#CAFAwards2024
የ 2024 የአፍሪካ የአመቱ ምርጥ ሽልማት ስነስርዓት ዛሬ ምሽት በሞሮኮ ማራካሽ “ Palais des Congrès " ይካሄዳል።
በስነ ስርዓቱ የሚጠበቁ ሽልማቶች የትኞቹ ናቸው ?
- የአመቱ ምርጥ ተጨዋች
- የአመቱ ምርጥ አሰልጣኝ
- የአመቱ ምርጥ ግብ ጠባቂ
- የአመቱ ምርጥ ብሔራዊ ቡድን
- የአመቱ ምርጥ ክለብ
የሽልማቱ የመጨረሻ እጩዎች እነማን ናቸዉ ?
የአመቱ ምርጥ ተጨዋች :-
⏩ አሽራፍ ሀኪሚ
⏩ ሴርሁ ጁራሲ
⏩ ሲሞን አዲንጋራ
⏩ አዴሞላ ሉክማን
⏩ ሮንዌን ዊልያምስ
የአመቱ ምርጥ ግብ ጠባቂ :-
⏩ አንድሬ ኦናና
⏩ ያህያ ፎፋና
⏩ ሮንዌን ዊልያምስ
የአመቱ ምርጥ አሰልጣኝ :-
⏩ ኤሜርስ ፋኢ
⏩ ሴባስቲያን ዴሳብሬ
⏩ ሁጎ ብሩስ
የሽልማት ስነስርዓቱ ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሞሮኮ መካሄዱን ይጀመራል።
እነማን ያሸንፋሉ ?
@tikvahethsport @kidusoyoftahe
ላሚን ያማል ጉዳት አጋጥሞታል !
የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና የፊት መስመር ተጨዋች ላሚን ያማል የቁርጭምጭሚት ጉዳት እንዳጋጠመው ክለቡ አስታውቋል።
ተጨዋቹ ትላንት ምሽት ባርሴሎና በሌጋኔስ በተሸነፈበት ጨዋታ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ መውጣቱ አይዘነጋም።
ይህንንም ተከትሎ ስፔናዊው ተጨዋች ላሚን ያማል በጉዳት ምክንያት ቢያንስ ለአንድ ወር ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ተገልጿል።
የዘንድሮው የጎልደን ቦይ ሽልማት አሸናፊው ላሚን ያማል በዘንድሮው የውድድር አመት ተደጋጋሚ ጉዳቶች እያጋጠሙት ይገኛሉ።
@tikvahethsport @kidusoyoftahe
ኪሊያን ምባፔ ወደ ልምምድ ተመልሷል !
በጉዳት ላይ የነበረው ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ወደ ልምምድ መመለሱ ተገልጿል።
ባጋጠመው ጉዳት ምክንያት የራዮ ቫዬካኖ ጨዋታ ያመለጠው ኪሊያን ምባፔ በዛሬው ዕለት በግሉ ልምምድ መስራቱ ተነግሯል።
ተጨዋቹ በቀጣይ ለፊፋ ኢንተርኮንቲኔንታል ካፕ ጨዋታ ከሪያል ማድሪድ ስብስብ ጋር ወደ ኳታር እንደሚያመራ በይፋ ተገልጿል።
ይሁን እንጂ ኪሊያን ምባፔ በፊፋ ኢንተርኮንቲኔንታል ካፕ ጨዋታ ላይ ይሳተፋል ተብሎ እንደማይጠበቅ ተጠቁሟል።
ሪያል ማድሪድ የፊታችን እሮብ ምሽት 2:00 ሰዓት ከሜክሲኮው ክለብ ፓቹካ ጋር የኢንተርኮንቲኔንታል ካፕ ፍፃሜ ጨዋታውን የሚያደርግ ይሆናል።
@tikvahethsport @kidusoyoftahe
#Wanaw_News
ዋናው የስፖርት ብራንድ ለከንቲባ አዳነች አቤቤ በሰጠው ልዩ ስጦታ የአዲስ አበባን የስፖርት ራዕይ አጉልቶ አሳይቷል።
“ጠንካራ የስፖርት ምክር ቤት አደረጃጀት ለሁለንተናዊ ብልፅግና!” በሚል መሪ ቃል በተካሄደው 15ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ስፖርት ምክር ቤት መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ዋናው የስፖርት ልብስ ተሳትፏል። በከንቲባ አዳነች አቤቤ የተመራው ጉባኤ ለከተማው ወጣቶች 1,314 የመጫወቻ ሜዳዎችና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በማዘጋጀት በ11 ወረዳዎች 128 የስፖርት ማሰልጠኛ መርሃ ግብሮችን በማዘጋጀት ጉልህ ክንዋኔዎችን አክብሯል።
ለእነዚህ ጥረቶች እና የበለፀገ የስፖርት ባህል ራዕይ በመገንዘብ ዋናው የስፖርት ብራንድ ለከንቲባ አዳነች አቤቤ ልዩ የአዲስ አበባን መንፈስ እና ማንነት የሚገልጽ ስጦታ አበርክቷል። ይህ ተግባር ዋናው የስፖርት ብራንድ የአካባቢን ስፖርት ልማት ለመደገፍ እና የህብረተሰቡን የአትሌቲክስ ተሳትፎ ለማጠናከር ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
አንድ ላይ፣ የበለጠ ንቁ እና አቅም ወዳለው ትውልድ
“ውድድር ባለበት ሁሉ ዋናው የስፖርት ብራንድ አለ”!
