tikvahethmagazine | Unsorted

Telegram-канал tikvahethmagazine - TIKVAH-MAGAZINE

199913

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። #ኢትዮጵያ ያግኙን +251913134524

Subscribe to a channel

TIKVAH-MAGAZINE

#ፋይዳ

ስለ " ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጥያቄ አለዎት ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቤተሰብ አባላቱ ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር በተያያዘ በርካታ ጥያቄዎች ይደርሱታል።

በዚህም የሚነሱ ጥያቄዎችን በቀጥታ እንዲመልሱ የሚመለከታቸው አካላትን ለማግኘት ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል።

ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ምላሽ እሰጣለሁ በማለት ማረጋገጫ ልኳል።

ቤተሰቦቻችን በ "ፋይዳ" ዲጂታል መታወቂያ ላይ ያላችሁን ጥያቄ ከዛሬ ጀምሮ ባሉ ሁለት ተከታታይ ቀናት ውስጥ በ @tikvahmagbot ላይ መላክ ትችላላችሁ።

#TikvahEthiopia

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

በኡጋንዳ የተከሰተውና ሴቶችን ነጥሎ ስለሚያጠቃው በሽታ እስካሁን ምን ይታወቃል?

በ2023 ለመጀመሪያ ጊዜ እንደታየ የሚነገረውና በኡጋንዳዊያን ዘንድ በተለምዶ ‹Dinga Dinga› ማለትም የሚያንዘፈዝፍ/የሚያስደንስ በማለት የሚጠሩት በሽታ ሴቶችንና ህፃናትን እያጠቃ ይገኛል ተብሏል።

በሽታው እስካሁን በኡጋንዳ ቡንዲቡግዮ ወረዳ  300 የሚጠጉ ሰዎችን ያጠቃ ሲሆን ምንም አይነት ሞት ግን አልተመዘገበም።

የዲንጋ ዲንጋ ምልክቶች ምንድ ናቸው?

በዲንጋ ዲንጋ በሽታ የተያዙ ታካሚዎች የሚከተሉትን ምልክቶች ያሳያሉ፦

► የዳንስ እንቅስቃሴዎችን የሚመስል ከመጠን ያለፈ የሰውነት መንቀጥቀጥ/መንዘፍዘፍ፤

► ትኩሳት እና ከፍተኛ ድካም፤

► የመራመድ ወይም ሰውነት ያለመታዘዝ ችግር፤

የኡጋንዳ ሚዲያዎች እንደዘገቡት፣ አንዳንድ ሰዎች ሰውነታቸው ከቁጥጥር ውጭ በሆነ ሁኔታ ስለሚንቀጠቀጥ በእግር ለመራመድ በበሽታው ለተያዙት የማይቻል ነው ይላሉ።

ፔሸንስ ካቱሲሜ የተባለች ታካሚ በበሽታው ስትያዝ ያጋጠማትን  ለመገናኛ ብዙኃን ስትገልጽ፦

"ድካም ተሰማኝ እና ሰዉነቴ አልታዘዝ አለኝ፣ ለመራመድ ስሞክር ሰውነቴ ከቁጥጥር ውጪ በሆነ መልኩ ይንቀጠቀጣል፣ በጣም ይረብሸኝ ነበር።" ብላለች።

የጤና ባለሞያዎች ምን እያሉ ነው?

የወረዳው የጤና ኦፊሰር የሆኑት ዶ/ር ኪይታ ክርስቶፈር፥ የዲንጋ ዲንጋን መንስኤ ለማወቅ እየሞከሩ መሆኑን ገልጸው የታካሚዎች ናሙናም ወደ ኡጋንዳ ጤና ሚኒስቴር ለምርመራ ተልኳል ብለዋል።

ዶ/ር ክርስቶፈር፥ የበሽታው የማገገሚያ ፍጥነት ከፍተኛ መሆኑንና አብዛኞቹ ታካሚዎች ተገቢውን ህክምና በወሰዱ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ማገገም መቻላቸውን ተናግረዋል።

አክለውም በባህላዊ መንገድ የተቀመሙ መድኃኒቶችን ለዚህ የጤና ችግር ጠቃሚ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ምንም ዓይነት ሳይንሳዊ ማስረጃ ስለሌለ እንዳይወስዱ አስጠንቅቀዋል።

በሽታው በአንቲባዮቲክስ መድኃኒቶች ሊታከም ይችላል ሲሉም ያክላሉ።

በማኅበራዊ ሚዲያ የተለቀቁ ቪዲዮዎች በበርካቶች እይታ ቢያገኙም እስካሁን ድረስ የኡጋንዳ ጤና ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ በይፋ የሰጠው መግለጫ የለም።

ዲንጋ ዲጋን ምን ሊያስከትል ይችላል?

ዲንጋ ዲንጋ ትክክለኛ መንስኤ አሁንም እንቆቅልሽ ነው። ባለሙያዎች ከቫይረስ ኢንፌክሽን እስከ የአካባቢ ሁኔታዎች ድረስ የተለያዩ መላምቶችን ያስቀመጡ ሲሆን ነገር ግን እስካሁን የተረጋገጠ ነገር የለም።

አንዳንዶች ይህንን ክስተት በ1518 በፈረንሳይ ስትራስቡርግ ከተማ ሰዎች ባልታወቀ ምክንያት ለቀናት ከቁጥጥር ውጭ በሆነ መልኩ ያስጨፍር ከነበረው ታሪካዊው የዳንስ ቸነፈር ጋር እያመሳሰሉትም ይገኛሉ።

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

#Hawassa

በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ታቦር ክፍለ ከተማ አዲሱ ገበያ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በአንድ የገበያ ማዕከል ኮንቴነር ላይ የተነሳ የእሳት አደጋ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር መዋሉን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሠላምና ፀጥታ መምሪያ አስታዉቋል።

የእሳት አደጋዉ የተከሰተው ጠዋት 1:30 አከባቢ ታቦር ክፍለ ከተማ ፋራ ቀበሌ በተለምዶ አዲሱ ገበያ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በአንድ የንግድ ሼድ ሱቅ ነው።

በከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ነፃ የስልክ መስመር (7614) በደረሰ ጥቆማ የከተማ አስተዳደሩ እሳት አደጋ እንዲሁም የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ እስት አደጋ መኪኖች ከፀጥታ አካላትና ከአከባቢው ሕብረተሰብ ጋር በመሆን የእሳት አደጋውን በቁጥጥር ስር ማዋላቸው ተገልጿል።

"እንደ ወቅቱ ነፋሻማነትና ፀሐያማነት የእሳት አደጋዉን በቀላሉ መቆጣጠር አዳጋች ነበር"ያሉት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ቶርባ በከተማ አስተዳደሩ የተዘረጋዉ ፈጣን የመረጃ ልዉዉጥ አደጋውን ለመቆጣጠር አግዟል ነው ያሉት።

አደጋዉ የከፋ ጉዳት እንዳያደር ላደረጉ የአከባቢው ነዋሪዎች፣ፈጣን ምላሽ ለሰጡ የሀዋሳ ከተማ እና ሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የእሳት አደጋ ሰራተኞች እንዲሁም የፀጥታ አካላት የከተማ አስተዳደሩ ሠላምና ፀጥታ ምስጋና አቅርበዋል።

የእሳት አደጋው ትክክለኛ መንስኤ እየተጣራ ነዉ ያሉት መምሪያ ኃላፊው ወቅቱ በጋ በመሆኑ ፀሐያማና ነፋሻማዉ  የአየር ፀባይ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ስለሚታሰብ ሕብረተሰቡ ተገቢዉን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስበዋል።

#TikvahFamilyHawassa

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

#AddisAbaba

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 በሻሌ 72 አካባቢ በሚገኝ የግል ባንክ ውስጥ የሚሰራ የደንበኞች አገልግሎት ሰራተኛ ከደንበኞች አካውንት በመቀነስ ለግል ጥቅሙ አውሏል ተብሎ በቁጥጥር ስር ውሏል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ እንዳስታወቀው ግለሰቡ በቁጥጥር ስር እስከዋለበት ቀን ድረስ ከ5 የባንኩ ደንበኞች ከ2መቶ 78ሺህ ብር በላይ ወደ ግሉ አስተላልፏል።

ተከሳሹ ድርጊቱን መፈጸሙን ያመነ ሲሆን ከሂሳብ ወደ ሂሳብ እና በሞባይል ባንኪንግ በማስተላለፍ የወሰደ መሆኑም በምርመራ መረጋገጡን ፖሊስ አስታውቋል።

በተጨማሪም የኃላፊዎቹን አለመኖር በመጠቀም ለደንበኞች መልዕክት እንዳይደርስ ሲስተም ላይ የራሱን ስልክ ቁጥር በማስገባት በፈፀመው ወንጀል ክስ እንደተመሰረተበትም ተገልጿል። 

ተጠርጣሪው እንዴት በቁጥጥር ስር ዋለ?

የአንደኛ የግል ተበዳይ ለወላጅ አባታቸው በባንክ ቤቱ በአካል ቀርበው ገንዘብ አስተላልፈው ሊሄዱ ሲሉ ስልኮትን ይስጡኝ ሞባይል ባንኪንግ እንዲጠቀሙ ላስተካክል  በማለት ይቀበላቸዋል።

ለኃላፊው የግል ተበዳይ የስልክ ቁጥር መቀየራቸውን ዋሽቶ በመግለፅ አዲስ ስልክ ላይ መልዕክት እንዲደርሳቸው ጠይቀውኛል በማለት ኃላፊውን በማታለል የራሱን ስልክ አስገብቶ ያስተካክላል።

ከዚያም ከ35ሺህ ብር በላይ ወደ ግል ሂሳቡ ያስተላልፋል። የግል ተበዳይ ይህንን ጉዳይ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄደው በማመልከታቸው በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል። ተጠርጣሪው በዚህ መልኩ የሌሎች ተበዳዮችን ስልክ በመቀየር ወንጀሉን መፈጸሙን የፖሊስ መረጃ ያሳያል።

ፖሊስ በመልዕክቱ ህብረተሰቡ የባንክ ሂሳቡን ሲያንቀሳቅስ በስልኩ ላይ ምንም ዓይነት መልዕክት ካልደረሰው በአካል ወደ ባንኩ ቀርቦ ሊያመለክት እንደሚገባ አስተላልፏል። 

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

#EFDA: የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ባደረገው የድኅረ ገበያ ጥናት ያልተመዘገቡና የጥራት ደረጃ የማያሟሉ የጸረ-ወባ መድኃኒቶችን ዝርዝር አስታውቋል።

የመድኃኒት ዝርዝሮቹ ከላይ ተያይዘዋል።

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

"በሰቆጣ ቃልኪዳን እስካሁን መድረስ የቻልነው ሀገሪቱ ካሏት ወረዳዎች ከአንድ አራተኛ በታች ነው " - ዶ/ር ሲሳይ ሲናሞ

በኢትዮጵያ በተመጣጠነ ምግብ እጥረት ምክንያት በእድሜያቸው ሊደርሱበት የሚገባው ቁመት ላይ ያልደረሱ ወይም መቀንጨር ያጋጠማቸው ህጻናት ቁጥር 39 በመቶ ሲሆን 11 በመቶ ህጻናት ደግሞ መቀጨጭ እንዳጋጠማቸው ጥናቶች ያመላክታሉ።

ይህንን ሃገራዊ የህጻናት የመቀንጨር ምጣኔን ለመቀነስ እየተሰሩ ካሉ ስራዎች ውስጥ የሰቆጣ ቃልኪዳን አንዱ ነው።

ይህ ቃልኪዳን የህጻናትን የመቀንጨር ምጣኔ  መቀነስ ቢችልም እየተተገበረ የሚገኝባቸው ወረዳዎች ቁጥር ግን ሃገሪቱ ካሏት አጠቃላይ ወረዳዎች ሩቡን ያህል ብቻ መሆኑን በሰቆጣ ቃልኪዳን የፌደራል ፕሮግራም ማስፈጸሚያ ክፍል ሲኒየር ፕሮግራም ማናጀር የሆኑት ዶ/ር ሲሳይ ሲናሞ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የመቀንጨርን ምጣኔን በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ 2022 ዜሮ ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራበት ያለው የሰቆጣ ቃልኪዳን በአሁኑ ሰዓት በ 334 የኢትዮጵያ ወረዳዎች ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።

ቃልኪዳኑ የሁለተኛ ምዕራፍ የአምስት አመት የማስፋፊያ ትግበራ ላይ ነው።

ዶ/ር ሲሳይ "ሃገራዊ የመቀንጨር ምጣኔ መረጃው 39 በመቶ ነው። እንደ ሰቆጣ ቃልኪዳን በአርባ ወረዳዎች ጀምረን ገና ዘንድሮ ነው 334 ወረዳዎች መድረስ የቻልነው" ሲሉ ገልጸዋል።

ይህም በሀገሪቱ ካሉ ወረዳዎች አንድ አራተኛ በታች ነው የሚሉት ዶ/ር ሲሳይ፥ "የኢትዮጵያ ወረዳዎች ከ 1,100 በላይ ናቸው የሰቆጣ ቃልኪዳንን ተጽዕኖ ለማየት በጣም ብዙ ስራ መስራት አለብን" ብለዋል።

ለዚህም ተግባራዊ የሚሆንባቸውን አካባቢዎች ከፍ አድርገን በርካታ ወረዳዎችን ካልደረስን ይህንን ሀገራዊ ቁጥር በፍጥነት መቀነስ አንችልም፤ ነገር ግን በልዩነት ይሄ ሥራ በተሰራባቸው አካባቢዎች ተስፋ ሰጪ ውጤት አለ ሲሉ አክለዋል።

የሰቆጣ ቃልኪዳን ከ 7.8 ሚሊየን በላይ የሆኑ ህጻናትን እስከ 2022 ዓ/ም ድረስ ከመቀንጨር በመታደግ ሙሉ እድገታቸው ተመጣጣኝ እንዲሆን ለማድረግ በ 2007 ዓ/ም ቃል የተገባበት ስምምነት መሆኑ ይታወቃል።

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

Ethiopian Incorporated : Transforming the way Businesses Run in Africa የተሰኘ መፅሀፍ ከቀናት በፊት ተመርቋል።

መፅሀፉ በአይ ኢ ኔትዎርክስ መስራች እና ዋና ስራ-አስፈጻሚ አቶ መርዕድ በቀለ የተጻፈ ነው።

ደራሲዉ አቶ መርዕድ በጣት ከሚቆጠሩ አፍሪካዊያን መሃል አንዱ በመሆን በ24 ዓመቱ ፤ በጊዜዉ የነበረዉን ዉስን የኢንተርኔት አቅርቦት እና ስለ ኢንተርኔት የነበረዉን የተገደበ ግንዛቤ ሳይገድበዉ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ያደረገዉን CCIE ሰርተፊኬት ሊቀበል ችሏል፡፡ 

የ IE Network Solutions መስራች እና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆነዉ አቶ መርዕድ በቀለ፣ በአሁን ሰዓት ከ200 በላይ ለሆኑ ወጣቶች የስራ ዕድል የፈጠረ ካምፓኒ ባለቤት ነው።

ከቀናት በፊት ያስመረቁት መፅሀፍ ከዳበረ የስራ ፈጣሪነት እና የድርጅት አመራርነት በመነሳት የተጻፈ መሆኑ ተገልጿል።

መጽሀፉ በየትኛዉም የዕድሜ ክልል ላሉ ይስማማል የተባለ ሲሆን በተለይ ደግሞ የራሳቸዉን ድርጅት ለመፍጠር ህልም ኖሯቸዉ መንገዱን ማወቅ ለሚሹ ፣ በኢትዮጵያ ቢዝነስ በመስራትና ለማደግ ለሚሹ ፣ ለተለያዩ ድርጅት ባሌቤቶች እና ስራ ፈጣሪዎች እንዲሁም የኢትዮጵያን እና የአፍሪካን ገበያ አንድ እርምጃ ከፍ ማድረግ ለሚሹ የተጻፈ ነው ተብሏል።

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

ኢትዮጵያዊን ሥራ ፈጣሪዎች በየግሬት ሪፍት ቫሊ ኢኖቬሽን ሰሚት ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ ቀረበ።

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ የፈጠራ ሥራዎችን ለማጎልበት የግሬት ሪፍት ቫሊ ኢኖቬሽን ሰሚት ማዘጋጀቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ አስታውቋል።

ከጥር 23- 24 በስካይላይት ሆቴል በሚዘጋጀው በዚህ ዝግጅት በግብርና፣ በጤና እና በትምሕርት ዘርፍ የማኅበረሰብ ልማትን ለሚያፋጥኑ የላቁ የፈጠራ ውጤቶች  $750,000 የአሜሪካ ዶላር በሽልማት መልክ ይበረከታል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ትረስት ፈንድ ሊቀ-መንበርሉሊት እጅጉ "ይህ የፈጠራ ውድድር አሸናፊዎች በተዘጋጀላቸው በመቶ ሺዎች የአሜሪካ ዶላር የሚገመት ሽልማት ለሀገር ምሰሶ በሆኑ ዘርፎች ያሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት መላ እንዲፈጥሩና ችግር እንዲፈቱ ያስችላቸዋል" ብለዋል።

ሉሊት እጅጉ ግሬት ሪፍት ቫሊ ኢኖቬሽን ሰሚት/ጉባዔ ለፈጠራ ባለሙያዎች አስቸኳይ ጥሪ ያቀርባል ያሉ ሲሆን "ተስፋ ሰጪ የፈጠራ ሐሳብ ባለቤቶች ለውድድር እንድታመለክቱ፤ አጋሮች ድጋፍ እንድታደርጉ ጥሪ እናስተላልፋልን" ብለዋል።

አመልካቾቶ የተጀመሩ ምርቶች ወይም አገልግሎቶች፣ ወይም በትንሹ አዋጭነታቸው የታየ ደረጃ ላይ ቢሆን ይበረታታሉ ተብሏል። በተጨማሪም የሽያጭ ዝርዝር ስትራቴጂክ እቅድ ሊኖራቸው ይገባል ተብሏል።

ለማመልከት ስለ ቢዝነሱ 5-10 ስላይድ፤ ከ 10 ገጽ ያልበለጠ ዝርዝር የቢዝነስ እቅድ፣ የፋይናንሺያል ሞዴል እና ትክክለኛ የንግድ ፍቃድ ማዘጋጀት አለባቸው ተብሏል።

በግብር፣ በጤና እና በትምሕርት ዘርፎች ልዩ ፈጠራ ያላችሁ ኢንተርፕርነሮችና ሥራ ፈጣሪዎች፣ የስታርትአፕ አንቀሳቃሾች ይህን ዌብሊን https://www.grvsummit.com በመጠቀም የመወዳደሪያ ሐሳባችሁን እስከ እሁድ, ታኅሣሥ 9 2017 ዓ.ም. ድረስ እንድታስገቡ ይሁን።

በተጨማሪም ጉባዔው የፓነል ውይይቶች፣ ወርክሾፖች፣ ኤግዚቢሽን እና ከኢንዱስትሪ ባለድርሻዎች ጋር የትውውቅ መድረክ የተዘጋጁበት በመኾኑ ተሳታፊዎች ልምድ እንደሚቀስሙበትና ተጠቃሚ እንደሚኾኑበት ይሆናል ተብሏል።

ለበለጠ መረጃ info@grvsummit.com መልዕክት መላክ ይቻላል ተብሏል።

@TikvahethMagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

መኖሪያዎን በፍጥነት እና በጥራት እየገነባን እንገኛለን!

እርሶም በካሬ 99,000 ብር በ15% ቅድመ ክፍያ

📌ቦሌ ደንበል (ከ71 ካሬ ጀምሮ)

📌 ገርጂ መብራት ሀይል
(ከ 169 ካሬ ጀምሮ)

📌ብስራተ ገብርዔል ከሚገኙ አፓርትመንቶች መኖሪያዎን ይምረጡ !

📌 የንግድ ሱቆች ከ 20 ካሬ ጀምሮ በገርጂ ሳይት

📞 0931333432 ወይም 0909340800

ማን እንደ ቤት🏘
ፓልም ሪል እስቴት 🌴

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

ኮንሰፕት ሀብ (Concept Hub) የሐሳብ መድረክ ነው።

ዛሬ በይፋ እንድታነቡት የምንጋብዛችሁ "ሐሳብ አለኝ" የተሰኘው ዲጂታል መጽሔት እና በብሎግ አማራጭ የቀረቡት የጹሑፍ ሥራዎች ወጣቶች እድሉ ቢኖራቸው ለሚሰሩት ሥራ ጥቂቱ ማሳያ ነው።

ወጣቶች ተቀባይ ብቻ አይደሉም። ከሌሎች የሚማሩት ብዙ ነገር እንዳለ ሁሉ ሐሳባቸውን የሚገልጹበት፤ የሚሞክሩበትና ፈጠራቸውን የሚያጎለብቱበት መድረክም ያስፈልጋል።

ይህ መድረክም ወጣቶች ሐሳባቸውን እንዲያካፍሉ፤ ለማኅበረሰባቸው ጠቃሚ የሚሉትን ሐሳብ እንዲያዋጡ፤ አዲስ እይታና የፈጠራ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት ነው።

በተጨማሪም፥ ወጣቶችን እንዲጽፉ፤ ጥናትና ምርምር እንዲያደርጉ፤ የመፍትሔ ሐሳቦችን እንዲያፈላልጉና ለማኅበረሰብ ለውጥ እንዲሰሩ እድሉን መስጠትና ያስፈልጋል ይህ መድረክም ለዚህ የታሰበ ነው።

የተለያዩ ክህሎት ያላቸው ወጣቶች፤ ወጣት ባለሞያዎች፤ ወጣት መምህራንና ጸሐፊያን፤ ጋዜጠኞች፣ የጤና እና የኢኮኖሚ ባለሞያዎች፤ የሰብዓዊ መብትና የአከባቢ ጥበቃ ተሟጋቾች ሌሎች ብዙ ወጣት ሞያተኞችን አሉን ይህ መድረክ ማኅበረሰብ የሚጠቅም ሐሳባቸውን የሚያካፍሉበትም መድረክ ጭምር ነው።

ኮንሰፕት ሀብ ኢትዮጵያ (Concept Hub Ethiopia ) በቲክቫህ ኢትዮጵያ የተጀመረ ተነሳሽነት ሲሆን በዲጂታል መጽሔት ብቻም ሳይሆን በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በወጣቶች የሚደረጉ ውይይቶች፤ ዶክመንተሪዎች፤ የዲጂታል አጫጭር ሥልጠናዎች ወደፊት ይዞ ይመጣል።

🖥 www.concepthub.net

#TikvahFamily 🩵

@Concepthubeth

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

#Update

በሊባኖስ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉ እንዲሁም ከዚያ በፊት ወደ አገር ለመመለስ ጠይቀው የመውጫ ቪዛ ሲጠባበቁ የነበሩ 316 ዜጎች ወደ አገራቸው መመለሳቸውን በቤይሩት-ሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንጽላ ጀነራል ጽ/ቤት አስታውቋል።

ከተመለሱት ዜጎች ውስጥ 167 ዜጎች  በሊባኖስ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉና በሊባኖስ ከአለም አቀፉ የስደተኞች  ድርጅት(IOM) ጋር በመተባበር ረቡዕ ታህሳስ 2 ቀን ወደ አገር እንዲመለሱ የተደረጉ ሲሆኑ 17 እናቶችና 22 ህፃናት ይገኙበታል ተብሏል፡፡

በተለያዩ ምክንያቶች የመኖሪያና የሥራ ፈቃድ ሳይኖራቸው በሊባኖስ ረዥም ዓመታት ሲኖሩ የነበሩ ሰነድ አልባ ዜጎቻችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ባቀረቡት በጥያቄያቸው መሠረትት ደግሞ 149 የሚሆኑት ወደ ሀገር ቤት ተመልሰዋል።

@TikvahethMagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

ከደቡብ ሱዳን ተነስተዉ በሱርማ ወረዳ ከብት ለመዝረፍ የሞከሩ አርብቶአደሮች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

ከደቡብ ሱዳን መነሻቸዉን አድርገዉ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሚገኘዉ ምዕራብ ኦሞ ዞን ሱሪ ወረዳ የአርብቶ አደሮችን ከብቶችን ዘርፈዉ ለመሄድ የሞከሩ 46 የደቡብ ሱዳን አርብቶ አደሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን የሠላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ

የኢፌዲሪ የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ የፌዴራል ፖሊስ እና የክልልና የአካባቢዉ ፖሊስ በመቀናጀት በቁጥጥር ስር ማዋላቸዉን የክልሉ ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊው ገልጸዋል።

የተዘረፉ 250 ከብቶች እና 21 የተለያዩ ጦር መሳሪያዎች መያዛቸዉንና የተመለሱ ከብቶችም ለባለቤቶች የተሰጡ መሆኑን ተናግረዋል።

ዘራፊዎቹ አሁን ላይ በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደሚገኙ  አቶ አንድነት አሸናፊ ገልጸዋል።

መረጃው የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።

@TikvahethMagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

𝐍𝐞𝐰 𝐓𝐫𝐚𝐢𝐧𝐢𝐧𝐠 𝐏𝐫𝐨𝐠𝐫𝐚𝐦 𝐀𝐧𝐧𝐨𝐮𝐧𝐜𝐞𝐦𝐞𝐧𝐭 📣📣📣

"National Customs Procedure" Second Round Training

For More Information join our channel @EFFSAAtrainingcenter
and Registration,

📱 +251 903 182525
📞 +251 115 589045
📍 Kazanchis, Nigist Towers Hotel and Apartments, 4th floor (In front of Elilly Hotel)

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

#የሥራ_ማስታወቂያ

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ81 የሥራ መደቦች በዜሮ ዓመት የሥራ ልምድ ከ800 በላይ እንዲሁም የሥራ ልምድ በሚጠይቁ 41 የሥራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር እንደሚፈልግ አስታውቋል።

አመልካቾች ከታህሳስ 9 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ቅዳሜን ጨምሮ ባሉት 15(አስራ አምስት) ተከታታይ የሥራ ቀናት አስፈላጊ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃችሁን ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በመያዝ፦

📍 በአዲስ አበባ ከተማ ፒያሳ እናት ህንፃ አጠገብ በሚገኘው የተቋሙ ቢሮ፣

📍 በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት፣

እንዲሁም በሁሉም ክልሎች የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት በአካል ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ተቋሙ ገልጿል።

ስራ ልምድ ለሚጠይቁ የሥራ መደቦች አመልካቾች አግባብነት ያለው የሥራ ልምድ ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ዜሮ ዓመት ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ለሚጠይቁ ስራ መደቦች ላይ ደግሞ የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና (Exit Exam) ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

እንዲሁም የዩኒቨርስቲ መመረቂያ ውጤት ለወንድ 2.5 እና ለሴት 2.00 መሆን አለበት። የትምህርት ደረጃ /Level/ ለሚጠይቁ ስራ መደቦች የCOC ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባችኋልም ተብሏል።

ዜሮ ዓመት ለሚጠይቁ ስራ መደቦች ላይ የሚያመለክቱ ተወዳደሪዎች ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የተመረቁ መሆን አለባቸው የተባለ ሲሆን መስፈርቱን አሟልተው ለሚመረጡ ተወዳዳሪዎች ተቋሙ የሚሰጠውን ስልጠና ለመውሰድ ፍቃደኛ መሆንና ተቋሙ በሚመድብበት ቦታ ለመስራት ፈቃደኛ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ቋንቋ ክህሎት ያላቸው እንዲሁም መሠረታዊ የኮምፒዩተር ክህሎት (Basic computer skill) ያላቸው ተወዳዳሪዎች ይበረታታሉ ተብሏል።

❗️ተቋሙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ማስታወቂያውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ሊሰርዝው እንደሚችል ጠቁሟል።

ዝርዝሩን ይመልከቱ https://ics.gov.et/job/national-job-opening

#Share

@TikvahethMagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

𝐍𝐞𝐰 𝐓𝐫𝐚𝐢𝐧𝐢𝐧𝐠 𝐏𝐫𝐨𝐠𝐫𝐚𝐦 𝐀𝐧𝐧𝐨𝐮𝐧𝐜𝐞𝐦𝐞𝐧𝐭 📣📣📣

"National Customs Procedure" Second Round Training

For More Information join our channel @EFFSAAtrainingcenter
and Registration,

📱 +251 903 182525
📞 +251 115 589045
📍 Kazanchis, Nigist Towers Hotel and Apartments, 4th floor (In front of Elilly Hotel)

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

ስምንተኛውና የመጨረሻው የይዞታ ማረጋገጫ ሥራ በ337 ቀጠናዎች ላይ ተግባራዊ ይሆናል ተባለ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ይዞታ ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ በ2017 በጀት ዓመት ኤጀንሲው የመጨረሻ ያለውንና 8ኛውን የመሬት ይዞታ የማረጋገጥና የእወጃ መርሐግብር ሊጀመር መሆኑን ገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ዋና ዳሬክተር የሆኑት አቶ ግፋወሰን ደሲሳ በሰጡት መግለጫ ኤጀንሲው የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ከጀመረበት ከ 2007ዓ/ም እስከ 2016ዓ/ም በጀት ዓመት ድረስ በ 337 ቀጠናዎች ላይ የይዞታ ማረጋገጥ መርሐ ግብሮችን ማካሄዱን አስታውሰዋል።

በ2017 በጀት ዓመት 8 ኛውን ዙር የይዞታ ማረጋገጥ ስራ በ 136 ቀጠናዎች የሚገኙና ይዞታቸው ያልተረጋገጡ የከተማዋ ክፍት መሬቶች ምዝገባ በተመረጡ 6 ክፍለ ከተሞች እንደሚከናወን ነው የገለጹት።

የተመረጡት ክ/ከተሞች እና ወረዳዎች የትኞቹ ናቸው ?

1. የካ ክ/ከተማ በወረዳ 1,2,3,9,10,11,12 በ25 ቀጠናዎች፤

2. በለሚ ክ/ ከተማ በወረዳ 2,3,5,9,10,13 በ 44 ቀጠናዎች፤

3. በአቃቂ ክ/ከተማ ወረዳ 1,2,3,6,9,13 በ19 ቀጠናዎች፤

4. በንፋስ ስልክ ላፍቶ በ ወረዳ 6,7,10,11,14 የሚገኙ 22 ቀጠናዎች፤

5. በቦሌ ክ/ከተማ በወረዳ 3,12,13 በ15 ቀጠናዎች፤

6. በኮልፌ ቀራንዮ በወረዳ 3 በ11 ቀጠናዎች፤

ያልተረጋገጡ ይዞታዎችን የማረጋገጡ ስራ  በስልታዊ ዘዴ /በመደዳ/ የማረጋገጥ ሥራ የሚከናወን  ሲሆን ስራውም ከታህሳስ 10/04/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ አምስት ወራት ውስጥ እስከ ሚያዝያ 15 /2017 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን ሙሉ ወጪውም በመንግስት እንደሚሸፈን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም ከመሬት ይዞታዎች ጋር ተያይዞ ለመሬት ይዞታ ማረጋገጥ በተመረጡ ቀጠናዎችና ሰፈሮች ውስጥ ብቻ ስራው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ባለው 5 ወራት ውስጥ የመረጃ ልዩነት እንዳይፈጠር ሲባል ምንም አይነት የስነ ንብረት ዝውውር እንደሚቆም ተናግረዋል።

በመጨረሻም ኤጀንሲው አረጋግጦ ላልመዘገበው ይዞታ ምንም ዓይነት ህጋዊ ዋስትና እንደማይሰጥ የገለፀው የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ከ ታህሳስ 20/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 የስራ ቀናት በክ/ከተማ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት አስፈላጊውን መረጃ ይዘው የይዞታ ይረጋገጥልኝ ማመልከቻ እንዲያቀርቡ ጥሪ አስተላልፏል።

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

#UZDcars መኪናዎን ለመግዛት ከ መሸጫ መሸጫ መዞር ወይንም ደግሞ ከ ደላላ ደላለ መደወል አሰልቺ እንደሆነ ይገባናል፡፡ እሱንም በማሰብ ነው መጀመሪያ በቀላሉ ሳይለፉ መኪናዎን እነዲያገኙ ያሉንን መኪናዎች በሙሉ Online ያስቀመጥነው፡፡

ከምንም በላይ ደግሞ ሻጮችም መኪናቸው እነዲሸጥላቸው UZD cars ምርጫቸው ስላደረጉ በዛ ያለ የመኪና ስብስብ አለን፡፡

ያሉትን መኪናዎች ለማየት ከታች ያለውን Link ይጫኑ!

@usedcarsinethiopia

UZD cars‘ን ስለመረጡ እናመሰገናለን::

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

ከተዳከመው የንባብ ባህላችን ጀርባ ያሉ እውነታዎች

የሕትመት ግብአቶች ዋጋ መናር፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው እና በቅርቡ መጻሕፍት ላይ የተጣለው የተጨማሪ አሴት ታክስ ለመጻሕፍት ህትመት ዘርፉ ተደራራቢ ፈተናዎች ሆነውበታል።

"የንባብ ባህላችን ተዳከመ"፤ "እንባቢ ትውልድ የለም" ከሚሉት ወቀሳዎች ጀርባ መጽሐፍ ለማሳተም ያሉ ተግዳሮቶች፤ የአሳታሚዎች አለመኖርና መሰል ተግዳሮቶችን በዘርፉ ላይ ያሉ ባለሞያዎችን በማናገር አልታየህ ኪዳኔ በጥናት የደረጀ ጹሑፍ አቅርቦልናል።

በዚህ ጹሑፍ ደራሲ ሌሊሳ ግርማ፤ ጠበቃና የህግ አማካሪ ወንድሙ ኢብሳ፤ ደራሲ ህይወት እምሻው፤ ደራሲ እንዳለ ጌታ ከበደ (ዶ/ር)፤ የደራሲያን ማኅበር ፕሬዝዳንት አቶ አበረ አዳሙ፤ የተራኪ ዋና ስራ አስፈፃሚ ናሆም ፀጋዬ እና ሌሎችም ሐሳባቸውን ሰጥተውበታል።

በዚህ ጹሑፍ ከተነሱ ሀሳቦች መካከል፦

- ለመጀመሪያ ጊዜ የሚታተም አዲስ መጽሐፍ “ብዙ” ከተባለ እስከ 3ሺ ቅጂ ቢታተም ነው፡፡

- አንድ ደራሲ አንዱን መጻሕፍ በ400 ብር ዋጋ እንዲሸጥ ዋጋ ካወጣለት፤ ከዋጋው ላይ 40 በመቶውን የሚወስደው አከፋፋዩ ነው፡፡

- መጽሐፍት አከፋፋዮች ድርሻቸውን የሚያሰሉት ከትርፍ ላይ ስላልሆነ የማሳተሚያ ወጪ ተቀንሶ ደራሲው የሚገኘው ትርፍ በወፍ ከ60 እና 70 ብር አይበልጥም።

- ለዘመናት የደራስያን አበሳ ሆኖ የቀጠለው አሳታሚ የማጣት ችግር ነው፡፡

- ከዓመታት በፊት በተሰራ ጥናት ህጋዊ የወረቀት አስመጪዎች ቁጥር 2 ብቻ ነበሩ፤

- ደራሲያን ስራዎቻቸውን ለአድማጮች በትረካ መልክ ለማቅረብ ፍላጎት የላቸውም

ሙሉ ጹሑፉን ያንብቡት https://concepthub.net/article/5

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

ያገለገለም ሆነ አዲስ መኪና ስለመግዛት እያሰቡ ነው? UZD cars የ ዘረጋውን የ online መኪና መገበያያ platform በመጠቀም ራስዎን ከ መሸጫ መሸጫ ከ መዞር ይቆጥቡ። አላማችን ለገዚዎች ስለሚገዙት መኪና ሙሉ መረጃ በመስጥት፤ የ ባንክ ብድር በማመቻቸት እና እንደገዚ ዋጋ በመደራደር የ መኪና ግብይትን ቀላል እና ውጤታማ ማድረግ ነው።

ለ መኪና ባለንብረቶችም መኪናችሁን ለመሸጥ በቂ የሆነ የ መሸጥ ልምድ ያለን ስለሆነ የ uzd cars ቤተሰብ አባል በመሆን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ይሁኑ።

ከታች ያለውን Link በ መጫን ይቀላቀሉ።

/channel/usedcarsinethiopia

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

#EEU

° "የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኖች ከመስከረም ወር ጀምሮ ያለባቸውን የኋላ ክፍያ በታህሳስ ወር በሚወጣው ቢል ላይ ተጨምሮ የሚከፍሉ ይሆናል፡፡ " የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

ከ200 ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ የተጠቀሙ ደንበኖች የፍጆታ ሂሳብ ላይ እና አዲስ ደንበኛ ማገናኘትን ጨምሮ ደንበኞች በሚፈፅሟቸው ልዩ ልዩ የአገልግሎት ክፍያዎች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡

በዚህ መሠረት ደንበኞች ወርሃዊ የፍጆታ ሂሳብ በሚከፍሉበት ወቅት የፍጆታ መጠናቸው ከ200 ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ ከሆነ እላፊ የመጣው የፍጆታ መጠን የተጨማሪ እሴት ታክስ ተሰልቶ ሂሳባቸው ላይ የሚደመር ይሆናል፡፡

የተጨማሪ እሴት ታክስ ተግባራዊ የሚደረገው ከህዳር ወር የክፍያ ደረሰኝ ጀምሮ ሲሆን፤ የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኖች ከመስከረም ወር ጀምሮ ያለባቸውን የኋላ ክፍያ በታህሳስ ወር በሚወጣው ቢል ላይ ተጨምሮ የሚከፍሉ ይሆናል፡፡

ዓመታዊ የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያን በተመለከተ

ወርኃዊ የኤሌክትሪክ የፍጆታ መጠናቸው ከ50 ኪሎ ዋት ስዓት በላይ የሆኑ ደንበኞች 10 ብር ከወርሃዊ ኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ ጋር የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያ እየከፈሉ ይገኛሉ ብሏል።

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቲቪ) ዓመታዊ የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያ የመሰብሰብ መብት የተሰጠው ሲሆን ሁለቱ ተቋማት ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያ ስርዓትን በመጠቀም በየወሩ እንዲሰበሰብ ህዳር 2 ቀን 2015 ዓ.ም ስምምነት ማድረጋቸው ይታወሳል።

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

ድብቁ የወሲብ ገበያ: ቴሌግራም ያቀጣጠለው የወሲብ አብዮት

ቴሌግራም በሀገራችን ኢትዮጵያ ሰፊ ተጠቃሚዎች ካሉት መተግበሪያዎች አንዱ ነው። ቴሌግራም ጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎችን ከደንበኞች ጋር ለማገናኘት፣ ለትምህርትና ለመረጃ ልውውጥ አወንታዊ ሚናን ይጫወታል።

በአንጻሩ ደግሞ ላልተረጋገጡ መረጃዎችና የሤራ ትንተና፣ ማንነትን መሠረት ላደረጉ ጥቃቶች፣ ለህገወጥ ንግዶች፣ ለገንዘብ ማጭበርበርና ለመሳሰሉት ተጠቃሚዎችን ማጋለጡን የተለያዩ ሪፖርቶች ይጠቁማሉ።

ምንተስኖት ደስታ በሥነ-ሕብረተሰብ (ሶሲዮሎጂ) ከሐረማያ ዩንቨርስቲ የተመረቀ ሲሆን በአሁን ሰዓት በስንቅ ዩዝ ኢኒሼቲቭ ፕሮጀክት ማናጀር ሆኖ እየሰራ ይገኛል፡፡

በቴሌግራም ከሚታማባቸው ጉዳዮች አንዱ ስለሆነው ልቅ የወሲብ ገበያ ከኢትዮጵያ አንፃር የዳሰሰበትን ጹሑፍ በሐሳብ አለኝ ቅጽ 1 ዲጂታል መጽሔት ላይ አስነብቦናል።

ምንተስኖት በጹሑፉ በዚህ ላይ ከሚሳተፉ፤ ይኸው ተግባር ሱስ ከሆነባቸው ወጣቶችን ቃለመጠይቅ በማድረግና እና የተለያዩ ቻናሎችን በማጥናት ጥሩ ጹሑፍ አቅርቦልናል።

በዚህም፦

- ለዲጂታል ወሲብ አገልግሎቶች ከ500 - 3000 ብር እንደሚጠየቅ፤

- የህፃናት ወሲብ በሚያስደነግጥ ሁኔታ ተፈላጊ ስለመሆኑ፤

- ስለባህል ህክምናና ማስታወቂያዎቹ፤

- ከመንግስት እና ከቤተሰበሰ ስለሚጠበቀው ነገር በጹሑፉ አንስቷል።

አንብቡት 👉 https://concepthub.net/article/4

@tikvahethmagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

"በሰርግ መልሳችን ቀን ግን ይሆናል ብዬ አሰቤ አላዉቅም ነበር" - ዶክተር በየነ አበራ

በሰርጉ ማግስት የሙሽሪት ቤተሰቦች ከጠሩት የመልስ ፕሮግራም ላይ ላይ ተነስቶ በመሄድና የተሳካ ቀዶ ጥገና በማድረግ እናትና ልጅን የታደገዉ ዶክተር በብዙዎች ምስጋና ተችሮታል።

ይህ የሚያስመሰግን ተግባር የተፈጸመው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ የንግስት እሌኒ መሐመድ መታሰቢያ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነው።

በሆስፒታሉ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር በየነ አበራ በትላንትናው ዕለት በሰርጉ ማግስት የሙሽሪት ቤተሰቦች በጠሩት የመልስ ዝግጅት ላይ ነበር።

በዚህ ዝግጅት ላይ እንዳለ ነው እንግዲህ ከሚሰራበት ሆስፒታል የስልክ ጥሪ የደረሰው። የስልክ ጥሪውም እናትና ልጅን እንዲታደግ የቀረበ ነበር።

ዶክተር በየነ ስለሁኔታው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲናገሩ "መልስ በሀገራችን ባህልና ወግ ትልቅ ቦታ እሚሰጠዉ አዉቃለሁ በዕለቱ አማቾቼ አክብረው ጠርተዉን ፕሮግሙ እየተካሄደ ነበር ስልክ የተደወለልኝ" ሲል ያስረዳል።

"የመጀመሪያዉ ዙር አላነሳሁም! በድጋሚ ሲደወልልኝ አነሳሁት አንዲትን እናት ምጥ እንዳስቸገራትና ቀዶ ሕክምና የግድ እንደሚያስፈልጋት  ተነገረኝ፤ አላመነታሁም!" በማለት የመልስ ዝግጅቱን አቋርጦ ለመሄድ መወሰኑን ነግሮናል።

ይህንን ጉዳይ እንዴት ለሙሽሪት እንዳስረዱና እንዳሳመኗት ጠይቀናቸዋል፤ እሳቸው ሲመልሱም፦

"በፍቅር ሕይወታችን ወቅት የትዳር አጋሬን በተደጋጋሚ እንደዚህ አይነት አጋጣሚዎች ሊከሰቱ እንደሚችሉ በተደጋጋሚ እነግራት ነበር፤ በሰርግ መልሳችን ቀን ግን ይሆናል ብዬ አሰቤ አላዉቅም ነበር" ሲሉ ሁኔታውን ይግልጻሉ።

ከዚያም "ለሙሽራዋ ባለቤቴና ለሚዜዎቼ ነገርኳቸዉና ወደ ሆስፒታሉ አመራሁ። የሙሽራዋ ባለቤቴን ጨምሮ ጓደኞቼና ጓደኞቿ ለሙያው ያለኝ ፍቅርና ቁርጠኝነት ስለሚያዉቁ ሊጫኑኝ አልፈለጉም፤" ያሉት ዶክተር በየነ "ቤተሰቦቿን ግን ተመልሼ ይቅርታ ለመጠየቅ ወስኜ ነበር ወደ ሆስፒታል የሄድኩት" ይላሉ።

አክለውም "ወደ ሆስፒታሉ ስደርስ የቀደ ጥገና ቲሙ ዝግጁ ስለነበር አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርጌ ቀዶ ሕክምናውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀናል" ብለዋል።

ዶክተር በየነ አበራ የመጀመሪያ ዲግሪያቸዉን በሕክምና ከሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስፔሻሊቲ  መርሐግብራቸዉን ደግሞ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ሰርተዋል።

ዶክተር በየነ አበራ እናመሰግናለን 👏

#TikvahEthiopia

@TikvahethMagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

𝐍𝐞𝐰 𝐓𝐫𝐚𝐢𝐧𝐢𝐧𝐠 𝐏𝐫𝐨𝐠𝐫𝐚𝐦 𝐀𝐧𝐧𝐨𝐮𝐧𝐜𝐞𝐦𝐞𝐧𝐭 📣📣📣

"National Customs Procedure" Second Round Training

For More Information join our channel @EFFSAAtrainingcenter
and Registration,

📱 +251 903 182525
📞 +251 115 589045
📍 Kazanchis, Nigist Towers Hotel and Apartments, 4th floor (In front of Elilly Hotel)

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

#ተለቀቀ

"ሐሳብ አለኝ" ቅጽ 1 መጽሔት በዚህ Telegram Mini App ላይ ያገኙታል 👉 @ConceptHubeth_bot

ይጎብኙን www.concepthub.net

#TikvahFamily 🩵

@TikvahethMagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

#ሐሳብአለኝ

ሐሳብ አለኝ ዲጂታል መጽሔት ቅጽ 1 በነገው ዕለት ለአንባቢያን ይደርሳል፤ ይጠብቁን!

#አዳዲስድምጾች: የሐሳብ መሪነትና ሙያዊ ብቃት የሚንጸባረቅበት መድረክ

#EmergingVoice : A hub for thought leadership and professionalism

#TikvahFamily 🩵

@Concepthubeth

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

ቀጣዩ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የሊቀ-መንበር ማን ይሆናል ?

አፍሪካ ህብረት የሊቀ-መንበርነት ምርጫ በወርሀ የካቲት በ አዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህ ምርጫ በየአራት አመቱ የሚካሄድ ሲሆን፣ ተመራጩም የአፍሪካ ህብረት ህጋዊ ተወካይና ዋና የአፍሪካ ህብረት ዋና ሥራ አስፈፃሚ እንዲሁም ኮሚሽኑ የገንዘብ ነክ ጉዳይ የበላይ ሀላፊ ይሆናል።

በ2025 አ.ም በአዲስ አበባ በሚካሄደው 38ተኛው ጉባኤ አዲስ ሊቀ-መንበር ይመረጣል ተመራጩም ሊቀመንበር የአሁኑን የአፍሪካ ህብረት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሙሳ ፋኪ ማህማትን የሚተካ ይሆናል።

በዚህ የምርጫ ፉክክር የቀድሞው የኬንያ ጠቅላይ ሚንስትር ራይላ ኦዲንጋ ለዘንድሮም ምርጫ ከፍተኛ ግምት አግኝተዋል።

ራይላ የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ- ልማት ልዩ መልክተኛ ( special Envoy) ሆነው ከ 2018 እስከ 2024 አገልግለዋል።

ራይላ ለአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበነት ቦታ ከሌሎች ተወዳዳሪዎች ከፍተኛ ፉክክር ይገጥማቸዋል ተብሎ ይታሰባል።

ከዚህም መካከለሰ የ59 ዓመቱ የጅቡቲው የውጪ ጉዳይ ሚንስትር መሀሙድ አሊ የሱፍ ሌላው ለምርጫው ከፍተኛ ግምት የተሰጣቸው ናቸው።

የ55 ዓመቱ የ ቀድሞው  የማዳጋስካር ሪቻርድ ራንድሪያ ማናድራቶ የኢኮኖሚና የፋይናንስ ሚኒስቴር ለዋና ሥራ አስፈፃሚነት በምርጫው ይወዳደራሉ።

እነዚህ ተወዳዳሪዎች ዛሬ በአፍሪካ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ አፍሪካን በሚመለከት ያላቸውን እቅድ የፖሊሲ ጉዳዎች እና ቅድሚያ የሚሰጡዋቸው ሀሳቦች ላይ ክርክር ያካሂዳሉ።

የምርጫ ክርክሩ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴሌቪዥን እንዲሁም በሌሎች የኦላይን እና የቀጥታ ስርጭት አማራጮች ከምሽት 1 ሰዓት እስከ 3 ሰዓት ድረስ የሚተላለፍ ይሆናል።

#Mjadala
#TheAfricaWeWant
#AddisAbaba

@TikvahethMagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

#Update

° "ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የውጭ አገር ሰዎች ባልተፈቀደላቸው የሥራ መስክ ተሰማርተው ይገኛሉ"

° "ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ የአገራችንን ህግ ተላልፎ ከተገኘ በህግ ተጠያቂ ይሆናል" -
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ለእስርና እንግልት እየተዳረጉ ነው በሚል የተሰሩ ዘገባዎችን አስመልክቶ በትላንትናው ዕለት የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት "ሕጋዊ የስደተኝነት ዕውቅና ኖሯቸው ለእስርና እንግልት የተዳረጉ ስደተኞች በሀገሪቱ የሉም" የሚል መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በበኩሉ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ የህግ ጥሰት የፈፀሙ የውጭ ዜጎችን የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል።

በመግለጫውም ከጎረቤት አገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ዜጎች ለ9ዐ ቀናት ያለ ቪዛ ክፍያ በቀን ማህተም ገብተው እንዲቆዩ መፈቀዱን አስታውሷል።

ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የውጭ አገር ሰዎች የስራ ፈቃድና መኖሪያ ፈቃድ ሳይኖራቸው ባልተፈቀደላቸው የሥራ መስክና ህገወጥ የማዕድን፣ የገንዘብ፣ አደገኛ እፅ፣ የሰዎች ዝውውርና መሰል ህገወጥ ተግባራት ላይ ተሰማርተው ይገኛሉ ብሏል።

በተለይ በርካታ ኤርትራዊያን ወደ ሀገር የሚገቡት በህገወጥ መንገድ ነው ያለው መግለጫው ከተፈቀደላቸው የጊዜ ገደብ በላይ በመቆየት በህገ-ወጥ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ ሲል ከሷል።

በዚህም

- ለውጭ አገር ዜጎች ባልተፈቀዱ የስራ መስኮች በመሰማራት በህገወጥ መንገድ ከትንሸ ሱቅ ችርቻሮ እስከ ያልተፈቀዱ ትላልቅ ስራዎች ተሰማርተው ሳለ፤

- በርካታ የኤርትራዊ ዜግነት ያላቸው ዘመድ ለመጠየቅ በማስመስል ከዱባይ፣ ከኤርትራ፣ ከኡጋንዳ በመመላለስ የኮንትሮባንድ እና ሌሎች ህገወጥ ተግባራት ሲያከናውኑ፤

- በተለያዩ አገራት ከሚገኙ ሌሎች ህገ-ወጥ ደላሎች ጋር በመተሳሰር ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ሲሳተፉ፤

- ለተለያዩ ሕገወጥ ተግባራት የሚያገለገሉ ሐሰተኛና የተጭበረበሩ የጉዞና የይለፍ ሰነዶች፣ ማህተሞች፣ የባንክ ቡኮች በማዘጋጀትና በመጠቀም ህገ-ወጥ ተግባራት ሲፈጽሙ ተገኝተዋል ብሏል።

መግለጫው አክሎም ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ የአገራችንን ህግ ተላልፎ ከተገኘ በህግ ተጠያቂ ይሆናል። ይህ ግን በአንድ ሀገር ዜጋ ብቻ ተፈጻሚ የሚደርግ አሰራር ተደርጎ በአንድ አንድ ሚድያዎች መዘገቡ ስህተት ነው ብሏል።

በተጨማሪም በስደተኝነት የተመዘገበ ማንኛውም የኤርትራዊ ዜግነት ያለው ሰው ያለ ፈቃዱ ከአገር እንዲወጣ እና ተገቢነት የሌለው ክፍያ እንዲክፍል የተደርግ ሰው የለም ብሏል።

ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።

@TikvahethMagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

መኖሪያዎን በፍጥነት እና በጥራት እየገነባን እንገኛለን!

እርሶም በካሬ 99,000 ብር በ15% ቅድመ ክፍያ

📌ቦሌ ደንበል (ከ71 ካሬ ጀምሮ)

📌 ገርጂ መብራት ሀይል
(ከ 169 ካሬ ጀምሮ)

📌ብስራተ ገብርዔል ከሚገኙ አፓርትመንቶች መኖሪያዎን ይምረጡ !

📌 የንግድ ሱቆች ከ 20 ካሬ ጀምሮ በገርጂ ሳይት

📞 0931333432 ወይም 0909340800

ማን እንደ ቤት🏘
ፓልም ሪል እስቴት 🌴

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

#Update

° "ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ለእስርና እንግልት እየተዳረጉ ነው በሚል የሚሰራጨው መረጃ ትክክል አይደለም" - የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛው የሥደተኞች ኮሚሽን (UNHCR) በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ትግራይና አፋር ክልል በኩል ከኤርትራ የሚገቡ ስደተኞች ጥበቃ እና ከለላ ያስፈልጋቸዋል ሲል በሪፖርቱ ጠቅሶ እንደነበር ይታወሳል።

ቢቢሲ በሰራው ዘገባም በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞች መጠነ ሰፊ እስራት እየተፈጸመባቸው ፖሊስ የሚወስደው ርምጃ እየተጠናከረ መምጣቱን ዘግቦ ነበር።

ይህን ተከትሎም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በጉዳዩ ላይ ከደቂቃዎች በፊት መግለጫ አውጥቷል።

አገልግሎቱ በመግለጫው፥ የሚዲያዎቹን ዘገባ ተከትሎ አደረኩት ባለው ማጣራት፣ ሕጋዊ የስደተኝነት ዕውቅና ኖሯቸው ለእስርና እንግልት የተዳረጉ ስደተኞች በሀገሪቱ አለመኖራቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል።

በዚህም በሀገሪቱ የሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ላይ ያነጣጠረ የዘፈቀደ እስርና እንግልት እየተከናወነ ነው በሚል በሀገር ውስጥና በውጭ ሚዲያ አውታሮች የተሰሩ ዘገባዎችን ተቋሙ "መሠረተ ቢስ" ሲል አጣጥሎታል።

አክሎም፥ ስደተኞች የሀገሪቱን ሕግና ሥርዓት ጥሰው ለእስር የተዳረጉበት ሁኔታ የሚኖር ከሆነ፣ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የሚከታተለው ይሆናል ሲል አክሎ ገልጿል፡፡

በተጨማሪም የስደተኞች ምዝገባ ቆሟል በሚል ሚዲያው የሚያሰራጨው መረጃም ከእውነት የራቀ ነው ያለው አገልግሎቱ፥ "የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት የስደተኝነት መስፈርትን ለሚያሟሉ አካላት ምንም ልዩነት ሳያደርግ የምዝገባ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፤ እየሰጠም ይገኛል" ብሏል፡፡

የወሳኝ ኩነት ምዝገባና የምስክር ወረቀት አገልግሎትን ጨምሮ የስደተኝነት መታወቂያ የመስጠት ተግባር ከበፊቱ በተጠናከረና በተደራጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑንም ተቋሙ ገልጿል።

ኢትዮጵያ ከ26 ሀገራት ከለላና ጥበቃ ፈልገው ለመጡ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ከለላና ጥበቃ እየሰጠች ትገኛለች፡፡ ከነዚህ ውስጥ አብዛኛውን ቁጥር የሚይዙት ከጎረቤት ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ሱዳንና ኤርትራ የሚመጡ ስደተኞች ናቸው፡፡

#Ethiopia
#Eritrea
#Refugees

@TikvahethMagazine

Читать полностью…

TIKVAH-MAGAZINE

መኖሪያዎን በፍጥነት እና በጥራት እየገነባን እንገኛለን!

እርሶም በካሬ 99,000 ብር በ15% ቅድመ ክፍያ

📌ቦሌ ደንበል (ከ71 ካሬ ጀምሮ)

📌 ገርጂ መብራት ሀይል
(ከ 169 ካሬ ጀምሮ)

📌ብስራተ ገብርዔል ከሚገኙ አፓርትመንቶች መኖሪያዎን ይምረጡ !

📌 የንግድ ሱቆች ከ 20 ካሬ ጀምሮ በገርጂ ሳይት

📞 0931333432 ወይም 0909340800

ማን እንደ ቤት🏘
ፓልም ሪል እስቴት 🌴

Читать полностью…
Subscribe to a channel