ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ
#Peace
" እየተከተላችሁት ያለው መንገድ የተገኘውን ሰላም የሚያደፈርስ አገርን እና ህዝብን ለከባድ ቀውስ የሚያጋልጥ ነው !!! "
በትግራይ ክልል ሁኔታ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ከወራት በፊት ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና ለህወሓት ሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በላኩት የተግሳፅ ደብዳቤ ምንድነበር ያሉት ?
" ካህናት አበው ፣ የቤተክርስትያን ሊቃውንት ፣ ምእመናን ፣ የአገር ሽማግሌዎች የዕድሜ ባለፀጎች በሃዘን እያነቡ አካሄዳችሁን እንድታስተካክሉ ሲለምኗችሁ እና ሲመክሯችሁ ሰክናችሁ ማሰብ እና ማዳመጥ የተሰናችሁ ምክንያት ምን ይሆን ?
' የእኔ አካሄድ ብቻ ነው ልክ ' በሚል እልህ እና አስተሳሰብ የፈረሰ እንጂ የተገነባ ህዝብ እና አገር የለም።
የናንተ መለያየት አልበቃ ብሎ በአንድነት እና በመከባበር የኖረውን ህዝብ ለማራራቅ እየሄዳችሁበት ያለው ርቀት ህዝብን ለማገልገል መቆማችሁን ጥያቄ ውስጥ የሚከት የጥፋት እና የመጠፋፋት መንገድ በመሆኑ ቆም ብላችሁ አስቡ።
ይህ ሳይሆነ ከቀረ እየተከተላችሁት ያለው መንገድ የተገኘውንም ሰላም የሚያደፈርስ አገርን እና ህዝብን ለከባድ ቀውስ የሚያጋልጥ ነው።
ስለሆነም ህዝባችሁ የሚሰጣችሁ ምክር እና ተግሳፅ ተቀብላችሁ በስክነት እና በማስተዋል የህዝባችሁን ጥያቄ እንድትመልሱ አደራ እንላለን።
የተፈጠረው የሃሳብ አለመጣጣም ለመፍታት ከአቅም በላይ አይደለም። ችግሮቻችሁን በጥበብ እና በሰለጠነ አሰራር በመፍታት ጅምር ሰላሙን በማፅናት ህዝባችሁን እና አገራችሁን በልማት ለመካስ ከልብ እንድትተጉ የአባትነት ምክራችንን እናስተላልፋለን። "
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
" በጉዳዩ ላይ ምርመራ እየተደረገ ነው " - የአዲስ አበባ የወንጀል ምርመራ ባልደረባ
የአዲስ አበባ ፖሊስ የወጣቷ አሟሟት በመጣራት ላይ መሆኑን አሳወቀ።
ቀነኒ አዱኛ ገና ለጋ ወጣት ስትሆን የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ፤ ሞዴልና የማስታወቂያ ባለሙያም ነበረች።
በአፋን ኦሮሞ ዘፈኖቹ በእጅጉ የሚታወቀው የወጣት አንዷለም ጎሳ የፍቅር አጋር እንደነበረችም የተነገረ ሲሆን ሰኞ ሌሊት በአዲስ አበባ ከተማ ፣ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሰንሻይን አካባቢ በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው በድንገት ሕይወቷ አልፏል።
ከ1 ዓመት በላይ ከፍቅር አጋሯ ጋር አንድ ላይ በአንድ ቤት እንደኖሩ የተገለጸ ሲሆን ከህልፈቷ በኃላ አንዷለምን ፖሊስ ለጥያቄ ፈልጎ እንደወሰደው ተመላክቷል።
የወጣቱ ድምጻዊ አንዷለም ማናጀር እንደሆኑ የገለጸው ሌሊሳ ኢንድሪስ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ በሰጠው ቃል ፤ ቀነኒ ከሚኖሩበት ሕንጻ መውደቋን እና ንጋት 11 ሰዓት አካባቢ መሞቷን ፤ አንዷለም እና ቤተሰቦቹ ወድቃ እንዳገኟት ገልጿል።
" እኔ ንጋት 11 ሰዓት ስልክ ተደውሎ ቀነኒ ጉዳት ደርሶባት ሆስፒታል እንደገባች ተነገረኝ ፤ እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት ከአምስተኛ ፎቅ ወድቃ ነው የሞተችው ሁኔታውን ለማጣራት ምርመራ ተጀምሯል " ብሏል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ ለቪኦኤ ሬድዮ በጉዳዩ ላይ መረጃ ለመስጠት ጊዜው ገና መሆኑን ተናግረዋል።
አንድ የአዲስ አበባ ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ባልደረባ ለሬድዮ ጣቢያው ፣ ፖሊስ በጉዳዩ ላይ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ከመግለጽ ውጭ ምንም መረጃ እንደማይሰጡ ተናግረዋል።
የወጣት ቀነኒ አዱኛ አስከሬን በዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታል የአስክሬን ምርመራ ከተደረገለት በኋላ ሱሉልታ ወደሚገኝ እህቷ ቤት የተወሰደ ሲሆን በአዲስ አበባ ስርዓተ ቀብሯ ይፈጻማል።
ለጋዋ ወጣት በሚቀጥለው ቅዳሜ ልደቷን ለማክበር በሚል ፎቶዎች እየተነሳች ነበር።
በቅርቡ ከፍቅር አጋሯም ጋር ትዳር የመመሥረት ዕቅድ ይዛ እንደነበር ተገልጿል።
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ሁኔታ ?
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ሌተናል ጀነራል ፍስሃ ኪዳኑ ላይ የእግድ ደብዳቤ ፅፈዋል።
የእግድ ደብዳቤው ዘላቂና ጥቅማ ጥቅም እስከማስቀረት የዘለቀ እንደሆነ በፃፉት ደብዳቤ ለሚመለከታቸው አካላት በግልባጭ አስታውቀዋል።
ፕሬዜዳንቱ ትናንት በሦስት ከፍተኛ የሰራዊት አመራሮች ላይ ጊዚያዊ የእግድ ደብዳቤ መፃፋቸው ይታወሳል።
ዛሬ " ኋላፊነታቸው በአግባቡ አልተወጡም " ያሉዋቸውን የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊ ላይ ሙሉ የእግድ ደብዳቤ ፅፈዋል።
የእግድ ደብዳቤው የተፃፈላቸው ሌተናል ጀነራል ፍስሃ ኪዳኑ ከዛሬ መጋቢት 2/2017 ዓ.ም ጀምሮ ከማንኛውም መንግስታዊ ጥቅም በመራቅ ማንኛውም የፀጥታ አካል እንዳያዙ እግድ ተላልፎባቸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም ህግና ስርዓት እንዲጣስ ውሳነ በመስጠትና በማሰማራት ተሳትፈዋል በተባሉ ሦስት ከፍተኛ የሰራዊት አመራሮች ከተወሰደው ጊዚያዊ የእግድ ትእዛዝ በኋላ በዓዲግራት እና በዓዲጉዲም ከተሞች በታጠቁ ኃይሎች የታገዘ መፈንቀለ ስልጣን ተካሂደዋል። መቐለም ሙከራዎች ነበሩ።
በዓዲግራት የተካሄደው በሰራዊት የታገዘ መፈንቅለ ስልጣን ያለ ግጭት የተካሄደ ሲሆን በዓዲጉዲም ከተማ ታጣቂዎች በወሰዱት እርምጃ የከተማው በርካታ ሰዎች የአካል ጥቃት ሰለባ እንደሆኑ ተነግሯል።
በዓዲጉዲም ከተማ የአካል ጉዳት የደረሰ ቢሆንም የሞተ ሰው ስለመኖሩ ማረጋገጥ አልተቻለም።
አንዳንድ መረጃዎች የዓዲጉዶም ከንቲባ የሚገኙባቸው 9 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱ ቢያመላክቱም ከሚመለከታቸው አካላት በኩል ማረጋገጫ ማግኘት አልተቻለም።
የዓዲግራት ከተማ አስተዳደር ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ ፤ የደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት ባሰማራቸው የሰራዊት አባላት የከንቲባ ፅህፈት ቤት በመስበር መፈንቅለ ስልጣን ተካሂዷል ብሏል።
" በጠበንጃ የሚፀና ስልጣን የለም " በማለት ወጣቱ መብቱ ለማስከበር እንዲታገል አሳስቧል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ከታማኝ ምንጮች የደረሱት መረጃ እንደሚያመለክቱት በመቐለ ፣ በዓዲጉዶምና በዓዲግራት ከተሞች " የሰራዊት ጣልቃ ገብነት እንዲቆም " ደብረፅዮ (ዶ/ር) የሚመሩትን የህወሓት ቡድን የሚኮንኑ ሰላማዊ ሰልፎች ለማካሄድ ዝግጅት እየተደረገ ነው።
ፎቶ ፦ ሌተናል ጀነራል ፍስሃ ኪዳኑ (በግራ በኩል) እና የዓዲጉዶም ከንቲባ ኢንጅነር ዓንዶም ወልዱ (በቀኝ በኩል)
#TikvahErhiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
የNGAT ፈተናና ምዝገባ ቀን ተራዘመ።
የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና እና ምዝገባ ቀናት ተራዘመ።
ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ መጋቢት 01/2017 መጠናቀቁ እና ፈተናው መጋቢት 05/2017 ከ3፡00 ጀምሮ እንደሚሰጥ መገለጹ ይታወሳል።
ይሁን እንጂ በአንዳንድ ተፈታኞች ጥያቄ መሰረት ምዝገባው እስከ መጋቢት 04/2017 ዓ.ም እስከ ምሽቱ 12:00 የተራዘመ መሆኑን አሳውቋል።
ፈተናው ደግሞ መጋቢት 12/2017 ከ3:00 ጀምሮ እንደሚሰጥ ገልጿል።
በተለያየ ምክንያት ምዝገባ ያመለጣቸው አመልካቾች ምዝገባቸውን ወደ https://ngat.ethernet.edu.et/registration በመግባት መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።
#MoE
@tikvahethiopia
አንጋፋው የማሲንቆና በገና ተጫዋች ድምጻዊና የሙዚቃ መምህር አለማየሁ ፋንታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
ግጥምና ዜማ በመድረስ ክራር ፣ በገና እና ማሲንቂ በመጫወት የሚታወቁት አለማየሁ ፋንታ ፤ ለበርካታ ዓመታት በያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት በመምህርነት አገልግለዋል፡፡
በተለየ የማሲንቆ አጨዋወታቸው የሚታወቁ ሲሆን፤ በዓለም ዙሪያ የኢትዮጵያን ባህል ማስተዋወቅ ችለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ባወጣው የሀዘን መግለጫ ፤ ለኢትዮጵያ የሙዚቃ ማህበረሰብና ለመላው ሕዝብ ከባድ ሀዘን ነው ብሏል፡፡
በነገው ዕለት የአስክሬን ሽኝት መርሐ-ግብር ተደርጎ ስርዓተ ቀብራቸው ፒያሳ በሚገኘው በገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ በ9 ሰዓት የፈጸማል።
#ኤፍኤምሲ
@tikvahethiopia
#ኮሬ
🚨" ማንም ከህግ በላይ መሆን አይችልም ህገ መንግስት ይከበር "- የታጣቂዎች ግድያ ከዘጠኝ አመታት በላይ ያማረራቸው ዞን ነዋሪዎች
➡️ " መንግስት ይህን ሕዝብ ስለማወቁ እጠራጠራለሁ " - የኮሬ ዞን የቀድሞ አመራር
ሰሞኑን የንጹሐን ሕይወት በታጠቁ አካላት ጥቃት ማለፉን የኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ የጀሎ ቀበሌ ነዋሪዎች እንደተረዳ የኮሬ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቋል።
ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መልዕክት ምን አለ ?