ማህበራዊ ገጾቻችን
Instagram|Facebook |TikTok |X|wanawsportswear?si=TSJ9HZINs4MzMPj2">Youtube
🌍በአፍሪካውያን የተመረት 🌍
ዋናው ወደፊት»»»Читать полностью…
አሸናፊዎች ተለይተዋል።
ትክክለኛ ምላሽ ቀድመው የሰጡት ከስር የተገለፁት የቤተሰባችን አባላት ናቸው።
ትክክለኛ ምላሽ የሰጡትን በመፈለጉ ሂደት የተዘለለ እና ያልታየ ካለ ማሳወቅ ይቻላል። Edit የተደረገ መልስ ተቀባይነት አይኖረውም።
ስጦታ የሚበረከትላቸው ቀድመው የመለሱ ሶስት አሸናፊዎች ብቻ ናቸው።
⏩ የማንችስተር ዩናይትድ እና ማንችስተር ሲቲ
1ኛ. @eliabte
2ኛ. @AGarnacho17
3ኛ. Tame dan
⏩ የቼልሲ እና ብሬንትፎርድ
1ኛ. @adugna25
2ኛ. @Dua_Lipa1223
3ኛ. @Miko_Ye_Michael
⏩ የባርሴሎና እና ሌጋኔስ
1ኛ. @Sa_aved
2ኛ. Faris kemal
3ኛ. Misael/cheru
🔴 አሸናፊዎች @Kidusyoftahe ስልክ ቁጥር በማስቀመጥ ሽልማታቸውን መውሰድ የሚችሉ ሲሆን ሽልማቱ በነገው ዕለት የሚደርሳቸው ይሆናል።
@tikvahethsport
" አሁንም ለዋንጫ ለመፎካከር ዝግጁ አይደለንም " ማሬስካ
የሰማያዊዎቹ ዋና አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬሳካ ቡድናቸው አሁንም የሊጉን ዋንጫ ለማሸነፍ ለመፎካከር ዝግጁ እንዳልሆነ ገልጸዋል።
የምሽቱ ጨዋታ አስቸጋሪ እንደነበር የገለፁት አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ትልቅ ድል ነበር ያሳካነው “ ማሸነፍ ይገባን ነበር " በማለት ተናግረዋል።
አሰልጣኙ አክለውም “ አሁንም ቼልሲ የፕርሚየር ሊጉን ዋንጫ ለማሸነፍ ዝግጁ ነው ብዬ አላስብም " በማለት ገልፀዋል።
ስድስተኛ ተከታታይ ድላቸውን ያሳኩት ሰማያዊዎቹ ከሊጉ መሪ ሊቨርፑል በሁለት ነጥቦች ዝቅ ብለው በ 3️⃣4️⃣ ነጥቦች ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ይቅናዎት!
ኦዶች ከመቼውም ጊዜ በላይ ከፍ ተደርገዋል።
ታዲያ ምን ይጠብቃሉ? ለማሸነፍ በተመቻቹ ኦዶች ይወራረዱ!
አሁኑኑ Betika.et ላይ ብቻ!
ቤቲካ የአሸናፊዎች ቤት!
ባርሴሎና ሽንፈት አስተናግዷል !
የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና የስፔን ላሊጋ የአስራ ስምንተኛ ሳምንት መርሐ ግብሩን ከሌጋኔስ ጋር አድርጎ 1ለ0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።
የሌጋኔስን የማሸነፊያ ግብ ሰርጂዮ ጎንዛሌዝ ከመረብ አሳርፏል።
ባርሴሎና በውድድር ዘመኑ አራተኛ የሊጉ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል።
በጨዋታው የባርሴሎናው የፊት መስመር ተጨዋች ላሚን ያማል ጉዳት አጋጥሞታል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
1️⃣ኛ ባርሴሎና :- 38 ነጥብ
1️⃣5️⃣ኛ ሌጋኔስ:- 18 ነጥብ
ቀጣይ ጨዋታቸው ምን ይመስላል ?
ቅዳሜ ⏩ ባርሴሎና ከ አትሌቲኮ ማድሪድ
እሁድ ⏩ ሌጋኔስ ከ ቪያሪያል
@tikvahethsport @kidusyoftahe
90 '
ቼልሲ 2-1 ብሬንትፎርድ
⚽ ኩኩሬላ ⚽ ምቤሞ
⚽ ጃክሰን
ሳውዝሀምፕተን 0-5 ቶተንሀም
⚽⚽ ማዲሰን
⚽ ሰን
⚽ ኩሉሴቭስኪ
⚽ ሳር
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
47 '
ቼልሲ 1-0 ብሬንትፎርድ
⚽ ኩኩሬላ
ሳውዝሀምፕተን 0-5 ቶተንሀም
⚽⚽ ማዲሰን
⚽ ሰን
⚽ ኩሉሴቭስኪ
⚽ ሳር
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
43'
ቼልሲ 1-0 ብሬንትፎርድ
⚽ ኩኩሬላ
ሳውዝሀምፕተን 0-4 ቶተንሀም
⚽ ማዲሰን
⚽ ሰን
⚽ ኩሉሴቭስኪ
⚽ ሳር
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
37 '
ሳውዝሀምፕተን 0-4 ቶተንሀም
⚽ ማዲሰን
⚽ ሰን
⚽ ኩሉሴቭስኪ
⚽ ሳር
ቼልሲ 0-0 ብሬንትፎርድ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
" እንደ 15ዓመት በታች ልጆች ነው የተጫወትነው " በርናርዶ ሲልቫ
የማንችስተር ሲቲው ተጨዋች በርናርዶ ሲልቫ ቡድናቸው በመጨረሻ ደቂቃዎች እንደ ታዳጊ ቡድኑ ደረጃ መጫወቱን ገልጿል።
" በመጨረሻ ደቂቃ የተጫወትነው እንደ 15ዓመት በታች ተጨዋች ነው " ያለው ሲልቫ ዋጋም አስከፍሎናል የተፈጠረው ነገር ይገባናል በማለት ተናግሯል።
ቡድኑ ራሱን መመልከት አለበት ሲል የተደመጠው ተጨዋቹ የማንችስተር ሲቲ ደረጃ ላይ አይደለንም ብሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
“ ድሉ የሚገባን ነው “ ሩበን አሞሪም
የማንችስተር ዩናይትዱ ዋና አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የምሽቱ ድል የሚገባቸው መሆኑን ከጨዋታው በኋላ ተናግረዋል።
ቡድናቸው አሁንም መሻሻል እንደሚገባው የገለፁት አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም “ ነገርግን ለደጋፊው ትልቅ ድል ነው “ ሲሉ ቡድናቸው ጥሩ መስራቱን ጠቁመዋል።
በጨዋታው ልዩነት ፈጥረናል የሚሉት አሰልጣኙ “ የተመዘገበው ድል ይገባናል “ ሲሉ ከጨዋታው በኋላ በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የስፔን እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ሾመ !
