#Infinix_HOT50_Pro+
አዲሱ የኢንፊኒክስ HOT 50 Pro+ ስልክ 7.8 ሚ.ሜ. ያህል ቀጭን ዲዛይን ይዞ የመጣ ሲሆን ይህም ስልኩን ለአያያዝ ምቹ ከማድረጉም በላይ እጅዎት ላይ እጅግ ያምራል፡፡
@Infinix_Et | @Infinixet
#Infinix #InfinixHOT50Pro+ #WOOOWNewHOT #InfinixHOT50Series
#EthiopianAviationUniversity
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ለ200 ጋቦናውያን ልዩ የአቪዬሽን ስልጠና የሚወስዱ ተማሪዎችን ተቀብሏል።
በተለያዩ የአቪዬሽን ዘርፎች ትምህርታቸውን ለሚከታተሉት ተማሪዎቹ በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል ተደርጓል።
@tikvahuniversity
#TVTI
በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ2017 ዓ.ም በደረጃ-6 (BSc) ትምህርታችሁን ለመከታተል የመግቢያ ፈተና የተፈተናችሁ መደበኛ ሰልጣኞች ምዝገባ ህዳር 3 እና 4/2017 ዓ.ም እንደሚካሔድ ኢኒስቲትዩቱ አሳውቋል።
@tikvahuniversity
#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ
🔔 የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ጀምሯል❗️
BSc fields of study:
→ Doctor of Medicine
→ Doctor of Dental Medicine
→ Bachelor of Dental Science
→ Nursing
TVET Programs:
→ Dental Therapy
→ Nursing
→ Medical Laboratory
→ Pharmacy
→ Radiography
★ የ CPD ማዕከል አገልግሎት!
☎️ 0913398780 / 0911596059
አድራሻ፦
CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ
Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege
#ጥቆማ #የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በ Trainee Cabin Crew, Senior Accountant I እንዲሁም በሌሎች የሙያ ዘርፎች አመልካቾችን አወዳድሮ ለመቅጠር ማስታወቂያ አውጥቷል።
ለ Trainee Cabin Crew ለማመልከት ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ (ዝቅተኛው) 200 ነጥብ ያስመዘገበ/ች መሆን አለባቸው።
አመልካቾች ዕድሜያቸው ከ19 እስከ 30 ዓመት፣ ቁመት ቢያንስ 1.58 ሜትር እና 212 ሴ.ሜ የሆነ ክንድ ለሴት እንዲሁም ለወንድ ቢያንስ 1.70 ሜትር ቁመት መሆን አለበት።
የምዝገባ ጊዜ፦
ከህዳር 8 እስከ 12/2017 ዓ.ም
ምዝገባው የሚከናወንባቸው ዩኒቨርሲቲዎች፦
- አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (አዳማ)
- አዲስ አበባ (በኦንላይን - ማመልከቻው ሲከፈት ይፋ ይደረጋል)
- አምቦ ዩኒቨርሲቲ (አምቦ)
- አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ (አርባ ምንጭ)
- አሶሳ ዩኒቨርሲቲ (አሶሳ)
- ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ባህር ዳር)
- ወሎ ዩኒቨርሲቲ (ደሴ)
- ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ (ድሬዳዋ)
- ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ( ጋምቤላ)
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ (ጎንደር)
- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ (ሀዋሳ)
- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ (ጅግጅጋ)
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ (ጅማ)
- መቐለ ዩኒቨርሲቲ (መቐለ)
- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ)
- መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ (ሮቤ)
- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ (ሰመራ)
- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ (ወልቂጤ)
ተጨማሪ መረጃዎች፣ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፣ ዝርዝር ጉዳዮች እንዲሁም ሌሎች የወጡ ማስታወቂያዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ድረ-ገጽ ላይ ሰፍሮ ይገኛል ይመልከቱ 👇
https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies
@tikvahethiopia
#WolaitaSodoUniversity
በ2017 ዓ.ም ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተከታትላችሁ ማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚካሔደው ህዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ8ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ።
በ2017 ዓ.ም ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ ጊዜ ወደፊት በሌላ ማስታወቂያ ጥሪ ይደረግላችኋል ተብሏል።
@tikvahuniversity
#Infinix_HOT50_Pro+
እጅግ ዘመናዊ ሆኖ በተሰራው አዲሱ የኢንፊኒክስ HOT 50 Pro+ ህይወትዎን ያዘምኑ! ይዞ በመጣቸው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ትምህርትዎን፣ ሥራዎን እና የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎትን ያቅሉ፡፡
@Infinix_Et | @Infinixet
#Infinix #InfinixHOT50Pro+ #WOOOWNewHOT #InfinixHOT50Series
#JigjigaUniversity
በ2017 ዓ.ም ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች መግቢያ እና ምዝገባ የሚካሔደው ከህዳር 7-9/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
የ2016 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም አዲስ ገቢ ተማሪዎች መግቢያ እና ምዝገባ የሚካሔደው ከታህሳስ 1-3/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- ከ8-12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
- ስምንት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- የሌሊት አልባሳት እና የስፖርት ትጥቅ።
(የዩኒቨርሲቲው መልዕክት ከላይ ተያይዟል።)
@tikvahuniversity
#BoranaUniversity
በ2016 ዓ.ም በቦረና ዩኒቨርሲቲ በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች፣ በ2016 ዓ.ም ትምህርት ጀምራችሁ በአንደኛ ሴሚሰቴር በውጤት እና በተለያዩ ምክንያቶች ዊዝድሮዋል በመሙላት ያቋረጣችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ ቦረና ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወነው ህዳር 12 እና 13/2017 ዓ.ም መሆነኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
ትምህርት የሚጀመረው ህዳር 17/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል፡፡
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ8ኛ ክፍል ሰርቲፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
- ስምንት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።
@tikvahuniversity
#አቢሲንያ_ባንክ
ቀጣይ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ቅዳሜ ጥቅምት 30 ከረፋዱ 4:30 በፌስቡክ ፔጃችን ላይ ይደረጋል፡፡ በየሳምንቱ አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ!
ዛሬውኑ የፌስቡክ ፔጃችን በመቀላቀል እና ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሸለሙ!
የፌስቡክ ሊንክ፡ https://www.facebook.com/BoAeth
አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!
#Facebook #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#AmboUniversity
በ2017 ዓ.ም አምቦ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ አንደኛ ዓመት ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ተማሪዎች የ2017 ዓ.ም ምዝገባ የሚከናወነው ህዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
የምዝገባ ቦታ፦
- የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ካምፓስ፣
- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ሃጫሉ ሁንዴሳ ካምፖስ አምቦ ከተማ።
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ8ኛ ክፍል ሰርቲፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
- አራት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።
በ2017 ዓ.ም አዲስ የተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም (Remedial) ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ወደፊት ጥሪ ይደረጋል ተብሏል።
@tikvahuniversity
#AksumUniversity
አክሱም ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም አዲስ የተመደባችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ መርሐግብር ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት ህዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና ማስረጃ፥
- የ2ኛ ደረጃ የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
- ስድስት 3X4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- የለሊት አልባሳት እና የስፖርት ትጥቅ።
የ2017 ዓ.ም አዲስ ለተመደባችሁ የሪሚዲያል ተማሪዎች ወደፊት ጥሪ እንደሚደረግ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
@tikvahuniversity
#RayaUniversity
ራያ ዩኒቨርሲቲ ለ2017 ዓ.ም አንደኛ ዓመት አዲስ ገቢ ተማሪዎች ለህዳር 2 እና 3/2017 ዓ.ም አድርጎት የነበረውን ጥሪ አራዝሟል።
@tikvahuniversity
#KotebeUniversityOfEducation
በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ውጤት ያመጣችሁና ለ2017 የትምህርት ዘመን ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት ህዳር 4 እና 5/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ስርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪብት ዋናውና ኮፒው፣
- የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
- ስድስት 3×4 ጉርድ ፎቶ ግራፍ፣
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡
@tikvahuniversity
ልዩ የትምህርት ድጋፍ ዕድል ከፋዌ ኢትዮጵያ
ፋዌ ኢትዮጵያ ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር እድሚያቸው ከ 15 እስክ 25 የሆኑ ወጣቶችን በተለይም በዝቅተኛ ኢኮኖሚያዊ ደረጃ የሚገኙ ሴት እና የአካል ጉዳተኛ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የከፍተኛ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ እንድትሆኑ ሲጋብዝ ታላቅ ደስታ ይሰማዋል፡፡
ዕድሉ ሁሉን አቀፍ የገንዘብ፣ የትምህርት እና ስልጠና እንዲሁም የማኅበራዊ ድጋፍን የሚያካትት ሲሆን፤ የትምህርት ድጋፉ የሚሰጠው በቴክኒክና ሙያ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ በሚሰጡ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና ተዛማጅ የትምህርት ዘርፎች (STEM) ኮርሶች ነው፡፡
ምዝገባው የሚካሔደው በአዲስ አበባ ጄኔራል ዊንጌት ፖሊቴክኒክ እና ተግባረ እድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች፣ በአዳማ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፣ በሀዋሳ ፖሊቴክኒክ እና በሀዋሳ ተግባረ እድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች እንዲሁም በባህር ዳር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በሚሰጡት መደበኛ የትምህርትና ስልጠና መርሐግብሮች ነው። አመልካቾች በ2014፣ 2015 ወይም 2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱ እና የ2017 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ መግቢያ ውጤት የሚያሟሉ መሆን አለባቸው፡፡
የማመልከቻ ቀናት ከጥቅምት 22-29/2017 ዓ.ም ባሉት የሥራ ቀናት ብቻ ይሆናል፡፡
ለበለጠ መረጃ፦
አዲስ አበባ 0911330024 / 0902662688
አዳማ 0911383055
ባህርዳር 0913042043
ሀዋሳ 0965679139
ድረ-ገፅ 👉 www.faweethiopia.org
ሴቶችን ማስተማር ህብረተሰብን ማስተማር ነው!
ምዝግባውም ሆነ የመረጣው ሒደተ ከማንኛውም ክፍያ ነጻ ነው።
#DillaUniversity
በ2016 ዓ.ም በሪሚዲያል ፕሮግራም ዲላ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በፍሬሽማን ፕሮግራም ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወነው ህዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣
- የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
- ስምንት 3X4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- የትራስ ጨርቅ፣ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።
በሌላ በኩል በዲላ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛው ፕሮግራም በ3ኛ ዲግሪ ለመማር አመልክታችሁ ተቀባይነት ያገኛችሁ እና በትምህርት ሚኒስቴር በመጀመሪያ እና 2ኛ ድግሪ ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የስኮላርሺፕ (Scholarship) ተማሪዎች ተቋሙ ባሉት ፕሮግራሞች ምዝገባ የሚካሔደው ህዳር 9 እና 10/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።
@tikvahuniversity
#ሜድስኬፕ_ጤና_ሳይንስና_ቢዝነስ_ኮሌጅ_እንጅባራ_ካምፓስ
✔️ ሙሉ ዕውቅና እና ፈቃድ ያለው ኮሌጃችን፤ ልምድ ባላቸው ስፔሻሊስት ሀኪሞችና የጤና ባለሙያዎች የተቋቋመ ኮሌጅ ነው።
ለ2017 የትምህርት ዘመን በሚከተሉት የትምህርት መስኮች በመደበኛ፣ በቅዳሜና እሁድ፣ በኤክስቴንሽን መርሐግብር ምዝገባ ጀምረና
በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በዲፕሎማ
➫ በፋርማሲ
➫ በነርሲንግ
➫ በማኔጅመንት
➫ በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ
➫ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት
➫ በኢኮኖሚክስ
➫ በኮምፒውተር ሳይንስ
➫ በእንሰሳት ጤና
➫ በአይሲቲ
በሪሚዲያል ፕሮግራም
➫ በ Natural Science
➫ በ Social Science
በኮሌጃችን ሲማሩ በነፃ የሚሰጡ ስልጠናዎች፦
✍️ Basic Computer Skills & Programming
✍️ የህይወት ክህሎት ስልጠና
✍️ Peachtree Accounting
አድራሻ፦
እንጅባራ ከተማ ዋናው አደባባይ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት
ስልክ ቁጥር፦
0995222294 / 0962791808 / 0921940650
መቐለ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 2,729 ተማሪዎች አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በቅድመ-ምረቃ እና በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
🎓 በሦስተኛ ዲግሪ - 22
🎓 በሁለተኛ ዲግሪ - 743
🎓 በስፔሻሊቲ - 19
🎓 በሰብ-ስፔሻሊቲ - 3
🎓 በመጀመሪያ ዲግሪ - 1,942
@tikvahuniversity
#DambiDolloUniversity
በ2017 ዓ.ም ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችዉ እና በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ወስዳቹ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚከናወነዉ ህዳር 11 እና 12/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- ከ8-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣
- አራት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ።
በ2017 ዓ.ም አዲስ ለተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ወደፊት ይገለፃል ተብሏል፡፡
@tikvahuniversity
4ኛ ዙር የጋዜጠኝነት ስልጠና ቅዳሜ ህዳር 7/2017 ዓ.ም ይጀምራል!
ልምድ ባላቸው ጋዜጠኞች በመሰልጠን ከፍተኛ ልምድ ለማግኝት ቀድመው ይመዝገቡ።
በስልጠናው የሚሰጡ፦
👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሆች
👉 የብሮድካስት ጋዜጠኝነት፣ የፕሬስ ጋዜጠኝነት እና የዲጂታል ሚዲያ ጋዜጠኝነት
👉 የመዝናኛ፣ የመደበኛ ፕሮግራም ዝግጅት እና ዶክመንተሪ ዝግጅት ተካተዋል።
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) አካቷል፡፡
ስልጠናው ለሦስት ወር የሚቆይ ሲሆን በማታ፣ በቅዳሜና እሑድ፣ በቀን እና በርቀት ይሰጣል።
☀️ በተመጣጣኝ ዋጋ፣ በምቹ ቦታ እና በዘርፉ ባሉ ብቁና የተመረጡ ጋዜጠኞች የሚሰጥ።
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: /channel/sagetraininginstitute
TikTok: sage_training_institute" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
#ጥቆማ
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በደረጃ ስድስት በቅዳሜና እሁድ እንዲሁም በማታ ፕሮግራም ለመሰልጠን ፍላጎት ያላችሁ እንድትመዘገቡ ተጋብዛችኋል።
የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ህዳር 5/2017 ዓ.ም
በኦንላይን ለመመዝገብ 👇 http://196.188.248.35
የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ቀን 👇
ህዳር 6/2017 ዓ.ም
የመግቢያ ፈተናውን ያለፉ አመልካቾች የምዝገባ ጊዜ 👉 ከህዳር 12-15/2017 ዓ.ም
(የኢንስቲትዩቱ መልዕክት ከላይ ተያይዟል።)
@tikvahuniversity
#ScholarshipOpportunity
ነፃ የትምህርት ዕድል!
ክቡር ኮሌጅ ከአጋር ተቋማት ጋር በመተባበር ለዚህ ዓመት በመደበኛው ፕሮግራም በመጀመሪያ ዲግሪ መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ውስን የትምህርት ዕድል (Scholarship Opportunity) አመቻችቷል፡፡
በዚህ ብቃትን መሰረት አድርጎ በተዘጋጀ የከፍተኛ ትምህርት ዕድል ለመሳተፍና ለመወዳደር ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማመልከት ትችላላችሁ።
ያመልክቱ 👉 Scholarship.kibur.edu.et
✍️ ክቡር ኮሌጅ ሊሸፍን ያዘጋጀው የገንዘብ መጠን ለአንድ ተማሪ 50,000 ብር ነው፡፡
✍️ ሴት አመልካቾች ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡
✍️ ለነፃ የትምህርት ዕድል ያለው ቦታ ለአስር (10) ተማሪዎች ነው፡፡
✍️ የተዘጋጀው በመደበኛ መርሐግብር መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ብቻ ነው።
✍️ ማመልከት የሚቻለው እስከ ህዳር 7/2017 ዓ.ም ድረስ ብቻ ነው፡፡
Scholarship.kibur.edu.et
ለበለጠ መረጃ፦
☎️ 0113698558 / 0904848586
#WoldiaUniversity
በ2016 ዓ.ም ወልድያ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ መርሐግብር የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች እንዲሁም በ2016 ዓ.ም አንደኛ ሴሚስቴር ያልተማራችሁ (ዊዝድሮዋል ሞልታችሁ የወጣችሁ) ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ህዳር 18 እና 19/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
በአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ለመከታተል የተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ጥር 19 እና 20/2017 ዓ.ም መሆኑን ተገልጿል፡፡
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
- ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
- አራት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
- የሌሊት አልባሳት እና የስፖርት ትጥቅ።
የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች መማር ማስተማር ህዳር 23/2017 ዓ.ም እንዲሁም የአቅም ማሻሻያ ተማሪዎች መማር ማስተማር ጥር 22/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡
@tikvahuniversity
ወደ ተመደብንባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ስንሔድ በM-PESA የሃገር ውስጥ በረራችንን ብናደርግ ፀዴ ቅናሽ እናገኛለን! 5% ቅናሽ ተገኝቶ ማን አይኑን ያሻል? እፍስስስ ነው እንጂ!
የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👇 /channel/Safaricom_Ethiopia_PLC
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን /channel/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#MPESASafaricom #FurtherAheadTogether
የፊታችን ሰኞ ህዳር 2/2017 ዓ.ም ከ 32ኛ እስከ 36ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኢዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ ይጀምራሉ።
👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 Advanced Graphics + Video Editing + Motion Graphics + Digital Marketing በአንድ ላይ
👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: /channel/sagetraininginstitute
TikTok: sage_training_institute" rel="nofollow">https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
#WallagaUniversity
በ2016 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የማለፍያ ውጤት አምጥታችሁ ለ2017 ዓ.ም ወለጋ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የቅድመ-ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ህዳር 4 እና 5/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
የምዝገባ ቦታ፦
ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ዋና ካምፓስ፣ ነቀምት
ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
- ከ8ኛ-12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውና ኮፒው
- ስምንት 3X4 ጉርድ ፎቶግራፍ
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ፡፡
መደበኛ የሪሚዲያል ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ወደፊት ይገለፃል ተብሏል፡፡
@tikvahuniversity
#Infinix_HOT50_Pro+
አዲሱ የኢንፊኒክስ HOT50 Pro+ ጥንቅቅ ብሎ የተሰራው ዲዛይኑ ከአያያዝ ምቹነት አልፎም ለዕይታ ማራኪ ከመሆኑ ባሻገር በሶስት የቀለም አማራጮች ቀርቧል፡፡
@Infinix_Et | @Infinixet
#Infinix #InfinixHOT50Pro+ #WOOOWNewHOT #InfinixHOT50Series
ጥራትን ከሚገርም ዋጋ ጋር ይዞ የመጣውን አዲሱን Kimem Itel Pro እናስተዋውቅዎ! በአቅራቢያችን ወደሚገኝ የሳፋሪኮም ሱቅ ጎራ ብለን የግላችን እናድርገው። በቅመም አይቴል ፕሮ እንንበሽበሽ!
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
#TVTI
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩቱ በደረጃ ስድስት ስልጠና ለመውሰው ለተመዘገቡ ሰልጣኞች የመግቢያ ፈተና ሰጥቷል፡፡
በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ከደረጃ ስድስት እስከ ስምንት ስልጠና እየሰጠ የሚገኘው ኢንስቲትዩቱ፤ ሀገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያሠለጠነ ይገኛል።
ኢንስቲትዩቱ በ2017 ዓ.ም ስልጠና ለመስጠት በ2015 እና 2016 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና የማለፊያ ውጤት ያመጡ እና በ2014 እና 2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተከታትለው ያጠናቀቁ ተማሪዎችን ተቀብሎ የመግቢያ ፈተና እንዲወስዱ አድርጓል።
@tikvahuniversity
#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ
🔔 የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ጀምሯል❗️
BSc fields of study:
→ Doctor of Medicine
→ Doctor of Dental Medicine
→ Bachelor of Dental Science
→ Nursing
TVET Programs:
→ Dental Therapy
→ Nursing
→ Medical Laboratory
→ Pharmacy
→ Radiography
★ የ CPD ማዕከል አገልግሎት!
☎️ 0913398780 / 0911596059
አድራሻ፦
CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ
Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege