tikvahethiopia | Unsorted

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1527734

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Subscribe to a channel

TIKVAH-ETHIOPIA

#ግብር

" መኖር ከማይችል ሰው ግብር አትሰበስብም ፤ በልቶ ከማያድር ሰው ግብር አትሰበስብም ! " - አቶ ካሳሁን ፎሎ


➡️ " እንደ ሀገር ግብር መሰብሰብ አለበት ልማትም መቀጠል አለበት ፤ የሰው ህይወትም መቀጠል አለበት ፤ ሰው እየተራበ መስራት አይችልም ምርታማ መሆን አይችልም ! "


የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ፕሬዘዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ስለ ገቢ ግብር አዋጁ ምን አሉ ?

" የደመወዝ ገቢ ግብር ከዚህ በፊት መነሻው 600 ብር ነው፤ አሁን በረቂቁ የቀረበው 2,000 ሆኖ ነው።

በመሰረቱ 600 በሆነበት ሰዓት አንደኛ ገንዘብ የመግዛት አቅሙ ትልቅ በመሆኑ ፣ 1 ዶላርም 20 ብር ነበር ያኔ የዛሬ 10 ዓመት አካባቢ ነው ይሄ ነገር የተሻሻለው ፤ ሁለተኛ የመንግሥት ሰራተኞች መነሻ ደመወዝ 600 ነበር ያኔ 600 ለአንድ ሰው ለአንድ ወር ቢያንስ ምግብ መብላት ብቻ ይበቃዋል በሚል ታሳቢ አማካይ ተወስዶ ነው 600 የተባለው።

አሁን ግን 300% ፣ 200% ጨመርን (ማለትም 2000 ብር አደረግን) እሱ አይደለም ዋናው መነሻው ስንት ነው አሁን ? በአጭሩ ፤ እንኳን የኑሮ ውድነቱን ታሳቢ ያደረገ መንግሥት እራሱ ሰራተኛው በ600 ብር ሊያኖረው አይችልም ፤ የኑሮ ውድነቱ ከሚታሰበው በላይ በተለይም በሪፎርሙ መንግሥት በይፋ ያረጋገጠው ታችኛው የሰራተኛ ክፍል ጎድቶታል፤ ' ሊቋቋመው አይችልም ' በሚል መነሻ ደመወዙን ከፍ አድርጓል ፤ መነሻ ደመወዝን ከፍ ሲያደርግ ይሄን ታሳቢ አድርጓል።

አሁንም ቢሆን እነዚህ ሰዎች መኖር ከማይችል ሰው ግብር አትሰበስብም ፤ በልቶ ከማያድር ሰው ግብር አትሰበስብም። በቀን 2.15 ዶላር የሚያገኝ ሰው ድሃ ነው ከዚያ በታች የሚያገኝ በሙሉ ድሃ ነው ፤ እኛ ደግሞ እዛ ሁሉ አልደረስንም።

እኛ እያቀረብን ያለነው ሃሳብ 8,324 መነሻ ይሁን ነው። እንኳን የኛ ሀሳብ የመንግሥት እራሱ ያስቀመጠው መነሻ ላይ እንኳን አልደረሰም።

ሌላው በፊት የግብር ምጣኔው ከ0 ጀምሮ 10% ፣ 15% ፣ 20% ፣ 25% ፣ 30% ፣ 35% ይቀጥል ነበር አሁን 10%ን ከመሃል አወጡና ከ0 ጀምረው ቀጥታ 15% ነው የገቡት። አሁን ቀጥታ ከ15 ከከፍተኛው ነው ሲጀምር የጀመሩት። ይሄ ትክክል አይደለም።

35% ከየት ጀመረ 14,100 በላይ የሚያገኝ ሰው 35% ግብር ይከፍላል ፤ 35% ከሰራተኛ በአሁኑ የኑሮ ውድነት 15% በእያንዳንዱ በምግብ ዋጋም፣ በሚገዛው እቃም 15% ይጨምራል ይሄ ሲደመር 50% ይመጣል፤ 7% የጡረታ አለ ጡረታ የሚያገኘው ከ60 ዓመት በኃላ አሁን ግን 57% ከደመወዙ ላይ ይሄዳል በቀረችው 43% ፦
- ልጆች ያስተምራል
- ምግብ ይበላል
- ልብስ ይገዛል
- ቤት ይከራያል ምንድነው የሚያደርገው ?

ይሄና ይሄ ብቻ ስላልሆነ ነው ዝም ያልን እንጂ ይሄም ከፍ ብሎ እኮ ይበቃል ማለት አይደለም።

ግን እንደ ሀገር ግብር መሰብሰብ አለበት ልማትም መቀጠል አለበት ፤ የሰው ህይወትም መቀጠል አለበት ፤ ሰው እየተራበ መስራት አይችልም ምርታማ መሆን አይችልም። "

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#HoPR🇪🇹

ነገ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ያካሂዳል።

በዚህም ስብሰባ ሰፊ ክርክር ሲካሄድበት ብዙ ሃሳቦች ሲሰነዘሩበት የነበረውን የፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ያጸድቃል።

ረቂቅ አዋጁ በንግዱ ማህበረሰብና በተቀጣሪ ሠራተኞች ላይ ሊጣል የታሰበው የግብር ምጣኔ ከፍተኛ ነው የሚል ቅሬታ ሲነሳበት ቆይቷል።

አሁን ካለው የኑሮ ውድነትና የዋጋ ንረት አኳያ፣ እስከ 35 በመቶ የሚደርሰው የገቢ ግብር መጠን መቀነስ እንዳለበት ሲጠቆም ነበር።

የገቢ ግብር መነሻው 2,000 ብር ተብሎ የተቀመጠው ዝቅተኛ በመሆኑ መጠኑ ከፍ እንዲል ሲጠየቅ ነበር።

ለአካል ጉዳተኞች የግብር መጠኑ በተለየ መልኩ እንዲቀነስ እና ከተለያዩ የሙያና የንግድ ዘርፎች አንጻር የአዋጁ ድንጋጌዎች በደንብ ታይተው መስተካከል እንዳለባቸው ሲጠየቅ ነበር።

መንግስት ሲሰጥ የነበረዉ ማብራሪያ ደግሞ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጎ የታክስ ፍትሀዊነትን እና የኢኮኖሚ ልማት እንዲሁም እድገትን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ እንደሆነ ገልጿል።

ም/ቤቱ ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን እንዲሁም የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅን ያፀድቃል።

መረጃው ከህ/ተ/ም/ቤት እና ካፒታል ጋዜጣ የተውጣጣ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ፎቶ፦ በአፋር ክልል አፍዴራ ወረዳ ትናንት በነበረ ዝናብ አዘል ከባድ ነፋስ የሰው ህይወት ጠፍቷል ፤ በንብረት ላይም ከባድ ጉዳት መድረሱን የአፋር ክልል አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

በአደጋው የ1 ሰው ሕይወት አልፏል።

በተጨማሪም በ32 ሰዎች ላይ ከባድ ፤ በ22 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት መደረሱ ተመላክቷል።

አደጋው በ3 ባንኮች፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮ ቴሌኮም መሠረተ ልማቶች እንዲሁም በ5 የጨው ፋብካዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

ትምህት ቤቶች እና ጤና ጣቢያዎችን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማት በአደጋው ተጎድተዋል።

በዚህ ዝናብ በቀላቀለ ከባድ ነፋስ በከተማው ጉዳት ያልደረሰበት አንድም ቤት የለም ተብሏል።

የዚህ መረጃ ባለቤት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Sidama

🔴 የሲዳማ ክልል ም/ቤት አቶ ዳዊት ዳንግሳን የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አድርጎ ሾመ።

የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ምርጫ ዙር 4ኛ ሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ላለፉት ሶስት ቀናት በ11 አጀንዳዎች ላይ ሲወያይ ቆይቷል።

በዚህም የ2018 ዓ/ም በጀት፣ የተለያዩ ሹመቶችን እንዲሁም አዳዲስ አዋጆች በማፅደቅ ተጠናቋል።

በጀትን በሚመለከተ ፦

የክልሉን የ2018 ዓ.ም በጀት 32 ቢሊዮን 823 ሚሊዮን 357 ሺህ 21 ብር እንዲሆን አፅድቋል።

ከበጀቱ 19 ቢሊዮን 336 ሚሊዮን 298 ሽህ 596 ብር ከክልሉ የውስጥ ገቢ የሚሰበሰብ እንደሆነም ተመላክቷል።

ሹመትን በሚመከተ ፦

ምክር ቤቱ በርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ደስታ ሌዴሞ የቀረቡ ሹመቶችን ተቀብሎ ያፀደቀ ሲሆን በዚሁ መሰረት :-

➡️ አቶ ዳዊት ዳንግሳ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ (በዚህ ቦታ የነበሩት አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ በወንጀል ተጠርጥረው መታሰራቸው ይታወሳል)
➡️ አቶ ፍቅሬኢየሱስ አሸናፊ የመሬት አስተዳደር እና ኢንቨስትመንት ቢሮኃላፊ
➡️ አቶ ቢንያም ሰለሞን በጠቅላ ፍርድ ቤት የፍርድ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት
➡️ አቶ ገነነ ሹኔ በጠቅላይ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነዉ ተሹመዋል።

ፍትሕን በሚመለከት ፦

በክልሉ በ2017 በጀት ዓመት በወንጀል እና ፍትሐብሔር መዝገቦች 43 ሺህ 653 አዳዲስ የክስ መዝገቦች የቀረቡ እንዲሁም 1 ሺህ 480 መዝገቦች ከካለፈው ዓመት የዞሩ በድምሩ 45 ሺህ 133 የክስ መዝገቦች ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን  44 ሺህ 307 መዝገቦች ውሳኔ ማግኘታቸውንና ቀሪዎቹ 826 መዝገቦች ለቀጣይ ዓመት መዘዋወራቸዉ በጉባኤዉ ላይ ተገልፆል።

ኦዲትን በሚመለከት ፦

ለምክር ቤቱ በቀረበዉ ልዩ ልዩ የኦዲት ሪፖርቶች በሲዳማ ክልል የበጀት አስተዳደር፣ ውሎ አበል፣ በነዳጅ ክፊያና በፕሮጀክቶች አፈፃፀም እና ጥራት ላይ የታዩ ክፍተቶቾ ለምክር ቤቱ ቀርበዋል።

በምክር ቤቱ ከተነሱ የኦዲት ሪፖርቶች መካከል ፦
° ያለ አግባብ የተከፈለ የአበል ብር 2,567,732,09 /ሁለት ሚሊዮን አምስት መቶ ስልሳ ሰባት ሺ ሰባት መቶ ሰላሳ ሁለት ብር ከዘጠኝ ሳንቲም/ ፤

° ያላግባብ የተከናወነ የነዳጅ ግዢ ብር 60,940,354,58 /ስልሳ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ አርባ ሺ ሶስት መቶ ሃምሳ አራት ብር ከሃምሳ ስምንት ሳንቲም/ ይገኙበታል።

አዋጆችን በተመለከተ ፦

የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 50/2017 ዓ/ም ፣ የአስፈጻሚ አካላት ማቋቋሚያ፣ ስልጣንና ተግባር  ለመወሰን የወጣ የአዋጅ ቁጥር 51/2017 ዓ/ም፤ የፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባርን ለመወሰን የወጣ አዋጅ ቁጥር 52/2017 ዓ/ም እና የሀዋሳ ከተማ መዋቅራዊ የዉስጥ አደረጃጀትን መልሶ ለማዋቀር የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 53/2017 ዓ/ም ቀርቦ ዉይይት ከተደረገባቸው በኋላ ፀድቀዋል።

የክልሉን ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አደረጃጀት ስልጣንና ተግባርን ለመወሰን እንዲሁም የክልሉን መንግስት አስፈፃሚ አካላት ማቋቋሚያ እና ስልጣንና ተግባርን ለመወሰን የወጡ አዋጆችንም አፅድቋል።

በአዋጁ መሠረት የፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተጠሪነቱ ለክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዲሆንና በክልል መዋቅር ያሉ 20 ቢሮዎች ሰምና መጠሪያ ማሻሻያ የተደረገባቸዉን ጨምሮ በርዕሰ መስተዳድሩ ሰብሳቢነት የመስተዳድሩ ምክር ቤት አባላት እንደሆኑ አዋጁ ይደነግጋል።

በሌላ በኩል የሀዋሳ ከተማ መዋቅርን መልሶ ለማደረጃት የቀረበዉ ረቂቅ አዋጅ ከዚህ ቀደም የነበረዉን የክፍለ ከተማ ብዛት ስያሜ ላይ ለዉጥ በማድረግ በ5 ክፍለ ከተሞችና በ26 ቀበሌዎች ዳግም እንዲዋቀር በሙሉ ድምፅ ፀድቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

ፎቶ፦ የክልሉ ኮሚኒኬሽን

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SafaricomEthiopia

የየእለቱን ዜናዎችን በSMS እናግኝ! 🗞📲
ከሳፋሪኮም ቁጥራችን 'A’ ብለን ወደ 30000 SMS አሁኑኑ በመላክ ወይም ወደ *799# በመደወል የቲክቫህ ትኩስ መረጃዎችን እናግኝ! በቀን 1ብር ብቻ! ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት ⚡️

#1Wedefit
#Furtheraheadtogether

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Tigray

ከሁሉም የሃይማኖት የቋማት የተወጣጡ እና በሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተመሩ አባቶች መቐለ ከተማ ይገኛሉ።

የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባውን ከሁለት ሳምንት በፊት ባካሄደበት ወቅት የተገኙት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ለዳግም ግጭት ቅስቀሳ የሚያደርጉ አካላት ስለመኖራቸው ያመላከተ መላሽ መስጠታቸው ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ለተነሳላቸው ጥያቄ የሰጡት ምላሽ በፌደራሉ መንግስት እና ማንነታቸውን ባልጠቀሷቸው በክልሉ የሚንቀሳቀሱ አካላት መካከል መቃቃር ስለመኖሩ አመላካች ሆኗል።

ለጥያቄው በሰጡት ምላሽም " የሁሉም እምነት አባቶች እዚህ ተወካዮች አላችሁ፣ ሌላ ምንም ስራ የላችሁም በፍጥነት ትግራይ ወደ ግጭት፣ ወደ ጦርነት እንዳይገባ ስራችሁን አሁን ጀምሩ፣ ከተጀመረ ወዲያ ብትናገሩ ዋጋ የለውም " ብለው ነበር።

" ባለሃብቶች፣ ምሁራን፣ ኤምባሲዎች ውጊያ እንዳይጀመር አሁን ሚናችሁን ተወጡ ምክንያቱም ከተጀመረ ከዚህ በፊት እንደምናቀው አይደለም ነገር ይበላሻል " ማለታቸውም የሚታወስ ነው።

የጠቅላይ ሚኒስትሩን መልእክት ተከትሎ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በማግስቱ ለአስቸኳይ ስብሰባ ተቀመጦ እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።

በወቅቱ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ ፓስተር ይታገሱ ሃይለ ሚካኤል ተቋሙ እያደረገ ስላለው ተግባራዊ እንቅስቃሴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " በቅርብ ጊዜ የሚደረጉ ነገሮች እንደሚኖሩ ተስፋ እናደርጋለን አሁን በውይይት ደረጃ ላይ ነው ያሉት ምን ይደረግ፣ እንዴት እናድርግ ውጤታማ የምንሆነው እንዴት ነው በሚለው ላይ መክረዋል በቅርብ ጊዜ ተግባራዊ የሆነ እንቅስቃሴ ውስጥ ይገባሉ " ብለው ነበር።

የስብሰባው አላማም የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልእክት ነገሩን በአጽንዖት መያዝ እንደሚያስፈልግ ጠቋሚ በመሆኑ መሆኑን ፓስተር ይታገሱ አስታውቀዋል።

መደረግ ባለባቸው ጉዳዮች ላይ ተከታታይ ውይይት ያደረጉት አባቶች በዛሬው ዕለት ወደ መቀሌ አቅንተዋል።

በመቐለ የሚገኙት አባቶች በምን በምን ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ተጨማሪ መረጃ ከተቋሙ እንዳገኘን የምናጋራቹ ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

ፎቶ፦ ድምጺ ወያነ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ንብተራ ኦንላይን!
ሁሉንም በአንድ ጥላ ስር የሚያገኙበት!

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ

***
ይሠሯል ከልብ እንደ ንብ!

#Nib #nibmobilebanking #NibQR #nib #nibtera #nibbank

Facebook  / Instagram / linkedin / nibinternationalbank6204">X / nibinternationalbank6204">Youtube / nibinternationalbank">Tiktok / Website

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ሰኞ ሀምሌ 7/2017 ዓ.ም በትግራይ እንዳስላሰ - ሽረ ከተማ ሁለት እንስቶች አሲድ ተደፍቶባቸው ጉዳት እንደደረሰባቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመስማት ችሏል።

ለጊዜው ስሙ ይፋ ያልተደረገ አንድ ግለሰብ በከተማዋ በሚገኘው አንድ መጠጥ ቤት በሚሰሩ ሁለት እንስቶች ላይ አሲድ በመድፋት ከባድ የአካል ጉዳት አድርሶባቸዋል።

ድርጊቱ በርካቶችን አስደንግጧል።

የተፈጠረው ምንድነው ? በማለት ቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ወደ ከተማዋ የፓሊስ ምንጮች ደውሏል።

" የወንጀል ተግባሩ መነሻና አፈፃፀም እየተጣራ ነው " ሲሉ መልሰዋል።

የጭካኔ ድርጊቱ የመጠጥ ቤቶች በስፋት በሚገኙበት 03 ቀበሌ ተብሎ በሚጠራ አከባቢ መፈፀሙ ያረጋገጡ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጮች " ማንኛውም መነሻ ይኑረው አስነዋሪ እርምጃው ከሰብአዊነት ያፈነገጠ ጭካኔ የተሞላበት ነው " በማለት ገልፀውታል።

ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ደግሞ አሲድ በላያቸው ላይ የተደፋባቸው እንስት  አህቶች ለህይወት አስጊ በሆነ ሁኔታ ይገኛሉ ብለዋል።

" በሴቶች ላይ የሚፈፀመው ይህን መሰል አስነዋሪ ጥቃት ማስቆም ካቃተን እንደ ህዝብ የመቀጠል ዕጣ ፈንታችን ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል " ሲሉ በአፅንኦት ተናግረዋል። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#NationalExam🇪🇹

በአገር አቀፍ ደረጃ በወረቀትና በበይነ-መረብ ሲሰጥ የቆየው የ2017 ትምህርት ዘመን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂ (12ኛ ክፍል) ፈተና መጠናቀቁ ተገልጿል።

ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8/ 2017 ዓ.ም  በመላ አገሪቱ በወረቀትና በበይነ-መረብ ሲሰጥ የቆየው የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መለቀቂያ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል፡፡

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ኮደርላብ የ2025 የክረምት ካምፕን ይቀላቀሉ - ተማሪዎችን እናበቃ!

የኮደርላብ 2025 የክረምት ካምፕ ተማሪዎችን ዲጂታል ችሎታዎች፣ ኮድ ማድረግ፣ ሮቦቲክስ፣ የwebsite development እና ሌሎችንም ለማስተማር ዝግጅቱን ጨርሷል!

🚀 ከ6 እስከ 18 አመት ለሆኑ ተማሪዎች ክፍት ነው።

📅 የሚፈጀው ጊዜ፡- 4 ሳምንታት project based learning ( games , animations , python projects and website development)

🎓 የፕሮጀክት ማሳያዎችን፣ የቡድን ስራን እና የምስክር ወረቀቶችን ያካትታል

ክፍያ ለአጠቃላይ 4 ሳምንት ስልጠና 6000Birr

📲 አሁኑኑ በhttps://forms.gle/HcjfaWrmC9PWmzGM7 ይመዝገቡ

ወይም በ +251 907 945085 ይደውሉልን

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የአውሮፕላን ነዳጅ መቆጣጠሪያዎች በጥብቅ ይፈተሹ " - ህንድ

ከአንድ ወር በፊት ህንድ ውስጥ በደረሰ የቦይንግ 787-8  አውሮፕላን መከስከስ አደጋ የ260 ሰዎች ህይወት መቀጠፉ ይታወሳል።

የአደጋው መንስዔ የቦይንግ አውሮፕላኑ ከተነሳ ከሰኮንዶች በኋላ የነዳጅ መቆጣጠሪያዎች ጠፍተው ወደ ሞተሩ የሚደርሰው ነዳጅ መቋረጡ መሆኑን በህንድ የአውሮፕላን አደጋ የምርመራ ቢሮ (AAIB)  ይፋ የተደረገ ቅድመ ሪፖርት አሳይቷል።

አውሮፕላኑ ከተነሳ በሰከንዶች ውስጥ የነዳጅ መቆጣጠሪያ ማብሪያና ማጥፊያዎች ደህነንት ጠፍተው ነዳጅ ተቋርጦ ነበር ተብሏል።

መቆጣጠሪያዎቹ ከመብራት ወደ መጥፋት በመቀየራቸው ወደ ሞተሩ የሚወስደው ነዳጅ መቋረጡ ተመላክቷል። በዚህም አውሮፕላኑ ሊከሰከስ ችሏል።

ሪፖርቱን ተከትሎ ህንድ አየር መንገዶች የአውሮፕላን ነዳጅ መቆጣጠሪያዎችን በጥብቅ እንዲፈትሹ መመሪያ አወጥታለች።

የአገረቱ ሲቪል አቪዬሽን የህንድ እና አለም አቀፍ አየር መንገዶች በነዳጅ መቆጣጠሪያዎች ላይ የራሳቸውን ፍተሻ አድርገው ሪፖርት እንዲያቀርቡ መመሪያው እንደወጣ ገልጿል።

አየር መንገዶች የቦይንግ አውሮፕላኖች የነዳጅ መቆጣጠሪያዎች ማብሪያና ማጥፊያዎችን እስከ ሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ፈትሸው እንዲያጠናቅቁ ጠይቋል።

" የተቀመጠውን ቀነ ገደብ በጥብቅ መከተል የመብረር ብቃት እና የአፕሬሸኖችን ደህንነት ለማረጋገጥ መሰረታዊ ጉዳይ ነው " ብሏል።

የአሜሪካ የፌደራል አቪዬሽን ባለስልጣን ይፋ የተደረገውን ሪፖርት ተከትሎ " የቦይንግ የነዳጅ መቆጣጠሪያዎች ማብሪያና ማጥፊያዎች ደህንነታቸው የተጠበቀ ነው " ብሏል። መቆጣጠሪያዎቹ በሚቆለፍ መልኩ የተገጠሙ መሆኑን አመልክቷል።

የህንድ አየር መንገድ ፓይለቶች ማህበር ከአደጋው ጋር ተያይዞ በአውሮፕላኑ ፓይለቶች ላይ የሚሰነዘረውን የስም ማጉደፍ ተከላክሎ መግለጫ አውጥቷል።

ማህብሩ " አብራሪዎች በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ማድረግ ያለባቸውን በስልጠናቸው እና በተሰጣቸው ኃላፊነት መሰረት እርምጃ ወስደዋል " ብሏል።

አደጋውን ተከትሎ ከኮክፒት የተገኘ የድምጽ ቅጂ አንደኛው ፓይለት " ለምን አቋረጥከው ? " ሲል የሚሰማ ሲሆን ሌላኛው አብራሪ ደግሞ " አኔ አላቋረጥኩትም " ሲል ይደመጣል።

በህንዱ የአውሮፕላን አደጋ በተአምር ከተረፈው አንድ ሰው በስተቀር ሌሎች ተሳፋሪዎች እና የበረራው አባላት ሁሉ መሞታቸው ይታወሳል።

መረጀው ከቢቢሲ የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" መሬታችን ለቀማኛ አንሰጥም ፤ ህይወታችን ለመሬታችን እንክፍላለን " - የማይቅነጣልና የቀይሕ ተኽሊ ነዋሪዎች

➡️ " ህዝብ ያልተቀበለው ባለሃብት አናስተናግድም ፤ የህዝቡ ጥያቄ ተቀብለን እርምጃ ወስደናል" - የወረዳዎቹ አመራሮች


በትግራይ ክልል ማእከላዊ ዞን በመቶዎች የሚቆጠሩ የማይቅነጣልና የቀይሕ ተኽሊ ተምቤን ወረዳ ነዋሪዎች " አከባቢያችንን ይበክልብናል ! በራሳችንና በእንስሶቻችን ህይወት ላይ አደጋ ያስከትልብናል " ያሉት ተግባር ተቃወሙ።

ተቃውሟቸው የመኪና መንገድ እስከ መዝጋት የደረሰ ነው።

ነዋሪዎቹ ቅዳሜ ሐምሌ 6/2017 ዓ.ም ባሰሙት ተቃውሞ ' ወርዒ ' ተብሎ በሚጠራው ወደ ተከዜ የሚፈስ ታላቅ ወንዝ ላይ የተጀመረው ህገ-ወጥ የወርቅ ማዕድን የማጣራት ተግባር ተቃውመዋል።

ነዋሪዎቹ ባሰሙት የተቃውሞ ድምፅ
- መሬታችን አንሰጥም !!
- ለመሬታችን ይቀላል አንገታችን !!
- ወንዛችን በአደገኛ ኬሚካል አይበከልም !!
ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ሐምሌ 7/2017 ዓ.ም ወደ ወረዳዎቹ አመራሮች ደውሎ በሰጡት ቃል የህዝቡ ጥያቄ ልክ መሆኑ በመቀበል የአከባቢው ህዝብ ሐምሌ 6/2017 ዓ.ም በቁጣ ተነሳስቶ " ለሰዓታት የመኪና መንገድ ዘግቶ ነበር " ብለዋል።

" ህዝብ ያልተቀበለው ልማትና ባለሃብት የመንግስት አመራር አያስተናግድም " ያሉት አስተዳዳሪዎቹ " ለህዝብ ቁጣ መነሻ የሆነው በወንዝ ዳር የወርቅ ማዕድን የማጣራት ስራ በተሳተፈው ባለሃብት ላይ እርምጃ ተወስዷል " ብለዋል።

" ባለሃብቱ ለስራ ያሰማራቸው ማሸነሪዎች ከአከባቢው እንዲያነሳና ስራው እንዲያቆም ፈጣን አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል " ሲሉ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በትግራይ ከጦርነቱ በኋላ በተለይ ደግሞ በሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ከህገ-ወጥ የወርቅ ማዕድን ስራ ጋር ተያይዞ እስከ ሞት የሚያደርሱ ግጭቶችና ችግሮች በመከሰት ላይ መሆናቸውን መረጃ መስጠታችን ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ሥራን በክብር
ግብርዎን በቴሌብር!


ከሥራዎ ገበታ ሳይነሱ ምቾትዎ እንደተጠበቀ ባሉበት ሆነው ግብርዎን በቀላሉ በቴሌብር ይክፈሉ!

👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_SuperApp ወይም *127#

ቴሌብር ሱፐርአፕ ➡️ ክፍያ ➡️ ግብርና የመንግሥት አገልግሎት ➡️ የግብር ክፍያ


ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#TaxPayment
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

በአዲስ አበባ በፒኤስጂ እና ቼልሲ መካከል የተደረገውን የዓለም የክለቦች ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ በዲኤስቲቪ ሲመለከቱ የነበሩ ደጋፊዎች በነበሩበት ሆቴል በተፈጠረ ግጭት የሰው ህይወት አለፈ።

ትላንት ምሽት በአሜርካ ኒው ጀርሲ በሚገኘው ሜትላይፍ ስታዲየም በፒኤስጂ እና ቼልሲ መካከል የተደረገውን የዓለም የክለቦች ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ " ለቡ " አካባቢ በሚገኝ ሆቴል ውስጥ በዲኤስቲቪ እየተመለከቱ በነበሩ ተመልካቾች መካከል በተፈጠረ ግጭት የአንድ ለጋ ወጣት ህይወት አልፏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በለቡ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በመገኘት የሟቹ ወጣት የቀብር ስነስርዓት ሲፈፀም ተመልክቷል።

በቀብር ስነስርዓቱ ላይ የተገኙ የሟቹ ወዳጆች ፣ ጓደኞች " አሟሟቱ እጅግ የሚያሳዝን ነው " ያሉ ሲሆን " ግለሰቡም ተይዟል " ብለዋል።

" እስከ ምሽት 3:00 ሰአት ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር ካመሸ በኋላ ከጓደኞቼ ጋር ትንሽ ልዝናና ብሎ ሆቴሉ እንደገባ ነው ክስተቱ የተፈጠረው " ሲሉ ተናግረዋል።

በአሟሟቱ ቤተሰቦቹ እጅግ ከፍተኛ ሀዘን ውስጥ እንደሚገኙ ለመመልከት ችለናል።

" ወጣቱ ከኳስ ስሜታዊነት መቆጠብ ወይም የእግር ኳስ ጨዎታዎችን ተሰባስቦ ከማየት መቆጠብ አለበት ካልሆነ ግን የቤተሰብን ሀዘን ማብዛት ነው " ሲሉ ያነጋገርናቸው ለቀስተኞች ተናግረዋል።

" ወጣቶች እባካችሁ ለቤተሰቦቻችሁ ሀዘን አታብዙ፣ ሁሉን በማስተዋል አድርጉ፣ ማታ ማታ አታምሹ፣ በአጭሩ እየተቀጫችሁ ሃዘናችንን አታብዙት " የሚሉ እና ሌሎች ልብ የሚነኩ ሃሳቦች ሲሰነዘሩ እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ በስፍራው ተገኝቶ ተመልክቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በስልክ ቃላቸውን የሰጡ አንድ እናት ሟቹን ወጣት እንደሚያውቁት ገና በ22 ዓመቱ በተፈጠረው ፀብ እንደተቀጠፈ ገልጸዋል።

" በውጭ ኳስ ምክንያት የለጋ ወጣት ህይወት መጥፋቱ እጅግ ያሳዝናል። ሁሉም ወጣቱ ከስሜታዊነት መራቅ አለበት፣ የሚመለከታቸው አካላትም እንዲህ ያለው ነገር እንዳይፈጠር የራሳቸውን ድርሻ መወጣት አለባቸው " ሲሉ እናታዊ መልዕክታቸውን በሀዘን ስሜት አስተላልፈዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ 80 ግለሰቦች ላይ ክስ መመስረቱ ተነገረ።

‎የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ  በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት ከ116 ግለሰቦች ላይ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሞባይል ባንኪግ በማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩ 80 ግለሰቦች ላይ ወንጀል ምርመራ በማጣራት ለፌደራል ዐቃቤ ህግ በማስተላለፍ ክስ እንዲመሰረት ማድረጉን አመልክቷል።

‎ተከሳሾቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ከሌሎች የግል ባንኮች የሚደውሉ በማስመሰል እንዲሁም የኮምፒውተር ስርዓትን በመጠቀም አሳሳች መረጃዎችን በማሰራጨት ወንጀሉን እንደፈጸሙ ፖሊስ ገልጿል።

‎የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የቀረበው ክስ እንደሚያብራራው፣ ተጠርጣሪዎቹ ማንነታቸውን በመሰወር፣ ሀሰተኛ ሰነዶችን እና መታወቂያዎችን በማዘጋጀት እና በመጠቀም የተበዳዮችን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው  ማዋላቸው በምርመራ ተረጋግጧል።

‎በተጠርጣሪዎቹ ላይ የቀረበው ክስ በዋናነት በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ እና የኮምፒዩተር ወንጀል አዋጅ ቁጥር 958/2008ን እንዲሁም የብሄራዊ የክፍያ ስርዓት አዋጅ ቁጥር 718/2003ን የተላለፉ መሆናቸውን ይገልጻል።

‎ለወንጀል ድርጊቱ ማስፈጸሚያነት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ ፦
- በርካታ የባንክ አካውንቶች፣
- የሞባይል ቀፎዎች፣
- ሲም ካርዶች እና ኮምፒውተሮች የተያዙ ሲሆን፣ ጉዳዩን ለማጣራት ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።

ፖሊስ ፥ ህብረተሰቡ ከማያውቋቸውና አጠራጣሪ ከሆኑ የስልክ ጥሪዎችና መልዕክቶች ራሱን እንዲጠብቅ አሳስቧል።

(በክሱ ከተጠቀሱት ተጠርጣሪዎች መካከል የተወሰኑት ስም ዝርዝራቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Ethiopia🇪🇹

" ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ የሚያደርጉ የአሜሪካ ፓስፓርት የያዙ ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ የሌሎች ሃገራት  ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች የኢትዮጵያን ቪዛ ለማግኘት ወደ አገራችን ሲመጡ ከተፈቀደላቸው የቆይታ ጊዜ በላይ በሀገራችን ሕግ መሠረት ቅጣት የሚያስከትል በመሆኑ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ ለማሳሰብ እንወዳለን " - አምባሳደር ነብያት ጌታቸው

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#MoE
#NationalExam🇪🇹

ትምህርት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ  " ባለፉት ሶስት አመታት በተወሰነ መልኩ ያጋጥሙ የነበሩ የጸጥታ ችግሮች፣ የፈተና ስርቆት ሙከራዎች፣ የፈተና ስርዓትና አስተዳደር የዲሲፒሊን ግድፈቶች በዘንድሮው አመት ቀንሰው ተገኝተዋል " ብለዋል።

ለዚህም " የበይነ መረብ የፈተና ሽፋን በአንድ አመት ውስጥ በአራት እጥፍ ማደጉ፤ የፈተና ግብረ ሀይሉ ያልተቆጠበ ጥረት፤ እንዲሁም ተማሪዎች ሰርቶ ውጤት ማምጣት አማራጭ የሌለው መፍትሄ መሆኑን መገንዘባቸው " ምክንያቶች ናቸው ሲሉ ገልጸዋል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው " ፈተናው በ4 ዙሮች እንዲሠጥ ነው የተደረገው። በአራቱም ዙሮች የተሰጡ ፈተናዎች ተቀራራቢ (አቻ) ናቸው " ብለዋል።

በ2017 የትምህርት ዘመን በአጠቃላይ ከተመዘገቡ ተፈታኞች 608,742 መካከል 581,905 (95.6%) ፈተናውን እንደወሰዱ አመልክተዋል። ከነዚህም ውስጥ 134,828 (23.2%) በበይነ መረብ ብቻ የተፈተኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በአማራ ብሔራዊ ክልል ያሉ እና የተወሰኑ የህግ ታራሚዎች በድምሩ 4,966 ተፈታኞች ከነሐሴ
26-28/2017 ዓ/ም በሁለተኛ ዙር የተዘጋጀላቸውን ፈተና በወረቀት እንደሚወስዱ አመልክተዋል።

#MoE

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

" ዛሬ ወሬ የለም " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ

የሃይማኖት አባቶች ልዑክ በመቐለ !


ከአዲስ አበባ ተነስቶ በጥዋቱ ትግራይ ክልል መቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ የደረሰው የሃይማኖት አባቶች ልዑክ ከሁሉም የሃይማኖት ተቋማት የተወጣጣ ሲሆን አጠቃላይ ልዑኩ ከ20 በላይ አባላት አሉት።

የሰላም ልኡኩ ከአውሮፕላን ማረፍያ በቀጥታ ወደ መቐለ ፕላኔት ሆቴል አዳራሽ በማመራት በፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ከሚመራው የጊዚያዊ አስተዳደሩ የካቢኔ አባላት ጋር #በዝግ ተወያይቷል።

ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጄነራል) ከሰላም ልኡካኑ ጋር የነበራቸውን ቆይታ አጠቃልለው ሲወጡ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የሚገኙባቸው የጋዜጠኞች ቡድን መረጃ ፍለጋ ተጠግተው ነበር።

ፕሬዝዳንቱ በሳቅ ታጅበው " ዛሬ ወሬ የለም " በማለት ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

የሰላም ልኡኩ በሆቴሉ ጥቂት ደቂቃዎች እረፍት ወስዶ መልሶ በተመሳሳይ አዳራሽ ከትግራይ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ተወካዮች ጋር ተወያይቷል።

በዚሁ ወቅት በቦታው ላይ የነበሩ ጋዜጠኞች ውይይቱን ለመከታተል ጥያቄ ቢያቀርቡም መከታተል ይቅርና አዳራሹ ውስጥ እንዳይዘልቁና ፎቶም እንዳያነሱ ተከልክለዋል።

ከሰዓት በኃላ ከውይይቱ ተሳታፊዎች በተገኘው መረጃ የሰላም ልኡካኑ በመጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ተፈናቃዮች ጎብኝተው የማወያየት ፕሮግራም የነበራቸው ቢሆንም ባልታወቀ ምክንያት ይሄ ፕሮግራም ሳይካሄድ ቀርቷል።

የሰላም ልኡኩ ቀጥሎ ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ነው የተወያየው። ውይይቱ እንደ ጠዋቱ
#በዝግ መካሄዱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተረድቷል።

የድርጅቱ / የህወሓት ልሳን የሆነው የወይን ጋዜጣ ጋዜጠኞችም ጭምር ወደ ስብሰባው አዳራሽ እንዳይገቡ ተከልክለው ነው ውይይቱ የተካሄደው።

ከአዲስ አበባ የተጓዘው የሰላም ልኡክ ያካሄዳቸው የውይይቱ ርእሰ ጉዳዮች አልታወቁም። ከግምት ባሻገር የተሰጠ ይፋዊ መረጃ የለም። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ የሰላም ልኡኩ ቀኑን ሙሉ ከተለያዩ አካላት ጋር ያካሄደውን ውይይት በማስመልከት የሚሰጥ ጋዜጣዊ መግለጫ ይኖር እንደሆነ ለጊዚያዊ አስተዳደሩ የሚድያ ዴስክ ጠይቆ ያገኘው አመርቂ መልስ የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

ፎቶ፦ ትግራይ ቴሌቪዥን

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ኮደርላብ የ2025 የክረምት ካምፕን ይቀላቀሉ - ተማሪዎችን እናበቃ!

የኮደርላብ 2025 የክረምት ካምፕ ተማሪዎችን ዲጂታል ችሎታዎች፣ ኮድ ማድረግ፣ ሮቦቲክስ፣ የwebsite development እና ሌሎችንም ለማስተማር ዝግጅቱን ጨርሷል!

🚀 ከ6 እስከ 18 አመት ለሆኑ ተማሪዎች ክፍት ነው።

📅 የሚፈጀው ጊዜ፡- 4 ሳምንታት project based learning ( games , animations , python projects and website development)

🎓 የፕሮጀክት ማሳያዎችን፣ የቡድን ስራን እና የምስክር ወረቀቶችን ያካትታል

ክፍያ ለአጠቃላይ 4 ሳምንት ስልጠና 6000 Birr

📲አሁኑኑ በhttps://forms.gle/HcjfaWrmC9PWmzGM7 ይመዝገቡ
ወይምበ+251907945085 ይደውሉልን

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

በ2018 ዓ.ም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የጥራት ቁጥጥር እንደሚጀመር ታውቋል።

የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ በመጪው አመት 2018 ዓ.ም በመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ የጥራት ቁጥጥር እንደሚጀምር አስታወቀ፡፡

የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ በአሁን ወቅት በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ እየተካወነ ያለው ዳግም ምዝገባና ምዘና ስራ ሲጠናቀቅ ይኸው እንቅስቃሴ በመንግስት ኮሌጆች፣ የማሰልጠኛ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች ላይም በቀጣዩ አመት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

አቶ ውብሸት ታደለ በዝርዝር ምን አሉ ?

" አሁን እየተከናወነ ያለውን የመጀመሪያው ዙር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ምዝገባና ግምገማ እንደጨረስን፣ በሁለተኛውና በሶስተኛው ዙር የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን እንመዘግባለን፣ እንገመግማለን፡፡ በፌደራልና በክልሎች የተከፈቱ ኮሌጆችና የማሰልጠኛ ተቋማት አሉ፡፡ መጀመሪያ የምናየው እነሱን ነው፡፡ ቀጥለን ደግሞ ሁሉንም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን እናያለን፡፡

እስካሁን የግል ተቋማት ላይ ያተኮርነው፣ እዚህ ዘርፍ ላይ የነበረው ችግር ሰፊ ስለሆነ ነው፡፡ ያለንን የሰው ሀይልና ሀብት ወደዚህ ዘርፍ በማዞር ቅድሚያ ሰጥተናል፡፡ ሁሉንም አንድ ላይ ማየት አንችልም፡፡ አሁን የግሎቹን ተቋማት ካጠናቀቅን በኋላ፣ ወደ መንግስት ትምህርት ተቋማት ግምገማ እንገባለን፡፡

የመንግስት የትምህርት ተቋማት በመሰረተልማት በኩል ችግር የለባቸውም፡፡ የራሳቸው ህንፃና ግቢ አላቸው፡፡ ስለዚህ እነሱ ጋ ትኩረት የምናደርገው ጥራት ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ ፕሮግራሞቹ/ትምህርቱ በበቂ መምህራንና አኳሀን መሰጠቱን እናያለን፡፡ አካዳሚያዊ የድርጊት መርሀግብራቸው ትክክል መሆኑን እንፈትሻለን፡፡

የተገቢነትና አስፈላጊነት ጥያቄ የሚነሳባቸው፣ ዝም ብለው ያለ በቂ ጥናት የሚከፈቱ ፕሮግራሞች አሉ፡፡ የትምህርት ግብአት እና የላቦራቶሪ ቁሳቁሶች፣ እንዲሁም የዳታ ማዕከላቸው ይታያል፡፡ ለተማሪዎችና ለአስተማሪዎች የሚቀርቡት አገልግሎቶች ደረጃቸውን የጠበቁ ናቸው ወይ የሚለውን እናያለን፡፡

ቀደም ብለው የተቋቋሙት ነባሮቹ ዩኒቨርሲቲዎች የዚህ አይነት ችግር ላይኖርባቸው ይችላል፡፡ አዳዲሶቹ ዩኒቨርሲቲዎች ግን በነዚህ መስፈርቶች በኩል ክፍተት ይኖሩባቸዋል፡፡

በአጠቃላይ ግን ጥራትን እናምጣ ካልን፣ ሁሉንም የመንግስት ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎችን መፈተሽ አለብን፡፡ በዳግመ ምዝገባችን፣ በተቋማቱ የሚሰጡትን ሁሉንም ፕሮግራሞቻቸውን እናያለን፡፡ ፋይሎቻቸውን እንዲያስገቡ አድርገን እያንዳንዱን ፕሮግራም እንመዝናለን፡፡ አያስፈልጉም የምንላቸውን ፕሮግራሞች እንዲዘጉ፣ ያስኬዳሉ የምንላቸውን ደግሞ እንዲያስቀጥሉ እናደርጋለን፡፡

የመንግስት ተቋማትን ከግሎቹ በበለጠ ጠንከር ያለ ምዘና እናደርጋለን፡፡ ጠበቅ አድርገን ለማየት እንሞክራለን፡፡ የግሎቹን እንደጨረስን፣ በየክልሉ ያሉትንና በፌደራል ደረጃም ያሉትን ኮሌጆችና የማሰልጠኛ ተቋማትን እናያለን፡፡ ከዛም ወደ ዩኒቨርሲቲዎች እንሔዳለን፡፡ ይህ ስራ በ 2018 ዓ.ም የሚጀመር ይመስለኛል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

Addis Ababa University

Announcement of Professional Training Programs

Python Programming + Data Analytics and Visualization

By: Addis Ababa University,
College of Technology and Built Environment,
School of Electrical & Computer Engineering

Registration Deadline: July 24, 2025

Training Starts on: July 26, 2025

Online Registration Link: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6

Telephone: +251-913-574525/ +251-940-182870

Email: sece.training@aait.edu.et

For more information: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6  

Telegram Channel: /channel/TrainingAAiT

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" እሳተ ገሞራው እንደፈነዳ መረጃው ደርሶናል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረ በጣም ከፍተኛ አቧራ እየወጣ ነው " - ሰመራ ዩኒቨርሲቲ

በአፋር ክልል የኤርታሌ እሳተ ገሞራ እየፈነዳ መሆኑን ሰመራ ዩኒቨርሲቲና አንድ የዘርፉ ባለሙያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የጂዖሎጂ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ኖራ ያኒሚኦ በሰጡን ገለጻ፣ እሳተ ገሞራው መፈንዳቱን ከአካባቢው ማህበረሰብ ማረጋገጣቸውን ገልጸው፣ ለነዋሪዎቹ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፈዋል።

" እሳተ ገሞራው እንደፈነዳ መረጃው ደርሶናል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረ በጣም ከፍተኛ አቧራ እየወጣ ነው " ያሉት ተመራማሪው፣ " በአካባቢው በሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጉዳት ሊያስከትል ስለሚችል ቢያንስ እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ ማራቅ የሚቻልበት መንገድ ቢፈጠር ጥሩ ነው " ሲሉ አስገንዝበዋል።

" ኤርታሌ በቀን በጣም ብዙ ሰው የሚጎበኘው ቦታ ስለሆነ ወደዚያ የሚሄዱ ጎብኝዎች ጥንቃቄ ያድርጉ፣ ምክንያቱም የሚፈጠረው ነገር አይታወቅም " ሲሉም ተናግረዋል።

" ከዚህ በፊት ኤርታሌ ላይ እንደዚህ አይነት ነገር የተለመደ አልነበረም፣ እሳት ገሞራ ከመፍሰስ ውጭ፣ አሁን ግን ብናኞቹ ወደሰማይ እየወጡ ስለሆነ ጉዳትም ሊያስከትል ይችላል " ያሉት አቶ ኖራ፣ ክስተቱ እስከሚረጋጋ ድረስ ወደ አካባቢው ቀርበው ፎቶ የሚያነሱ ሰዎች እየተስተዋሉ በመሆኑ ከዚህ ተግባር እንዲታቀቡ አሳስበዋል።

አክለው፣ " አንድ ልጅ በጣም ተጠባብሶ ፎቶ እያነሳ ነበር " ሲሉ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቅናቸው አንድ የዘርፉ ባለሙያ በበኩላቸው፣ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታው እንደተከሰተ ገልጸው፣ ጉዳዩን ይበልጥ ለማጣራት በውጭ ሀገራት ከሚገኙ ባለሙያዎች ጋር እየተነጋገሩ እንደሆነ፣ መረጃውን አጣርተውም ተጨማሪ ማብራሪያ እንደሚሰጡን ነግረውናል።

ግን እሳተ ገሞራው ተከስቷል መባሉ ትክክል ነው ? ስንል  ላቀረብንላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽም "እውነት ነው። እየፈነዳ እንደሆነ ሰምቻለሁ፣ ፎቶግራፎችም ደርሰውኛል " ብለዋል።

" ዛሬ ምሳ ሰዓት አካባቢ እንደተከሰተ ነግረውኛል፤ ከአፋር ክልልም ደውየ አጣርቻለሁ " ብለው፣ " የሳተላይት መረጃዎችን እያጠናከርን ነው " ሲሉም ተናግረል።

በአካባቢው ላለፉት በርካታ ዓመታት ተደጋጋሚ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ያስተናገደ ሲሆን፣ በተለይም ከ2017 ዓ/ም ጀምሮ ከፍተኛ ፍንዳታዎችን እንደታዩ፣ የመሬት መንቀጥቀጥ በስፋት እንደተከሰተ ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲያሟሉዋቸው የተቀመጡት መስፈርቶች በጣም ዝቅተኛ ናቸው ! "  - ባለስልጣኑ

" የግል ትምህርት ተቋማትን ስጋት ላይ የጣለው አዲሱ መመሪያ ምን ይላል " በሚለው ከዚህ ቀደም በቀረበው ዘገባችን፣ የዘርፉ ተዋናዮችን ቅሬታዎች አቅርበናል፡፡

የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ደግሞ ለቅሬታዎቹ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡

የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ፣ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ በትምህርት ተቋማቱ የዳግመ ምዝገባና የመስክ ምልከታው የሚታዩት ዋና ዋና የሚባሉት መስፈርቶች ናቸው ብለዋል፡፡ የትምህርት ተቋማቱ፣ ትውልድን ለማስተማር በትንሹ ምን ማሟላት አለባቸው የሚለውን ነው የምናየው በማለትም ተናግረዋል፡፡

አቶ ውብሸት ታደለ በዝርዝር ምን መለሱ ?

" አንድ የትምህርት ተቋም ስናስብ የራሱ የሆነ ድባብ ሊኖረው ይገባል፡፡ አንዳንዶቹ ተቋማት የሆነ ህንፃ ላይ አንድና ሁለት ወለል ብቻ ተከራይተው ከቡቲኩና ከካፌው ጋር እየተጋፉ ነው የሚሰሩት፡፡ ይህ ትክክል አይደለም፡፡ የኮሌጅነት ቅርፅ እንዲኖራቸው የሚያስችሉ መስፈርቶች መቀመጥ አለባቸው፡፡ ግን ደግሞ የተቀመጡትን ሁሉንም መስፈርቶች በሙሉ እንተግብር አላልንም፡፡ በጣም መሰረታዊ የሚባሉትን ብቻ እንዲያሟሉ ነው እያደረግን ያለነው፡፡ በጣም በዝቅተኛ መስፈርት ነው እየተመዘኑ ያሉት፡፡ እነዚህን ዝቅተኛ መስፈርቶችስ ምን ያህሎቹ ተቋማት ያሟላሉ የሚለውን ደግሞ ሪፖርቱ ሲለቀቅ የምናየው ይሆናል፡፡   

መስፈርቶቹ ምንድናቸው ካልን አንደኛው የመማሪያ ህንፃን የሚመለከት ነው፡፡ ከአምስት ፕሮግራሞች በላይ ያላቸው ተቋማት የራሳቸው ግቢና ህንፃ እንዲኖራቸው ተደንግጓል፡፡ ተከራይተውም ቢሆን፣ የራሳቸው ግቢና ህንፃ ይኑራቸው፣ ከሌሎች የንግድ ስራዎች ጋር ሊዳበሉ አይገባም ነው፣ ይህ አንድ መሰረታዊ መስፈርት ነው፡፡

ግን ደግሞ በአብዛኞቹ ኮሌጆች ዘንድ መስፈርቶቹን ለማሟላት ስለሚቸገሩ ለድርድር እያቀረብናቸው ነው፡፡ ለምሳሌ ከአምስት ፕሮግራሞች በታች የሚሰጡ ጀማሪ ባለሀብቶች፣ የራሳቸው ህንፃና ግቢ እንዲኖራቸው አናስገድድም፡፡ እነሱ ከሌሎች ቢዝነሶች ጋር ተዳብለው መስራት ይችላሉ ብለናል፣ እስኪጠናከሩ ድረስ፡፡ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ተረድተን ነው በዚህ ደረጃ መስፈርቱን አውርደን እየሰራን ያለነው፡፡ መስፈርቶቹ በምንም መልኩ ሊሟሉና ሊተገበሩ አይችሉም የሚባሉ አይደሉም፡፡ 

ሁለተኛው መስፈርት ለማስያዣነት የሚያስቀምጡት ገንዘብ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር፣ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ መቼ ገብተው መቼ እንደሚወጡ አይታወቅም ነበር፡፡ በተለይም አወጣጣቸው ስርዓት ስላልነበረው፣ መቼ እንደወጡ እንኳን ማወቅ አይቻልም ነበር፡፡ ይህን ስርዓት ለማስያዝ ነው 500 ሺህ ብር ማስያዣ እንዲያስቀምጡ የጠደነገገው፡፡ ከእንግዲህ፣ ማንኛውም ተቋም ከገበያው ሲወጣ፣ አወጣጡ ስርዓት ያለው ይሆናል፣ የጠራ መረጃም ይኖረናል ማለት ነው፡፡

ሶስተኛው መስፈርት የሰው ሀይሉን የሚመለከት ነው፡፡ ከበፊቱ መመሪያ ብዙም የተጨመረ ነገር የለውም፡፡ አንድ ነገር ነው ብቻ ነው ያሻሻልነው፡፡ የማስተርስ ተማሪ ፒኤችዲ ዲግሪ በሌለው ረዳት ፕሮፌሰር መሰልጠን የለበትም የሚል ነው፡፡ የአስተማሪው የትምህርት ደረጃ ከሚያሰለጥነው የትምህርት ደረጃ አንድ እርከን ከፍ ይበል ነው፡፡ ለምሳሌ የዲግሪ ተማሪ ማስተርስ ዲግሪ በያዘ መምህር፣ የማስተርስ ዲግሪ ተማሪ ደግሞ የዶክትሬት/ፒኤችዲ ዲግሪ ባለው መምህር መሰልጠን አለባቸው፡፡ አሁን ግን ፒኤችዲ ዲግሪ ሳይኖራቸው ረዳት ፕሮፌሰር የሚል ማዕረግ ያላቸው አስተማሪዎች ናቸው ከነሱ ጋር አቻ የሆነን የማስተርስ ዲግሪ ስልጠና የሚሰጡት፡፡ ማስተርን በማስተር ማለት ነው፡፡ ይህ ሊሆን አይችልም ብለናል በመስፈርቱ፡፡

ከዚያ ውጭ፣ በግል ኮሌጆች ድጋፍ ሰጪ ሰራተኛውም፣ የአስተዳደር ሐላፊዎችም ፒኤችዲ ዲግሪ ይኑራቸው አልተባለም፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ ዲኖቻቸው/ የተቋማቱ ሐላፊዎች እንኳን ፒኤችዲ ከሌላቸው ብለን ጥብቅ ቁጥጥር አናደርግም፣ እውነት ለመናገር፡፡ ትኩረታችን አስተማሪዎቹና ትምህርቱ ላይ ነው፡፡ በሒደት ደግሞ ወደ ስታንዳርዱ እናስገባቸዋለን የሚል እሳቤ ነው ያለን፡፡

አራተኛው መስፈርት መምህራንን መዋዋስ በተመለከተ ነው፡፡ ሁሉንም ትምህርቶች በትርፍ ሰዓት/ፓርታይም መምህር አታስተምሩ ነው እንጂ ሁሉም አስተማሪዎቻችሁ የሙሉ ሰዓት ተቀጣሪዎች/ፉልታይም መምህራን ይሁኑ አላልንም፡፡ ትምህርት ብዙ ማንበብ፣ መጣርና ማማከር የሚያስፈልገው፣ የምርምር ስራ የሚያስፈልገው ስራ ነው፡፡ ይህንን ሁሉ ስራ የሆነች ሰዓት ላይ ብቻ አስተምሮ በሚሔድ በትርፍ ሰዓት ብቻ በሚሰራ መምህር ልታስኬደው አትችልም፡፡ መምህሩ ሶስት አራት ቦታ ላይ ከተጠመደ እንዴት ነው የምርምር ስራውን የሚሰራውና የሚያሰራው፡፡ የተወሰኑ የራሳችሁ ቋሚ መምህራን ይኑሩዋችሁ፣ ሌሎችን ደግሞ በፓርታይም መምህራን መሸፈን ትችላላችሁ ነው ያልነው፡፡ 

አምስተኛው መስፈርት፣ አንድ ተቋም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ቢያንስ 25 በመቶ ካላሳለፈ ይዘጋል የሚል ነው፡፡ አንድ ተቋም አራት አመት ካስተማራቸው 100 ተማሪዎች ቢያንስ 25ቱን ማሳለፍ ካልቻለ መዘጋት ነው ያለበት፡፡ ተማሪዎችን ካላሳለፈ እኮ እያስተማረ አይደለም፣ የሀገር ሀብት እያባከነ ነው ያለው፡፡

አራት አመት ሙሉ ካስተማራቸው ተማሪዎች 75 ከመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች ከወደቁ፣ ያንን ሁሉ ሀብት ያባከነው ለምንም ነው ማለት ነው፡፡ ያ ተቋም ለምን ይቀጥላል፡፡እንዳይዘጋ ከፈለገ በደንብ አሰልጥኖ ተማሪዎቹን አብቅቶ የመውጫ ፈተናን ማሳለፍ ነው ያለበት፡፡ እንደገና ደግሞ 25 በመቶ ካላሳለፈ የሚባለው በኮሌጅ ደረጃ ሳይሆን በፕሮግራም ደረጃ ነው፡፡ ለምሳሌ 25 በመቶ ያላሳለፈው የአካውንቲን ትምህርት ከሆነ፣ ያ ትምህርት ነው የሚዘጋው እንጂ ተቋሙ አይደለም የሚዘጋው፡፡

ይህንን አሰራር ደግሞ በአንዴ ተግብሩ አላልንም፡፡ የእፎይታ ጊዜ ሰጥተናቸዋል፡፡ ይህ አሰራር የሚተገበረው መመሪያው በፀደቀበት በ 2015 ዓ.ም ትምህርት በጀመሩ ተማሪዎች ላይ ነው፡፡ ያኔ አንደኛ አመት የነበሩ ተማሪዎች በ 2019 ዓ.ም የሚመረቁ ናቸው፣ በነዚህ ላይ ህጉ ተግባራዊ ይደረጋል፡፡ ድንገት ተነስተን ዘንድሮ ቢያንስ 25 በመቶ አስመርቅ አላልንም፡፡ ለ 2019 ዓ.ም ካስተማርካቸው ተማሪዎች 25 በመቶውን ለማሳለፍ ተዘጋጅ ብሎ የቤት ስራ መስጠት የተጋነነ አይደለም፡፡ "

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" በትግራይ ላይ የሚታሰብና የሚደረግ የውክልና ግጭት (Proxy Conflict) ተቀባይነት የለውም " አሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጄነራል)።

" በዓፋር እንጂ በትግራይ ነፃ (ሓራ) መሬት ብሎ የለም " በማለትም ተናግረዋል።

ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ትላንት በመቐለ የሰማእታት ሀውልት አዳራሽ በተካሄደው 36ኛው የሰማእታት ቀን የማጠቃለያ ፕሮግራም ተገኝተው እንዳሉት " ነፃ (ሓራ) መሬት ተብሎ ትግራይ ላይ ለሚቃጣ ማንኛውም ዓይነት ጥቃት ተጠያቂዎቹ የፌደራል እና የዓፋር ክልል መንግስታት ናቸው " ሲሉ ተደምጠዋል።

" ነፃ (ሓራ) መሬት ብሎ በትግራይ የለም " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " በዓፋር ክልል ያለው የትግራይ ታጣቂ በፌደራልና በዓፋር ክልል መንግስታት እውቅና እገዛ የሚንቀሳቀስ ነው " ሲሉ ተናግረዋል። 

" በዓፋር በኩል ያሉ ታጣቂዎች ትግራይ ላይ የሚቃጡት ማንኛውም ዓይነት ጫናና ግጭት ጊዚያዊ አስተዳደሩ የፌደራልና የዓፋር መንግስታት ፍላጎት እንጂ የነሱ አድርጎ አይመለከተውም "  ብለዋል።

" እዚያ ካሉት ታጣቂዎች ያለው ማንኛውም ዓይነት ልዩነት ከውይይት ውጪ ሊፈታ አይችልም " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " የፌደራልና የዓፋር መንግስታት ጉዳዩ ሰላማዊ እልባት እንዲኖረው ማገዝ አለባቸው " ብለዋል።

" የትግራይ ቁጥር አንድ ጥያቄ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት እንዲተገበር ነው ፤ ከዚህ ውጪ የውክልና ግጭት (proxy Conflict) እንዲካሄድ የሚደረገው ጥረት ተቀባይነት የለውም የሚሳካም አይደለም " ሲሉ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ንብተራ ኦንላይን!
ሁሉንም በአንድ ጥላ ስር የሚያገኙበት!

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ

***
ይሠሯል ከልብ እንደ ንብ!

#Nib #nibmobilebanking #NibQR #nib #nibtera #nibbank

Facebook  / Instagram / linkedin / nibinternationalbank6204">X / nibinternationalbank6204">Youtube / nibinternationalbank">Tiktok / Website

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ለወላጆች

ፋይዳ ለትምህርት ቤት አስፈላጊ መታወቂያ ነው።

ወላጆች ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ያልተመዘገቡ ልጆቻቸውን በትምህርት ቤታቸው ሆነ በማንኛውም የፋይዳ ምዝገባ ባለበት ቦታ (ቴሌና ባንክን ጨምሮ) ወስደው ማስመዝገብ እንደሚችሉ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽ/ቤት አሳውቋል።

በተለይ ከ10 ዓመት በታች ላሉ ህፃናት ከጣቶቻቸው ማነስ እና በትግስት ካለመቀመጥ ጋር ተያይዞ በቀላሉ መረጃቸውን ማሽን ላይ ለመመዝገብ ዕክል ሊያጋጥም እንደሚችል ጠቁሟል።

ለተሻለ ምዝገባ ያለው አማራጭ ምንድነው ?

1. ጣቶቻቸውን ሲያስቀምጡ በስሱ ጫን በማለት አሻራ እንዲሰጡ ማድረግ። ካልተያዘም ደጋግሞ መሞከር።

2. የሚቀመጡበትን ወንበር ወደ አሻራ መስጫው ማሽን ቀርበው እንዲሰጡ ማመቻቸት።

3. ለማንኛውም ለሚያጋጥም ችግር በተጨማሪ የተመደበው የምዝገባ ባለሙያን እገዛ መጠየቅ።

ጽ/ቤቱ " ከፋይዳ በስልክዎ መልዕክት ካልደረሰዎ በስተቀር ከአንድ ግዜ በላይ መመዝገብ አይቻልም " ሲል አስገንዝቧል።

#ፋይዳለተማሪ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

Freelance Ethiopia Afriwork

ስልካችሁን ብቻ በመጠቀም ከቤታችሁ በመሆን ለስራ አፕላይ ያርጉ! ✨

✅ ከ70 ሺ በላይ ቅጥሮችን ያሳካ
✅ ከ15 ሺ በላይ ቀጣሪዎች የሚገኙበት
✅ ከ300 ሺ በላይ ደንበኞች ያሉት

አሁኑኑ ቻናላሽንን በመቀላቀል ➡️➡️ /channel/+bOAJV6PZV9s2ZjRk ወይም afriworket.com ላይ በመሄድ ለርሶ እና ለቤተሰቦ የለውጥ መጀመሪያ ይሁኑ!

የህልሞ ስራ ከኛ ጋር!

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ተቀጣሪው ሰራተኛ በቀን አንድ ጊዜ በልቶ መዋል አልቻለም ምክንያቱም በርካታ ወጪዎች አሉበት ፤ ... ህክምና ሄዶ መታከም የማይችልበት ሁኔታ ላይ ደርሷል !! " - ኢሰማኮ

➡️ " ልማት ያለ ሰው ሰው ያለ ልማት ሊኖሩ አይችሉም !! "

🔴 " የኢትዮጵያ ሰራተኞች ኑሮን አልቻሉም፤ ቋሚ ኮሚቴው ፍቃደኛ ከሆነ ከስራ ሲውጡ ፌስታል ይዘው ሆቴል አካባቢ ቆመው የሚለምኑ ሰራተኞችን አብረን ማየት እንችላለን !! "

የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን (ኢሰማኮ) ፓርላማው ፍቃደኛ ከሆነ በስራ መውጫ ስዓት ፌስታል ይዘው ከሆቴል ተመላሸ ምግብ የሚለምኑ ሰራተኞች መኖራቸውን ማሳየት እንደሚችል ተናገረ፡፡

ይህን ያለው በቅርብ ይጸድቃል ተብሎ በሚጠበቀው የፌዴራል ገቢ ግብር ማሻሽያ ረቂቅ አዋጅ  ላይ ዛሬ/በህ/ም/ቤት የፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት ባካሄደበት ወቅት ነው፡፡

የኢትዮጵያ የሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን ዋና ፕሬዘዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ምን አሉ ?

" ከገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከሰራተኛው ለመቁረጥ የቀረበው ሃሳብ ውስብስብ የዋጋ ንረትን እና የድህነት መጠንን ያላገናዘብ ከመሆኑም በላይ ማጭበርበር ሳይኖር በአግባቡ ከደሞዙ ግብር የሚከፍለውን ሰራተኛ ከችግር የሚውጣ ሳይሆን ችግር ውስጥ የሚከት ነው።

ሰራተኛው በቀን አንድ ጊዜ በልቶ መዋል አልቻለም ምክንያቱ ደግሞ በርካታ ወጪዎች ስላሉበት ነው።

ተቀጣሪው ሰራተኛ ህክምና ሄዶ መታከም የማይችልበት ሁኔታ ላይ ደርሷል። እውነት ለመናገር አንድ ሰው በ5 ሺ ብር ደሞዝ ቤት ኪራይ ይከፍላል ፣ ይበላል ? ፣ ልብስ ይለብሳል ? ፣ ህክምና ይሄዳል ?

ህክምናውን እንተው እየጸለየ ይኑር ፤ ቤት ኪራይውንም እንተወው በበረንዳ በሰዎች ላይ በጥገኝነት ይኑር ግን በቀን አንድ ጊዜ እየበላ መኖር የለበትም ወይ ?

አንድ ድርጅት ከትርፉ 35 በመቶ ግብር ይከፍላል ፤ ሰራተኛውም 35 በመቶ ይከፍላል ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ?

ነጋዴውም፣ ድርጅቱም ከትርፉ ነው እኮ 35 በመቶ የሚከፍለው ሰራተኛው ግን ከትርፉ ሳይሆን ከሚበላው ላይ ነው የሚከፍለው ይህ እንዴት ነው ? እኩል የሚሆነው።

ስለሰዎች ስናስብ ልማት ለማስቀጠል ነው ልማት ያለ ሰው ሰው ያለ ልማት ሊኖሩ አይችሉም።

ስለዚህም የሰራተኛውንም ጫና የመንግስትን ዓላማ ታሳቢ ያደረገ የግብር ምጣኔ መጣል አለበት።

አሁን በማሻሻያው የግብር መነሻ 2000 ሺ ብር ሲሆን ምን ታሳቢ ተደርጎ ነው ?  አንድ ስልት ሲሰራ ሰውን ማኖር አለበት ይህ መነሻ ግን ታሳቢ አልተደረገም።

ቋሚ ኮሚቴው እንደገና ከሚመለከታቸው ሰዎች ጋር ቢመካከር ይሻላል።

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ኑሮን አልቻሉም፤ ቋሚ ኮሚቴው ፍቃደኛ ከሆነ ከስራ ሲውጡ ፌስታል ይዘው ሆቴል አካባቢ ቆመው ሲለምኑ አብረን ማየት እንችላለን። "

የገንዘብ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ፍቃዱ ሆረታ ምን አሉ ?

" አዋጁ በይድረስ ይድረስ የተዘጋጀ ሳይሆን ሁለት ዓመት ጥናት ተሰርቶበት የተዘጋጀ ማሻሻያ ነው።

2000 ብር መነሻ የተደረገበት ምክንያት የመክፈል አቅማችን ዝቅተኛ ስለሆነ ነው።

መነሻን ከዚህ ከፍ ለማድረግ ቢፈለግ አገሪቱ ያላት ገቢ አይፈቅድም ወደፊት ገቢው እያደገ ሲሄድ ግን መነሻን ከፍ ማድረግ ይቻላል።

የኑሮ ውድነቱ ግብር በመክፍል ብቻ የመጣ አይደለም። በኢትዮጵያ ብቻም ያለ ችግር አይደለም።

ከውጭ የምናስገባቸውን መዳበሪያ ፣ ነዳጅ እና መሰል ግብዓቶች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በሰዎች ላይ ጫና ይፍጥራል።

ይህን ችግር ለመፍታት ደግሞ መንግስት ደሞዝ ጨምሯል። መንግስት አቅም በፈቀደ መሰረት ድጋፍ አድርጓል።

በገቢ ግብር ላይ ያለውም ጫናውን መቀነስ ነው እንጂ ማጥፋት አይደለም። በነባሩ አዋጅ ላይ መነሳት ብናመለከት 600 ነው ወደ 2000 ያደገው በውይይት ተደርጎበት ነው።

በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና የሞያ ማህበራት ተሳትፎ የተደረገ ማሻሻያ እንጂ ዝም ብሎ የመጣ ቁጥር አይደለም።

የግብር መነሻው ከተቀጣሪ ሰራተኛ አሁን ካቀረብነው ከፍ ካለ መንግስት ከፍተኛ ገቢ ያጣል። በተለይ በክልሎች ገቢ ላይ የበረታ ጫና ያሳድራል። "

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ኢትዮጵያ🇪🇹

የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ፣ የኑሮ ውድነትን ታሳቢ በማድረግ የገቢ ግብር መነሻ ገቢ ከ2,000 ብር ወደ 5,000 ብር ከፍ እንዲል ጠንካራ ጥያቄ ቀርቧል።

ጥያቄው የቀረበው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ በፓርላማው የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ባደረገዉ ዉይይት ላይ ነው።

በአሁኑ ረቂቅ አዋጅ መሰረት፣ ከ2,000 ብር በላይ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር እንዲከፈል የሚለው ሀሳብ ቀርቧል።

ይህ የገቢ ግብር አዋጅ ከዘጠኝ ዓመታት በላይ ስራ ላይ መዋሉ የተገለጸ ሲሆን፣ አሁን በማሻሻያው ከግብር ነፃ የሚሆነው ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ በ300% በማሳደግ ወደ 2,000 ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል።

በተጨማሪም፣ ከፍተኛው የማስከፈያ መጣኔ የሆነው 35% ግብር የሚያርፍበት ገቢ ደግሞ ወደ 14,000 ብር ከፍ እንዲል ሆኗል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ፣ የአዋጁ መሻሻል መንግስት ግብር በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እንደሚረዳ ገልጸዋል።

ከግብር ከፋዩ ህብረተሰብ የሚነሱ " ግብር በዝቷል ይቀነስ " የሚሉ ሀሳቦች ሚዛናዊ በሆነ መልኩ እንደሚታዩም አክለዋል።

በውይይት መድረኩ ከተነሱት አስተያየቶች መካከል፣፦
- የገቢ ግብር መነሻው ከአምስት ሺህ ብር ጀምሮ እንዲሆን፣
- ለአካል ጉዳተኞች በተለየ መልኩ ግብር እንዲቀነስ፣
- በተለያዩ የሙያና የንግድ ዘርፎች አንፃር በደንብ እንዲታይ የሚሉ ሀሳቦች ቀርበዋል።

የመረጃው ባለቤት የካፒታል ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ከ3 ጊዜያት በላይ ሲራዘም የቆየዉ ቶምቦላ ሎቶሪ ዛሬ ይወጣል ተባለ።

የሀዋሳ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታን ለማጠናቀቅ ታስቦ ለሽያጭ የቀረበዉ ቶምቦላ ሎተሪ ከሶስት ጊዜያት በላይ ሲራዘም ቆይቶ ዛሬ በብሔራዊ ሎተሪ አደራሽ እንደሚወጣ የሀዋሳ ከተማ የሕብረተሰብ ተሳትፎ ልማት ፈንድ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ዘሪሁን ቃሚሶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።

አስቀድሞ ጥር ‎20/2017 ዓ/ም ከዚያም ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ሌላ ጊዜ ደግሞ ሰኔ 30/2017 ዓ/ም ዕጣዉ እንደሚወጣ ተገልፆ ሲራዘም የቆየዉ ሎተሪ 500 ሺህ ትኬቶች ለገበያ የቀረቡ ሲሆን 1 መቶ ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብም ዕቅድ ተይዞበት ነበር።

" ሶስቱንም ዙሮች ትኬቶቹ በበቂ ሁኔታ ስላልተሸጡና በተለያዩ አከባቢዎች የተሰራጩ የቲኬት ወረቀቶችም ተሰብስበዉ ስላላለቁ " በሚል መውጫው ሲራዘም ነበር ተብሏል።

250 ካ.ሜ ለንግድ እና 200 ካ.ሜ ለመኖሪያ የሚሆን መሬትን ጨምሮ ኩዊት ባጃጅ፣ ሞተር፣ ቴሌቪዥን፣ ፍሪጅ ዕጣ የሚወጣባቸው ሲሆኑ 14 ዕድለኞች ይታወቃሉ።

#Update ዕጣው ወጥቷል።

በዚህ መሰረት፦
‎1ኛ ዕጣ 0189833 ➡️ 250 ካሬ ለንግድ አገልግሎት የሚሆን መሬት
‎2ኛ  ዕጣ 0385625 ➡️ ለመኖሪ አገልግሎት የሚሆን መሬት
‌‎3ኛ ዕጣ 0122191 ➡️ ኪዉ ባጃጅ
‎4ኛ ዕጣ 0274157 ➡️ ባለ 3 እግር ባጃጅ
‌‎5ኛ ዕጣ 0043656 ➡️ አፓች ሞተር ሣይክል
‎6ኛ ዕጣ 0116134 ➡️ ኤል (ሊፋን) ሞተር ሣይክል
‎7ኛ ዕጣ 0176687 ➡️ ማቀዝቀዣ ፍሪጅ
‎8ኛ ዕጣ 0185323 ➡️ HP Cori i5 ላፕቶፕ
‎9ኛ ዕጣ  0367397 / 0023129 ➡️ ለሁለት ሰዎች 54 ኢንች ቴሌቪዥን
‎10ኛ ዕጣ 0480480 ፣ 0263409፣  0041937፣ 0208319፣ 0273773 ➡️ ለ5ቱ ለእያንዳንዳቸው ሞባይል ቀፎ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamliyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…
Subscribe to a channel