የስፔን እግርኳስ ፌዴሬሽን በዛሬው ዕለት ራፋኤል ሎዛንን የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አድርጎ መሾሙ በይፋ ተገልጿል።
የ 2030 አለም ዋንጫ ውድድርን በጣምራ እንድታዘጋጅ ከቀናት በፊት በይፋ የተመረጠችው ስፔን አዲስ የእግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አግኝታለች።
ራፋኤል ሎዛን ብቸኛ ተቀናቃኛቸው የነበረውን ሳልቫዶር ጎማን በመርታት የፌዴሬሽኑን ፕሬዝዳንትነት ምርጫ ማሸነፍ ችለዋል።
የ 57ዓመቱ ፕሬዝዳንት ራፋኤል ሎዛን እ.ኤ.አ ከ 2019 ወዲህ በስፔን እግርኳስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ነበሩ።
@tikvahethsport @kidusoyoftahe
🔥 ይጋብዙ ፣ ይሸለሙ 🔥
👉🏽አሁንም መሸለማችንን እንደቀጠልን ነው 🎁💥
ከእናንተ የሚጠበቀው የሳፋሪኮም መስመራችሁን በመጠቀም የተጠቀሱትን ቅደም ተከተሎች መተግበር ነው🫰🏽
ያስተውሉ 👉🏽 በእርስዎ ጋባዥነት የሚቀላቀለው ሰው ቁጥር ሲጨምር የሽልማቱም መጠን እየጨመረ ይሄዳል 😱 እንዲሁም ተጋባዦቻችሁ ገፁን ከተቀላቀሉ በኃላ “back” የሚለውን ተጭነው “check subscription” እንዲያደርጉ ያሳስቡ 💥
የቴሌግራም ቻናላችን 👉🏽 /channel/Safaricom_Ethiopia_PLC
የቴሌግራም ቦታችን👉🏽 /channel/official_safaricomet_bot
መልካም እድል 🎁
#MPESASafaricom #SafaricomEthiopia #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
ሀሪ ማጓየር ውሉን ለማራዘም ንግግር ላይ ነው !
እንግሊዛዊው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ሀሪ ማጓየር በአዲስ ኮንትራት ዙሪያ ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር ንግግር ላይ እንደሚገኝ አረጋግጧል።
ሀሪ ማጓየር በማንችስተር ዩናይትድ ቤት ያለው ለአንድ ተጨማሪ አመት የመቆየት አማራጭ ያካተተው ውል በውድድር አመቱ መጨረሻ ይጠናቀቃል።
ኮንትራቱ ሊጠናቀቅ የስድስት ወራት እድሜ የቀረው ሀሪ ማጓየር በማንችስተር ዩናይትድ ቤት ሳምንታዊ 190,000 ፓውንድ እንደሚከፈለው ይታወቃል።
“ ቀሪው የውድድር አመት እና ለተጨማሪ አመት የመቆየት አማራጭ አለኝ እየተደረገ ያለው ንግግርም በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል “ ሲል ሀሪ ማጓየር ተናግሯል።
@tikvahethsport @kidusoyoftahe
ቼልሲ ተጨዋቾቹ በቀጣይ ይመለሳሉ !
የሰማያዊዎቹ የፊት መስመር ተጨዋች ጇ ፊሊክስ ሐሙስ በሚደረገው የኮንፈረንስ ሊግ ጨዋታ ወደ ሜዳ እንደሚመለስ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ገልጸዋል።
ፖርቹጋላዊው የፊት መስመር ተጨዋች ጇ ፊሊክስ በጉዳት ምክንያት ያለፉት የቡድኑ ጨዋታዎች እንዳመለጡት ይታወሳል።
ቤልጂየማዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች በበኩሉ በሚቀጥለው የፕርሚየር ሊግ መርሐግብር ወደ ሜዳ እንደሚመለስ አሰልጣኙ አረጋግጠዋል።
ቼልሲ በቀጣይ ሐሙስ በኮንፈረንስ ሊግ ከሻምሮክ ሮቨርስ እንዲሁም እሁድ በሊጉ ከኤቨርተን ጋር ይጫወታሉ።
@tikvahethsport @kidusoyoftahe
ዲያጎ ሚሊቶ በፕሬዝዳንትነት ተመርጧል !
የቀድሞ የኢንተር ሚላን ተጨዋች ዲያጎ ሚሊቶ የአርጀንቲናው ክለብ ሬሲንግ ፕሬዝዳንት በመሆን ማሸነፉ ተገልጿል።
የ 45ዓመቱ ዲያጎ ሚሊቶ እስከ አውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ማሸነፍ የዘለቀው የእግርኳስ ህይወቱ የጀመረበትን የልጅነት ክለቡ ሬሲንግ በፕሬዝዳንትነት የሚመራ ይሆናል።
ዲያጎ ሚሊቶ የምርጫውን ስልሳ በመቶ ድምፅ ማሸነፉ የተገለፀ ሲሆን በቀጣይ አራት አመታት ክለቡን በፕሬዝዳንትነት የሚያገለግል ይሆናል።
“ ህልሜ እውን ሆኗል ለመሆን ሳልመው የነበረው ቦታ ላይ ሆኛለሁ “ ሲል ዲያጎ ሚሊቶ ከድሉ በኋላ ተናግሯል።
አርጀንቲናዊው የቀድሞ የፊት መስመር አጥቂ ዲያጎ ሚሊቶ በኢንተር ሚላን ቤት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ እና ሴርያ ዋንጫዎችን አሳክቷል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
-Mackbook Air M3 (2024)
16GM RAM
256GB SSD Storage
175,000 birr
Contact us :
0953964175 @heymobile
Facebook |Instagram |Telegram
@Heyonlinemarket
ሳውዝሀምፕተን አሰልጣኙን አሰናበተ !
ትላንት ምሽት በቶተንሀም በሰፊ የግብ ልዩነት የተሸነፈው ሳውዝሀምፕተን አሰልጣኝ ሩሴል ማርቲንን ከሀላፊነት ማሰናበቱ ይፋ ተደርጓል።
ክለቡ ካደረጋቸው አስራ ስድስት የሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው በአንዱ ሲሆን በአስራ ሶስቱ ተሸንፏል።
ሳውዝሀምፕተን አሁን ላይ በሊጉ በአምስት ነጥቦች የመጨረሻውን ደረጃ ይዘው ይገኛሉ።
ስኮትላንዳዊው አሰልጣኝ ሩሴል ማርቲን ከአሰልጣኝ ስቲቭ ኩፐር ፣ አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ እና ጋሪ ኦኔል በመቀጠል አራተኛው ተሰናባች የፕርሚየር ሊግ አሰልጣኝ ሆነዋል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ሰማያዊዎቹ ጣፋጭ ድል ተቀዳጅተዋል !
በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐግብር ቼልሲ ከብሬንትፎርድ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።
የሰማያዊዎቹን የድል ግቦች ኒኮላስ ጃክሰን እና ኩኩሬላ ከመረብ አሳርፈዋል።
ቼልሲ ማሸነፉን ተከትሎ ከፕርሚየር ሊጉ መሪ ሊቨርፑል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ #ሁለት ማጥበብ ችለዋል።
ኢንዞ ፈርናንዴዝ ባለፉት ሰባት ጨዋታዎች ሰባት የግብ ተሳትፎ ማድረግ ችሏል።
ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ የቼልሲው ተጨዋች ኩኩሬላ ቀይ ካርድ ተመልክቷል።
በሌላ ጨዋታ ቶተንሀም ከሳውዝሀምፕተን ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 5ለ0 በሆነ ሰፊ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
የቶተንሀምን የማሸነፊያ ግቦች ጄምስ ማዲሰን 2x ፣ ሰን ፣ ኩሉሴቭስኪ እና ፓፔ ሳር ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።
ሰን ሁንግ ሚን በፕርሚየር ሊጉ የቶተንሀም የምንግዜም ብዙ አመቻችቶ ማቀበል የቻለችው (68) ተጨዋች መሆን ችሏል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
2️⃣ ቼልሲ :- 34 ነጥብ
1️⃣0️⃣ ቶተንሀም :- 23 ነጥብ
ቀጣይ መርሐግብር ?
