tikvahethiopia | Unsorted

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1575599

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። መረጃ እና መልዕክት ፦ 0998999899 ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም 0979333111 @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Subscribe to a channel

TIKVAH-ETHIOPIA

" የትናንቱ ህወሓት ዛሬ የለችም ነገም አትመጣም " - የህወሓት የቁጥጥር ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ነበር ተኽለብርሃን አርአያ

ነባር ታጋዩ በፓርቲው ውስጥ ከማእከላይ ኮሚቴ እስከ ቁጥጥር ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ለዓመታት በኃላፊነት ነበሩ።

ሐቀኛ ፣ ከሙስናና አድሎአዊ አሰራር የፀዱ ናቸው ተብለው በትግል ጎዶቻቸው የሚወደሱት ታጋዩ ከሁለት ዓመታት በፊት የተካሄደውንና የህወሓትን አመራር ለሁለት ቡድን ከፍሎ ክፉኛ ያዳከመው 14ኛ ጉባኤ ህገ-ወጥ ነው ብለው በመቋወም ፓርቲውንና ስልጣናቸውን ለቀዋል።

ታጋይ ተኽለብርሃን አርአያ ጥር 6/2018 Landa Report ከተባለ ሚድያ ጋር ህወሓትን አስመልክተው በሰጡት ከአንድ ሰዓት በላይ ርዝማኔ ባለው ቃለ-መጠይቅ ምን አሉ ?

- ህወሓት በተለይ ከ1993 ዓ.ም የመሪነት መከፋፈል ወዲህ የዓላማ ጥራት ችግር ያጋጠመውና መዳከም የጀመረ ነው።

- ላለፉት 25 ዓመታት ሰብአዊ ሀብቱ ( Social capital ) የበተነ ፓርቲ ነው።

- አመራር እና አባሉ በኪራይ ሰብሳቢነትና ሙስና መዘፈቅ ከጀመረ ቆይቷል።

- አዲስ ተተኪ ሀሳብ የሌለው ፤ በኔትወርክና ጥቅም የተሳሰረ ልል መሪነት ነው ያለው።

- የአሁኑ ህወሓት ስትራቴጂክ አመራር የለውም።

- ስትራቴጂክ አመራር የሌለው ፓርቲ ደሞ ፓርቲ ሆኖ አይቀጥልም።

- የግል ጥቅም እንጂ የአላማ አንድነት ያላሰባሰበው አመራር ቡድኖች እየፈጠረ አንዱ ሌላውን እያሳደደ እየበላ ፓርቲውን ወደ ማይድንበት ደረጃ አድርሶታል።

- ለ60 ቀናት ተሰብስበው ከመጨቃጨቅ ባሻገር የፈጠሩት የአስተሳሰብና የአመራር አንድነት አልነበረም።

- በመጨረሻ አንዱ ቡድን ሌላውን ቡድን ገፍትሮ ነሀሴ 2016 ዓ.ም ቁጥጥር ኮሚሽን ያልደገፈውና ያልተቀበለው ጉባኤ አካሄደ።

- ጉባኤው ህወሓት ወደ አራት ቡድን መከፋፈል ያዋለደ ነው።

- አንዱ ቡድን ስምረት ሌላው ወለዶ የሚባሉ ፓርቲዎች መስርቷል ፤ የተቀሩት ህወሓት ነን የሚሉት ደግሞ ለሁለት ቡድን ተከፍለው ውስጥ ለውስጥ እየተባሉ ነው።

- ደብረፅዮንና ጌታቸው ህወሓት በማዳከም ታሪክ ይጠይቃቸዋል።

- የትናንቱ ህወሓት ዛሬ የለችም ነገም አትመጣም።

- ዛሬ ያለው ህወሓት ስርዓትና መርህ አልባ ነው።

- ለአሁኑ መድረክ የሚዋጅ ህወሓት የለም።

- ስለ ግሉ ጥቅሙ እንጂ ስለ ህወሓት ጥንካሬ የሚጨነቅ አመራር የለም።

ትግራይ እንዴት ነው መዳን ያለባት ?

- የአሁኑ አጀንዳ ትግራይ እንዴት መዳን አለባት እንጂ ፤ ህወሓት እንዴት መዳን አለበት አይደለም መሆን የሚገባው።

- ውይይትን እና ስርዓት ማስቀደምን ያስፈልጋል።

- የተለያዩ አመለካከቶች የሚያስተናግድ አቋፊ መንግስት ማቋቋም ያስፈልጋል።

- የፓለቲካ የስህበት ማእከሉ ፓርቲዎች ሳይሆን መንግስት ስለ ማጠንከር መሆን አለበት።

- ምርጫ መካሄድና አለማካሄድ የህዝብ  እንጂ የፓርቲዎች መብት አይደለም።

- ህዝብ ለምርጫ ይዘጋጃል ፓርቲዎች የሚያወዳድራቸው ሀሳብና እጩ ያቀርባሉ።

- እኔ የሌለሁበት ምርጫ አይካሄድም የሚለው አይሰራም።

- ለምርጫ ምቹና አስቻይ ሁኔታ መፈጠር አለበት።

- ትግራይ በህዘብ ምርጫ የቆመ ስቪል መንግስትና አስተዳደር ያስፈልጋታል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ተወዳጁ የኪነጥበብ ባለሙያ ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ኢቢኤስ ቴሌቪዥን አሳወቀ።

በቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢነት፣ በተዋናይነትና በሌሎች የጥበብ ስራዎች ውስጥ ስመጥር እና ተወዳጅ ከሆኑ የጥበብ ሰዎች አንዱ የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባደረበት ህመም በድንገት ከዚህ ዓለም ተለይቷል፡፡

ለበርካታ ዓመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈው የቤተሰብ ጨዋታ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባለትዳርና የ3 ልጆች አባት ነበር።

#EBS

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" መኪናው ‎ዳገት እየወጣ ባለበት ሰዓት ፍሬን መቆጣጠር ባለመቻሉ ወደ ኋላ በመመለሱ (ስትራፕ አድርጎ) ከሌላ መኪና ጋር በመጋጨቱ ነው አደጋው የደረሰው " - ፖሊስ

ዛሬ ‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ ጭልአሼ ደምባ ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ በክፍት አይሱዙ መኪና ተጭነው ለቅሶ ደርሰው ሲመለሱ በነበሩ ሰዎች ላይ በደረሰ ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ የ5 ሰዎች ሕይወት ማለፉ የወረዳው ፖሊስ ገልጾልናል።

የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር አብረሃም አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፤ ‎አደጋው የደረሰበት የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ - 3 -13227 አአ የሆነ ተሽከርካሪ ነው።

" ለቅሶን በማሳበብ ከ30 በላይ ተሳፋሪዎችን ጭኖ ሲጓዝ ነበር፤ ዳገት እየወጣ ባለበት ፍሬን መቆጣጠር ባለመቻሉ ወደ ኋላ በመመለሱ (ስትራፕ አድርጎ) ከሌላ መኪና ጋር በመጋጨቱ አደጋዉ ተከስቷል " ብለዋል።

‎በአደጋውም እስካሁን 4 ወንድ እና 1 ሴት በድምሩ የ5 ሰዎች ሕይወት ማለፉንና በ7 ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት እንዲሁም በ24 ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱንና ጉዳት የደረሰባቸው ወደ ተለያዩ የሕክምና ተቋማት መወሰዳቸውንም አስታውቀዋል።

‎አሽከርካሪው መጠነኛ ጉዳት ደርሶበት በአሁኑ ሰዓት በሕግ ቁጥጥር ስር መሆኑንም የቦረዳ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር አብረሃም አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ለታ ተስፋዬ (ዶ/ር) አርፈዋል መባሉ እውነት ነው" - የደምቢ ዶ/ሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት

የቀድሞ የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ለታ ተስፋዬ ጁሌ (ዶ/ር)፣ ወደ አሜሪካ ለስራ ሂደው እንደነበርና "ቨርጂኒያ" ባረፉበት ሆቴል "ሞተው መገኘታቸው" በማህበራዊ ሚዲያው ተሰራጭቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ለጊዜው የቤተሰቦቻቸውን ስልክ ባያገኝም፣ ቀድሞ በኃላፊነት ደረጃ የሰሩበት ዩኒቨርሲቲ አካላትን የጠየቀ ሲሆን፣ "ህይወታቸው አልፏል" መባሉ እውነት መሆኑን ገልጸውልናል።

ለታ ተስፋዬ (ዶ/ር) " ህይወታቸው አልፏል " መባሉ እውነት ነው ? የተቋሙ የቀድሞ ፕሬዚዳንት እንደመሆናቸው መጠን ጉዳዩን አጣርታችሁ ነበር? ያልናቸው የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ታደሰ ረጋሳ (ዶ/ር)፣ " አርፈዋል መባሉ እውነት ነው " ብለውናል።

የሞታቸው ምክንያቱ ምን እንደሆነ ዩኒቨርሲቲው ማወቅ ችሏል ? ለሚለው ጥያቄም፣ " ምክንያቱን አልሰማንም" ፣ ወደ አሜሪካ በሄዱበት ሞቱ መባሉ ግን "ትክክል ነው" ብለው፤ "ትናንት ነው ሞቱ የተባለው" ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ።

የቀድሞ የዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት የነበሩ አሁን ተመርቀው የወጡ ሌላኛው አካል ደግሞ፣ " እውነተኝነቱን ማረጋገጥ ችያለሁ ዶ/ር ለታ ማረፉ እውነት ነው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" አሜሪካ ነው ያረፉት " ያሉት እኝሁ አካል፣ "እኔ ባለፉት ሁለት ዓመታት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት ነበርኩ፤ ግቢ በነበረኝ ቆይታ አውቃቸዋለሁ፤ ዶ/ር ለታ በቴክኖሎጂ ዘርፉ ተማሪዎቹን ሲያግዙ፣ የግቢው ገጽታ ሲሰሩና ሌሎች ኃላፊነቶችን ሲወጡ የነበሩ በጣም ጠንካራ ፕሬዚዳንት ነበሩ " ሲሉ ገልጸዋቸዋል።

" ያኔ ከእኔም ጋር በቅርበት እንተዋወቅ ነበር፤ አብረንም እንሰራ ነበር " ሲሉ አስታውሰው፣ "በሞታቸው ጣም አዝኛለሁ፣ ለአካባቢውም ሰዎች በጣም ትልቅ ሀዘን ነው" ብለዋል።

ዩኒቨርሲቲው ዛሬ ከሰዓት ባወጣው የሐዘን መግለጫ፣ "የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ለታ ተስፋዬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል" ብሏል።

በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር እና በፊዚክስ ዘርፍ ትልቅ አሻራ ያሳረፉ መሆኑን ገልጾ፣ "ለ6 ዓመታት በደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ በፕሬዚዳንትነት አገልግለዋል" በማለት፤ አሟሟታቸውን በተመለከተ "ባልተጠበቀ በድንገተኛ ህይወተ እልፈት" ከማለት ውጭ ያስቀመጠው ዝርዝር የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ፣
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

"በ10 እና በ15 ደቂቃ ውስጥ ሱቅና መኖሪያ ቤት እንዴት ሆኖ ነው የሚደመሰሰው? ምን ማለት እንደሆነ አልገባኝም" - እንባ የሚተናነቃቸው እናት

በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 4 ነዋሪ ከነቤተሰባቸው የሚኖሩበት "50 ዓመት የኖሩበት የይዞታ" ቤታቸው፣ "'ዛሬ 8 ሰዓት ሊፈርስ ነው' ተባልኩ" ሲሉ ቅሬታቸውን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ገልጸዋል።

ምን አሉ? "ከዚህ በፊት መጥተው በ13.5 ለክተው ነበር ቦታውን። አሁን እንደገና ትናንት መጥተው ሙሉ ቤቱን ለኩት። ሱቅ፤ መኖሪያ ቤት አለ። ሁለቱንም የያዘ ነው ግቢው። ከዚያ በኋላ 'በሙሉ ነው የሚፈርሰው' ብለው እያንዳንዱን ቤቱን ለኩት።

እንዴት ይሆናል? ልኬት አውጥታችኋል፤ ለመንገድ ልማት 13.5 ለክታችኋል እሱን ተቀብለናል ብዬ ስላቸው 'ለመንገዱ ርዝመት ነው እንጅ ልኬት አይደለም' አሉኝ። ምንም መናገር አልቻልኩም ለዛ ነው ብዬ ዝም አልኩ።

እንዳለ ሙሉውን ቤት እያንዳንዱን ለክተው ጨርሰው ዛሬ ጠዋት መጥተው 'እቃችሁን አውጡ ዛሬ እናፈርሳለን' አሉ።

የ95 አመት እናት አለችኝ። ሱቁ መተዳደሪያችን ነው። ቤቱ መኖሪችን ነው። ሙሉ ንብረታችን ያለበት ቤት ነው። በ10 እና በ15 ደቂቃ ውስጥ ሱቅና መኖሪያ ቤት እንዴት ሆኖ ነው የሚደመሰሰው? ምን ማለት እንደሆነ አልገባኝም።

እኛእኮ ልማቱን እንቀበላለን፤ ተቀብለናልም። ይልማ። ሀገራችን እንድትለማ ነው የምንፈልገው። ግን አግባብ ባለው መንገድ እኛም ሳንጎዳ፣ ብዙ ነገር ተነጋግረን መፈረም ያለብንንም ፈርመን መሆን አለበት። ያለወረቀት/ደብዳቤ ሜዳ ላይ መጥተው ለምንድን ነው እንዲህ የሚያደርጉት?" ብለዋል።

እኝሁ እናት ይህን ያደረጉት እነማን እንሆኑና ህጋዊ ደብዳቤ ይዘው እንደሆን ስንጠይቃቸውም፣ "ምንም ነገር የለም። ከወረዳ 4 ነው የመጣነው፤ ከቦሌ ክፍለ ከተማ ነው የመጣነው' ነው የሚሉት። ከአትላስ ጀምሮ እያፈረሱ፤ '8 ሰዓት እናንተ ጋር እንደርሳለን፤ እስከዛ እቃችሁን አውጡ' ብለው ሄዱ" ሲሉ ተናግረዋል።

"ለመንገድ ልማት እሺ ብለን ተቀብለን ለክተዋል። መስመር አድርገው ነው የሄዱት። አሁን ሙሉውን ሱቁንም መኖሪያ ቤቱንም እንዳለ ደምስሳችሁ ባዶ እንዲሆን ነው የምንፈልገው አሉ" ብለው፣ "እቃችንን፣ ንብረታችንንስ የት ወስደን እንጣለው? አስፓልት ላይ እናስቀምጠው አውጥተን? ግራ ነው የገባን። ምንድን ነው እንዲህ አይነት ነገር?" ሲሉ ጠይቀዋል።

ልዩ ቦታውን ስንጠይቃቸው፣ "በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አዲስ አለማየሁ ትምህርት ቤት ፊት ለፊት በእምነት መድኃኒት ቤት ከሚለው ጀምሮ እስከ ሱቁ ድረስ ነው የኔ ቤት" ብለው፣ ቪዲዮም ቀርጸው ልከዋል።

"ቤቱ የግል ይዞታችን፤ ንብረታችን ነው። ወደ 50 ዓመት የተኖረበት ቤት ነው" ያሉት እኝሁ እናት፣ "ልማቱን ተቃዋሚ አይደለሁም፤ ግን በትክክለኛ በህጉ መንገድ መፍረስ ያለበት ይፈርሳል ለመንገድ፤ የቀረውን ደግሞ ማልማት ያለብኝን መንግስት በሰጠኝ ዲዛይን ማልማት እችላለሁ። ከዚህ በፊት ተጠይቅ አላውቅም" ብለዋል።

ወደ ቦሌ ክ/ክፍለ ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን፣ አመራሮቹን የመጠየቅ ሙከራው ይቀጥላል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

በፈለጉት መጠን - በፈለጉት ጊዜ - በፍጥነት!

ከአቢሲንያ ወደ አቢሲንያ ገንዘብዎን ያለገደብ!

ከአቢሲንያ ወደአቢሲንያ የፈለጉትን የገንዘብ መጠን ያህል በየትኛውም ሰዓት ማስተላለፍ ይችላሉ።

👉 ከአቢሲንያ ጋር አሁኑኑ ይጀምሩ – ያድሱ እና ይደጉ!

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

በጋምቤላ ክልል ሁሉም አድማ ብተናና መደበኛ ፖሊስ አባላት ለምን ትጥቅ ይፈታሉ ? ትጥቅ ያስረክባሉ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጋምቤላ ክልል እስከ ነገ 11:00 ሰዓት ድረስ የአድማ ብተናና መደበኛ ፖሊስ አባላት ትጥቅ ፈተው እንዲያስረክቡ ስለተላለፈው አስቸኳይ ጥብቅ መመሪያ አዲሱን የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አነጋግሯቸዋል።

‎በቅርብ ወደ ኃላፊነት የመጡት ኮሚሽነር ኡማን ኡጉሉ በክልሉ ተፈጥሮ በነበረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ለፀጥታ መዋቅሩ #የተሃድሶ_ስልጠና መስጠት አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በክልሉ በ3 ዞኖች ስር በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ኢታንግ ልዩ ወረዳ የሚገኙ የአድማ ብተናና መደበኛ ፖሊስ አባላት ትጥቃቸዉን ግምጃ ቤት በማስረከብ ወደ ተሃድሶ ስልጠና እንዲገቡ መመሪያ መተላለፉን ገልፀዋል።

‎የቆይታ ጊዜያቸውን፣ የስልጠናውን ቦታና ሁኔታ እንዲሁም ፖሊሳዊ አገልግሎት በማን ይከናወናል ?ለምን ስልጠናዉ በዙር አልተከፋፈለም ? በሚል ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተነሳላቸዉ ጥያቄ አዲሱ ኮሚሽነር ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

‎የፖሊስ አመራርና አባላትስ ምን አሉ ?

‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጋምቤላ ክልል የተለያዩ መዋቅሮች የሚገኙ የፖሊስ አባላትና አመራሮችን አነጋግሯል።

" በክልሉ ተፈጥሮ ከነበረው የፀጥታ ችግር ጋር ተያይዞ የተሃድሶ ስልጠና መዘጋጀቱ አስፈላጊ ነው ብለን እናምናለን " ያሉ ሲሆን ቅሬታ አሳድሮብናል ያሉትን ጉዳይ ተናግረዋል።

ይኸውም " ስልጠናዉ በዙር አለመደረጉ በፖሊሳዊ አገልግሎቶች ላይ ክፍተት እንደሚፈጥር ፤ በሌላ መልኩ የመመሪያው አስቸኳይነት፣ በህመምና ወሊድ ምክንያት እረፍት ላይ ያሉ ጭምር እንዲገቡ አስገዳጅ መመሪያ መሰጠቱ " ቅሬታ ፈጠረብን ብለዋል።

‎" የፖሊስ አዛዥነት የስራ ኃላፊነት ' ለሚሊሻ አስረክብ ' ተብያለሁ " ያሉ አንድ የፖሊስ አመራር " ለክልሉ ሰላምና መረጋጋት የሚከፈል የትኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ስለሆንኩ በምመራው ወረዳ የሚገኙ የፖሊስ አባላት በአንድ ቀን ትጥቅ እንዲያስረክቡ አድርገናል " ብለዋል።

‎ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ ተጨማሪ መረጃ የምናደርስ ይሆናል።

#TikvahErhiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አለሙ ጨእቾ ናቸው፣ የፓርቲው ም/ሊቀመንበር ባለቤታቸው ናቸው። እኔ ፀሐፊ ነበርኩ ሊቀመንበሩ የአጎቱን ልጅ በኔ ቦታ መርጦታል " - አቶ ሁሴን ቃሲም

" 'አንድ ቤተሰብ ነው' የሚባለው በእርግጥ ምክትሏ ባለቤቴ ነች፤ በህዝብ ነው የተመረጠችው። ፀሐፊው የወንድሜ ልጅም አይደለም በዝምድና አንገናኝም " - የፓርቲው ሊቀመንበር

ሲዳማ ክልል ላይ አዲስ የተመሰረተው "ሲዳማ ራሽናል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ" (Sidama Rational Party) ከመስራቾቹ በኩል ከወዲሁ ተቃውሞ ተነሳበት።

በመጀመሪያ " ጠቅላላ ጉባዔ ፀሐፊ አድርጎ ነበር የመረጠኝ " ሲሉ የሚያስታውሱት አቶ ሁሴን ቃሲም፣ " ምርጫው ፍትሃዊ አይደለም፤ ከአንድ ቤተሰብ የተሰባሰቡ ናቸው ብዬ ባልኩት ዳግም እንዲካሄድ ከተባለ በኋላ እኔን ከውስጥ አስወጡኝ " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አቶ ሁሴን፣ " ህዝብ ይፈልገኛል፤ እነርሱ ግን በውስን ሰዎች ከስልጣን አግልለውኛል " ሲሉም ፓርቲውን ከወዲሁ ተጠያቂ አድርገውታል።

" በመጀመሪያ ጊዜ ጠቅላላ ጉባዔ ሲጠራ ከምርጫ ቦርድ 5 ሰዎች ከአዲስ አበባ ተልከው ነበር፤ በዚያ መረጡንና እንደገና መጨረሻ ላይ ማታ ግርግር ነበር " ብለው፣ የስልጣን ስብጥር ላይ ችግር መኖሩን አስረድተዋል።

" የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አለሙ ጨእቾ ናቸው፣ የፓርቲው ም/ሊቀመንበር ባለቤታቸው ናቸው። እኔ ፀሐፊ ነበርኩ ሊቀመንበሩ የአጎቱን ልጅ በኔ ቦታ መርጦታል " ሲሉም አክለዋል።

" ሌላ አንድ ገንዘብ ያዥ የተደረገ ልጅ አለ፤ ብዙ ምዝበራ አካሂዷል። ከአውሮፓ መንግስት የተሰጠንን ኮምፑዩተር እና ፕሪንተር ሁሉ ሸጦ በልቶታል። ከእሱም  ስንከራከር ስለነበር 'ካልወጣ' ብሎ ነው ተፅዕኖ ያደረገብኝ " ነው ያሉት።

" ሊቀመንበሩ አሉታዊ ተፅዕኖ አድርጎብናል " የሚል ቅሬታ ያነሱት አቶ ሁሴን፣ የፓርቲው አመራሮች " ከአንድ ወገን የተሰባሰቡ ናቸው " ሲሉ ገልጸው፣ ግን ፓርቲው ትክክለኛ ጥያቄና ዓላማ ይዞ እንደተነሳ ተናግረዋል።

" በስልጣን ላይ ያሉት የፓርቲው ሰዎች ከአንድ ቤተሰብ ናቸው " ብለው፣ " ሌላ ሰው እንዳይገባ አድርገው ያልሆነ ምክንያት እያቀረቡ ያጉላላሉ " ሲሉ ጠቅሰው፣ " እኔ ብቻ ሳልሆን በመጀመሪያ ምክትል ሊቀመንበር ተደርገው የተሾመ ነበር፤ አሁን እሱንም እኔንም አገለሉን " ብለዋል።

" የሊቀመንበሩና ፀሐፊውን ጀርባ ስናጠና የጥቅም ትስስር አላቸው " ሲሉ የተቹት አቶ ሁሴን፣ " መጀመሪያ 33ቱም ሰዎች እያንዳንዳቸው 500 ብር አዋጡ ተብሎ " እንደነበር አስታውሰው፣ "በቃለ ጉባዔም ተነጋግረን መወሰን አለብን ያልወሰነውን ለምንድን ነው አዋጡ የሚባለው ? " ብለው ሲጠይቁ፣ አለመግባባት መፈጠሩን አስረድተዋል።

" ፓርቲው ለግለሰብ፣ ለግል ጥቅም ተብሎ የተደራጀ አይደለም። የህዝብ ፍላጎት ሌላ ነው፤ መልካም አስተዳደር ይፈልጋል፤ ዘረኝነትን አይፈልግም። መጀመሪያ የተነሳንበት አላማ አሁን የሚስተዋለው አልነበረም፤ መጨረሻው በተወሰኑ ግለሰቦች ነው ችግሩ የተፈጠረው " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ፓርቲው ከወዲሁ "ትችት" እና "የአግላይነት" ቅሬታ እየተነሳበት ነው፤ አላማውን እንዴት ማሳካት ይችላል? የፓርቲው አመራሮች "የአንድ ቤተሰብ አባል ናቸው"፣ ፀሐፊው የእርስዎ የአጎት ልጅ"፣ የፓርቲው ም/ሊቀመንበርም "የእርስዎ ባለቤት" ናቸው ተብሏል? ምላሽዎ ምንድን ነው? ሲል የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አለሙ ጨእቾን ጠይቋል።

ምን መለሱ ?

" መጀመሪያ በሸንጎ ቀርቦ ነው ይህ ሁሉ የተደረገው። ከመነሻው ጀምሮ ለዚህ ፓርቲ ያለውን በደል ለማስተካከል እኛ እየታገልን አቶ ሁሴን ቃሲም ከጊዜ በኋላ መጥቶ መጀመሪያ ስንካሰስ ከዚያ በኋላ የራሱን ስራ ለመስራት ወደቤቱ የገባ ነው።

ህዝብ አልመረጠውም። ህዝብ ካልመረጠው አላስቀምጠውም። ህዝብ 'ጨቅጫቃ ነው፤ የሚመች ሰው አይደለም' በሚል እጅ አጥቷል። ቅሬታ ካለው አቅርብ ተብሏል ከዚህ በፊት፤ አላቀረበም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ሊቀመንበሩን፣ አቶ ሁሴን ቃሲም ግን "ህዝብ መርጦኛል" ነው ያሉት ሲላቸውም፣ "ህዝብ እንዳልመረጠው ህዝብ ዳግም ይሰባሰብና ይበል፤ የሱን ጉዳይ። እንዳውም አጭበርባሪ በመሆኑ የመጡትን ሰዎች ረብሾ ብዙ ሁከት ነው ያነሳው" ሲሉ ከሰዋል።

አቶ አለሙ፣ ስልጣን የያዙ የፓርቲው አመራሮችን በተመለከተ ለተነሳው ቅሬታ ደግሞ፣ "'አንድ ቤተሰብ ነው' የሚባለው በእርግጥ ምክትሏ ባለቤቴ ነች፤ በህዝብ ነው የተመረጠችው። ፀሐፊው የወንድሜ ልጅም አይደለም በዝምድና አንገናኝም" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

በሌላ በኩል፣ የፓርቲው ሎጎ ላይ ያለው የበግ ምልክት ምንን የሚያመላክት ነው? ስንል ላቀረብነው ተጨማሪ ጥያቄ ደግሞ፣ "የበጉ ምልክት ሰላም፤ ነጻነት ነው። ህዝብን ያገናኛል፤ ሰው አይገፋም፣ አይጎዳም ብለን ነው ምስጢሩን ያስቀመጥነው" ሲሉ መልሰዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvaherhiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ

" ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ራስገዝ ይሆናሉ ተብለው ከሚጠበቁ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ለመሆን የሚያስችለንን ስራ እየጨረስን ነው"-ጎንደር ዩኒቨርሲቲ

የጎንደር ዪኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር ከተያዙ እና በቀጣይ ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ ራስ ገዝ ይሆናሉ ተብለው ከሚጠበቁ የኒቨርሲቲዎች አንዱ ነው።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አጸደወይን "በሚወጣው መስፈርት ተገምግሞ ማረጋገጫ እየተሰጠ ለዛ ብቁ የሆኑ ተቋማት ከ2019 ጀምሮ ይሆናሉ ተብሏል ከዛ ውስጥ እኛ አንዱ እንሆናለን ብለን እየሰራን ነው" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ዶ/ር አስራት" የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ እንደ ሴክተር የከፍተኛ ትምህርት ሴክተር እቅድ ሲታቀድ በአስር ዓመት ውስጥ ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ እንሆናለን ብለን አቅደን ነው ስንሰራ የነበረው" ያሉ ሲሆን ለእዚህም የተለያዩ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አስረድተዋል።

40 የሚሆኑ የተለያዩ ሰነዶችን መዘጋጀታቸውን ገልጸው በተጨማሪም ከተቋሙ ስትራቴጂክ እቅድ እና ከሴኔት ሌጅስሌሽን ጀምሮ የተለያዩ መመሪያዎችን፣ ፖሊሲዎችን ሲዘጋጁ መቆየታቸውን ጠቅሰዋል።

ፖሊሲዎቹ ከተዘጋጁ በኋላም የአሜሪካ ኤምባሲ ለዩኒቨርሲቲው የቀጠራቸው አማካሪዎች የማማከር ስራዎችን እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አጸደወይን የዩኒቨርሲቲውን የራስ ገዝነት ጉዞ በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ?

በአሁኑ ሰዓት ዝግጅታችን ከሞላ ጎደል ጨርሰናል ማለት ይቻላል።

አሁን እየሰራን የምንገኘው የሰልፍ አሰስመንት (Self-assessment) ወይም ደግሞ የት ላይ ነን ትምህርት ሚኒስቴር ያወጣው ራስ-ገዝ ለመሆን ያወጣቸው መስፈርቶች፣ ያወጣቸውን ነጥቦች ራሳችን በራሳችን ገምግመን የት ላይ እናርፋለን የሚለውን አንድ ቲም አቋቁመን እየሰሩ ነው የሚገኙት።

በዛ መስፈርት መሰረት 60 እና ከዚያ በላይ ካመጣን ወደ ራስ-ገዝነት እንሸጋገራለን ወይም ደግሞ ለጥያቄ ብቁ ነን ማለት ነው ይህንን እየሰራን ነው የምንገኘው።

ከሞላ ጎደል የራስ-ገዝነት ደረጃ መጎናፀፍ የፋይናንስ ነፃነትንም፣ የአስተዳደር ነፃነትንም፣ የሰው ሀብት ነፃነትንም የሚያጎናፅፍ ነው።

ከብዙ ዓመታት በኋላ የተገኘ እድል በመሆኑ ይህንን እድል ለመጠቀም እየሰራን ነው የምንገኘው።

እንግዲህ በእኛ በኩል እንደ ትምህርት ሚኒስቴርም አሁን ቀጣይ ይሆናሉ ተብለው የተያዙ ዩኒቨርሲቲዎች ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ ይሆናል ተብሎ ነው የሚጠበቀው።

ይህ ማለት እንግዲህ የሚወጣው መስፈርት ተገምግሞ ማረጋገጫ እየተሰጠ ለዛ ብቁ የሆኑ ተቋማት ከ2019 ጀምሮ ይሆናሉ ተብሏል።

ከዛ ውስጥ እኛ አንዱ እንሆናለን ብለን ነው እየሰራን ያለነው ወደፊት ደግሞ የሚሆነውን እናያለን"ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

አንዱን እንዴት ማፈስ ይቻላል?

በቅርንጫፍም ሆነ በዲጂታል አማራጭ አዲስ ሒሳብ በመክፈት ተቀማጭ ሲያደርጉ፣ ነባር ሒሳብዎ ላይ ተጨማሪ ገቢ ሲያደርጉ፣ በፊት ገፅታዎ እና በጣት አሻራዎ የደንበኝነት ምዝገባ ሲያካሂዱ፣ በባንካችን የውጭ ምንዛሬ ሲመነዝሩ ወይም ገቢ ሲያደርጉ አስደሳች ሽልማት የሚያስገኝ የዕጣ ቁጥር ያገኛሉ።

አዲስ ሀዩንዳይ ኤሰንት፥ መኪና ቲቪ፥ ላፕቶፖችን ጨምሮ በየ15 ቀኑ ፍሪጅ፣ የልብስ ማጠቢያ ማሽን እና ሌሎች አስደሳች ስጦታዎችን ያግኙ። አገልግሎቶቹን ደጋግመው በመጠቀም የዕጣ ቁጥር ያሳድጉ።

👉 ከአቢሲንያ ጋር አሁኑኑ ይጀምሩ – ያድሱ እና ይደጉ!

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#አሁን : በሀዋሳ ከተማ ወደ አዲሱ መናኸሪያ መስመር አጠና ተራ አካባቢ ከባድ የእሳት አደጋ መከሰቱን የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች ጠቁመዋል።

አቅራቢያው ትልቅ ትራንስፎርመር እንዳለ ገልጸው እሳቱ ከተነሳ 1 ሰዓት እንዳለፈው አንድ የእሳት አደጋ መኪና መጥቶ ውሃ አልቆት እንደተመለሰ አስረድተዋል።

ህዝቡ በራሱ እሳቱን ለማጥፋት ርብርብ እያደረገ መሆኑንም አመልክተዋል።

እሳቱና ጭሱ ከወልደ አማኑኤል አደባባይ ወደ መናኸሪያ መንገድ ሲኬድ እንደሚታይ ገልጸው በአስቸኳይ የሚመለከተው አካል ርብርብ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

#Natnael

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#የአእላፋትዝማሬ

ነገ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ።

ከቀን 6:00 ጀምሮ መንገዶች ይዘጋሉ።

ነገ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ የሚካሄደው የአእላፋት ዝማሬ መርሐ ግብር ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ይፋ አድርጓል።

መርሀ ግብሩ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅም፡- 

➡️ ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ  የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፤

➡️ ከቦሌ በጌቱ ኮሜርሻል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ ወይም ደንበል አካባቢ፤

➡️ ከመስቀል ፍላወር ወደ ደንበል የሚወስደው መንገድ በተለምዶ ጋዜቦ አደባባይ፤

➡️ ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ለከባድ ተሽከርካሪዎች አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ፤ ለቀላል ተሽከርካሪዎች ጥላሁን አደባባይ፤

➡️ ከጎፋ በአዲሱ መንገድ ወደ  ለገሃር መብራት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተ-ክርስቲያ መስቀለኛ፤

➡️ ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ  ለገሃር መብራት፤

➡️ ከአምባሳደር  መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ሐራምቤ መብራት፤

➡️ ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ- መንግሥት  የሚወስዱ መንገዶች ከታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ መርሀ ግብሩ እስኪጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

ከዛሬ ታህሳስ 27 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በሚዘጉ መንገዶች ላይ ለረጅም ሆነ ለአጭር ሰዓት ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ ፦
📞በ011-1-26-43-59 ፣
📞በ011-5-52-63-02/03፣
📞በ011-5-52-40-77፣
📞በ011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 በነፃ የስልክ መስመሮች በ987፣ 991፣ 816 እንዲሁም በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያን (Citizen Engagement Application) EFPApp በመጠቀም ጥቆማ መስጠት ይቻላል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" እኔ የማወጣው 'ጉማ' የለም፤ የኦሮሞ ህዝብ እንዲያውቅልኝ የምፈልገው ነገር እጄ ከዚህ ነገር ንፁህ ነው " - ድምፃዊ አንዱአለም ጎሳ

ድምፃዊ አንዱአለም ጎሳ ከሰሞኑ ሽምግልናና ከፍቅረኛው ቀነኒ አዱኛ አሟሟት ጋር በተያያዘ በቪዲዮ መልዕክቱን አስተላልፏል።

ድምፃዊው " እኔ የማወጣው 'ጉማ' የለም " በማለት እጁ ከነገሩ ንፁህ እንደሆነ " የኦሮሞ ህዝብ ይወቅልኝ " ሲል ተናግሯል።

" እኔም መጥፎ ሃዘን ውስጥ ነኝ፤ ሃዘኔን እንኳን በደንብ ማዘን አልቻልኩም " ያለው ድምፃዊው " እስር ቤት ነበርኩ ከዛ ስወጣ ይኸው በመጥፎ ነገር ቀጥሏል " ብሏል።

ድምፃዊ አንዱአለም ጎሳ " ያጠፋኋት ወይም የጎዳኋት ነገር የለም፤ የማወጣው 'ጉማ' የለም " ያለ ሲሆን " ሽማግሌ የላኩት ለእኔ ወይም ለሌላው እንዲወግኑ ሳይሆን እኔም እውነት አለኝ ሚስቴን አጥቻለሁ ያንን እውነት ተመልከቱልኝ ብዬ ነው  " ሲል ገልጿል።

በዝርዝር ምን አለ ?

" እኔና ቀኖ ቆንጆ የፍቅር ግንኙነት አለን ግን ጭንቀት ነበረባት ጭንቀቱ ቤት ከመዋል ይሆናል ብዬ አብረን እንድንሰራ የኢንተርቴይንመንት ስራ ከፍቼ ሰጥቼያት ነበር። ይህንን ካደረኩ በኋላ ራስን የማጥፋት ሙከራ ማድረጓን ቀጥላለች።

ነገሩ ከአቅሜ በላይ ስለሆነ ለአባቷ አስደውዬ ' ይህ አጋጥሞኛል ፣ ይህ ችግር ደርሶብኛል መኖር አልቻልኩም ' አለችው ፤ እኔም ተቀብዬ እንድትጨነቁ አይደለም ነገር ግን ከቀን ወደ ቀን እየከሳች ነው መፈታት አለበት ነገሩ ብያለሁ ለማንም ጠርቼው ይህንን ነገር ፍቱላት ብዬ ተሰብሰቡ ብዬ አውርቼዋለሁ ሆኖም መልስ የሰጠም ሆነ ተገናኝቶ የመከረ በጉዳዩ ላይ የለም ስለእሷም የጠየቀኝ የለም " ብሏል።

ድምፃዊ አንዱአለም ጎሳ ፍቅረኛው ቀነኒ አዱኛ በተደጋጋሚ ራሷን ለማጥፋት እንደምትሞክር ተናግሯል።

ህይወቷ ባለፈበት ቀን ስለተፈጠረው ነገር ሲያስረዳ ምን አለ ?

" ሆስፒታልም አብረን ሄደናል የልደቷን ፎቶ የተነሳችበት ቦታ የወስድኳት እኔ ነኝ ከዛ ስወጣ ሰዎችን ለማግኘት ሄድኩ እሷ በጊዜ ልግባ ብላ ነው የተለያየነው።

ማታ ጥሩ ጊዜ እያሳለፍን ነበር ለወንድሟም ስትደውል ነበር ድንገት ስለ ውሎዋ ስጠይቃት ' እኔን የማመን ችግር አለብህ ' በማለት ከምንተኛበት ተነስታ ሄደች።

ስትቆይብኝ ተጠራጥሬ ሄድኩ ሌሎች ክላሶች ውስጥ የለችም ቼክ ሳደርግ ኪችኑ ዝግ ነው አበባ ነገር ላይ ቆሜ ሳያት የልብስ ማጠብያ ማሽኑን ተደግፋ ላርጎ ስትጠጣ ነበር ምነው ቀኖ ብዬ በዛ ዘልዬ ገባሁ።

ከዚህ ቀደም እንዲህ ዓይነት ነገር አላደርግም ብላ ቤተሰብ ፊት ቃል ገብታልኝ ነበር። ወንድሜም፣ ጓደኛዋም እንዲመክሯት ነግሪያቸው ነበር።

በተደጋጋሚ ቃል ገብታልኝ ነበር ነገር ግን ቃሉን ስላልጠበቀችልኝ በዛን ጊዜ እኔም ሰው ነኝ እና እንደዚህ አይነት ህይወት መኖር አልችልም። በተደጋጋሚ እያደረግሽ ስለሆነ ነገ ቤተሰብ ጠርቼ እንለያያለን አልኳት።

ከዛ በሩን ለመክፈት በሩ ጋር እንደደረስኩ ' እንደዛ ነው እንዴ ? ይስፋልክ ' ብላ ከፎቅ ላይ ዘለለች። እኔ ልይዛትም አልደረስኩም ፣ መጮህ ብቻ ነበር የቻልኩት። ጮህኩኝ፣ ልጆቹም ተነሱ። ያለው ነገር የተፈጠረው ይህ ነው " ሲል አስረድቷል።

አክሎም ፦

" ቀኖዬ ያደረገችኝ ነገር የለም እሷን የምጎዳበት ምንም ምክንያት የለም ተይ ብዬ መምከር ከመደገፍ ውጪ ያደረኳት ነገር የለም እጄ ንፁህ ነው ሽማግሌዎቹ ይህንን ይመልከቱልን ከቤተሰቧ ጋር ግንኙነቴን ያስቀጥሉ ብዬ ነው የላኩት ስለ 'ጉማም' አልተወራም። እጄ ንፁህ ነው የማወጣው 'ጉማ' የለም " ሲል ገልጿል።

ድምፃዊ አንዱአለም ፖሊስ የቀነኒ አዱኛን ዲያሪ ማግኘቱን ገልፆ " በየገፁ ብዙ ነገር ያወራል ለቤተሰብ ለእኔም ለሁሉም በዲያሪው ላይ ስንብት አለ " ብሏል።

" ከቻላችሁ እውነትን በጥልቀት ተመልክታችሁ ድረሱበት በአሉባልታ ያለኝን ግንኙነት አታፍርሱ እሷም በሰላም ትረፍ ነፍሷንም እረፍት አትንሷት " ያለው አንዱአለም ጎሳ " እኔም ተረጋግቼ ለምትጠይቁት ጥያቄ መልስ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ " ብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" 23 ተከሳሾች አንድ መዝገብ ላይ ነበሩ፤ 2 አመት ሊሆነን ነው ክርክር እያደረግን፤ ሦስቱ ህሙማን ስለሆኑ የዋስትና ክርክር አድርገን በጣም ላመማቸው ዋስትና ፈቅደዋል፤ ውጭ ሆነው ይከራከራሉ " - ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ

በሽብር ወንጀል ተከሰው ሁለት ዓመታት ለተቃረበ ጊዜ የታሰሩ በአንድ መዝገብ ካሉ 23 ተከሳሾች መካከል ሦስቱ በገንዘብ ዋስትና ተፈትተው ክሳቸውን ከእስር ቤት ውጭ ሆነው እንዲከራከሩ መደረጋቸውን ጠበቃቸው አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ዋስትና ከተፈቀደላቸው እስረኞች መካከል፣ የቀድሞ የፓርላማ አባልና ኢዴፓ አመራር አቶ አብዱራህማን አህመዲን እንደሚገኙበት፣ ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እንዲወጡ ዋስትና የተፈቀደላቸው እያንዳንዳቸው 200 ሺሕ ብር በማስያዝ መሆኑም ተገልጿል።

" ለአቶ አብዲራህማን አህመዲንም የዋስትና ክርክር አድርጌ በዋስ ነው እንጅ ዝም ብሎ የተፈታ የለም " ያሉት ጠበቃ ሰለሞን፣ " በእነርሱ መዝገብ ሥር ያሉ 23 ተከሳሾች ከአመት በላይ ሆኗቸዋል " ብለዋል።

" ከዚያ ክርክር አድርገን በሰነድ ማስረጃ ላይ አስተያየት ሰጥተን ዋስትና ከሚከክለው ዋስትና ወደ ማያስከለክለው ፍርድ ቤቱ ቀየረው" ሲሉ አስታውሰው፣ "እንደገና ድጋሚ የዋስትና ክርክር አደረግን፤ ለሦስት ሰዎች ዋስትና ተፈቀደ፤ ሦስቱ ወጡ፣ ሌሎቹ ተከላከሉ ተብለዋል" ሲሉም አክለዋል።

አቶ አብዲራህማን ከዚህ በፊት ድምፅ ስላልተውንላቸው ነው እንጅ፤ የቀድሞ ፓርላማ አባል፣ የኢዴፓ አመራር እንደነበሩ ያስረዱት ጠበቃ ሰለሞን፣ " ሀይለኛ ህመምተኛ ቢሆኑም፤ ማንም ሰው ድምፅ አልሆነናቸውም ነበር፤ ለዚያ ነው አሁን ሚዲያ ላይ የወጡት " ሲሉ ገልጸዋል።

" 23 ተከሳሾች አንድ መዝገብ ላይ ነበሩ እኔ ጠበቃቸው ነኝ ሁለት አመት ሊሆነን ነው ክርክር እያደረግን ሦስቱ ህመምተኞች ስለሆኑ ዋስትና ክርክር አድርገን በጣም ላመማቸው ዋስትና ፈቅደዋል፤ ውጭ ሆነው ይከራከራሉ " ሲሉም ለቲክቫህ ተናግረዋል።

" በዋስትና እንዲከራከሩ ነው የተደረጉት እንጅ የተደረገው ከእስረኛ መፈታት ጋር ምንም አያገናኘውም " ብለዋል።

" የቀድሞ የፓርላማ አባል አቶ አብዱራህማን አህመዲን በሽብር ወንጀል ተከሰው ቂሊንጦ መሆናቸው አልታወቀም ነበር አመት አልፏቸዋል፤ ግራና ቀኝ እግሩ መቆም፣ መንቀሳቀስ አይችልም፤ ተቦርቡሮ አልቋል አጥንታቸው " ነው ያሉት።

ጠበቃ ሰለሞን፣ " ከዓመት በኋላ አዲስ ዋስትና ክርክር ስናደርግ ከ23ቱ ለሦስቱ ዋስትና ፈቀዱ " ሲሉም አክለው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የቀድሞ ፓርላማና፣ የኢዴፓ ከፍተኛ አመራር እንደሆኑ የሚነገርላቸው አቶ አብዱራህማን አህደመዲን በሽብር ወንጀል ተከሰው በእስር የሚገኙ ቢሆንም እስከዛሬ እምብዛም ስለሳቸው አልተሰማም።

የፌደራል ዐቃቢ ህግ በእነአብዱራህማን አህመዲን ጨምሮ በ23 ተከሳሾች ላይ ክስ የመሰረተው በ2016 ዓ/ም እንደነበር፣ በእስር ላይ አንድ አመት ከ9 ወራት ገደማ እንዳስቆጠሩ፣ ከ23ቱ ሦስቱ ዛሬ ዋስትና ተፈቅዶላቸው ከቂሊንጦ እንደወጡ ተገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የመንግስት ሰራተኞች ከቤተሰባቸው በውርስ እና በስጦታ መሬት ማግኘት እንዲችሉ የፈቀደው አዲሱ አዋጅ !

ከሰሞኑን የአማራ ክልል መሬት ቢሮ አዲስ የገጠር መሬት አጠቃቀም አዋጅ ይፋ አድርጓል።

በአዲሱ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ዙሪያ በተሰጠ ማብራሪያ " አዲሱ አዋጅ ከዚህ በፊት ሲነሱ የነበሩ የዘርፉ ችግሮችን በመለየት የመፍትሄ አማራጮችን አካቷል " ተብሏል።

እስካሁን የነበረው አዋጅ ባህላዊ የመሬት አያያዝ እና የግጭት አፈታት ስርአቶችን ግምት ውስጥ ማስገባትና እዉቅና መስጠት ላይ ችግሮች የነበሩበት እንደሆነ በአሁኑ አዋጅ ግን ሽምግልና አንዱ የግጭትና አለመግባባትን የሚፈታበት አማራጭ ሁኖ እንዲካተት መደረጉ ተገልጿል።

ይህ አዋጅ የመንግስት ሰራተኞች ከቤተሰባቸው በውርስ እና በስጦታ መሬት ማግኘት እንዲችሉ ፈቅዷል።

አዲሱ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ምን አዲስ ነገር ይዟል ?

- በአዲሱ አዋጅ ካሁን በፊት ተግባራዊ በተደረጉ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ህጎች ያልነበሩና የገጠር መሬት ባለይዞታዎችን መብትና ጥቅም ለማስፋት በግል ይዞታ ላይ የለማን የማይንቀሳቀስ ንብረት መሸጥ እና ማስተላለፍ እንዲችሉ ይፈቅዳል።

- የገጠር መሬት ባለይዞታዎች መሬታቸውን በስጦታም ይሁን በውርስ ማስተላለፍ የሚችሉት በገጠር መሬት አዋጅ ለተፈቀደላቸዉ የህብረተሰብ ክፍሎች ነበር፡፡ ይህ ከቤተሰቦቻቸዉ መሬት የማግኘት መብት ሊኖራቸዉ የሚገቡ የህብረተሰብ ክፍሎችን ጥቅም ገድቦ ቆይቷል። በአሁኑ አዋጅ የመንግስት ሰራተኞች ከቤተሰባቸው በዉርስና በስጦታ መሬት ማግኘት እንዲችሉ ይፈቅዳል።

- በአዲሱ አዋጅ የገጠር መሬት ባለይዞታዎች የይዞታ መብትን ለፈለጉት ሰው በስጦታ፣ በውርስ ማስተላለፍ መብትን ለማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ይፈቅዳል።

- የገጠር መሬት ይዞታን ለብድር ዋስትና ማስያዣነት በመጠቀም የብድር አገልግሎት ማግኘት የሚቻልበትን ድንጋጌ አካቷል። ይህም የክልሉን አርሶ አደር የብድር አቅርቦት ችግር መፍትሄ የሚሰጥ ነው ተብሏል።

- በአዲሱ አዋጅ በአስገዳጅ ሁኔታ የመሬት አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ ስርአቱ ዲጂታላይዝ መሆን እንዳለበት በግልፅ ተመላክቷል፡፡

- ለሴቶች፤ ለህፃናት፤ ከቀያቸዉ በጊዜያዊነት ለለቀቁ፤ በህግ ጥላ ስር ያሉ፣ ለህሙማን፤ ለአረጋዊያንና…ወዘተ ጉዳዩን ልዩ ትኩረት በመሰጠት የህግ ከለላና መብት ጥበቃ ሰጥቷል፡፡ ይህ ድንጋጌ ከዚህ በፊት በነበሩ ህጎች ላይ ተካቶ ተፈጻሚ ቢሆንም በልዩ ትኩረት የተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን  መብትና ጥቅም ጥበቃ ትኩረት እና ባለቤት በመስጠትም በኩል ትኩረት ተሰጥቶታል።

(በአዲሱ አዋጅ ከተካተቱ ነጥቦች ውስጥ በዚህ ክፍል የቀረበው በከፊል ነው)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ሰምተዋል?

ግዙፉ የ 60,000,000 ብር ሎተሪ ሊወጣ ጥቂት ሠአታት ብቻ ቀርተውታል!

የእድልዎ ቀን ዛሬ ነው! ህይወትን የሚቀይረው የ60 ሚሊዮን ብር ሎተሪ ዛሬ ይወጣል። በ100 ብር ብቻ ሰዓቱ ሳይረፍድ አሁኑኑ እድልዎን ይሞክሩ!
ትኬትዎን በ www.ethiolottery.et ፣ በ ቴሌብር ሱፐር አፕ፣ በ8989 ላይ የትኛውንም ፊደል በመላክ  እንዲሁም *8989# በመደወል ይቁረጡ።

መልካም እድል!
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

" ለምረቃው ነበር የሄደው ነገ እንደሚመጣ ነው እየጠበቅን የነበረው! " - የሟች ለታ ተስፋዬ (ዶ/ር) ቤተሰብ

➡️ " ' የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ነበሩ ' በሚል በየማህበራዊ ሚዲያው የተሰራጨው መረጃ #ሐሰተኛ ነው ! "

🔴 " ' ለስራ ጉዳይ ልዑካን ቡድን ሆነ ነው የሄደው ' የተባለውም ሐሰተኛ መረጃ ነው ! "

የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ዶክተር ለታ ተስፋዬ የሞቱት " ከመንግስት ልዑካን ቡድን ጋር ወደ አሜሪካ በሄዱበት " እንደሆነ እና " የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ እንደነበሩ " በማህበራዊ ሚዲያ በስፋት ተሰራጭቷል።

ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ የለታ (ዶ/ር) የቅርብ ቤተሰብ ግን፣ " ለታ (ዶ/ር) ህይወታቸው ያለፈው ለሥራ በሄዱበት ነው  ፤ ' የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ነበሩ ' በሚል የተሰራጨው መረጃ ሐሰተኛ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጩት መረጃዎች በጣም ደስ የማይል ክፍተት አለባቸው። 'የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ' ተብሎ የተሰራጨው ከየት የመጣ መረጃ እንደሆነ የማይታወቅ ነው። 'ለሥራ ጉዳይ ልዑካን ቡድን ሆኖ ሄደ' የሚለውም የተሳሳተ መረጃ ነው" ብለዋል።

" ሦስተኛ ዲግሪ PhD ሰርቶ ለምርቃት ነበር ወደ አሜሪካ የሄደው። ለምርቃት ሂዶ ነው ይሄ ነገር የተፈጠረው እንጅ ለመንግስት ሥራ አልነበረም የሄደው " ያሉት እኝሁ አካል፣ " የተሰራጨው መረጃ ሰውን በጣም ስላሳሳተው ኮሜንቶቹ በሙሉ አስቀያሚ ናቸው " ነው ያሉት።

ታዲያ እያገለገሉ የነበረበት ተቋም የትኛው ነው ? ሲል ቲክቫህ ላቀረበላቸው ጥያቄም፣ " በፊት ደምቢ ዶሎ ነበር፤ ከዚያ በኋላ ፒኤቺዲውን ነው እየሰራ የነበረው። በዝርዝር ባልገባልህም ሌሎች ምደባዎች ነበሩ። ግን ሙሉ በሙሉ አልገባም ነበር ፤ ምረቃውን ጨርሶ ለመምጣት ነበር የሄደው " ሲሉ መልሰዋል።

እርሰዎም እንዳሉት " የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ነበሩ " የሚለው በማህበራዊ ሚዲያ በሰፊው ተሰራጭቷል፤ ይህ "ሐሰተኛ" ከሆነ በምን ዘርፍ ነው ሲሰሩ የነበረው ታዲያ ? ስንል በድጋሚ ስንጠይቃቸው፣ " ከደምቢ ዶሎ እንደወጣ ይቺን ጊዜ ትምትህርት ላይ ነው የነበረው። በተጨማሪ ሌላም ዘርፍ ተመድቦ ነበር። ርክክብ ያላደረገበት የካውንሲንግ ጉዳዮች ነበሩት " ነው ያሉት።

ለታ (ዶ/ር) ሰሞኑን ወደ አሜሪካ የሄዱት እዚሁ ኢትዮጵያ ሆነው ትምህርታቸውን ከተማሩ በኋላ ለምረቃ እንደነበር አስረድተዋል።

" ለምረቃው ነበር የሄደው ነገ እንደሚመጣ ነው እየጠበቅን የነበረው " ሲሉም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ለታ ተስፋዬ (ዶ/ር) በምን ምክንያት ህይወታቸው እንዳለፈ ስንጠይቃቸውም፣ " አሁን ላይ በአሟሟቱ ዙሪያ የተረጋገጠ ምንም አይነት መረጃ አልደረሰንም። ጉዳዩን የያዘው የአሜሪካ ፓሊስ ነው። ውጤቱን ለቤተሰብ ነው የምሰጠው ስላለ ገና ግልጽ የሆነ መረጃ የለም " ሲሉ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ከፖለቲካ በላይ ለሕዝብ ቅድሚያ ይሰጥ " - የአሜሪካው አምባሳደር

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባደሳር ኧርቪን ማሲንጋ ዛሬ #ሁመራን ጎብኝተው ነበር።

አምባደሳር ማሲንጋ በጉዟቸው ሕዝቡ እየተጋፈጠ ያለውን ችግር በዐይናቸው እንደተመለከቱ እና የመሠረተ ልማት፣ ውስን የጤና አገለግሎት እና የመሠረታዊ አገለግሎቶች አለመኖር የሕዝቡን ኑሮ እንደጎዳው ጠቅሰዋል።

በግጭት የተፈናቀሉ ሰዎች ለዓመታት በዓለም አቀፍ ድጋፍ ላይ ጥገኛ ሆነው መቆየታቸውን ያነሱት አምባሳደሩ፣ " ምንም እንኳን ሰብአዊ እርዳታ ወሳኝ ቢሆንም፤ ዘላቂ መፍትሄ አይደለም " ብለዋል

አምባሳደሩ " ሁሉም ወገኖች ከፖለቲካ በላይ ለሕዝብ ቅድሚያ ይስጡ " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

" ከምንም ነገር በላይ ሕዝቡን በማስቀደም መጻኢ ፖለቲካዊ ዕድላቸውን በተገቢው ጊዜ እንዲወስኑ ዕድል ሊሰጣቸው ይገባል " ብለዋል።

" ሁሉም ሰው ደኅንነቱ እና ክብሩ በተጠበቀ ሁኔታ ቀጣይ ሕይወቱን የት መገንባት እንዳለበት እንዲወስን በኢትዮጵያ የሚመራ እና በተባበሩት መንግሥታት የሚታገዝን ሂደት አሜሪካ ትደግፋለች " ብለዋል።

ለዚህም " ሁሉም ወገኖች ከፖለቲካ በላይ ሕዝብን በማቀስደም የወደፊት የፖለቲካዊ ዕጣ ፈንታቸውን በተገቢው ወቅት እንዲወስኑ እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን " ሲሉ ገልጸዋል።

" የወደፊቱ መንገድ ውስብስብ ነው " ያሉት አምባሳደሩ " ነገር ግን ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው ጉዳይ ጉዳት ላጋጠማቸው ደኅንነት መሆን አለበት " ብለዋል።

አሜሪካ ኢትዮጵያውያን ለዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት በሚያደርጉት ጥረት ውስጥ ድጋፍ ለመስጠት ቁርጠኛ መሆኗን አመልክተዋል።

ከጦርነቱ በፊት በትግራይ ክልል አስተዳደር ስር የነበረው ሁመራ እና አካባቢው አሁን ላይ በአማራ ክልል ስር " ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን " በሚል እየተዳደረ ይገኛል።

ዛሬ የአሜሪካው አምባሳደር ወደ ስፍራው ባቀኑበት ወቅት ከዞኑ አስተዳዳሪና ሌሎች አካላት ጋርም መክረዋል።

አቶ አሸተ ደምለው " የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ በገዛ ርስቱ ሲሳደድና ሲገፋ መቆየቱን የአለም አቀፍ ማህበረሰብ ያውቀዋል፤ የበደሉ መቋጫ የሆነው የማይካድራው ጀምላ ጭፍጨፍ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ጥያቄው ታፍኖ በሀገርም በውጭም በደሉ እንዳይወጣ ተደርጎ ቆይቷል፤ ሰሚም አድማጭም አጥቶ የቆየ ሕዝብ ነው " ብለዋል።

" ከለውጡ ማግስት መንግስት የሕዝቡ ጥያቄ የእውነትና የፍትህ መሆኑን እውቅና የሰጠበትና የአለሙ ማህብረሰብ በደሉን እንዲያይ የተደረገበት ማሳያ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኢርቪን ማሲንጋ በዞናችን መተው ያደረጉት ውይይት አንዱ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ አማራ ነኝ በማለቱ ብቻ ሲሳደድና ሲገፋ ቆይቷል " ያሉ ሲሆን " የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ሀገሩን የሚወድና በሰላም መኖር የሚፈልግ አማራዊ ማንነቱን የሚያስጠብቅ፣ ባሕሉን የሚያከበር ኩሩ ሕዝብ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" የወልቃይት ጠገዴ አማራ ሕዝብ የጎንደር በጌምድር አማራ መሆኑ በርካታ ታሪካዊ ማስረጃዎች አሉን ፤ ሕዝቡም ' አማራ ነኝ ' በማለት ሞትን ሳይፈራ ለበርካታ አመታት ታግሏል በዚህም ጽኑ ትግል ነጻነቱን አውጇል " ሲሉ አሳስበዋል።

የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ጥያቄ ለመፍታት በሚደረገው መንገድ የአብሮነትና ዘላቂነት መንገድ መከተል አለብን ብለዋል።

#USEmbassyAA
#AmharaCommunication

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የገቢዎች ሚኒስቴር ባለ (QR-Code) ማንዋል ደረሰኝ የጠየቁ የህትመት ትዕዛዙ ያለበትን ደረጃ ማወቅ የሚችሉበትን አድራሻ ይፋ አደርጓል።

ሚኒስቴሩ ፥ ለባለ (QR-Code) ደረሰኝ ከብርሃንና ሰላም ህትመት ትዕዛዝ የጠየቁ ግብር ከፋዮች ይህን ሊንክ
https://www.mor.gov.et/qr በመጫን እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) በማስገባት የህትመት ትዕዛዙ ያለበትን ደረጃ ማረጋገጥ እንደሚችሉ አሳውቋል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ከውጪ አገር በቴሌብር ገንዘብ ሲላክልን 9% ስጦታ አለን።

*127# ደውለን ወይም ቴሌብርን በስልካችን በዚህ ሊንክ
https://bit.ly/telebirr_SuperApp ጭነን ስንመዘገብ እንዲህ ነን!

#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን
#ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን
#ስንጭን_እንዲህ_ነን
#ስናስጀምር_እንዲህ_ነን

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

አሜሪካ #ኢትዮጵያን ጨምሮ በ75 ሃገራት የቪዛ ሂደቶችን ልታቋርጥ ነው።

የአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት የውጪ ሃገር ዜጎች ዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV)ን ጨምሮ ወደ አሜሪካ ሄደው በቋሚነት መኖር ሲፈልጉ የሚሰጣቸው ቪዛ (Immigrant Visa) ሂደት በ75 ሃገራት እንደሚቋረጥ ተገልጿል።

ፎክስ ኒውስ የስቴት ዲፓርትመንትን የውስጥ ማስታወሻ ተመለከትኩ ብሎ ባወጣው መረጃ፣ እርምጃው ከፊታችን የፈረንጆቹ ጥር 21፣ 2026 ጀምሮ ወደ ስራ ይገባል።

ይህ ውሳኔ በርካታ የዲቪ አሸናፊዎች ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ያሳድራል። የዲቪ አሸናፊዎች በዚህ ውሳኔ ምክንያት ቪዛ የማግኘት እድላቸው ችግር ውስጥ ይገባል።

ሂደቱ ይቋረጥባቸዋል ከተባሉ ሃገራት መካከል ፦
- ኢትዮጵያ
- ግብፅ
- ሶማሊያ
- ኤርትራ
- ሩሲያ
- ሱዳን
- ደቡብ ሱዳን ይገኙበታል።

የስቴት ዲፓርትመንት ውሳኔ በመንግስት ድጋፍ ላይ ጥገኛ የሚሆኑ የውጪ ሃገር ሰዎችን ለመቀነስ ነው ተብሏል።

ባለፈው ህዳር የቪዛ ኦፊሰሮች የአመልካቾችን ፦
° ጤና፣
° የቋንቋ ክህሎት፣
° ፋይናንስና የተለያዩ መመዘኛዎችን በመመልከት በመንግስት ድጋፍ ለመኖር የሚፈልጉ አይነት ከሆነ ቪዛ እንዲከለክሏቸው ታዘው ነበር።

የስቴት ዲፓርትመንት ቃለ አቀባይ ቶሚ ፒጎት የ75ቱ ሃገራት የቪዛ ሂደት ስቴት ዲፓርትመንት የመንግስትን ድጋፍ የሚጠቀሙ የውጪ ዜጎች እንዳይገቡ ለመከላከል እንዲቻል የቪዛ ሂደቱ እስኪገመገም እንደሚቆም አረጋግጠዋል።

በቅርቡ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከአሜሪካ መንግስት ድጋፍ በመቀበል የሚኖሩ የውጪ ሃገር ሰዎችን ቁጥር ይፋ አድርገው ነበር።

ትራምፕ በአሜሪካ ከሚኖሩ የኢትዮጵያ ተወላጅ ስደተኞች መካከል 47.6% ያህሉ ቢያንስ ከቤተሰብ አንዱ የመንግስት ድጋፍ ተጠቃሚ እንደሆኑ ገልጸዋል።

የቪዛ ሂደቱ በስቴት ዲፓርትመንት እስኪገለጽ ድረስ ላልተወሰነ ጊዜ ይቆያልም ተብሏል።

በሌላ በኩል ጊዜያዊ ቪዛ ማለትም ፦
- የቱሪስት /የጉብኝት/ ቪዛ
- የተማሪዎች የትምህርት ቪዛ
- አብዛኛው የስራ (ቢዝነስ) ቪዛ የአሁኑ ውሳኔ #እንደማይመለከታቸው ተነግሯል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ

Via @tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" በኋላ ለሚወሰደው እርምጃ እራሱና እራሱ ብቻ ኃላፊነቱን ይወስዳል " - የጋምቤላ ፖሊስ ኮሚሽን

የጋምቤላ ፖሊስ ኮሚሽን ለአድማ ብተና እና ለክልሉ ፖሊስ አባላት በሙሉ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላለፈ።

ኮሚሽኑ በቅርቡ በክልሉ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሁሉም የአድማ ብተና እና የመደበኛ ፖሊስ አባላት የጦር መሳሪያ እንዲፈቱ ከክልሉ ኮማንድ ፖስት አቅጣጫ መቀመጡን አስታውሷል።

በዚህም መሰረት ከጦር መሣሪያ ግምጃ ቤት ፈርመው ያወጡትን የጦር መሣሪያ ገቢ ያላደረጉ የአድማ ብተና እና የመደበኛ ፖሊስ አባላት እስከ ነገ ጥር 7 ቀን 2018 ዓ/ም 11:00 ሰዓት ድረስ ገቢ እንዲያደርጉ በጥብቅ አሳስቧል።

" ከተጠቀሰው ጊዜ በኋላ የጦር መሣሪያ በእጁ የተገኘ እንደ ፀረ-ሠላም ተቆጥሮ መንግሥት እርምጃ ይወስድበታል፤ ለዚህም እራሱ እና እራሱ ብቻ  ኃላፊነቱን ይወስዳል " ሲል አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ፎቶ ፦ በግንባታ ላይ የሚገኘው ግዙፉ የአደይ አበባ ስታድዮም የመጫወቻ ሜዳ በፊፋ (FIFA) ተገምግሞ እውቅና ማግኘቱን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

@tikvahethsport

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የቴሌኮም ሰራተኞቹ ለስራ በተሰማሩበት በታጣቂዎች ታገቱ ፤ ታጣቂዎቹ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ጠይቀዋል !

የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ውስጥ ሥራ ላይ የነበሩ 11 የኢትዮ ቴሌኮም እና የዜድቲኢ ሠራተኞችን አግተው መውሰዳቸው ተነገረ።

ባለፈው ሳምንት በተለያዩ ቀናት በታጣቂዎቹ የታገቱት ሠራተኞችን ለመልቀቅ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ መጠየቁ ተገልጿል።

ታጣቂዎቹ የመጀመሪያውን ዕገታ የፈጸሙት ባለፈው ሳምንት አርብ ጥር 1/2018 ዓ.ም. ቂልጡ ካራ በተባለ ወረዳ ውስጥ ነው።

የሞባይል ኔትዎርክ ማስፋፊያ ሥራ እያከናወኑ በነበሩ የኢትዮ ቴሌኮም እና የቻይናው ኩባንያ ዜድቲኢ ባልደረቦች ላይ እገታ የተፈጸመው።

በዕገታው ከተያዙት ውስጥ 5ቱ የዜድቲኢ ባልደረቦች ሲሆኑ፣ 2ቱ የኢትዮ ቴሌኮም ሠራተኞች መሆናቸው ታውቋል።

7ቱ ባለሙያዎች በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች ተይዘው መወሰዳቸውን ለደኅንነታቸው ሲሉ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የኢትዮ ቴሌኮም ባለሥልጣን ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ አረጋግጠዋል።

" አርብ ረፋድ አራት ሰዓት ላይ በሥራ ላይ እያሉ ነው የታገቱት። ሠራተኞቹ እቃዎቻቸውን እና መኪናቸውን ትተው ተወስደዋል። የት እንደተወሰዱ ምንም መረጃ የለንም " ሲሉ ተናግረዋል።

በቀጣዩ ቀን ቅዳሜ ጥር 2/2018 ዓ.ም. ደግሞ ሌሎች 4 ሠራተኞች እዚያው ምዕራብ ወለጋ ቦጂ ዲርመጂ ወረዳ ውስጥ በታጣቂዎች መወሰዳቸውን ገልጸዋል።

ከአጋቾቹ መካከል የተወሰኑት የተያዙትን 4 ሰዎች ለመልቀቅ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ብር እንዲከፈላቸው #ዜድቲኢን መጠየቃቸው ተነግሯል።

በቅዳሜው ዕገታ በታጣቂዎቹ ከተያዙት 4 የቴሌኮም ኩባንያዎቹ ሠራተኞች መካከል 3ቱ የዜድቲኢ ሠራተኞች ሲሆኑ አንዱ የኢትዮቴሌኮም ሠራተኛ ነው።

ስሜ አይጠቀስ ያሉት የኢትዮ ቴሌኮም አመራር " በቂልጡ ካራ ወረዳ ያሉት ሁሉም ሠራተኞች ተይዘዋል። ያገቷቸው ታጣቂዎች በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አባላት መሆናቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል " ሲሉ ተናግረዋል።

ታጣቂዎቹ ዕገታውን የፈጸሙት፤ ኢትዮ ቴሌኮም በአካባቢው ያለውን 5% እስከ 12% የሚደረስ የ4ጂ የቴሌኮም ሽፋን ወደ 82% በመቶ ለማሳደግ እየሠራ ባለበት ሰዓት እንደሆነ ገልጸዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም ከቻይናው ኩባንያ ጋር በመሆን በአካባቢው ያለውን የኔትወርክ ሽፋን ለማስፋት ከፍተኛ ገንዘብ መድቦ ባለፉት ሁለት ወራት ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AddiAbaba

" ለአጭርም ይሁን ለረጅም ሰዓት ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍጹም የተከለከለ ነው ! " - ፖሊስ


ከዛሬ ጀምሮ የመንገድ ግንባታ በሚደረግባቸው ቦታዎች ተሽከርካሪዎችን አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማትና የመንገድ ግንባታ በሚደረግባቸው ፦

1. ከቅዱስ ኡራኤል፣ በአትላስ ሆቴል ኤድሞል እስከ ቦሌ ብራስ ድረስ፣

2. አደይ አበባ ስታዲየም አካባቢ

የሚቆሙ ተሽከርካሪዎች በመንገድ ስራው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደሩ መሆኑን ገልጿል።

ከዛሬ ጥር 04/2018 ዓ/ም ጀምሮ በተጠቀሱት አካባቢዎች ላይ የግንባታ ስራውን ከሚያከናውኑት ተሽከርካሪዎች በስተቀር ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት ተሽከርካሪን አቁሞ መሄድ ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Afar : የአፋር ክልል ፓሊስ ጠቅላይ መምሪያ፣ ዛሬ በሰመራ ከተማ የመገልበጥ አደጋ የደረሰበትን ተሽከርካሪ ሹፌር በቁጥጥር ስር ማዋሉን ይፋ አድርጓል።

" አሽከርካሪው በወቅቱ አምልጦ የነበረ ቢሆንም ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር ባደረገው ክትትል በቁጥጥር ውሎ ምርመራው በመጣራት ላይ ይገኛል " ብሏል።

" የአደጋው መንስኤ ከልክ በላይ ፍጥነትና የመሪን አጠቃቀም ችግር ነው " ያለው ጠቅላይ መምሪያው፣ አደጋው በአጠቃላይ በ87 ሰዎች ላይ ሞትና ጉዳት መድረሱን አረጋግጧል።

Via @thiqaheth

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

ምሽት 5:05 ላይ 4.8 በሬክተር ስኬል የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ቮልካኖ ዲስከቨሪ አሳውቋል።

እንደ ድረገጹ መረጃ የመሬት መንቀጥቀጡ የተከሰተው በአፋር ክልል ፣ ከትግራይ በደቡባዊ ዓዲግራት 90 ኪሎሜትር አካባቢ እንደሆነ ጠቁሟል።

ንዝረቱ በአፋር እንዲሁም ትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች ጠንክሮ ተሰምቷል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ እየተካሄደ ካለ የመንገድ ስራ ፕሮጀክት ጋር በተያያዘ መንገዶች ይዘጋሉ።

የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን እንዳሳወቀው ከዛሬ ጀምሮ እስከ እሁድ ታህሣስ 26/ 2018 ዓ.ም ድረስ፤ ከእንግሊዝ ኤምባሲ ወደ 22 የሚወስደው መንገድ ለትራፊክ ዝግ ተደርጓል።

ከእንግሊዝ ኤምባሲ በ22 ወደ ኤድናሞል የመንገድ ፕሮጀክት እየተገነባ እንደሚገኝ ይታወቃል።

በተመሳሳይ ከቦሌ ብራስ ወደ ኤድናሞል የሚደስደው መንገድ ከዛሬ ጀምሮ በከፊል ለትራፊክ ዝግ ተደርጓል።

ከቦሌ ብራስ ወደ አትላስ የኮሪደር ልማት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ይታወቃል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Gambella

የጋምቤላ ክልል ፖሊስን በኮሚሽነርነት የሚመሩት አቶ ኡጉላ ኡጁሉ ትላንት አመሻሹን በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ባለቤታቸውንም ዋቢ በማድረግ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ዘግቧል።

አቶ ኡጉላ በፌደራል ፖሊስ አባላት ተይዘው ወደ ቤታቸው ለፍተሻ ከመወሰዳቸው አስቀድሞ በጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ነበሩ ተብሏል።

በጋምቤላ ከተማ ስድስት ኪሎ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ወደሚገኘው የፖሊስ ኮሚሽነሩ መኖሪያ ቤት የሄዱ የፌደራል ፖሊስ አባላት በአራት ተሽከርካሪዎች የተጫኑ እንደነበሩ የአቶ ኡጉላ ባለቤት ገልጸዋል።

የጦር መሳሪያ የታጠቁት ፖሊሶች በቤታቸው ፍተሻ ካደረጉ በኋላ፤ ለኮሚሽነሩ ከመንግስት የተሰጣቸውን ሽጉጥ ይዘው እንደሄዱ ባለቤታቸው አስረድተዋል።

የፌደራል ፖሊስ አባላቱ አቶ ኡጉላን ወደ ቤት ሲያመጧቸውም ሆነ በፍተሻ ወቅት " አካላዊ ጥቃት እንዳልፈጸሙባቸው " ገልጸዋል።

ፍተሻው ተጠናቅቆ ባለቤታቸውን መልሰው ይዘዋቸው የሄዱት ለ12 ሰዓት ሩብ ጉዳይ ገደማ እንደነበር ተናግረዋል። ይሁንና ባለቤታቸው ወደየት እንደተወሰዱ እና እስካሁንም ያሉበትን እንደማያውቁ አስረድተዋል። 

በነገራችን ላይ በጋምቤላ ክልል የፖሊስ ኃላፊዎች በጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር ሲውሉ የአሁኑ የመጀመሪያው አይደለም። ከሶስት ዓመት በፊት የክልሉን ፖሊስ ኮሚሽን ሲመሩ የነበሩት አቶ አቡላ ኡባንግ እና ምክትላቸው አቶ ቱት ኮር ጨምሮ 12 የጸጥታ ዘርፍ አባላት በቁጥጥር ስር ውለው ነበር።

ትላንት ሐሙስ የፌደራል ፖሊስ አባላት በጋምቤላ ከተማ ያሉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ሲንቀሳቀሱ ነበር። በዚህም ወቅት የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ትላንት ከእኩለ ቀን በኋላ በፌደራል ፖሊስ ተሽከርካሪዎች ሰዎች ታስረው ሲወሰዱ መመልከታቸውን የገለጹ አንድ ነዋሪ ፤ ከታሰሩት ሰዎች ውስጥ በክልሉ ባሉ የመንግስት ተቋማት ውስጥ የሚሰሩ እና የጸጥታ ኃይሎች እንደሚገኙበት አስረድተዋል።

አሁን ላይ በክልሉ መረጋጋት እና አንጻራዊ ሰላም እየሰፈነ መሆኑን የክልሉ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ ተነግረዋል። ተፈናቃዮችም ወደ ቄያቸው እየተመለሱ እንደሆነ ገልጸዋል።

በአሁን ወቅት ጋምቤላ ከተማን ጨምሮ ሙሉ የክልሉን ሰላም እያስጠበቁ የሚገኙት የመከላከያ ሰራዊት እና የፌዴራል ፖሊስ አባላት ናቸው።

በሰሞነኛው የፀጥታ ችግር ስራ ያቆሙ የመንግሥት ሰራተኞችም ወደ ስራቸው በአስቸኳይ እንዲመለሱ ማሳሰቢያ እንደተሰጠም ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።

ይህ መረጃ በዋነኝነት ባለቤትነቱ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድረገጽ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

✨🏑 ከ16 ሚሊዮን ብር የገና ስጦታ የድርሻዎን ይውሰዱ!!

የገና በዓል አስመልክተን 2 አውቶሞቢሎችን ጨምሮ ሌሎች አጓጊ ሽልማቶችን የሚያሸልሙ የገና ጨዋታ ስጦታዎች በቴሌብር ሱፐርአፕ አዘጋጅተናል፡፡

💡 በቴሌብር የአገልግሎት ክፍያዎችን መፈጸም፣ ገንዘብ መላክና መቀበል፣ ጥቅልና የአየርሰዓት መግዛት እንዲሁም በዘመን ገበያ መገበያየት ተጨማሪ የጨዋታ ነጥቦችን ያስገኝልዎታል፡፡

🚘 የገና ዋዜማ መኪና የሚያሸልም በቀን እስከ 36 የሎተሪ ትኬት ያገኛሉ!

💁‍♂️ በየዕለቱ 15 ነጥቦችንን በመሰብሰብ ቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_SuperApp ላይ ዕድልዎን ይሞክሩ!

🗓 እስከ ታኅሣሥ 28 ቀን 6:00 ብቻ!

#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

Читать полностью…
Subscribe to a channel