" በአርሶ አደር ሹኩር ዩሱፍና በወጣት ቡጥሳ ጉይባ ላይ በደረሰው አሳዛኝ የሞት አደጋ የአካባቢ ማህበረሰብ ጥልቅ ሀዘኑን ገልጿል።
አርሶ አደሩ የጀሎ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ፣ ቅዳሜ የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ/ም ከብቶቹን ውሃ በማጠጣት ላይ ሳሉ በምዕራብ ጉጂ ዞን ጋላና ወረዳ የሚንቀሳቀሱ የጋላና ፎሌዎች (ታጣቂዎች) ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ ጄሎ ቀበሌ ዘልቀው በመግባት ጥቃት ፈጽመዋል።
ከጀሎ ቀበሌ ከማሳቸው ተፈናቅለው ወደ ኬሌ ቀበሌ አስተዳደር ተጠግቶ የሚኖሩ ነገር ግን ቀን በቀን ወደ ቀበሌያቸው ከብቶቻቸውን ውሃ ለማጠጣት ሲሄዱ ከነበሩ ሰዎች መካከል አቶ ሽኩር ላይ ጥቃቱ ደርሷል።
አቶ ሹኩር የኬሌ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ደርሰው በጥቃቱ የደረሰባቸው ጉዳት ከባድ በመሆኑ ለአርባ ምንጭ ሆስፒታል ሪፈር ተደርገው፣ መንገድ ላይ ሕይወታቸው ማለፉን ከቤተሰቦቻቸው ለማረጋገጥ ተችሏል።
'ከአርሶ አደሩ ግድያ በኋላ 10 ሰዓት ገደማ ቡጥሳ ጉይባ የተባለ ወጣት ለጊዜው ማንነቱ ባልተረጋገጠና የታጠቀ አካል ከባድ የጥይት ምት ደርሶበት ወደ ኬሌ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተወስዶ ወደ አርባምንጭ ሪፈራል ሆስፒታል ቢባልም መንገድ ላይ ህይወቱ ማለፉን ተከትሎ 'ወጀ' ተመልሷል' የሚል ከቤተሰብ የደረሰልን መረጃ ያመለክታል።
የአካባቢው ነዋሪዎችም፣ ‘ጥቃት የፈጸመው አካል ማንነት ተረጋገጦ ለህዝብ ይፋ አንዲደረግና በህግ ቁጥጥር ሥር እንዲውል’ ሲሉ ጠይቀዋል።
‘ማንም ከህግ በላይ መሆን አይችልም፣ ህገ መንግስት ይከበር’ ብለዋል።
ከምዕራብ ጉጂ በሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች በሚፈጸም ወረራ ከመኖሪያቸውና ከማሳቸው የተፈናቀሉ የጀሎና የዶርባዴ ቀበሌ ነዋሪዎች በአጎራባች ቀበሌዎች ውስጥ ባሉ የላስቲክ ቤቶችና ዛፎች ሥር እየኖሩ ችግሩ ሲያስገድዳቸው ቀን በቀን ወደ ማሳዎቻቸው ሄደው እንጨት እየለቀሙ መንገድ ላይ አውጥተው ይሸጣሉ።
ከቋሚ ተክሎች ሊበላ የሚችል አንዳች ነገር የለም፤ በጉጂ ታጣቂዎች ሀብቶች ተጨፍጭፈዋል፤ በእሳት ተቃጥሎ ወድሟል።
ከሐምሌ 16 ቀን 2009 ዓ/ም ጀምሮ የኮሬ ዞን ዋናው የንግድና የሕዝብ ትራንስፖርት መስመር የሆነው የኬሌ ቶሬ ጨለለቅቱ ዲላ መንገድ ተዘግቶ፣ የማህበራዊ፣ ከኢኮኖሚያዊና ፖሊቲካዊ እንቅስቃሴዎች ተቋርጠዋል።
‘የጄሎና የዶርባዴ ቀበሌ ነዋሪዎች ጨምሮ ከ13 በላይ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው መች ተመለሱ? የምዕራብ ጉጂ አዋሳኝ ቀበሌዎች ለተደጋጋሚ ጥቃት ሰለባ እየሆኑ መች የፌዴራል መንግስት ጠየቀን?’ ሲሉ የኮሬ ዞን ማህበረሰብ ቅሬታ እያሰሙ ይገኛሉ " ብሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የቀድሞ የኮሬ ዞን አመራር በበኩላቸው፣ " መንግስት በኮሚዩኒኬሽን ሚንስትሩ በኩል፣ 'ኢትዮጵያ ከመቸውም ጊዜ በላይ ሰላሟ የተረጋገጠ ነው' በሚል መግለጫ በሰጡበት ዕለት የኮሬ አርሶ አደሮች መከራ መቀጠሉ ያሳዝነኛል " ብለዋል።
" መንግስት ይህን ሕዝብ ስለማወቁ እጠራጠራለሁ " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ : https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-03-11-2
@tikvahethiopia
ወጣትነት በዘህራህ ልዩ ከወለድ ነጻ የሴቶች ቁጠባ ሒሳብ ሲታገዝ፣ የስኬት ጉዞ ከመቼውም ይልቅ ይፋጠናል!
አቢሲንያ አሚን ዕሴትዎን ያከበረ!
#AbyssiniaAmeen #IFB #bankofabyssinia #አቢሲኒያአሚን
#Banking #BanksinEthiopia #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#ዘህራ #የሴቶችቁጠባ #አቢሲንያአሚን
#Update #NGAT
የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና መጋቢት 5 እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ መጠናቀቁን ገልጿን።
ፈተናው የሚሰጠው ዓርብ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ መሆኑንም አሳውቋል።
ተፈታኞች በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በሚመደቡበት የፈተና ማዕከላት እንዲገኙ ብሏል።
➡️ ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በሚሄዱበት ወቅት ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።
➡️ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 3 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡
➡️ የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
➡️ የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡
#MoE
@tikvahethiopia
#NewsAlert
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ለሦስት ከፍተኛ የሰራዊት አዛዦች ላይ ጊዚያዊ የእግድ ደብዳቤ ፃፉ።
እግዱ የተፃፈላቸው ከፍተኛ አመራሮች ፦
- ሜጀር ጀነራል ዮውሃንስ ወ/ጊዮርጊሰ
- ሜጀር ጀነራል ማሾ በየነ
- ብርጋዴር ጀነራል ምግበይ ሃይለ ናቸው።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም የፃፉት ጊዚያዊ የእግድ ደብዳቤ ፦
" ከመንግስት ውሳኔ ውጪ መላ ህዝባችን ፣ ወጣቱን ወደ ግርግር ፤ የፀጥታ ሃይላችን ወደ እርስ በርስ ግጭት ብሎም ህዝባችን ወደ እማይወጣበት አዘቅት የሚያስገባ አደገኛ እንቅስቃሴ አልቆመም ስለሆነም እርስዎ ስርዓት ባለው አካሄድ መግባባት እስኪደረስ ድረስ ከመጋቢት 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ከአዛዥነትዎ የታገዱ መሆንዎን አስታውቃለሁ " ይላል።
በትግራይ ክልል በአመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት እንዲፈታ ብዙ ጥረት ቢደረግም ምንም መፍትሄ ሳይገኝለት ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን ነዋሪዎችም ሁኔታው ስጋት ላይ ጥሏቸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#Update #MoE
" እስከምሽት ድረስ እየሞከሩ መቆየት ይችላሉ " - ትምህርት ሚኒስቴር
ሀገር አቀፍ የ2017 ዓ.ም የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የአመልካቾች ምዝገባ ከ የካቲት 27/2017 ዓ.ም እስከ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም ማታ 12፡00 ሰዓት ድረሰ ብቻ እንደሚከናወን የትምህርት ሚኒስቴር ማስታወቁ ይታወሳል፡፡
ዛሬ በሚያበቃው የአመልካቾች የምዝገባ ሂደት ለመመዝገብ የሞከሩ ተፈታኞች የመመዝገቢያው ማስፈንጠሪያ ወይም ሊንክ እየሰራ አይደለም የሚል ተደጋጋሚ ቅሬታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።
ከምዝገባ ጋር ለተያያዘ ማንኛውም ጥያቄ በሚል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያስቀመጣቸው ስልኮች ቢኖሩም እየሰሩ አለመሆኑንም ጠቁመዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑትን ዶ/ር ኤባ ሚጀናን ማብራሪያ ጠይቋል።
በምላሻቸውም " የኔትወርክ ችግር ይሆናል እንጂ ሲስተሙ ይሰራል ደጋግማቹ ሞክሩ " ብለዋል።
አክለውም " ሁሉም ሳይሆን የተወሰኑ ሰዎች ናቸው ለመመዝገብ እክል የገጠማቸው በርካታ ሰዎች አሁንም እየተመዘገቡ ነው " ያሉ ሲሆን እስካሁን ባለው 8 ሺ የሚጠጋ ሰው መመዝገቡን ጠቁመዋል።
" ፕሮሲጀሩን መከተል ግድ ይላል ከዘለሉ ላይሰራ ይችላል ነገር ግን ሁል ጊዜ ብዙ ሰው በመጨረሻ ነው የሚመዘገበው ፣መጨናነቅ ይኖራል እንዳይዘጋ በሚል በርካታ ሰዎች በአንድ ላይ ስለሚሞክሩ ጫና ይኖራል በዚህ ምክንያት ካልሆነ በቀር ምንም ችግር የለበትም " ነው ያሉት።
ሊራዘም የሚችልበት አጋጣሚ ይኖራል ወይ ? ስንል ላነሳንላቸው ጥያቄም " መራዘም ሳይሆን እስከምሽት ድረስ እየሞከሩ መቆየት ይችላሉ ኔትወርክ ያለበት አካባቢ በመሆን ደጋግመው ይሞክሩ " ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የተፈታኞች የመፈተኛ 'User Name' እና 'Password' በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ መሆኑን እና የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 750 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈፀም እንደሚጠበቅባቸው ማስታወቁ ይታወሳል።
ፈተናው የሚሰጥበትን ቀን በቀጣይ እንደሚገልጽ አሳውቋል፡፡
መመዝገቢያ ፦ https://ngat.ethernet.edu.et/registration
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia
ምን ትጠብቂያለሽ? የሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች ሩጫ ጥቂት ቀናቶች ብቻ ቀርቶታል! ፍጠኝ ቲሸርትሽን በእጅሽ አስገቢ!
ከ M-PESA ላይ በመግዛት የ540 ብር ቲሸርት በ389 ብቻ ታገኛለሽ።
#Andegna #1Wedefit #FurtherAheadTogether
#USAID
ከስድስት ሳምንት ግምገማ በኋላ አሜሪካ 83 በመቶ የሚሆነውን የአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) ፕሮግራሞችን መሰረዟን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በX ገጻቸው አስታውቀዋል።
" በቢሊዮን ዶላር ወጪ ይደረግባቸው የነበሩ 5,200 ኮንትራቶች ተቋርጠዋል " ያሉት ሚኒስትሩ " እነዚህ ለብሔራዊ ጥቅማችን ምንም የማያገለግሉ አንዳንዶቹ እንደውም የሚጎዱ ጭምር ናቸው " ሲሉ ነው የገለጹት።
ቀሪ 18 በመቶ የሚሆኑት ፕሮግራሞች (1000 የሚጠጉ) በስቴት ዲፖርትመንቱ በአግባቡ እየተመራ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።
Via @tikvahethmagazine
#ብርሃን_ባንክ
#ይቀበሉ_ይመንዝሩ_ተጨማሪ_2%_ #እና_ልዩ_ስጦታ_ያገኛሉ
ከውጪ ሃገራት የሚላክልዎትን ገንዘብ ከብርሃን ባንክ ጋር ከሚሰሩ አለምአቀፍ የገንዘብ አስተላላፊዎች #ሪያ #ዳሃብሽል #ዌስተርን_ዩኒየን #መኒግራም #ትራንስ_ፋስትና #ወርልድ_ረሚት በኩል ሲቀበሉ ወይም በእጅዎ ያለውን የውጭ ሃገር ገንዘብ በባንካችን ሲመነዝሩ ከእለቱ የምንዛሬ ተመን በተጨማሪ 2% እና ልዩ ስጦታ ያገኛሉ!
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
#moneytransfer #Stressfreebanking #berhanbank #bank #finance #bankinethiopia
🔈#የኢትዮጵያውያንድምጽ
“ ወደ 29 ኢትዮጵያውያን ይበልጥ የከፋ ቦታ ተወስደዋል። ” - ኢትዮጵያዊያን በማይናማር
ካሉበት ችግር እንዲያወጣቸው መንግስትን በተደጋጋሚ የተማጸኑ ፣ ማይናማር “ ታይሻንግ ካምፕ ” ታግተው የነበሩ 29 ኢትዮጵያውያን እስከዛሬ ሲደርስባቸው ከነበረው የከፋ ስቃይ ወዳለበት ስፍራ ተገደው መወሰዳቸውን ጓደኞቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
የተወሰዱት “ ዋልዋይ ” የተሰኘ ማይናማር ላይ ያለ ቦታ እንደሆነ፣ የድረሱልን ተማጽኖ ቢያስሙም የሚደርስላቸው ባለመገኘቱ ራሳቸውን እስከማጥፋት ሙከራ እያደረጉ እንዳሉ ታውቋል።
በአካባቢው ባሉ ካምፓች የነበሩ ሌሎች ሰዎች ከእገታ እየወጡ እንደሆነ፣ " ዋልዋይ " ካምፕ የሚገኙትን ታጋቾች ግን እንዳይወጡ አጋቾቹ በድብቅ እንደያዟቸው ተመልክቷል።
ኢትዮጵያዊያኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በተጨማሪ ምን አሉ ?
“ በማይናማር ካምፕ የነበሩ 29 ኢትዮጵውያን ካምፓኒው ‘ወደ ሌላ ቦታ ልውስዳችሁ’ ሲላቸው ለደኀነታቸው አስተማማኝ ስላልሆነ እዚሁ ነው መቆት የምንፈልገው ብለው ነበር፡፡
ነገር ግን ካምፓኒው የጸጥታ ኃይሎችን ወዳነበሩበት ካምፕ በማምጣት እጃቸውን በግዴታ እየጎተተ በመኪና አሳፍሮ በማይናማር 'ዋልዋይ' የሚባል ቦታ ወስዷቸዋል፡፡
የተወሰዱት ገና አዲስ በመሰራት ባለ ኮምፓውንድ ነውና በጣም ከፍተኛ የሆነ ስቃይ እየደረሰባቸው ይገኛሉ፡፡ ኮምፓውንዱ ህግ እና ስርዓት የለውም። በጋንግስተሮች ብቻ የሚተዳደር ነው። ለደኅንነታቸው የሚጮህላቸው የለም።
ሴቶችን ፀጉራቸውን ላጭተዋቸዋል። ወንዶችና ሴቶችን በኤሌክትሪክ ይገርፏቸዋል፤ በጨለማ ክፍል በማስገባት ከሦስት ቀናት በላይ ምግብ በመከልከል በሰንሰለት ያንጠለጥሏቸዋል።
እናም በማይናማር የነበሩ ወደ 29 ኢትዮጵያውያን ይበልጥ የከፋ ቦታ ተወስደዋል። እንዲያውም ራሳቸውን ለማጥፋት ሙከራ እያደረጉ ነው። በሰጡን መረጃ መሰረት።
እዚያ ከሄዱ በኋላ ይበልጥ ከባድ ችግር እየገጠማቸው ነው። ለካምፓኒው ሥራ ቢሰሩም ባይሰሩም ሁሌም ይቀጠቀጣሉ፡፡ ተስፋ ወደ መቁረጥ ደርሰዋል፡፡ የተወሰኑ ሰዎች ራሳቸውን የማጥፋት ሙከራ አድርገዋከል ” ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል፥ በማይናማር ታግተው አስከፊ ጊዜ ያሳለፉና ከወር በፊት ከእገታ የወጡ፣ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የኢትዮጵያ መንግስትን የቪዛና ሌሎች ጉዳዮች ይሁንታ እየጠበቁ ታይላንድ ከሚገኙ ከ250 በላይ ዜጎች መካከል ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የተረጋገጠላቸው ለመመለስ ትኬት ያላቸው 40 ሰዎች ብቻ መሆናቸውን ኢትዮጵያውያኑ ነግረውናል፡፡
ሌሎች ወደ ኢትዮጵያ መግባት የሚችሉት በራሳቸው ሙሉ ወጪ ትኬት ሲቆርጡ መሆኑን እንደተናገሩ፣ የደርሶ መልስ ቪዛና ለትኬት መቁረጫ ገንዘብ የሌላቸው በርካቶች ጭንቀት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ " የዛሬው የጸሎትና ምስጋና መርሐ ግብር ተካሄደ።
በመስቀል አደባባይ በተካሄደው በዚሁ መርሐ ግብር ላይ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምዕመን ተገኝቶ ነበር።
መርሐ ግብሩ ነገ እሁድም ይቀጥላል።
" መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ " መርሐ ግብርን የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከቢሊግርሃም የወንጌል ማህበር ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ነው።
@tikvahethiopia
#Peace #Unity
" የትግራይ ህዝብ ከአስከፊው ጦርነት ገና አላገገመም።
በአመራሮች ክፍፍል እና ስልጣን ምክንያት ዳግም ውጥረት ውስጥ መገባቱ እጅግ በጣም የሚያሳዝን ነው።
ላለፈው በደል እና ለደረሰው ጥፋት መቼ ፍትህ ተሰጠ ? መቼ ተጠያቂነት ተረጋገጠ ? መቼ የተጎዳ ተካሰ ? ለመሆኑ እነዚያ አስከፊ የጨለማ ወራት እንዴት ተረሱ ?
እነዚያ በሰላም መጥፋትና ጦርነት ምክንያት ሴቶች በግፍ በጭካኔ የተደፈሩበት ፣ ወጣቶች የተረሸኑበት ፣ የብዙዎች ደም የፈሰሰበት ፣ በርካቶች ሀገራቸውን ጥለው የሸሹበት ፣ ህጻናት ያለቁበት ፣ እናቶች ልጆቻቸውን ተሸክመው መግቢያ ያጡበት ፣ አዛውንቶች በመጦሪያ እድሜያቸው የጦርነት ሰለባ የሆኑባቸው ወቅቶች ከመቼው ተረሱ ?
ሰላም ሰፈነ ተብሎ ፍትህ እና ማገገም ሲጠበቅ ዳግም እንዲህ ያለ ውጥረት ውስጥ መገባቱ እጅግ የሚያሳዝን ነው።
የሃይማኖት አባቶች ፣ የሃገር ሽማግሌዎች ሁሉ እባካችሁ አሁንም ልዩነት በተፈጠረባቸው ወገኖችና አመራሮች መካከል ሰላም ይወርድ ዘንድ ፤ የከፋ እልቂት እንዳይመጣ ጥረታችሁን ቀጥሉ።
የእርስ በእርስ ልዩነቱና ያለው አጠቃላይ ሁኔታ ለአንዳንዱ ሰርግና ምላሽ ሆኖለት ዳግም የከፋ የደም መፋሰስ እስኪመጣ በጉጉት እየጠበቀ ነው። ለግላቸው የፖለቲካ ትርፍ የህዝብን ደም መፋሰስ የሚጠብቁ ብዙዎች አሰፍስፈው እየጠበቁ ነው።
ይህ የሰላም መደፍረስ እና ህዝብን ጭንቀት ላይ የሚጥል ሁኔታ ሊቆም ይገባል። እልህ መገባባት ውጤቱ ደም መፋሰስ ብቻ ነው። በእርስ በእርስ መለያየት አንድም ቀን ማደር አይገባም። የትግራይ ህዝብም ዳግም ሊሰቃይ አይገባም።
ለህዝብ ስትሉ ችግሮቻችሁን በጠረጴዛ ዙሪያ ፍቱ !!!
በእግዚአብሔር ስም፤በአላህ ስም እንማፀናለን !! "
From : Tikvah Ethiopia Family Tigray Region
@tikvahethiopia
#Adigrat
🚨 " በር ሰብረው ነው የገቡት " - አቶ ኪዱ ገብረ ፃድቅ (የትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን የፀጥታ ኃላፊ)
➡️ " እኛ በር ሰብረን አልገባንም ህዝቡ ግቡ ብሎ በሰልፍ ስለመጣ ነው " - አቶ ረዳኢ ገ/እግዚአብሔር
ከዚህ ቀደም የዓዲግራት ከተማ ሁለት ከንቲባዎች (አንድ በጊዜያዊ አስተዳደሩ አንድም እነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመሩት ህወሓት) እንደተሾሙባት ይታወቃል።
ማክሰኞ በደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት ቡድን የተሾሙት ከንቲባ በሰራዊት ኃይል በመታገዝ በኃይል በር በመስበር ፅ/ቤቱን እንደያዙት የምስራቃዊ ዞን የፀጥታ ኃላፊ አቶ ኪዱ ገብረ ፃድቅ አሳውቀዋል።
አቶ ኪዱ ገብረ ፃድቅ ምን አሉ ?
" የሰራዊቱ አመራሮች ' በምክር ቤት ለተመረጠው ከንቲባ አስረክቡ ' በማለት ወደ ከተማዋ ሰራዊት አስገብተዋል። ወደ ከንቲባ ፅ/ቤትም በኃይል ገብተዋል። ቁልፍ የላቸውም ሰብረው ነው የገቡት " ብለዋል።
አቶ ኪዱ ሰኞ ዕለት በዓዲግራት መግቢያ ቤተ ሓርያት በተባለ አካባቢው " ወጣቶች እያደራጃቹ ነው " በሚል በፀጥታ ኃይሎች ለ 4 ሰዓታት ታግተው ነው የተለቀቁት።
ማክሰኞ ቁልፍ ሳይኖራቸው በሩን ሰብረው ገብተዋል የተባሉት አቶ ረዳኢ ገ/እግዚአብሔር ፤ " ሰብረን አልንገባንም " ብለዋል።
አቶ ረዳኢ ገ/እግዚአብሔር ምን አሉ ?
" በህዝብ ሳይመረጥ በራስ ፍላጎት ብቻ በስልጣን ላይ የመቆየት ፍላጎት ስለነበረ ህዝቡ አገልግሎት አጥቶ ለሶስት ወራት ቆይቷል።
እኔ በምክር ቤት ተሹሜ ለሶስት ወራት ፅ/ቤት ሳልገባ መንገድ ዳር ነበርኩኝ። ችግሮች እንዳይፈጠሩ ስላሰብን ነው እስካሁን የቆየነው። አሁን ሰብረን አይደለም የገባነው የከተማው ህዝብ ከየአቅጣጫው ወጥቶ ' በሩ ይከፈት ' ብሎ ጠየቀ መልስ በማጣቱ ገፍቶ ነው የገባው በዚህም ወደ ፅ/ቤት ገብተናል " ብለዋል።
የፀጥታ ኃይሎች በአካባቢው የፀጥታ ችግር እንዳይፈጠር ራቅ ብለው ይከታተሉ ነበር እንጂ ወደ አስተዳደሩ ቅጥር ግቢ አልገቡም ሲሉ አክለዋል።
#VOATIGRIGNA
@tikvahethiopia
" እንደ ሀገር ትልቅ ችግር እያለፍን ነው። ዱዓ ማድረግ አለብን " - ኡስታዝ አቡበከር አህመድ
ዳሽን ባንክ የረመዳን ወርን ምክንያት በማድረግ ለደንበኞቹ፣ ለአጋርና ባለድርሻ አካላት ልዩ የኢፍጣር መርሃ ግብር ዛሬ በሸራተን ሆቴል አካሂዷል።
“መርሃ ግብሩ ባንኩ የማህበረሰብ ተሳትፎን ለማሳደግና ከደንበኞቹ ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር በማሰብ የተዘጋጀ ነው” ተብሏል።
በመርሃ ግብሩ የተገኙት ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ ለባንኩ ምስጋና አቅርበው፣ "እንደ ሀገር ትልቅ ችግር እያሳለፍን ነው። ዱዓ ማድረግ አለብን" የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።
የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው አለሙ፣ ለባንኩ ደንበኞችና ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች መልካም የረመዳን ፆም ወቅት እንዲሆን ተመኝተዋል።
ባንኩ ከደንበኞች እሴትና የፋይናንስ ፍላጎት ጋር የሚጣጣሙ ሸሪዓን ያሟሉ የባንክ አገልግሎቶችንን ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።
ሌላው የመርሃግብሩ አካል የነበረው በባንኩ የወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ዋና መኮንን ይፋ የሆነው፣ "ለማህበራዊ ኃላፊነት ሸሪክ ሁኑ" የሚለው ንቅናቄ ነው።
የንቅናቄው ዋነኛ ግብ ባንኩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችንና ማህበራዊ ጉዳዮችን ለመደገፍ ያለመ እንደሆነ፣ ይህም የባንኩን ደንበኞች እንደ የሂሳብ መክፈቻ፣ የተቀማጭ ገንዘብ መጠንና የፖስ "POS" ግብይቶችን ከዚህ ዓላማ ጋር ለማስተሳሰር መሆኑ ተገልጿል።
ከየካቲት 2017 ዓ/ም እስከ ሰኔ 2017 ዓ/ም የሚቆየው ይህ ንቅናቄ የባንኩን የፋይናንስ አካታችነትና ማህበራዊ ኃላፊነት የመወጣት ቁርጠኝነት የሚያጠናክር ይሆናል።
ባንኩ ማህበራዊ ሃላፊነትን ለመወጣት ባለው ቁርጠኝነት መሰረት ከደንበኞቹ በአደራ የሰበሰበውን ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ለ31 አገር በቀል የግብረ ሰናይ ድርጅቶች መለገሱ ይታወሳል።
#TikvahErhiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምን አለ ?
" ... አንዳንድ የኦርቶዶክስ ክርስትና አማኝ ነን የሚሉ ግለሰቦች፣ የእስልምና ሃይማኖት ነቢይ በሆኑት በነቢዩ መሐመድ (የአላህ እዝነትና ሰላም በእሳቸው ላይ ይሁንና) ላይ ድፍረት የተሞላበት ክብረ ነክና ጽያፍ ንግግር ሲያደርጉ ታየረተዋል፡፡ ይህም ሙስሊሙን ወገን ብቻ ሳይሆን ሰላም ወዳዱን ወገን ሁሉ አሳዝኗል፡፡
ጉባኤችንም ይህ ዓይነቱ ኢ-ሥነምግባራዊ እና ሕገ ወጥ ተግባር የትኛውንም የሃይማኖት ተቋም የማይወክል፣ ይልቁንም የሚወገዝ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ ይወዳል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንዳንድ የኦርቶዶክስ አማኝ ነን የሚሉ ወንድሞችና እህቶች የግለሰቡን ሕገ-ወጥ ተግባር ተቋማዊ ለማድረግ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንዲያጤኑና ግለሰብንና ተቋምን እንዲለዩ እንመክራለን፡፡
በአንፃሩ አንዳንድ ሙስሊም ነን የሚሉ ግለሰቦች ተደፈርን በሚል ስሜት የክርስትና አስተምህሮንና የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር የሚነቅፍና የሚያጠለሽ፣ መላውን ክርስቲያን በሚያዋርድ መልኩ ምላሽ ሲሠጡ እና ድርጊቱን በፈፀመው ግለሰብ ላይ የደቦ ፍርድ ሲያስተላልፉ ይታያሉ፡፡
ይህም ሕገ-ወጥነትን ከማስፋፋት ባለፈ ጥፋትን በሌላ ጥፋት ማረም ፈጽሞ የማይቻል መሆኑን ተገንዝበው ከድርጊታቸው በመታረም የሕግ የበላይነትን እንዲስቀድሙ ጉባኤያችን በአጽንኦት ይመክራል፡፡
በየትኛውም አካል የተፈፀሙትና የሚፈፀሙት ይህን መሠል ሕገ-ወጥ ተግባራት በሁሉም ሃይማኖቶች አስተምህሮ ተቀባይነት የሌላቸው ብቻ ሳይሆን የሚወገዙ ተግባራት መሆናቸውን ጉባኤያችን እያስገነዘበ ድርጊቱ በወንጀል የሚስጠይቅ ስለመሆኑም ለማስታወስ ይወዳል፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዝሀ ሀይማኖት መገኛና መኖሪያ ከመሆኗ አንፃር የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የትኛውንም ዓይነት የሃይማኖት ተቋማትን፣ አስተምህሯቸውንና መገለጫዎቻቸውን የሚያንቋሽሹና የሚያዋርዱ ንግግሮችንም ሆነ ተግባራትን በጽኑ ያወግዛል። "
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#Update
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን ትእዛዝ " አልቀበልም አልፈፅምም " አለ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት ፤ " በቢሮው ስም የቀረበው መግለጫ የአንድ የጊዚያዊ አስተዳደሩ አካል ሳይሆን የአንዱ ቡድን ወታደራዊ ክንፍ መሆኑ በግልፅ የሚያሳብቅና የተፈጠረውን ችግር የሚያባብስ ነው " ብሎታል።
ትናንት መጋቢት 1/2017 ዓ.ም ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በሦስት ከፍተኛ የሰራዊት አመራሮች የጣሉት ጊዚያዊ እግድ ተከትሎ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመሩት ህወሓት " እገዳው መሰረተ ቢስ እና የማይተገበር " በማለት ውድቅ ለማድረግ ጊዜ አልወሰደበትም።
ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት ደግሞ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ጊዚያዊ እግድ ሙሉ በሙሉ በመፃረር ባወጣው መግለጫ ፤ በግልባጭ የተፃፈለትን ትእዘዛዝ እንደማይቀበል በመግለፅ " የህግ ማስከበር እርምጃው " ይቀጥላል ብሏል።
የሰላምና ፀጥታ ቢሮ መግለጫ ተከትሎ ከመቐለ በ115 ኪሎ ሜትር ርቀት በምትገኘው የዓዲግራት ከተማ በሰራዊት የታገዘ መፈንቅለ ስልጣን መካሄዱን ለማወቅ ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ዛሬ ጠዋት ወደ ምስራቃዊ ዞን የሰላምና የፀጥታ ሃላፊ ደውሎ " ከቀበሌ የተወጣጡ ጥቂት ደጋፊዎች በሰራዊት በመታገዘ ጊዚያዊ አስተዳደሩ የሾማቸው ከንቲባ ሲገለገሉት የነበረው ፅሕፈት ቤት በመስበር በደብረፅዮኑ ህወሓት ለተመረጡት ከንቲባ አስረክበዋል " ብለውታል።
በትግራይ ክልል ያለው የፓለቲካና የፀጥታ ሁኔታ እጅግ አሳሳቢና ተለዋዋጭ ደረጃ ላይ ይገኛል ያሉትን ሁኔታዎች እየተከታተልን እናቀርባለን።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#ቢክ_እስኪብርቶ #አልሳም
ቢክ እስኪብርቶ በኢትዮጵያ ሊመረት ነው።
የብዙዎቻን ባለውለታ የሆነውና ከልጅነታችን ጀምሮ የምናውቀው ቢክ እስኪብርቶ በኢትዮጲያ ለረዥም ጊዜ አገልግሎት ሰጥቷል።
በአልሳም ኃ/የተ/የግል/ማ ብቸና አስመጪ እና አከፋይነት ከሃያ አመታት በፊት ጀምሮ ቢክ እስኪብርቶን ለኢትዮጲያ ገበያ ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡
መገኛውን ኬንያ ካደረገው ሃኮ ኢንደስትሪስ ከሚባል ኩባንያ ለረዥም ጊዜ ያስመጣ የነበረ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ከቢክ ኢስት አፍሪካ ሊሚትድ ከሚባለው ተቋም ሲያስመጣ ቆይቷል።
የካቲት 29/2017 ዓም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነሩ ዘለቀ መኮንን የክብር እንግዳ ሆነው በተገኙበት (ዶ/ር ) የአጋርነት ስምምነት አድርጓል። በተደረገው የአጋርነት ስምምነት አልሳም ቢክ እስክርቢቶን በኢትዮጵያ ውስጥ ለማምረት ከኢስት አፍሪካ ሊሚትድ ጋር ተስማምቷል።
ስምምነቱን የአልሳም ግሩፕ ኃላፊ አቶ ካሚል ሳቢር እና የቢክ ኩባንያ የመካከለኛው ምስራቅ እና አፍሪካ ቀጣናዎች ኃላፊ ፒተር ቫን ደን ብሮክ ፈርመውታል፡፡
አልሳም ከማምረቱ በተጨማሪ የምርቱ ስርጭትም ለምስራቅ አፍሪካ አገሮች ኢትዮጲያን ጨምሮ ለጅቡቲ፣ ለሶማሊያና ለኤርትራ የሚያከፋፍል ይሆናል።
ይህም ለአገራችን የቴክኖሎጂ ሽግግር ከመፍጠሩ በተጨማሪም የፍላጎት እና ምርት ምጣኔውን ያስተካክላል፣ የውጭ ምንዛሬ ያስገኛል፣ ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድልም ይፈጥራል ተብሎ ይታመናል ።
ፕሮጀክቱም በቀጣይ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገልጿል ።
አልሳም ኃላ/የተ/የግል ማህበር ከተመሰረተ 25 ዓመታት ያለፉት ሲሆን በአስመጪነት፣ በላኪነት፣ በአገር ውስጥ ንግድ፣ በሪል እስቴትና በማኑፋክቸሪንግ የሥራ ዘርፎች ተሰማርቶ የሚገኝ ኩባንያ ነው።
#አልሳም
በሁሉን አቀፍ ዲጂታል የትምህርት አስተዳደር ሶሉሽናችን አሰራርዎን ያዘምኑ!
🚀👨👩👧👦 የትምህርት ተቋም የአስተዳደርን፣ ከመምህራን፣ ተማሪዎች እና ወላጆች ጋር የተቀናጀ ትስስር ለመፍጠር የሚያስችል
📊 🔄 የተማሪዎችን ውጤት ክትትል፣ የመረጃ ልውውጥ፣ የተማሪ-ወላጅ-መምህር ተሳትፎን በማጎልበት እንዲሁም የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት በማቅረብ የትምህርትን ጥራት በእጅጉ የሚያሳድግ
💳⏩ የክፍያ ሂደቶችን በቴሌብር በማቀናጀት የወላጆችን ጊዜና ጉልበት በመቆጠብ የትምህርት ተቋማትን አስተዳደራዊ ቅልጥፍና የሚያሳድግ
ትምህርትን ያሳድጉ፣ አስተዳደርን ያመቻቹ፣ ጠንካራ ግንኙነቶችን ዛሬውኑ ይገንቡ!
📍የድርጅት የአገልግሎት ማዕከሎቻችንን ይጎብኙ!
ለተጨማሪ መረጃ: https://bit.ly/41pAAAv
#SmartEducation
#EducationAdministrationSolution
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#Update
በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " እገዳው መሰረተ ቢስና የማይተገበር " ሲል ውድቅ አደረገው።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን " አምባገነን ፕሬዜዳንት ነበር " ሲል አጣጥሏቸዋል።
ደብረፅዮን (ዶ/ር) የሚመሩት ህወሓት ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ሦስት ከፍተኛ የሰራዊት አመራሮች ላይ የወሰዱት ጊዚያዊ የእግድ እርምጃ አስመልክቶ ሌሊት መግለጫ አውጥቷል።
በዚህም ፕሬዜዳንቱ የወሰዱት እርምጃ " በሌለ ስልጣናቸው የወሰዱት የማይተገበር " ሲል በፅኑ ተቃውሞታል።
" እገዳው መሰረተ ቢስና የማይተገበር " ሲል ውድቅ ያደረገው መግለጫው ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳን " ከስልጣቸው የኋላፊነት ቦታ ማንሳቱን " አስታውሰዋል።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን " አምባገነን ፕሬዜዳንት ነበር " ሲልም አጣጥሏቸዋል።
" የእግድ እርምጃውን የተደራጀ ሰራዊት ለማፍረስ ሲደረገው የቆየው ተንኮል አካል ነው " ያለ ሲሆን " እርምጃው አደገኛ ውጤት የሚያስከትል ነው " ሲል አስጠንቅቋል።
" መሰረተ ቢስ " ሲል የገለፀው የሦስቱ ከፍተኛ የሰራዊት አመራሮች ጊዚያዊ እግድ ፤ የሰራዊት አባላትና ህዝቡ እንዳይቀበሉት የሚል ጥሪም አስተላልፏል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#Tigray
" ጊዚያዊ አስተዳደሩ ያለችውን ትግራይ ማስተዳደር የማይችልበት ሁኔታ ተፈጥረዋል" - አቶ ጌታቸው ረዳ
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የክልሉን ወቅታዊ ሁኔታ በማስመልከት ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በዚህም የደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመሩት ህወሓት የተወሰኑ የሰራዊት አመራሮችን በመጠቀም በጊዚያዊ አስተዳደሩ ላይ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ እያካሄደ እንደሆነ ተናግረዋል።
" ቡድኑ በድርጅቱ የቁጥጥር ኮሚሽንና በኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ኮሚሽን እውቅና የሌለው ህገ-ወጥ ጉባኤ ያካሄደ ነው " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ቡድኑ በማንኛውም መመዘኛ እና መለኪያ ወደ ስልጣን አይመለስም " ሲሉ አክለዋል።
ጥቂት የሰራዊት አመራሮች እንደ መሳሪያ በመጠቀም በየወረዳው እና ቀበሌው በጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሾሙ የስራ ሃላፊዎች ማህተም በመቀማት ላይ ተጠምዷል ሲሉም ተናግረዋል።
" ይህ ህገ-ወጥ ተግባር የተረጋጋ መንግስታዊ አገልግሎትና ፀጥታ እንዳይኖር እክል ፈጥሯል " ሲሉም ገልጸዋል።
" ጊዚያዊ አስተዳደሩ ያለችውን ትግራይ ማስተዳደር የማይችልበት ሁኔታ ተፈጥረዋል " ሲሉም አክለዋል።
" የክልሉን ፀጥታ በማድፍረስ የፕሪቶሪያ ስምምነት ለማፍረስ የተጀመረው እንቅስቃሴ እጅግ አደገኛና ጥፋት የሚያስከትል ነው " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ተግባሩ በአስቸኳይ እንዲቆም ሁሉ መተባበር አለበት " ብለዋል።
ሌላው አቶ ጌታቸው ረዳ በመግለጫቸው በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መንግስታት መካከል በግልፅ የሚታይ ወጥረት አለ ብለዋል።
" ውጥረቱ ወደ ግጭት ተሸጋግሮ ትግራይ የጦርነት አውድማ እንዳትሆን መስራት ይጠበቅብናል " ሲሉ ተደምጠዋል።
ትናንት የካቲት 30 እና ዛሬ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም በትግራይ ምስራቃዊ ዞንና በመቐለ የተወሰኑ የሰራዊት አመራር ያሰማሩት ኃይል ፓትሮል በመጠቀም በጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሾሙ አስተዳዳሪዎች ማህተም የመቀማት እና ከአንዱ ከተማ ወደ ሌላ ከተማ የሚወስድ ከተማ የቁጥጥር ኬላ የመስራት ምልክቶች መታየታቸው አቶ ጌታቸው ረዳ አስታውቀዋል።
ዛሬ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም የምስራቃዊ ዞን የፀጥታና የሰላም ሃላፊ በአከባቢው በሚገኙ የሰራዊት አመራር ከሁለት ሰዓት በላይ ታግተው መለቀቃቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አረጋግጠዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#Afar #Somali #Iftar
ዛሬ የአፋር እና ሶማሌ ወንድማማች ህዝቦች የኢፍጣር መርሐ ግብር በጅግጅጋ እየተካሄደ ይገኛል።
በመርሃ ግብሩ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሃጂ አወል አርባ፣ የሰላም ሚንስትሩ አቶ መሀመድ እድሪስ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋን ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ተገኝተዋል።
#SomaliRegionGovCommunication
@tikvahethiopia
" ይህ በአደባባይ የተላለፈ የጥላቻ ንግግርና ሀይማኖታዊ ትንኮሳ በህዝበ ሙስሊሙ ላይ የፈጠረውን ህመም በአግባቡ በመረዳት የሚመለከታቸው የፀጥታና የህግ አካላት ተጨማሪ ጥፋት ከመከተሉ በፊት እርምጃ ይውሰዱ " - ጠቅላይ ም/ቤቱ
ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች በተለይ ደግሞ በቲክቶክ ላይ አንድ ግለሰብ ነብዩ ሙሀመድ " ﷺ " እና እስልምናን መዝለፉ በርከቶችን አስቆጥቷል።
ጉዳዩን በተመለከተም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት መግለጫ ልኮልናል።
በዚህም መግለጫው የጥላቻ ንግግር በማድረግ ግጭት ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ አጥብቆ አሳስቧል።
የእስልምናን መልካም እሴቶች እና የነብዩ ሙሀመድን (ሰ.ዐ.ወ) ክብር በመዳፈር ህዝበ ሙስሊሙን የሚያስቆጡ የጥላቻ ንግግሮች በስፋት እየተሰራጩ መሆናቸውን የገለጸው ጠቅላይ ም/ቤቱ እነዚህ አካላት ከዛሬ ነገ ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸው ከጥፋታቸው ይታረማሉ በሚል ቀና እሳቤ ጉዳዩን በትዕግስት ሲከታተል እንደቆየ ገልጿል።
ይሁን እንጂ ችግሩን ከዚህ በላይ በትዕግስት መመልከት ውጤቱ የከፋ መሆኑን ጠቁሟል።
የኢስላምንና የነብዩ ሙሀመድን (ሰ.ዐ.ወ) ክብር የሚነኩ አካላት በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ለማድረግ ከየትኛው አይነት ተግባር ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚሰራም አሳውቋል።
በመሆኑም በተደጋጋሚ ተከስቶ በቸልታ እየታለፈ ያለው የኢስላምንና የነብዩ ሙሀመድን (ሰ.ዐ.ወ) ክብር የሚነካ የጥላቻ ንግግር ያደረጉ ግለሰቦች አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው የፍትህ፣ የፀጥታና የደህንነት አካላት የህግ ተጠያቂነትን ለማምጣትና መሰል ጥፋቶች እንዳይደገሙ ከመቼውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንዲሰሩ ም/ቤቱ አሳስቧል።
ጠቅላይ ምክር ቤቱ ፦
➡️ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጉዳዩ ከዚህ በላይ ከመካረሩ በፊት የጋራ አቋም በመያዝ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲያገኝ አስቸኳይ ውሳኔ እንዲወስን፤
➡️ ይህ በአደባባይ የተላለፈ የጥላቻ ንግግርና ሀይማኖታዊ ትንኮሳ በህዝበ ሙስሊሙ ላይ የፈጠረውን ህመም በአግባቡ በመረዳት የሚመለከታቸው የፀጥታና የህግ አካላት ተጨማሪ ጥፋት ከመከተሉ በፊት አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስዱ፤
➡️ የሰሞኑ የጥላቻ ንግግር ምንጩ የተራ ግለሰብ ቢመስልም ከጀርባ የአጀንዳና የሃሳብ ተጋሪዎች ያሉት በመሆኑ ህዝባዊ ቁጣ ከመቀስቀሱ በፊት የሀገርና የህዝብ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ሁሉ ከጠቅላይ ም/ቤቱ ጋር በመቆም ትንኮሳውን እንዲያወግዙ፤
➡️ ወቅቱ በሙስሊሞችና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች የጾም ወቅት እንደመሆኑ እንዲህ አይነት ከሀይማኖትና ከኢትዮጵያዊነት እሴት ያፈነገጡ የጥላቻ ንግግሮች የሚገሰፁበትና የሚታረሙበት የፅሞና ወቅት እንዲሆን ም/ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#Update
🔴 " ዛሬ ጠዋት 32 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል " - የወላጆች ኮሚቴ
➡️ " የታይላንድ መንግስት ያልተቀበላቸው ወደ 300 ልጆች ማይናማር ካምፕ ውስጥ አሉ። 32 ልጆች መጥተናል " - ተመላሽ ኢትዮጵያዊ
ከማይናማሩ እገታ ወጥተው ታይላንድ ካምፕ ከነበሩት ኢትዮጵያውያን መካከል 32 የሚሆኑት ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን የወላጆች ኮሚቴና ተመላሾቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
የወላጆች ኮሚቴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ " ዛሬ ጠዋት 32 ኢትዮጵያውን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል " ብሏል።
ልጆቹን ለሀገራቸው እንዲበቁ ላደረጓቸው ምስጋና አቅርቦ፣ ከእገታ ወጥተው በታይላንድ ያሉ፣ በማይናማር ገና ከእገታ ያልወጡና ወጥተው ወደ ታይላንድ ያልተሻገሩ፣ ጭራሹንም ያሉበት የማይታወቅ በርካታ ኢትዮጵያውያንን መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቋል።
ከተመላሾቹ መካከል አንዱ፣ 32 ልጆች መምጣታቸውን አረጋግጦ፣ " የታይላንድ መንግስት ያልተቀበላቸው ወደ 300 ልጆች ማይናማር ካምፕ ውስጥ አሉ። 32 ልጆች መጥተናል " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።
የውጩ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፣ 32 ልጆች እንደመጡ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መልዕክት አረጋግጧል።
ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ፣ ከማይናማሩ እገታ ወጥተው ወደ ታይላንድ ከተሻገሩ 133 ኢትዮጵያ መካከል 32ቱ ዛሬ ወደ አገራቸው ገልጾ፣ " 43 ኢትዮጵያውያንን ደግሞ ዛሬ ምሽት ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል " ብሏል።
" ቀሪዎቹ በታይላንድ ማቆያ የሚገኙ 58 ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው ለመመለስ ኤምባሲው ጥረት እያደረገ ይገኛል " ሲልም አክሏል።
ጃፓን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚገኙ ሌሎች ኢትዮጵያውያንን ወደ ታይላንድ በማሻገር ወደ አገራቸው ለመመለስ ጥረት እያደረገ ይገኛል ሲልም አክሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔈 #የኢትዮጵያውያንድምጽ
" እዚህ ያለነው ወደ 70 ኢትዮጵያውያን ነን ፤ ያለንበት ሁኔታ አስከፊ ነው ፤ ያናገረን አንድም አካል የለም " - ማይናማር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን
በማይናማር / ማይዋዲ KK2 የሚባለው ስፍራ የሚገኙ በቁጥር 70 የሚሆኑ ወጣቶች ከቦታው የሚያስወጣቸውን አጥተው ጭንቀት ላይ እንደሆኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ያሉበት ቦታ በማይናማር ወታደራዊ ሰዎች እየተጠበቀ እንዳለ ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያውያኑ " እኛ በጣም አስከፊ ሁኔታ ላይ ነን። 70 እንሆናለን። ማንም መጥቶ የጠየቀን የለም። መቼ እንደምንወጣም አናውቅም። ሁሉ ነገር ጨልሞብናል " ብለዋል።
" የሚሰጠን ምግብ የማይበላ ነው። ማደሪያ የለንም እንጨት ላይ ነው የምንተኛው ምን አይነት ሁኔታ ውስጥ እንዳለን ለመናገር ይከብዳል ስቃይ ላይ ነን " ሲሉ ገልጸዋል።
" ባለፈው አንድ ወንድማችን በጣም ታሞ በስንት መከራ ነው ህይወት የዘራው " ሲሉ አክለዋል።
" ያሉትን የMilitary ሰዎች ጠይቀናቸው ነበር አብረውን ካሉት ውስጥ ' የህንድ መንግሥት ዜጎቹን ለመውሰድ accept ስላደረገ እነሱ ይወጣሉ በእናተ በኩል ምንም ምላሽ የለም ' ብለውናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" ቢያንስ ትወጣላችሁ የሚለን የለ ወይ ስለኛ የሚናገር የለም እባካችሁ ስቃያችንን ስሙን " ሲሉ ተማፅነዋል።
" ህንዶቹ ነገ እና ከነገ ወዲያ ይወጣሉ ዛሬ እየተዘጋጁ ነው ከኛ ሀገር በኩል ያናገረን የለም በጣም ተጨንቀናል " ብለዋል።
እኚህ ወጣቶች ህይወትን ለማሸነፍ ሲሉ ታይላንድ ተብለው ወደ ማይናማር በግዳጅ የተወሰዱና በዛም በማፊያዎች ስንትና ስንት ስቃይ ያዩ ሲሆን ከዛ ስፍራው እንዲወጡ ከተደረጉ በኃላ አሁን ደሞ ሌላ ስቃይ እያዩ እንደሆነ አመልክተዋል።
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
" ከዚህ ቀደም ገዝተን ከታጠቅናቸው ድሮኖች የሚለያቸው በከፍተኛ altitude መብረር መቻላቸው፣ በAI የታገዙ በመሆናቸው redundant communication system ያላቸው መሆናቸው ፣ Anti Drone Jammer ስላላቸው ነው " - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በትላንትናው ዕለት " ስካይ ዊን ኤሮኖቲክስ " የተሰኘ ኢንዱስትሪ አስመርቀዋል።
ይህ ኢንዱስትሪ ፤ ለሲቪልና ወታደራዊ አገልግሎት የሚውሉ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን (ድሮን) የሚያመርት እንደሆነም ተናግረዋል።
ድሮኖቹ መረጃ ለመሰብሰብ፣ ለመከላከል አቅም እንዲሁም ለማጥቃት እንደሚውሉ ጠቅሰዋል።
" ከፍተኛ የsensor አቅም እና AI ያላቸው ድሮኖች ናቸው " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " አንዳንዶቹ suicide እንዳንዶቹ አጥቅተው የሚመለሱ ናቸው " ሲሉ አብራርተዋል።
ድሮኖቹ ከዚህ ቀደም ከተገዙት የሚለያቸው ነገሮችም እንዳለ ተናግረዋል።
" ከዚህ ቀደም ገዝተን ከታጠቅናቸው የሚለያቸው አንኳር ነገሮች አሉ። አንዱ ከዚህ ቀደም የምንገዛው test የሚደረገው sea level ላይ ስለሆነ እንደ ኢትዮጵያ ያለ ከፍተኛ altitude ላይ ለመብረር ይቸገራሉ የኛ UAV ተሰርተው test የሚደረጉት ከ2 ሺህ በላይ ስለሆነ በከፍተኛ altitude መብረርስ ስለሚችሉ ዝቅተኛ ቦታ ሲያገኙ የበለጠ functional ይሆናሉ " ብለዋል።
" ሌላው በAI የታገዙ በመሆናቸው redundant communication system ያላቸው ናቸው ሳተላይትም ይጠቀማሉ ከዚህ በተጨማሪ እያንዳንዱ ድሮን anti drone jammer አለው የሚወድቁ jmmer አይደሉም " ሲሉ ገልጸዋል።
ከውጭ የሚመጡት በኢትዮጵያ altitude ለመብረር ይቸገራሉ ሲሉ አክለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ " አቅም አባዢ አዳዲስ የጦር አቅሞችን በገዛ ገንዘባችን ለመታጠቅ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም " ያሉ ሲሆን " ድሮን ገዝቶ ለመታጠቅ የምንፈልገው አይነት የምንፈልገውን ቅርፅ መግዛት እንዳንችል ሻጮችም ሌሎችም ጫና ያሳድሩብን ነበር በኃላ ድሮን ገዝተን መታጠቅ ስንችል አጠቃቀሙ በፈለግነው ልክ operate ለማድረግ ፈተና ነበር " ብለዋል።
" ዛሬ ግን AI የታገዙ፣ ለማጥቃት የሚውሉ suicide ድሮችን ጭምር በኢትዮጵያ በዚህ ልክ ተመርቶ ማየት ለእንደኛ አይነት ህልመኛ ግለሰቦች አስደማሚ ውጤት ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
" ኢንዱስትሪው ድሮኖችን ከኢትዮጵያ ባሻገር ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም አለው " ሲሉም ተናግረዋል።
" ገበያ በስፋት ማፈላለግ አለብን " ያሉት ጠ/ሚኒስትሩ " በአፍሪካ ገበያ በስፋት እየሸጥን ተጠቃሚው እራሱ ከሚገጥመው ፈተናና ችግር በሚያመጣው ግብዓት መሰረት ማሻሻል ይጠበቅብናል " ብለዋል።
" የድሮን ቴክኖሎጂ ከአቬዬሽን ጋር የሚያያዝ ቢሆንም በውስጡ ከባድ የሚባሉ component አሉት አንዱ AI ነው የስማርት sensors በሌላ ተቋምም ቢሆን ማምረት ማጠናከር ያስፈልጋል " ሲሉ ገልጸዋል።
ከዚህ አሁን ተመረቀ ከተባለው ኢዱንስትሪ በተጨማሪ በአየር ኃይል እና በINSA የሚሰሩ ድሮኖች እንዳሉም ተናግረዋል።
ተቋማቱም እንዲናበቡና እንዲደጋገፉ መወዳደር ባለባቸው ሁኔታም ሊወዳደሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
እርስ በእርስ ቴክኖሎጂ መደበቅ እና መከልከል እንደማይገባ ይልቅም ለምርምር በመስጠት ይበልጥ እያደገ እንዲሄድ ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢንዱስትሪውን ባስመረቁበት ወቅት " መዘጋጀት ካልቻልን ጦርነት በማንኛውም ጊዜ ሊያጋጥምና ሀገር ሊያፈርስ ይችላል " ያሉ ሲሆን " ጦርነት ለማስቀረት በቂ ዝግጅት ማድረግ ይገባል ፣ ጦርነት አሳጥሮ ለመጨረስም በቂ ዝግጅት ያስፈልጋል " ሲሉ አክለዋል።
@tikvahethiopia
#Update
“በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አዕዋፋት ይመጣሉ። ባለፍኩበት የስራ ዘመን እንደዚህ አይነቱን አሰራር ለስለላ ተጠቅመውበት አያውቁም” - በዘርፉ 40 ዓመታት የሰሩ የአዕዋፍ ሳይንቲስት
በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማኦ እና ኮሞ ልዩ ወረዳ በጀርባዋ የኤሌክትሮኒክ ቁስ ተሸክማ ስትበር ተገኘች የተባለችው ወፍ የብዙዎችን ቀልብ ስባለች።
ብዙዎች “ለስለላ የተላከች ወፍ ነች” የሚል ስጋታቸውን በማኀበራዊ ሚዲያ ሲያንጸባርቁ የተስተዋሉ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም የክልሉን አካላት ስለጉዳዩ ጠይቆ ገና በምርመራ መሆናቸውን ከመግለጽ ውጪ ያሉት የለም።
የወፏ ጉዳይ እውነትም ስለላ ሊሆን ይችላል ይሆን ? እስከዛሬ በነበሩ መሰል ክስተቶች በወፍ አማካኝነት ስለላ ተደርጎ ያውቃል ? ስንል የአዕዋፋት ሳይንቲስት አቶ ይልማ ደለለኝን ማብራሪያ ጠይቋል።
በዘርፉ የ40 ዓመት ልምድ ያላቸው ባለሙያ ምን መለሱ ?
አሁን በግላቸው የአካባቢ ጥበቃ ላይ፣ ከዚህ ቀደም በዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን የሰሩት አቶ ይልማ እንዳሉት፣ ሰምንኛው የወፏ ጉዳይ በየዓመቱ የሚስተዋልና ሥጋት ሊደቅን የማይችል የተለመደ ሁነት ነው።
ባለሙያው፣ ከጀርባቸው ሶላር ጂፒኤስ፣ ከእግራቸው ቀለበት የተገጠመላቸው ወፎች የሆነ ወቅት ቅዝቃዜን በመሸሽ ከአውሮፓ ሀገራት 7000 ድረስ ኪሎ ሜትር አቋርጠው በየዓመቱ የሚመጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ወፎች ላይ ቀለበትና ሶላር ጂፒኤስ ገጥሞ መላክ ታዲያ ለምን አስፈለገ? የሚለውን ጥያቄ ሲያብራሩም፣ ከጀርባቸው ያለው ሶላር ጂፒኤስ ወፎች የት እንዳሉ፣ በምን ያህል ከፍታ እየበረሩ እንደሆነ፣ ወደየትኛው አገር እንደሄዱ አውሮፓያውያኑ የሚከታተሉበት እንደሆነ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ባለዎት ልምድ መሰረትና እንደብዙኅኑ ስጋት ቀለበትና ሶላር ጂፒኤስ በተገጠመላቸው ወፎች ስለላ ተደርጎ አያውቅም? የሚል ጥያቄ ለባለሙያው አቅርቧል።
አቶ ይልማ ምን መለሱ ?
ሰዎች ይህንን ከፖለቲካ ጋር ያያይዙታል። ነገር ግን ፒዩርሊ የሳይንስ ስራ ነው። እኔም ብዙ ጊዜ ወፎች ላይ ቀለበትና ጂፒኤስ ትራከር አስሪያለሁ።
ኢትዮጵያ እንኳን በሚመጡበት ወቅት ያን ቀለበትና ጂፒኤስ አስረን የት ድረስ እንደሚሄዱ የምንከታትልበት ሲስተም አለ። ሳይንቲስቶች ከእውቀት ጉጉት የሚያደርጉት ነው እንጂ በፍፁም የስለላ ተግባር እንዳልሆነ ነው የምረዳው።
ያው ኢትዮጵያ ውስጥ ያን ያክል ጥልቅ እውቀት ስለሌለና አሁን ያለንበት የሰላም ሁኔታ ጋር ተደማምሮ ሰዎች እንደዚህ እንዲያስቡ አድርጓቸዋል። እውነት ለመናገር ለስለላ ቢሆን ኖሮ ወፍ ሳይሆን ድሮን ላይ በተገጠመ ነበር። ምክንያቱም የተፈጥሮ ወፍን እንቅስቃሴ መቆጣጠር አይቻልም።
በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አዕዋፋት ይመጣሉ። እነርሱ (አውሮፓውያኑ) ከኛ የተሻለ ፍለጎቱ፣ እውቀቱ፣ አቆርቦቱ፣ የገንዘብ አቅሙም ስላላቸው በአዕዋፍ እንደዚህ ያደርጋሉ እንደዚህ ዓይነቱ ስራ ደግሞ ከገንዘብ በተጨማሪ ብዙ ጊዜና ክትትል ይፈልጋል።
ከዚህ ቀደምም በደርግ ዘመን የኢትዮ - ኤርትራና የካራማራ ጦርነት በነበረበት ወቅት ደርግም ደግሞ ኮሚኒስት ከመሆኑ የተነሳ ከአሜሪካና ከአውሮፖ ሀገራት ‘የተላከ ሰላይ ነው’ በሚል ብዙ ጭንቅላት የሚያዞር ችግር ነበር፤ እኛም ይህን ለማስረዳት ሞክረናል።
አሁንም ሰዎች ይህን ቢሉ እኔ አልፈርድም ምክንያቱም እኛ ባለሙያዎችም ብንሆን እንደዚህ አይነቱን ነገር ቀድመን ለማህበረሰቡ ማሳወቅ ይጠበቅብናል።
ባለፍኩበት የስራ ዘመን እንደዚህ አይነቱን አሰራር ለስለላ ብዙም ተጠቅመውበት አያውቁም። በእርግጥ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የወፎች እግር መልዕክት ይደረግላቸውና መልዕክት የሚላላኩትን ሰዎች ቤት እርግቧ ስለምታውቅ ከአንዱ ወደ ልላኛው ስታስተላልፋል።
በዛ ጊዜ የተጠቀለለ ወረቀት በትንሽየ እቃ አድርገው በወፍ ጀርባ ላይ ያደርጉትና ለሚፈለገው አካል ይደርስ ነበር። ምክንያቱም ወፍ ላይ መልዕክት ይኖራል ተብሎ ስለማታይ ጠላት ባለበት ጎራም አልፈው ወገን ጋር ሊያደርሱ ይችላሉ።
በወፎች ስለሚደረገው ስለላ ይህን ብቻ ነው የማውቀው ይኸውም ያኔ እንደአሁኑ ቴሌግራም፣ ፌስቡክን የመሳሰሉ የመልዕክት መለዋወጫዎች ስላልነበሩ ነው። አሁን ወፎች ለስላላ ጥቅም አይውሉም፤ አንዲያውም ጂፒኤስ የሚደረግባቸው ወፎች ረጅም ርቀት በመጓዝ በመጓዛቸው፣ በርሀብና በጥም ምክንያት 75% ይሞታሉ” ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia