tikvahethiopia | Unsorted

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1532594

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Subscribe to a channel

TIKVAH-ETHIOPIA

" በአርሲ ዞን አራት ወረዳዎች ተከሰተ የተባለውን ችግር የሚያጣራ የልዑካን ቡድን የማጣራት ሥራውን በዛሬው ዕለት ጀምሯል " - የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ " በኦሮሚያ ክልል፣ አርሲ ዞን በጉና፣ በመርቲ፣ በሸርካ እና በሆሎንቆ ዋቢ ወረዳዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች እና ካህናት እንዲሁም በሌሎችም የሃይማኖት ተቋማት አገልጋዮች እና ምዕምናን ላይ ግድያ እና ስቃይ መከሰቱን የሚያሳይ መረጃ መውጣቱን መነሻ በማድረግ ጉዳዩን ከመሰረቱ የሚያጣራ የተለያዩ የባለድርሻ አካላት ተወካዬች የተካተቱበት አጣሪ ቡድን ተቋቁሞ በዛሬው ዕለት የተከሰተውን ችግር በአካል ለማጣራት ችግሩ ወደ ተከሰተባቸው ቦታዎች በመጓዝ ሥራውን በይፋ ጀምሯል " ሲል አሳውቋል።

" የሉዑካን ቡድኑ የማጣራት ሥራውን ጨርሶ የመጨረሻ ሪፖርቱን ሲያቀርብ በጉዳዩ ላይ በጉባኤችን በኩል ይፋዊ መግለጫ እና ማብራርያ የሚሰጥ በመሆኑ ሁሉም ዜጋ በትእግስት የማጠቃለያ ሪፖርቱን እንዲጠብቅ ጉባኤችን በአክብሮት ይጠይቃል " ብሏል።

ጉባኤው " ይህ በእንዲህ እንዳለ አንዳንድ አካላት ኃላፊነት በጎደለው መልክ ከግምት እና ካልተሟላ መረጃ በመነሳት በማሕበራዊ ሚዲያ ጉዳዩን አስመልክተው መረጃዎች መስጠታቸውን ተመልክተናል " ሲል ገልጿል።

መረጃዎቹ ምን እደሆኑ በግልጽ ያላሰፈረው ጉባኤው " ይህ ተግባር የማጣራቱን ሂደት የሚጎዳ እና አንዳንድ አካላትን ወደ ተሳሳተ ድምዳሜ ሊወስድ የሚችል ተግባር በመሆኑ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ መረጃ የምታሰራጩ አካላት በሙሉ ከፍ ያለ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን " ብሏል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ባንካችን የዲጂታል ግብይት ተጠቃሚ ደንበኞችን ለማበረታታት ያዘጋጀውን የመኖሪያ ቤት ሽልማት አሸናፊ ይፋ አደረገ

   የአባመላ ቅርንጫፍ ደንበኛችን የባለ 2 መኝታ አፓርታማ ዕድለኛ ሆነዋል

ባንካችን አቢሲንያ ላለፉት አምስት ወራት ሲያከናውን የቆየውን በተለያዩ የዲጂታል ባንክ አማራጮች ግብይት የሚያከናውኑ ደንበኞችን የሚያበረታታ ዘመቻ (Merchant Engagement Campaign) በይፋ በማጠናቀቅ በዛሬው ዕለት ለአሸናፊ ደንበኞች የተዘጋጀውን የመኖሪ ቤት ዕጣ የማውጣት ሥነ-ሥርዓት አከናወነ።

ዕጣ የማውጣቱ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2018 ዓ.ም  የባንካችን የዲጂታል ባንክ ዋና ኦፊሰር የሆኑት ወ/ሮ ሶስና መንገሻና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች፣ተጋባዥ እንግዶችና ታዛቢዎች በተገኙበት በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ዕድል አዳራሽ ተካሂዷል።

በወጣው ዕጣ መሰረትም ባለ 2 መኝታ አፓርታማ የሚያስገኘው አሸናፊ የዕጣ ቁጥር 0001801876786 ሆኖ የወጣ ሲሆን ዕድለኛውም የባንካችን አባመላ ቅርንጫፍ ደንበኛ የሆኑትና በንግድ ሥራ የሚተዳደሩት የአዲስ አበባ ነዋሪው አቶ መሐመድ ከድር ሆነዋል።

ይህ የሽልማት መርሃ-ግብር ይፋ ከተደረገበት ከሚያዚያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባለፉት  አምስት ወራት ከ10 ሚሊዮን በላይ ግብይቶች የተከናወኑ ሲሆን በዚህም ከብር 138 ቢሊዮን በላይ ማንቀሳቀስ ተችሏል።

ባንካችን አቢሲንያ የዲጂታል መተግበሪያ በመጠቀም የሚደረጉ ግብይቶችን ለማበረታታትና አዳዲስ የዲጂታል ባንክ ደንበኞችን ለማፍራት ለመጀመሪያ ጊዜ ባዘጋጀው በዚህ መርሃ-ግብር በሞባይል ባንክ፣በፖስ  እና በሌሎች የዲጂታል አማራጮች ከብር 500 ጀምሮ ግብይት ለፈጸሙ ደንበኞች ከ3 ሚሊዮን በላይ የዕጣ ቁጥሮችን ወይም ኩፖኖችን ተደራሽ አድርጓል።  

ባንካችን ዕድለኞችን እንኳን ደስ አላችሁ እያለ በቀጣይም የባንካችንን እጅግ ዘመናዊ የዲጂታል ባንክአማራጮች በመጠቀም እግረ መንገዳቸውንም የተለያዩ ዕጣዎች ባለዕድል እንዲሆኑ ይጋብዛል።

/channel/BoAEth

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ቤተክርስቲያናችን ይህን አይነቱን ኢ-ሰብዓዊ ተግባር አጥብቃ ታወግዛለች " - የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ጥቅምት አጋማሽ 2018 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሀረርጌ ሚደግዱ አስተርዮ ማርያም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን አካባቢ ግድያ መፈጸሙንና የካቶሊካውያን ሕይወት ማለፉንና ንብረት መቃጠሉን ገልጾ " ታላቅ ሀዘን ተሰምቶናል " ሲል ባወጣው የሀዘን መግለጫ ገልጿል።

የቤተ-ክርስቲያኒቱ ጳጳሳት ጉባኤ አክሎም፥ በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት  ምዕመናን ላይ ተመሳሳይ ግድያ መፈጸሙን ተቋማቱ ያወጡትን መግለጫ ጠቅሶ " ቤተክርስቲያናችን ይህን አይነቱን ኢ-ሰብዓዊ ተግባር አጥብቃ ታወግዛለች " ሲል አስታውቋል።

" የዜጎችን ሰላም እና ደህንነት ለማረጋገጥ መንግስት አስቀድሞ አስፈላጊውን የሕግ ማስከበር ሥራ እንዲሠራ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታቀርባለች " ሲል ነው በመግለጫው ተጠቅሷል። 

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

🔵⚽️ በዲኤስቲቪ እናያለን ገና!!

ሁሉንም የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ጨምሮ ከ125 በላይ ምርጥ የመዝናኛ ቻናሎችን
👉 በስልክዎ ዳታ አልያም
👉 በቤትዎ ፋይበር በስማርት ቲቪዎ
እንዳሻዎ መመልከት ይችላሉ!

💁‍♂️ DStv Stream ሜዳ ፓኬጅ ከ10GB ጋር በ1240 ብር ወርኅዊ ክፍያ ብቻ!

ዛሬውኑ ይግዙ፤ ዘና ብለው በአማራጭ ይዝናኑ!!

🔗 ለተጨማሪ መረጃ: https://bit.ly/DSTV_Bundle

📍 የአገልግሎት ማዕከሎቻችንን ይጎብኙ!

#DSTV
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ብርሃን_ባንክ
በተመረጡ ቅርንጫፎች የሥራ ሰዓት ተራዘመ!
*****************************
ብርሃን ባንክ ሁሌም ለደንበኞቹ ምቾት ቅድሚያ በመስጠት የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ሲሆን አሁን ደግሞ የአገልግሎት አቅርቦቱን ለማሳደግ በተመረጡ 16 ቅርንጫፎች የሥራ ሰዓት ማራዘሙን ስንገልጽ በደስታ ነው!

የተሻሻለው የሥራ ሰዓት
ከሰኞ እስከ አርብ፡ ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ምሽቱ 2:00 (8:00 PM)
ቅዳሜ፡ ከጠዋቱ 2:00 እስከ ምሽቱ 12:00 (በነበረበት ይቀጥላል)

ፈጣንና አስፈላጊ መረጃ እንዲደርስዎ የባንካችንን ማኅበራዊ ሚዲያዎች ይቀላቀሉ!

Telegram፡ /channel/berhanbanksc
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
LinkedIn : https://www.linkedin.com/company/76151001

#ብርሃን_ባንክ
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ሥራችን!

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ተሽከርካሪዎች ከፖሊስ ፈቃድ ውጭ መጠገን ፣ ቀለም መቀየር ወይም ሌላ ይዞታ መለወጥ በወንጀል ያስጠይቃል " - የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት

በማንኛውም ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ተሽከርካሪዎች ከፖሊስ ፈቃድ ሳያገኙ መጠገን፣ ቀለማቸውን መቀየር ወይም ሌላ ማናቸውንም የቀደመ ይዞታቸውን የሚለውጥ ጥገና ማካሄድ በወንጀል እንደሚያስጠይቅ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት አስታውቋል። 

መመሪያውን የሚተላለፉ የተሽከርካሪ ሰርቶ ማሳያ ወርክሾፕ (ጋራዥ) ባለቤቶ ከ20 ሺሕ ብር የገንዘብ መቀጮ ጀምሮ በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርስ ቅጣት ይጠብቃቸዋል።

ይህ አስገዳጅ መመሪያ ተግባራዊ የተደረገው የትራፊክ አደጋ አድርሰው የሚሰወሩ ወንጀለኞችን ሕገ-ወጥ ድርጊት ለመቆጣጠር እንደሆነ የትራፊክ ማኔጅመንት የባለሥልጣን የትራፊክ ቁጥጥር እና ሁነት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ አያሌው አቲሳ ለአሐዱ ተናግረዋል።

አቶ አያሌው አቲሳ ምን አሉ ?

" ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ተሽከርካሪዎች ያለ ፖሊስ እውቅና የቀደመ ይዞታቸውን መለወጣቸው ፖሊስ አደጋ አድርሰው የሚሰወሩ ተሽከርካሪዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የሚያደርገውን ጥረት በማደናቀፍ ወንጀለኞች ለጥፋታቸው እንዳይቀጡ እድል ይሰጣል።

በአስገዳጅ መመሪያው መሠረት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ተሽከርካሪዎች የሚጠግኑ ጋራዦች በተሽከርካሪው ላይ ምንም አይነት ለውጥ ከማካሄዳቸው በፊት፤ ተሽከርካሪው አደጋ አለማድረሱን እና በፖሊስ እንደማይፈለግ የሚገልጽ ማስረጃ ከፖሊስ መውሰድ ይጠበቅባቸዋል።

ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበትን ተሽከርካሪ ያለ ፖሊስ ዕውቅና የሚጠግኑ የጋራጅ ባለንብረቶች በወንጀል ይጠየቃሉ ፤ የገንዘብ መቀጮም እንደሚጠብቃቸው የመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ መቆጣጠሪያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቀጥር 567/2016 ይደነግጋል። "

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የአሐዱ ነው።

Credit - አሐዱ (Ahadu)

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SafaricomEthiopia

😲 እስቲ አስቡት ስልካችሁን ስትከፍቱት የበሽ 1 ሚሊዬን እንዳሸነፋችሁ ብታውቁ! 🎉🎉🎉 ዛሬውኑ በሽ ይግዙ ቀጣዩ ሚሊየነር ሊሆኑ ይችላሉ!

ወደ *777*0# ይደውሉ ወይም በM-PESA የበሽ ጥቅል ይግዙ!

📲 የM-PESA መተግበሪያን አሁኑኑ ያውርዱ፡ https://onelink.to/ewsb22

የቴሌግራም ቦታችን👉🏽 /channel/official_safaricomet_bot

#MPESASafaricom
#furtheraheadtogether
#besh

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Earthquake

ዛሬ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ ከዓዲግራት ደቡባዊ ምስራቅ 43 ኪሎሜትር የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ በበርካታ አከባቢዎች ላይ ንዝረት ተሰምቷል።

ከምሽቱ 1:30 የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4.5 የተለካ እንደሆነ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቨይ መረጃ ያሳያል።

የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ ከተሰማባቸው አካባቢዎች አንዷ የትግራይ መዲና መቐለ ስትሆን ንዝረቱ በተለይም በፎቅ/ህንፃዎች ላይ አስፈሪ ስሜት እንደነበር የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ገልጿል።

ከጥቅምት 2 ቀን 2018 ዓ.ም ወዲህ ንዝረቱ ትግራይ እና አፋር በርካታ አካባቢዎች ጎልቶ የሚሰማ የተለያየ ልኬት ያለው መሬት መንቀጥቀጥ እየተሰማ ነው።

በተለይ እሁድ ጥቅምት 2/2018 ዓ.ም የተከሰተው በሬክተር ስኬል 5.6 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ አፋር ክልል የሰው ህይወት ቀጥፎ በርካታ ቤቶችን አፍርሶ ከ40 ሺህ በላይ ሰዎች ያለመጠለያ እንዲቀሩ አድርጓል። በተመሳሳይ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን አፅቢ ወምበርታ ወረዳ ቤቶች እንዲፈርሱ ምክንያት ሆኗል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ኢትዮጵያ በጣት ከሚቆጠሩ አረጋውያን፣ አፈ ማር ከሆኑ መካሪዎችዋ መካከል አንዱ የሆኑትን፣ ለመወደድ የታደሉትን የዘመናችን ጌጥ አጥታለች።

ይህንን የድካም ዓለም መገላገል ለእርሳቸው ዕረፍት ቢሆንም ለአገር ግን ታላቅ ጉዳት ከመሆኑም በላይ ዕድሜን ከጥበብ ጋር ያዋሐዱ በሁሉ ዘመን አይገኙምና ኀዘናችን ጥልቅ ነው። " - ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ  ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ፎቶ ፦ ቅዱስነታቸው በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሽኝት ላይ በእምባ ተሞልተው ነበር።

Photo Credit - Ahmed Nega

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2018 የቲክኒክና ሙያ ሰልጣኞች መግቢያ ነጥብ ይፋ አድርጓል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የተቋሙ ደብዳቤ፣ በ2018 ዓ/ም የስልጠና ዘመን ወደ ቲክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚገቡ ሰልጣኞች የመግቢያ ነጥብ በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ውጤታቸው መሰረት ለተፈጥሮና ማህበራዊ ሳይንስ የመግቢያ ውጤት ከደረጃ 1 እስከ 5 በዝርዝር አስቀምጧል።

የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ እና ቅድመ ዝግጅት (12ኛ ክፍል) ላጠናቀቁ ደረጃ 1 እና ደረጃ 2 ሰልጣኞች መቁረጫ ነጥብ፦

-ለወንዶች አርብቶ አደር አካባቢዎችን ሳይጨምር 134 እና ከዚያ በታች፣
-ለወንዶች አርብቶ አደር አካባቢዎች 132 እና ከዚያ በታች፣
-ሴቶች አርብቶ አደር አካባቢዎችን ሳይጨምር 121 እና ከዚያ በታች፣
-ሴቶች አርብቶ አደር አካባቢዎች 120 እና ከዚያ በታች፣
-ለሁሉም ክልል አካል ጉዳተኞች 120 እና ከዚያ በታች ሆኖ ተቆርጧል።

የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ እና ቅድመ ዝግጅት (12ኛ ክፍል) ላጠናቀቁ  ደረጃ 3 እና 4  ሰልጣኞች መቁረጫ የጥብ፦

-ወንዶች አርብቶ አደር አካባቢዎችን ሳይጨምር 135 እና ከዚያ በላይ፤
-ወንዶች አርብቶ አደር አካባቢዎች 133 እና ከዚያ በላይ፤
-ሴቶች አርብቶ አደር አካባቢዎችን ሳይጨምር 122 እና ከዚያ በላይ፤
-ሴቶች አርብቶ አደር አካባቢዎች 121 እና ከዚያ በላይ፤
-ለሁሉም ክልል አካል ጉዳተኞች 121 እና ከዚያ በላይ ሆኖ ተቆርጧል።

እንዲሁም፣ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ እና ቅድመ ዝግጅት (12ኛ ክፍል) ላጠናቀቁ ደረጃ 5 ሰልጣኞች መቁረጫ ነጥብ፦

-ወንዶች አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር 179 እና ከዚያ በላይ፤
-ወንዶች አርብቶ አደር አካባቢዎች 168 እና ከዚያ በላይ፤
-ሴቶች አርብቶ አደር አካባቢን ሳይጨምር 168 እና ከዚያ በላይ፤
-ሴቶች አርብቶ አደር አካባቢ 157 እና ከዚያ በላይ፤
-ለሁሉም ክልል አካል ጉዳተኞች 142 እና ከዚያ በላይ ሆኖ ተቆርጧል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ይህንን የድካም ዓለም መገላገል ለእርሳቸው ዕረፍት ቢሆንም ለአገር ግን ታላቅ ጉዳት ነው " - ቅዱስነታቸው

" እግዚአብሔር በየዘመናቱ አገርን ያለ መካሪ፣ ሕዝብን ያለዘካሪ አይተወውም ! "

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ  ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ እረፍት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።

" እግዚአብሔር በየዘመናቱ አገርን ያለ መካሪ፣ ሕዝብን ያለዘካሪ አይተወውም  " ያሉት ቅዱስነታቸው " ለዚህም ምስክሩ ታላቅ አረጋዊ ፣ የበሳል አእምሮ ባለቤት፣ አገርን የሚወዱ፣ ሕዝባቸውን የሚያከብሩ፣ የተጠቁት ወዳጅ ፣ የትውልድ አባት የሆኑት የክብር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ነበሩ " ብለዋል።

" ኢትዮጵያ በጣት ከሚቆጠሩ አረጋውያን፣ አፈ ማር ከሆኑ መካሪዎችዋ መካከል አንዱ የሆኑትን፣ ለመወደድ የታደሉትን የዘመናችን ጌጥ አጥታለች " ሲሉ ገልጸዋል።

" ይህንን የድካም ዓለም መገላገል ለእርሳቸው ዕረፍት ቢሆንም ለአገር ግን ታላቅ ጉዳት ከመሆኑም በላይ ዕድሜን ከጥበብ ጋር ያዋሐዱ በሁሉ ዘመን አይገኙምና ኀዘናችን ጥልቅ ነው " ብለዋል።

ቅዱስነታቸው ለቤተሰቦቻቸው፣ ለእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጽናናትን ተመኝተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በጥራት፣ በብራንድና በባትሪ ቆይታ አስተማማኝ የሆኑ የተለያዩ ሞዴል ላፕቶፖች በፈለጉት ስክሪን መጠን፣ ኮር አይ እና ጀነሬሽን አሉን።

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ. ሁሉም አሉን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት 👉 @samcomptech

@sww2844
0928442662 / 0940141114

Telgram : /channel/samcomptech

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ኢትዮጵያ የዩሮ ቦንድ ዕዳዋን መልሶ ለማዋቀር ያደረገችው ድርድር መክሸፍና መዘዞቹ ምን ይሆናሉ ?

ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. 2014 ከዓለም አቀፍ ገበያ በዩሮ ቦንድ አንድ ቢሊየን ዩሮን ለመበደር የበቃችው የአገሮችን ብድር የመክፈል አቅም የሚለኩት እንደ ፊች፣ ፑር እና ሙዲ የመሳሰሉ ተቋማት በአማካይ ‹‹B›› የተሰኘውንና በአንፃሩም ጥሩ የተባለ ደረጃ ሰጥተዋት እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

እነዚሁ የአገሮችን ብድር የመክፈል አቅም የሚለኩ ተቋማት አገሪቱ ብድር የመክፈል ጊዜዋ በደረሰ ጊዜ ከሁለት ዓመታት በፊት ማለትም በ2023 ዓ.ም. ደረጃዋን በእጅጉ አውርደው ወደ cc- ድረስ ዝቅ አድርገውታል።

ያኔም ብድሩ የተወሰደው በኢንዱስትሪ ፓርኮች ግንባታ ላይበማዋል ምርታማነትን አሳድጎ ብድሩንም መመለስ ይቻላል በሚል ነበር፡፡

ከዚያ ወዲህ ግን ኢትዮጵያ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና ከሁለት ዓመታት በላይ በዘለቀ ደም አፋሳሽ ጦርነት ስትናጥ ኢኮኖሚዋ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ገብቷል።

በዩሮ ቦንድ ከተበደረችው ብድር ባለፈ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና መንግስታት የተበደረቻቸውን ብድሮች የመክፈሏ ነገር ችግር ውስጥ ስለገባ የብድር መክፈያ ጊዜዋ እንዲራዘምላት ከአበዳሪዎቿ ጋር ተደጋጋሚ ድርድሮችን ስታደርግ ቆይታለች፡፡

ሆኖም ድርድሩ ውጤታማ መሆን ባለመቻሉና አገሪቱ ከብድርና ዕርዳታ እየተገለለች መጥታ ብድር መክፈል እያቃታት በመሆኑ የብድር መክፈያ ጊዜ ሽግሽግ ድርድሩ እስኪሳካ ጊዜያዊ የብድር መክፈያ ጊዜ የማራዘም መርሐ ግብር ውስጥ ተገብቶ ቆይቷል፡፡

ከሰሞኑም ኢትዮጵያ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ዕዳዋን የመክፍያ ጊዜ ለማራዘም ያደረገችው ድርድር ያለ ውጤት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ የአበዳሪዎቹ ኮሚቴ ጉዳዩን ወደ ሕግ ለመውሰድ እንደሚገደድ አስታውቋል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ማክሰኞ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ እ.ኤ.አ. በ2024 ተከፍሎ መጠናቀቅ የነበረበትን ከ13 ዓመታት በፊት በዩሮ ቦንድ ሽያጭ የተበደረችውን አንድ ቢሊዮን ዶላርና 6.625 በመቶ ወለድ ያካተተ ዕዳ መልሶ ማዋቀር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ፣ ቦንዱን ከገዙት (አበዳሪዎች) ቡድን ጊዜያዊ ኮሚቴ ጋር ለሶስት ሳምንታት ገደማ የተገደበ ውይይት ሲካሄድ መቆየቱን አስታውቋል።

ኢትዮጵያ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ዕዳዋን የመክፍያ ጊዜ ለማራዘም ያደረገችው ድርድር ያለ ውጤት ተጠናቀቀ፣ የአበዳሪዎቹ ኮሚቴ ጉዳዩን ወደ ሕግ ለመውሰድ እንደሚገደዱ አስታውቀዋል፡፡

በውይይቱ ላይም ከኢትዮጵያ መንግሥት ተወካዮች በተጨማሪ በኢትዮጵያ መንግሥት የተቀጠሩት ዋይት ኤንድ ኬዝ ኤልኤልፒ የተባለ የሕግ አማካሪና ላዛርድ የተባለ የፋይናንስ አማካሪ መሳተፋቸውን ገልጿል።

የኢትዮጵያን ቦንድ የገዙ ቡድኖች በመወከል ደግሞ ቡድኖቹ ያቋቋሙት ጊዜያዊ ኮሚቴና የሕግና የፋይናንስ አማካሪዎች መሳተፋቸውን ጠቅሷል።

ጉዳዩን በሚመለከት ባለሙያዎች ምን አሉ ?


የቢዝነስና ኢንቨስትመንት አማካሪው አቶ ከፈለኝ ኃይሉ የድርድሩ አለመሳካት ምንነት እንዲሁም ሊኖረው የሚችለውን ተፅዕኖ ለሪፖርተር ጋዜጣ ሲያብራሩ፣ ቴክኒካል የሚሏቸውን ሁነቶች በመጥቀስ " አለመተማመን እንዳለ አመላካች ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" አልተሳካም ማለት መሉ በሙሉ ተስፋ የለውም ማለት አይደለም፣ መስማማት ያልቻሉት ፋይናንስ ነክ ባልሆኑ ጉዳዮች ነው። በቀጣይ በሚኖር ድርድር መስማማት ካልቻሉ ግን ኢትዮጵያ ዕዳዋን መከፍል የማትችልበት ሁኔታ (Default) ውስጥ ትገባለች ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያ ጥሩ አይደለም " ብለዋል።

ኢትዮጵያ ዕዳዋን መክፈል ከማትችልበት ሁኔታ (Default) ውስጥ ከማስገባቱ በተጨማሪም ተሻጋሪ ተጽዕኖ እንደሚኖረው ፤ በዋናነትም ኢትዮጵያ የወሰደችውን በድር መክፈል የማትችል ተደርጋ እንድትቆጠርና በዚህም ከሌሎች የግል አበዳሪዎች አዲስ ብድር ለማግኘት እንዳትችል እንደሚያደርጋት ወይም ብታገኝ እንኳን ፍተኛ ወለድ ክፍያ እንደሚሆን ገልጸዋል።

" በአጠቃላይ ይህ ሁኔታ ከተፈጠረ የኢትዮጵያን ብድር የመክፈል እይታ ያበላሻል " ብለዋል።

ድርድሩን ያለስምምነት መጠናቀቁን ተከትሎ የአበዳሪዎቹ ኮሚቴ ጉዳዩን በሕግ አግባብ ለማየት መወሰኑ ምን ዓይነት የሕግ አግባቦችን ያካትታል በሚል ጥያቄ ቀርቦላቸው መልሰዋል።

" ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ገበያው ወጥታ ሌሎች ብድሮችን እንዳታገኝ ሊያሳግዱ ይችላሉ። ከዚህ በተጨማሪም ሸቀጦችን ወደ አገር ለማስገባት ኤልሲ (Letter of Credit) ሙሉ በሙሉ መክፈት የማይቻልበት ሁኔታ ሊፈጥር ይችላል "  ብለዋል።


" በተጨማሪም በውጭ አገር የሚገኙ የኢትዮጵያ መንግሥት ሀብትና ንብረቶችን አስገድደው በማሸጥ እንዲከፈላቸው ሊያደርጉ ይችላሉ፣ በዚህም የኢትዮጵያ ንብረቶች ሊያዙ ይችላሉ " ሲሉ አስረድተዋል።


በሌላ በኩል በዚህ ምክንያት በኢትዮጵያ ላይ የሚፈጠረው የገጽታ መበላሸት ደግሞ የውጭ አገር ባለሀብቶች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመጡ ሊገድብ እንደሚችል ገልጸዋል።

የኢኮኖሚ ተንታኙ (ዶ/ር) ተስፋቸው ተፈራ ደግሞ ፥ ኃያላን መንግሥታት በአነስተኛ ወለድ ይሰጡ የነበረው ብድር እየተመናመነ በመምጣቱ አገሮች የካፒታል ፍላጎታቸውን ለማሟላት ወደ ዓለም አቀፍ የቦንድ ገበያ በመውጣት በቦንድ ሽያጭ ብድር የሚየመገኙበት ሁኔታ በገቡበት ወቅት ኢትዮጵያ በዩሮ ቦንድ ሽያጭ የተበደረችውን መክፈል ባለመቻሏ ድርድር ውስጥ መግባቷና ድርድሩም በስኬት አለመጠናቀቁ ዋጋ እንደሚያከፍል ተናግረዋል።

" ኢትዮጵያ የዩሮ ቦንድ ዕዳዋን መልሶ ለማወቀርና የክፍያ ጊዜውን ለማራዘም ያደረገችው ድርድር አለመሳካቱ እንዳለ የሚቀጥል ወይም በቀጣይ ድርድር ስምምነት የማይደረስበት ከሆነ፣ ከፓሪስ ክለብ አበዳሪዎች ተመሳሳይ የዕዳ ቅነሳና የመክፈያ ጊዜ ለማግኘት የመግባቢያ ስምምነት የደረሰችበትን ጉዳይ እንደሚያበላቸው ገልጸዋል።

የዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ጊዜያዊ ኮሚቴ አባላት ከኢትዮጵያ ጋርየተደረገው ድርድር ባለመሳካቱ መበሳጨታቸውንና በቀጣይከኢትዮጵያ መንግሥት የተሻሻሉ የድርድር ፍሬ ሐሳቦችን ለመስማት ዝግጁ መሆናቸውን፣ ነገር ግን አሁን ባለበት ደረጃ ድርድሩ እክል እንደገጠመውና መፍትሔ ካልተገኘም ኢትዮጵያን በሕግ እንደሚጠይቁ ገልጸዋል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#NGAT

የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ተለቋል።

የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ዙር የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ዛሬ ከሰዓት መለቀቁን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል።

ውጤት ለማየት 👇
https://result.ethernet.edu.et/

ከ28 ሺህ በላይ ተፈታኞች ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም በ53 የፈተና ማዕከላት  የተሰጠውን ፈተና መውሰዳቸው ይታወሳል።

ሁለተኛው ዙር የ NGAT መግቢያ ፈተና በጥር 2018 ዓ.ም ይሰጣል።

Via @tikvahuniversity

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የኑሮ ሁኔታ በጣም ከባድ ነው የሚከፈለን ብር 760 ነው፡፡ ... እኛ ሴቶች እንጨት ለቅመን ነው የምንማረው ወንዶችም እንጨት እየለቀሙ እየጋገሩ ይማራሉ " - የመምህራን ማሰልጠኛ ተማሪዎች

ከ40 አመት በላይ መምህራንን በማሰልጠን የሚታወቀዉ የደሴ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ በመምህርነት በዲግሪና ዲፕሎማ የሚሰለጥኑ ተማሪዎች በወር ለምግብ የሚሰጣቸዉ 760 ብር ለመኖር ስላላስቻላቸዉ ሰዉ ቤት ተቀጥረዉ በቤት ሰራተኝነት ከጫካ ጭራሮ እየለቀሙ የራሳቸውን ምግብ ለማብሰል መገደዳቸውን ገልጸዋል።

ከእነዚህ ተማሪዎች አንዱ በእንጨት ለቀማ ወቅት ሕይወቱ እንዳለፈም ሰልጣኞቹ ተናግረዋል።

በወር የሚከፈላቸው 760 ብር ነው ፤ አንድ እንጀራ ለመግዛት የዋጋውን ውድነት አልቻሉትም ከዚህ ኑሮ ውድነት በመነሳት ወንዶች ኩሽና ተፈቅዶላቸው እንጀራ እየጋገሩ እየኖሩ ናቸው። 

ነገ ተማሪዎችን ለማስተማር የሚሰለጥኑ መምህራን የሚማሩትን ሳይሆን የሚበሉትን በማሰብ የማገዶ እንጨት በመልቀም፣ የቀን የጉልበት ሠራተኛ በመሆን፣ እንዲሁም ሊጥ አብኩተው ለምግባቸው የሚሆን እንጀራ በመጋገር ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ ነው የተባለው።

ሰልጣኝ መምህራኑ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ምን አሉ ?

በ760 ብር የምግብ ወርሃዊ ክፍያ የመኖሪያ ቤት ተሰጥቷቸው በኮሌጅ የሚማሩ ተማሪዎች ከትምህርት በኋላ የሚመገቡትን ምግብ ለማብሰል በደሴ ወደሚገኙት የጦሳ፣ አዘዋና ሌሎች እንጨት ለመልቀም ወደሚያስችላቸው ጫካዎች ሲያመሩ ከሞት ጋርም ተጋፍጠዋል፡፡

ለመማር በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ በጦሳ ተራራ እንደዚሁም በአዘዋ ተራራ ካለቀምን በስተቀር እንጨት አይገኝም ብለዋል።

በዚህም አንድ ሳሙኤል የተባለ የእንግሊዝኛ ክፍል የዲግሪ ተማሪ በጦሳ ተራራ እንጨት ሊለቅም ሄዶ ህዳር 28 ቀን ህይወቱ አልፏል፡፡

ችግሩ በተለይ ሴቶች ላይ የጎላ ነው የምትለው ሠልጣኝ ተማሪ የግማሽ ቀን የቤት ሰራተኝነትና በሌሎች ስራዎች እራሳችን እየደጎምን ነው ትምህርት የምንማረው ብላለች፡፡ 

" የኑሮ ሁኔታ በጣም ከባድ ነው የሚከፈለን ብር 760 ነው፡፡ ባለን አቅም እየሰራንም ነው የምንማረው በትምህርታችን ላይ ውጭ ውለን ስንገባ እየደከመን ማጥናት እንቸገራለን እንጨት ለቅመን ነው የምንማረው ወንዶችም እንጨት እየለቀሙ እየጋገሩ ይማራሉ " ስትል ተናግራለች።

" አሁን አሁንማ ሥራም ጠፍቷል ፤
አሁን የቀን ስራ ሰርተን ለመማር የማንችልበት ጊዜ ላይ እንገኛለን " የሚለው ተማሪ " ወቅታዊ ሁኔታው ተጨማሪ ስራ ሰርተን ለመማር አላስቻለንም " ብሏል።

" ሴቶች የግማሽ ቀን ስራ ካገኙ ይሰራሉ ወንዶች ቅዳሜና እሁድ ይሰራሉ። ዘንድሮ ግን የለም፤ መስራት አትችልም የተግባር ልምምድ ስለምንሄድ ትንሽ ከበድ ይላል። ባለፈው አመት ይሻላል ውጭ ላይም ትንሽ አስፈሪ ነው ሰዓቱ " ሲል ገልጿል።

በትምህርቱ ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ ነው መባሉን
የደሴ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ መምህር የሆኑት መምህር አበበ ደሴ እንደሚገልፁት ተማሪዎች የዕለት ኑሯቸውን በማሰብ ስለሚጠመዱ ትምህርት የመቀበል አቅማቸው ውስን ሆኗል ብለዋል፡፡ 

" ግማሾች የቀን ስራ ሰርተው ነው የሚኖሩት። ሴቶችም ቢሆኑ በእንጀራ ጋጋሪና ካፍቴሪያ ውስጥ ተቀጥረው እየሰሩ ነው። ክፍል ውስጥም ገብተው ስታይ በአብዛኛዉ ከሚማሩበት የሚያንቀላፉበት ነው የሚበልጠው። ወጥተው የሚመገቡት የለም " ሲሉ አስረድተዋል።

የደሴ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ሀሰን ወርቁ በበኩላቸው ተማሪዎቹ ያሉበት ችግር ለመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል።

ወርሃዊ የምግብ ክፍያቸውም ከ760 ብር ከፍ እንዲል ለክልሉ ትምህርት ቢሮ/ጥያቄ መቅረቡን አመልክተዋል።

" በአብዛኛው ከመማር ማስተማሩ ይልቅ ስለ እሚበሉት ፣የሚጠጡት ነው የሚያስቡት በትምህርት ላይ ተፅዕኖ አለው። ይህንን ታሳቢ አድርገን ክልል ላይም ጥያቄ እያቀረብን ነው፡፡ " ብለዋል።

Credit - ዶቼ ቨለ ሬድዮ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" አጨዳ ላይ ቆይተው ምሳ ሊበሉ ጥላ ሥር አርፈው እየበሉ ባሉበት አምስት ሰዎች ተገድለዋል " - የአካባቢው ቤተክህነት አመራር

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በዚሁ ወር 25 ምዕመናን እንደተገደሉባት በገለጸችበት አርሲ ዞን ታጣቂዎች ትናንት በድጋሚ በተፈናቃይ አርሶ አደሮች ላይ ግድያ መፈጸማቸውን የአካባቢው ቤተ ክህነት አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ለደኀንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዲነገር ያልፈለጉት አመራሩ በሰጡን ቃል፣ ትናንት መርቲ ወረዳ ጋዶ የሚባል ቦታ ላይ " የሚሊሻ የጤፍ አጨዳ ውጡ ተብለው ታዘው አጨዳ ላይ ቆይተው ምሳ ሊበሉ ጥላ ሥር አርፈው እየበሉ ባሉበት አምስት ሰዎች ተገድተዋል " ብለዋል።

" ሸሽተውም ይሁን ተይዘው ያልታወቀና ያልተገኙ የጠፉ ሰዎችም አሉ። ሸሽተው የተጠፉ ናቸው። ቁጥራቸው በትክክል አልታወቀም ግን ብዙ ናቸው " ሲሉም አክለዋል።

የሟች አርሶ አደሮች አስከሬን ትላንት ምሽት ወደ ከተማ መግባቱን፣ የቀብር ሥነ ስርዓቱ ዛሬ በመርቲ ወረዳ አቦምሳ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን እንደተፈጸመ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በወረዳው በዚሁ ወር የተፈጸመውን ግድያ በማስታወስ የአሁኑም ግድያ በዚያው አቅራቢያ መፈጸሙን የገለጹት እኝሁ አካል፣ ሟቾቹን " ከዚህ በፊት አፈናቅለዋቸው ነበር " ሲሉ ገልጸዋል።

ጥቃቱ ተደጋጋሚ መሆኑንና አራት አመት እንዳስቆጠረ፣ በዚህ አራት አመት ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንደተገደሉ አስረድተዋል።

" የትላንቱ ግድያ በተፈጸመበት ቦታ አጠገብ ህብረተሰቡ ተፈናቅሏል። ታጣቂዎች በቤታቸው እየገቡ ይገድሏቸዋል፤ ያንን እያየ  ሰው ተፈናቅሏል፤ ከዚህ ሸሽተው የነበሩ ሰዎች ናቸው 'ሚሊሻ አገርን እየጠበቀ ነው፤ ኑ ለአጨዳ ውጡ' በተባሉበት ነው የተገደሉት፤ ደኀና ተደብቀው የነበሩት ናቸው የተገደሉት " ነው ያሉት።

" ከዚህ ቀደምም ለአባቶች መልዕክት አስተላልፈናል። ሰሚ አካል ካለ ይህንን ሰምቶ መንግስት እንዲህ አይነቱን ወንጀለኛ አውጥቶ ህዝቡ በሰላም የሚኖርበትን ነገር ቢመቻችልን። እየሆነ ያለው ነገር በጣም ከባድ ነው " ብለዋል።

በጥቅምት 2018 ዓ/ም በአርሲ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች 25 የኦሮቶዶክስ እምነት ተከታዮች መገደላቸውን ቤተ ክርስቲያኗ ጭምር ማሳወቋ የሚታወስ ሲሆን፣ የትናንቱን የአርሶ አደሮች ግድያ ጨምሮ በዚሁ ወር የሟቾች ቁጥር 30 ደርሷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአካባቢውን አካላት ምላሽ ለማካተት ሙከራ ቢያደርግም ለጊዜው አልተሳካም። የቅርቡን የዞኑ ግድያ በተመለከተ ምላሽ የጠየቅናቸው የዞኑና የክልሉ አካላት ፈቃደኛ ሳይሆኑ መቅረታቸው ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ድጋፍ ማድረግ በምትፈልጉበት ወቅት ተገቢውን ማጣራት አድርጉ " - ፖሊስ

ያልታመመ ሰው ታማሚ በማስመሰል ተሽከርካሪ ውስጥ አስተኝተው ከህብረተሰቡ ገንዘብ ሲለምኑ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።

አንድን ወጣት የኩላሊት ታማሚ በማስመሰል በተከራዩት የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- 26734 ኦሮ የሆነ ሚኒባስ ውስጥ አስተኝተው በእርዳታ ስም ከህብረተሰቡ ገንዘብ ሲሰበስቡ የነበሩት ተጠርጣሪዎች ሊያዙ የቻሉት አያት አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ባደረገው ክትትል እንደሆነ ገልጿል።             

በተሽከርካሪው ውስጥ በተደረገ ፍተሻ ፦
- በዕርዳታ ስም የተሰበሰበ 23 ሺህ 325 ብር
- በሃሰት የተዘጋጀ የህክምና ሰነድ እና የድጋፍ ደብዳቤ ተገኝቷል።

በሰነዶቹ ላይ በተደረገው ማጣራት ሃሰተኛ መሆናቸው እንደተረጋገጠ ፖሊስ ገልጿል፡፡

ገንዘብ በመሰብሰብ ስራ ላይ ለተሰማሩት ግለሰቦች በቀን 300 ብር የሚከፈላቸው ሲሆን ተሽከርካሪውን በቀን 3000 ሺህ ብር እንደተከራዩት እና ለአሽከርካሪው 1 ሺህ ብር እንደሚከፈለውም አረጋግጫለሁ ብሏል።             

በወንጀሉ በቀጥታ የተሳተፉ እና የተባበሩ በአጠቃላይ 9 ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝም አሳውቋል።

ህብረተሰቡ በየመንገዱ የሚካሄዱ እንዲህ አይነት ህገ ወጥ ተግባራትን በመከላከል ረገድ የድርሻውን እንዲወጣ ፤ ድጋፍ ማድረግ በሚፈልግበት ወቅት ተገቢውን ማጣራት እንዲያደርግና አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ ለሚመለከተው አካል ጥቆማ እንዲሰጥ ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ጦርነት ብታሸንፍም ባታሸንፍም ጣፋጭ ሆኖ አያውቅም " - ጀነራል ሳሞራ የኑስ

➡️ " ህዝቡ እስካሁን ድረስ የጦርነቱን ጦስ በጫንቃው ተሸክሟል፡፡ እንደዚህ ዓይነት  ከባድ ስህተት  መደገም የለበትም ! "

" በትግራይ ክልል የሀሳብ ልዩነት ሲፈጠር በጦርነት ብቻ ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆም አለበት " ሲሉ የቀድሞው  የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል ሳሞራ ዩኑስ ተናገሩ።

ጀነራል ሳሞራ ይህን ያሉት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት ቃል ነው።

ጀነራል ሳሞራ የኑስ ምን አሉ ?

" ከዚህ ቀደም  የተፈፀመው ከባድ ስህተት የትግራይን ህዝብ ዋጋ አስከፍሏል፡፡  አሁን የትግራይ ህዝብ ጦርነት በቃኝ ብሏል፡፡  በሆነ አጋጣሚ የጦርነት አዝማሚያ ቢፈጠር እንኳ ህዝቡ ይህንን የመደገፍ ሀሳብ የለውም።

ከዚህ ቀደም ችግሮችን በውይይት መፍታት ባለመቻሉ የተቀሰቀሰው ጦርነት የትግራይን ህዝብ ከባድ ጉዳት አድርሶበታል፡፡ ህዝቡ እስካሁን ድረስ የጦርነቱን ጦስ በጫንቃው ተሸክሟል፡፡ እንደዚህ ዓይነት  ከባድ ስህተት  መደገም የለበትም።

ጦርነት ብታሸንፍም ባታሸንፍም ጣፋጭ ሆኖ አያውቅም። በክልሉ በርካታ ወጣት ህይወቱን አጥቷል፣ እናቶችም በሀዘን ተጎድተዋል፣ ተቸግረዋልም፤ በመሆኑም ህዝቡ በተደጋጋሚ ውጊያ ውስጥ ሊማገድ አይገባውም።

በትግራይ ውስጥ ማንኛውም ችግር ወይም የሀሳብ ልዩነት ሲፈጠር በጦርነት ብቻ ለመፍታት የሚደረግ ሩጫ መቆም አለበት። ልዩነቶች በሰላምና በሰላም ብቻ መፈታት አለባቸው በሚል እምነት መፅናት ያስፈልጋል።

በክልሉ የጦርነት ችግር ይመጣል እያሉ ያልተጨበጠ ወሬ የሚለፍፉ የጦር ጀነራሎችን እሰማለሁ። ይህ የግል ሀሳባቸው ሊሆን ይችላል፤ እኔ የምላቸው ግን የእውነት የህዝብ አገልጋይ ከሆኑ በትግራይ ክልል ያለውን የፀጥታ ችግር መፍታት የመጀመሪያው ጉዳያቸው ሊያደርጉት ይገባል። " ብለዋል።

#ኢፕድ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ባለፉት ሦስት ወራት በአዲስ አበባ በወቅቱ የተመዘገበ ፍቺ ቁጥር 853 ነው " - የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት

የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በመዲናዋ የወሳኝ ኩነት ምዝገባ የሚያከናውንባቸው አምስት ኩነቶች ማለትም በልደት፣ ሞት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ እና ጉዲፈቻ በአጠቃላይ በሩብ አመቱ በወቅቱ፣ በዘገየ እና ጊዜ ገደብ ባለፈበት 172 ሺ 11 ኩነቶችን ምዝገባ ማከናወኑን ገልጿል።

ኤጀንሲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጸው በሩብ አመቱ በአዲስ አበባ በወቅቱ፣ በዘገየ እና ጊዜ ገደብ ባለፈበት የተመዘገበ ፍቺ ቁጥር 3 ሺ 32 መሆኑን አሳውቋል።

ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጥጋቡ ሹመይ"ፍቺን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ በሩብ አመቱ 3 ሺ 32 ተብሎ ነው ነገር ግን አብዛኛው ተመዝጋቢ ጊዜ ገደቡ ያለፈበት ተመዝጋቢ ነው"ብለዋል።

እንደ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገለጻ ባለፉት ሦስት ወራት በወቅቱ ወይም ፍቺው በተፈጠረ በ 30 ቀናት ውስጥ ምዝገባ ያከናወኑ ነዋሪዎች ቁጥር 853 ነው።

የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የኩነት እና የነዋሪዎች ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጥጋቡ ሹመይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ?

" ወሳኝ ኩነቶች በሦስት ደረጃ ይመዘገባሉ የመጀመሪያው በወቅታዊ ሲሆን ልደት እንደተከሰተ በ90 ቀናት ውስጥ መመዝገብ አለበት የቀሩት ኩነቶች ደግሞ በ 30 ቀናት መመዝገብ ይኖርባቸዋል።

ሁለተኛው በዘገየ ተብለው የሚመዘገቡ ናችው የዘገየ ተብለው የሚመዘገቡ ኩነቶች በተከሰተ በአንድ አመት ውስጥ ምዝገባ ሲከናወን ማለት ነው።

ሦስተኛው ጊዜ ገደቡ ያለፈበት ምዝገባ የሚባለው ነው እነዚህ ኩነቶች በተከሰቱ ከአንድ አመት በላይ ጊዜ ገደብ ካሳለፉ በኋላ የሚመዘገቡ ከሆነ ጊዜ ገደቡ ያለፈበት ምዝገባ ይባላሉ።

የወሳኝ ኩነት ምዝገባዎች በሃገር አቀፍ ደረጃ እና በአዲስ አበባ እየተከናወነ ያለው በሦስቱም መንገዶች ነው ።

በሩብ አመቱ በልደት፣ በጋብቻ ፣ ፍቺ፣ ሞት እና ጉዲፈቻ በወቅቱ መመዝገብ የቻልነው 30 ሺ 571 ናቸው።

ልደት 25 ሺ 876 ፣ ጋብቻ 2536፣ ፍቺ 853  ፣ ሞት 1258 ፣ ጉዲፈቻ 58 በወቅቱ ተመዝግበዋል።

ከእቅዳችን አንጻር ሁሉም ኩነቶች ላይ የተሻለ አፈጻጸም ቢኖረንም የሞት ምዝገባ ግን ከእቅዳችን አንጻር ዝቅተኛ ነው ይህ የሆነበት ምክንያት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር (እድር) በቅንጅት መስራት እንዳለብን ያሳያል።

በዘገየ ምዝገባ ማለትም ከተከሰተ ከ 30 ቀን እስከ አንድ አመት ባለው ጊዜ የተመዘገበ ልደት 4,194 ፣ ጋብቻ 844  ፣ፍቺ 416 ፣ ሞት 818 ጉዲፈቻ 12 መዝግበናል።

ጊዜ ገደብ ባለፈበት የተመዘገቡ ኩነቶች ልደት 123 ሺ 717 ፣ ጋብቻ 7326፣ ፍቺ 1763 ፣2320 ሞት ፣ጉዲፈቻ 30 ናቸው።

በአጠቃላይ በሩብ አመቱ በአምስት ኩነቶች በወቅቱ፣ በዘገየ እና ጊዜ ገደብ ባለፈበት ብለን የመዘገብናቸው ኩነቶች 172 ሺ 11 ኩነቶችን ናቸው።

ከእዚህ ውስጥ ልደት 153 ሺ 787፣ ጋብቻ 10 ሺ 696፣ ፍቺ 3,032 ፣ ሞት 4 ሺ 396፣ ጉዲፈቻ 100 ተመዝጋቢዎችን ይይዛሉ።

ፍቺን በተመለከተ የሚዘዋወረው መረጃ በሩብ አመቱ 3 ሺ 32 ተብሎ ነው ነገር ግን አብዛኛው ተመዝጋቢ ጊዜ ገደቡ ያለፈበት ተመዝጋቢ ነው።

ጊዜ ገደቡ ያለፈበት ምዝገባ ማለት ከእዚህ በፊት ፍቺው ተከስቶ ሳያስመዘግቡት ቀርተው የፍቺ ምስክር ወረቀቱን ያላገባ ለማውጣት እና ለተለያዩ አስተዳደራዊ ጉዳዮች በሚጠየቁበት ወቅት መጥተው የተመዘገቡ ናቸው።

ወሳኝ ኩነት ምዝገባውን ለማሳደግ ለምሳሌ ልደትን በተመለከተ ከ 143 ጤና ተቋማት ጋር በቅንጅት ነው የምንሰራው።

ፍቺም በወቅቱ እንዲመዘገብ ለማድረግ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 11 ምድብ ችሎቶች አሉት በሁሉም ምድብ ችሎቶች የሚፈጸሙ ፍቺዎችን በወቅቱ ለመመዝገብ ባለሞያዎቻችን ገብተው የመመዝገብ ስራ እየሰራን እንገኛለን የጉዲፈቻም በተመሳሳይ።

ከሞት ምዝገባ ጋር ተያይዞም የሞት መረጃ የምናገኘው በጤና ተቋማት እና በማህበረሰብ በኩል ነው በማህበረሰቡ ውስጥ የሚከሰቱ የሞት መረጃዎች የሚገኙት በእድሮች በኩል በመሆኑ የእኛ ወረዳዎች ከእድር አመራሮች ጋር በመስራት ላይ እንገኛለን።

በቅርቡ አዲስ ሲስተም አልምተናል ለምረቃ ዝግጅት ላይ እንገኛለን ወደ ተግባር ሲገባ ወደ እድሮች ተደራሽ አድርገን በእድር አባሎች ላይ የሚከሰት ሞት እዛው ተመዝግቦ የምዝገባ መረጃው በሲስተሙ ወደ እኛ የሚገባ ይሆናል።

በጤና ተቋማትም ሲስትሙ ተደራሽ ይሆናል ስልጠና ሰጥተን አስፈላጊውን ግብአት አሟልተን በሙከራ ደረጃም እየወሰድን ወደ ተሟላ የምዝገባ ስርአት እንዲገቡ እናደርጋለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የልጄ ሊዛ ደም ባክኖ ሊቀር ነው፤ ፍትህ ልናጣ ነው ተቸግረናል " - የሟች ተማሪ ሊዛ አባት

" ባለቅስም እንባ ነው ሊዛን አላገኘኋትም፥ የልጄን ገዳይ ግን አያይዙኝ " - እናት


ከሳምንታት በፊት በደሴ ከተማ ተደፍራና ተገድላ የተገኘቸው ዘንድሮ ትመረቃለች ተብላ ስትጠበቅ የነበረችው የፋርማሲ ተማሪዋ ሊዛ ደሳለ ወላጆች እስካሁን የልጃቸው ገዳይ መያዝና አለመያዙን ባለማወቃቸው ፍትህ እንዲሰጣቸው ጠየቁ።

የተማሪ ሊዛ አባት መምህር ደሳለ ሞላ፣ ከሚያገኙት ትንሽ የመምህር ደመወዝ እየከፈሉ ልጃቸውን እያስተማሩ እያለ የሞት ዱብ እዳ እንደሰሙ፣ በጉዳዩ ላይ በሳምንት ፍትህ እንደሚሰጣቸው ቢነገራቸውም እሳከሁን ምንም እንዳልተባሉ ዛሬ ምሽት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የተማሪዋ አባት መምህር ደሳለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

" እኔ ሀዘን ላይ በመሆኔ የሊዛ እክስት አጎቶች 'ለሕግ አመልክተን እንምጣ' ብለው ሂደው ነበር። በዚህም 'የህግ ጉዳዩን ባጭር ጊዜ እንጨርሳልን፣ በጣም ቢበዛ ሳምንት ነው የሚፈጀብን ከዚያ ውጭ አይሄድም' እንዳሏቸው ነበር የነገሩኝ።

እኔም የተጨበጣቸው ነገር ይኖራል በሚል በተስፋ ነበር የቆየሁት። ነገር ግን አንድ ሳምንት አልፎ አሁን ወደ ሶስተኛ ሳምንት ሆነ። የፍትህ ሂደቱ እንዳውም እየተዳከመ መጥቷል። ነገሩ እየቀዘቀዘ ነው። ለውጥ አላየሁም።

ቤተሰቡ ተበሳጭቷል፥ 'ሶስትም ሆነ አራት  ኮንትራት መኪና ይዘን ደሴ ፖሊስ ጣቢያ ገብተን ምርመራው ከምን ደረሰ? ብለን ጮኸን፥ ልጃችንም የወደቀችበት ቦታ ላይ አልቅሰን እንመጣለን' በሚል አዲስ አቋም ተይዟል። እኔ ቆይ እያልኩ ነው። መሄዳችን አይቀርም።

እኔ በቶሎ ፍትህ እንደሚሰጠኝ እርግጠኛ ነበርኩ፤ ምክንያቱም ልጄ ከጓደኞቿ ቤት 10 ሜርት ባልራቀ ቦታ ነው ተደብድባ ህይወቷ ያለፈው። የጠሩዋት ሰዎች ሲጯጯሁ ሳይሰሙ አይቀሩም ግን 'አንሄድም' ብለዋል። እነዛ ሰዎች ማዳን ይችሉ ነበር። ያ የሆነው ሆኖ አልፏል።

ግን አንድ ሰሞን ሆሆ ተብሎ ጉዳዩ አሁን ግራ እያጋባኝ መጥቷል። የልጄ ሊዛ ደም ባክኖ ሊቀር ነው፣ ፍትህ ልናጣ ነው ተቸግረናል። የህግ ክፍተት ያሳያል። ምናልባት ሂደቱ ውስብስብ ሊሆን ይችላል፥ እኛ ግን እምነታችን እየተሸረሸረ መጥቷል።

በሰባት ቀን ብለውን አሁን ሶስተኛ ሳምንት ባንገባ ተስፋችን አይሟጠጥም ነበር፣ ገና ነው ቢሉን ኑሮ። ተቃርበናል ካሉ በኋላ ይህን ብሎን የነበረው ደሴ ፖሊስ ምርመራ ቡድን ነው። መራቅና መቀዝቀዝ ምን ማለት ነው ?

ሕጉ እየላላ ነው መጣው፤ ምን አይነት ጥርጣሬና ሀሳብ አለ? በሚል እንኳ ደውለው አልጠየቁንም። መረጃም ከመሰብሰብ አኳያ ክፍተት አለባቸው። ወይ ገዳዩን ይዘዋል፥ አለበለዚያ ግን እኛን ባለመጠየቃቸው ራሱ ለምን? የሚል ጥያቄ እያስነሳብኝ ነው" ብለዋል።

መምህር ደሳለ፥ " ካልተረጋገጠ እኮ የልጀ ገዳይ ተይዟል ሊባል አይችልም። ተጠርጣሪ የተያዙ ሰዎች አሉ። ያንም እርግጠኛ አይደለሁም። መርማሪ እንደሚለው ግን ወደ 9፣ 10 ተጠርጣሪዎች ታስረው ነበር ወደ 3፣ 4 የተፈቱ አሉ " ሲሉም ተናግረዋል።

የተማሪ ሊዛ እናት ወ/ሮ የንጉሴ ጌጤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

" ፍትህ እንዲሰጠኝ እፈልጋለሁ። እስካሁን ፍትህ የምናገኝ ነው መስሎኝ የነበረው። አሁን ላይ ግን ዝም ብሎ ነው ያለው። ውስጤ ቆስሏል። ቤተሰቦቼ 'ደሴ ሄደን እንጩህ' እያሉ ነው። የሚለቀስበት ጠፍቶን ነው እንጅ ፍትህ እንፈልጋለን።

በእርግጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው በሊዛ ሞት ያስተዛዘነኝ። ግን ደግሞ ልጄ የደሴ ህዝብ በሚኖርበት 10 ሜትር ላይ ስትወድቅ/ስትሞት ምንም ሳይሰሙና ጩኸት ሳይኖር አይቀርም ነበር። ቢያንስ የልጄን ገዳይ ማወቅ አለብኝ። ባለቅስም እንባ ነው ሊዛን አላገኘኋትም፣ የልጄን ገዳይ ግን አያይዙኝ " ሲሉ ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ጉዳዩን ይዘውታል የተባሉትን ኢንስፔክተር ማብራሪያ ቢጠይቀም ጉዳዩ በምርመራ ሂደት መሆኑን ጠቁመው ዝርዝር ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል። የደሴ ከተማ ፓሊስን ለማግኘት ዛሬ ምሽት ያደረግነው ጥረት ደግሞ ያልተሳካ ሲሆን፣ በድጋሚ የምንጠይቅ ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamiliyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ከአትላስ - ቦሌ መድኃኒዓለም - ብራስ ኮሪደር !

የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ከአትላስ - ቦሌ መድኃኒዓለም - ብራስ የሚዘልቀውን ኮሪደር በራስ ኃይል እና በማህበራት ተሣትፎ እየገነባ ይገኛል፡፡

ይህ ኮሪደር በአጠቃላይ 2 ነጥብ 34 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን ሲሆን፣ ከ42 እስከ 50 ሜትር የጎን ስፋት አንዲኖረው ተደረጎ እየተገነባ ነው፡፡

ከቦሌ መደኃኒዓለም እስከ ብራስ ያለው የመንገዱ ክፍል፦
➡️ 1 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የሳይክል እና ምቹ የእግረኛ መንገድ፣
➡️ የህፃናት መጫዎቻ ሥፍራ፣
➡️ የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች፣
➡️ የመኪና ማቆሚያና ተርሚናል፣
➡️ አረንጓዴ ስፍራዎች እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎችን ያካትታል፡፡

በእስከ አሁኑ የግንባታ ሂደት፦
° የድሬኔጅ መስመር፣
° የውሃ፣
° የቴሌና የመብራት መስመሮች ዝርጋት፣ እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ስራዎች በባለድርሻ አካላት ቅንጅት በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡

የኮሪደሩ ግንባታ አፈፃፀም በየዕለቱ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገለት ሲሆን፣ በጥራት እና በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ለማብቃት በቀንና በለሊት ክፍለ ጊዜ በትጋት በመሰራት ላይ ነው።

(የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን)

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ሀገራችንን አላህ ሰላም ያድርግልን። ሀገራችንን አላህ አማን ያድርግልን።

እኛም የምንዋደድ አላህ ያድርገን። የምንከባብር አላህ ያድርገን። የምንረዳዳ አላህ ያድርገን። የምንመካከር አላህ ያድርገን።

ጥላቻን ከውስጣችን አላህ ያጥፋው።

በሃይማኖትም ሆነ በፖለቲካ መገዳደልን፣ መጋጨትን፣ መለያየትን ከሀገራችን ከውስጣችን አላህ ያንሳልን።

እንደ አባቶቻችን ከዛም በበለጠ የምንተባበር ፣ የምንከባበር፣ የምንዋደድ ፣ የምንረዳዳ አላህ ያድረገን። " - ታላቁ አባት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" እርቦናል፤ ጠምቶናል ፣ የ8 ወር ደመወዝ አልተከፈለንም። ... በመጠጥ ውሃም ችግር ላይ ወድቀናል፣ እኛ ማንን እንጠይቅ፣ በየጊዜው አመራሮች ይቀያየራሉ፣ ህዝቡ ተቸግሯል " - ሰልፈኞቹ

➡️ " የሀገር ሽማግሌዎች መጥተው ' ለ3 ቀን ታገሱን ' ሲሉ ጠየቁን፣ እኛም አባቶቻችንን ማስከፋት ስላልፈለግን እሺ ብለናቸዋል "

በአፋር ክልል የገዋኔ ወረዳ ዞን 3 ነዋሪዎች ከደመወዝ ጥያቄ እና ከመጠጥ ውሃ ችግር ጋር በተገናኘ በዛሬው እለት ጥቅምት 10/2018 ዓ/ም ከጠዋቱ ሶስት ሰአት አካባቢ ህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ መንገድ በመዝጋት አካሂደዋል።

ሰልፈኞቹ በሰልፉ ላይ ፦
- " ካልተከፈለን አናስተምርም "
- " እኛ የገዋኔ ነዋሪዎች እርቦናል ፤ ጠምቶናል "
- " ለወላጅ አልባ ህጻናት የ8 ወር ደመዝ ይሰጠን " የሚሉ እና ሌሎችም ደምጾችን አሰምተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም በሰልፉ ላይ የነበሩ የወረዳ ነዋሪዎችን ስለጉዳዩ ጠይቋል።

ነዋሪዎቹ በዝርዝር ምን አሉ ?

" የገዋኔ ወረዳ ሁሉም የመንግስት ሰራተኞች በ2017 ዓ.ም የ5 ወር ደመወዝ አልተከፈለንም፣ በ2018 ዓ.ም በጀት አመት ደግሞ የሀምሌ፣ የነሀሴ እና የመስከረም ወር አልተከፈለንም። በአጠቃላይ የ8 ወር ማለት ነው።

ይህ የሆነው በወረዳው የፋይናንስ ጽህፈት ቤት ሃለፊ ነው። ሃላፊው ወረዳው ላይ አይኖርም፣ አዲስ አበባ እና አዋሽ እንደሚኖር ነው የሰማነው። ቢሮ ስንሄድ አናገኘውም። ችግሩ የማን እንደሆነም እንኳ ማወቅ አልቻልንም።

ክልሉ እራሱ ጥያቄያችንን ሰምቷል፣ በባለፈው አመት ሲከፍሉን የመቼ፣ የመቼ ወር እንኳ እንደከፈሉ አልነገሩንም።

አልፎ አልፎ ይከፍላሉ፣ እኛን እያዘናጉን ነው፣ በዘንድሮው አመት ችግሮች ይስተካከላሉ ብለን ስንጠብቅ ይሄው መስከረም አልቆ ጥቅምት ላይ ነን፣ እስካሁን ግን የተስተካከለ ነገር የለም።

የመጠጥ ውሃ ችግር በክልሉ እንደአጠቃላይ እንዳለ እናውቃለን፣ ነገር ግን የእኛ የተለየ ነው፣ ይህን የውሃ ችግር ለመቅረፍ በ2012 ዓ.ም ከወረዳዋ 30 ኪሎሜትር እርቀት ላይ ከሚገኝ ቦታ ተቆፍሮ ተሰርቶ ነበር። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ተበላሽቷል፣ ከዛም በኋላ ችግሩ ተበብሶ ቀጥሏል።

አሁን ላይ አንዱን የሮቶ ውሃው ከ250 እስከ 350 ብር እየገዛን ነው፣ ይህንን ራሱ ለመግዛት እንኳ ደመወዛችን እየተሰጠን አይደለም። የገዋኔ ነዋሪ እያየው ያለው ሰቆቃ በጣም ያሳዝናል።

የወረዳዋ ነዋሪዎች አብዛኞቹ ወላጅ አልባ ህፃናት ናቸው። እርዳታ አያገኙም፣ በጣም ችግር ላይ ናቸው፣ ደመወዝ በአግባቡ ቢሰጥ ኖሮ በቤተሰቦቻቹው የጡረታ ገንዘብ ይተዳደሩ ነበር። ይህ ግን አልሆነም።

ከሌላ አካባቢ መጥተው በወረዳዋ በመምህርነት የሚያገለግሉ መምህራኖች ስራቸውን ለቀው ወጥተዋል። በዛሬው እለትም ከትምህርት ቤት ተማሪዎች ተመልሰዋል።

መብላት እና መጠጣት ያልቻለ መምህር እንደት አድርጎ ያስተምራል ? እኛ ማንን እንጠይቅ፣ በየጊዜው አመራሮች ይቀያየራሉ፣ ህዝቡ ተቸግሯል።

ይህን ተከትሎ በዛሬው እለት የወረዳው ነዋሪ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተን ነበር። ሰልፍ የወጡት ወጣቶች በመሃል መንገድ ላይ ደረቅ እንጨት እሳት በመለኮስ ተቃውሞ አሰምተናል። ለተወሰነ ደቂቃም የትኛውም ተሽከርካሪ እንዳይንቀሳቀስ አግደን ነበር። ሰልፍ ላይ እያለን የሀገር ሽማግሌዎች መጥተው ' ለ3 ቀን ታገሱን ' ሲሉ ጠየቁን፣ እኛም አባቶቻችንን ማስከፋት ስላልፈለግን እሺ ብለናቸዋል።

አባቶች በስአቱ ያሉን ' መንገዱን ክፈቱት መኪኖች ይሒዱ፣ ለእኛ ደግሞ የሶስት ቀን እድሜ ስጡን፣ ችግሩን ለመቅረፍ በዚህ ሶስት ቀን እኛ የወረዳውን አስተዳደር እንጠይቅ፣ መፍትሔ ከሌለው ግን ለእናንተ እናሳውቃለን ' ነው ያሉት፣ እነሱን የላካቸው የወረዳው አስተዳደር እንደሆነም ሰምተናል።

ሰልፍ የወጣንበት ዋነኛ ምክንያት ለ8 አመት በመጠጥ ውሃ ችግር ላይ በመሆናችን፣ የመንግስት ሰራተኛው ደግሞ የ8 ወር ደመወዝ ስላልተከፈለው ነው። የጡረታ ደመወዝ የሚያገኙ ህፃናት በርሃብ ውስጥ ስለሆኑ ነው።

ውሃ የምንገዛው በየወሩ ነው። ይህንንም የምናገኘው በመከራ ነው። ውሃውን የሚያመጡት የመንግስት መኪኖች ናቸው። በየጊዜው ጥያቄ ስንጠይቅ መፍትሔ እናመጣለን ነው ወረዳው ምላሹ፣ ዛሬ ደግሞ የሀገር ሽማግሌዎች ሰልፍ ላይ እያለን ለሶስት ቀን እንዲንታገስ ጠይቀውናል፣ ነገር ግን አስቡት እስኪ 8 አመት ለተጠየቀ ጥያቄ በ8 አመት መመለስ ሳይችሉ በሶስት ቀን ይመለሳል ብሎ ማሰብ ከባድ ነው " ብለዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን ከሰጡ መካከል በወረዳው የአመራርነት የስራ ሃላፊነት ያላቸው አንድ አካል ጉዳዩ በቀላሉ እንደማይፈታ እና የፌደራል መንግስት የማህበረሰቡን ችግር ተገንዝቦ መፍትሔ ቢሰጥ የተሻለ እንደሚሆን ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

የታላቁ የሃይማኖት አባት የቀድሞው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሥርዓተ ቀብር ተፈጽሟል።

ከስርዓተ ቀብራቸው ቀደም ብሎ በሚሊኒየም አዳራሽ ሽኝት ተደርጓል።

ታላቁ የሃይማኖት አባት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር በታላቁ አንዋር እና በኑር (በኒ) መስጂዶች ከአራት አስትርት ዓመታት በላይ ኢስላማዊ ሃይማኖታዊ ትምህርት አስተምረዋል።

ከ50 በላይ ሃይማኖታዊ መጽሐፍትንም ጽፈዋል፡፡

ቅዱስ ቁርአንንም ተርጉመዋል፡፡ የቁርአን ትርጉም ሥራቸውን በሲዲ በማሳተም አሰራጭተዋል፡፡

ከ50 ዓመታት በላይ በዘለቀ የአዲስ አበባ ቆይታ ቅዱስ ቁርአንን ከ300 ጊዜ በላይ በትርጉም (ተፍሲር) አስተምረዋል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የተፈጠሩ ሃይማኖታዊ አለመግባባቶችን በመፍታት የሃይማኖታዊ አባትነታቸውን ሚና ተወጥተዋል።

በ1967 ዓ.ም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ሲመሰረት የምክር ቤቱ አባልና የዑለማ ሊቀመንበር በመሆን አገልግለዋል።

ከ2010 መጋቢት እስከ ግንቦት ወር 2014 ዓ.ል ድረስ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን በፕሬዚዳንትነት እንዲሁም የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ በመሆን አገልግለዋል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ባለትዳርና የአምስት ወንዶችና የአራት ሴቶች አባት እንደነበሩ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ፎቶ፦ የታላቁ አባት የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ አስክሬን ፒያሳ በሚገኘው ኑር መስጂድ የዱዓ እና የሽኝት ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ።

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ አስከሬን ለ40 ዓመታት ባስተማሩበት ኑር መስጂድ ሶላተል ጀናዛ ተሰግዶበታል።

ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ሥርዓተ ቀብራቸው የሚፈፀም ይሆናል።

Photo Credit - EBC & ENA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

የታላቁ አባት የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ ሰኞ ከቀኑ 10:00 ሰዓት እንደሚፈጸም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አሳውቋል።

ስርዓተ ቀብራቸውን ለማስፈጸምም ኮሚቴ ተዋቅሮ እየሰራ ሲሆን ኮሚቴ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመነገገር በወሰነው መሰረት አጠቃላይ መርሃግብሩ ይህን ይመስላል።

1) ሰላተል ጀናዛው ከቀኑ 6፣00 በዙሁር ወቅት ላይ ለ40 አመታት ባስተማሩበት ፒያሳ በሚገኘው የኑር (በኒ) መስጂድ ይሰገዳል።

2) ከቀኑ 8:00 ሰአት ጀምሮ በሚሊኒየም አዳራሽ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች በተገኙበት የሽኝት ፕሮግራም ይከናወናል።

3) ከቀኑ 10 ሰአት የቀብር ስነስርዓታቸው ይፈጸማል።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ታላቁ አባት ሐጂ ኡመር ኢድሪስ አረፉ።

የቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ወደ አኼራ ሄደዋል።

ታላቁ የሃይማኖት አባት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባጋጠማቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ወደ አኼራ ሄደዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለአባታችን ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ቤተሰቦች እንዲሁም ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ መፅናናትን ይመኛል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

‎" ተገቢዉን ፍትሕ አለማግኘቷ ያንገበግበኛል " - ወላጅ አባት

‎አርሶ አደር ዳንሳሞ አሌ በሲዳማ ክልል ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ዳኤ'ላ ወረዳ ቃዳዶ ቀበሌ ዳዱርቾ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ነዋሪ ናቸው።

ከዛሬ ሶስት ዓመታት በፊት ደጌ ዳንሳሞ አሌ የተበለች የ15 አመቷ ታዳጊ ልጃቸውን 'አበበ ክፍሌ' የተባለ ወጣት ግብራበሮቹን በማሰባሰብ ለቅሶ ቤት ተልካ ከምትመለስበት አፍነው ወደ ጫካ በመውሰድ ጭካኔ በተሞላበት መልኩ ጓደኞቹ አፍነዉ ይዘዋት በግድ ይደፍራታል።

‎ታዳጊዋ ደጌ በደም ተለውሳ፣ ትንፋሽ አጥሯት ከወደቀችበት አንስተው ቦታ በመቀየር ይህን እንስሳዊ ድርጊት ሲፈፅሙባት የተመለከች አንዲት ሴት ጩኸት ታሰማለች፤ እነሱም ተሸክመዋት ለማምለጥ ይሞክራሉ።

አባቷን ጨምሮ ከለቅሶ ቤት ሲመለሱ የነበሩ የአከባቢዉ ነዋሪዎች ጩኸቱን ወደ ሰሙበት ለእርዳታ ሲሯሯጡ በመጨረሻም ክፍሌና ጓደኞቹ ደጉን ጥለዋት ይሸሻሉ።

ሰው ለማገዝ ከሌሎች ሰዎች ጋር አብሮ ሮጦ የደረሰዉ አባቷ አቶ ዳንሳሞ አሌ የሚያየውን ማመን ያቅተዋል፤ የገዛ ልጁ በደም ተለውሳ በእርቃኗ ተዝለፍልፋ ወድቃ ሲያያት የሚይዘዉ የሚጨብጠውን ያጣል።

ከዚህ በኃላ ምን ተፈጠረ ?

‎አርሶ አደር ዳንሳሞ አሌ ስለሁኔታው ለቲክቪህ ኢትዮጵያ እስረድተዋል።

" ሰው ለመርዳት በሮጥኩበት ልጄ ተደፍራ በወደቀችበት ነበር የደረስኩት እርቃኗን ሆና ሳይ እራሴን መቆጣጠር አቃተኝ፣ የምይዘዉ የምጨብጠዉን አጣሁ፤ የለበስኩትን ጃኬት ነበር አውልቄ ሸፈንኳት፤ ጮሆኩ ሰዎች ሊያረጋጉኝ ሞከሩ፤ በጣም አሳዛኝ ልብ ሰባሪ ድርጊት ነበር " ብለዋል።

‎" አበበ ክፍሌና ጓደኞቹ ከአከባቢው ተሰወሩ ደጉ በዛኑ ምሽት ብዙ ደም ፈሷት ስለነበር ወደ ዳኤላ ሆስፒታል ተወሰደች ከዚያም ለተሻለ ሕክምና ወደ ሐዋሳ እንድትጓዝ ተደረገ " ሲሉ ገልጸዋል።

‎ደጌ ከአካላዊ መደፈር በዘለለ ከፍተኛ ስነልቦናዊ ጉዳት ስለደረሰባት እዚያዉ ሀዋሳ በአንድ ድርጅት ውስጥ እንድትቆይ ተደረገች።

‎ፖሊስ ዋናው ተጠርጣሪ ግለሰብ አበበ ክፍሌና ቀንደኛ ተባባሪ ጓደኛዉ ኢያሱ ግዴሳ ማምለጣቸዉንና ሶስቱን ግብራበሮች ግን መያዙን ገልፆ ክስ መሰረተባቸዉ።

‎ፍርድ ቤቱ በነዚህ ሶስት ግብራበሮቹ ላይ የ6 አመት ፅኑ እስር ፈርዶባቸው የነበር ቢሆንም ከ2 አመት እስር በኋላ በአመክርዎ ይለቀቃሉ።

ዋናው ወንጀለኛ እና በታዳጊዋ ላይ ጥቃት ያደረሰው " አበበ ክፍሌ" የተባለው ሰው ግን እስከ ዛሬ ድረስ አልተያዘም ለፍርድም አልቀረበምም።

የደጉ አባት ይህን ጉዳይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲያስረዱ " ከተፈፀመባት ነውረኛ ተግባር በላይ ተገቢዉን ፍትሕ አለማግኘቷ ያንገበግበኛል " ሲሉ ነው የገለፁት።

‎በዚህ መሃል አርሶ አደር ዳንሳሞ ሌላ አሳዛኝ ጉዳይ አጋጠመኝ ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። ይህም የአከባቢው ሽማግሌዎች " ነገሩን በሽምግልና ካልፈታን " ማለት መጀመራቸው ነው።

" ፖሊስ ' ማግኘት አልቻልኩም ተሰውሮብኛል ' ያለውን ግለሰብ ሽማግሌዎቹ ከየት አመጡት " በማለት ሽምግልናውን እምቢ ማለታቸውን ገልጸዋል።

ሽማግሌዎችም " እንዴት አምቢ ትላለህ ? ሌላስ ልጅህ ላይ መሰል ነገር ቢደርስ ሽማግሌ አይደል የሚፈታው ? " እያሉ ያስጨንቋቸው እንደጀመረ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ደጌ አሁንም ፍትሕ እንደተጠማች ሀዋሳ እንደርሷ ጥቃት የደረሳቸውን ታዳጊዎች ሰብስቦ በሚያኖር ድርጅት ውስጥ ናት።

" የደጌ ታናሽ ግን ገና 12 አመቷ ነው ሽማግሌዎችን እምቢ አልክ ብለው በሷ እንዳይበቀሉኝ እፈራለሁ " ሲሉ አባት ተናግረዋል።

" ‎ስለ ጉዳዩ ከወረዳው እስከ ክልሉ ባለድርሻ አካላት መስሪያ ቤት ደጅ ብጠናም ' የተዘጋ ፋይል ነው ፤ የነሱ ፋይል ጠፍቶብናል ስናገኝ እናሳውቃለን ' በማለት ብዙ አንገላቱኝ " ሲሉ ስለ ፍትህ ድምጻቸውን አሰምተዋል።

‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ የዳ'ኤላ ወረዳ እና ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስና ፍትሕ (ዐቃቤ ሕግ) አካለትን ለማነጋገር ቢሞክርም " በአካል ካልተገኛችሁ መረጃ መስጠት አንችልም " በማለታቸው በዚህ መረጃ ምላሻቸዉን ማካተት አልተቻለም ፤ መረጃዉ እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ሚዛን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት !

1⃣0⃣ኛ ዙር የቴክኖሎጂና የቋንቋ ኮርሶች ምዝገባችንን በማጠናቀቅ ላይ እንገኛለን።
የመክፈል አቅም ለሌላቸው በክሬዲት (ከወለድ ነፃ በሆነ ብድር/ዱቤ) መማር የሚችሉበት እድል ከማመቻቸት ባሻገር፤
✔️ ተመርቀው ሥራ ላጡ ሁሉ 25% ቅናሽ (መስፈርት: ከቀበሌ ደብዳቤ ማፃፍ)፣
✔️ ለዩኒቨርስቲና ኮሌጅ ተማሪዎች 12% ቅናሽ (መስፈርት: የታደሰ የትምህርት ቤት መታወቂያ ማሳየት)፣
✔️ ለመምህራንና ለጤና ባለሙያዎች 12% ቅናሽ (መስፈርት: ሙያዊ ማስረጃንና ተመጣጣኝ ህጋዊ ማስረጃ ማሳየት)፣
✔️ 12ኛ ክፍል ማለፊያ ውጤት ላላመጡ 20% ቅናሽ (መስፈርት: ስም እና አድሚሽን ቁጥር ማሳየት)፣
እነዚህን እድሎች አመቻችተናል።

ለመመዝገብ፦ http://www.mizantechinstitute.com

📱 በቴሌግራም @MizanInstituteOfTechnologyEthio አግኙን።

🗺በአካል: ቤተል አፕል ፕላዛ 7ኛ ፎቅ፣ 0987143030
በማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችን አገኙን፦
🌐👍mizantechinstitute?_t=ZM-8u1PtL1rMqD&_r=1">🌐📱mizaninstituteoftechnology7830?si=1GRXkSTCTu6p6ncD">▶️🌐📧 🗺

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

‎" ወጣቶቹ ያለ ፍርድቤት ትዕዛዝ ታስረዋል፤ ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸውም ተደርጓል " - ቤተሰቦችና ነዋሪዎች

‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን ኮቾሬ ወረዳ ፍሰሃ ገነት ተብሎ የሚጠራዉ አከባቢ ነዋሪዎች እና " ልጆቻችን ያለ አግባብ ታስረዋል " የሚሉት ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

በአከባቢዉ ማህበረሰብ በተደጋጋሚ ሲጠየቅ የቆየዉን የፍሰሃ ገነት የወረዳ መዋቅርነት ጥያቄ " በማህበራዊ ሚዲያዎች አሰራጭታችኋል " በሚል ወጣቶችን እያሰሱ እያሰሩ ነው ሲሉ ነው ቃላቸውን የሰጡት።

" ‎ስድስት ወጣቶች ያለ ፍ/ቤት ትዕዛዝ ታስረዋል " የሚሉት ነዋሪዎቹ የፍሰሃ ገነት ወረዳ በቀደመዉ ጊዜ የወረዳ መዋቅር የነበረዉ መሆኑንና የመዋቅር ጥያቄዉ የሕብረተሰቡ በመሆኑ እነዚህም ወጣቶች ይህንኑ ሃሳባቸዉን በማህበራዊ ሚዲያ በማሰራጨታቸው ብቻ ከስራና የትምህርት ገበታቸው እየታሰሱ መታሰራቸውንና ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸዉ መደረጉን ገልጸዋል።

‎" ፖሊስ ልጆቻችንን እንዳናገኝ ከማድረጉም በላይ ' በተባባሪነት አስራችኋለዉ ' እያለ እያስፈራራን ነዉ " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የተናገሩት የአከባቢው ወጣቶች " እኛም እየተፈለግን በመሆኑ አከባቢያችንን ለቀን ሸሽተናል " ሲሉ ተናግረዋል።

‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጌዴኦ ዞንና የኮቾሬ ወረዳ ፖሊስ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረገው የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ፈቃደኛ ባለመሆናቸዉ የኮቾሬ ወረዳ አዛዥ ደግሞ ስልካቸዉ ባለመስራቱ ለጊዜው አልተሳካም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…
Subscribe to a channel