tikvahethiopia | Unsorted

Telegram-канал tikvahethiopia - TIKVAH-ETHIOPIA

1532594

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Subscribe to a channel

TIKVAH-ETHIOPIA

#AmazonFashion

ሙሉ ልብስ ሽያጭና ኪራይ   የአመቱ የማጣሪያ ሽያጭና ታላቅ ቅናሽ ሙሉ ልብስ(ሱፍ) ሽያጭ ከ 12 ሺ -15 ሺ ብቻ፤ በርካታ አማራጭ ስላለን ለብዛት ፈላጊዎች ለሚዜዎች ለተመራቂ ተመራቂዎች በብዙ አማራጭ አለን። በተጨማሪም የሙሉ ልብስ ኪራይም  በሌላኛው ብራንቻችን አለን።

አድራሻ: ፒያሳ downtown ህንፃ ምድር ላይ 

☎️ 0919339250 / 0911072936 /0939721321

https://t.me/joinchat/AAAAAEc8iQJX1Zjgepjq1w

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል !

በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የጭካኔ የግድያ የተከሰሱት ተጠርጣሪዎች ጥፋተኞች ተብለው የፍርድ ውሳኔ ተላለፈባቸው።

ተከሳሾቹ ለፍርድ ውሳኔ ማቅለያ ይሆነናል በማለት " የቆየ ህመም አለብን " ቢሉም የመቐለ ዓይደር ስፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል ሃኪሞች የምርመራ ማስረጃ " የቆየ ህመም የለባቸውም " ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

የመቐለ ማእላዊ ፍርድ ቤት በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ አሰቃቂ ግድያ የመጨረሻ የፍርድ ውሳኔ ውሎ ምን ይመስል ነበር ?

የተጠርጣሪ ጠበቆች ትናንት ሀምሌ 3 " ደምበኞቻችን የቆየ ህመም አለባቸው ይህንን ለማረጋገጥ የህክምና ማስረጃ ለአርብ ሀምሌ 4 እናቀርባለን " ብለው ነበር።

ፍርድ ቤቱ ይህን ተቀብሎ ለዛሬ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ቀነ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።

ዛሬ አርብ ሀምሌ 4/2017 ዓ.ም ከመንግስት ሰራተኞች የስራ ሰዓት በፊት ቤተሰብ የሚገኙባቸው የሚድያና የሴቶች መብት ተቆርቋሪዎች በፍርድ ቤቱ በራፍ ደርሰው ተሰባስበዋል።

ተከሳሾች ለውሳኔ ማቅለያ ይሆነናል ብለው የጠየቁት የህክምና ማስረጃ የቆየ ህመም እንደሌለባቸው አረጋግጧል።

ዳኞችም ይህን ካረጋገጡ በኋላ በተከሳሾች ላይ ውሳኔ ሰጥተዋል።

አንደኛና ሁለተኛ ተከሳሾች ያሬድ ገብረስላሰ በላይ እና ኣንገሶም ሃይለማርያም በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

በፍርድ ቤቱ ውሳኔ አለመርካታቸው የገለፁት አስተያየት ሰጪዎች የወንጀል ደርጊቱን ከማጠራት እስከ ምርመራና ውሳኔ ድረስ በችግሮች የተተበተበ እንደነበር በመግለፅ ማረሚያ ቤት የፍርድ ውሳኔውን በጥብቅ እንዲተገብረው ጠይቀዋል። 

" የጭካኔ ግድያው የሞት ፍርድ ያሰጥ ነበር " ያሉ ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ደግሞ " የተበዳይ ቤተሰቦች ወደ ቀጣዩ የፍርድ ቤት ይግባኝ ይጠይቁ " ብለዋል።

ከነሀሴ 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሀምሌ 4/2017 ዓ.ም የተጓዘው የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ ግድያ በዚሁ ተቋጭቷል ሲል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መረጃውን ልኳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ የእንስቷን ግድያ ከመነሻው እስከ ፍርድ ሂደቱ ሲከታተል ቆይቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

አዲሱ የዩትዩብ ሞኒታይዤሽን መመሪያ ምን ይዟል ?

ከፊታችን ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ዩትዩብ፤ ዩትዩብን ተጠቅመው ገቢ በሚያስገቡ ላይ ጥብቅ መመሪያ አውጥቷል።

መመሪያው ምን ይላል ?

- ከአሁን በኋላ ዩትዩብ ክፍያ የሚፈጽመው አዲስና የራሳቸው ፈጠራ ብቻ ለሆኑ ፤ በብዛት ወይም በድጋሚ በዩትዩብ ላይ ላልዋሉ ስራዎች ነው።

- ክፍያ የሚፈጸምላቸው ቪድዮዎች እውነት እና የራስ ስራ ላይ የተመሰረቱ ብቻ መሆን አለባቸው።

- አርተፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ተጠቅመው የሚሰሩ ሰዎች ክፍያ አይከፈላቸውም።

- በድምፅና ትንሽ የቪድዮ ስራ ብቻ ተጨማምሮባቸው የሚቀርቡ የሌላ ሰዎች ስራዎች ክፍያ አያገኙም።

- በተለያዩ ተንቀሳቃሽ ቪድዮዎች ወይም የሰው ቪድዮዎች ላይ reaction መስጠት እና የሰው ቪድዮዎችን እየሰበሰቡ ማቅረብ ከዩትዩብ ክፍያ ውጭ ይደረጋሉ።

- የራሳቸው ስራ ያልሆነ ቪድዮ ማለትም እዛው ዩትዩብ ላይ በሌሎች የተሰሩ ቪድዮ የሚያቀርቡ ሰዎች የራሳቸውን ሃሳብ እንዲጨምሩና እንዲሰሩ የሚጠየቁበት መንገድ ቢኖርም ያለማስጠንቀቂያም ሊታገዱ ይችላሉ።

ዩትዩብ በአዲሱ መመሪያው ኦሪጅናል ለሆኑ እና ሰዎች በራሳቸው ጥረት ለሰሯቸው ስራዎች ክፍያ ይከፍላል። ክፍያ ለማግኘት የራስን የፈጠራ ስራ ዩትዩብ ላይ መጫን ግዴት ይሆናል።

ዩትዩብ ይህን ወደማድረግ የገባው ሰዎች የራሳቸውን የፈጠራ ስራ እንዲሰሩ ለማበረታታ ነው።

ዩትዩብ ክፍያ ለመክፈል ከዚህ ቀደም ያስቀመጠው አስገዳጁ 1 ሺህ ሰብስክራይበር እንዲሁም 4,000 የዕይታ ሰዓት በ12 ወራት ውስጥ ማግኘት አሁንም እንደ ግዴታ ይቀጥላል ተብሏል።

#YouTube #TheVerge

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

💎 ትልቁ ይገባዎታል!

በፀሐይ ባንክ "ዳይመንድ የቁጠባ ሒሳብ" ተጠቃሚ ይሁኑ!

9.5% እስከ 10% የሚደርስ የወለድ መጠን የሚያስገኝ ልዩ የቁጠባ ሒሳብ!

እርስዎ በርትተው ይቆጥቡ፤ እኛ ዳጎስ ባለ የወለድ ምጣኔ እንደግፍዎታለን! አሁኑኑ የፀሐይ ባንክ "ዳይመንድ የቁጠባ ሒሳብ" ይክፈቱ!

ለበለጠ መረጃ አቅራቢያዎ ወደሚገኝ የፀሐይ ባንክ ቅርንጫፍ ጎራ ይበሉ ወይም ወደ 921 ነጻ የጥሪ ማዕከላችን ይደውሉ፡፡

ፀሐይ ባንክ
ለሁሉ!


የፀሐይ ባንክ የቴሌግራም ገጽን ይቀላቀሉ 👇 /channel/tsehaybanksc

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቬትናም የሚያደርገውን የመጀመሪያውን በረራ በዛሬው ዕለት ምሽት ያስጀምራል።

አየር መንገዱ አፍሪካን ከ ኤዥያ ጋር ያገናኘው የዛሬ 52 አመት እ.ኤ.አ በ 1973 ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቻይናዋ ከተማ ሻንጋይ በመብረር  እንደነበር የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ይፋ በማድረጊያ ስነ ስርአቱ ላይ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኤዢያ 27 መዳረሻዎች ያሉት ሲሆን ወደ ቬትናም ሃኖይ ከተማ የሚያደርገው በረራ 28 ኛው መዳረሻው ይሆናል።

አቶ መስፍን " 190 በረራዎች በሳምንት ወደ ኤዢያ እናደርግ ነበር የአሁኑ በረራ በሳምንት ለ አራት ቀናት የሚከናወን በመሆኑ በአህጉሩ በሳምንት የምናደርገውን በረራ ወደ 194 ከፍ አድርገነዋል " ብለዋል።

ሃኖይ ለንግድ እና ለቱሪዝም የምትመረጥ መዳረሻ በመሆኗም የቀጥታ በረራ በመጀመሩ 120 የሚሆኑ አፍሪካውያን በዛሬው ምሽት ወደ ቬትናም ሃኖይ እንደሚጓዙ ተገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው " አየር መንገዱ በየጊዜው የሚጨምራቸው መዳረሻዎች በምን መስፈርት የተመረጡ ናቸው ? አፍሪካን እርስ በእርስ የማገናኘት ሥራስ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው ? " ሲል ጠይቋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው ምን ምላሽ ሰጡ ?

" ወደ አንድ ሃገር እና ከተማ የበረራ መስመር ከመክፈታችን በፊት የአዋጭነት ጥናት እናካሄዳለን።

አዋጭነት ማለት ገበያው አለ ወይ በረራ ብንጀምርስ በቂ መንገደኛ እናገኛለን ወይ የሚለው ላይ ጥናት እናካሂዳለን።

ያ ጥናት በቂ መንገደኛ አለ ሲለን በረራውን እንጀምራለን።

እድገት የሚመጣው አዳዲስ የበረራ መስመሮችን በመጨመር ወይም ባሉት ላይ የበረራ ምልልሱን በመጨመር ነው።

አፍሪካ ውስጥ በአሁኑ ሰአት በ 40 ሃገራት ወደ 61 ከተሞች እንበራለን።

ወደ ፊት እያየን የምንበርባቸው ሃገሮች ተጨማሪ ከተሞችን አዋጭ ሆነው ስናገኛቸው ፈቃዱን እንዳገኘን እንበራለን።

በተጨማሪም የማንበርባቸው ሃገሮችም ፈቃድ እንዳገኘን አዋጭነት እያየን እንበራለን በዚህ መንገድ አፍሪካ ውስጥ መዳረሻችንን እና የበረራ ምልልሱን እንጨምራለን።

አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Update

የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ያለውን ቀነ ቀጠሮ ሰጠ።

ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም በእስር የሚገኙ ተከሳሽ ተጠርጣሪዎች ለውሳኔ ማቅለያ የሚሆን የህክምና ማስረጃ እናቀርባለን ባሉት መሰረት ለዛሬ ሀምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።

ይሁን እንጂ ዛሬ ችሎት ላይ የቀረቡት የተከሳሽ ጠበቆች " የመቐለ ዓይደር ሰፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነገ አርብ ሀምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም የህክምና ማስረጃ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቶናል " ብለዋል።

ፍርድ ቤቱም ይህን አድምጦና ተቀብሎ የመጨረሻ ቀነ ቀጠሮ ለነገ ሰጥቷል።

በእንስት ዘውዱ ሃፍቱ የግድያ ወንጀል ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል በሚል ዛሬ በመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት የተበዳይና ተከሳሽ ቤተሰቦች ፣ በርካታ ሚድያዎች ፣ በሴት ጥቃት መከላከል ዙሪያ የሚሰሩ ስቪክ ማህበራት አመራሮችና አባላት ተገኝተው ነበር ።

ሁለት አመት ያስቆጠረው የእንስት ዘውዱ ሃፍቱ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል ነገ ሀምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም የመጨረሻ መቋጫ የፍርድ ውሳኔ ያገኝ ይሆን ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የችሎቱን ውሳኔ ተከታትሎ ያቀርባል።

ቲክቫህ ኢትጵዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#DStvEthiopia

ከ32 ቡድን 2 ብቻ ቀሩ! የዓለም ምርጡ ክለብ ማነው?

⏰ እሁድ ሀምሌ 6 ከምሽቱ 04፡00 ሰዓት
Chelsea vs PSG
📺 Channel 223 SS FIFA Club World Cup በጎጆ ፓኬጅ

⚽️ አንድም የጨዋታውን ደቂቃ እንዳያመልጥዎ ሁሉንም ጨዋታዎች በጎጆ ፓኬጅ ላይ በቻናል 223 ይመልከቱ! 📺✨

📣 አዲሱን የዲኤሲቲቪ ስጦታ እየተጠቀማችሁ ነው?

🎊 እስከ ሐምሌ 24 ድረስ ባሉት ቀናት በመረጡት የዲኤስቲቪ ፓኬጅ የአንድ ወር ሙሉ ክፍያ ሲከፍሉ ዲኤስቲቪ ያለተጨማሪ ክፍያ ከፍ ወዳለው ፓኬጅ ከተጨማሪ ቻናሎች ጋር በስጦታ ያገኛሉ!

ደንበኝነትዎን አሁኑኑ አራዝሙ ስጦታ ያግኙ!
⬇️
https://mydstv.onelink.me/vGln/xepsjmo7

ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው!

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #FIFACWC

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#USA #VISA

" የቪዛው የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር አጥሯል ፤ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትም ተከልክሏል " - ኤምባሲው

የአሜሪካ ኤምባሲ ለኢትዮጵያውያን የሚሰጠው ቪዛ የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ማጠሩን አስታውቋል።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስደተኛ ባልሆኑ የቪዛ አመልካቾች ላይ ባደረገው የፖሊሲ ለውጥ ምክንያት ውሳኔው መተላለፉን ኤምባሲው ገልጿል።

በአዲሱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፖሊሲ መሠረት፤ " ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለኢትዮጵውያን የሚሰጠው ቪዛ ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚያገለግል እና የሦስት ወር ቆይታ " እንደሚኖረው አስታውቋል።

ኤምባሲው ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. በፊት የተሰጡ ቪዛዎች ባሉበት እንደሚቀጥሉ ገልጿል።

ለንግድ እና ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን የሚያገኙት ቪዛ "B1" እና "B2" በሚለው ምድብ ውስጥ ይካተታል።

እስካሁን በነበረው አሰራር በዚህ ምድብ ውስጥ የሚገቡ ተጓዦች የሚያገኙት ቪዛ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ነበር። በተጨማሪም የቪዛው የቆይታ ጊዜ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ያስችል ነበር።

አሁን ይፋ የተደረገው ፖሊሲ የቪዛውን የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ከማሳጠር በተጨማሪ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትን ከልክሏል።

በአዲሱ ፖሊሲ ቪዛ የሚያገኙ ተጓዦች የቆይታ ጊዜ ባይጠናቀቅም እንኳ ከአሜሪካ ከወጡ በኋላ በዚያው ቪዛ ተመልሰው መግባት አይችሉም።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተለያዩ አፍሪካ አገራትን ቪዛ የቆይታ ጊዜን ወደ ሦስት ወራት ማሳጠሩን ትላንት ይፋ አድርጓል። ይህ ውሳኔ ከተላለፈባቸው ሀገራት መካከል ናይጄርያ እና ጋና ይገኙበታል።

#USEmbassyAddisAbaba #BBCAmharic

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ለቀናት ህመም ላይ እንደነበረ የተነገረ ሲሆን ሀምሌ 2 ቀን 2017 ዓ/ም በአሜሪካ ሲያትል ከተማ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ጋዜጠኛው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከጋዜጠኝነት እስከ የዜናና ወቅታዊ መረጃ ዳይሬክተር በመሆን አገልግሏል።

በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን " #የሚዲያ_ዳሰሳ " በሚል ርእስ ሲያቀርበው በነበረው ትንታኔ በአድማጭ ተመልካቾች ዘንድ ይታወሳል።

ወደ አሜሪካ በመሄድም በPhD ተመርቋል።

ከትምህርቱ ጎን ለጎንም እስከ ህልፈቱ ድረስ TBS በተባለው የትግርኛ ቴሌቪዥን በአማርኛና በትግርኛ ቋንቋዎች ወቅታዊና የመዝናኛ ፕሮግራሞች ሲያቀርብ ነበር። 

በ1963 ዓ/ም በትግራይ ውቕሮ ከተማ የተወለደው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ  የጋዜጠኝነትን ኮሙዩኒኬሽንን ክፍል በዲግሪ ተመርቋል። በጋዜጠኝነት ሙያ ለረጅም አመታት ሰርቷል።

መረጃው የቲቢኤስ ቴሌቪዥን ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት

የሁለት ወር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Modern Accountancy) የክረምት
ስልጠና
የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 07/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ

☎️  0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: /channel/sagetraininginstitute
Tiktok: sage_training_institute" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" መንግስት ሁሉን አቀፍ እና አካታች ፖለቲካዊ ውይይት ማድረግ አለበት " - የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ)

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦነግ/ ከአምስት አመት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ አካሄደ።

በዚህ ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የኦነግ በማዕከላዊ ኮሚቴ ሰሞኑን ባካሄደው ስብሰባ ምን አለ ?

- መንግስት በሀገሪቱ ውስጥ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ሁሉን አቀፍ ፖለቲካዊ ውይይት ያድርግ፤

- የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴ ውስጥ ካሉ አካላት ጋር በመነጋገር ችግሮች ይፍታ፤

- የፖለቲካ ምህዳሩ እንዲሰፋ እና ነፃ እንዲሆን ይሁን ሲል መጠየቁን አቶ ለሚ ተናግረዋል ።

ፓርቲው ላለፉት አምስት አመታት በየደረጃው ያሉ አመራሮቹና አባላቶቹ በመታሰራቸው እንዲሁም ከዋናው ጅምሮ በዞን እና ወረዳዎች ያሉት ጽህፈት ቤቶቹ በመዘጋታቸው የፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ለማድረግ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ማሳለፉን የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት አስታውሰዋል።

በፓርቲው በውስጥ የገጠሙትን ችግሮች እና ክፍተቶች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ በቅርቡ ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ ኮሚቴ መዋቀሩንም አቶ ለሚ ገልፀዋል።

ፓርቲው በሀምሳ አመት የትግል ጉዞው ያስመዘገባቸው ድሎች እና ድክመቶች በዚህ ጉባኤው ይገመግማል ያሉት አቶ ለሚ የወደፊት የሰላማዊ ትግል አቅጣጫ ያስቀምጣል ብለዋል።

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦነግ/ በቀጣይ ጉባኤው እያደረገ ያለው ሰላማዊ ትግል ፀንቶ እንደሚቀጥል የተናገሩት አቶ ለሚ " መንግስት የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት ዴሞክራሲን መለማመድ አስፈላጊ መሆኑን እንዲገነዘብ ከወዲሁ እናሳስባለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ፎቶ፦ ፋይል

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነቀምቴ
#TikvahEthiopiaFamliyNekemte

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Sidama

ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አዲስ ፖሊስ አዛዥ ተሹሟል።

የምስራቅ ሲዳማ ዞን ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ማቴዎስ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ሆነዉ ተሹመዋል።

በፀጥታ ዘርፉ ዉስጥ ሪፎርም ዉስጥ እንደሆነ በሚነገረው የሲዳማ ክልል ፖሊስ ተቋም ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ በተፃፈ ደብዳቤ የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ማቴዎስ ከዛሬ ሐምሌ 2/2017ዓ/ም ጀምሮ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ሆነዉ ተሹመዋል።

የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ኮማንደር መልካሙ አየለ በምን ምክንያት እንደተነሱ እስካሁን የተገለፀ ነገር የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AddisAbaba

የትምህርት ቤት ክፍያ !

20 በመቶ ትምህርት ቤቶች በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ጭማሪ ላይ ከወላጆች ጋር አለመስማማታቸውን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በቅርቡ ባጸደቀው የግል ትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሰራር ስርአት ደንብ ቁጥር 194/2017 መሰረት በ2018 የትምህርት ዘመን አገልግሎት ክፍያ ላይ ከ ተማሪ ወላጅና አሳዳጊዎች ጋር ካልተስማሙ መንግስታዊ ካልሆኑ የትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት መካሄዱን የከተማው ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

በውይይት መርሃ ግብሩ ፦
- የትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) ፣
- የትምህርት እና ሥልጠና ባለሥልጣን ከፍተኛ አመራሮች
- የግል ትምህርት ቤቶች አሰሪዎች ማህበር ፣
- የግል ትምህርት ቤት ባለቤቶች እና የተማሪ ወላጅ ኮሚቴ ተወካዮች እንደ ተሳተፉ ቢሮው በማህበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል።

ውይይቱ የተካሄደው በጭማሪው ላይ መስማማት ላይ ያልደረሱ ትምህርት ቤቶች ደንቡ በሚያስቀምጠው መሰረት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ውሳኔ ያሳለፈ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ የጋራ አስተሳሰብ ለመያዝ እንዲቻል መሆኑን ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ "በደንቡ መሰረት 80 ፐርሰንት ያህል ትምህርት ቤቶች ከወላጆችና አሳዳጊዎች ጋር በመስማማት የአገልግሎት ክፍያ መጨመራቸው የሚበረታታ ተግባር ነው" ብለዋል።

እንደ ትምህርት ቢሮ ሃላፊው ገለጻ 20 በመቶ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ከክፍያ ጭማሪ ጋር በተያያዘ ከወላጆች እና አሳዳጊዎች መስማማት ላይ አለመድረሳቸውን አመላክቷል።

የትምህርትና ስልጠናና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢዘዲን ሙስባህ "በደንቡ ላይ በመግባባት ወደ ስራ መገባቱን በዚህም መሰረት በርካታ ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር በመስማማት መጨመራቸውን ፣ መመሪያውን መሰረት በማድረግም ባለስልጣኑ በተቀሩትና መስማማት ባልቻሉት ላይ  ውሳኔ መስጠቱን" አሳውቀዋል ።

ባለሥልጣኑ ምን ውሳኔ እንዳሳለፈ በዝርዝር ባይገለጽም የወላጆችን የመክፈል አቅም እና የትምህርት ተቋማቱን የግብአት አቅርቦት ታሳቢ አድርጎ ተግባራዊ የሆነ መሆኑን ስለመናገራቸው ትምህርት ቢሮው አሳውቋል።

#AddisAbabaEducationBureau

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" መንግስት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የመዝጋትም ሆነ የማዳከም ፍላጎት የለውም " - የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን

የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች በዳግመ ምዝገባው ዙርያ ላቀረቡት ቅሬታ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ፣ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ መንግስት ተቋማቱን የማጥፋት እቅድ አለው እየተባለ ለሚቀርበው ቅሬታ በሰጡት አስተያየት፣ " ይሔ አስተያየት ስህተት ነው፣ እነዚህን ተቋማት የማዳከም አላማ የለም " ብለዋል፡፡

" ይልቁንም መንግስት እነዚህን ተቋማት የማጠናከር አላማና ፍላጎት ነው ያለው፣ የዳግመ ምዝገባና ምዘና ሒደቱ ትኩረትም ይህን እውን ማድረግ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡

የዳግመ ምዝገባና ምልከታ ሒደቱ በአዲስ አበባ መጠናቀቁን ተናግረው፣ በቀጣይ የትኞቹ ተቋማት ይቀጥላሉ፣ የትኞቹ አይቀጥሉም የሚለውን ለመግለፅ ሪፖርት በመዘጋጀት ላይ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

የአዲስ አበባው የዳግመ ምዝገባና ምዘና ስራ በመጠናቀቁ፣ በቅርቡ በክልሎች ይህንን ስራ ለመጀመር ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ውብሸት ታደለ በዝርዝር ምን አሉ ?

" አሁን እየተከናወነ ባለው ዳግመ ምዝገባና ምዘነና ሒደት የተፈለገው፣ የትምህርት ተቋማቱ መሰረታዊ በሆነ መንገድ ራሳቸውን እንዲያድሱ ነው፡፡

ባለቤትነታቸው እንኳ የማይታወቅና አጠራጣሪ የሆኑ ተቋማት አሉ፡፡ እነዚህን ችግሮች የማጥራት ስራ ነው እየተሰራ ያነው፡፡መዝጋት የምትፈልገውን ተቋም ይህን ያህል ጊዜ ማቆየት አያስፈልግም፡፡ በፖሊሲ አቅጣጫ አስቀምጠህ ከገበያ እንዲወጡ ማድረግ ይቻላል፡፡ ግን እሱ አይደለም አላማችን፡፡

የእኛ አላማ፣ ትናንሽ ቢዝነሶች ሆነው የጀመሩት ተቋማት ወደ አንድ ተደራጅተውና ተጠናክረው እንዲመጡ ነው፡፡ ካልቻሉ ደግሞ ከገበያው መውጣት አለባቸው፡፡

ክቡር ሚኒስትሩ (ፕሮፌሰር ብረሀኑ ነጋ) ከዚህ በፊት የተናገሩት ነገርም (50 ተቋማት ይበቃሉ ማለታቸው ይታወሳል) ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ ጠንከር ጠንከር ያላችሁ ተቋማት ሁኑ፡፡ ጥቂት ተቋማት ይበቃሉ፡፡ ይህ ሁሉ ተቋም አለ ማለት፣ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የተለየ ለውጥ ይመጣል ማለት አይደለም ነው ያሉት፡፡ ጥራት ያለው ትምህርት የሚሰጥ ተቋም ያስፈልጋል ነው ያሉት፡፡ የእኛም አላማ ይኸው ነው፡፡

ከዚህ በፊት ወጣ የተባለው፣ ' አብዛኞቹ ተቋማት መስፈርቱን አያሟሉም ተብለዋል ' የተባለው ዘገባ ስህተት ነው፡፡ ሚድያዎችን ለመተባበር ብለን የሰጠናቸውን መረጃ አዛብተው ዘገቡት፡፡ ከዛም፣ ሁሉም የግል ትምህርት ተቋማት መስፈርቱን አያሟሉም ተባለ ተብሎ ተስተጋባ፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡

በወቅቱ ያልነው፣ አብዛኞቹ ተቋማት ለዳግመ ምዝገባ የሚሆን የተሟላ ሰነድ አላቀረቡም ነው፡፡ ሰነድ አስገቡ ስንላቻው ስለነበር ማለት ነው፡፡ ሰነድ አላሟሉም ማለትና ያስገቡትን ሰነድ ገምግሞ መስፈርቱን አላሟሉም ማለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡

ቀደም ሲል ሒደቱ በጣም ቀላል ነበር ኮሌጅ ለመክፈት፣ ትንሽ ገንዘብ ካለህ አንድ ሁለት ክፍል ተከራይተህ መክፈት ነበር፡፡ በዚህ መሰሉ ሒደት መቀጠል አይቻልም አሁን፡፡ ይህን ቀላል አካሔድ የለመዱ ተቋማት መቀጠል አይችሉም፡፡ የተቀመጠውን መስፈርት አሟልተው በትንሹ ኮሌጅ የሚያስብል ስራ ሰርተው ነው ይህንን ቢዝነስ መጀመርና ማስኬድ ያለባቸው፡፡

አሁን በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በተቀመጠው መስፈርት መሰረት እንደ ኮሌጅ መቀጠል እችላለሁ የሚሉት ተቋማት ናቸው የተመዘገቡት፡፡ ከተመዘገቡት መካከል ደግሞ፣ አሁን ግምገማ ተደርጎ፣ ሰነዶቻቸው ተፈትሸው፣ የመስክ ምልከታም ተደርጎ፣ በትክክል መስፈርቱን ያሟላሉ የሚባሉትን ውጤት እንገልፃለን፡፡

አሁን ባለው ሁኔታ የአዲስ አበባን ተቋማት ምዝገባና ምልከታ ሙሉ በሙሉ አጠናቀናል፡፡ ውጤቱን ለመግለፅ ሪፖርቱን በማዘጋጀት ላይ ነው ያለነው፡፡ ጎን ለጎን ደግሞ በክልሎች ይህንን ስራ ለመጀመር ቅድመ ዘግጅት እያደረግን ነው፡፡ ስራው በአዲሱ የበጀት አመት የሚጀመር ይሆናል፡፡

እስካሁን ከዘርፉ የወጡ ተቋማትን በተመለከተ የተለያየ አሀዝ ይቀርባል፡፡ ለምሳሌ መጀመሪያ ላይ 84 ተቋማት ሳይመዘገቡ ቀሩ፡፡ በኋላ ላይ ግን ዘግይተው የመጡ አሉ፡፡ ከነሱ ውስጥ በቂ ምክንያት ያቀረቡትን መዝግበን እየገመገምን ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ተመዝግበው ከነበሩት ውስጥ ለመውጣት ሒደት ላይ ያሉ አሉ፣ ጎንለጎን ማለት ነው፡፡ ይህ የእነሱ ገባ ወጣ ማለት፣ ከዘርፉ የወጡ ተቋማት ብዛት በየጊዜው እንዲለያይ አድርጎታል፡፡ እንደዛም ሆኖ፣ አሁን የምዝገባና የግምገማ ሒደት ላይ ስለሆንን ትክክለኛ ቁጥሩን ማስቀመጥ ቢያስቸግርም ቢያንስ 80 የግል ትምህርት ተቋማት፣ ስራቸውን አቋርጠው ከዘርፉ ተሰናብተዋል፡፡

የዳግመ ምዝገባው መመሪያ ላይ በቂ ውይይት አልተደረገበትም፣ ከዘርፉ ተዋናዮች ግብአት አልተወሰደም የሚለውም ጉዳይ ትክክል አይደለም፡፡ ከተቋማቱ ባለቤቶች በሁለት መንገድ ግብአት ተቀብለናል፡፡ አንደኛው፣ ከውይይት መድረክ የተገኘው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በፅሑፍ የተቀበልነው ነው፡፡ በዚህ መንገድ በአዲስ አበባ በሀይሌ ግራንድ ሆቴል ከተደረገ ውይይትና በፅሑፍ ከቀረቡልን ሀሳቦች ግብአት ወስደናል፡፡አስፈላጊ የሆኑትንና ያስኬዳሉ የምንላቸውን ሀሳቦች በግብአትነት ተጠቅመንባቸዋል፡፡

ለምሳሌ ፦ ከእነሱ ተቀብለን ካካተትናቸው ሀሳቦች አንዱ፣ በመውጫ ፈተና ቢያንስ 25 በመቶ ያላሳለፈ ተቋም መቀጠል የለበትም የሚለው መስፈርት መቼ ተግባራዊ መሆን ይጀምር የሚለው ላይ የእነሱን ሀሳብ ተቀብለን የእፎይታ ጊዜ እንዲሰጥ አድርገናል፡፡

ይህ መስፈርት መተግበር የሚጀምረው፣ መመሪያው በወጣበት ጊዜ ትምህርት በጀመሩ ተማሪዎች ላይ እንጂ፣ በነባር ተማሪዎች ላይ መሆን የለበትም የሚለው ሀሳብ ከነሱ የመጣ ነው፡፡ ይህ ሀሳባቸው አሳማኝ በመሆኑ ተቀበልነው፡፡ አሁን ለትግበራው ሁለት አመት ገደማ አላቸው፡፡ በ 2019 ዓ.ም ገደማ ነው መተግበር የሚጀምረው ይህ መመሪያ፡፡ ሌሎችም የተቀበልናቸው ሀሳቦች አሉ፡ " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AAiT

Announcement of Professional Training Programs

Python Programming + Data Analytics and Visualization

By: Addis Ababa University,
College of Technology and Built Environment,
School of Electrical & Computer Engineering

Registration Deadline: July 24, 2025

Training Starts on: July 26, 2025

Online Registration Link: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6

Telephone: +251-913-574525/ +251-940-182870

Email: sece.training@aait.edu.et

For more information: https://forms.gle/M1DPS1zFP4K9QT4V6  

Telegram Channel: /channel/TrainingAAiT

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

ባለንበት ሆነን ወርሃዊ የውሃ ፍጆታችንን በቀላሉ በቴሌብር በመክፈል ጊዜያችን መቆጠብ እንችላለን።

ቴሌብር ሱፐርአፕ ➡️ ክፍያ ➡️ የውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ➡️ ክፍያ
*127# ደውለን ወይም ቴሌብርን በስልካችን በዚህ ሊንክ https://bit.ly/telebirr_SuperApp ጭነን ስንመዘገብ እንዲህ ነን!

#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን
#ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን
#ስንጭን_እንዲህ_ነን
#ስናስጀምር_እንዲህ_ነን

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Ethiopia🇪🇹

ከዩቲዩብ ፣ ቲክቶክና ከሌሎች የዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር ሊጣል ነው።

በኢትዮጵያ ለ9 ዓመታት ስራ ላይ የቆየውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ፣ ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር ለመጣል የሚያስችል ንዑስ አንቀጽ ተካቷል።

በታቀደው የአዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ መሰረት፣ ከማህበራዊ ሚዲያ የሚገኝ ገቢ ለምሳሌ ፦
- ከዩቲዩብ፣
- ፌስቡክ፣
- ኢንስታግራም፣
- ቲክቶክና ሌሎችም መድረኮች
- በኢንተርኔት ከሚሰራጩ መረጃዎች
- በኢንተርኔት ከሚፈፀሙ ግብይቶች፣
- ከስፖንሰርሺፕ ከመሳሰሉት የዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ላይ ግብር እንደሚጣልባቸው በዝርዝር ያስቀምጣል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዉይይት እየተደረገበት የሚገኘዉ ይህ ረቂቅ አዋጅ ፤ እነዚህ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች በመደበኛነት የሚከናወኑ ከሆነ፣ የሚገኘው ገቢ በንግድ ስራ ገቢ ስር የሚመደብ ሲሆን፣ የንግድ ስራ ገቢ ግብርም የሚከፈልበት መሆኑን ይገልጻል።

ሆኖም፣ በአዋጁ የተቀመጡትን መስፈርቶች የማያሟላ ከሆነ፣ ገቢው " ሌሎች ገቢዎች "  በሚለው ስር ተመድቦ ከጠቅላላ ገቢው ላይ 15% (አስራ አምስት በመቶ) ግብር እንዲከፈልበት ይደረጋል ይላል።

ከዚህ በተጨማሪም፣ ለዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ክፍያ የሚያመቻቹ መድረኮች ለእያንዳንዱ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪ የተከፈለውን ገንዘብ የሚያሳይ ሪፖርት ለታክስ ባለስልጣን የመላክ ግዴታ እንደሚኖርባቸው ያስቀምጣል።

ይህን ተከትሎም፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) የማውጣት ፣ ገቢያቸውን የማስታወቅ እና ሌሎች የታክስ ከፋይ ግዴታዎችን የመወጣት ሃላፊነት እንደሚጠበቅባቸው ያስገድዳል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው። #CAPITAL

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" በአነስተኛ ጀልባዎች ለመሻገር የሚደረጉ ሙከራዎች ከንቱ ይሆናሉ "- የዩናይትድ ኪንግደም ጠ/ሚ

ዩናይትድ ኪንግደም ከፈረንሳይ በአነስተኛ ጀልባዎች ወደ አገሪቱ የሚገቡ ስደተኞችን በሳምንታት ጊዜ ውስጥ አዲስ በተወጠነ እቅድ መሰረት መመለስ እንምትጀምር ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ኪር ስታመር መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

በእቅዱ መሰረት አገር ውስጥ የሚገቡ አንዳንድ ስደተኞች ወደ ፈረንሳይ ሲመለሱ፤ ዩናይትድ ኪንግደም ደግሞ ተመጣጣኝ ቁጥር ያላቸውን ጥገኛ ጠያቂዎች የደኅንነት ፍተሻ አድርጋ ትቀበላለች።

የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለሦስት ቀናት የሥራ ጉብኝት ለንደን ይገኛሉ።

መሪዎቹ በጋራ በሰጡት መግለጫ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ስታመር " በአነስተኛ ጀልባዎች ለመሻገር የሚደረጉ ሙከራዎች ከንቱ ይሆናሉ " ብለዋል።

እቅዱ በሳምንት እስከ 50 የሚደርሱ ሰዎች እንዲመለሱ እንደሚያደርግ የተዘገበ ቢሆንም፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን አሃዙን አላረጋገጡም።

" ለውጥ አምጪው " እቅድ የሰዎች ዝውውር ላይ የተመለደውን አካሄድ ለመስበር የሚያግዝ እና ውጤታማ ከሆነ በስፋት የሚሰራበት ነውም ብለዋል።

ሕገ-ወጥ ስደት " ዓለም አቀፍ ቀውስ፣ የአውሮፓ ሕብረት ቀውስ እና የሁለቱ አገሮቻችን ቀውስ ነው " ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ሦስት 5Lሚኒባሶች ናቸው የተወሰዱት ፤ ሦስት ሆነው ነበር ያደሩት አንዱ ጥበቃ አብሮ ጠፍቷል " - ባለንብረቶቹ

ትላንት (ረቡዕ ለሐሙስ) ከሌሊቱ 9 ሰዓት ገደማ ፓርክ ከተደረጉበት ሦስት 5L ሚኒባሶች እንደተወሰዱባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ ባለንብረቶች ተሽከርካሪዎቹን ያየ ሁሉ እንዲጠቁማቸው በአጽንኦት ተማጽነዋል።

ባለንብረቶቹ " ሦስት 5L ሚኒባሶች ናቸው የተወሰዱት፤ ሦስት ሆነው ነበር ያደሩት አንዱ ጥበቃ አብሮ ጠፍቷል። ሁለቱ 'ተኝተን ነበር' አሉ። ከተቀጠረ ሦስት ቀናት የማይሞላው ጥበቃ ነው ከተሽከርካሪዎቹ ጋር አብሮ የጠፋው " ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።

" ጥበቃው የተቀጠረው በኤጀንሲ ነበር። ኤጄንሲው ተመሳጥሮ እንዳይሆን የሚል ጥርጣሬ አለን። ምክንያቱም ኤጀንሲው የተሟላ ዶክሜንት አልያዘም ጥቃውን ሲቀጥረው፤ ዋስትና አልያዘም 'መጣል' በሚል" ብለዋል።

አክለው፣ "ኮሚቴዎች ደግሞ 'አይቻልም' ብለው ሲመልሱ አማላጅ ፓሊስ ጠርቶ 'ፓሊሱ እኔ ኃላፊነቱን እወስዳለሁ፤ በሦስት ቀናት ያመጣል ይስራ' እንዳላቸው ነው ኮሚቴዎቹ የነገሩን። የኤጀንሲው ሰውም፣ ፓሊሱም፣ ሁለቱ ጥበቃዎችም ተይዘዋል" ነው ያሉት።

ሦስቱም ተሽከርካሪዎች ከአንድ ፓርኪንግ ከቆሙበት እንደተወሰዱ፣ የተወሰዱትም ቃሊቲ ቶታል ጨፌ ኮንዶሚኒየም እንደሆነ፣ አንዱ መኪና ኦሮ ኮድ 03 34021 መሆኑን ተናግረዋል።

ሌላኛው የጠፋው ተሽከርካሪ ኦሮ ኮድ 03 ኦሮ 41867 እንደሆነ፣ ከጠፉት ከሦስቱ አንዱ እንደተገኘ በዚህ ዘገባ ታርጋቸው የተገለጹት እንዳልተገኙ ገልጸው፣ ተሽከርካሪዎቹን ያየ በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች እንዲጠቁማቸው ተማጽነዋል።

የባለንብረቶቹ ስልክ ቁጥሮች 0912049042፤ 0965206720
ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አዲስ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
 
@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#ግብር

" የቤተክርስቲያን ወሳኝ አካል የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ሊመለከተው ይገባል " - አባቶች

➡️ የሃይማኖት ተቋማት ከተቋቋሙበት ዓላማ ባሻገር የገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ ሲሳተፉ ታክስ መክፈል እንዳለባቸው መወሰኑ ይታወቃል !

ቤተ ክርስቲያን የተጨማሪ ገቢ ግብር መክፈል እንዳለባት በተላለፈ ውሳኔ ላይ ውይይት መደረጉን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገለጸች።

ውይይቱ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የተካሄደ ሲሆን፦
- ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣
- ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የደቡብ ምስራቅ ትግራይና የራያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
- ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስአበባ እና የሐድያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
- ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩንቨርስቲ ፕሬዘዳንትና የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሊቀ ጳጳስ ተገኝተው ነበር።

ከመንግሥት በኩል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ የሥራ ኀላፊዎች እና መጋቢ ታምራት የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ በውይይቱ ተካፍለዋል።

የሃይማኖት ተቋማት ከተቋቋሙበት ዓላማ ባሻገር የገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ ሲሳተፉ ታክስ መክፈል እንዳለባቸው የሚደነግገውን አዋጅ ላይ በከተማ አስተዳደሩ የተጋበዙ የሥራ ኀላፊዎች ዝርዝር ማብራሪያ አቅርበዋል።

ከቤተክርስቲያን ወገን የተገኙ መሪዎችና የሥራ ኃላፊዎች ፤ ጉዳዩ ዙሪያ መለስ ውጤቶችን ከግምት ባስገባ መልኩ ተጨማሪ ምክክር ሊደረግበት የሚገባ መሆኑን አሳውቀዋል።

በተጨማሪ የቤተክርስቲያን ወሳኝ አካል የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ሊመለከተው እንደሚገባ መጠቆማቸውም ተገልጿል።

ውይይቱ ቀጣይነት እንዳለው ተጠቁሟል።

መረጃው የመንበረ ፓትርያርክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" የትልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክት ማሽን ጭነን ቅድሚያ ስጡን ብለን ብንጠይቅም የሚሰማን አላገኘንም ፤ ተሰልፈን መንገድ ላይ ለማደር ተገደናል " - አሽከርካሪዎች

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ቀደም ሲል በቤንዚን ላይ ብቻ ይስተዋል የነበረው ሰልፍ ከቅርብ ጊዜያት ወዲ በናፍጣ ላይ ጎልቶ መታየት የጀመረ ሲሆን ቲክቫህ ኢትዮጵያም አሽከርካሪዎች አነጋግሯቸዋል።

ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን የሚሰሩ የተለያዩ ማሽነሪዎችን ጭነዉ በነዳጅ ሰልፉ ላይ የነበሩ አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " ማሽነሪዎቹ በየመንገዱ ባደሩ ቁጥር የሚሰራዉ ፕሮጀክት ከመጓተቱም በላይ የክረምት የጎርፍ ሙላት ፕሮጀክቱን ያበላቸዋል ይህን ለማደያ ባለሙያዎች ብንገልፅም ከሰልፉ ወጪ ለመቅዳት የንግድ ቢሮ ትዕዛዝ እንደሚያስፈልግ ነግረውናል " ብለዋል።

" በከተማ ሁሉም ማደያዎች ለመንግስት አምቡላንሶች እንጂ ለሌሎች የሕክምና ተቋማት አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎች ቅድሚያ እየተሰጠ አይደለም " ያሉ ሌሎች አሽከርካሪዎች ደግሞ " ይህ ተገቢነት የለዉም " ብለዋል።

በአንድ ማደያ የናፍጣና ቤንዚን ረጃጅም ሰልፎች በተመሳሳይ ሰዓት መመደባቸዉ ለእግልታችን ሌላኛዉ ምክንያት ነዉ ያሉት በሰልፉ ላይ ያነጋገርናቸው አሽከርካሪዎች " የከተማ አስተዳደሩ ንግድ መምሪያ ጉዳዩን በአግባቡ መምራት አለመቻሉንና እንደዉም በተቃራኒው ምሳ ሰዓት ዘግቶ በመዉጣት ለሚፈጠሩ መጨናነቆች ምክንያት እየሆነ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

" ተመዝግበዉ ያደሩ ናቸዉ " በሚል በየሰልፉ መሃል እንዲገቡ የሚደረጉ ተሽከርካሪዎች አሽከርካሪዎች እርስ በርስ እንዲጋጩ እያደረገ ስለመሆኑ አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" በነዳጅ ማደያዎች ሀዋሳ ከተማን የሚመጥን መስተንግዶ አላገኘንም " ሲሉም ወቅሰዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽና ማብራሪያ ለማግኘት ወደ ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ የእጅ ስልክ ደጋግሞ ቢደውልም ስልክ ባለመነሳቱ ምላሽ ማግኘት አልተቻለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" በተማሪነትም ሆነ በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎቻችን ከተፈቀደላቸው የቪዛ ቆይታ ጊዜ በላይ በአሜሪካ መቆየት በአሁኑ ወቅት ተቀባይነት የሌለውና ከፍተኛ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን መገንዘብ ያሻል " - አምባሳደር ነብያት ጌታቸው

ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የአሜሪካ ቪዛ የያዙ ኢትዮጵያውያና የሌላ አገር ዜግነት ያላቸው ዜጎች ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ከቆዩ ቅጣት እንደሚከተላቸው የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ይህን ያሉት ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው።

በዚህም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአሜሪካ መንግስት የቪዛና አገልንሎትና ኢምግሬሽን ጉዳዮችን በሚመለከት አዳዲስ አሰራሮችንና አካሄዶችን ይፋ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው ለዜጎች ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

"በተማሪነትም ሆነ በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎቻችን ከተፈቀደላቸው የቪዛ ቆይታ ጊዜ በላይ በአሜሪካ መቆየት በአሁኑ ወቅት ተቀባይነት የሌለውና ከፍተኛ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን መገንዘብ ያሻል" ሲሉ ተናግረዋል።

"ወደፊትም ለትምህርትም ሆነ ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የመጓዝ እድል ያላቸው ዜጎች እነኝህን የተቀመጡ የቪዛ ቆይታ ጊዜዎች ካላከበሩ ለተለያዩ ችግሮች ሊጋለጡ የሚችሉ በመሆኑ ተገቢውን ጥንቃቄ እንደረግ ማሳሰብ እንፈልጋለን" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ወደ አሜሪካ ለመጓዝ፣ ቪዛ ለማግኘት ለአሜሪካ ኤምባሲ ማመልከቻ የሚያስገቡ ከመንግስትም ሆነ ከግል ተቋማት የሚመነጩ ሰነዶች ትክክል ስለመሆናቸው እያረጋገጡ እንዲሆን አሳስበዋል።

በአጠቃላይ የአሜሪካ መንግስት የቪዛ አገልግሎትን የኢምግሬሽን ጉዳዮችን የሚያወጣቸውን አዳዲስ አሰራሮች በመከታተል ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

አምባሳደሩ፣ "ከአሜሪካም ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ የሚያደርጉ የአሜሪካ ፓስፓርት የያዙ ኢትዮጵያውያን፣ የሌሎች ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች የኢትዮጵያን ቪዛ ለማግኘት ወደ አገራችን ሲመጡ ከተፈቀደላቸው የቆይታ ጊዜ በላይ በሀገራችን ሕግ መሠረት ቅጣት የሚያስከትል በመሆኑ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ ለማሳሰብ እንወዳለን" ሲሉም ተናግረዋል።

አምባሳደር ነብያት፣ "ይህ አሰራር የትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ ያልያዙትን ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ይጨምራል" ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvaEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Houthis

የየመን ሁቲዎች በጉዞ ላይ የነበረ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት ከፈጸሙ እና መርከቡ ቀይ ባህር ውስጥ ከሰጠመ በኋላ 6 መርከበኞች መትረፋቸውን እና ቢያንስ 3 ሌሎች ሰዎች መሞታቸውን የአውሮፓ የባህር ኃይል ተልዕኮ አስታወቀ።

የላይቤሪያን ባንዲራ የሚያውለበልበው እና በግሪክ የሚንቀሳቀሰው 'ኤተርኒቲ ሲ' የተባለው የጭነት መርከብ 25 ሠራተኞችን ይዞ እየተጓዘ ነበር።

መርከቡ ሰኞ ዕለት ከትንሽ ጀልባዎች በተተኮሱ የሮኬት ቦምቦች ከተመታ በኋላ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በዚህም የመንቀሳቀስ አቅሙን እንዳጣ የእንግሊዝ የባሕር ንግድ ሥራዎች ኤጀንሲ (UKMTO) ገልጿል።

ጥቃቱ ማክሰኞ ዕለትም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን መርከበኞቹን የማዳን ሥራ የተጀመረው ሌሊት ላይ ነው።

በኢራን የሚደገፉት ሁቲዎች፤ ኤተርኒቲ ሲ ላይ ጥቃት የፈጸሙት ወደ እስራኤል እየተጓዘ ስለነበረ እንደሆነ አስታውቀዋል።

ቁጥራቸው ያልታወቀ ሠራተኞችንም " ደህንነቱ ወደ የተጠበቀ ቦታ " እንደወሰዱ ተናግረዋል።

በየመን የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ሁቲዎች " በሕይወት የተረፉ የቡድን አባላትን አፍነው መውሰዳቸውን " ገልጾ፤ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጥሪ አቅርቧል።

የፊሊፒንስ ባለስልጣናት ከቡድኑ አባላት ውስጥ 21 ያህሉ ዜጎቻቸው እንደሆኑ ተናግረዋል።

ከቀሪዎቹ መካከል አንዱ የሩስያ ዜግነት ያለው እንደሆነ እና በጥቃቱ በደረሰበት ከፍተኛ ጉዳት እግሩን እንዳጣም ተገልጿል።

ሁቲዎች በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ይህንን ዓይነቱን ጥቃት ሲፈጽሙ ይህ ሁለተኛቸው ነው።

ቡድኑ እሁድ ዕለት 'ማሲክ ሲስ' በተባለ ሌላ የላይቤሪያን ባንዲራ የሚያውለበልብ የግሪክ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት ፈጽመዋል።

የእሁዱን ጥቃት የፈጸሙት መርከቡ፤ " በተወረረው የፍልስጤም ግዛት ውስጥ በሚገኙ ወደቦች ላይ የተጣለውን የጉዞ ክልከላ የጣሰ ኩባንያ ንብረት በመሆኑ " ነው ብለዋል።

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ወደ 54 እንስሳት ነው የምናሳድነው፤ ኢንደሚክ የሆኑ ለምሳሌ ጭላዳ ዝንጀሮንም፣ የምኒልክ ድኩላንም እናሳድናለን " - የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን

በአራት ክልሎች ኢንደሚክ የሚባሉትን ጨምሮ ወደ 54 የኢትዮጵያ ብርቅዬ የዱር እንስሳትን በውጪ ዜጎች እየታደኑ በዶላር እየተሸጡ መሆኑን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገረ።

በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት አጠቃቀም ባለሙያ አቶ ፋንታዬ ነጋሽ በሰጡን ገለጻ፣ ለምሳሌ " አንድ ኒያላ 15 ሺሕ ዶላር ነው የሚሸጠው፤ ይሄ ይበቃል? አይበቃም? የሚለው ገና እየታየ ነው በሕግ፤ አልጸደቀም እንጂ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ድረስ ገብቷል ረቂቁ። ዋጋው በቂ አይደለም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ እንዲህ አይነት በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ብርቅዬ እንስሳት መታደናቸው ልክ አይደለም የሚሉ ቁጣዎች እየተሰነዘሩ ነው፤ ለዚህ ትችት ያላችሁ ምላሽ ምንድን ነው ? ሲል አቶ ፋንታዬን ጠይቋል።

" ኢንደሚክ እንስሳት ይታደናሉ፤ ያም ደግሞ ዝም ብሎ በዘፈቀደ ሂዶ ማደን ሳይሆን ሳይንሳዊ በሚሆን መንገድ ተጠንቶ፤ ተቆጥረው ይህን ያክል ቢገደል ተብሎ በሚሰጥ ኮታ መሠረት ነው። የእንስሳቱን የመኖር ህልውና ምንም አደጋ ላይ በማይጥል መልኩ ተጠንቶ ነው ያ የሚደረገው፤ ያም ሲደረግ ደግሞ ከፌደራል፣ ከክልል የተውጣጡ ባለሙያዎች አጥንተው ሳይንሳዊ የሆነ ሪሰርች ቀርቦ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" ወደ 54 እንስሳት ነው የምናሳድነው፤ ሁሉም የየራሳቸው ዋጋና ኮታ አላቸው። ኢንደሚክ የሆኑ ለምሳሌ ጭላዳ ዝንጀሮንም፣ የምኒልክ ድኩላንም እናሳድናለን " ብለዋል ባለሙያው።

ይህ የሚሆነው አንድ እንስሳ ምን ያህል ቢገደል ነው የእንስሳቱን ቁጥር የማይጎዳው? ተብሎ ቀንዱ ተለክቶ እድሜው ታውቆ እንደሆነ አስረድተው፣ "ለምሳሌ ኒያላን ከ29.5 ኢንቺ በታች ቱሪስቶች በስህተት እንኳ ከገደሉ የእንስሳውን እጥፍ ነው የሚከፍሉት። ማንኛውንም ሴት እንስሳ ቢገድሉ ደግሞ የዋጋውን እጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋል " በማለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በሌሎች ሀገራት የሌሉ ኢትዮጵያ ብቻ የምትታወቅባቸው ብርቅዬ እንስሳት እየታደኑ የሚሸጡ ከሆነ በአንድ ወቅት ህልውናቸው ሊጠፋ ስለሚችል ጭራሹንም መጠሪያ ማጣትን አያስከትልም ወይ? ከጠፉ ደግሞ የቱሪስት ፍሰት አይኖርምና ከሚገደሉ ይልቅ በቱሪስት የሚያስገኙት ገቢ አይሻልም ወይ? በሚል ለሚነሳው ስጋት ምላሽ እንዲሰጡም አቶ ፋንታዬን ጠይቀናቸዋል።

ምን መለሱ?

" ያልከው ስጋት ምናልባት ስፓርታዊ ሃንቲንግ ምንድን ነው? ብለው በትክክል ካለመረዳት የመጣ ነው። መስጋታቸው ምንም ሊደንቅ አይገባም፤ ግን ደግሞ ሳይንሱን ቢያውቁት ግልጽ ይሆንላቸዋል።

ሲቀጥል እንስሳቱ የሚታደኑት ፓርክ ላይ አይደለም። ይልቁንም ለእነርሱ ተብሎ የተከለለ የአደን ቀበሌ አለ፤ ከፓርኮቻችን ቢያንስ 5 ኪሎ ሜትር የራቀ ቦታ እንጂ ብሔራዊ ፓርኮች ውስጥ አደን አይፈቀድም። ነገር ግን ዓለም አቀፍ ህግ በሚፈቅደው መልኩ የአደን ቀበሌ ተብሎ ይቋቋልማል፤ እዚያ አደን ቀበሌ ላይ ነው ኮታ የሚሰጠው።

ኒያላ ብቻ ሳይሆን ወደ 54 እንስሳትን እናሳድናለን፤ አንድ ቱሪስት ደግሞ ኒያላ ብቻ ብሎ አይመጣም። ሌሎች እንስሳትን (የምኒልክ ድኩላ፣ ተራ ድኩላ፣ የቆላ አጋዘን...) አብሮ ይገዛል። ሁሉም በሳይንሳዊ መንገድ ተጠንተው ኮታ ተሰጥቷቸው ነው የሚታደኑት " ብለዋል።

በዚሁ አደንም ከፍተኛ ገቢ እንደሚገኝ፣ 85 በመቶው ገቢ እንስሳው ለታደነበት ክልል፣ 15 በመቶው ለፌደራል መንግስት እንደሚገባ፣ አደኑ በኦሮሚያ፣ ደቡብ፣ ሶማሌና አፋር ክልሎች እንደሚከናወን፣ የታደኑትን እንስሳትን ትክክለኛ ቁጥር ለጊዜው ባያስታውሱም በዚህ ዓመት ወደ 177 ሚሊዮን ብር ገቢ እንደተገኘ ገልዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AddisAbaba

ሽንኩርት ፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች #ከቫት ነጻ እንደሆኑ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አሳውቋል።

ቢሮው " ማህበረሰቡ ዕለት በዕለት የሚሸምታቸው ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ተደርገዋል " ሲል ገልጿል።

ከሰሞኑን ለቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በወረደው ሰርኩላር ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች ከቫት ውጭ መደረጋቸውን አመላክቷል።

በሰርኩላሩ ላይ " የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ 1341/2016 አንቀፅ 10 እና አዋጅን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ቁጥር 570/2017 ዓ.ም መሰረት ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች አትክልቶች ያሉ ምርቶች ወደሀገር ውስጥ ሲገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ ተመርተው ለግብይት ሲቀርቡ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ መደረጋቸውን ተደንግጓል " በሚል ተቀምጧል።

በዚህም መሰረት ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች የሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች ብቻ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የተደረጉ መሆናቸው ታውቆ ከሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ተገቢው ክትትል በማድረግ እንዲፈፀም አዟል።

ይሁንና በአዋጁ ከታክስ ነፃ ከተደረጉ ውጪ የፍራፍሬ ምርቶች በሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች የቫት አሰራሩ የሚቀጥል መሆኑን በመግለፅ ተገቢው ክትትል እንዲደረግ ቢሮው አሳስቧል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" ካምፓኒዎቹን መቀመቅ የሚከት እብደት እንዲቆም የሚመለከተው አካል ሃላፊቱን ይወጣ " - አቶ በየነ ምክሩ

አሁን ላይ በአዲስ አበባ የሚገኙትና የትእምት (EFFORT) ዋና ስራ አስፈፃሚ መሆናቸውን የሚናገሩት አቶ በየነ መክሩ ' ላዛ ትግርኛ ' ለተባለ የዩቱብ ሚድያ ቃለ መጠይቅ ሰጥተው ነበር።

በዚህም " ህገ-ወጥ " ሲሉ የጠሩት የደብረፅን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት በትእምት ካምፓኒዎች ላይ ከፍተኛ አደጋ እንዲያንዣብብ እየተንቀሳቀሰ ነው በማለት ከሰዋል።

መጋቢት 2017 ዓ.ም በትግራይ በወቅቱ በነበረው ጊዚያዊ  አስተዳደር ላይ በተከሰተው ከፍተኛ የፓለቲካ አለመረጋጋት ምክንያት ወደ አዲስ አበባ መውጣታቸው የተናገሩት ዋና ስራ አስፈፃሚው የሳቸውንና የባለ አደራ ቦርድ ሰብሳቢ ቴድሮስ ሓጎስ የሚጠቀሙበት ማህተም ከህግ አገባብ ውጪ በማስቀረፅ " ህገ-ወጡ ቡድን " አደገኛ ተግባራት በመፈፀም ላይ ይገኛል ብለዋል።

" ዋና ስራ አስፈፃሚ ፣ ቦርድና የባለ አደራ ቦርድ በስራ እያለ ቡድኑ የራሱ  ህገ-ወጥ  ቦርድና የባለ አደራ ቦርድ በመሰየም ዋና ስራ አስፈፃሚ ለመቅጠር ማስታወቅያ በማስነገር ላይ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል።

አቶ በየነ " ካምፓኒዎቹን መቀመቅ የሚከት  ይህንን መሰል እብደት እንዲቆም የሚመለከተው አካል ሃላፊቱን ይወጣ " ብለዋል።

" የቡድኑ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ካምፓኒዎቹ ከስራ ውጭ  እንዳያደርግ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ተከታታይ ምክክሮች እያካሄድን ነው " ያሉ ሲሆን " ጉዳዩ በህግ-ማእቀፍ እንዲታይ በክልሉ ፍትህ ቢሮ ክስ መመስርተናል " ሲሉ አስታውቀዋል።

ይህን ሳይሳካ ከቀረ ግን የፌደራል መንግስት በትእምት ካምፓኒዎች ላይ በጦርነቱ ጊዜ ያስቀመጠው እግድ መልሶ ለማየት የሚገደድበት ሁኔታ ዝግ አይደለም ብለዋል። 

በተጨማሪ ምን አሉ ?

- " የትእምት 60 በመቶ ሃብት በጦርነቱ ወድሟል ፤ መሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ አርጅቷል ፤ ትራንስ ኢትዮጵያ ከነበሩት 500 መኪኖች አሮጌ 100 መኪኖች ብቻ ነው የቀሩት ፤ አልመዳ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ  በአውሮፕላን ቦንብ ሙሉ በሙሉ ወድመዋል። "

- " የፌደራል መንግስት ከጥቅምት 2013 እስከ ጥቅምት 2015 ዓ.ም በትእምት ካምፓኒዎች ላይ አኖሮት የነበረው እግድ ለጊዜው ሲያነሳ ካምፓኒዎቹ ከህወሓት ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው መስራት እንዳለባቸው ቅድመ ማስጠንቀቂያ ስጥቶ ነው ያስረከበን። " 

- " የፌደራል መንግስት በትእምት ካምፓኒዎች ያስቀመጠው  እግድ ሙሉ በሙሉ ባለነሳበት ሁኔታ ሆነን ከፓለቲካ ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው እንዲያንሰራሩ ስንሰራ ነበር፤ ህገወጡ የህወሓት ቡድን ከካምፓኒዎቹ ላይ እጁ የማያነሳ ከሆነ የፌደራል መንግስት እግድ ሊቀጥል ይችላል። "

- " ህገ-ወጥ ቡድኑ በሃይል ካስቀመጣቸው አመራሮች የተደረገ ርክክብ የለም ፤ ዋና ስራ አስፈፃሚና ቦርድ የነበረው ነው ያለው። "

ትእምት ኢንቨስትመንት በስሩ 15 ካምፓኒዎች እንዳሉት ይታወቃል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

" በወረዳዎቹ በቂ የጸጥታ ኃይል የለም። ጥቂት የጸጥታ ኃይሎችም ታጣቅዎቹ ጥቃት ካደረሱና ዝርፊያ ከፈጸሙ በኋላ ይመጡና ወዲያው ይመለሳሉ " - ፓርቲው

ቦሮ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ፣ " የ'ሸኔ' ታጣቂዎች በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተለይ በመተከልና ካማሺ ዞኖች እያደረሱት ያለው ጥቃት ቀጥሏል " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ፓርቲው ሰሞኑንም በወንበራ ወረዳ ጥቃት መድረሱን ገልጾ፣ " የክልሉ መንግስት ለጉዳዩ በቂ ትኩረት በመስጠት በቂ የጸጥታ ኃይል በመላክና በአከባቢው የመከላከያ ካምፕ በማቋቋም የህዝቡን ሰላምና ደህንነት እንዲያስጠብቅ " ጠይቋል።

" በካማሺ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች፣ በመተከል ዞን በቡለን፣ ድባጢና ወምበራ ወረዳዎች ታጣቂዎቹ የሚያደርሱት ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሏል " ያለው ፓርቲው፣ " ታጣቅዎቹ ንጹሐንን እና የጸጥታ አካላትን ይገድላሉ፣ የግልና የመንግስት ሀብት፣ ንብረት፤ የመንግስት ተቋማትን ይዘርፋሉ፤ ያወድማሉ " ሲልም ከሷል።

" ባለፈው ወር ቡለን ከተማ፣ ድባጢ ወረዳ በርበር ከተማ ሁለት ጊዜ ጥቃት ያደረሱ ሲሆን፣ በቡለን ከተማ በአንድ ሌሊት ብቻ የአረፋ በዓል በማክበር ላይ የነበሩ 11 የክልሉ ልዩ ኃይል አባላትን ከመግደል ባለፈ በርካታ ንጽሐንን፣ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የሃይማኖት አባቶችንና የጸጥታ አካላት ገድለዋል፤ ንጽሐንን አግተዋል " ብሏል።

ታጣቂዎቹን ተቋማትን " ዘርፈዋል፤ አውድመዋል " ሲል የከሰሰው ፓርቲው፣ " ሰሞኑን በወምበራ ወረዳ ወግዲና ሌሎች ቀበሌዎች ተመሳሳይ ጥቃቶችን ፈጽመዋል። ይህ ታጣቂ ቡድን በድባጢ ወረዳ ከ60% በላይ፣ በቡለን ወረዳ ከ30% በላይ ቀበሌዎችን በራሱ ቁጥጥር ስር በማደርግ ሰሞኑን ደግሞ በወንበራ ወረዳ በወግዲ ቀበሌ ግዛቱን ለማስፋፋት እየጣረ ይገኛል " ሲል ጠቁሟል።

ፓርቲው፣ " የሸኔ ታጣቂዎች በየወረዳዎቹ በሚኖሩ በሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ላይ ነው ጥቃት የሚያደርሱት " ብሎ፣ " በዚህ ምክንያት ነዋሪዎቹ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ይገኛሉ። በርካቶችም ተፈናቅለው ወደ አጎራባች ከተሞችና ወረዳዎች እየሄዱ ይገኛሉ " ብሏል።

" ታጣቂዎቹ በወረዳዎቹ ይህንን ሁሉ ጥቃት ሲፈጽሙና ወረዳዎች ‘ካቅማችን በላይ ነው’ እያሉ ለክልሉ መንግስት ሲያሳውቁ የክልሉ መንግስት ግን ለምን በቂ ትኩረት መስጠት እንዳልፈለገና ህዝቡን መከላከል ለምን እንዳልቻለ ለእኛ እንቆቅልሽ ሆኗል " ነው ያለው።

ፓርቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ " ህዝቡም በተደጋጋሚ ለክልሉ መንግስት የይድረሱልኝ ጥሪ ቢያቀርብም ሰሚ አላገኘም። በወረዳዎች በቂ የጸጥታ ኃይል የለም። ጥቂት የጸጥታ ኃይሎችም ታጣቅዎቹ ጥቃት ካደረሱና ዝርፊያ ከፈጸሙ በኋላ ይመጡና ወዲያውኑ ወይንም በነጋታው ይመለሳሉ " ሲል ነው የገለጸው።

" ህዝቡ ከፍተኛ ስጋት ላይ ይገኛል። ከሁሉም በላይ ይህ ሁሉ ጥቃትና በደል በህዝቡ ሲደርስ ክስተቱ በየትኛውም የመንግስት ሚዲያ አለመዘገቡና ሽፋን አለማግኘቱ ህዝቡን አሳዝኗል " በማለትም ወቅሷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#SafaricomEthiopia

⚡️ በዕለታዊ የዳታ ጥቅሎች ዘና ፈታ እንበል! 🥳

በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በፈጣን ዳታ እንንበሽበሽ!

#1wedefit
#Furtheraheadtogether

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#Axum

የአክሱም ከተማ ፖሊስ በከተማው ክንደያ በተባለ ቀበሌ ሁለት ተጠርጣሪዎች አደገኛ ኬሚካል በመጠቀም የወርቅ ማጣራት ተግባር ሲያከናውኑ በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው አሳውቋል።

ፖሊስ ከህብረተሰብ በደረሰው ጥቆማ የፍ/ቤት የፍተሻ ትእዛዝ በመያዝ የተለያዩ የፍትህ አካላት ፣ የአገር ሽማግሌዎችና የጤና ባለሙያዎች በማሳተፍ ነው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ያዋላቸው፡፡

የከተማዋ አቃቤ ህግ የህበረተሰብ የጤና ጠንቅ የሆነውን አደገኛ ኬሚካል በመጠቀም ህገወጥ ተግባር ሲፈፅሙ የተገኙት ተጠርጣሪዎቹ በአጭር ጊዜ አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ከባለ ድርሻ አካላት በመሆን ይሰራል ብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

Photo credit - Tigrai Television

@tikvahethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-ETHIOPIA

#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የ2017 ዓ/ም የግብር ዘመን ግብር አወሳሰንና አሰባሰብ አሰራር ይፋ አድርጓል።

አዲሱ መመሪያ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመክፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው ግብር ከፋዮችን በሚመለከት።

እንዲሁም የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ያልተወጡ ግብር ከፋዮችን በተመለከተ መደረግ ስላለበት ዝርዝር ሃሳብ የያዘ ደብዳቤ በቢሮው የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ ተፈርሞ ለሁሉም ለግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ተልኳል።

ደብዳቤው "የተወሰኑ ግብር ከፋዬች በህጉ የተጣለባቸውን ግዴታ ለመወጣት የተሰማሩበትን የስራ ዘርፍ ባለው የተለየ ባህሪ ምክንያት መቸገራቸውን በተለያየ ጊዜ በመጥቀስ አቤቱታ ያቀረቡ" መሆኑን ገልጿል።

ይሁን እንጂ የግብር ሕጉ ለየትኛውም የንግድ ዘርፍ በተለየ መልኩ የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ቀሪ አለማድረጉንም አሳውቋል።

ይህንኑ ግዴታ አለመወጣትም አስተዳደራዊ ቅጣት የሚያስከትል መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የተለየ ባህሪ ያላቸው የተወሰኑ የሥራ ዘርፎች የግብር ህጉን ድንጋጌዎች በአስከበረ አግባብ የገቢ አሰበሰቡን እና የአገልግሎት አሰጣቱን ፍታሀዊነት ማዕከል ያደረገ የአሰራር ሥርዓት ለ2017 የግብር ማሳወቂያ ጊዜ ሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታን ተፈጻሚነት በቅጣት ብቻ በማለፍ ማዘግየት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል ብሏል።

ስለሆነም የደረጃ "ሀ" እና የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዬች የሂሳብ መዝገብና የሂሳብ መግለጫ መሰረት በማድረግ የማሳወቅ፣ የመከፈል እና ሰነዶችን የመያዝ ግዴታን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ግብር ከፋዬች በማይወጡበት ጊዜ ለደረጃ «ሐ» ግብር ከፋዬች የወጣውን ገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 የትርፍ ሕዳግ እና በግምት ግብር አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 138/2010 በቁርጥ የወጪ ሰንጠረዥ መጠቀም ዘርፉ ግዴታውን በገቢ ግብር ሕጉ መሰረት እንዳይወጣ ከተማውም ማግኘት የሚገባውን ገቢ እንዳይሰበስብ ምክንያት ስለሚሆን ይህንኑ ክፍተት ለመዝጋት በገቢ ግብር አዋጁ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 80 መሰረት ግብር በግምት በሚሰላበት ጊዜ፦

ከግብር ከፋዮች ግንዛቤ የተለየ ድጋፍ የሚፈልጉ እና ሥራቸውም ከመንግስት ጋር በተገባ ውል ብቻ የሚያከናውኑ በማህበር የተደራጁ :-

- የትምህርት ቤቶችና የምገባ ማዕከላት መጋቢ እናቶች

- በከተማ ጽዳትና ውበት ደረቅ ቆሻሻ እና ገጸ-ምድር ማስዋብ ላይ የተሰማሩ

- ከንግድ ቢሮ ትስስር የተፈጠረላቸው የሸገር ዳቦን የሚሸጡ ማህበራት

ከመንግስት ተቋማት ጋር ያላቸውን ውልና በበጀት ዓመቱ ከአሰራቸው የመንግስት ተቋም ዓመቱን ሙሉ የተከፈላቸውን ክፍያ የሚገልጽ መረጃ ሲያመጡ መረጃን መሰረት አድርጎ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ገቢው ተወስኖ እንዲሰበሰብ።

በተጨማሪም የሸገር ዳቦን የሚሸጡ በተጓዳኝ የሚከናውኑ የንግድ ስራዎች መኖራቸው በመስክ ምልከታ ተረጋግጦ በየዘርፉ የቀን ገቢ ግምት እንዲገመትላቸው ተደርጎ ግብሩ ተወስኖ እንዲሰበሰብ።

የንግድ ሥራ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሞያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ጠበቆች ፣የኢንሹራንስ ወኪሎች ፣ኢንሹራንስ ጉዳት ገማች ግለሰቦች በሚመለከት:-

➡️ ከግብር አመቱ አጠቃላይ እንደ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።

➡️ የንግድ ሥራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች ከግብር አመቱ አጠቃላይ ገቢ 35 በመቶ እንደ ወጪ 65 በመቶ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ሆኖ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።

➡️ በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 ተሸከርካሪ የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ አጠቃላይ የኪራይ ገቢ ላይ በሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት በመረጃ የሚወሰን በመሆኑ ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ።

➡️ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ ተፈጻሚ የማይደረግባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭዎች /በቴክኖሎጂ ስምሪት የሚሰጣቸውን የሜትር ታከሲዎች ጨምሮ/ የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 ሠንጠረዥ "ሐ" መሠረት ግብሩን በማስላት ተወስኖ ገቢው እንዲሰበሰብ መወሰኑን ይገልጻል።

(ተጨማሪውን ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia

Читать полностью…
Subscribe to a channel