Youtube https://youtu.be/_0l6c0I7ouM 👉ስለ ግቢው ወቅታዊ መረጃ 📌ዲፓርትመንቶች ፡⚽️ስፓርት፡🎤ኪነጥበብ ምሽቶች ፡📄የጊቢ ማስታወቂያ ፡ ምልከታወችና ታሪክ ወግ ፡📷📷አስገራሚ ፎቶወች ፡ እውነታዎች እና መረጃወች📃 መፀሀፍት ፡ ሳይኮሎጂ ሁሉም ይዳሰሱበታል:: Contact
ለሴት ተማሪዎች
"ከዚህ ቀደም ባዘጋጀነው የውይይት መድረክ ብዙ ሴት ተማሪዎች ደስተኛ እንደነበሩና በድጋሜ እንዲዘጋጅ በቀረበ ጥያቄ መሠረት አርብ በ23-09-2016 ሴቶቻችንን ያቀራርባል ያልነውን ውይይት አዘገጅተናል"
ዝግጅቱንም ብሎክ 07 ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ መታችሁ ተሳተፉ ሲል የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ዳይሮክትሬት ጥሪ አቅርቧል።
@dbu11
@dbu_entertainment
የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ በ Doctor of Medicine መምህራን አወዳድሮ ለመቅጠር ባለፈው ወር ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ መሠረት ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን አሟልታችሁ የተመዘገባችሁ ብቻ ግንቦት 22/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት በአስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ግቢ ለፈተና መጠራችሁን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡
ተፈታኞች ለፈተና ስትሔዱ መታወቂያ መያዝ እና በሰዓቱ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡ ማንኛውም ተፈታኝ የሞባይል ስልክ ይዞ ወደ ፈተና መግባት አይችልም፡፡
@dbu11
ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ለ5 የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንቶች ከባድ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የበጀት እና የፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የገንዘብ ሚንስቴርን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም በገመገመበት ወቅት
የ ወላይታሶዶ፣ጋምቤላ እና ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንቶች ከሃላፊነታቸው የተነሱ ሲሆን
ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣
አዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ፤
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
ጂንካ ዩኒቨርሲቲ እና ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በፌድራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የተቋማት ኦዲት ሪፖርት የ2014 በጀት ዓመት ተቀባይነት የሚያሳጣ አስተያየት ከተሰጣቸው 24 መስሪያ ቤቶች ውስጥ እርምጃ ከተወሰደባቸው ተቋማት ውስጥ ተካተዋል።
@DBU11
@DBU_ENTERTAIN
#Advertisment
እማዬ ሾርባ እና ስቲም ቡና
በልዩ አቀራረብ እና መስተንግዶ በአዲስ መልክ ተመልሰናል።
ሾርባ
ድንች ቅቅል
ቺፕስ(በካቻፕ)
እርጥብ/በአቮካዶ/ካቻፕ/በእንቁላል)
ቡና እና ሻይ
የለውዝ ሻይ
ቀሽር
እንዲሁም እንደምርጫዎ ቢያዙን እናስተናግዶታለን።
አድራሻ አልሚ ምግብ ቤት አጠገብ
0934892799
0980000091
ለማስታወስ ያህል
ሆሄ ተስፋ በአዲስ አበባ ለ4ኛ ዙር ያዘጋጀውን ልዩ ኪነጥበባዊ ዝግጅት ታደሙልኝ ይላል።
እሁድ 8:00
መገናኛ ዋአች ህንፃ
1ኛ ፎቅ - ጣዕም ባህላዊ የምግብ አዳራሽ
የመግቢያ ዋጋ በነፃ
@DBU11
@DBU_ENTERTAIN
ለደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የበጎ አድራጎት የተማሪዎች ቡድን በልዩ ፍላጎት ዘርፍ ለተማሪዎች እንኳን ደህና
መጣቹ (WELCOME) ፕሮግራም አዘጋጅቶ ኑ አብርን በጎ ስራዎችን እንስራ ይላል።
ይህ የእንኳን ደህና መጣቹ ፕሮግራም በዋናነት አይነ ስውራንን ለማገዝ ታስቦ የተዘጋጀ ፕሮግራም ሲሆን ይህ ታላቅ ፕሮግራም የሚዘጋጅው እሁድ ግንቦት 18 ከቀኑ 7:30 ጀምሮ በPR አዳራሽ ይካሄዳል።
በእለቱ በአይነስውራን ተማሪዎች የተዘጋጁ ተውኔትን ጨምሮ የተለያዩ ፕሮግራሞች ይቀርባሉ።
የደብረ ብርሃን ዩኒቭርሲቲ የበጎ አድራጎት የተማሪዎች ክበብ!
@DBU11
ህግ አስከባሪዎቹ አሸንፈዋል🔨🔨
ጂሲ ካፕ
ዛሬ በተደረገው የህግ ተማሪዎች እና የኢንድስትሪያል ኢንጅነሪንግ ተማሪዎች የማጣሪያ ጨዋታ በ 2-1 ውጤት በህግ ተማሪዎች አሸናፊነት ተጠናቋል።
የህግ ኮሌጅ በ3 ቢጫ ካርድ የተቀጣ ሲሆን የኢንድስትሪያል ኢንጅነሪንግ ምንም ካርድ ሳይታይበት ጨዋታውን ጨርሷል።
ጨዋታዎቹ ነገ ሲቀጥሉ
በኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ማኔጅመንት(COTM) እና በሲቪል ኢንጅነሪንግ መካከል የሚደረገው ጨዋታ ነገ አርብ 10:00 ጀምሮ ይካሄዳል።
@DBU11
@DBU_ENTERTAIN
ሆሄ ተስፋ- አዲስ አበባ
መሰረቱን ደብረብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ያደረገው ሆሄ ተስፋ የኪነጥበብ ቡድን 4ኛ የሆነውን የኪነጥበብ መድረክ እሁድ ግንቦት 18 አዲስ አበባ መገናኛ ዋአች ህንፃ 1ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው ጣዕም ባህላዊ የምግብ አዳራሽ ያቀርባል።
መገኘት የሚችሉ ቤተሰቦቹንና የኪነጥበብ አድናቂዎችን በዕለቱ እንዲገኙለት ግብዣውን አስተላልፏል።
ሆሄ ተስፋ የኪነጥበብ ቡድን
@DBU11
ትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና ድጋሚ ተፈታኞች የምዝገባ ጊዜን አሳወቀ።
በ2016 ዓ/ም ሰኔ ወር ላይ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና በድጋሚ ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ ተፈታኞች ምዝገባ የሚከናወነው ከግንቦት 14 እስከ 21/2016 መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
የምዝገባ ክፍያ 500.00 ብር በመክፈል በ https://exam.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።
የአገልግሎት ክፍያ 500.00 ብር በ ' ቴሌ ብር ' ብቻ የሚፈጸም መሆኑ አስገንዝቧል።
#ለመጀመሪያ_ጊዜ የመውጫ ፈተና የሚፈተኑ እጩ ተመራቂዎች ምዝገባ የሚካሄደው እና የአገልግሎት ክፍያ በተቋማቸው በኩል መሆኑን የገለጸው ሚኒስቴሩ አስፈላጊ የመፈተኛ መረጃዎችን በተቋማቸው በኩል እንደሚደርሳቸው አሳውቋል።
@DBU11
ሆሄ ተስፋ የኪነጥበብ ቡድን
ለሴሚስተሩ የመጀመሪያ የሆነውን የኪነጥበብ ፕሮግራም ቅዳሜ 10/9/2016 በደመቀ ሁኔታ አመሻሹን አቅርበዋል።
ግጥም፣ተውኔት፣ሙዚቃ እና የተለያዩ የመዝናኛ ዝግጅቶችን በወር 2 ጊዜ በቋሚነት የሚቀርብ ሲሆን በዘንድሮ ሴሚስተር በትምህርት ፕሮግራም መጣበብ እና በበዓል መደራረብ ምክኒያት ሊዘገይ ችሏል።
ከወትሮውም አቀራረብ ለየት ባለ መልኩ በኪነጥበቡ የሙዚቃ መሳሪያ ባለሞያዎች የተሰራ አዲስ የመሳሪያ ሙዚቃ(Instrumental Music) በዝግጅቱ ላይ ቀርቧል።
@dbu11
GC CUP
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የተመራቂ ተማሪዎች የኳስ ግጥሚያ ከነገ ቅዳሜ 10/09/2016 ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው ስቴዲየም ይካሄዳል።
ሁላችሁም በኳስ ግጥሚያ እና በመዝናኛ ዝግጅቱ ላይ እንድትገኙ ተጋብዛችኋል።
በነገው እለት የሚካሄደው ጨዋታም
Software Vs COTM
LAW VS ELECTRICAL
የእሁድ ጨዋታ
Chemical with Mechanical Vs Industrial with Food
"በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ2017 በጀት ዓመት አዳዲስ ፕሮጀክቶች አይኖሩም።" - መንግሥት
ይህ የተገለፀው የትምህርት ሚኒስቴር፣ የሚኒስቴሩ ሁለት ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የስምንት የምርምር እና የ14 የአፕላይድ ዩኒቨርስቲዎች የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድን በገንዘብ ሚኒስቴር በተገመገመበት ወቅት ነው፡፡
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በተቋማቱ በሚቀጥለው ዓመት ምንም አይነት አዳዲስ ፕሮጀክቶች እንደማይኖሩ ጠቅሰዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር እና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የበጀት ዕቅዳቸውን በተቀመጠላቸው የበጀት ጣሪያ መሠረት አስተካክለው በጥቂት ቀናት ውስጥ ለገንዘብ ሚኒስቴር እንዲያቀርቡ ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል፡፡
@dbu11
የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አመራረጥ አዲስ መመሪያ በመዘጋጀት ላይ እንደሚገኝ ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡
ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሃብት ብክነት እና ብልሹ አሰራር ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ለፋና ቴሌቪዥን የሰጡት ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እንደገለፁት፤ በትግራይ ክልል ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በስተቀር በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የሱፐርቪዥን ቡድን በመላክ ዩኒቨርሲቲዎቹ ያሉባቸውን ችግሮች መጠናቱን ገልፀዋል፡፡
"ዩኒቨርሲቲዎች የብዙ ደሃ ሕዝብ ሃብት የሚፈስባቸው ቦታዎች ናቸው" ያሉት ሚኒስትሩ፤ ስለዚህ ተቋማቱ በሙስናና ብልሹ አሰራር የተጨመላለቀ አስተዳደር ሊኖራቸው አይገባም ብለዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲዎች በዋናነት የተማረ የሰው ኃይል ከማምረት ይልቅ፣ ህንጻ ማምረት ላይ የተሰማሩ ተቋማት እንደነበሩ ያስታወሱት ሚኒስትሩ፤ "ዩኒቨርሲቲዎች የሚታለቡ የጥገት ላሞች ናቸው" የሚለው የአንዳንድ ግለሰቦች አባባል አሁን ላይ አይሠራም ብለዋል፡፡
ሦስት ጊዜ መጥፎ የኦዲት ግኝት ያለበት ዩኒቨርሲቲን የሚመሩ ከፍተኛ አመራሮች በሙሉ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ የሚያዝ የገንዘብ ሚኒስቴር መመሪያ መኖሩን ጠቁመዋል፡፡ ኃላፊዎቹም በህግ የሚጠየቁበት አግባብ መኖሩንም አክለዋል፡፡ ይህንን አሰራር በመከተል "ሦስት ጊዜ መጥፎ የኦዲት ግኝት ያለበት ዩኒቨርሲቲን የሚመሩ አመራሮችን በሙሉ እንቀይራለን" ሲሉ ተናግረዋል፡፡
@DBU11
የአስራት ወልደየስ የጤና ሳይንስ ካምፓስ የተማሪዎች ህብረት የቴሌግራም ቻናሉ ከቁጥጥሩ ውጪ መሆኑንና ከዚህ በኋላ በቀድሞው ቻናል ሊተላለፍ የሚችለው ይዘት እንደማይወክለው ገልፁአል።
የተማሪዎች ህብረት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናሉ /channel/Asrat_WHS መሆኑን አውቃችሁ በዩኒቨርሲቲው የምትገኙ የጤና ሳይንስ ተማሪዎች እና የሚመለከታችሁ አዲሱን ቻናል እንድትቀላቀሉ ጥሪ አቅርበዋል።
@DBU11
ለተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ
የምርቃት ጊዜ እንደመቃረቡ እና ጊዜውም አጭር እንደመሆኑ መጠን ለባይንደር እና ህትመት ስራዎች ብዛቱ መታወቅ ስላለበት እንዲሁም የማሰሪያ ገንዘቡ ገቢ መሆን ስላለበት የባይንደር እና የህትመት ፎርም ከዛሬ ሃሙስ ግንቦት 22/2016 ጀምሮ በክፍል ተወካዮች በኩል ለእያንዳንዱ ክፍል ስለሚሰራጭ እስከ ቅዳሜ ድረስ ክፍያውን እንድታጠናቅቁ ስንል እናሳስባለን።
የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተመራቂ ተማሪዎች(GC) ኮሚቴ
@DBU11
@DBU_ENTERTAIN
#ሆሄ_ተስፋ
አዲስ አበባ - መገናኛ በጣዕም የባህል ምግብ አዳራሽ ተዘጋጅቶ የነበረው የሆሄ ተስፋ የኪነጥበብ ቡድን ልዩ ኪነጥበባዊ ዝግጅት በሙዚቃ እና በስነፅሁፍ ጥበባዊ ዝግጅት ታጅቦ በድምቀት ተጠናቋል።
በዝግጅቱ ላይ የተለዩ እንግዶች የተገኙ ሲሆን
👉የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባህል ማዕከል ተጠሪዎች
👉የመቅረዝ ስነኪን ተጠሪዎች
እንዲሁም በዝግጅቱ ላይ የምንወደዳቸው እና የምናደንቃቸው ገጣሚያን
ገጣሚ ጥላሁን ስማው (የማስተዋል እያዩ "ከፋኝ" ሙዚቃ ግጥም ደራሲ)
ገጣሚት መንበረማርያም ኃይሉ(የቃል ሰሌዳ እና የጊዜ ሰሌዳ የግጥም መድብሎች አዘጋጅ)
የወደ ግጥም ኪነት ተጠሪዎች
እንዲሁም ሌሎች በዝግጅቱ ላይ ተገኝተዋል።
የባህላዊ ምግብ አዳራሽ ባለቤት የሆኑት አቶ ዮሃንስም እንደገለፁት ይህን ዝግጅት በቋሚነት በድርጅታችን በኩል እንዲካሄድ ስንፈቅድ ከልዩ ደስታ ጋር ሲሆን በወር አንድ ጊዜ ለሚደረገው ቋሚ የሆሄ ተስፋ መድረክ ሁሌም በራችን ክፍት ነው ሲሉ ገልፀዋል።
መገኛውን ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ያደረገው ክበብ በአዲስ አበባ መመስረቱ የተመረቁትን፣በዩኒቨርሲቲ ካሉት ጋር እንዲያገናኝ እንዲሁም አቅምና ክህሎትን በማጎልበት ትልቁን ህልም የሚያሳካ መንገድ እንደሆነ ተገልፁአል።
@DBU11
@DBU_entertain
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
-----------------------------
የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ በDocter of Medicine/MD/ መምህር በቅጥር አወዳድሮ ለመመደብ በቁጥር 0635/02-01/6 በቀን 08/08/2016 ዓ.ም ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ መሠረት ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን አሟልታችሁ ለተመዘገባችሁ ብቻ በቀን 22/09/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት በአስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ግቢ ለፈተና የተጠራችሁ መሆኑን እናሳውቃለን ፡፡
ማሳሰቢያ
-------------
* ለፈተና የሚመጣ ተወዳዳሪ ራሱን የሚገልጽ መታወቂያ ካልያዘ ፈተና ላይ አይቀርብም፡፡
* ማንኛውም ተወዳዳሪ የሞባይል ስልክ ይዞ መግባት አይችልም፡፡
* በሰዓቱ ያልተገኘ ተወዳዳሪ ወደ ፈተና መግባት አይችልም፡፡
ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ
አስራት ወልደየስ ጤናሳይንስ ካምፓስ
@DBU11
ለማስታወስ ያህል
ሆሄ ተስፋ በአዲስ አበባ ለ4ኛ ዙር ያዘጋጀውን ልዩ ኪነጥበባዊ ዝግጅት ታደሙልኝ ይላል።
እሁድ 8:00
መገናኛ ዋች ህንፃ
1ኛ ፎቅ - ጣዕም ባህላዊ የምግብ አዳራሽ
መግቢያ በነፃ
Use map https://maps.app.goo.gl/1x9HsYgRDesDKALi9
@DBU11
@DBU_ENTERTAIN
Civil Engineers እንኳን ደስ አላችሁ!
ትላንት አርብ 10 ሰዓት Construction technology management ከ Civil Engineering ጋር ባደረገው ጨዋታ
በ4-1 ውጤት ገንቢው ሲቪል ወደ ፍፃሜ ጨዋታ ተሸጋግሯል።
ሲቪል ኢንጅነሪንግ በ 1 ቢጫ ካርድ የተቀጣ ሲሆን በአንፃሩ ኮተም ዲፓርትመንት የ2 ቢጫ ካርድ ባለቤት ሆነው ተሸንፈዋል።
ነገ እሁድ የፍፃሜ ጨዋታው በሲቪል እና በህግ ተማሪዎች መካከል ይካሄዳል።
መልካም እድል!
@DBU11
@DBU_ENTERTAIN
የሃዘን መግለጫ
=========
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የ5ኛ ዓመት የአካውንቲንግና ፋይናንስ ትምህርት ክፍል የዕረፍት ቀናት ተማሪ የነበረው ኃይሉ የሽጥላ ማርሸት በአደረበት ህመም ምክንያት በ13/9/2016 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል፡፡
በመሆኑም የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በተማሪያችን ህይወት ማለፍ የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቹ፣ለጓደኞቹና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን እንመኛለን፡፡
የደ/ብ/ዩ/ማህበረሰብ
@DBU11
ጂሲ ካፕ
የመጀመሪያ ዙር ማጣሪያ ጨዋታ ተጠናቋል።
በመጀመሪያ የጨዋታ ቀን በተደረገው የቅዳሜ ጨዋታ ላይ COTM VS Software Engineering ጨዋታ COTM በ1-0 ውጤት COTM ወደ ቀጣይ ዙር ተሸጋግሯል።
Law VS Electrical Engineering በተደረገው ጨዋታ ደግሞ በ3-0 ውጤት Law ወደ ቀጣይ ዙር ሊያልፍ ችሏል።
በቀጣይ በተደረገው የእሁድ ጨዋታ
Chemical Engineering VS Industrial የነበረ ሲሆን
በ2-2 አቻ ውጤት የተለያዩ ሲሆን በፔናሊቲ ጎል 4-2 በመሆን Industrial Engineering ወደቀጣይ ዙር ተሸጋግሯል።
ከCivil Engineering ጋር ለሚደረገው ጨዋታ ምርጥ ተሸናፊ መለያ ኬሚካል ኢንጅነሪንግ ከሶፍትዌር ኢንጅነሪንግ ጋር ማክሰኞ ጨዋታ የተደረገ ሲሆን በ1-1 አቻ ውጤት የተለያዩ ሲሆን ኬሚካል ኢንጅነሪንግ በፔናሊቲ ጎል 3-2 ኬሚካል ኢንጅነሪንግ ከሲቪል ጋር ለመጫወት ውድድሩን አልፏል።
ዛሬ ረቡዕ በተደረገው ጨዋታ
ኬሚካል ኢንጅነሪንግ ከሲቪል ኢንጅነሪንግ ጋር በ8-1 ጎል ሲቪል ኢንጅነሪንግ ወደቀጣዩ የግማሽ ማጣሪያ ጨዋታ ሊያልፍ ችሏል።
#Notice
ለሴት ተማሪዎች
ሐሙስ በቀን 15-09-2016ዓ.ም የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ዳይሮክትሬት በብሎክ 07 ከቀኑ 9:00ሰዓት ጀምሮ ሴት ተማሪዎችን ለማቀራረብ የሚያግዝ ውይይት አዘጋጅቷል። በዝግጅቱ አዝናኝና አስተማሪ ፊልሞች እንዲሁም የካርድ ሽልማቶችን አዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል።
ቦታ፦ ብሎክ 07
ሰዓት፦ ከቀኑ 9:00
የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ዳይሮክትሬት
@dbu11
@dbu_entertainment
ታላቅ የኪነጥበብ ድግስ
ሆሄ ተስፋ ኪነጥበብ ቡድን በበዓልና በፈተና ምክንያት ሲያሸጋግር የቆየውን የኪነጥበብ ዝግጅቹን ለታዳሚዎች ለማቅረብ ዝግጅቴን ጨርሻለው ይላል።
በዝግጅቱ እንደተለመደው ፦
ግጥም
ሙዚቃ
መነባነብ
ሙዚቃዊ ግጥሞች እንዲሁም
የመፅሃፍ ጥቆማ ና የተለያዩ አዝናኝ ፕሮግራሞችን አዘገጅቶ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በዩኒቨርስቲው PR ተገኙልኝ ብሏል።
ሆሄ ተስፋ
@dbudaily
@dbu11
@dbu_entertainment
🌸እዮብ ቡቲክ
/Eyob New Brand Market🌸
💰 የሴቶች ልብስ በተመጣጣኝ ዋጋ👗👖👚👡
⚜️ቀሚስ ⚜ጃኬት
⚜ኮት ⚜ሸሚዝ
⚜ቶፕ ⚜ቱታ
⚜ሹራብ ⚜ጨርቅ እና ጅንስ ሱሪ
⚜️ የሚፈልጉትን ልብስ ይዘዙን እናስመጣለን።
⚜️ የሚፈልጉትን ልብስ ለመጠየቅ DM @eyoborder1
⚜️አድራሻ፦ ደብረብርሃን ,ማእከል(ምኒልክ አደባባይ) ባለው ቅያስ ገባ ብሎ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
Join Us On Telegram
@eyobmarket12
For Orders
@eyoborder1
☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️
☎️ 0913439338
🌸ጥራት ላላቸው ልብሶች ትክክለኛው ቦታ🌸
ለተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ
(ቪዲዮው ይታይ👆)
የምርቃት ጊዜ እየደረሰ እንደመሆኑ መጠን ከምንሰራቸው ጊዜ ከሚጠይቁ ስራዎች አንዱ የመፅሄት ህትመት ስራ ሲሆን ይህም ተማሪዎች አብረው ከኖሩት ከጓደኞቻቸው፣ከዲፓርትመንት እና አሶሴሽን፣እንዲሁም ከሚፈልጉት የተለያዩ ማስታወሻዎች ጋር ተሰንዶ የሚያዝ ማስታወሻ ስለሆነ
መፅሔቱን ማሰራት የምትፈልጉ በክፍል ተወካዮቻችሁ በኩል መልሳችሁን እንድታደርሱን መልዕክታችን ነው።
@DBU11
@DBU_ENTERTAIN
BEST DISCOUNT
TECNO AND INFINIX ORGIONAL CHARGER AND EARPHONE
BOTH FOR ONLY 5OO ETB
CALL +251940219376
@DBU11
@DBU_ENTERTAIN
የመውጫ ፈተና መቼ ይሰጣል?
የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከሰኔ 14 እስከ ሰኔ 21 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
ፈተናውን 250 ሺህ ተማሪዎች ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በሚኒስቴሩ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ኤባ ሚጀና እንዳሉት፥ የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ተማሪዎች ትምህርታቸውን አጠናቀው ሲወጡ ሊኖራቸው የሚገባውን እውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት ለመለካት የሚሰጥ ነው፡፡
የሚወጡ ጥያቄዎችም የየትምህርት ክፍሎች ምሩቃን እንዲኖራቸው የሚጠበቀውን እውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት መሠረት አድርገው የሚዘጋጁ ናቸው ብለዋል።
ሚኒስቴሩ ፈተናውን ለመስጠት አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁን ጠቅሰው፤ፈተናው ተዘጋጅቶ እንዲገመገም ተደርጓል ነው ያሉት።ከግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈተናውን የሚወስዱ ተማሪዎች ዝርዝር በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ተረጋግጦ ነው ወደ ሚኒስቴሩ የሚላከው ብለዋል፡፡
በፈተናው ሞባይል ይዞ የሚመጣና መታወቂያ ሳይዝ የሚመጣ ተማሪ ፈተናውን መውሰድ እንደማይችል ጠቅሰው፥ ተማሪዎች ይህን አውቀው ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባቸዋል ማለታቸውን ኢፕድ ዘግቧል።
@DBU11
የክርስቶስ ትንሳኤ በዓል በግቢያችን በዚህ መልኩ ተከብሮ ውሏል።
ለመላው ክርስቲያኖች በድጋሜ መልካም በዓልን DBUDAILY ይመኝላችኋል።
መልካም ፋሲካ!
Photo by:Yibe
@DBU11
@DBU_ENTERTAINMENT