እሁድ - ቼልሲ ከ ኤቨርተን
እሁድ - ቶተንሀም ከ ሊቨርፑል
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
80 '
ቼልሲ 2-0 ብሬንትፎርድ
⚽ ኩኩሬላ
⚽ ጃክሰን
ሳውዝሀምፕተን 0-5 ቶተንሀም
⚽⚽ ማዲሰን
⚽ ሰን
⚽ ኩሉሴቭስኪ
⚽ ሳር
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
እረፍት
ቼልሲ 1-0 ብሬንትፎርድ
⚽ ኩኩሬላ
ሳውዝሀምፕተን 0-4 ቶተንሀም
⚽ ማዲሰን
⚽ ሰን
⚽ ኩሉሴቭስኪ
⚽ ሳር
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
" መፍትሔ መፈለግ አልቻልኩም " ጋርዲዮላ
የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ቡድናቸው የዚን ያህል የከፋ ችግር ውስጥ ይገባል ብለው ጠብቀው እንዳልነበረ ገልጸዋል።
“ በአመቱ መጀመሪያ አስቸጋሪ የውድድር አመት እንደሚሆን አውቅ ነበር “ ያሉት ጋርዲዮላ " የዚን ያህል ከባድ ይሆናል ብዬ ግን አላሰብኩም ነበር " ሲሉ ተናግረዋል።
" አሰልጣኝ እኔ ነኝ መፍትሔ የማፈላለግ ሀላፊነት የእኔ ነው ነገርግን ማግኘት አልቻልኩም እኔ በቂ አይደለሁም እውነታው ይሄ ነው።“ ጋርዲዮላ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
27 '
ሳውዝሀምፕተን 0-4 ቶተንሀም
⚽ ማዲሰን
⚽ ሰን
⚽ ኩሉሴቭስኪ
⚽ ሳር
ቼልሲ 0-0 ብሬንትፎርድ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
15 '
ሳውዝሀምፕተን 0-3 ቶተንሀም
⚽ ማዲሰን
⚽ ሰን
⚽ ኩሉሴቭስኪ
ቼልሲ 0-0 ብሬንትፎርድ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ይገምቱ ይሸለሙ
የባርሴሎና እና ሌጋኔስን ጨዋታ ውጤት ገምተው በትክክል ላወቁ ሶስት ቤተሰቦቻችን የአንድ መቶ ብር ካርድ የምንሸልምዎ ይሆናል።
የውድድሩ ህጎች ምን ይመስላሉ ?
√ ተሳታፊዎች ግምቶቻቸውን ከዚህ ፖስት ስር ባለው የሀሳብ መስጫ ሳጥን #ብቻ ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።
√ ኤዲት የተደረጉ ምላሾች በፍፁም ተቀባይነት አይኖራቸውም።
√ ግምትዎን መላክ የሚቻለው እስከ 5:00 ሰዓት ብቻ ነው።
🔴 ይነበብ
አንድ የቤተሰባችን አባል ግምት ማስቀመጥ የሚችለው #አንዴ ብቻ ነው። ከአንድ ጊዜ በላይ የመለሰ ቤተሰባችን ሽልማት አይደርሰውም።
መልካም ዕድል !
@tikvahethsport
ማንችስተር ዩናይትድ ድል አድርጓል !
ማንችስተር ዩናይትድ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ያደረገውን ተጠባቂ የፕርሚየር ሊግ መርሐግብር 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
የማንችስተር ዩናይትድን የማሸነፊያ ግቦች አማድ ዲያሎ እና ብሩኖ ፈርናንዴዝ ከመረብ ሲያሳርፉ ለማንችስተር ሲቲ ቫርዲዮል አስቆጥሯል።
ማንችስተር ዩናይትድ በዘንድሮው የውድድር አመት የተቆጠሩበት አርባ ሁለት በመቶ ግቦች ከቆመ ኳስ የተቆጠሩ መሆናቸው ተገልጿል።
አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ከአሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በኋላ የመጀመሪያ የማንችስተር ደርቢ ጨዋታቸውን ያሸነፉ የመጀመሪያው የማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሆነዋል።
ማንችስተር ሲቲ ካለፉት አስራ አንድ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው በአንዱ ብቻ ነው።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
5️⃣ ማንችስተር ሲቲ :- 27 ነጥብ
1️⃣2️⃣ማንችስተር ዩናይትድ :- 22 ነጥብ
ቀጣይ የሊጉ መርሐግብር ?
ቅዳሜ - አስቶን ቪላ ከ ማንችስተር ሲቲ
እሁድ - ማንችስተር ዩናይትድ ከ በርንማውዝ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe