
የዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ ለምን ናይጄሪያን ከንረቱ አልታደገም ?
ብዙዎች የዳንጎቴ ማጣሪያ ፋብሪካ ስራ ሲጀምር የነዳጅ ዋጋ ይቀንሳል የሚል ተስፋ የነበራቸው ቢሆንም በተግባር ግን ሁኔታው የተለየ ሆኗል።
ፋብሪካው ነዳጅን " ከምድር የሚያወጣ " ሳይሆን " የሚያጣራ " በመሆኑ እንደ ማንኛውም የዓለም አቀፍ ተገበያይ ለዋጋ መለዋወጥ ተጋላጭ ሆኗል።
በተጨማሪ ናይጄሪያ ሀገር ውስጥ የምታመርተው ድፍድፍ ነዳጅ ለነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካው በቂ ባለመሆኑ ዳንጎቴ ከአሜሪካ እና ብራዚል ድፍድፍ ነዳጅን በዶላር ገዝቶ ለማጣራት ተገድዷል። ይህም ፋብሪካው በሀገር ውስጥ የሚሸጠውን ነዳጅ ዋጋ እንዲጨምር አስገድዶታል።
የኢኮኖሚ ባለሙያዎች በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነት ተባብሶ ከቀጠለ አንድ በርሜል ነዳጅ እስከ 200 ዶላር ሊደርስ ይችላል። ይህ ከሆነ የዳንጎቴ ማጣሪያ ፋብሪካ መኖር የነዳጅ አቅርቦት እንዳይቋረጥ ከመርዳት ባለፈ የዋጋ ጭማሪውን ለመከላከል አቅም እንደማይኖረው ተመላክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከሮይተርስ እንዲሁም ከተለያዩ የናይጄሪያ መገናኛ ብዙሃን ነው የሰበሰበው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
" ወደ ሀገራችን 140 ሺህ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የገቡ ቢሆንም የኃይል መሙያ ጣቢያዎች ግን አልተሟሉም " - ኢንጅነር ጌቱ ገረመው
⚫️ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ አገልግሎት የክፍያ ተመን ይፋ ሆነ።
እስካሁን ባለው መረጃ ወደ 140 ሺህ የሚጠጉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገራችን የገቡ ቢሆንም ከተሽከርካሪዎቹ ቁጥር ጋር የሚመጣጠን የኃይል መሙያ ጣቢያዎች ግን እስካሁን እንዳልተሟሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ተናገሩ።
ይህን ያሉት ሳሊተ ምህረት አካባቢ ተቋማቸው ያስገነባውን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ መሙያ ጣቢያ ባስመረቀበት ነው።
ኢንጅነር ጌቱ ገረመው በዝርዝር ምን አሉ ?
" በነዳጅ ለሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ከውጭ ሀገራት የሚገባ ነዳጅ ለሀገራችን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያስወጣ ከመሆኑም በላይ የአየር ብክለትን የሚያስከትልና ሀገራችን ከምትከተለው የአረንጓዴ ኢነርጂ ፖሊሲ ጋር የማይጣጣም ነው።
በመካከለኛው ምስራቅ የተፈጠረው ዓይነት የጸጥታ ችግር በነዳጅ አቅርቦት ላይ ምን ያህል ጉዳት እንደሚያደርስ መገንዘብ ይቻላል።
በመጀመሪያው ምዕራፍ በአዲስ አበባ 32 እንዲሁም በሌሎች የክልል ከተሞች 8 በድምሩ 40 የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባትና አገልግሎት ለማስጀመር በጥቅላላው 10 ሚሊዮን ዶላር ገደማ የሚጠጋ ወጪ የሚጠይቅ ሥራ በማከናወን ላይ እንገኛለን።
አሁን የተመረቀው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ የኃይል መሙያ ጣቢያ 170 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ነው። በከተማችን ከተገነቡት ስድስት ጣቢያዎች መካከል በዚህ በተቋማችን የተሽከርካሪ ጥገና ማዕከል እና በፒያሳ ኤሌክትሪክ ሕንጻ ግቢ ውስጥ የሚገኙ ሦስት ጣቢያዎችን አጠናቀን ክፍት አድርገናል።
በቀጣይ ለተያዙት 34 ፕሮጀክቶች የሚያስፈልጉ የኃይል መሙያ መሣሪያዎች፣ ትራንስፎርመሮች እና ተያያዥ ግብዓቶች እየተዘጋጁ ነው።
በአዲስ አበባ ከመረጥናቸው 26 ቦታዎች መካከል በ18 ላይ በአጭር ጊዜ ውስጥ የግንባታ ሥራቸው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራሉ።
በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ 2,300 ፈጣን የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን (Fast Charging Stations) የመገንባት ዕቅድ ይዘናል። ለዚህም አዲስ አበባ ብቻ 1,176 የሚሆኑ መሰል ማዕከላት ያስፈልጓታል።
የኃይል አጠቃቀም ባህላችንን ለማሻሻል በሰዓት ላይ የተመሠረተ የክፍያ ተመን አውጥተናል። በዚህም መሠረት፦
- ከምሽቱ 4:00 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ፦ 14.85 ብር በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት (kWh)
- ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 11:00 ሰዓት ድረስ፦ 16.57 ብር በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት (kWh)
- የኃይል ፍላጎት በሚበዛበት ከቀኑ 11:00 እስከ ምሽቱ 4:00 እንዲሁም ከጠዋቱ 12:00 እስከ 4:00 ሰዓታት ድረስ 18.28 ብር በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት (kWh) ክፍያ አገልግሎቱን ማግኘት ይቻላል።
በሁለተኛው ምዕራፍ በቢሾፍቱ፣ በሞጆ፣ በባቱ፣ በአዳማ፣ በሻሸመኔ እና በሀዋሳ ከተሞች ጣቢያዎችን እንገነባለን።
በኢትዮ-ጂቡቲ ኮሪደር ላይ አስፈላጊውን መሠረተ ልማት ለማሟላት ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት እየሠራን እንገኛለን " ብለዋል።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ150 እስከ 200 የሚሆኑ የኃይል መሙያ ጣቢያዎች እንዳሉ ገልጿል።
እነዚህም በአስመጪዎች፣ በገጣጣሚዎች፣ በሆቴሎችና በሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ላይ የተተከሉ ናቸው።
ነገር ግን በአንድ ጊዜ በርካታ ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችሉ ደረጃቸውን የጠበቁ ጣቢያዎችን በአዲስ አበባ በስፋት ማቅረብ እንደሚገባ ገልጿል።
በመመሪያ እንደተቀመጠው የከተማ አስተዳደሮች፣ ከንቲባዎችና የክልል አመራሮች የኃይል መሙያ ጣቢያ የሚገነባ ባለሀብት ከተገኘ መሬት የማቅረብ እና የማዘጋጀት ኃላፊነት አለባቸው ተብሏል።
መሬት ለዚህ አገልግሎት ሲቀርብ ቢቻል ቢቻል በነፃ፣ ካልሆነም ደግሞ በረጅም ጊዜ ክፍያና በጣም በተመጣጣኝ (ርካሽ) ዋጋ መቅረብ እንዳለበት ተጠቁሟልም
በአሁኑ ወቅት ዘርፉን ከሚፈታተኑት ከዋና ዋና ማነቆዎች አንዱ የመሬት አቅርቦት በመሆኑን የገለጸው ሚኒስቴሩ ይህ ጉዳይ በአመራሩ ዘንድ ትኩረት አግኝቶ መፈታት እንዳለበት አሳስቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
መጋቢት 20 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
በፊንቴክ ኢንቨስትመንት የተጭበረበሩ ሰዎች ስለሚዲያዎች ሚና ያነሱት ሃሳብ ምንድነው ?
በአቶ ዳንኤል ዮሐንስ እና አቶ ግርማይ ገ/ሚካኤል በሚመራው " ፊንቴክ ኢንቨስትመንት " ከ1.7 ቢሊዮን ብር በላይ ጉዳት መድረሱን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል።
" ብራችን ተበላ " ያሉ ተበዳዮች ለጉዳቱ መባባስ ታማኝ ናቸው ያሏቸው ሚዲያዎች እና ታዋቂ ሰዎች ከፍተኛ ድርሻ እንደነበራቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
" ገንዘባችን በፊንቴክ የተበላው ታማኝ ናቸው ባልናቸው ሚዲያዎች ላይ በተላለፉ ማስታወቂያዎችና ዜናዎች እንዲሁም ለዘመናት በስራዎቻቸው በምናውቃቸው አርቲስቶች እና ታዋቂ ሰዎች አማካኝነት ነው " ሲሉ ተበዳዮቹ ተናግረዋል።
አክለውም ፦
- የፌስቡክ፣
- የቲክቶክ
- የቴሌግራም ገጾች ላይ በተደጋጋሚ ስለ ፊንቴክ የሚወጡ አጓጊ መረጃዎች አእምሯቸው መረጃውን እንደ እውነት እንዲቀበለው አስገዳጅ ሁኔታ ፈጥሮባቸው እንደነበር ያስረዳሉ።
ድርጅቱ ትልልቅ ገጾችና ሚዲያዎች ያላቸውን የህዝብ አመኔታ እንደ ዋስትና እንደተጠቀመበት የሚያነሱት ተበዳዮቹ አንዳንዶቹ ተቋማት ወይም የዜና ዘጋቢዎች ክፍያ በመቀበል " ዜና መሰል ማስታወቂያዎችን " ሲሰሩ ሌሎች ደግሞ በቂ ማጣራት ሳያደርጉ ዘገባዎችን በማቅረባቸው ህዝቡ በስፋት እንዲዘናጋ አድርገዋል ይላሉ።
" እንትና የሚባለው የማውቀው ገጽ የዘገበውማ ውሸት አይሆንም፤ መንግስት የሚያውቀው ሚዲያ ከዘገበውም ሀሰት አይሆንም " የሚለው እምነታቸው ለጉዳት እንዳጋለጣቸውም ይናገራሉ።
በተጨማሪም ታዋቂ አርቲስቶች፣ የሚዲያ ሰዎች እና ጥቂት ግለሰቦች መኪና ሲረከቡ የሚያሳዩ ፎቶዎች በስፋት መሰራጨታቸው ማህበረሰቡ ውስጥ ትልቅ እምነት እንዲያድር ማድረጉን ተበዳዮች ያስታውሳሉ።
" ታዋቂው አርቲስት እገሌ መኪናውን ካገኘ እኔ ለምን እዘገያለሁ ? ቶሎ ከፍዬ መኪናዬን ልውሰድ " የሚል ስሜት እንዲፈጠርባቸው ማድረጉንም በቁጭት ይገልጻሉ።
ትላንት ድርጅቱን እንደ ትልቅ የኢንቨስትመንት አማራጭ " መኪና በ950 ሺህ ብር " እያሉ ሲያስተዋውቁ የነበሩ አንዳንድ ገጾችና ሚዲያዎች ዛሬ የድርጅቱ መሪዎች በቁጥጥር ስር ሲውሉ ቀዳሚ ዘጋቢ በመሆን " ሰበር ዜና " እያሉ መዘገባቸው " እጃችንን ታጥበናል፤ እኛ የለንበትም " የሚል አካሄድ መሆኑን ተበዳዮች ይተቻሉ።
ይህ ክስተት ብዙ ተከታይ ያላቸው የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና ሚዲያዎች ከየትኛውም ድርጅት ጋር ከመስራታቸው በፊት ማጣራት ማድረግ እንዳለባቸው ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ነው ብለዋል።
በተመሳሳይ ሃሳባቸውን ያካፈሉን ቤተሰቦች ደግሞ የመንግስት ባለስልጣናት እና የስራ ኃላፊዎች ፊንቴክ በሚያዘጋጃቸው የተለያዩ መድረኮች ላይ መገኘታቸው ዜጎች ሂደቱ ህጋዊ እንደሆነ አምነው ገንዘባቸውን እንዲከፍሉና እንዲበሉ ትልቅ ግፊት ማድረጉን ገልጸዋል። " እነዚህስ አይጠየቁም ወይ ? " ብለዋል።
በሌላ በኩል፥ በዚህ የፊንቴክን ጉዳይ አቶ ገዛኸኝ ተሬሳ የተባሉ ግለሰብ የግል የማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸውን ተጠቅመው " እንዲህ ያለ ርካሽ ነገር የለም፤ እያጭበረበሩ ነው " በማለት ማህበረሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግና መንግሥትም እርምጃ እንዲወስድ ሲታገሉ መቆየታቸው ተነስቷል። የአሁኑ ውጤት እንዲገኝም የእኚህ ግለሰብ ጥረት ትልቅ ድርሻ እንደነበረው ተገልጿል።
#ማሳሰቢያ ፡- ከዚህ ዜና ጋር ከላይ ተያይዘው የቀረቡት ምስሎች (Screenshots) ፊንቴክ ኢንቨስትመንት የተለያዩ ሚዲያዎችን እና ማህበራዊ ገጾችን እንዴት ይጠቀም እንደነበር ለማሳየት በተበዳዮች በማስረጃነት የቀረቡ ናቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
#ALERT🚨
ሩሲያ ከመጋቢት 23 ጀምሮ የነዳጅ (ቤንዚን) ኤክስፖርት ልታግድ ነው።
የሩሲያ መንግስት በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ጦርነት ሳቢያ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ የሚታየውን የዋጋ መለዋወጥ ለመቋቋም ከመጋቢት 23 ቀን 2018 ጀምሮ የቤንዚን የውጭ ኤክስፖርት ለማገድ መወሰኑ ታውቋል።
የሀገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ኖቫክ የኢነርጂ ሚኒስቴር እገዳውን የሚጥል ረቂቅ ውሳኔ እንዲያዘጋጅ ትዕዛዝ የሰጡ ሲሆን እገዳው እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ድረስ እንደሚቆይ የሩሲያ መንግስታዊ የዜና ወኪል ታስ ዘግቧል።
ሩሲያ ይህን እርምጃ የወሰደችው የሀገር ውስጥ የነዳጅ አቅርቦትን ለማረጋጋትና የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ነው ተብሏል።
ሩሲያ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ወደ 5 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የሚጠጋ ቤንዚን ወደ ውጭ ሀገራት ልካለች። አሁን የተጣለው እገዳ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ የራሱ ተጽዕኖ ሊኖረው እንደሚችል ይገመታል።
መረጃው የ'ዘ ኢኮኖሚክ ታይምስ' ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA🇪🇪🇹
አራተኛው የ"ኢንቨስት ኢን ኢትዮጵያ" ከፍተኛ የንግድ ፎረም 13.7 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ የኢንቨስትመንት ስምምነቶች በመፈራረም ተጠናቀቀ ።
ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አራተኛው የ"ኢንቨስት ኢን ኢትዮጵያ" ከፍተኛ የንግድ ፎረም በዛሬው እለት ተጠናቋል።
በፎረሙ ማጠቃለያ ላይ ከ13.7 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የሚያወጡ የኢንቨስትመንት ስምምነቶች መፈረማቸውን ተገልጿል።
ለተከታታይ ሁለት ቀናት ሲካሄድ በቆየው በዚህ ፎረም ላይ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) ፣ አምባሳደሮች፣ የልማት አጋሮች እና የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች ተገኝተዋል።
የኢንቨስትመንት ኮሚሽን በፎረሙ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጸው፣ ኮሚሽኑ ቀደም ብሎ ሲያከነውናቸው ከነበሩ 17 የኢንቨስትመንት ድርድሮች መካከል ሰባቱን በተሳካ ሁኔታ መፈራረም ችሏል።
እነዚህ ስምምነቶች በድምሩ ከ13.7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ካፒታል ያላቸው ሲሆኑ፣ በሪል ስቴት፣ በታዳሽ ኃይል፣ በሶላር ሴል ማምረቻ፣ በጨርቃጨርቅ፣ በአልሙኒየም እና በማዕድን ዘርፎች ላይ ያተኮሩ ናቸው።
በመርሃ ግብሩ በማጠቃለያ ላይ ንግግሩ ያደረጉት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) "ኮሚሽኑ ባለሀብቶች ያነሷቸውን የአፈጻጸም ፍጥነት እና የቅንጅት ጥያቄዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ የተፈረሙት ስምምነቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ መሬት ላይ ወርደው ስራ እንዲጀምሩ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል" ብለዋል ።
አክለውም ፎረሙ
• በማኑፋክቸሪንግ እና ንግድ፣
• በማዕድን እና ኢነርጂ፣
• በግብርና እና ግብርና ማቀነባበሪያ፣
• በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች፣
• በካፒታል ገበያ እና ከአየር ንብረት ጋር በተጣጣሙ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ ውጤት ተኮር ውይይት እንዲደረግ አስችሏል"ብለዋል።
የኢንሸስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በተጨማሪ ምን አሉ ?
" ከዚህ ፎረም በፊት በ17 የኢንቨስትመንት ስምምነቶች ላይ በንቃት ስንሰራ ቆይተናል እስካሁንም ሰባቱን በተሳካ ሁኔታ የፈረምን ሲሆን፣ አጠቃላይ የተመዘገበው የኢንቨስትመንት ካፒታል ከ13.7 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ ነው።
ዛሬ የፈረምናቸው ስምምነቶች በዘርፍም ሆነ በመጡበት ሀገር የተለያዩ ናቸው።
ዘርፎቹም ሪል ስቴት፣ የሶላር ሴል ማምረቻ፣ ጨርቃጨርቅ እና አልባሳት፣ አልሙኒየም ማምረት፣ የችርቻሮ ንግድ እና ስርጭት፣ ማዕድን፣ የታዳሽ ኃይል ምርት እና የ'ግሪን አሞኒያ' ምርትን ያካትታሉ።
የእውነተኛ ስኬት መለኪያው እነዚህ የኢንቨስትመንት ቃል ኪዳኖች ምን ያህል በፍጥነት መሬት ላይ ወደሚንቀሳቀሱ ፕሮጀክቶች ይቀየራሉ የሚለው ነው።
እዚህ የተደረጉት ውይይቶች፣ ግንኙነቶች እና ግንዛቤዎች አሁን ወደ ተግባር መሸጋገር አለባቸው።
ኮሚሽኑ ሂደቱን በመከታተል እና አፈጻጸሙን በማቀላጠፍ የቅርብ ክትትል ያደርጋል " ብለዋል።
በሦስተኛው “ኢንቨስት ኢን ኢትዮጵያ 2025” ፎረም በአጠቃላይ 1.6 ቢሊዮን ዶላር የሚገመቱ የኢንቨስትመንት ውሎች መፈረማቸው የሚታወስ ሲሆን እነዚህም ፕሮጀክቶች አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ መግባታቸው መገለጹ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
9 ስደተኞች በጅቡቲ የባህርዳርቻ ሞቱ።
በጁቡቲ የባህር ዳርቻ አቅራቢያ ከትናንት በስተያ የሰመጠች ጀልባ ውስጥ ከነበሩት ስደተኞች ዘጠኙ መሞታቸውን ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ጉዳይ ድርጅት (IOM) አስታወቀ።
ሌሎች 45 ስደተኞች ደግሞ በህይወት ይኑሩ ይሙቱ እንደማይታወቅ ድርጅቱ ገልጿል።
አደጋው የደረሰው ከትናንት በስተያ መጋቢት 15/ 2018 ዓ.ም. ለሊት ጅቡቲ ከምትገኘው ኦቦክ ከተባለችው ትንሽ ከተማ በስተሰሜን ባለ የባህር ዳርቻ መሆኑን IOM አስታውቋል።
ጀልባዋ 320 ሰዎችን አሳፍራ ነበር።
በፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘገባ መሠረት የምሥራቅ መስመር በሚባለው በዚህ የፍልሰት መንገድ ከሚሰደዱት አብዛኛዎቹ ከኢትዮጵያ የሚመጡ ናቸው።
በዚህ መስመር እ.ኤ.አ 2024 የ922 ስደተኞች ሕይወት አልፏል። ይህም እስከዛሬ ከተመዘገበው ሞት ከፍተኛው ተብሏል።
መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
ፎቶ፦ IOM
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA🇪🇹
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከልማት አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 4ኛው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ የኢንቨስትመንት ፎረም በመከናወን ላይ ይገኛል።
" ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ዝግጁ ናት " በሚል መሪ ቃል መክፈቻውን ያደረገው ፎረሙ እስከ ነገ የሚቀጥል ይሆናል።
ፎረሙን የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በይፋ አስጀምረውታል።
በፎረሙ ላይ በርካታ ቁጥር ያላቸው ዓለም አቀፍ ባለሃብቶች፣ የንግድ መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና የልማት አጋሮች እየተሳተፉ ይገኛል።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ፥ ዘንድሮ በሚካሄደው 4ኛውን በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ የኢንቨስትመንት ፎረም ከ 2.6 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ የሚያወጡ ስምምነቶችን ለመፈረም መታቀዱን መግለጻቸው ይታወቃል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 17 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
አፖሎ አዲስ ነገር ይዞ መጥቷል፤ ለመገረምም ለመገልገልም ተዘጋጁ።
አቢሲንያ ባንክ
የሁሉም ምርጫ !
" ቀይ ስጋ እና ስብ የበዛበት ምግብ በተደጋጋሚ የሚበላ ሰው ለአንጀት ካንሰር ይዳርጋል፤ አመጋገብ ላይ ጥንቃቄ ይደረግ " - ፕሮፌሰር ብርሀኑ ቆጢሶ
በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች በአንጀት ካንሰር እንደሚጠቁ መረጃዎች ያሳያሉ።
በኢትዮጵያም በየዓመቱ ከሚመዘገቡ 80 ሺህ አዳዲስ የካንሰር ታማሚዎች መካከል ከ6 ሺህ በላይ የሚሆኑት በዚሁ በሽታ የሚጠቁ ወንዶች ናቸው። ሆኖም ትክክለኛው ቁጥር ከዚህም በላይ ሊሆን ይችላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህን መረጃ ያገኘው የጤና ሚኒስቴር ከጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በመተባበር የመጋቢት ወር " የአንጀት ካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫ ወር " መሆኑን ምክንያት በማድረግ በሽታውን ለመከላከል ባዘጋጁት የንቅናቄ መድረክ ላይ ነው።
በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ትልቁ አንጀት ቀዶ ህክምና ሰብ ስፔሻሊቲ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ቆጢሶ ፤ " የአንጀት ካንሰር ከ50 ዓመት በላይ ባላቸው ሰዎች ላይ እየጨመረ ይሄዳል ቢባልም፣ በሀገራችን ግን ከ50 ዓመት በታች ያሉ #ወጣቶችም በዚህ በሽታ እየተጠቁ ነው " ብለዋል።
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ቆጢሶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የአንጀት ካንሰር እንደማንኛውም ካንሰር ድንገት የሚከሰት ነው። በሽታው የሚጀምረው የአንድ ሴል የእድገት ሁኔታ ሲለወጥ በሚፈጠር እብጠት ወይም ዕጢ ነው።
ይህ በሽታ በቁጥራዊ መረጃዎች ሲታይ ሲጋራ በሚያጨስ ሰው ላይ በዝቶ ይታያል። በጣም ጠጪ በሆነ ሰው ላይ መጠኑ የበለጠ ይታያል። ሲጋራ የማያጨስ ሰው የአንጀት ካንሰር ፈጽሞ አይዘውም ማለት ግን አይቻልም።
ቀይ ስጋ እና ስብ የበዛበት ምግብ በተደጋጋሚ የሚበላ ሰው ከሆነ ለአንጀት ካንሰር ይዳረጋል። በጥናትም የተረጋገጠ ነው። በተቻለ መጠን አመጋገብ ላይ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ ነው።
ይህ በሽታ ከ50 አመት በላይ ባላቸው ሰዎች ላይ እየጨመረ እንደሚሔድ አለም አቀፍ መረጃዎች ይገልጻሉ። ጥናቶችም ያሳያሉ። እኛ ጋር ስንመጣ ከ50 አመት በታች ያሉ ወጣቶች በዚህ በሽታ እየተጠቁ ነው ያሉት። በሽታውም እየጨመረ ነው።
አሁን ባለን መረጃ መሰረት ኢትዮጵያ ውስጥ በወንዶች ላይ ካንሰሩ በብዛት እየታየ ነው። ስለዚህ በወንዶች ላይ የመጀመሪያው ካንሰር በሽታ ሆኖ እየተመዘገበም ነው። በዚህ በሽታ ሴቶች አይጠቁም ማለት አይቻልም። ሴቶች ላይ ግን ከጡት እና ከማህጸን በር ጫፍ ካንሰር በመቀጠል ሶስተኛ ደረጃ ላይ ያለ በሽታ ነው።
የበሽታው ምልክት የሚታየው በሽታው አድጎ ትልቅ ደረጃ ላይ ደርሷል በምንልበት ጊዜ ነው። በሽታው በውስጣችን ሆኖ ምንም የህመም ስሜት ላይሰማን ይችላል። ግን አልፎ አልፎ ፦
- የማስቀመጥ፣
- ደም የቀላቀለ እና ንፍጥ ነገር ያለበት ተቅማጥ መኖር ቀዳሚ ምልክቶቹ ናቸው። እንዲህ አይነት ምልክቶች ሲታዩ ወደ ጤና ተቋማት መሔድ አስፈላጊ ነው።
በአሁኑ ወቅት ህክምናው የሚሰጥባቸው ጥቁር አንበሳ፣ ቅዱስ ጳውሎስ፣ ዳግማዊ ምኒልክ፣ የካቲት 12 እና ጦር ሀይሎች ሆስፒታል ላይ ነው። የሰለጠነ ባለሙያ አስቀምጠናል በእነዚህ ቦታዎች ህክምናውን ማግኘት ይቻላል " ብለዋል።
በጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሕይወት ሰለሞን በበኩላቸው ፥ " ከ6,000 በላይ ሰዎች በአንጀት ካንሰር ይጠቃሉ ይባል እንጂ ይህ ቁጥር ትክክለኛ አይደለም፤ የበሽታውን መጠን የሚገልጽ አይደለም። ካልሆነ የበሽታውን ክብደት ማሳወቅ አንችልም፣ ከዚህ በኋላ የተቀናጀ ጥናት ማድረግ ይኖርብናል " ሲሉ አሳስበዋል።
አክለው " በሽታው ለታማሚው ራሱ በቀላሉ የሚታወቅ አይደለም። ስለዚህ እንደ ሀኪም ህብረተሰቡን የበሽታውን ምልክት ማሳየት፣ መግለፅ እና ለበሽታው አጋላጭ የሆኑትን ነገሮች ማሳወቅ ስራችን መሆን አለበት " ብለዋል።
" ብዙ ጊዜ በተቅማጥ የሚጠቁ ሰዎች አንድ እና ሁለት ጊዜ ከታዩ በኋላ ሁሌም የሆድ ጥገኛ ተህዋሲ ተብሎ ስለሚታሰብ በዚያው እየቆየ እንደሚሄድና በመጨረሻ ወደ ህክምና ሲመጡ በሽታውን ለማከም አዳጋች ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የጥንቃቄ መልዕክት ⚠️
ለውድ ቤተሰቦቻችን በሙሉ ፦
በ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቤተሰብ አባላት የመሰባሰቢያ ቻናል ስር በቴሌግራም ድርጅት በኩል የሚለቀቁ ማንኛውም አይነት " Sponsored Ads " ከእኛ እውቅና ውጪ መሆናቸውን በድጋሜ እንገልጻለን።
በተለይ በአሁኑ ሰዓት " Eblan Travel Agency " በሚል ስም የሚሰራጨው የካናዳ የቪዛ ማስታወቂያ እኛ የማናውቀው እና በኛ ያልተረጋገጠ መሆኑን እናሳውቃለን።
እነዚህ ማስታወቂያዎች ቴሌግራም ያለ እኛ ፍቃድና ቁጥጥር ለኩባንያው ክፍያ ስለተፈጸመ ብቻ በራሱ ስልተቀመር Algorithm / የሚያሰራጫቸው ናቸው።
እኛ በራሳችን በኩል በቻናሉ ላይ ለምንለጥፋቸው ማስታወቂያዎች ሙሉ ኃላፊነት የምንወስድ ሲሆን እንዲህ ያሉ በቴሌግራም በኩል "Ad" ተብለው የሚመጡ መልዕክቶችን ግን እውቅና አንሰጥም።
ውድ ወጣቶች ፦ በተለይ የጉዞና የቪዛ ጉዳዮችን በሚመለከት በድርጅት ስም በሚንቀሳቀሱ አካላት እንዳትታለሉ ፤ ያለአግባብ ገንዘባችሁን እንዳትሰጡ ፤ ከፍተኛ ጥንቃቄም እንድታደርጉ እናሳስባለን።
አይደለም በዚህ በ 'ቴሌግራም' ማስታወቂያ በአካል " ቢሮ አለን ኑ " ብለው የምታገኟቸውን ማንኛውም ድርጅቶች ተችግራችሁ፣ በብዙ ስቃይ ያመጣችሁትን ብር አንስታችሁ ከመስጠታችሁ በፊት መርምሯቸው ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው መሆናቸውን አጣሯቸው።
ራሳችሁን ጠብቁልን " ወደ ውጭ እንልካለን " የሚሉ ብዙሃኑ የወጣቶችን ብር እያጨበረበሩ እንደሚዘርፉና እንደሚሰወሩ በተደጋጋሚ አሳውቀናል።
እኛም ያለኛ እውቅና የሚተላለፉ ማስታወቂያዎችን ባየን ቁጥር ወደዛ እንዳትሄዱ ወዲያውኑ ጥንቃቄ እንድታደርጉ መረጃውን የምናደርሳችሁ ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፦
- " በትምህርት ሆነ ፣ በስብሰባ ወይም በሌላ ጉዳይ ወደ ውጭ ሰዎች እንልካለን "
- " በወራት ውስጥ ቪዛ እናስመታላችኃለን "
- " ትንሽ ብር አስገቡና መኪና ግዙ ፣ እቃ እናምጣላችሁ " የሚሉ መሰል ማስታወቂያዎችን እንደማያስተናግድ እና ከዚህ ቀደምም አስተናግዶ እንደማያውቅ እንገልጻለን።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
በአዋሽ ሬሚት ያለ እንግልት ገንዘብ ይላኩ።
=============================
ውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን አሁን ገንዘብ መላክ ቀላል ሆኗል!
በቪዛ (Visa) ወይም በማስተርካርድ (MasterCard) በመጠቀም፦
👉በቀጥታ ወደ አዋሽ ባንክ ሂሳብ ወይም ወደ አዋሽብር -ፕሮ ዋሌት ፈጣን፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና አስተማማኝ የገንዘብ ዝውውር ያድርጉ።
የአዋሽ ሬሚት መተግበሪያ አውርደው ይጠቀሙ!
ለአንድሮይድ ተጠቃሚዎች 👉 https://play.google.com/store/apps/details?id=com.sc.awashremit
ለ IOS ተጠቃሚዎች👉 https://apps.apple.com/us/app/awash-remit/id6759370340
" ትዳራቸው የፈረሰ፣ ብቸኛ መተዳደሪያ ታክሲያቸውንና የሚኖሩበትን ቤት ሸጠው ጎዳና ላይ የወደቁ፣ በጭንቀት ምክንያት የአዕምሮ ህመምተኛ የሆኑ አሉ " - ከ1,300 በላይ ቆጣቢዎች
" ከ1,300 በላይ " ነን ያሉ ዜጎች " ፊንቴክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ " የተሰኘው የኤሌክትሪክ መኪና አስመጪ ድርጅት፣ " በቆጠቡት መሰረት ተሽከርካሪዎች ባለመረከባቸው " ከፍተኛ ቅሬታ እያቀረቡ ይገኛሉ።
ቆጣቢዎቹ ድርጅቱ " አካውንታችን ታግዷል " እንዳላቸው ገልጸው፣ " የሀገሪቱን የ'አረንጓዴ አሻራ' መርሀግብር ሽፋን በማድረግ፣ ስልጣን ያላቸው ሰዎችና ታዋቂ ሰዎችን በማሳተፍ እጅግ በተጠና መልኩ ከ1.4 ቢሊዮን ብር በላይ የዜጎችን ንጹህ ጥሪት ተወስዶ ይገኛል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ስሞታቸውን አስገብተዋል።
" መጀመሪያ ለቅድመ ክፍያ 950 ሺሕ ብር " መክፈላቸውን አውስተው፣ ከዚያ በኋላም " መኪናዎቹ ጂቡቲ ደርሰዋል " በሚል " የሊብሬና የታርጋ ተብሎ ያለ ምንም የመንግስት ሪሲት ተጨማሪ 450 ሺሕ ብር እንድንከፍል ተደርገናል " ነው ያሉት።
" የከፈልንባቸው " ያሏቸውን መኪናዎች በአካል አይተው እንደነበር የገለጹት ስሞታ አቅራቢዎቹ፣ " ድርጅቱ እኛን በውሸት ቀጠሮ እያመላለሰ እነዛኑ መኪኖች ለሌላ ሶስተኛ ወገን በመኪና መሸጫ ቤቶች እየሸጣቸው መሆኑን ደርሰንበታል " በማለት፣ " ይህ ከዘረፋም በላይ ትልቅ ክህደት ነው " ሲሉ ወቅሰዋል።
ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ፣ " ትዳራቸው የፈረሰ፣ ብቸኛ መተዳደሪያ ታክሲያቸውንና የኖሩበትን ቤት ሸጠው ጎዳና ላይ የወደቁ፣ በጭንቀት ምክንያት የአዕምሮ ህመምተኛ የሆኑና በህመም ላይ እያሉ የመታከሚያ ገንዘብ ያጡ ብዙ ወንድም እህቶች አሉን " ሲሉም ገልጸዋል።
እስከ ላይ ድረስ " ደጅ ብንጠናም እስካሁን ምንም መፍትሄ አላገኘንም " የሚሉት እኝሁ አካላት፣ " ድርጅቱ አካውንቱን ባዶ በማድረግና ገንዘባችንን ወደ እህት ኩባንያዎች በማሸሽ 'አካውንታችን ታግዷል' የሚል የፌዝ መልስ እየሰጠን ይገኛል " በማለት መፍትሄ ጠይቀዋል።
ቅሬታቸውን ለብቻቸው ለቲክቫህ ያስገቡ ሌላኛው ቆጣቢ በበኩላቸው፣ ለቁጠባ ምዝገባ በሄዱበት ወቅት ተሽከርካሪ " ከ2 እስከ 3 ወራት እንደሚያስረክቡን ነግረውን ነበር " ብለው፣ " ይኼው አሁን (ሳንረከብ) 8 ወር ሆኖናል " ይላሉ።
" ዘገየብን " ብለው ሲጠይቁ " 'ዶላር አተን ነው' " እንዳላቸው የገለጹት ቆጣቢው፣ ድርጅቱ ላከልን ባሉት " ደብዳቤ " መኪናቸው " እንደገባ እና እስከ ውል ቁጥር 650 ከ4ኛ ዙር ጋር ጎን ለጎን " ሊሰጧቸው ቃል ገብተው እንደነበር ያስታውሳሉ።
ግን፣ " ከ950 ሺሕ ተጨማሪ የቀረጥ 285 ሺሕ፣ 130 ሺሕ የታርጋ አስከፍለውን ይሰጡናል ብለን ስንጠብቅ ከ4ኛ ዙር ከተሰጠ በኃላ " እንኳ ወራት አለፈው ብለዋል።
በመስቀል አደባባይ ስላደረጉት የ4ኛ ዙር ርክክብ ስነ ስርአት በሚተላለፉ ፕሮግራሞች " አርቲስቶች፣ አምባሳደሮች 'በቃሉ የሚገኝ ድርጅት' እያሉ የተሳሳተ መረጃ ለህዝቡ ሲሰጡ አይተን አዝነናል " በማለት መፍትሄ ጠይቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስሞታቸውን "የድርጅቱ ማርኬቲንግ ማናጀር" ናቸው ለተባሉት አቶ ያብስራ ለተባሉት አካል በተደጋጋሚ ቢደውልም ስልካቸው አይጠራም።
ስለጉዳዩ የጠየቅናቸው ሌላኛዋ የድርጅቱ አካል እሳቸውን እንደማይመለከት በመግለጽ፣ " እኔ ምንም ምላሽ ልሰጥህ አልችልም " ብለዋል።
የድርጅቱን አካላት ማግኘት እንዳልተቻለ፣ የድርጅቱ ናቸው የተባሉት የቢሮ ስልኮችም አብዛኛዎቹ እንደማይሰሩ ስልገልጽላቸውም፣ " እኔ ቢሮ አልገባሁም። እረፍት ወጥቻለሁ " ብለዋል።
የድርጅቱ አካላት " ምላሽ አለን " ብለው ብቅ ካሉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ በሩ ክፍት ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#AddisAbabaRevenuesBureau
ማንም ልጅ በልቶ እንጂ ሳይበላ በባዶ ሆድ ትምህርት ቤት ገብቶ መማርም ሆነ መጫወት አይችልም የሚለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰው ተኮር የሆነው የተማሪዎች ምገባ ስንትና ስንት ደሀ እናቶችን እፎይ አሰኘ! ልጇ እየቦረቀ በማለዳ ወደትምህርት ቤት ሲሄድ መርቃ ከመሸኘት በቀር ጓዳዬ ባዶ ነው ምን እቋጥርለታለሁብሎ መጨነቅ ለከተማችን እናቶች ተረት ሆነኮ።የአዲስ አባ ከተማ አስተዳደር የልማት ስራዎች ሰው ተኮር ናቸው ለሚለው አንዱ መገለጫ የተማሪዎች ምገባ ነው።
(የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ)
#ምርጫ2018
ፓርቲዎች ለመጪው ምርጫ እጩዎቻቸውን እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
ገዢው ብልፅግና ፓርቲም ለመጪው ምርጫ የሚወዳደሩ እጩዎችን እያስተዋወቀ ሲሆን ከነዚህም እጩዎች መካከል ጋዜጠኛ ፣ አርቲስት ፣ እንዲሁም አርሶ አደር የሆኑ ይገኙበታል።
በአዲስ አበባ ለምክር ቤት እጩ ሆነው ከቀረቡት መካከል አንደኛው በሙዚቃ አቀናባሪነት የሚታወቀው ካሙዙ ካሳ ነው።
ሙዚቀኛው ፥ ስራው አርቲስት ፣ የትምህርት ደረጃው መካከለኛ ደረጃ ትምህርት እንዲሁም የሚወዳደረው የካ ክፍለ ከተማ መሆኑ ተገልጾ ይፋ ተደርጓል።
ሌላኛዋ የቀድሞ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛዋ ወ/ሮ በሻቱ ቶሎማርያም እዛው የካ ክፍለ ከተማ እጩ ሆና ቀርባለች።
ከዚህ በተጨማሪ አቶ ሹሜ ግዛው የተባሉ አርሶ አደርም በእጩነት ቀርበዋል።
በዚህ ክፍለ ከተማ ሌሎች በፌዴራል ደረጃ፣ በከተማ፣ በክፍለ ከተማ አመራርነት ላይ የሚገኙ እጩዎችም ቀርበዋል።
ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረቡ እጩዎች መካከል ደግሞ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፣ ወ/ሮ አይሻ መሃመድ ፣ ዶ/ር ሌሊሴ ነሜ ይገኙበታል።
መረጃው የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia